ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ኀ በረዶ፡ ነጭ በረዶ ኆጻ መ ሳይ ጥቃቅን ።
ኀ፡ የሐ ዲቃላ ፫ኛ ።
ኈ፡ የኀ ዲቃላ በመኾኑ ስለ ቀለበቱ ኈ፱፻ ይባላል ።
ኀለፈ)፡ ዐለፈ (ግእዝ) ።
ኀላፊ፡ ዋቢ ሰጪ መድን ዘበኛ ("በሰጠው በሼጠው በጥበቃው የሚያልፍ ተጠያቂ ተያዥ") ።
ኀላፊ፡ ዋና ባለቤት/አዛዥ ("የሥራ ኀላፊ እንዲሉ") ።
ኀላፊ፡ ያለፈ/የሚያልፍ ዘመን ትውልድ ።
ኀላፊነት፡ ኀላፊ መኾን ("ተያዥነት") ።
ኀላፊዎች (ኀላፍያን/ያት)፡ ያለፉ የሚያልፉ ነገሮች ።
ኀሙስ (ኀመሰ)፡ የቀን ስም ("ዐምስተኛ ቀን በሮብና ባርብ መካከል ያለ በሕ ዝብ አነጋገር ዐሙስ ይባላል") ።
ኀሚ፡ ዐምስተኛ የቀባርዋ ምት ።
ኀምሳ (፶)፡ የቍጥር ስም ("፭ ጊዜ ፲ ወይም ፲ ጊዜ ፭") ።
ኃምስ፡ ፭ኛ ፊደል ("ኤ ኃምስ ቤ ኃምስ እንዲል የፊደል ተማሪ ያገር ስም መጨረሻ ፊደል በኃምስነት ሲነገር በቂ ይኾናል ሺዌ ጐንደሬ ጐዣሜ የሺዋ የጐንደር የጐ ዣም ሰው ማለት ነው") ።
ኃምስነት፡ ፭ኛነት ።
ኀምራዊ ይ፡ የቀይ ዐይነት ("የቀይ ወገን ኀምራዊ ሐር እንዲሉ") ።
ኀምር፡ ወይን ጠጅ ("የጥቍር ቀይ ደ ባባ") ።
ኀሳር፡ ውርደት፡ ዐሳር ።
ኀሳር፡ ጠባ ።
ኀራጅ (ዐረ. ኸረጀ፡ ወጣ)፡ ዋጋን በማሳረር የሚሼጥ ዕቃ ።
ኀራጅ አለ፡ ዕቃን ከብትን ንብረትን አደባባይ አውጥቶ እያጫረተ ዋጋ ላበለጠ ሼጠ ።
ኀርም (ኀረመ)፡ የፊደል ስም ፫ኛ ኅ ("ኀርም ኀ እንዲሉ ትርጓሜው ልዩ ብቸኛ ማለት ነው") ።
ኀተመ)፡ በማኅተም ረገጠ/ዐተመ (ግእዝ) ።
ኀቲም፡ መርገጥ/ማተም ።
ኀቲም ቀለበት፡ የማኅተም ቀለበት ስም የተጻፈበት ።
ኀዋት (አኀው. ትግ. አኅዋት)፡ ወንድሞች/ወንድማማቾች ("ባንድ ስፍራ ተሰብስበው ውርርድ ጋሬዳ የሚያደርጉ ጓደኞች ባልንጀሮች የኀዋት ዳኛ
ኀው (እኅው)፡ በትግሪኛ ወንድም ማለት ነው ።
ኃዘና፡ የመሶብ ዐይነት ዕቃ ወይም ቅርጫት (ጥራር እንጀራ ማስቀመጫ) ። "ዐረብ 'ኸዝና' ከሚለው ጋራ አንድ ነው ኸዝና የገንዘብ ሣጥን ይባላል።"
ኀይለ መለኮት፡ የመለኮት ኀይል ።
ኀይለ ሚካኤል፡ የሚካኤል ኀይል ።
ኀይለ ማርያም፡ የማሪያም ኀይል ።
ኀይለ ሥላሴ፡ የሥላሴ ኀይል ።
ኀይለ ሩፋኤል፡ የሩፋኤል ኀይል ።
ኀይለ ቃል፡ የኀይል ንግግር ።
ኀይለ ቃል፡ የቃል (ወልድ) ኀይል ።
ኀይለ አንበሳ፡ ያንበሳ ኀይል ።
ኀይለ እግዚአብሔር፡ የግዜር ኅይል ።
ኀይለ ገብርኤል፡ የገብሬል ኀይል ።
ኀይለ ጊዮርጊስ፡ የጊዮርጊስ ኀይል ።
ኀይለኛ (ኞች)፡ ሐርበኛ/ጐበዝ/ብ ርቱ (ኢሳ. ፴፩፡ ፳) ።
ኀይለኛ(ኝ)ነት፡ ኀይለኛ መኾን ።
ኀይሉ/ኀይሌ፡ የወንድ ከፊለ ስም ("ዳግመኛም የርሱ ኀይል የኔ ኀይል ተብሎ ይተረጐማል ኀይል እንደ ግእዝ ሥርዐት ዘርፍና ቅጽል ይዞ ሲነገር") ።
ኀይል መንፈሳዊ፡ የመልአክ ኀይል ።
ኀይል ሥጋዊ፡ የሰው ኀይል ።
ኀይል፡ ብርታት/ጕልበት/ጕብዝና/ጥናት/ጥንካሬ/ችሎታ ።
ኀይል፡ ገንዘብ/ሰራዊት (ግእዝ) ("የጦር ኀይል እንዲሉ") ።
ኀደረ)፡ ዐደረ (ግእዝ) ።
ኀጢአተኛ (ኞች/ኃጥእ/ኃጥኣን)፡ ባለኀጢአት/ኀጢአታም ("ሕግ አፍራሽ ክፉ አድራጊ ግፈኛ በደለኛ አመንዝራ") (መዝ. ፴፮፡ ፩፡ ፩፡ ፳) ።
ኀጢአተኛነት፡ ኀጢአተኛ መኾን ("አመንዝራነት") ።
ኀጢአቱን አመነ፡ በድያለኹ/አጥፍ ቻለኹ አለ ("ንስሓ ገባ ስሕተቱን ድፍረቱን ለቄስ ነገረ ተናዘዘ") ።
ኀጢአት ሠራ፡ ሕግን ተላለፈ ("የማይገባ ሥራ ሠራ ክፉ አደረገ አመነዘረ") ።
ኀጢአት፡ ከሕግ የወጣ ክፉ ሥራ/በደል/ዐመፅ ("ምንዝር በኀልዮ በነቢብ በገቢር የሚደረግ") ።
ኀጢአት፡ ያመንዝራ ዘር ርክሰት ።
ኃጥእ (ኀጥአ)፡ ኀጢአተኛ ሰው ("ጽድቅን እውነትን ያጣ ያላገኘ") ።
ኀጫ (ኆጻ)፡ ነጭ ጸዐዳ ("የእብነ በረድ ዐፈር አሸቦ የሚመስል") ።
ኀፍረት (ኀፍረ)፡ ዕፍረት ("የወንድና የሴት ብልት") (ኢሳ. ፫፡ ፲፯) ።
ኂጣን (ኄጠ፡ ኀየጠ)፡ ሽንገላ/ድለላ ("ፑሊቲክ") ።
ኅሊና፡ ዐሳብ ("ልባዊ ረቂቅ ሥራ ኅሊና ቢስ ክፉ ዐሳቢ ዐሳበ መጥፎ") ።
ኅሊናውን ሳተ፡ ልበ ቢስ ኾነ ("አእምሮውን ዐጣ") ።
ኅላፍ (ፎች)፡ እኩሌታ የብራና ቅጠል ("ታጥፎ ተላልፎ ከሙሉው ጋራ የሚጠረዝ") ።
ኅልፈተ ዓለም፡ የሰማይና የምድር መደምሰስ/መጥፋት ።
ኅልፈት፡ ማለፍ/መታጣት ።
ኅምር፡ እንሶስላ/ሒና ።
ኅሩይ (ኀረየ)፡ የሰው ስም ("የተመ ረጠ ምርጥ") ።
ኅርመት፡ በነጥብ የተወሰነ አንድ ቃል ።
ኅርመት፡ የፊደል ቅንጣት ("አንዱ ቅ ርጽ ንቅስ አጣጣል") ።
ኅብስተ ሕይወት፡ የሕይወት እንጀራ ("ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ") ።
ኅብስተ ሕይወት፡ ድንጋይ ዳቦ ።
ኅብስተ መና፡ ከሰማይ ከወረደ መና የተጋገረ ኀብስት እስራኤል ዘመን በገዳም የተመገቡት ።
ኅብስት (ኀበዘ፡ ኅብዝት)፡ ክብእንክብል ጭብጦ የሚያካክል ዳቦ ("ለቡሔ ላራስ ጥሪ የሚጋገር ሲበዛ ኅብስቶች ይላል በግእዝ ግን እንጀራም ኅብስት ይባላል") ።
ኅብረት፡ አንድነት/ስምምነት ።
ኅብር፡ ባንድ ቃል ኹለት ትርጓሜ የሚያሳይ ቅኔ ወይም ግጥም ።
ኅብር፡ አንድ ስምም ("የጠባይ የግብር የነገር እከሌና እከሌ ኅብር ናቸው") ።
ኅብሮች፡ ስምሞች/ግጥሞች ።
ኅዋ፡ ከምድር በላይ ያለ ክፍት ባዶ ።
ኅይለ ድንግል፡ የድንግል ማሪያም ኀይል ።
ኅዱግ፡ ያቡን ምክትል፡ ዱግ ።
ኅዳር ሚካኤል፡ (የኅዳር ሚካኤል) በኅዳር ፲፪ኛ ቀን የሚውል የሚ ከብር የቅዱስ ሚካኤል በዓል ።
ኅዳር ታጠነ፡ የኅዳር ሚካኤል ለት በሰማይ በጽርሐ አርያም ስለ ዓለም ደኅንነት ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ የፈጣሪን መን በር ዐጠኑ ("ጸሎትን አሳረጉ በምድር በቤተ ክሲያን ጸሎተ ዕጣን ተደረገ ስለ ወባና ስለ ወረርሽን ቈለኛ ኹሉ በየመሬቱ እሳት አንዶ ጪስ አጨሰ ከዚህ በኋላ የደጋው ቈላ ወረደ የቈላው ደጋ ወጣ") ።
ኅዳር፡ የወር ስም ("፲፫ኛ ወር ሰዎች ኹሉ ሰብላቸውን ለመጠበቅ ጐዦ እየሠሩ በዱር የሚያድሩበት") ።
ኅዳር ጽዮን፡ (የኅዳር ጽዮን) በኅዳር ፳፩ ቀን የሚነግሥ የመቤታችን ታቦት ።
ኅዳግ (ኀደገ)፡ በመጽሐፍ አርእስት አንጻር በጽፈት ሥር ያለ ባዶ ብራና ወረቀት ሳይጻፍበት የተተወ የቀረ የእጅ ማ ረፊያ መጨበ፵ ።
ኅድረት፡ ማደር ።
ኅድረት፡ የንስጥሮስ ሃይማኖት ("ቃል ከማርያም በተወለደ ሰው ዐደረ እንጂ ከድንግል ማርያም ሥጋ ነሥቶ አልተወለደም ማለት የተዋሕዶ ተቃራኒ") ።
ኅጥር (ዐረ. ዐጥር)፡ የሽቱ ስም ("በያይነቱ ሽቱ ኅጥር ስንቡል እንዲሉ") ።
ኅጭጭ አለ፡ እንደ ኆጻ ጮኸ ("ሢጥጥ አለ") ።
ኅፅቦ (ኀፀበ)፡ ታጥቦ የተወቀጠ የስንዴ ፍትግ ።
ኆረጠ፡ ፈጀ ሖረጠ ።
ኆጻ/ኀጫ፡ ከገደል ከተራራ የሚገኝ ነጭ የእብነ በረድ አሸዋ ("የብራና ማጠቢያ ማጽጃ በግእዝ ግን የባሕር አሸዋ ጠጠር ማለት ነው") ።
ኋለኛ ው (ኞች)፡ የኋላ ("በኋላ ያለ ፊተኞች ኋለኞች ይኾናሉ") ።
ኋለኛይቱ፡ ያች ኋለኛ ("ቱ ቦታን ያመለክታል።") ።
ኋሊት (ድኅሪት/ድኅሪተ)፡ ፊጥኝ/ግርንግሪት ።
ኋሊት፡ ኋለኝት ።
ኋላ (ከዋላ)፡ ደቂቅ አገባብ ("የቦታ ስም ዠርባ በስተኋላ ቆመ ወደ ኋላ ኼደ ዃላ ተብሎ ሊጻፍም ይችላል") ።
ኋላ፡ ኀርም ።
ኋላ፡ የጊዜ ስም ("የሚመጣ ጊዜ ከዚህ በኋላ አኹን ተመለስና ኋላ ና") ።
ኋት (ክዋ)፡ ለሩቅ ሴት የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ እሷን ገደልኋት") ።
ኋቸው (ክዎሙ/ን)፡ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ እነሱን ወደድኋቸው") ።
ኋችኹ (ኩክሙ/ን)፡ ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ እናንተን አመንኋችኹ ከዚህ የቀረውን የኀን ግስና ነባር በዐ ተራ ተመልከት") ።
ኋደሬ፡ ከጀንገደር የተበጀ ጣብ (ጐዣም) ።
ወንድሞች፡ ኀዋት ።
No comments:
Post a Comment