Friday, June 6, 2025

 

፳ኛ ፊደል ("በግእዝ እልፍ ቤት በአበገደ ተራ ቍጥር ") "በፊደልነት ስሙ ርእስ በአኃዝነት ረ፪፻ ይባላል"
ንኡስ አገባብ "በመንገድኸ ላይ ብዙ ወንበዴ አለ፡ በል እንዴት መጣኸ ጕድ፡ ተው ይቅርብኸ" "የረን ጠባይ ያልተረዱ ሰዎች ግን እረ እያሉ ይጽፋሉ ረጋ ብለኸ ረግን እይ"
የመና/የነ ተወራራሽ "አጠራቀመ አጠናቀረ" ("ምንድን ምንድር ")
ረመመ/ረሚም/ረመ) አረመመ ዝም ጥርቅም አለ፡ ጨመተ፡ ከመናገር ተከለከለ። ሰይጣን ቢያረምም መንፈስ ቅዱስ ይመስላል። ረመረመን እይ፡ የዚህ ደጊም ነው።
ረመሰ (ረምሰ) ከውሃ ከጭቃ አገባ፡ ወሸቀ፡ ነከረ፡ ዘፈቀ፡ ዘፈዘፈ፡ አራሰ፡ አቀዘቀዘ። ተባ ብለኸ ኣተባን ተመልከት።
ረመሰ (ትግ) ጐዳ፡ እሰነፈ፡ አደከመ፡ ኣኰሰሰ።
ረመሰ (ዕብ፡ ራማስ፡ ረገጠ ።ራማሽ፣ ኼደ) ቀሰቀሰ፡ ነቀነቀ፡ ወዘወዘ።
ረመሰ ዐሸ፡ ለወሰ፡ አቦካ።
ረመሰ/ሩፋኤል
ረመረመ በእግር ጠቀጠቀ፡ ረገጠ፡ አበራየ፡ አኼደ። (ያይጥ ተረት) እኔን እኔን
ረመሽት በመራቤቴ ክፍል ያለ እ።
ረመደ እግሩ ምድር ነካ፡ ረገጠ ለመኼድ።
ረመደደ ረመጠጠ።
ረመዳን (ዐረ) ኅፅበተ ንስሓ።
ረመጠ (ረመፀ) ከረመጥ አገባ፡ ሸጐጠ፡ ቀበረ፡ ደፈነ፡ ጠበሰ።
ረመጠጠ (ትግ፡ ረምጠጠ፡ ቈነጠጠ) ረገጠ፡ ተነሣ፡ ደፈጠጠ። ረመደደን እይ።
ረማሽ የረመሰ፡ የሚረምስ፡ ወሻቂ፡ ዘፍዛፊ፡ አቡኪ፡ ለዋሽ።
ረማጭ/ረማፂ የረመጠ፡ የሚረምጥ። (ተረት) አማጭ ረማጭ።
ረምረም አለ ተሰማ ሰኰናው ረምታው።
ረምራሚ የረመረመ፡ የሚረመርም።
ረምታ (ረዐመ) የብዙ ሰልፈኛ እግር ድምፅ። ረምታ ከረመረመ ሲወጣ ይቻላል።
ረምድ (ትግ፡ ረምዲ) የሕፃን ዐይን በሽታ፡ ዐይንን የሚጨፍን የሚጫን፡ ከአባት ከናት ወደ ልጅ የሚራመድ።
ረምድ/ረመረመ
ረሞ በፀሓይ ሙቀት የጋለ አሸዋ ሲረግጡት እንደ ረመጥ የሚያቃጥል።
ረሰረሰ (ትግ፡ ረስረሰ፡ አርከፈከፈ ረበረበ ረጩ) ወረዛ ፈጽሞ ራሰ ሾቀ ጨቀየ ቀባ።
ረሳ አስገዳፈ
ረሣ ዘነጋ ረሳ።
ረሳ/ረስዐ ዘነጋ፡ ገደፈ፡ ዐጣ፡ አጠፋ፡ ተወ ጭንቁን የተማረውን ያየውን የሚያውቀውን። (ተረት) ምጡን ርሺው ልጁን አን
ረስራሳ የረሰረሰ የራሰ።
ረሸተ የእኸልን ዘር አበዛ።
ረሸነ/ረስነ (ጋለ። ዐረ፡ ረሸ፡ አርከፈከፈ ውሃን) በረሽ መታ ገደለ።
ረሺ፡ (ረሳዒ) የረሳ፡ የሚረሳ፡ ገዳፊ መርሳት፡ መዘንጋት መግደፍ፡ ማጣት፡
ረሽ ራሰ
ረሽ ግንጥል ጠመንዣ ጥይቱ የሚበተን የወፍ ማደኛ።
ረቀረቀ (ረከረከ። ትግ፡ ራዕርዐ) መላልሶ መታ፡ ደበደበ፡ በክርን ደቀደቀ። ዛሬ ሌሊት ዝናቡ ሲረቀርቀው ዐደረ መሬቱን ሲደበድበው ማለት ነው።
ረቀረቀ አብዝቶ ፎከረ።
ረቀቀ (ረቀ) ቀጠነ፡ ሣሣ፡ አነሰ፡ ደቀቀ፡ ከግዘፍ ራቀ። (ነገሩ ረቀቀ) ጥልቅ ኾነ።
ረቂቅ (ቆች) የረቀቀ፡ ቀጪን፡ ሥሥ፡ ላይን የማይታይ፡ ቢታይም የማይጨበጥ፡ ነፍስ፡ መልአክ፡ ነፋስ፡ ውሃ፡ እሳት፡ ብርሃን፡ ጨለማ፡ ጪስ፡ ጉም የመሰለው ኹሉ። (የረቂቅ ረቂቅ)
ረቂቅ መዠመሪያ የተጻፈ ማንኛውም ጽፈት፡ ከርሱ ለሚቀዳ ምስክር የሚኾን ቀሪ ደብዳቤ ወይም ሌላ።
ረቂቅ በጣም ያነሰ፡ ጥቃቅን ጽፈት፡ የድጓ ምልክት።
ረቂቅ የደቀቀ፡ የላመ፡ የለዘበ፡ ልም ልዝብ የመገበሪያ ዱቄት።
ረቂቅነት ረቂቅ መኾን።
ረቃቂ የሚረቅቅ።
ረቅራቂ የረቀረቀ፡ የሚረቀርቅ፡ መቺ ደብዳቢ።
ረበረበ (ረበበ) ("(ዘፀ. ፵፥ )") በተራ አስቀመጠ/ሰደረ/ደረደረ/ደረበ/አነባበረ "ፅንፊትን በፍም በእድሞ ጋድም ላይ ረበረበ"
ረበረበ አርከፈከፈ/ረጨ ውሃን
ረበበ (ረቢብ - ረበበ) ዘረጋ ረደ ("በላይ አደረገ የክንፍ የባለክንፍ (አድራጊ )")
ረበበ ረበከ
ረበበ ተዘረጋ/ተጋረደ/ሰፈረ/ዐደረ/መላ ("(ተደራጊ)") "ደጉን ሰው መንፈስ ቅዱስ ረቦበታል" እንዲል ባላገር ("(ኢሳ. ፷፩፥ ሉቃ. ፫፥ ፳፪ ፬፥ )")
ረበተ ፈራ/ታወከ "ረበደን አስተውል"
ረበከ ወዘፈ/ረፈጠ/ረፈቀ
ረበየ) አረባየ ረገጠ/ረመረመ/ ጠቀጠቀ ("በጤፍ ርሻ ላይ ከብትን ነዳ ")
ረበየ)"ከዐረየ የወጣ ነውና በረየን እይ"
ረበያ ሰጠ ረበደ የአረበደ ከፊል
ረበጠ (ዐረ) አሰረ/ቀፈደደ
ረቢ (ዐረ) "የኔ ጌታ እግዜር" ።ዘሩ ረበበ ነው
ረባ (ረብሐ)
ረባ (ረብሐ) ወለደ በዛ
ረባ (ረብዐ) አራት አደረገ
ረባ (ትግ. ረባዕ) ያራት ዓመት በቅሎ (" ሸረፍ ድርስ ")
ረባ ጠቀመ ("(ኢሳ. ፴፥ ፊልጵ. ፫፥ )")
ረባዳ ዘጣ/ዘብጥ/ጐድጓዳ ዋዲያትበገደልና በአረኸ መካከል ያለ ስፍራ "ረባዳ መሬት" እንዲሉ
ረብ መተኛት/መጋደም
ረብ አለ ተዘረጋ ተኛ ተጋደመ
ረብራቢ የረበረበ/የሚረበርብ ("ደርዳሪ አርከፍካፊ ")
ረብጣ ጥቅል ("ያቡጀዲ ጣቃ ባንድነት የታሰረ የንግድ ዕቃ)
ረተ) አረተ (ማረየ) ጠነቈለ (ደንቃራ/ጦስ ጣለ፡ ክፉ መድኀኒትና አስማት በሰው ቤት በሰው መሬት ቀበረ) ኣንድ ቍራ በመንገድ አጠገብ ቢያገኝ አንድ ድንጋይ አንሥቶ አስቀመጠ፡ ባዶ እንስራ ቢያይ ቀኝ እግሩን ዕንቅፋት ቢመታው ወደ ኋላው ተመለሰ፡ የመታውን ድንጋይ መታ።
ረተረተ) አረተረተ፡ አረጠረጠ፡ አሶመሶመ። ዘበዘበ ነገር ኦዋሸከ እዚያም እዚያም ኣለ።
ረታ ቀና ቀጥ አለ ሰላ (ተገብሮ)
ረታ ተባ በቀጥታ ተናገረ። ኣንደበቱ ረታ።
ረታ የሰው ስም።
ረታ/ረትዐ ኣሸነፈ፡ ድል አደረገ በሙግት በክርክር በሰንጠረዥ። የማታ ማታ እውነት ይረታ (ገቢር)
ረታኝ ስለቴን አደረሰልኝ ታቦቱ።
ረታኝ አሸነፈኝ።
ረትመት የወንዝ ስም በሞላሌ አጠዓብ ያለ ዠማ። ረት የረታ፣መት የመታ ማለት ይመስላል።
ረቺ/ረታዒ የረታ፡ የሚረታ፡ አሸናፊ።
ረዐይት (ረዐየ) ረዣዥሞች ሰዎች ከጥፋት ውሃ በፊት የነበሩ በራሳቸው ደመና የሚገፉ፡ ቁመታቸው ሺህ ክንድ።
ረከሰ (ረኵሰ) አደፈ፡ ርኩስ ኾነ፡ ከቅድስና ራቀ (ዘፍ፯፡ ፲፪። ሐጌ፪፡ ፲፫) (ታቦት ረከሰ) ዲያቆን ወይም ቄስ ስላመነዘረ፡ በስሕተት ታቦት ረከሰ ይባላል።
ረከሰ በረሰ፡ ተሻረ፡ ጠፋ፡ ተበላሸ፡ አስማቱ ክታቡ።
ረከሰ ወረደ፡ ተዋረደ፡ ወደቀ፡ ከመወደድ ከመክበር ተለየ፡ ሰው በነውር የሚገዛው ዐጣ፡ እኸሉ ዕቃው በገበያ።
ረከረከ (ረኰተ)
ረከረከ (ትግ፡ ሐባ፡ ረክረከ) አጐነበጠ፡ ወለደ፡ አወላገደ፡ ጻፈ፡ የበራ ሽንት እስመሰለ። ረገረገን ተመልከት።
ረከበ (ረኪብ፡ ረከበ) አገኘ፡ ደረሰ። የረከሰው ቀሊል እንዲሉ።
ረከበ ወጣ፡ በላይ ኾነ፡ ተቀመጠ።
ረከቦት የፈላ ቡና ወይም የስኒ ማስቀመጫ ማቅረቢያ ከንት ከብረት የተዘጋጀ ዕቃ።
ረከፈ) ረገፈ) አርከፈከፈ ረ።
ረኪ የሚረካ።
ረኪስ ለሸያጭ ጕዳት ለገዢ ጥቅም የሚኾን ለውጥ።
ረኪስ መርከስ፡ አለመወደድ።
ረካ (ዕብ፡ ራኸ፡ ላላ። ረወየ) ጠጣ፡ ጠጥቶ ጠገበ፡ ራሰ (ሐጌ፩፡ )
ረካሽ የሚረክስ።
ረካቢ የረከበ፡ ያገኘ፡ የወጣ።
ረክራኪ የረከረከ፡ የሚረክርክ፡ አጐንባሽ፡ ወልጋጅ።
ረክብ መገናኛ ቀን፡ ሐዋርያት ከትንሣኤ በኋላ ጌታን ያገኙበት ዕለት፡ የትንሣኤ ፳፭ኛ የበዓለ ኀምሳ እኩሌታ በዓል ሮብ የሚውል። ከዚህ የተነሣ ካህናት ቢያመቱ ስለ ቤተ ክሲያን ጕዳይ በኢየሩሳሌም ይሰበሰባሉ።
ረኰተ) ተራኰተ፡ ተጣላ፡ ተከራከረ፡ ተሟገተ። እከሌና እከሌ በዳኛ ላይ ሲራኰቱ ዋሉ።
ረኸጥ (ርሕፀ) ኤርጣጣ፡ ሰነፍ፡ ውዝፍ ሴት፡ ወፍራም፡ የፈሰሰ ውሃ፡ የማታቀና ምጣድ የለሽ።
ረዊጽ) መሮጥ - መሮጥ። ሮጥ አለ - ሮጠ። ሩጫ ጀመረ - ሩጫ ጀመረ።
ረዘመ - ረጃጅም ሆነ።
ረዘመ (ረዚም ረዘመ)
ረዘም አለ፡ ረዘመ - ረዘም አለ/ረዘመ።
ረዘም አደረገ፡ አረዘመ - ረዘም አደረገ/አረዘመ።
ረዘረዘ (ረዘዘ) ፌዴፌዴ ተረፈ - በጣም በዛ/ተረፈ።
ረዘዘ (ትግ. ረዘዘ, ደከመ ደነዘዘ. ሐረር. ረዘ) ሸጐረ, ቈለፈ, ቀረቀረ፡ በቤት/በግጥን ውስጥ አደረገ/አኖረ ዕቃን/ገንዘብን - ዘጋ, ቆለፈ፡ በቤት/በግድግዳ ውስጥ አኖረ ዕቃን/ገንዘብን።
ረዛሚ፡ የሚረዝም/በላጭ - የሚረዝም/የሚበልጥ።
ረዣዥም፡ ውስጠ ብዙ ረዥም ("(12 8)") - ብዙ ረዥሞች ("(12 8)").
ረዣዥሞች፡ የብዙ ብዙ ማለት ነው - እጅግ ብዙ ማለት ነው። ቁመታቸው 3 ሺህ ክንድ የኾነ የደቂቀ ሴት ልጆች ሰማይ ዳሶች ("(ሔኖ. 2 2)") - ቁመታቸው ሦስት ሺህ ክንድ የሆኑ የሴት ልጆች... ("(ሄኖክ 2 2)").
ረዥሜ፡ የረዥም ወገን፡ የዶሮ ቅልጥም - የረዥም ዓይነት፡ የዶሮ ጭን።
ረዥም (ሞች) የረዘመ/የበለጠ/የበዛ/የተረፈ፡ መለሎ/ትልቅ/ቀውላላ - የረዘመ/የበለጠ/የበዛ/የተረፈ፡ ረጅም/ትልቅ/ቀጭን። (ተረት) የሞተ ልጅ ዐንቱ ረዥም ነው (ትልቅ) - (ምሳሌ) የሞተ ልጅ ኧረ ትልቅ ነበረ። በረዥም ፈንታ እረጅም ማለት የስሕተት ስሕተት ነው - በረዥም ፋንታ እረጅም ማለት ስህተት ላይ ስህተት ነው።
ረዥም ጐታ ራቀ።
ረዥምነት፡ ረዥም መኾን - ርዝመት።
ረዳ፡
ረዳ (ረድአ) ሸክምን/ሥራን ተቀበለ/ዐዝ/ደገፈ/አሳረፈ/አገለገለ (ሸክምን/ሥራን ተቀበለ/አገዘ/ደገፈ/አሳረፈ/አገለገለ).
ረዳ፣ (ጽጌ፣ረዳ) የንጨት ስም ያበ ባው መልክ ነጭ መዐዛ ጣፋጭ የኾኑ ከሥር እስከ ... እሾኸ ኣለሙ።
ረዳ መንገሻ፡ የልብስ ስም ("ጥለትና ቍቲት ያለው ከባሕር የመጣ ሸማ በነጠላና በኩታ በቡልኮ ዐይነት የተሠራ") - ("ጥለትና ቁቲት ያለው ከባሕር የመጣ ሸማ በነጠላና በኩታ በቡልኮ ዓይነት የተሠራ"). "ረዳ መንገሻ የተባለው በነጋዴውስም ነው" - "ረዳ መንገሻ የተባለው በነጋዴዎችም ነው".
ረዳ መንገሻ የንቅፍል ዐጀቡ ልጅ፡
ረዳ፡ የሰው ስም.
ረዳት (ቶች) ረጂ፣ ረድ (ዘፍ፪፡ ) ረዳትነት፡ ረዳት መኾን፡ ዐዥነት።
ረዴ (ረዳኢ፡ ረድኤት) ረጂ። የምሽት ረያ እንዲሉ።
ረዴ (ረድእየ) የሰው ስም የኔ ... ማለት ነው።
ረዴት (ረድኤት) ዕገዛ ጥበቃ በረከት ጸጋ።
ረድ (ረድእ) መነኮሳትን አስተማሪን የሚረዳ ጥቍር ራስ አናኮ ደቀ መዝሙር ተማሪ። ረድ ለሴትም ይነገራል (ግብ ሐዋ፱፡ ፴፯)
ረዶች (አርድእት) አናኮዎች፣ ተማሪዎች።
ረጂ (ረዳኢ) የረዳ፣ የሚረዳ፣ ዐጋዥ (ኢሳ፴፩፡ )
ረጃት፡ ከወላጅ ወደ ልጅ የሚተላለፍ ደዌ - ከወላጅ ወደ ልጅ የሚተላለፍ በሽታ።
ረገመ (ረጊም - ረገመ) ስደበ/አዋረደ ("(፪ሳሙ. ፲፯፥ ፲፩፥ ፲፫)") "ከልጅነት ከሕዘብ አንድነት ለየ ካደ ቅርስን ውርስን ከለከለ እምኔም አትድረስ ዘር ተኸ አትቃም ወልደኸ አትሳም ጥቍር ውሻ ውለድ አለ (ተረት) የሚያድግ ልጅ እይጥላኸ የሚሞት ሽማግሌ አይርገምኽ ።ዐጥንትን እይ"
ረገረገ (ረከረከ) ነቀነቀ, ወዘወዘ.
ረገረገ፡ ዐጨቀ, ጠቀጠቀ, ከተተ, መላ ጐደጐደ, አከማቸ.
ረገረገ፡ ከጭቃ አገባ/ደባለቀ (ከጭቃ ጋር አገባ/ደባለቀ).
ረገረገ፡ ጠፈጠፈ, ረገጠ, ደመደመ.
ረገበ (ረጊብ - ረግበ) ላላ ጐረበ
ረገበ፡ ረገደ
ረገብ አለ ላላ ጐረብ አለ "ሳበ ለኸ (ጥብ)ሳብን እይ"
ረገኝ/ረግኝ/ረግናደር የነገር ዘዬ ይኾናል
ረገዘ (ረጊዝ - ረገዘ) በጦር በሾ ተል ወጋ ("(ግእዝ)")
ረገደ (ረገፀ) ምድርን በእግሩ ደቃ
ረገደ፡ ራደ / ተንቀጠቀጠ / ፈራ / አከበረ ("አቶ እከሌ ከተሾመ ዠምሮ ሰው ኹሉ ይረግድለታል")
ረገደ፡ አመካን ከፈለ
ረገዳ / ርግዶ / ርግዶሽ፡ ጭፈራ ("የሐዘን ዝላይ ሽብሸባ")
ረገድ፡ ምክንያት / ሰበብ / በኩል / ረድፍ / ተራ / ክፍል / ወፃን
ረገጠ (ረገፀ) በሰኰና መታ ከብት ሰውን ("ወይም ሰው ሰውን በእግር ደበደበ ኣረባየ ") ("(፪ነገ. ፯፥ ፲፯ )") "ምድርን በሣማው ተጠቀ ረመረመ" "(ወሰንን ረገጠ ከለለ (ዐውድማን ረገጠ) አስተካከለ ደመደመ (ስበትን ረገ) ተነ አሰረ (ወይንን ረገጠ መቀጠመቀ (በርኖስን ሸማን ረገጠ) ዐጠ ።ረገጠ ፈረ አሸበሸበ ዘለለ ረገጠ ጣሰ ዐለፈ ዳኛን ።ረገጠ ፈረሱ ፈረሲቱን የመም ህራን ዐማርኛ ነው"
ረገጠ፡ ጨፈረ / ዘለለ ("ዳንኬራ መታ")
ረገጣ/ርግጫ፡ የመርገጥ ሥራ ("ርም ርማ ጥቅጠቃ ")
ረገጥ፡ መርገጥ (ፀጥ ረገጥ) ጫማ ያረፈባት ምድር "እከሌ ከባልንጀራው ጋራ ስለ ተጣላ ወጥ ረገጡ እንዳይደርስ ተከልክሏል ።ወጥረ ጉጥ በል የሀጥር አንጻር ማለት ይኾናል"
ረገፈ (ረጊፍ - ረገፈ - አስጌጠ - ሸለመ) ወደቀ/ተጣለ/ተንጠባጠበ ("(ኢዮ. ፲፫፥ ፳፭)") "አበባው ፍሬው አዝመራው እንባው ረገፈ" እንዲሉ "ከዋክብት የስቅለት ለት እንደ ቅጠል ረገፉ (ፈንጣጣው ከፍኙ ዕከኩ ቂጥኙ ረገፈ) ጠፋ"
ረገፈ (ረጊፍ - ረገፈ)
ረገፈ፡ ፈረሰ ("ዐፈር መሬት ኾነ ")
ረገፈቀረ፡ ተለየ
ረገፍ፡ የቀረ/የተለየ "ሠም ረግፍ" እንዲሉ
ረጊ (ረጋዒ) የሚረጋ ሰው/ከብት ርጉ (ርጉዕ) የረጋ/የጸና ግግር ርጎ የረጋ ወተትወፍራም ዝቡጥቡጥ ("(ዘፍ. ፲፰፥ )")
ረጋ (ረቀየ) ፈነጠቀ፡ ነዛ፡ በተነ፡ ወረወረ (ውሃን, ሽቶን, መድኀኒትን, ደምን, ወፈርን) - ፈነጠቀ፡ ረጨ፡ በተነ፡ ወረወረ (ውሃን, ሽቶን, መድኃኒትን, ደምን, ስብን) ወረራን አስተውል የዚህ ዘር ነው - ወረራን ተመልከት የዚህ ግስ ዘመድ ነው።
ረጋ (ረግዐ) ቆመ/ዐረፈ/ተሰበሰበ/ ተጋገረ/ወፈረ/ይደግ/ደረቀ/ጸና/ተፀነስ (ተረት) "የረጋ ወተት ቅቤ ያወጣዋል" (አገር ረጋ) ሰላም ኾነ ጸጥ አለ "ረጃን እይ የዚህ ዘር ነው"
ረጋ (ዎች) የሠራተኛ/የባለጅ ተወላጅ ያልኾነ ሰው ከጠይቦች ተምሮ ሸክላን/ብረትን የሚሠራ (ተረት) "ላይሉኝ ወሶ ደርሼ ነበር እረጋ ለቅሶ ረጋ በጋልኛምስክር ማለት ነው"
ረጋ ሠራሽ ረጋ የሠራው መሣሪያ/ዕቃ ("ማማር ጥናት ጥንካሬ የሌለው ድዝድዝ ") ሩጋ ስማርድ
ረጋ ረገበ
ረጋ በል ቁም።
ረጋ አለ ረጋ
ረጋሚ (ዎች) የረገመ/የሚረግም ("ካጅ ልጄም አይዶል ባይ ")
ረጋቢ የሚረግብ/የሚላላ ረገብ (ረጊብ) መርገብ
ረጋጅ፡ የረገደ / የሚረግድ ("ረጋጭ")
ረጋጭ (ጮች) የረገጠ/የሚረግጥ ሓሪ ("(ኢሳ. ፲፮፥ )") "ጭቃ ረጋጭ" እንዲሉ
ረጋጭነት፡ ረጋጭ መኾን ("ጨፋሪነት ")
ረጋፊ፡ የሚረግፍ/የሚወድቅ ("ወዳቂ ጠፊ ") "ዓለም ዐላፊ መልክ ረጋፊ" እንዲሉ
ረግ ንኡስ ኣገባብ ("የአንክሮና የሐዘን ተጨማሪ ቃል ") "ረግ ወየው ረግ ሞዬ" እንድትል አልቃሽ ።ኝ ምእላድ እየኾኑ ሲያጋንኑት
ረግረጋም፡ ረግረግ ያለበት/የበዛበት ("ቀበሌ ባለረግረግ" - ረግረግ የበዛበት ቀበሌ).
ረግረጌ፡ የረግረግ ወንዝ ("ወይም ዐይነት" - ወይም ዓይነት).
ረግረግ (ጎች) በውስጡ ውሃ በላዩ ጭቃና ቀጤማ ሙሽ ያለበት ስፍራ. "ሲረግ ጡት የሚያረገርግ የሚንቀጠቀጥ መሬት" ("(ኢዮ. ፵፥ ፳፩ መዝ. ፵፥ ኢሳ. ፳፪፥ ፲፩)") - "ሲረግ ጡት የሚያረገርግ የሚንቀጠቀጥ መሬት" ("(ኢዮ. 40 21 መዝ. 40 2 ኢሳ. 22 11)").
 ረግረግ ) የረግረግ ምድር.
ረግራጊ፡ ዐጫቂ ("ከታች ጐድጓጅ" - ከታች ያለ ጐድጓጅ).
ረግራጊ፡ የረገረገ/የሚረገርግ ("ነቅናቂ ወዝዋዥ" - ነቃናቂ ወይም ወዝዋዥ). "ደብተራ አቴናወጊ ወዝቡን ረግራጊ እንዳሉ ዐጢ ቴዎድሮስ" - "ደብተራ አቴናወጊ ወዝቡን ረግራጊ እንዳሉ ዐጢ ቴዎድሮስ".
 ረግጥ ይገል) ወፍራም/ረዥም/ደንደሳም ኀይ ለኛ ሰው ጎልያዳዊ
ረጠረጠ (ትግ፡ ረጥረጠ) ተወ መቆምን መርጋትን። (ረተረተ) እይ።
ረጠረጠ የረጠጠ ደጊም ነው።
ረጠበ፡ (ረጥበ) ተነከረ፣ ራሰ፣ ረሰረሰ፡ ቀየ፡ ወዛ፡ ለመለመ (ተገብሮ)
ረጠበ፡ ሰጠ፡ ቀለተ፡ በጠፋ ተካ፡ ረዳ፡ ዐገዘ (ገቢር) (እጁ ረጠበ) ገንዘብ ኣገኘ (ዘሌ፳፭፣ ፵፱)
ረጠጠ (ዐረ፡ ረጸጸ፣ አነጣጠረ። ዕብ፡ ራጼጽ፡ አሸበሸበ) ዐመቀ፡ ተጫነ፡ ጨቈነ፡ ወዘፈ። ረጸጸ የቀስትን ራጼጽ የሰውነትን ጭቈና ያሳያል።
ረጣቢ የሚረጥብ፡ ሰጪ።
ረጣጭ የረጠጠ፡ የሚረጥጥ፡ ዐማቂ ተጫኝ።
ረጥል (ዐረ) ኪሎ፡ በግእዝ ልጥር፡ በአማርኛ ነጥር፡ በፈረንጅኛም ሊትር ይባላል።
ረጥል፡ ረከበ
ረጥረጥ አለ አረጠረጠ። ረጥረጥ አለ፦ ወፈረ ወጡ።
ረጨ፡ ፈነጣጠቀ፡ በታተነ፡ ወራወረ - ረጨ፡ በተነ፡ ወረወረ።
ረጨረጩ (ርሕፀ) በፍርሀት ተንቀጠቀጠ።
ረጪ (ረቃዪ) የረጨ/የሚረጭ - የረጨ/የሚረጭ። በታኝ - የሚበትን።
ረፈረፈ (ትግ፡ ረፍረፈ፡ ፈረፈረ) ጣለ፡ ለሸለሸ፡ አስተኛ፡ አጋደመ በሽታ ሰውን። ረፈረፈ፦ ረበረበ፡ ጐዘጐዘ።
ረፈቀ (ረፊቅ፡ ረፈቀ፡ ተቀመጠ) አስቀመጠ፡ ቍጭ አደረገ፡ ወዘፈ፡ ተነሣ፡ ጨቈነ።
ረፈተ (ዐረ፡ ረፈፀ) ወታደርን አሰናበተ፡ አሳረፈ። ረፈጠን እይ።
ረፈደ (ረፍደ) የጧት ጊዜ ዐልፎ ከሦስት ሰዓት በላይ ኾነ።
ረፈጠ (ዐረ፡ ረፈዐ እንቢ አለ) ረፈቀ አስቀመጠ።
ረፈጥ ከቀፎ በአፍኣ የትም ወድቆ የሚታይ የንብ ኵስ ብጫ መሳይ።
ረፋቂ የረፈቀ፡ የሚረፍቅ፡ ወዛፊ ተኝቶ ጨቋኝ።
ረፋድ የረፈደ ፀሓይ ሙቀት የዠመረበት ጊዜ።
ረፍረፎ ያልተሠራ ያልተመሸጠ የሴት ጠጕር፡ ቈንዳላ።
ረፍራፊ የረፈረፈ፡ የሚረፈርፍ፡ ረብራበ ጐዝጓዥ።
ሩሕ (ዐረ) ትንፋሽ - እስትንፋስ።
ሩሕ፡ ከናንህ ያስማት መጻፍ ወይም ክታብ - ከአፍ የሚወጣ የምትሃት ቃል/ጽሑፍ ወይም ክታብ። ሩሕ እፍ ማለትን ከአንደበቱ ጥንተ ጸሓፊውን ከነዓንን ያሳያል - ሩሕ እፍ ማለት ከአንደበቱ የመጀመሪያ ጸሐፊውን ከነዓንን ያሳያል።
ሩቅ (ቆች/ርሑቅ) የራቀ፡ በአይን የሚታይና የማይታይ ነገር፡ ሰማይ ሩቅ ዐደራ ጥብቅ እንዲሉ።
ሩቅ ውዱቅ ከፈጣሪ የራቀ፡ በአንጦርጦስ የወደቀ ሰይጣን። ዕሩቅ ቢል ከክብር ብርሃን የተራቈተ ያሠኛል።
ሩቅነት ሩቅ መኾን፡ አለመቅረብ።
ሩቅና ቅርብ ርሱ አንተ ርሷ አንቺ እነርሱ እናንተ የሚባሉ የስም ምትኮች። የቦታ እዚያ እዚህ። (የቅርብ ሩቅ) በአይን ሲያዩት ቅርብ የሚመስል ወደ ርሱ ሲኼዱ ግን ዳገትና ቍልቍለት ዘወርዋራ መንገድ ያለበት ስፍራ ጊዜ ፈጅ።
ሩብ (ቦች) የብር አራተኛ ክፍል "ገንዘብከጣሊያን ወዲህ ግን ስሙኒ ይሏታል"
ሩት የሴት ስም፡ በቅዱስ መጽሐፍ የታወቀች የሞአብ አገር ሴት።
ሩካቤ የወንድና የሴት መገናኘት።
ሩፋኤል የመልአክ ስም፡ ከሰባቱ የመላእክት አለቆች አንዱ፡ ፫ኛ አለቃ። ትርጓሜው የአምላክ ፈውስ ማለት ነው።
ሩፌ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም፡ ይኸውም ከፊለ ስም ነው። ሩፋኤላዊት ወይም ወልደ ሩፋኤል ወለተ ሩፋኤል በማለት ፈንታ ሩፌ ይባላል። አቶ ሩፌ እመት ናፌ እንዲሉ።
ሪሓን (ርሔ) ነጭ ሽቶ - ነጭ ሽቶ። ርያንን እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው - ርያንን ተመልከት፡ ከዚህ ጋር አንድ ነው።
ሪሕ (ዐረ፡ ነፋስ) ከቀዝቃዛ ነፋስ/ከብርድ የሚመጣ የእግር ቍርጥማት - ከብርድ የሚመጣ የእግር ህመም/ቁርጠት። የደም ሥር በሽታ ነዘራ ቃንዛ - የደም ሥር በሽታ/ህመም/ቁርጠት።
ሪም ጥቂት መሬት፡ ዐረመ፡ ዕሪም
ሪቅ (ቆች) ቁመተ ረዥም ጐነ ሰፊ ጐታ። ዘንችን እይ። ዕሪቅ ተብሎ ቢጻፍ ግን ዕንጨቱ ታርቆ የተሠራ ማለት ነው። መቶ ዳውላ እህል ይይዛል።
ሪቦ ጋድሚያ ረበበ
ሪወጠ) ሮጠ (ሮጸ)
ሪዛም፡ ሪዝ ያለው/ባለሪዝ - ሪዝ ያለው/ባለ ሪዝ። ሪዘ ብዙ ሪዙ ያደጋ የረዘመ ሰው - ሪዘ ብዙ ሪዝ ያለው ረጅም ሰው።
ሪዝ (ዞች) ዕድሜው ከአንድ ዓመት የማይበልጥ የበግ ጥቦት - ዕድሜው ከአንድ ዓመት በታች የሆነ የበግ ጠቦት። ጠጕሩ በውድ የሚሸጥ በርኖሱ እስከ ሠላሳ ጥሬ ብር የሚያወጣ - ሱፉ ውድ የሚሸጥ ሲሆን በርኖሱ እስከ ሠላሳ ብር ሊወጣ ይችላል። ተባቱም እንስቱም ሪዝ ይባላል - ወንዱም ሴቱም ሪዝ ይባላል።
ሪያ አውሬ፡ ůሪያ።
ራሔል፡ የሴት ስም፡ የያዕቆብ ሚስት - የሴት ስም፡ የያዕቆብ ሚስት።
ራሔሎ፡ የልጆች በሽታ ወረርሽኝ፡ ክረምት ሲወጣ የሚመጣ ጕንፋን/ትክትክ - በልጆች ላይ የሚከሰት የወረርሽኝ በሽታ፡ ከክረምት በኋላ የሚመጣ ጉንፋን/ትክትክ። ባንዳንድ ዘመን እየበረታ ልጆችን ይገድላል - በአንዳንድ ጊዜያት እየጠነከረ ልጆችን ይገድላል። ባላገሮችም ራሔሎ ኺጂ ቶሎ ቶሎ እያሉ ንፍሮ ይበትናሉ - ገበሬዎችም "ራሔሎ ሂጂ ቶሎ ቶሎ" እያሉ ንፍሮ ይረጫሉ። ይህ ስም የማቴዎስ ወንጌል ("(. 2 . 18)") ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች መጽናናትም አልቻለችም የሉምና ካለው ንባብ የተያያዘ ነው - ይህ ስም በማቴዎስ ወንጌል ("(ምዕ. 2 ቁጥር 18)") ላይ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች መጽናናትም አልቻለችም የሉምና ከሚለው ንባብ ጋር የተያያዘ ነው።
ራመመ ጠረገ፡ ፈገፈገ፡ ዐጠበ፡ አጠዳ ብራናን።
ራማ የሰማይ ስም፡ ከ፯ቱ ሰማያት አንዱ፡ የጠፈር ሦስተኛ። ትርጓሜው ልዕልና ርዝመት ደርብ ሰገነት ማለት ነው።
ራማሚ የራመመ፡ የሚራምም፡ ጠራጊ፡ ፈግፋጊ።
ራሰ፡ (ርእሰ) ራስ፡ ተባለ፡ ራስ፡ ኾነ፡ ላቀ፡ ሠለጠነ፡ ከሌሎች፡ በለጠ፡ በክብር፡ በማዕ
ራሰ መላጣ በራ ጠጕር አልባ።
ራሰ ሠሪ ጠጕር የምትሠራ ሴት፡ ዐሻሚ ጐንጓኝ ቈናኝ።
ራሰ በራ በስተፊቱ ጠጕር የሌለው መላጣ።
ራሰ ቡሓ በራሱ ላይ ነጭ ዕከክ ቈረቈር ያለበት ሰው።
ራሰ ቢስ መጥፎ ምናምንቲ ሰው።
ራሰ ክፍት ያየውን የሰማውን በቶሎ የሚያዝ ዕውቀት የሚገባው ብልኀ ሰው።
ራሰ ዘናና ራሰ ትልቅ ጭንቅሎ ጭንቅላታም ገመሞ ራስ።
ራሱ ዞረ ናላው ተናወጠ ተበሳጨ አበደ።
ራሱን ሰወረ ባለመታወቅ ኖረ።
ራሱን ቻለ ሰው ሳይዘውና ሳይደግፈው ተቀመጠ ቆመ ሕፃኑ በሽተኛው።
ራሱን ቻለ ገዦ ወጣ ትዳር ያዘ መታገዝን ተወ አባት እናቱን አላስቸገረም።
ራሱን አራቀ እኔ በማለት ፈንታ እሱ አለ (ዮሐ፲፯፡ ፩፫)
ራሱን ዐወቀ አእምሮው ተመለሰ።
ራሱን አወጣ አዳነ እተረፈ።
ራሱን አዋረደ ትሕትናን ገንዘብ አደረገ።
ራሱን ጣለ አዳፋ ልብስ ለበሰ።
ራሳ በይፋት ክፍል ያለ አገር ወይም ተራራ።
ራሳም ዱላ ከንተሮ ቋራም በትር።
ራሳም ጭንቅላታም።
ራስ (ርእስ) ካንገት በላይ፡ ያለ፡ ጭንቅላት፡ ዐናት፡ የሕዋሳት፡ ኹሉ፡ ጠቅላይ፡ የአ ካል፡ የጎላ፡ የማንኛውም፡ ነገር፡ ፵ፍ፡ መጨረሻ፡ ከራስ፡ በላይ፡ ነፋስ፡ እንዲሉ።(የንዝርት፡ ራስ) ቀንድ፡ ቅል ራሱ፡ ራስኸ፡ ሳቸው፡ ራሳችኹ ራስዎ፡ ራሷ፡ ራስ፡ ራስሽ፡ ራሳችን፡ ራሴ፡ እሱ፡ ራሱ፡ እኔ፡ ራሴ፡ እያለ፡ በ፱፡ ሰራዊት፡ ይዘረ
ራስ ላይ ወጣ አሰከረ አዞረ ጠጥ ሰውን።
ራስ መጠበቂያ ሰይፍ ዱላ ሽጕጥ ጠመንዣ።
ራስ ማሰሪያ ሻሽ ደበላ።
ራስ ምታት የራስ በሽታ ከፀሓይ ቀት የሚመጣ ምች። መታን እይ።
ራስ ሳመ) አጥብቆ ለመነ/ዐደራ አለ ስላንድ ሥራ ምክንያት
ራስ ሳይጠና ጕተና ሳይተርፍ መቸር አላቅም መሥራት።
ራስ ስሞሽ ጥብቅ ልመና ጅጊ።
ራስ ቍር/ጌራ ኀጺን የብረት ቆብ የጥንት ተዋጊ በራሱ ላይ የሚደፋው ቦርቦርቲ (፩ተሰ፡ ፭፡ )
ራስ ቅል የራስ ቅል የራስ ዐጥንት ቅል የሚመስል (ዮሐ፲፱፡ ፲፯)
ራስ በራስ በላይ በላዩ ቶሎ ቶሎ ላምን ትውለድ በታኅሣሥ ሚስትኸ ትውለድ ራስ በራስ
ራስ ቢትወደድ ድርብ የማዕርግ ስም ባለሙሉ ሥልጣን። ራስ ቢትወደድ ተሰማ የልጅ ኢያሱ ሞግዚት ነበሩ። ባተን አስተውል።
ራስ ብቻ ሰው። እከሌ እንድራሱን (ብቻውን) ኹለት ራሱን መጣ ኹለት ሰው ኹኖ ሌላ ሰው ጨምሮ አስከትሎ ማለት ነው።
ራስ፡ አለ፡ ራሰ
ራስ አእምሮ ዕውቀት ማስተዋል ይህ ሰው ራስ የለውም።
ራስ ከብዶ ራሰ ትልቅ ዓሣ። የሐዲስ መምህራን ሥጋው አይበላም ይላሉ።
ራስ ከብዶ የቅኔ አገባብ ስም፡ መጽሐፈ ሰዋስው ፫፻፲፩ኛ ገጽ ተመልከት።
ራስ ክምር ራሱ (ፍሬው) ክብ እንክብል ኳስ የሚያኸል ዕንት ዳግመኛም ስሙ የፈረስ ዘንግ ይባላል።
ራስ ክምር ራሱ ክምር የሚመስል ራሰ ክምር ታናሽ ቅጠል ጐጐት።
ራስ ወርቅ/ጌራ ወርቅ ራስ የተባለ መኰንን በራሱ ላይ የሚያደርገው የራስ ወርቅ (ወርቀ ርእስ ሽልማት በራስ ቍር ዐይነት የተሠራ)
ራስ የማዕርግ ስም ከንጉሥነት በታች ከደጃዝማችነት በላይ ያለ ማዕርግ። ራስ ጐበና ራስ ዳርጌ ልዑል ራስ መኰንን እንዲሉ። ሀምባ ራስ ቢል የተራራ የመንደር ሹም ማለት ነው። ዐምባን እይ።
ራስ ዳሸን/ራስ ዘዐሸን የስሜን ተራራ ዐሸን ራስ ማለት ነው። ዳሸንንና ሏሒትን እይ።
ራስ ጠባቂ በሕፃን ራስ ላይ የበቀለ አንድ ሽበት።
ራስ ጠባቂ ታማኝ አሽከር።
ራስ ፍልጠት እኩሌታ የራስ ዕመም።
ራስጌ በስተራስ በኩል ያለ ስፍራ የግርጌ አንጻር። ጌን ተመልከት።
ራስጌ ቤት የንጉሥ ዕልፍኝ። ያንጣፊ አለቃም ራስጌ ቤት ይባላል።
ራሶች የራስነት ማዕርግ ያላቸው ጌቶች መኳንንት።
ራሶች/አርእስት ብዙዎች ወናቶች ጭንቅላቶች።
ራሪ የሚራራ።
ራራ/ራኅርኀ ዐዘነ፡ ምሕረት አደረገ (ሮሜ፱፡ ፲፭)
ራርቶ ዐዝኖ (ዓሞ፭፡ )
ራሮት ዐዘን፡ ሀዘኔታ።
ራሽ፡ የሚርስ፡ ልጥ፡ ዓመድ፡ ያበባ
ራቀ (ርሕቀ) ተገለለ፡ ተወገደ፡ ተነጠለ፡ ተለየ፡ ፈቀቅ አለ (፪ነገ፡ ፭፡ ፲፱ ።ሉቃ ፳፪፡ ፵፩) ካይን የራቀ ከልብ ይርቃል። ይህች ልጅ በውበቷ ዛፍ የራቀው ዐረግ ትመስላለች።
ራቂ/ረሓቂ የሚርቅ፡ የሚወገድ።
ራቂ/ረሐቂ የቅርብ ሴት ትእዛዝ አንቀጽ፡ ሴትዮ ከመጥረቢያ አጠገብ ራቂ።
ራቂያ ርቀት።
ራቅ ማሰሬ የማዕርግ ስም፡ የቀድሞ ሊጋባ ራቅ ማሰሬ ይባል ነበር። ትርጓሜውም፦
ራቅ ራቅ አለ ገለል ገለል አለ።
ራቅ/ረሐቅ ለቅርብ ወንድ የሚነገር ትእዛዝ አንቀጽ፡ ገለል በል፡ ወግድ።
ራቅ/ርሒቅ መራቅ፡ ገለል።
ራበ (ርኅበ) ሆድን ሞረሞረ ("ውስጥ ውስጡን በገበገ ") (ሽለላ) "እንደ ራበኝእንደ ሞረሞረኝ ከበላ ሰው ጋራ ልሞት ነው መሰለኝ"
ራብ (ረኃብ) ችጋር/ቀጠና/ጠኔ
ራብ ያላበት/የበዛበት "ሲበዛ ራብተኞች ያሠኛል"
ራብተኛ (ርኁብ) የተራበችጋረኛ
ራብዕ (ረብዐ) አራተኛ ፊደል
ራብዕነት ራብዕ መኾን ("አራተኛነት ")
ራት የማታ ምግብ፡ አረተ እራት።
ራቻ በበትር የተወቃ እኸል፡ አረተ እራቻ።
ራእየ ማርያም የመጽሐፍ ስም ("በሲኦል የኃጥኣንን ነፍሳት ቅጣት ያየችው ማየት ") "ልጇ እያዞረ አሳይቷታል ይላሉ"
ራእየ ዮሐንስ የዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ራእይ "የመጽሐፍ ስም፡ ኀላፍያትንና መጻእያትን የሚናገር መጽሐፍ"
ራዎት (ረወየ) ርኰት, ኰዳ, የእጅ ዋን - የእጅ አንጓ/ክርን አካባቢ? በግእዝ መርወይ ይባላል ("(ኢዮ. 38 37)"). ዳግመኛም የጋሻ ዋንጫ ይሉታል - በተጨማሪም የጋሻ እጀታ ይሉታል። ኪጋሻ ጋራ የሚያዝ ማለት ነው - ከጋሻ ጋር የሚያያዝ ማለት ነው። ሲበዛ ራዎቶች ይላል - በብዙ ቁጥር ራዎቶች ይባላል። ራዎት ኩፋርን እይ - ራዎት ኩፋርን ተመልከት።
ራዛ (ዞች) ነጭ እሞራ እንደ ሩዝ፡ ንጣት ያለው አንበጣ - እንደ ሩዝ ነጭ የሆነ አንበጣ።
ራዠ (ረዘየ)
ራያ (ዮች) ያዦር ስም፡ በትግሬ አውራጃ ያለ ቈላ በረሓ፡ ሕዝቡም ራያ ይባላል፡ እነዚሁም ጋሎች ናቸው። ራያና አዘቦ እንዲሉ።
ራጨት፡ የቡሖ ዕቃ ዕጣቢ ልቅላቂ ሴት የምትረጨው - ሴት ቡሃ (የሸክላ ዕቃ) ስትታጠብ የምትረጨው ውሃ/ፈሳሽ?
ራፎን የጠንቋይ ጽፈት ፲፯ ጊዜ የሚጻፍ አስማት።
(ትግ. ጽሒራ) መቃብር አፍ ራሽ ("ሬሳ አውጭ በግእዝ ጽዕብ ይባላል")
ሬማ የዛፍ ስም፡ ቅጠሉ ቡና የሚመስል ዕንጨት፡ ለቤተ ክሲያን ደወል ይኾናል።
ሬሳ (ሶች) ነፍስ የተለየችው ሥጋ የወደቀ የተጋደመ በድን። (ተረት) ርጥብ ሬሳ ደረቁን አስነሣ። እቤተ ክሲያን ሲደርስ የጠላቴ ሬሳ የኔ ከቤት ይነሣ። ከበደን እይ። (የባሪያ ሬሳ) ዘመድ ስለሌለው ለባዕድ ተሻካሚ የሚከብድ። ሀረግን አስተውል።
ሬሳ ሸሽ በጣረ ሞት ጊዜ ከሰው ከእንስሳ የሚወጣ ዘር ቅዘን ተቅማጥ የበድን ዕጣቢ። ሬሳ ከረሳ ሊወጣ ይችላል።
ሬስ የፊደል ስም ትርጓሜው ራስ ማለት ነው።
ሬብ ሥጋዊ የፈጋራ መዝጊያ ("ማጡኔው ወይም ሸምቀቆው እንደ መረብ የሚከ ፈትና የሚዘጋ ") "ጐንደሮች ግን ሬብን ቂጥ ይሉታል ሙርጥን እይ"
ሬቦ ቃለ አኅስሮ ("የማዋረድ ቃል ") "ሬባም የባለጌ ስድብ"
ሬንዥ የምድር ዘይት ድፍድፍ ወይም ጭቃ ቅጥራን አስፋልት። የመፍቻውና የቅጥራኑም ምስጢር አጣብቆ መያዝ ነው።
ሬንጅ (ዐረ) በያይነቱ ቀለም።
ሬንጅ () እንግሊዝ መፍቻ።
("(ጥር)") ቅር ትዝ ውል ሲላላ አንተ ለሚባል ትእዛዝ ይኾናል
የዜማ ምልክት ("(አንብር)") ራእይ (ርእየ) በሕልምና በተመሥጦ ጊዜ በዐይነ ኅሊና የሚታይ ረቂቅ ነገር
ርኁብ (ርኅበ) የተራበ - የራበው። ጥራዘ ጥቂት መጣፍ፡ የጽጉብ ተቃራኒ - ጥቂት የያዘ መጽሐፍ፡ የጠገበ ተቃራኒ።
ርኅሩኅ (ራኅርኀ) የራራ/የሚራራ፡ ወዛኝ - ያዘነ/የሚያዝን፡ አዛኝ። ራራን ተመልከት - ራራን ተመልከት።
ርኅሩኅነት፡ ርኅሩኅ መኾን፡ ዐዛኝነት - አዛኝ መሆን፡ ርኅራኄ።
ርኅሩኆች (ርኅሩኃን) የሚራሩ፡ ሀዘንተኞች - የሚያዝኑ፡ አዛኞች።
ርኅራኄ፡ መራራት፡ ዐኔታ፡ ቸርነት፡ ደግነት - ማዘን፡ መተሳሰብ፡ ቸርነት፡ ደግነት።
ርመጃቸው ርገጫቸው።
ርመጅ የሴት ልጅ ስም፡ ርገጭ።
ርሙጥሙጥ አለ ተርሞጠሞጠ።
ርሙጥሙጥ ዝኒ ከማሁ፡ የተርሞጠሞጠ።
ርሚጦ (ረምፅ) በረመጥ ተጠብሶ የበሰለ የውሻ መኖ።
ርሚጦሽ ዝኒ ከማሁ። እንቍልልጦሽ የውሻ ርሚጦሽ እንዲሉ ልጆች።
ርምስ የተረመሰው፡ ሽቅ ንክር ዝፍዝፍ።
ርምስምስ አለ ተርመሰመሰ።
ርምስምስ የተርመሰመሰ፡ አኚትጕንዳን፡ ዘመሚት ሀሸን።
ርምረማ ረገጣ፡ ጥቅጠቃ።
ርምርም የተረመረመ፡ የተረገጠ፡ ጥቅጥቅ ርግጥ የጤፍ ዕርሻ።
ርምርሞሽ የመረምረም ሥራ።
ርምቡቅ ልልነት ያለው መሬት ሲረግጡት የሚሠረጐድ።
ርምድ የቂጥኝ ቍስል ካንዱ ወዳንዱ በሩካቤ የሚተላለፍ።
ርምድ የተረመደ፡ የተላከከ።
ርምጃ ርግ፵፡ አካኼድ (ዘፍ፴፫፡ ፲፬ ።፩ሳሙ፡ ፳፡ ።መዝ፲፯፡ ፲፩ ።፵፬፡ ፲፰)
ርምጥምጥ (ጦች) የተርመጠመጠ፡ ኵልፍልፍ ልክስክስ።
ርሰት፡ (ርሕሰት) ርጥበት፡ ርጥብነት፡ ራስ፡ (ርሒስ) መራስ
ርሱ ቅሉ ርሱ ራሱ። ርሱ የቅሉ ቅጽል ነው። ዳግመኛም ቅሉ ግን ተብሎ ይፈታል።
ርሱ/ርእሱ/ለሊሁ እሱ ራሱ ቅሉ ባለቤቱ። እንቶ፡ ያ። እሱን እይ። ደቂቅ አገባቦች ሲሰማሙት በርሱ የርሱ ከርሱ ለርሱ ይላል ትርጓሜውንም በዚያ የዚያ ከዚያ ለዚያ በል።
ርሳስ አድማስ፡ ቱንቢ (ዘካ፮፡ )
ርሳስ/ዐረ፡ ርጻጽ የጥይት ዐረርና ሌላም መሣሪያ የሚኾን ማዕድን እንደ ብረት ከመሬት የሚወጣ። ዐረር የግእዝ ስሙ ነው።
ርሳስ/ዐረ፡ ቢልስን ቀለም በተጌጠኛ ዕንጨት የተሸፈነ ከሰል ጽፈት መጻፊያ ቢጋር መበገሪያ።
ርሳቸው/እሳቸው ራሳቸው ቅላቸው ባለቤታቸው እነዚያ እኒያ እሊያ።
ርሳችን/እሳችን ራሳችን ቅላችን ባለቤታችን እኛ።
ርሳችኹ/እሳችኹ ራሳችኹ ቅላችኹ ባለቤታችኹ እናንተ።
ርሴ እሴ ራሴ ቅሌ ባለቤቴ እኔ እኔው።
ርስ፡ (ርሱዕ) የተረሳ፡ የተዘነጋ መረሳት፡ መዘንጋት፡ መገደፍ፡ መታ
ርስ በርሱ ክስ በክሱ እዚያው በዚያው።
ርስ በርስ ወገን ከወገን ዘመድ ከዘመድ። ዕውቀትና ትምርት የሌለው ሕዝብ ርስ በርስ ይዋጋል።
ርስ ወገን፡ ቤተ፡ ዘመድ።
ርስ የዜማ ምልክት (ድርስ)
ርስ/ርእስ እስ ራስ ባለቤት የስም ምትክ እየኾነ በ፱ ሰራዊት ይዘረዘራል። እስን ተመልከት።
ርስሽ/እስሽ ራስሽ ቅልሽ ባለቤትሽ አንቺ።
ርስተ ምድር ("ኀላፊ የሚያልፍ")
ርስተ ሰማይ ("የማያልፍ")
ርስተ ጕልት ("ንጉሥ ለባለማሉና ላገልጋዩ ርስት አድርጎ የሰጠው ጕልት ርስ ትነት ከጕልትነት ያለው መሬት")
ርስተኛ (ኞች) የርስት ጌታ ("ባለ ርስት ትክክለኛ")
ርስት ("ካባት ወደ ልጅ ሲወርድ ሲያያዝ ሲተላለፍ የሚኖር መሬት ምድር ቦታ ስፍራ ልጅም ባይኖር በዘር ይወርዳል እንጂ ወደ ባዕድ አይኼድም")
ርስት መሬት,—ወረሰ።
ርስት ተከለ ("ርስትን ሰጠ አስረከበ")
ርስኸ/እስኸ ራስኸ ቅልኸ ባለቤትኸ አንተ።
ርስዎ/እስዎ ራስዎ ቅልዎ ባለቤትዎ።
ርስዎታ ርስዎ ማለት አንቱታ ከበረታ።
ርሷ እሷ ራሷ ቅሏ ባለቤቷ ያች።
ርሩ/ርኅሩኅ የራራ፡ ያዘነ (ምሳ፳፪፡ )
ርሾ ተቀማጭ የኾነ ጥቂት ገንዘብ።
ርሾ/ዕብ፡ ሽኦር የቡሖ የወተት ቅሬታ ሌላውን የሚያቦካ የሚያሖመጥጥ (ማቴ፲፫፡ ፴፫። ፲፮፡ ) ሲበዛ ርሾዎች ይላል።
ርቀት ረቂቅነት፡ ቅጥነት፡ ሥሥነት። (ላቀ) ርቀት,—ራቂያ,—ራቀ።
ርቀት/ርሕቀት ራቂያ፡ ሩቅነት (መክ፯፡ ፳፬)
ርቄ በምንዝ ክፍል ያለ አገር። ዝናቡ መጣ ከወደ ርቄ ሊሞት ነው እሉ መላጣው ብርቄ እንዲል እረኛ።
ርቄ/ርሒቅየ እኔ ለሚል ቦዝ አንቀጽ፡ ተገልዬ ተለይቼ ማለት ነው።
ርቆሽ ዝኒ ከማሁ።
ርቢ (ዎች) ባለቤቱ ባልኾነ ሰው ዘንድ የከብት መርባት "የርቢ ከብት የከብት ርቢ" እንዲሉ "ካ፲፱፻፴፫ ወዲህ ግን የፈረንጅ ተማሮች ርቢን ርባታ ይሉታል፡ የስሕተት ስሕተት ነው"
ርቢት (ርብዒት) ካራት አንድ ጤት
ርባ (ርባሕ) የግስ አንቀጽ ወለድ "ርባ የርባታ ከፊል ነው"
ርባ ሥባ ለቤት እንስሳ የሚነገር ምርቃት "ለሰውም ይኾናል፡ ውለድ ብዛ ይድላኸ ማለት ነው"
ርባ ረበበ
ርባ ቅምር "ቅምር የተባለ ላለቅነትና ለጭፍርነት ለርባታ ተወስኖ የተመደበ ግስ ነው ሌሎችም የሰዋስው ክፍሎች ይነ ገሩበታል"
ርባ ግስ የግስ ርባታ ከነጓዙ ርባ ዘርዛሪ ዘጠኙ ሰራዊት ("ከውእቱ እስከ ንሕነ ያሉ የስም ምትኮች (መራ ሕያን")
ርባታ በሩቅ ወንድ የተነገረ ያንድ ግስ ብዛት/ብዙነት "ተመልሰሽ ርባን እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው"
ርባታ አስተማረ፡ ዐወቀ አሠኘ
ርባና ቢስ ጥቅመ መጥፎ
ርባን ሥራ በላዩ ቀጪን ሽቦ የተጠመጠመበትና ረቂቅ ንቅስ ያለበት የወርቅ/የብር መስቀል ቀለበት ኵክ ማውጫ ድኰት ግርጃ "ላንጥረኛውና ለሸያጩ ጥቅም የሚሰጥ ስለ ኾነ ርባን ሥራ ተባለ"
ርባን ርባና ረብ ጥቅም
ርባን የለሽ ጥቅም አልባ
ርባን ጌጠኛ ቀለበት
ርብ በጐንደር አውራጃ ያለ ያገርና የወንዝ ስም "ከርብ እስከ መተማ" እንዲሉ
ርብ ያገር ስም ("—ረበበ ")
ርብረባ ስደራ/ድርደራ
ርብራብ መረባርብ
ርብርብ የተረባረበ/የተርከፈከፈ ("ንብብር ድርብርብ ርክፍክፍ ")
ርብርቦሽ ንብብሮሽ
ርብትብት (ቶች) የተርበተበተ ("ፈጥኖ መናገር መሥራት የማይችል ")
ርብትብት አለ ተርበተበተ
ርብክ የተረበከ ውዝፍ ጭቃ ("ዐዛባ ከተቀመጠበት የማይነሣ ሰው ርፍቅ ")
ርብድብድ (ዶች) የተርበደበደ ፈሪ
ርብድብድ አለ ተርበደበደ
ርቦ (ዎች) የቍና አራተኛ ታናሽ ስፌት
ርቦ አፍሳሽ ካራት አንድ ለባለመሬት የሚሰጥ ተጋዥ
ርቦበቁሙ ረባ ("(ረብዐ)")
ርተኛ (ኞች) የርት ባለርት (ርት ያለው ማርት አድራጊ - ዘዳ. ፲፰፥፲፡ ሚክ. ፭፥፲፪) በግእዝ "ማሪ" ይባላል።
ርተኛነት ማርተኛ መኾን (ግብ. ሐዋ. ፲፮፥፲፮)
ርቱ የርሱ ርት። ርቱም ርቴ ምቱም ምቴ እንዲሉ።
ርታታ/ርትዐት የሙግት ፍጻሜ፡ ዕድል፡ ቀጥታ።
ርት (ማረየ) ጦስ/ደንቃራ (ሰውን ለመጕዳት የተቀበረ መድኀኒት) ባውሬና በወፍ ጩኸት በውሻ ዕንጥስታ በአሳት ማናፋት ማመን ("ከዚህ የተነሣ እንዲህ ይኾናል ይደረጋል" ማለት - መላ መምታት/ጥንቈላ)
ርት ዐደር ተረቶ ያደረ የቈየ።
ርት የተረታ፡ የተሸነፈ።
ርት/ርቱዕ የረታ፡ የቀና። ፍት ርት እንዲሉ።
ርትረታ ሶምሶማ፡ ዝብዘባ።
ርችት/ረጪ የሚበተን የመድፍ ጥይት።
ርኝት ዐዉርና ወፍራም ሰው። ዘሩ ወረን ነው።
ርኤም (ሞች) የበረዶ እንስሳ (" ቀንዶቹ ባለብዙ ተቀጥላ የኾኑ ") "መጽሐፍ ግን ሪም ይላል" ("(ዘኍ. ፳፫፥ ፳፪ ዘዳ. ፴፫፥ ፲፯)")
ርኤም ከረከንድ ርኤም የዋሊያ "ከረከንድ የፈረስ ወገን ነው፡ አንድ ስም አይዶለም" "አውራሪሥን" እይ
ርእሰ ሀገር ዋና ከተማ/መናገሻ/መዲና
ርእሰ መድጐስ ሦስት ዐይነት የድጕስ መሣሪያ
ርእስ (ርእሰ) ራስ አለቃ ("(ግእዝ)") ርእስ የፊደል ስም ( ") ርእሰ ደብር የተራራ ራስ/ጫፍ ርእሰ ደብር ማዕርጉ ከሊቀ ጠበብት በታች የኾነ የደብተሮች ሹም "ደብር የተባለ መቅደሱ ነው"
ርኩም
ርኩም (ሞች) ያሞራ ስም፡ እረኸላረኽ ተራራ ለተራራ እየዞረ እባብ ፈልጎ የሚበላ ኣሞራ፡ ተባቱም እንስቱም ርኩም ይባላል፡ ድምፁ እንደ ነጋሪት ይተማል። (ተረት) ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ ይላል ርኩም።
ርኩሰ ርኩስ የርኩስ ርኩስ (ዘሌ፲፫፡ )
ርኩስ የረከሰ፡ ንጹሕና ቅዱስ ያይዶለ፡ ነውረኛ፡ በዝሙት በኀጢአት ያደፈ የተጨማለቀ።
ርኩስነት ርኩስ መኾን።
ርኩሶች የረከሱ፡ ነውረኞች፡ ኀጢአተኞች (፪ጴጥ፡ ፪፡ ፲፫)
ርካሽ የተናቀ፡ የተዋረደ ሽያጭ። በርካሽ ተሸጠ ተገዛ እንዲሉ።
ርካሽ የከብት ትራፊ ሣር ሽንት ስለ ተሸነበትና ስለ ተረገጠ ርካሽ ተባለ።
ርካብ (ቦች) ወደ ኮርቻ መውጫ ባለማፈኛ ኹለት ጠፍር በጫፉ ሰፋፊ የብረት ቀለበት ያለው፡ ቀለበቱም ርካብ ይባላል። ርካቡ ተበጠሰ ርካብ ቈነጠጠ እንዲሉ። ርካብሽ ወርቅ፡ የምራት ስም።
ርካታ የውሃ የመጠጥ ጥጋብ።
ርክሰት (ርኵሰት) ርክስና።
ርክስ (ረኪስ) መርከስ።
ርክስ አለ ረከሰ።
ርክርክ የተረከረከ፡ ውልግድግድ ጽፈት፡ የድጓ ምልክት።
ርክክብ ቅብብል።
ርክፍካፎ ትርፍ ቃል የነገር ርክፍካፎ እንዲሉ።
ርክፍካፎ ካፊያ፡ ነጠብጣብ። (ተረት) በሐምሌ ወጨፎ በኔ ርክፍካሮ።
ርክፍክፍ የተርከፈከፈ፡ የተረበረበ።
ርኰት
ርኰት ረመዷ።
ርኰት ራዎት የውሃ መያዣ ከጕማሬ ቈዳ የተበጀ። በግእዝ ጸፈን ይባላል።
ርኰት የውሃ መያዣ፡ ረካ።
ርዝመት (ኑዏ) ዝኒ ከማሁ, የቁመት ብዛት, ሞላልነት ("(ዘፍ. 7 15 ዘዳ. 30 20 ሕዝ. 19 11 1 7 ማቴ. 23 14)") - እንዲሁ, የቁመት ብዛት, ሙላት ("(ዘፍ. 7 15 ዘዳ. 30 20 ሕዝ. 19 11 1 7 ማቴ. 23 14)"). ረዘም (ረዚም), መርዘም - ርዝመት።
ርዝማኔ፡ ረዥምነት, ብልጽግና - ርዝመት, ብልጽግና።
ርዝራዥ፡ ፍድፋጅ, ትርፍራፊ ዱቄት - ትንሽ ቀሪ, ትርፍራፊ, ዱቄት መሰል ነገር። ርዝራዥ፡ ረጃት - ርዝራዥ፡ ውርስ።
ርያን (ርሔ) ነጭ የሽቱ ቅጠል ጣፋጭ፡ ሪሓን።
ርዳ፣ ተራዳ (ርዳእ፣ ተራድእ) ወግዝ፣ ተጋገዝ፣ የሳንሳ ያዝ።
ርዳታ፡ ወዜታ በገንዘብ በጕልበት መርዳት።
ርድና፣ ረድነት፡
ርገጤ፡ የሰው ስም "ርገጥ ማለት ነው"
ርጉም (ሞች) የተረገመ ("አባት እናት አውራሾች አሳዳጎች የካዱት ") ርጉም ኾነ፡ ምርቃት ዐጣ
ርጉም ተክለ ሃይማኖት፡ "አባቱን ያስገደለ የጐንደር ንጉሥ'"
ርጉኖ፡ ነውር/አልዛ ("ጥብቅ የጠበቀ ጣይ ")
ርጋ ዕረፍ/ጸጥ በል (ግጥም) "ርጋ ይወጣሉ ደጋ ወክፈሌን አስተውል"
ርጋታ (ርግዐት) ዕረፍት/ጸጥታ/ ምታ ሰላም
ርጋጭ ርጋጭ አለ፡ ያፈር ጣዕም ሰጠ ውሃው
ርጋጭ፡ የተረገጠ ውሃ/መሬት ("(ሕዝ. ፵፥ )")
ርጋፊ/ርጋፎ፡ የረገፈ/የወደቀ ("ድቃቂ ፍርፋሪ ")
ርግ፡ ዱካ/ፈለግ ("(ኢዮ. ፱፥ )")
ርግመት (መርገም) አደፍ ("(ትክቶ)") ግዳጅ "በኦሪት ሕግ ሴትን ከሰው አንድነት የሚለይ ለብቻ የሚያስቀምጥ"
ርግማን፡ መርገም/መረገም "በግእዝ ርግመት ይባላል" ("(ዘዳ. ፳፫፥ )")
ርግረጋ፡ ንቅነቃ, ውዝወዛ.
ርግቡ ርግብ ("የርሱ ርግብ ") ርግቧ/ርግቢቱ ያች ርግብ ("(ዘፍ. ፰፥ ፲፩)")
ርግብ (ቦች) የከፍተኛ ወፍ ስም ("በቤትና በዱር የሚኖር የዋህ ወፍ የመንፈስቅዱስ ምሳሌ ") "ተባቱንና እንስቲቱን ለመለየት"
ርግብ ርግብ አለ ክድን ግልጥ አለ ቅንድቡ
ርግብ አለ ረገበ
ርግብ የረገበ ("ጕርብ ልል (ቅጽል )")
ርግብ ገር/ደግ/ህዛኝ/ርኅሩኅ ሰው "ርግብ ሆዷ ዐዛኚቷ ማሪያም ርግብማ ወርቸ ነጭ ፍየል"
ርግብግቢት፡ የተርገበገበች ("ከግንባር በላይ ከቍንጮ በታች በመካከል ያለች ሥሥ የራስ ዐጥንት") - "የሆድና የደረት መገ ናኛም ርግብግቢት ትባላለች"
ርግብግብ (ቦች) የተርገበገበ ("ልምጥምጥ") - "ርግብግብ የላም ጋሻ ለናትኸ ግባላት እንዳሉ ዐጤ ቴዎድሮስን አባ ውርጂ አንተን ይስጠኝ"
ርግብግብታ፡ የፀሓይ ሰሌዳ ንቅናቄ ወራውራን
ርግቧ የርሷ ርግብ
ርግት አለ ጸጥ አለረጋ (ረጊዕ) መርጋት
ርግት ጸጥ/ዕርፍ
ርግድግድ አለ፡ ተገደገደ
ርግድግድ፡ የተገደገደ ("እንግድግድ ፍግምግም ")
ርግድግድታ፡ ፍግምግምታ
ርግጠኛ (ኞች) እውነተኛ/የታመነ/ ሐቀኛ
ርግጡን፡ እውነቱን
ርግጥ (ርጉዕ) የተረገጠ/የተጠቀጠቀ "ሳኦል በነገሡ ጊዜ እስራኤል የእጁ ጭብጥ የእግሩ ርግጥ ኾኑ"
ርግጥ (ጥዩቅ) ድርስ/እውነት/ነገር/ሐቅ ("(ማቴ. ፲፪፥ ፳፰)")
ርግጥ ኾነ፡ ተረገጠ/ታመነ (ጥጥ)ርግጥ አደረገ፡ ረገጠ
ርግፍ (ረጊፍ) መርገፍ.
ርግፍ ርግፍ አለ፡ ጠብ ጠብ አለ.
ርግፍ አለ፡ ረገፈ.
ርግፍ አደረገ፡ ፈጽሞ ተወ (ፈጽሞ ተወው).
ርጐፍት ረዳ፡
ርጐፍት፡ ጣፋጭ ሽታ ያለው ቅጠል.
ርጓ (ርግዑኦ) ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች ትእዛዝ አንቀጽ ይኾናል "ይኸውም በፈትልና በጥለት መወርወሪያዎች መካከል ያሉትን ኹለቱን ያሳያል ትርጓሜውም ቂረፋ ማለት ነው"
ርጓ ቀን ሽመል ወይም ቀርክሓ በግራና በቀኝ እጅ ከሸማ ጠርዝ ውጭ የምትቆም የምትረጋ ("በመወርወሪያ ውስጥ ተጋድማ ከቀሠም ጋራ ድውርን የምታር የምታ ሽከረክር የሸማኔ ዕቃ ") ዳግመኛም
ርጓ ቀጪን ሽመል ("ረጋ ")
ርጠጣ ዕመቃ፡ ጭቈና ና።
ርጣጭ ርጥጥ ወዛፋ።
ርጥ የጨፍ እንጀራ፡ አነባበሮ፡ ድልኸ፡ ሰሊጥ፡ ኑግ፡ ተልባ ያለበት። (ተረት) እንግዴህ ለርጥ አምሮቴ ቍርጥ። ዕርፍ መጣያን አስተውል።
ርጥረጣ/ርትረታ ሩጫ።
ርጥበት ርሰት፡ ልምላሜ፡ ጠል።
ርጥባርጥብ የርጥብ ርጥብ፡ ብዙ ዓይነት ርጥብ፡ ሥጋና ቅቤ ያለበት ምግብ።
ርጥባን ርዳታ፡ የጠፋ ምትክ።
ርጥብ (ቦጭ) የረጠበ፣ የራሰ፣ የለመለመ (ኢዮ፰ - ፲፮) (ተረት) ሳይርቅ፡ በቅርቡ - በርጥቡ እጅን እያሉ።
ርጥብ ልጅ ያልጠና፣ ያልጠነካረ፣ ዐራስ ጨቅላ።
ርጥብ ሬሳ ሙቶ ያልዋለ፣ ያላደረ፣ ትኵስ ሬሳ። ርጥብ ሬሳ ደረቁን አስነሣ እንዲሉ።
ርጥብ ቈርበት ተገፎ ያልሰነበተ ቄዳ።
ርጥብ እማኝ በሸንጎ የሚነሣ አዲስ ምስክር።
ርጥብ ዕንጨት ያልተቈረጠ ወይም ተቈርጦ ያልደረቀ ዕንጨት።
ርጥብ ዛፍ
ርጥብ ጋን ሰረረ) አለልክ ቀበጠ አበደ
ርጥብነት ርጥብ መሆን። ርጥብ አስተኔ፡ የርጥብ ዓይነት ወይም ወገን።
ርጥጥ የተረጠጠ፡ ዕምቅ፡ ጭቍን፡ ተቀማጭ፡ ውዝፍ፡ የሰንበት እበት።
ርጨት/ርቺት፡ (ትርጉም የለውም) - ረጨት/ርቺት።
ርጭ፡ ጭር/ዝም/ጸጥታ/ዝምታ - ጭጭ/ዝምታ። ርጭ አለ - ዝም/ጭጭ አለ (በውሃ እንደ ተመታ ልጅ) - (በውሃ እንደተመታ ልጅ) ድምጽ አጣ።
ርፍራፊ ዝኒ ከማሁ፡ ንስናሽ።
ርፍርፍ የተረፈረፈ፡ የተኛ፡ ንስንስ ጕዝ።
ርፍቅ የተረፈቀ ውዝፍ።
ርፍቆች ውዝፎች ወንዶችና ሴቶች።
ርፍጥ ፍቅ ቅምጥ።
ሮሐ፡ የላሊበላ ቤተ ክርስቲያን የተሠራችበት አገር - የላሊበላ ቤተ ክርስቲያን የተሠራችበት ቦታ ስም ነው። የሮሐ ትርጓሜ በግእዝ እራ ገበ/አታጨለማ ነው - የሮሐ ትርጉም በግእዝ "ረጋ" ወይም "አታጨልም" ማለት ነው።
ሮማ/ሮሜ/፲ሮም የከተማ ስም፡ በአውሮጳ ውስጥ የሚገኝ የጣሊያን ዋና ከተማ። ይኸውም ሮምሎስ ከሚባል ካቅኒው ስም የመጣ ነው። ጊዮርጊስ ወልደ ሐሚድ ሮምሎስና ወንድሙ ኢታሎ ከዳዊት ሸሽተው ከፍልስጥኤም የኼዱ የዔሳው ዘሮች ናቸው ይላል።
ሮማነ ወርቅ ከወርቅ የተበጀ፡ የሮማን ቅርጽ።
ሮማን የተክል ስም፡ ፍሬው የሚበላ ተክል፡ ቅርፊቱ ቀይ ሲበዛ ሮማኖች ይላል (ዘፀ፳፰፡ ፴፫)
ሮማዊ የሮም አገር ሰው፡ የሮማ ተወላጅ።
ሮማዊት የሮም ሴት።
ሮማውያት የሮማ ሴቶች።
ሮማውያን የሮም ሰዎች፡ የሮማ ተወላጆች።
ሮማይስጥ የሮምሎስ ቋንቋ፡ ላቲን።
ሮም በላዩ የሴት ሻንቅላ ሥዕል ያለበት የፈረንጅ ዐረቄ።
ሮምታ ባለማቋረጥ ግባት ተኵስ።
ሮሞች ሮማውያን፡ የግእዝ ሮሞች ያማርኛ ነው።
ሮሮ (ኦሮ) ጥቃት። እከሌ ሮሮ አይመረውም እንዲሉ።
ሮቃ (ኦሮ) ሖመር።
ሮቄ ማጥ።
ሮቢት የኦሮ ነገድ ("በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ ")
ሮቤል የሰው ስም ("የያዕቆብ የበ ክር ልጅ ")
ሮብ (ረቡዕ) የቀን ስም (አራተኛ ቀን ") "ሮብና ዐርብ ከበዓላ ኀምሳና ከልደት ከጥምቀት በቀር በክርስቲያን ሕግ ሥጋና ቅቤ ዕንቍላል አይበላም"
ሮብ ለት (ዕለተ ረቡዕ) የሮብ ቀን ("ሮብ የሚባል ቀን ")
ሮብ የወንዝ ስም ("በበጌምድር የሚገኝ ዠማ ")
ሮብየቀን ስም ("—ረባ (ረብዐ)")
ሮቹ ረዣዥሞች የኋላ እግሮቹ ዐጫጪሮች የኾኑ
ሮንዛዊ የሮንዝ ማለት ነው።
ሮንዜ ባንድ ቀበሎ የገባ ብዙ ድር በነጠላ በቡልኮ ጠርዝና ጠርዝ የሚታይ።
ሮንዜ የማግ ጥሙር በኩታ በነጠላ መፃፍ በጥለት ፈንታ የተሠራ።
ሮንዝ ዕጥፍ ደርብ ሽርብ ፈትል።
ሮጠ፡ በረረ (ረወጠ)
ሮጥ፡
ሮጸ/ጋለበ ሮጠ።
ሯሪ፡ ፈጣን፡ ኦሮቢ፡ ፈርጣ ("(ኤር፶፩ ፴፩ ዕን፪፡ )") - ፈጣን፡ ሮጣሪ፡ ፈጣን ("(ኤር. 51 31 ሕዝ. 2 2)").
ሯጭ (ረዋጺ)
ሯጭ አበበ ቢቂላ፡ ሯጭ አበበ ቢቂላ።
ሯጭ፡ ዥብ አባቱን ጥሎ የሸሸ - ሯጭ፡ ጅብ አባቱን ጥሎ የሸሸ። (ተረት) ልጄ መርዉጥ, አባቴ እንደበላኸ ሩጥ - (ምሳሌ) ልጄ ሮጣሪ, አባቴን እንዳየኸው ሮጥ በል። መዥሩጥን አስተውል - መዥሩጥን ተመልከት።
ሯጮች (ረዋጽያን) የሮጡ/የሚሮጡ, ፈጣኖች ("(፩ሳሙ ፳፪ ፲፯)") - የሮጡ/የሚሮጡ, ፈጣኖች ("(1ሳሙ. 22 17)"). ሯጭነት ሯጭ መኾን ኦሮቢነት በራሪነት - ሯጭነት ሯጭ መሆን ነው።

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ