ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ኀ : የሐ ዲቃላ ፫ኛ ኀ። በግእዝና በዐረብ ድምፁ እንደ ኸ የሚነገር። በተራ ቍጥር ዘጠነኛ ሲኾን ስሙ ኀርም ኀ፡ በአኃዝነት ኀ፣ ፭፻ ይባላል። ጻፎችም ግእዙን ለራብዕ ለውጠው ስሙን ብዙኃን ኀ ይሉታል። (ነገር ግን በፊደልነት መደበኛው ዘጠነኛ ጠ ነው።)
ኀ፡ በረዶ፡ ነጭ በረዶ፣ ኆጻ መሰል ጥቃቅን።
ኈ: የኀ ዲቃላ በመኾኑ ስለ ቀለበቱ ኈ፱፻ ይባላል።
ኀለየ: ዐሰበ (ግእዝ)።
ኀለፈ)፡ ዐለፈ (ግእዝ)።
ኀላፊ፡ ዋቢ፡ ሰጪ፡ መድን፡ ዘበኛ፡ በሰጠው፣ በሸጠው፣ በጥበቃው የሚያልፍ፡ ተጠያቂ፡ ተያዥ።
ኀላፊ፡ ዋና ባለቤት፡ አዛዥ። "የሥራ ኀላፊ" እንዲሉ።
ኀላፊ፡ ያለፈ፡ የሚያልፍ ዘመን፡ ትውልድ።
ኀላፊነት፡ ኀላፊ መሆን፡ ተያዥነት።
ኀላፊዎች፡ (ኀላፍያን፣ ያት)፡ ያለፉ፡ የሚያልፉ ነገሮች።
ኀልዮ፡ ማሰብ።
ኀሙስ፡ (ኀመሰ)፡ የቀን ስም፡ ዐምስተኛ ቀን፡ በሮብና በአርብ መካከል ያለ። በሕዝብ አነጋገር ዐሙስ ይባላል፡ "ጸለየን" እይ።
ኀሚ፡ ዐምስተኛ፡ የቀባርዋ ምት።
ኀምሳ፡ (፶)፡ የቁጥር ስም፡ ፭ ጊዜ ፲ ወይም ፲ ጊዜ ፭። "ዐመሰን" ተመልከት።
ኃምስ፡ ፭ኛ ፊደል። "ኤ ኃምስ ቤ ኃምስ" እንዲል የፊደል ተማሪ። የአገር ስም መጨረሻ ፊደል በኃምስነት ሲነገር በቂ ይሆናል። "ሺዌ" "ጐንደሬ" "ጐዣሜ"፡ የሺዋ፣ የጐንደር፣ የጐዣም ሰው ማለት ነው። ፮ኛውን "ዬ" እይ።
ኃምስነት፡ ፭ኛነት።
ኀምራዊ፡ የቀይ ዐይነት፡ የቀይ ወገን። "ኀምራዊ ሐር" እንዲሉ።
ኀምር፡ ወይን ጠጅ፡ የጥቁር ቀይ ደማባ።
ኀሠሠ: የወር ስም፡ ፬ኛ ወር ከመስከረም። "ምስጢሩ፡ ጌታን፡ ለመፈለግና፡ ያለበትን፡ ለመመራመር፣ ወደቤተልሔም፡ የሰብአ፡ ሰገልን፡ መምጣት ያሳያል። ባላገርም፡ ትሣሥ፡ ይለዋል።"
ኀሳር፡ ውርደት፡ ዐሳር።
ኀረመ: ለየ፣ ከለከለ።
ኀረገ (ግእዝ): ወጣ (ዐረገ)።
ኀራም: የተለየ፣ የተከለከለ፣ የተገዘተ። (ለምሳሌ: "ኀራም ነው" እንዲሉ)።
ኀራጅ፡ (ዐረ፡ ኸረጀ፡ ወጣ)፡ ዋጋን በማሳረር የሚሸጥ ዕቃ።
ኀራጅ አለ፡ ዕቃን፣ ከብትን፣ ንብረትን አደባባይ አውጥቶ እያጫረተ ዋጋ ላበለጠ ሸጠ።
ኀርም፡ (ኀረመ)፡ የፊደል ስም፡ ፫ኛ "ኅ ኀርም ኀ" እንዲሉ። ትርጓሜው ልዩ፣ ብቸኛ ማለት ነው።
ኀርም: የኀ ፊደል ስም፣ ኀ ዘጠኝ። (ኀርምን እይ)።
ኀበረ (ግእዝ): ዐበረ።
ኀተመ: በማኅተም ረገጠ፡ ዐተመ።
ኀቲም፡ መርገጥ፡ ማተም።
ኀቲም ቀለበት፡ የማኅተም ቀለበት፡ ስም የተጻፈበት።
ኀዋት (አኀው። ትግርኛ: አኅዋት): ወንድሞች፣ ወንድማማቾች፡ ባንድ ስፍራ ተሰብስበው ውርርድ፣ ጋሬዳ የሚያደርጉ ጓደኞች፣ ባልንጀሮች። (ለምሳሌ: "የኀዋት ዳኛ" እንዲሉ)። (ጅልንና ቂልን ተመልከት)።
ኀው (እኅው): በትግሪኛ ወንድም ማለት ነው።
ኃዘና፡ የመሶብ ዐይነት ዕቃ ወይም ቅርጫት፣ የጥራር እንጀራ ማስቀመጫ። ዐረብኛ "ኸዝና" ከሚለው ጋር አንድ ነው፤ "ኸዝና" የገንዘብ ሣጥን ይባላል።
ኀያል፡ (ኀየለ)፡ ኀይለኛ (ግእዝ)።
ኀይለ መለኮት፡ የመለኮት ኀይል።
ኀይለ ሚካኤል፡ የሚካኤል ኀይል።
ኀይለ ማርያም፡ የማሪያም ኀይል።
ኀይለ ሥላሴ፡ የሥላሴ ኀይል።
ኀይለ ሩፋኤል፡ የሩፋኤል ኀይል።
ኀይለ ቃል፡ የኀይል ንግግር።
ኀይለ ቃል፡ የቃል፡ (ወልድ)፡ ኀይል።
ኀይለ አንበሳ፡ የአንበሳ ኀይል።
ኀይለ እግዚአብሔር፡ የእግዜር ኅይል።
ኀይለ ገብርኤል፡ የገብርኤል ኀይል።
ኀይለ ጊዮርጊስ፡ የጊዮርጊስ ኀይል።
ኀይለኛ (ኞች)፡ ሐርበኛ፡ ጐበዝ፡ ብርቱ (ኢሳ፴፩፡ ፳)።
ኀይለኛ(ኝ)ነት፡ ኀይለኛ መሆን።
ኀይሉ፡ ኀይሌ፡ የወንድ ከፊለ ስም፡ ዳግመኛም "የርሱ ኀይል"፣ "የኔ ኀይል" ተብሎ ይተረጐማል። ኀይል እንደ ግእዝ ሥርዐት ዘርፍና ቅጽል ይዞ ሲነገር፡
ኀይል መንፈሳዊ፡ የመልአክ ኀይል።
ኀይል ሥጋዊ፡ የሰው ኀይል።
ኀይል፡ ብርታት፡ ጕልበት፡ ጕብዝና፡ ጥናት፡ ጥንካሬ፡ ችሎታ። (ዐየለን ተመልከት)።
ኀይል፡ ገንዘብ፡ ሰራዊት (ግእዝ)። (የጦር ኀይል እንዲሉ)።
ኀደረ (ግእዝ): ዐደረ።
ኀጢአተኛ (ኞች)፡ (ኃጥእ፣ ኃጥኣን)፡ ባለኀጢአት፡ ኀጢአታም፡ ሕግ አፍራሽ፡ ክፉ አድራጊ፡ ግፈኛ፡ በደለኛ፡ አመንዝራ (መዝ፴፮፡ ፩። ፩፡
፳)።
ኀጢአተኛነት፡ ኀጢአተኛ መሆን፡ አመንዝራነት።
ኀጢአቱን አመነ፡ በድያለሁ አጥፍቻለሁ አለ፡ ንስሓ ገባ፡ ስሕተቱንና ድፍረቱን ለቄስ ነገረ፡ ተናዘዘ።
ኀጢአት ሠራ፡ ሕግን ተላለፈ፡ የማይገባ ሥራ ሠራ፡ ክፉ አደረገ፡ አመነዘረ።
ኀጢአት፡ ከሕግ የወጣ ክፉ ሥራ፡ በደል፡ ዐመፅ፡ ምንዝር፡ በኀልዮ፣ በነቢብ፣ በገቢር የሚደረግ።
ኀጢአት፡ ያመንዝራ ዘር ርክሰት።
ኀጢኣት ሠራ: ሕግን ተላለፈ፡ ሰረቀ፡ አመነዘረ።
ኃጥእ፡ (ኀጥአ)፡ ኀጢአተኛ ሰው፡ ጽድቅንና እውነትን ያጣ ወይም ያላገኘ።
ኀጫ፡ (ኆጻ)፡ ነጭ ጸዐዳ የእብነበረድ፣ አፈር አሸዋ የሚመስል።
ኀፍረት፡ (ኀፍረ)፡ ዕፍረት፡ የወንድና የሴት ብልት (ኢሳ፫፡ ፲፯)። "ዐፈረን" አስተውል።
ኂጣን፡ (ኄጠ፡ ኀየጠ)፡ ሽንገላ፡ ድለላ (ፖለቲክ)።
ኅሊና ቢስ፡ ክፉ ዐሳቢ፡ ዐሳበ መጥፎ።
ኅሊና፡ ዐሳብ፡ ልባዊ ረቂቅ ሥራ።
ኅሊናውን ሳተ፡ ልበ ቢስ ሆነ፡ አእምሮውን ዐጣ።
ኅላፍ (ፎች)፡ እኩሌታ የብራና ቅጠል፡ ታጥፎ ተላልፎ ከሙሉው ጋራ የሚጠረዝ።
ኅልፈተ ዓለም፡ የሰማይና የምድር መደምሰስ፡ መጥፋት።
ኅልፈት፡ ማለፍ፡ መታጣት።
ኅምር፡ እንሶስላ፡ ሒና።
ኅሩይ፡ (ኀረየ)፡ የሰው ስም፡ የተመረጠ፡
ምርጥ።
ኅርመት፣ በነጥብ የተወሰነ አንድ ቃል።
ኅርመት፡ የፊደል ቅንጣት፡ አንዱ ቅርጽ፣ ንቅስ አጣጣል፡ የማተሚያ ቃል፡ (ግእዝ) የንስሳ፣ የአሞራ፣ የጦር መሣሪያ፣ የፀሐይ፣ የጨረቃ፣ የኮከብ ሥዕል የተቀረጸበት ማተሚያ፡ መርገጫ።
ኅብስተ ሕይወት : ድንጋይ ዳቦ።
ኅብስተ ሕይወት: የሕይወት እንጀራ (ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ)።
ኅብስተ መና: ከሰማይ ከወረደ መና የተጋገረ ኅብስት። እስራኤል ዘመን በገዳም የተመገቡት። (መና ቅንጣቱ፡ ኅብስት ዳቦው)። (ለምሳሌ: "እመት እከሊት የጋገረችው ዳቦ ኅብስተ መና ይመስላል")።
ኅብስት (ኀበዘ፣ ኅብዝት): ክብ እንክብል ጭብጦ የሚያካክል ዳቦ። ለቡሔ፣ ላራስ ጥሪ የሚጋገር። (ሲበዛ ኅብስቶች ይላል። በግእዝ ግን እንጀራም ኅብስት ይባላል። ዕብስትን አስተውል)።
ኅብረት: አንድነት፣ ስምምነት።
ኅብር : ባንድ ቃል ኹለት ትርጓሜ የሚያሳይ ቅኔ ወይም ግጥም። (ለምሳሌ: "ሀብኒ ማየ፡ ለእመ አልብኪ ማይ" - ውሃ ስጪኝ፡ ውሃ ባይኖርሽ ማይ - ይህን የመሰለ። ጉባኤ ቃና - "መላእክተ ላዕል ወትረ እምገጸ ዓለም ተኀብኡ፡ አዕዋፈ ሰማይ ኵሎሙ አኮኑ ሥጋ መላእክት በልዑ" (ራእይ ፲፱፡ ፲፰)። አዝማሪ ስለ ንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ - "ቡዳ ነው ተብዬ እኔ ታምቻለኹ፡ ርስዎ አደባባይ ነግ ሰው (ነግሠው) እበላለኹ። " ከረመ ብለኸ ከርሞን እይ። "ራበኝም ስላት ትልክልኛለች፡ በረደኝም ስላት ትልክልኛለች፡ ሌባዬ ተይዛ ባልጋ ተጨንቃለች። " ይተጌ ተዋበች በሞቱ ጊዜ (ራስ ዐሊ)። መጽሐፈ ቅኔና የለቅሶ ዜማ ግጥም ተመልከት። ግጥም - "ሥጋውና ጠጁ ሞልቶ በቤታቸው፡ ፈጣሪ ጠላና እንጀራ ነሣቸው")።
ኅብር: አንድ ስምም፡ የጠባይ፣ የግብር፣ የነገር። (ለምሳሌ: "እከሌና እከሌ ኅብር ናቸው")።
ኅብሮች: ስምሞች፣ ግጥሞች።
ኅዋ: ከምድር በላይ ያለ ክፍት ባዶ። (በግእዝ መሠረቱ ኀወወ ነው።)
ኅይለ ድንግል፡ የድንግል ማሪያም ኀይል።
ኅዱግ: ያቡን ምክትል (ዱግ)።
ኅዳር ሚካኤል (የኅዳር ሚካኤል): በኅዳር ፲፪ኛ ቀን የሚውል፣ የሚከብር የቅዱስ ሚካኤል በዓል።
ኅዳር ታጠነ: የኅዳር ሚካኤል ለት በሰማይ በጽርሐ አርያም ስለ ዓለም ደኅንነት ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ የፈጣሪን መንበር ዐጠኑ፡ ጸሎትን አሳረጉ። በምድር በቤተ ክሲያን ጸሎተ ዕጣን ተደረገ። ስለ ወባና ስለ ወረርሽን ቈለኛ ሁሉ በየመሬቱ እሳት አንዶ ጪስ አጨሰ። (ከዚህ በኋላ የደጋው ቈላ ወረደ፡ የቈላው ደጋ ወጣ)።
ኅዳር ጽዮን (የኅዳር ጽዮን): በኅዳር ፳፩ ቀን የሚነግሥ የመቤታችን ታቦት።
ኅዳር: የወር ስም (፲፫ኛ ወር)። ሰዎች ሁሉ ሰብላቸውን ለመጠበቅ ጐዦ እየሠሩ በዱር የሚያድሩበት።
ኅዳግ (ኀደገ): በመጽሐፍ አርእስት አንጻር በጽፈት ሥር ያለ ባዶ ብራና ወረቀት ሳይጻፍበት የተተወ፣ የቀረ (የእጅ ማረፊያ፣ መጨበ፵)።
ኅድረት : የንስጥሮስ ሃይማኖት፡ "ቃል ከማርያም በተወለደ ሰው ዐደረ እንጂ፡ ከድንግል ማርያም ሥጋ ነሥቶ አልተወለደም" ማለት (የተዋሕዶ ተቃራኒ)።
ኅድረት: ማደር።
ኅጥር፡ (ዐረ፡ ዐጥር)፡ የሽቶ ስም፡ በያይነቱ ሽቶ። ኅጥር ስንቡል እንዲሉ (፫ኛውን ዐጠረ እይ)።
ኅጭጭ አለ፡ እንደ ኆጻ ጮኸ፡ ስጥጥ አለ።
ኅፅቦ፡ (ኀፀበ)፡ ታጥቦ የተወቀጠ የስንዴ ፍትግ። "ጐረደ" "ላጠ" "ብላኸ" "ጕርዶንና"፡ "ልጦን" እይ።
ኆረጠ፡ ፈጀ፡ ሖረጠ።
ኆጻ፡ ኀጫ፡ ከገደል ከተራራ የሚገኝ ነጭ የእብነበረድ አሸዋ፡ የብራና ማጠቢያ፡ ማጽጃ። በግእዝ ግን የባሕር አሸዋ፡ ጠጠር ማለት ነው።
ኋለኛ (ው፣ ኞች)፡ የኋላ፡ በኋላ ያለ። ፊተኞች ኋለኞች ይሆናሉ።
ኋለኛይቱ፡ ያች ኋለኛ። "ቱ" ቦታን ያመለክታል።
ኋሊት፡ (ድኅሪት፣ ድኅሪተ)፡ ፊጥኝ፡ ግርንግሪት።
ኋሊት፡ ኋለኝት።
ኋላ፡ (ከዋላ)፡ ደቂቅ አገባብ። የቦታ ስም፡ ዠርባ። በስተኋላ ቆመ፡ ወደ ኋላ ኼደ። ዃላ ተብሎ ሊጻፍም ይችላል።
ኋላ ቀር (ኋላ ቀሮች): የማይራመድ፣ ከስልጣኔ ወደ ኋላ የቀረ።
ኋላ፡ የጊዜ ስም፡ የሚመጣ ጊዜ። ከዚህ በኋላ፡ አሁን ተመለስና ኋላ ና።
ኋልዮ: የኋላ ሽንቁር፣ ከኋላ ያለው።
ኋልዮተ ጥርስ: ከጥርሱ ኋላ።
ኋት፡ (ክዋ)፡ ለሩቅ ሴት የአንቀጽ ዝርዝር። "እኔ እሷን ገደልኋት"።
ኋቸው፡ (ክዎሙ፡ ን)፡ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር። "እኔ እነሱን ወደድኋቸው"።
ኋችኹ፡ (ኩክሙ፡ ን)፡ ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር። "እኔ እናንተን አመንኋችኹ"። ከዚህ የቀረውን የ"ኀን" ግስና ነባር በ"ዐ" ተራ ተመልከት።
ኋደሬ: ከጀንገደር የተበጀ ጣብ (ጐዣም)።
No comments:
Post a Comment