ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ተ፡ ፳፪ኛ ፊደል (በግእዝ እልፍ ቤት በአበገደ) ። በፊደልነት ስሙ "ታው" አኃዝ ሲኾን "ተ = ፲፻" ይባላል ።
ተ፡ የ"ከና" የ"ጠ" ተወራራሽ ። "እስኪ እስቲ እስክ እስት ከየት ተየት ወጠረ ወተረ ቀበጠጠ ቀበተተ"።
ተ፡ የመደረግና የመደራረግ ልማድ ። "ጣፈ ተጣፈ ተፈ ላከ ተላከ ተላላከ"። በ"ኣዐ" በሚነሣ ግስ በመደረግ ብቻ ራብዕ ይኾናል ("አመነ ታመነ ዐወቀ ታወቀ") ።
ተሐዋሲ፡ ተንቀሳቃሽ ።
ተሐዋስያን፡ ተንቀሳቃሾች ("ነፍሳት") ።
ተሓደደ፡ ታረሰ/ተዘራ/ታረመ/ታጨደ/ ተወቃ ።
ተሖደደ፡ ተጦመቀረ/ተተወ ምሳው ።
ተለለ (ጸሊል/ጸለለ/ተንካፈፈ)፡ ...ጠለለ ጠራ ጥሩ ኾነ ።
ተለለ (ጸልሎ/ጸለለ/አጨለመ - ተጸለለ/ጨለመ)፡ አላዋቂ ኾነ ።
ተለለ፡ ሞላላ ተኳዃነ፡ ተራዘመ፡ ተንዛዛ ነገሩ/ሰዉ።
ተለለ፡ አመመ በገረ አሠመረ...አለ ።
ተለለ፡ ፈሰሰ ወረደ ("እንባው ተለል አለ" እንዲሉ) ።
ተለላ፡ እመም ገዝም ቃዳ ።
ተለል፡ መትለል ።
ተለል ተለል አለ፡ ተላላ ሞኛሞኝ...ኾነ ።
ተለል አለ፡ መጥለል ዠመረ ፈሰስ...አለ ።
ተለመ (ተሊም/ተለመ)፡ ዕርሻ ዠ...መረ ወረሰ (አንድ ፈር እወጣ ቦደነ ገመሰ) ።
ተለመ፡ ያዘ ለከፈ (በሽታ ሰውን) ።
ተለመነ፡ ተማለደ፡ ልመናን፡ ተቀዕሺ፡ በጎ፡ አለ፡ ("ዘፍ. ፲፬፡ ፥፳፩ ። ፪ሳው. ፳፩፡ ፲፰")እባክኸ፡ ስጠኝ፡ መጽውተኝ፡ ተባለ ።እለምን ትለኹ፡ ተለመነኝ፡ እንዲሉ፡ ባልቴቶች ።
ተለመነ፡ ተቀፈፈ፡ ተቧገተ፡ በእንተ፡ ስማ፡ ለማርያም፡ ተባለ።
ተለመከከ፡ ተቀባ፡ ተላከከ።
ተለመዘገ፡ ተቈነጠጠ።
ተለመደ ፣ ተጠና፡ ተያዘ፡ ታወቀ፡ ገባ፡ ትምርቱ።
ተለመጠ፡ ለማጣ፡ ኾነ፡ ዘባ፡ ደራ።
ተለመጠ፡ በጠፍር፡ ተሳለ፡ ለዘበ።
ተለመጠ፡ ተለጠጠ፡ ተቈነነ።
ተለመጠጠ፡ ተቃጠለ፡ ተገረፈ፡ ሰፊ፡
ተለመጨጨ፡ ተለጠሰ፡ ተኛ።
ተለማ፡ ትልሚያ ዥሠራ ።
ተለማመነ፡ (ተጋነየ)፡ ተለማመጠ፡ ልመናን፡ ተቀባበለ።
ተለማመጠ፡ (ተጋነየ)፣ ለመነ፡ ተለማመነ ፣ተማለለ ፣ይስበረኝ፡ ይሠንጥረኝ፡ አለ፡ በትሕትና፡ በለዘብታ፡ ቃል፡ ተናገረ ።
ተለማማኝ ፣ የተለማመነ፡ የሚለማመን፡ ተለማማጭ ።
ተለማማኝነት፡ ተለማማጭነት።
ተለማማጭ፡ (ጮች)፡ የሚለማመጥ።
ተለማማጭ፡ አልማጭ፡ እንዲሉ።
ተለማማጭነት፡ ተለማማኝነት።
ተለማኝ፡ ተማላጅ፡ የሚለመን፡ ለማኝን፡ የማያሳፍር ።አብ፡ አይበልጥሞይ፡ አባትኸ፡ ተለማኝ፡ እናትኸ፡ (አዝማሪ) ።
ተለማዘገ፡ ተቈናጠጠ ።
ተለማገገ፡ ተሳሳበ፡ ተጣባ።
ተለማጠጠ፡ ተለቋጠጠ፡ ተረፈ።
ተለማጭ፡ ተለጣጭ፡ ተቈናኝ።
ተለማጭ፡ የሚለመጥ፣ክትክታ፡ ቀጨሞ፡ የመሰለው፡ ኹሉ።
ተለምዶ፡ ተጠንቶ፡ ተይዞ፡ ታውቆ፡ ሥራዬ፡ ተብሎ ።በኃይለ፡ ሥላሴ፡ ተለምዶ፡ ተለምዶ፡ መጣ፡ ሙሶሊኒ፡ የባሕር፡ ላይ፡ ዘንዶ፡ (ክራር፡ መቺ) ።
ተለሰቀ፡ ተጣበቀ፡ ተያያዘ፣ ብዙው፡ ኣንድነት፡ ኾነ።
ተለሰነ፡ ተቀባ፡ ተለቀለቀ፡ ታሸ፡ ታሠሠ፡ ተተካከለ፡ ("ማቴ. ፳፫፡ ፳፯ ። ግብ. ሐዋ. ፳፫፡ ፫") ።
ተለሳለሰ፡ ልስልስ፡ ተኳዃነ፡ ተለዛዘበ፡ (ለሰለሰ፡ ሥራ፡ ተወ፡ ተቀምጦ፡ ዋለ) ።
ተለሳቂ ፣ የሚለሱቅ፣ ለጥ፡ የሚል፡
ተለሳኝ፡ የሚለሰን፡ ግንብ፡ ግድግዳ ።
ተለስ፡ የሰሌን ምንጣፍ ።
ተለሽለሽ፣፡ ተጣለ፡ ወደቀ፡ ተጋደመ፡ ተኛ፡ ተረፈረፈ፡ ምድር፡ አላበሰ ።
ተለቀ ፣ ላቀ፡ ትልቅ፡ ኾነ።
ተለቀ፡ ትልቅ ኾነ ላቀ ።
ተለቀሰ፡ ታዘነ፡ ተቈዘመ፡ ውይ፡ ተባለውሎ፡ ተዋለ ፣ተነባ፡ መነጩ፡ ፈሰሰ፡ ወረደ፡ ተንቧቧ ።
ተለቀቀ፡ ተፈታ፡ ወጣ፡ ወለቀ፡ ተፈተ፡ ተተወ፡ ("ኤር. ፴፩፡ ፳፪ ።ግብ. ሓዋ. ፬፡ ፳፫")
ተለቀቀሰፊ፡ ኾነ፡ ተለየ ።
ተለቂ፡ (ተለቃሒ)፡ የተለቃ፡ የሚለቃ፣ ተበዳሪ ።
ተለቃ፡ (ተለቅሐ)፡ ተሰደረ፣ሰዉ፣ ተሰጠ፡ ገንዘቡ።
ተለቃሽ፡ የማች፡ ቤተ፡ ዘመድ።
ተለቃቂ፡ የሚለቀቅ፡ ከብት፡ እስረኛ
ተለቈደ፣ ለንባዳ፡ ኾነ።
ተለተለ (ትግ. ተልተለ/ሸደሸደ)፡ ፈታ ተረተረ መዘዘ (ያዲስ ልብስን ማግ ከድር ለየ አወጣ - ሥሩ "ተለለ" ነው) ።
ተለተለ፡ ቀደደ ሠነጠቀ በጣ (ቅሪላን ዦሮን ፊትን - "ዘለዘለንና ተነተነን" እይ) ።
ተለነቀጠ፡ ተፈጨ፡ ላመ፡ ለዘበ።
ተለከፈ፡ ቀረበ፡ ተደቀነ፡ ለቅልውጥ።
ተለከፈ፡ ተቀመሰ፡ ተነካ፡ ተነከሰ።
ተለከፈ፡ ተዠመረ፡ ተያዘ።
ተለኪ፡ የሚለካ ።
ተለካ፡ (ተለክአ)፡ ተመጠነ፡ ተሰፈረ፡ ተሸለገ፡ ተረተመ፡ ተከነዳ፡ ተመዘነ፡ (ተረት)፡ በሞኝ፡ ቁመት፡ መቃብር፡ ይለካበት። የሙሴን፡ ዜና፡ ሞት፡ ተመልከት፡ (ገጽ፡ ፬፻፩፳፩) ።
ተለካከፈ፡ ተቀማመሰ፡ ተነካካ፡ ተነከሰ ።
ተለካከፈ፡ ተዠማመረ፡ ተያያዘ።
ተለካኪ፡ የሚለካካ፡ ተመጣጣኝ።
ተለካካ፡ ተመጣጠነ፡ ተሸላለገ፡ ተከነ ዳዳ ።
ተለኰሰ፡ ተተኰሰ፡ ተቃጠለ፡ ተያያዘ ።
ተለኰፈ፡ ላመል፡ ተመታ፡ ተተነኰሰ።
ተለኳኰሰ፡ ተተኳኰሰ፡ ተቀጣጠለ።
ተለወሰ፡ ላቈጠ፡ ታሸ፡ ተዋዋደ፡ ተቦካ፡
ተለወጠ፡ (ተወለጠ)፡ ሌላ፡ ኾነ፡ እ ንደ፡ ሎጥ፡ ሚስት፡ እንደ፡ ማየ፡ ቃና።
ተለወጠ፡ ተሼጠ፡ ኦለባለቤቱ፡ ተሰጠ።
ተለወጠ፡ ታማ፡ ገማ፡ ሸተተ።ቃናው ተለወጠ፡ እንዲሉ።
ተለወጠ፡ ታደሰ፡ ረቀቀ፡ ("፩ቆሮ. ፲፭፡ ፶፩, ፶፪") ።
ተለወጠ፡ ከፋ፡ ወይም፡ ደግ፡ ኾነ።
ተለዋሽ፡ የሚለወስ፡ የሚታሽ፡ ዶቄት፡ ብትን፡ ድልኸ።
ተለዋወጠ፡ ተሻሻጠ፡ ተገዛዛ።
ተለዋወጠ፡ ተጐሳቈለ፡ ተጣቈረ፡ የሰ
ተለዋወጠ፡ አኹን፡ ሰው፡ አኹን፡ ሌላ፡ ኾነ፡ በትረ፡ ሙሴን፡ ዕሥሥትን፡ መሰለ፡ ተቀያየረ፡ ተዘዋወረ፡ ተወራረሰ ።
ተለዋዋጭ (ጮች፡ የሚለዋወጥ፡ ተ ሻሻጭ ። ጠባዩ፡ ኹናቴው፡ አንድነት፡ የሌለው።
ተለዋዋጭ፡ ተወራራሽ፡ ፊደል።
ተለዋዋጭነት፡ ተለዋዋጭ፡ መኾን።
ተለዋዘዘ፡ ተላዘዘ።
ተለዋዘዝ፡ ርጥብ፡ አስተኔ ።
ተለዋጭ፡ የሚለወጥ፡ ዕሥሥት፡ ዐይነት፡ ሰው ።
ተለዋጭነት፡ ተለዋጭ፡ መኾን።
ተለዘ (ትግ. በጣ)፡ ደከመ ("ጠለሰን" አስተውል) ።
ተለዘበ፡ (ለዘበ)፡ ዘነጋ፡ ተዘለነ፡ አመነ ። (ተረት)፡ ባንዱ፡ ታዘብ፡ ባንዱ፡ ተለዘብ፡
ተለየ፡ (ተሌለየ)፡ ተነጠለ፡ ተሠነጠቀ፡ ተከፈለ፡ አንድነትን፡ ዐጣ።
ተለየ፡ ተለመደ፡ ታወቀ።
ተለየ፡ ዐረፈ፡ ሞተ።
ተለያየ፡ ተፈራቀቀ፡ ተነጣጠለ፣ ባሳብ፡ በሞት፡ ወዲያና፡ ወዲህ፡ ተኳዃነ፡ ("መዝ. ፳፪፡ ፲፬") ።
ተለያዪ፡ የሚለያይ፡ ተፈራቃቂ ።
ተለይ፡ ባዳ፡ እንዲል፡ እረኛ ።
ተለይ፡ ብቻሽን፡ ኹን።
ተለደፈ፡ ተለጠፈ።
ተለገደ፡ ተወተፈ፡ ተቀረቀረ፡ ተመረገ።
ተለጊ፡ የሚለጋ፡ ዕሩር ።
ተለጋ፡ ተቀላ፡ ተመታ ።
ተለጋ፡ ተጠጣ፡ ተሠረገበ ።
ተለጋጅ፡ የሚለገድ፡ ተቀርቃሪ።
ተለጐመ ("ተጐ ለሰ ተሰፋ ተለባጅ የሚለበድ ተለጓሚ ") ።
ተለጐመ፡ ልጓም፡ ጥይት፡ ኳስ፡ ጐረሠ።
ተለጐመ፡ ተሰፋ፡ ተለበደ፡ ዐረብ፡ ለበሰ።
ተለጐመ፡ ዝም፡ አለ፡ አልተናገረም ።
ተለጐመ፡ ገባ፡ ተቀረቀረ።
ተለጐደ፡ ተለደፈ፡ ተለጠፈ።
ተለጓሚ፡ የሚለጐም፡ ከብት፡ ስፌት።
ተለጠጠ፡ ቀስ፡ ብሎ፡ ኼደ፡ ተቈነነ።
ተለጠጠ፡ ተሠነበጠ፡ ተከፈለ፡ ተነጠለ።
ተለጠጠ፡ ተሳበ፡ ተጐተተ፡ ("ኢሳ. ፭፡ ፳፰ ። ፳፩፡ ፲፭")
ተለጣጭ፡ (ጮች)፡ የሚለጠጥ፡ ተነጣይ፡ ተሳቢ፡ ተቈናኝ ።
ተለጯ፡ የልጭታት፡ ብድር፡ ተመላ
ተለፈለፈ፡ ብዙ፡ ሰዓት፡ ተነገረ።
ተለፈጠ፡ (ተለፍጸ)፣ ተለወሰ፡ ታሸ፡
ተለፊ ፣የሚለፋ፡ የሚዠለጥ፡ ለፊ ።
ተለፋ፡ (ለፋ)፡ ተጣረ፡ ተደከመ '
ተለፋለፈ፡ ቀጥሎ፡ ቀጥሎ፡ ተነጋገረ፡ ተንሣ፡ ተኸ።
ተለፋቀ፡ ተነዛነዙተጨቃጨቀ፡ አንዱን፡ ነገር፡ መልሶ፣ መላልሶ፡ ተናገረ።
ተለፋደደ ፣ ተለፋጨቀ፡ ተጨማለቀ፡ ባነጋገር ።
ተላ (ዕብ. ቱሎዕ)፡ ኾነ ተገኘ ተፈጠረ ተፍለከለከ ተርመሰመሰ ወጣ (የትል - ዘፀ.
፲፯፡ ፳፡ ዘኍ. ፭፡ ፳፪) ።
ተላ፡ ውሃ ተራጩ፡ ተሳካ፡ ተሳላ። (አልተላም)፡ አልበጀም፡ አልተሳላም።
ተላለመ፡ ዠማመረ ዐራረሰ ።
ተላለቀ (ተኃለቀ)፡ ተቀራደደ ተጋደለ ተጝተ ። ተላላቂ
ተላለከ፡ ተዳፈረ፡ ተጋፋ፡ ተወዳደረ ።
ተላለፈ፡ ተለዋወጠ (የሕብር የመልክ - ዘፍ. ፴፩፥፰፥፲ - "(ተደራራጊ)") ።
ተላለፈ፡ ተዳፈረ (ሕግ አፈረሰ - ዳን. ፫፥፳፰ - "(አድራጊ)") ።
ተላለፈ፡ ካንዱ ወደ ሌላው ተረማ መደ ተጋባ ተዛመተ ("(ተደራራጊ)") ።
ተላለፈ፡ ወደ ፊትና ወደ ኋላ ኼደ ("(ተገብሮ)") ።
ተላላ (ጽሉል)፡ ድልል ሞኝ ደንቈሮ ዝንጉ ። ("ተረት - የዝንብ ተላላ ካንድ በሬ ደም ይቀርባታል") ።
ተላላሰ፡ (ተላሀሰ)፡ ተነካካ፡ (ባከነ)፡
ተላላሰ፡ (ተላሐሰ)፡ የመላላስን፡ ብድር፡ ተከፋፈለ፡ የፍቅር፡ መሳሳም፡ ተሳሳመ ።
ተላላቀ ፣ ተበላለጠ ።
ተላላቂ፡ ተበላላጭ።
ተላላቂ ፣የሚተላለቅ ፣ዐለቀ።
ተላላከ፡ (ተላአከ)፡ ተጻጻፈ፡ ደብዳቤን፡ በደብዳቤ፡ ቃልን፡ በቃል፡ ብዙ፡ ጊዜ፡ ተመላለሰ።
ተላላኪ፡ (ዎች)፡ (ተላኣኪ)፡ የሚላላክ፡ አሽከር፡ መልክተኛ፡ መላክትን፡ አድርሶ፡ መላሽ፡ ተመላሽ ።
ተላላጠ፡ ተጋፈፈ፡ ተገፋፈል፣ በኹሉ፡ ወገን፡ ተላጠ፡ ተመላለጠ።
ተላላፈ፡ ተጋፈፈ፡ ተላላጠ ።
ተላላፊ (ዎች)፡ የተላለፈ/የሚተላለፍ (መንገደኛ በሽታ " ሕግ አፍራሽ - ምሳ. ፱፥፯፡ ፳፮፥፲፱፡ ኢሳ. ፵፰፥፰፡ ሆሴ. ፲፬፥፱)
ተላላፊነት፡ ተላላፊ መኾን ።
ተላሌ፡ የተላላ ወገን (የተደበቀን ዕቃ ማግኘት ያልቻለውን ሰው "ተሳሌ ሆይ" እን...ዲል የማሲንቆ ምት) ።
ተላመ፡ (ላመ)፡ ተለነቀጠ ።
ተላመደ፡ ተለማመደ፣ ተቃረበ፡ ተቀራረበ፡ ተዋወቀ፡ ተሰማማ ።ተላመደ፡ የግእዝና፡ ያማርኛ ፣ተለማመደ፡ ያማርኛ፡ ብቻ፡ ነው ።
ተላመጠ፡ ተዛባ፡ ተጓበጠ፡ ርስ፡ በርሱ።
ተላመጠ፣ ታኘከ፡ ተመሰኳ፡ ለዘበ፡ ተለነ
ተላሚ (ዎች)፡ የተለመ/የሚተልም (ዠማሪ ሀራሽ) ።
ተላማ፡ ተያያዘ፡ ተጋጠመ፡ (ተጠገነ) ።
ተላሰ፡ (ተልሕሰ)፡ ተጠረገ፡ ጠዳ፡ ተ
ተላሰ፡ ተቃጠለ፡ ተመለጠ።
ተላሰሰ፡ ተነቀለ፡ ተሰሰ።
ተላቀ ፣ (ተልህቀ)፡ ተበለጠ፡ እነሰ-
ተላቀሰ፡ ተዛዘነ፡ ዋይታ፡ ተቀባበለ፡ ተናባ፡ እንባ፡ በንባ፡ ተራ።
ተላቀቀ ፣ (ተደራራጊ)፡ ተለያየ፡ ተፋታ።
ተላቀቀ፣ ተደራጊ)፡ ተፈቀደ፡ ተፈቀደለት፡ መብት፡ ተቀበለ፡ ተሰናበተ - ለማገት።
ተላቃቂ፡ የሚላቀቅ፡ የሚፋታ፡ የሚለ
ተላቈጠ፡ ላቈጠ።
ተላተለ፡ ፈታታ ቀዳደደ ለያየ ።
ተላከ፡ (ተልእከ)፡ መልክት፡ ይዞ፡ ኼደ፡ መጣ።
ተላከ፡ በቤተ፡ ልሔም፡ ሐሪጽ፡ ዐሸ፡ ቍርባን፡ ሠራ፡ ዐበዘ፡ ጋገረ፡ አገለገለ።
ተላከከ፡ ተቀባ፡ ተዶለሰ፡ ተለጠፈ፡ ተጣበቀ፡ ተገጠመ፡ ተመካኘ ።
ተላከፈ፡ ተቃመሰ፡ ተናካ፣ ተናከሰ።
ተላከፈ፣ ተዣመረ።
ተላኪ፡ (ተለኣኪ)፡ የተላከ፡ የሚላክ፡ ብላቴና፡ ዲያቆን።
ተላካ፡ ተከናዳ ።
ተላካኪ፡ የሚላከክ፪ ተጣባቂ።
ተላኰሰ፡ ተታኰሰ።
ተላኰፈ፡ ተናካ፡ ተተናኰሰ።
ተላወሰ፡ ተልኰሰኰሰ፡ ተረገጠ፡ (ተደ ራጊ) ።
ተላወሰ፡ ተንቀሳቀሰ፡ ተነቃነቀ። ሽል፡ በማሕፀን፡ ይላወሳል፡ (ተደራራጊ) ።
ተላወሰ፡ ጥቂት፡ ጥቂት፡ ኼደ፡ ተራመደ።
ተላወጠ፡ (ተዋለጠ)፡ ገንዘብን፡ በገንዘብ፡ ከብትን፡ በከብት፡ ዕቃን፡ በዕቃ፡ ተሰጣጠ፡ ተቀባበለ፡ ተገዛዛ፡ በባለቤትነት፡ ተዛወረ፡ ("ሕዝ. ፳፯፡ ፲፭") ።
ተላዋሽ፡ የሚላወስ፡ ተንቀሳቃሽ።
ተላዘበ፡ ተለዛዘበ፡ ተዳቀቀ፡ ተላላመ ።
ተላዘዘ፡ ተራራሰ።
ተላገ፡ (ተልሕገ)፡ ተፋቀ፡ ታነጠ፡ ተነጠጠ፡ ለዘበ፡ ለሰለሰ፡ ተተካከለ፡ በምላስ፡ የተ ላሰ፡ መሰለ።
ተላገ፡ ተማሰለ፡ አብሲቱ።
ተላገደ፡ ተዛበት፡ ተናናቀ። ልማዱ፡ ግን፡
ተላገደ፡ አላገጠ፡ ተሣለቀ፡ ዘበተ፡ ናቀ፡ አቀለለ፡ ጡር፡ መስቃ፡ ተግዳሮት፡ ተናገረ፡ ነው፡ ("፩ሳሙ. ፲፯፡ ፲። ዕን.፩፡ ፲። ሶፎ.፪፡ ፰")
ተላጊ፡ የሚላግ፡ ተፋቂ።
ተላጋ፡ ተማታ፡ ተጋጨ። (እንቆቅልሽ)፡ ትንሽ፡ ዐለንጋ፡ ወንዝ፡ ለወንዝ፡ ትላጋ።
ተላጐደ፡ ተላጠፈ።
ተላጠ፡ ሸሸ፡ በረረ። እኛ፡ ሲመጡ፡ እኛ፡ ሲላጡ፡ እንዲል፡ ፈካሪ።
ተላጠ፡ ተሻረ፡ ተለወጠ፡ ቀረ። ፍርድ፡ ተላጠ፡ እንዲሉ።
ተላጠ፡ ተገፈፈ፡ ተለየ፡ ("ዘፍ. ፴፡ ፴፰") ።
ተላጠ፡ ተፈሳ፡ ተለቀቀ። (ላጤ)ላጤ፡ ብቸኛ ።ወንደላጤ፡ እንዲሉ ።
ተላጨ፡ ተፈገፈገ፡ ተገፈፈ፡ ተጠረገ፡ ተወገደ፡ ተጣለ፡ ወደቀ፡ ("ኢሳ. ፲፭፡ ፪") ።
ተላጪ፡ የሚላጭ።
ተላጭ፡ የሚላጥ፡ የሚሻር፡ ዛፍ፡ ብይን።
ተላፈ ፣ ተበላ፡ ተጠጣ።
ተላፈ፡ ተለየ፡ ተገፈፈ።
ተላፈ፡ ተቃጠለ፡ ተላጠ።
ተላፊ ፣ የሚላፍ፡ የሚለይ።
ተላፊ የሚላፋ ፣ለፋ ።
ተላፊ፡ የሚላፋ፡ ተጫዋች።
ተላፋ፡ (ተላፍዐ)፡ ተፋተገ፡ ተሻሸ፡ ተጫወተ፡ ተዳለቀ፡ ተቈላመጠ።
ተሌጠ፡ ተፌዘ፡ ተለገጠ።
ተልባ (ተላቤ)፡ የቅመም ስም (ቅባትነትና ማላጋነት ያለው ቅመም ከማር ጋራ...) ።
ተልባ መጠጥ (የተልባ መጠጥ)፡ ያቶ በዛብኸ ጦር ።
ተልባ ማሻ፡ በውስጡ ብር ያለበት ግምጃ የለበሰ ገበቴ ። አለቃ ገብረ ሐና ቀማኞችን ስለ ፈሩ "የሚካኤል ታቦት ነው" ብለውታል ።
ተልባ እግር (የተልባ እግር)፡ ...ከተልባ ልጥ የተሠራ ክታን ጥሩ ልብስ ። በግእዝ "ዐጌ" ይባላል (ኢሳ. ፫፡ ፳፫) ። ፈረንጆችም "ሊኖ" ይሉታል ።
ተልባ ውሃ፡ ሰጐዣም ክፍል የሚገኝ ታላቅ ተራራ ።
ተልባ፡ ውለ ቢስ የማይታመን ሰው ተንሸራታች ("እከሌ ተልባ ነው" እንዲሉ) ።
ተልባ ድርጥ (የተልባ ድርጥ)፡ በውሃ የታሸ የተልባ ልቍጥ ("ደረጠ" ብለኸ "ድርጥን" እይ) ።
ተልባ/ተልቢቱ፡ ተረታዊ የሴት ስም ።
ተልብማ፡ ተልባ መሳይ (ቀለመ ተልባ መልከ ተልባ እባብ ቦረቦጭ ሌላውም ነገር ኹሉ) ።
ተልታይ (ዮች)፡ የተለተለ/የሚተለትል (ተርታሪ ሠንጣቂ) ።
ተልከሰከሰ፡ ረከሰ፡ ለከሰ ።
ተልከሰከሰ፡ ቅጥ፡ ዐጣ፡ ተበተነ፡ ተረገጠ፡ ረከሰ።
ተልከሰከሰ፡ ባንድ፡ ስፍራ፡ መለስ፡ ቀለስ፡ አለ ። (ግጥም)፡ እከደከድዬ፡ ነገር፡ ተበላሸ፡ እሥጋ፡ ገበያ፡ ስልከሰከስ፡ መሸ ።
ተልከሰከሰ፡ አመነዘረ፡ ሸረሞጠ።
ተልከስካሽ፡ የማይለቅ፡ የማይኼድ፡ በ
ተልከፈከፈ፡ በምላሱ፡ ነካ፡ ነካአደረገ፡ ተልከሰከሰ ።
ተልከፍካፊ፡ የሚልከፈከፍ
ተልካሳ፡ ሰነፍ፡ ለከሰ ።
ተልካሳ፡ ደካማ፡ ዐቅመ፡ ቢስ፡ ሰነፍ፡ ታካታ፡ ሥራ፡ ጠብ፡ የማይልለት።
ተልካሻ፡ (ሾች)፣ዝኒ፡ ከማሁ።
ተልኰሰኰሰ፡ ተላወሰ፡ ተረገጠ ።
ተልኰሰኰሰ/ተላወሰ፡ ለኰሰ ።
ተልኰፈኰፈ፡ ተኵለፈለፈ ።
ተመለለ፡ ረዘመ/ወጣ።
ተመለመለ፡ ተለየ/ተመረጠ/ከበረ። (ተረት)፡ "ሰው ቢታጣ ተመለመለ ጐባጣ"።
ተመለመለ፡ ተኰተኰተ/ተቀነጠበ/ተቈረጠ።
ተመለሰ፡ ተተረጐመ።
ተመለሰ፡ ተደገመ/ተከለሰ/ተቀለሰ ዞረ (ኹለተኛ መጣ - ፪ሳሙ. ፲፱፥፲፭) ።
ተመለሰ፡ ንስሓ ገባ።
ተመለሰ፡ ወጣ (መብል/መጠጡ በገበባት) ።
ተመለሰ፡ ገባ/ተከተተ (ተረት)፡ "ጥጃ ቢሳሳት ከናቱ፡ ሰይፍ ቢመለስ ካፎቱ"። (ግጥም)፡ "ካገሩ የወጣ አገሩ እስኪመለስ ሲጭኑት አህያ ቢለጕሙት ፈረስ"።
ተመለስ፡ በአርእስትና በኅዳግ የተጻፈ ቃል ምልክት ፲።
ተመለከ፡ ተሸነፈ፡ ተገዛ።
ተመለከ፡ አምላክ ኾነ፡ ተጸለየበት/ተሰገደበት።
ተመለከተ (ተመልከተ)፡ አየ/መረመረ/ፈተነ/ጐበኘ/ተረዳ/አስተዋለ/ጠበቀ (ተመለከተኝ አለኝ) (ዘፍ. ፴፩፥፵፱፡ ፩ሳሙ. ፳፬፥፲፯፡ መዝ. ፴፭፥፳፩፡ ማቴ. ፮፥፳፮፡ ዮሐ. ፩፥፴፱፡ ማር. ፲፪፥፴፬) ።
ተመለከተ (ተመልከተ)፡ አየ/አስተዋለ/ጠበቀ (ነገርን/መጻፍን/ፊትን - ያዕ. ፩፥፳፬) ።
ተመለከተ፡ ምልክት ኾነበት/ተደረገበት/ተጻፈበት (የዜማው መጻፍ) ።
ተመለካከተ፡ ምልክት ተቀባበለ/ተጠቋቈመ፡ "ያ የተነጋገርነው ምልክት ይኹንኸ" ተባባለ።
ተመለጠ፡ መላጣ ኾነ፡ ተላጠ/ተቀረፈ፡ ጠጕርና ቅርፊት ዐጣ።
ተመለጠነ፡ ታወቀ ድጓው፡ ተዜመ/ተመራ አንገርጋሪው።
ተመላ ።
ተመላ/ተሞላ (ተመልአ)፡ የቢሩ ተገብሮ ፍችው እንደ ተገብሮው ነው፡ ጢም ቲፍ አለ።
ተመላለሰ፡ ብዙ ጊዜ ወዲህ መጣ ወዲያ ኼደ (፩ሳሙ. ፴፥፴፩፡ ዮሐ. ፲፪፥፴፭፡ ገላ. ፭፥፲፮) ። ወጣ ገባ አለ።
ተመላለሰ፡ ተለዋወጠ።
ተመላለሰ፡ ተከፋፈለ (ብድርን) ።
ተመላለሰ፡ ተገላመጠ (ግራና ቀኝ አየ - ዘፀ. ፪፥፲፪) ።
ተመላለጠ፡ ተላላጠ/ተቀራረፈ።
ተመላላሽ፡ የተመላለሰ/የሚመላለስ (ደጀ ጠኒ) ።
ተመላሽ፡ የሚመለስ ሰው፡ የተውሶ ከብት/ዕቃ፡ እወጣበት የሚገባ ገንዘብ።
ተመላታ (ተመላትሐ)፡ ጕንጭን ተማታ/ተጻፋ።
ተመላከተ፡ ተያየ (ተመለከተ)
ተመላጐደ፡ ተማታ/ተናጐደ፡ ተነባጀለ (የሞኝ አነጋገር ተናገረ) ።
ተመላጭ፡ የሚመለጥ/የሚቀረፍ።
ተመልማይ፡ የሚመለመል (ተኰትኳች) ።
ተመልካች (ቾች)፡ የተመለከተ/የሚመለከት፡ አስተዋይ/ጠባቂ/እረኛ/ነቢይ/ዳኛ (፩ሳሙ. ፱፥፱, ፲፩, ፲፰-፲፱፡ ፪ዜና. ፴፫፥፲፱፡ ኢሳ. ፶፪፥፰) ። "የበዪ ተመልካች" እንዲሉ።
ተመልካች ሐሳብ፡ የማይለወጥ ምክር።
ተመልካች ሐሳብ፡ የማይለወጥ ምክር (ጥልቅ ምክር) ።
ተመልካች ሐሳብ፡ ጥልቅ ምክር።
ተመልካች ሐዘን፡ የማያቋርጥ ሐዘን (የዘለዓለም ዋይታ) ።
ተመልካች ሐዘን፡ የዘለዓለም ዋይታ (የማያቋርጥ ሐዘን) ።
ተመልካች ልብ፡ አስተዋይ ልብ።
ተመልካች ልብ፡ አስተዋይ ልብ ።
ተመልካች ልብ፡ ጥልቅ ልብ።
ተመልካች ልብ፡ ጥልቅ ልብ (አስተዋይ ልብ) ።
ተመልካች ምድር፡ የማትበቅል ምድር።
ተመልካች ምድር፡ የሞተች ምድር።
ተመልካች ምድር፡ የሞተች ምድር (የማትበቅል ምድር) ።
ተመልካች ሞት፡ የማያመልጡት ሞት።
ተመልካች ሞት፡ የዘለዓለም ሞት።
ተመልካች ሞት፡ የዘለዓለም ሞት (የማያመልጡት ሞት) ።
ተመልካች ሰይጣን፡ ፯ ራሶች ያሉት ሰይጣን።
ተመልካች ሰይጣን፡ ፯ ራሶች ያሉት ሰይጣን ።
ተመልካች ርኵሰት፡ የማትነጻ ርኵሰት (የዘለዓለም ጥፋት) ።
ተመልካች ርኵሰት፡ የዘለዓለም ጥፋት (የማትነጻ ርኵሰት) ።
ተመልካች ርኵስ፡ የማያምን ርኵስ (የረከሰ ርኵስ) ።
ተመልካች ርኵስ፡ የረከሰ ርኵስ (የማያምን ርኵስ) ።
ተመልካች ቍም፡ የማይንቀሳቀስ ቍም።
ተመልካች ቍም፡ የማይንቀሳቀስ ቍም (ጽኑዕ ቍም) ።
ተመልካች ቍም፡ ጽኑዕ ቍም።
ተመልካች ቍም፡ ጽኑዕ ቍም (የማይንቀሳቀስ ቍም) ።
ተመልካች ቍስል፡ የማያድን ቍስል።
ተመልካች ቍስል፡ የማያድን ቍስል።
ተመልካች ቍስል፡ የማያድን ቍስል (የማያገግም ቍስል) ።
ተመልካች ቍስል፡ የማያገግም ቁስል።
ተመልካች ቍስል፡ የማያገግም ቍስል።
ተመልካች ቍጣ፡ የማያልፍ ቍጣ (የዘለዓለም መዓት) ።
ተመልካች ቍጣ፡ የዘለዓለም መዓት (የማያልፍ መዓት) ።
ተመልካች ቍጣ፡ የዘለዓለም መዓት (የማያልፍ ቍጣ) ።
ተመልካች ቃል፡ የማያልፍ ቃል።
ተመልካች ቃል፡ ጽኑዕ ቃል ።
ተመልካች ቃል፡ ጽኑዕ ቃል (የማያልፍ ቃል) ።
ተመልካች ቃል፡ ጽኑዕ ቃልል።
ተመልካች ዐይን፡ አስተዋይ ዓይን ።
ተመልካች እሳት፡ የማትጠፋ እሳት።
ተመልካች እሳት፡ የዘለዓለም እሳት።
ተመልካች እሳት፡ የዘለዓለም እሳት (የማትጠፋ እሳት) ።
ተመልካች ኵነኔ፡ የማያልፍ ኵነኔ።
ተመልካች ኵነኔ፡ የዘለዓለም ኵነኔ።
ተመልካች ኵነኔ፡ የዘለዓለም ፍርድ (የማያልፍ ኵነኔ) ።
ተመልካች ኵነኔ፡ የዘለዓለም ፍርድ (የማያልፍ ፍርድ) ።
ተመልካች ኲናት፡ መርማሪ ፍርድ ።
ተመልካች ዘንዶ፡ ፯ ራሶች ያሉት ዘንዶ።
ተመልካች ዘንዶ፡ ፯ ራሶች ያሉት ዘንዶ ።
ተመልካች፡ የሚያይ/የሚመረምር/የሚፈትን/የሚጐበኝ/የሚረዳ/የሚያስተውል/ጠባቂ።
ተመልካች ገሃነም፡ የማትጠፋ ገሃነም (የዘለዓለም ሲኦል) ።
ተመልካች ገሃነም፡ የዘለዓለም ሲኦል (የማትጠፋ ገሃነም) ።
ተመልካች ጽናት፡ ጽኑዕ ጽናት (የማይለወጥ ጽናት) ።
ተመልካችነት፡ ተመልካች መሆን (አስተዋይነት/ጠባቂነት/እረኝነት) ።
ተመልክቶ፡ አስተውሎ። በግእዝ ግን መመልከት ይባላል።
ተመመ (ደመመ)፡ ድም ድም አለ...ጮኸ ናረ ተሰማ (በሩቅ ነጋሪቱ ጐርፉ - ኤር.
፴፩፡ ፴፭፡ ሕዝ. ፵፫፡ ፪) ።
ተመመ፡ ተጨረሰ ተቈላቈለ ።
ተመማ፡ ጩኸት ንረት (ኢዮ. ፴፯፡ ፪) ።
ተመሰ፡ ደበሰ ደመሰ ።
ተመሰለ፡ መሰለ/ተደረገ/ተገኘ።
ተመሰለ፡ መሰል/አምሳያ ኾነ (ኢሳ. ፲፬፥፲፬ - ይሥሐቅ በዔሳው ተመሰለ - ሰይጣን በብርሃን መልአክ ተመሰለ) ።
ተመሰለ፡ በጦርነት ጊዜ የንጉሥን የጦር ልብስ ለበሰ።
ተመሰለ፡ ተሣለ/ተቀረጸ/ተበጀ ምስሉ።
ተመሰለ፡ ተተረተ/ተነገረ ምሳሌው።
ተመሠረተ (ተመሥረተ)፡ ተጣለ/ተዠመረ/ተወጠነ/ተሠራ/ተበጀ/ተገነባ መሠረቱ (ማቴ. ፯፥፳፭) ።
ተመሰቃቀለ፡ ተዘበራረቀ/ተጠላላ/ተደበላለቀ/ተገለባበጠ ።
ተመሰተረ፡ ተነቀለ/ተለቀመ።
ተመሰከረ፡ ተነገረ/ታወቀ/ተረዳ ነገሩ።
ተመሰኳ፡ ተመነዠኸ/ተለነቀጠ/ላመ።
ተመሰገ፡ ገባ/ተሰካ/ተጨመረ ("እጄ ውስጥ እሾኽ ተመስገብኝ") ።
ተመሰገነ (ተመዝገነ)፡ ምስጋና አገኘ (ወሰው ተባለ/ተወደስ/ተሞገሰ - ዮሐ. ፲፫፥፴፩-፴፪) ። "ተመስገን ጌታዬ ከሞላ ጐታዬ" እንዳለ ገበሬ።
ተመሰጋገነ፡ ተወዳደሰ/ተሞጋገሰ (ምስጋና ተቀባበለ) ።
ተመሠጠ፡ ልቡ/ሰውነቱ ወደ ሰማይ ተነጠቀ/ተወሰደ/ወጣ።
ተመሰጠረ (ተመስጠረ)፡ መሰጠረ።
ተመሳ (ተመስሐ)፡ ተጐረሠ/ተበላ ምሳው።
ተመሳ (ተመስሐ)፡ ተጐረሠ/ተበላ ምሳው።
ተመሳሰለ፡ ተነጻጸረ/ተባበረ (በመልክ/በሥራ - ፩ነገ. ፫፥፲፪፡ ኢዮ. ፳፰፥፲፱) ።
ተመሳሰለ፡ እርስ በርሱ መሰለ/ተዋደደ/ተስማማ።
ተመሳሳይ (ዮች)፡ የሚመሰል።
ተመሳሳይ (ዮች)፡ የተመሳሰለ/የሚመሳሰል (ተነጻጻሪ/ተባባሪ) ።
ተመሳሳይነት፡ ተመሳሳይ መኾን (ተባባሪነት) ።
ተመሳቀለ፡ አራት ገጽ መስቀልኛ ኾነ (ራስጌና ግርጌው ሳይለይ ቀረ ተዘባረቀ ተጣላ) ።
ተመሳቃ፡ ተፈካከረ ("እኔን አንተ አታኽለኝም" አለ - ፩ሳሙ. ፩፥፮) ።
ተመሳቃይ፡ የሚመሳቀል/የሚጣላ ።
ተመሳከረ፡ ተመሰካከረ ("ታውቃለኸና ዕወቅልኝ በኔም ባታውቅብኝ" ከተባባለ በኋላ የምስክርን ቃል ሰማ) ።
ተመሳካሪ፡ የሚመሳከር።
ተመሳጠረ፡ ተራቀቀ (በምስጢር/በስውር/በድብቅ ተነጋገረ/ተጨዋወተ - ለደግም ለክፉም ይነገራል።)
ተመሳጣሪ፡ የተመሳጠረ/የሚመሳጠር (ምስጢረኛ) ።
ተመሳጣሪነት፡ ተመሳጣሪ መኾን።
ተመስማሳ/ትምስምስ፡ የተትመሰመሰ...የሚትመሰመስ (ርብትብት) ።
ተመሥራች፡ የሚመሠረት/የሚወጠን።
ተመስካሪ፡ የሚመሰከር/የሚነገር።
ተመስገ፡ ተሰበሰበ/ተከማቸ/ተኛ።
ተመስገን፡ የሰው ስም ("ክብርኸ ይስፋ መንግሥትኸ ይባረክ") ።
ተመስጋኝ፡ የሚመሰገኝ (ጻድቅ) ።
ተመሥጦ፡ መነጠቅ (ወደ ላይ ማረግ የልብ/የኅሊና) ።
ተመረመረ፡ ተጠየቀ/ተፈተነ/ተፈተሸ (ጭምጭምታው ተሰማ ያለበት ታወቀ፡ ተቈፈረ/ጐደጐደ) ።
ተመረረ፡ ተጠቃ/ዐዘነ/ተበሳጨ (ሕዝ. ፳፯፥፴) ።
ተመረቀ፡ ተቀቀለ/በሰለ (መረቅ ኾነ) ። (ግጥም)፡ "ኹል ጊዜ በሥጋት እዱር ከመኖር ቆቅስ ብትመረቅ ይሻላት ነበር"።
ተመረቀ፡ ተባረከ (ንባብን/ዜማን/ቅኔን/ትርጓሜን የማስተማር መብት አገኘ) ። ማኅበር ደጋሽ እመሬት ወድቆ ምርቃት ተቀበለ ("የራቀውን ያቅርብልኽ የቀረበውን ያሰናዳልኽ በክብር ያንሣኽ" ተባለ) ። (ተረት)፡ "ተመርቂያለኹ ብለኸ ከተረገመ አትዋል"።
ተመረነ፡ ተያዘ/ተወሰነ/ታሰረ/ተጠመጠመ/ተቈራኘ።
ተመረኰዘ (ተመርጐዘ)፡ ምርኵዝ ያዘ/ጨበጠ/ተደገፈ።
ተመረኰዘ...ተደገፈ (ምርኵዝ በቁሙ፡ ማረ) ።
ተመረዘ፡ ክፉ ፈሳሽ መርዝ ገባበት/በመርዝ ተወጋ/ተጠላ/ተተኰረ።
ተመረገ (ተመርገ)፡ ተለጠፈ/ተደፈነ (ግድግዳው/ግንቡ በጭቃ) ።
ተመረገደ፡ ተዜመ/ተባለ መረግዱ።
ተመረጠ፡ ተወደደ/ተለየ/ተመለመለ።
ተመሪ (ተመራሒ)፡ የሚመራ (ዕውር/መሬትን/ቅኔን/ዜማን ተቀባይ) ።
ተመሪነት፡ ተመሪ መኾን።
ተመሪዎች፡ የሚመሩ (ደብተሮች/ሕዝቦች - ኢሳ. ፱፥፲፮) ።
ተመራ፡ ቅኔን/ዜማን/ቀላድን ተቀበለ።
ተመራ፡ በመሪ ኼደ (ዕውሩ/ውሃው) ።
ተመራ፡ በሰው ቤት ዐዶረ (እንግዳው/ወታደሩ) ።
ተመራመረ (መረመረ)፡ ተጠያየቀ/ተፈላለገ/ተሳለለ። "ኣብርሃም በፀሓይ ተመራምሮ እግዜርን አመነ"። "ጌታዬ ማረኝ አትመራመረኝ" እንዲል ባላገር። (ማረ ብለኸ ተማረንን አስተውል) ።
ተመራማሪ፡ የተመራመረ/የሚመራመር (ተሳላይ) ።
ተመራማሪነት፡ ተመራማሪ መኾን።
ተመራረቀ፡ ተበራረከ (የምርቃት ብድር ተመላለሰ) ።
ተመራሪ፡ የሚመረር (ተቈጪ) ።
ተመራራ፡ ማደሪያን/መሬትን ተቀባበለ።
ተመራቂ፡ የሚመረቅ (ምርቃት ተቀባይ) ።
ተመራዥ፡ የሚመረዝ/የሚጠላ።
ተመራጊ፡ የሚመረግ ቤት።
ተመራጭ (ጮች)፡ የሚመረጥ/የሚመለመል።
ተመርማሪ፡ የሚመረመር (ተጠያቂ) ።
ተመርጋጅ፡ የሚመረገድ።
ተመሸን፡ ተመነሸ። መንሽን ተመልከት።
ተመሸገ፡ ታጠረ/ተከበበ/ተቀጠረ/ተካበ (ተማሰ/ታረደ/ተጐደበ - ዘኍ. ፲፫፥፲፱፡ ፪ሳሙ. ፳፬፥፯) ።
ተመሸጠ፡ ተለጠሰ/ተኛ።
ተመቀሰ፡ ተቈረጠ/ተቀደደ በመቀስ።
ተመቀኘ (ሐመመ)፡ ቀና/ምቀኛ ኾነ (ሰውን ለመጕዳት/ለማጥፋት) ።
ተመቀኛኘ፡ ተቀናና (ምቀኛ ተኳዃነ) ።
ተመቃኘ፡ ተቃና።
ተመተመ (ተመመ)፡ መታ ለተመ...ገጫ ወጋ ።
ተመተመ፡ በእጅ አባበለ (ሕፃንን በቅሎን ፈረስን) ።
ተመተመ፡ አበሰለ አመጠጠ (እሳትንፍሮን) ።
ተመተመ፡ እረመደ ።
ተመተመ፡ ዝም በል ኣትናገር አለ (አንዱ የሥጋ ቤት ባልደረባ ባቡጀዲ የተሸፈነ ሥጋ ሰርቆ ሲኼድ ዐፄ ምኒልክን እሰገነት ላይ ቆመው ቢያያቸው "አፉን በእጁ ተመተመ" እሳቸውም ሣቁና ኺድ አሉት) ።
ተመተመ፡ ደመደመ አስተካከለ ልጥ...ፍን በጭድ ።
ተመታ፡ ተቀጠቀጠ (ዘፀ. ፴፯፥፯) ።
ተመታ፡ ተበጠበጠ/ተለቀ።
ተመታ፡ ተባለ/ተጠዘለ/ተወገረ/ተደበደበ/ተመደወተ/ተገረፈ (ተረት፡ "ባወጣው ዳኛ ተረታ በያዘው በትር ተመታ") ።
ተመታ፡ ተወጋ/ተገደለ/ተሸነፈ (ሕዝ. ፴፫፥፳፩) ።
ተመታች፡ ተሰረረች ፈረሲቱ።
ተመቸው፡ ደላው/ተስማማው።
ተመቺ (ቾች)፡ የሚመታ/የተወጋ/ድል የኾነ (ዘዳ. ፳፰፥፯, ፳፭፡ ኢያ. ፰፥፲፭፡ ፲፩፥፮) ።
ተመቻቸ፡ ተደላደለ/ተሸራሸ/ተተካከለ/ተሰማማ።
ተመች፡ ተረታኹ/አነሣኹ ("በል የተመች" - የተረታ ሰው ለፍርድ ስለ መመቸቱ የሚከፍለው ትርፍ ዕዳ - ይህ ቋንቋ በሐረርጌ ይነገራል) ።
ተመችቶታል፡ ደልቶታል/ኾኖታል/ተቀብሎታል) ።
ተመነሸ (ተመሸነ)፡ መንሽ ተባለ።
ተመነሸ፡ ተወጋ/ተወረወረ።
ተመነቀ፡ ተነቀነቀ/ተወዘወዘ።
ተመነተገ፡ ተቀማ/ተነጠቀ።
ተመነተፈ፡ ተቀማ/ተነጠቀ።
ተመነቸከ፡ ተጨቀጨቀ/ተነዘነዘ።
ተመነነ፡ ተናቀ/ተተወ።
ተመነዘረ፡ ተሴሰነ/ተቀነዘረ/ተሸረሞጠ።
ተመነዘረ፡ ተዘረዘረ/ተበተነ/ተሸረፈ/ተከፈለ።
ተመነዛዘረ፡ ተበታተነ/ተለዋወጠ።
ተመነዠኸ፡ ታኘከ/ተመሰኳ/ላሙ ለዘበ/ተለነቀጠ።
ተመነደለ፡ ታጠበ/ጠራ።
ተመነደረ፡ ታነጠ/ተገነባ/ተሠራ (መንደሩ/ዐምባው) ።
ተመነደበ (ተመንደበ)፡ ተመታ/ተነረተ/ተደበደበ።
ተመነደበ፡ ተቈረጠ/ተመደመደ።
ተመነደበ፡ ተቸገረ/ተጨነቀ (መከራ ተቀበለ) ።
ተመነደገ፡ ተነጠቀ/ተቀማ።
ተመነደገ፡ አደገ/ረዘመ።
ተመነገለ፡ ነገለ።
ተመነገገ፡ ተያዘ/ታሰረ (ከብቱ መንጋጋው) ።
ተመነጠረ፡ ተጠረገ/ታጨደ/ታጠበ/ተገረፈ። (ተረት)፡ "ያልጠረጠረ ተመነጠረ"።
ተመነጠቀ፡ ተነጠቀ/ተቀማ።
ተመነጠቀ፡ ወጣ ቶሎ ኼደ።
ተመነጨረ፡ ተጫረ/ተበተነ።
ተመነጨቀ፡ ተጨቀጨቀ/ተነዘነዘ/ተመነጠቀ።
ተመነጫጨረ፡ ተበታተነ።
ተመናሸ፡ ተዋጋ፡ መንሽ ።
ተመናሸ፡ ተዋጋ/ተወራወረ።
ተመናተገ፡ ተቃማ/ተናጠቀ።
ተመናተፈ፡ ተቀማ/ተናጠቀ። (ተረት)፡ "አሳግርቶች እንመናተፍ ካላችኹ እንመናተፍ"።
ተመናቸከ፡ ተጨቃጨቀ/ተነዛነዘ።
ተመናኘ፡ በገፍ ተሰጣጠ (እንደ ልብ ተዳደለ ተቀባበለ) ።
ተመናኘ፡ ያላሳብ ተዳደለ ናኘ ።
ተመናዘረ፡ ገንዘብ ለገንዘብ ተላወጠ።
ተመናደበ፡ ተማታ/ተቋረጠ።
ተመናጐለ፡ አስቀያሚ ነገር ተናገረ! ተነኋረጠ።
ተመናጠረ፡ ተጣረገ/ተወደደ/ተጋረፈ።
ተመናጠቀ፡ ተናጠቀ/ተቃማ።
ተመናጨረ፡ ተባተነ።
ተመናጨቀ፡ ተመናትከ/ተጨቃጨቀ።
ተመን፡ ዘንዶ (ግእዝ) ።
ተመንዛሪ፡ የሚመነዘር ብር።
ተመንጣሪ፡ የሚመነጠር (ታጫጅ) ።
ተመኘ (ተመነየ)፡ ዐሰበ/ከጀለ (በልቡ ፈለገ፡ ባገኘኹት አለ - ፩ዜና. ፲፩፥፲፯) ።
ተመኛኘ፡ ተከጃጀለ።
ተመኝ፡ የሚመኝ (ከጃይ) ።
ተመኝ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም፡ "ኣባት የተመኘውን ልጅ አገኘ" ማለት ነው።
ተመከ፡ ላይ ተሰደ ተሠረጐደ (ሥዕል ተቀበለ ታተመ) ።
ተመከመከ፡ ላላ፡ ለሰለሰ።
ተመከረ (ተመክረ)፡ ኾነ/ተደረገ (ተዶለተ/ተሤረ/ታደመ)፡ ምክሩ/ምክር ተቀበለ ሰውየው።
ተመከረበት፡ ጕዳዩ እንዲፈጸም ጥፋተኛው እንዲቀጣ ተደረገበት።
ተመከተ፡ ተቀየደ፡ ተጋረደ፡ ተከለለ (የቤቱ ውስጥ፡ ሰዉ ጋሻው) ።
ተመከኛኘ፡ የሠራኸው አንተ ነህ/አንተ ነህ ተባባለ።
ተመኪ፡ (ተመካሒ)፡ የሚመካ፡ ተከባሪ ።
ተመኪዎች፡ ተመኮች፡ የሚመኩ ("፪ጢሞ. ፫፡ ፪") ።
ተመካ፡ (ተመክሐ)፡ ካለ፡ እከሌ፡ እኔን፡ ማን፡ ያኸለኛል፡ አለ፡ በገዛ፡ አፉ፡ ተወደሰ፡ ራሱን፡ አከበረ፡ ("ኢሳ. ፲፡ ፲፭") ።
ተመካ፡ ባንድ ነገር ታመነ (መካ) ።
ተመካሪ፡ የሚመከር።
ተመካች፡ የሚመከት፡ ተቀያጅ።
ተመካኘ (ተመክነየ)፡ ተፈጠረ፡ ኾነ፡ ተደረገ (ምክኛቱ)፡ ተሰበበ፡ ተላከከ።
ተመካኘ፡ ተደረገ (ምክንያቱ...ከን) ።
ተመካከረ፡ ምክር ተለዋወጠ (መዝ. ፻፴፫፥፪፡ ዕብ. ፫፥፲፫) ።
ተመካከተ፡ ተገራረደ።
ተመክሮ፡ መመከር (ግእዝ) ። ተፈጥሮን ተመክሮ አይመልሰውም።
ተመዘመዘ፡ ራስ፡ ረሰረሰ ።
ተመዘመዘ፡ ቀጠነ፡ ረዘመ። ይህ፡ መኰንን፡ ጠጅ፡ ስላበዛ፡ ጥርሱ፡ ተመዝምዟል ።
ተመዘመዘ፡ ተተለተለ፡ ተተረተረ፡ ተሳበ፡ ተመዘዘ።
ተመዘቀ፡ ተነቀለ።
ተመዘበረ፡ (ተመዝበረ)፡ ፈረሰ' ተናደ፡ ባድማ፡ ኾነ፡ ጠፋ፡ ተፈታ።
ተመዘነ፡ ተለካ፡ ተሰፈረ፡ ተመጠነ፡ ዕቃው፡ ተገመተ፡ ጠባዩ፡ ("፩ሳሙ. ፪፡ ፫") ።
ተመዘዘ፡ ተሳበ፡ ተጐተተ፡ ተነቀለ፡ ወጣ ።
ተመዘዘ፡ ተፈተለ፡ ቀጠነ ።
ተመዘዘ፡ አደገ፡ ረዘመ፡ ተመነደገ ።
ተመዘገበ፡ ተጻፈ/እመዝገብ ገባ ።
ተመዛኝ፡ የሚመዘን፡ ተለኪ ።
ተመዛዘነ፡ በሚዛን፡ ተተካከለ፡ ተመጣጠነ፡ ከመበላለጥ፡ ራቀ፡ ተለዋወጠ ።
ተመዛዘዘ፡ ተነቃቀለ።
ተመዛዘዘ፡ ተነቃቀለ።
ተመዛዛኝ፡ የሚመዛዘን ።
ተመዛዥ፡ የሚመዘዝ፡ ተነቃይ ።
ተመዝማዥ፡ የሚመዘመዝ ።
ተመዠረጠ፡ ተነቀለ፡ ተመዘዘ፡ ወጣ።
ተመየደ; ተበጠረ፡ ተነቀሰ።
ተመይ፡ የሚመላ።
ተመደመደ፡ ተቈረጠ፡ ተጠረገ፡ ተናደ፡ ፈረሰ፡ ተደለደለ፡ ተተካከለ።
ተመደነ፡ ተማረ፡ ሠለጠነ።
ተመገ፡ ልል ኾነ ተመከ ።
ተመገመገ፡ ተሳበ፡ ተጐተተ፡ ተጠባ፡ ተመጠመጠ፡ ተለገለገ።
ተመገዘ፡ (ተገዝዐ፡ ተወሠረ)፡ ተገዘገዘ፡ ተከረከረ፡ ተከረከመ፡ ተቈረጠ፡ ተሠነጠቀ።
ተመጋዥ፡ የሚመገዝ፡ ተከርካሪ።
ተመጠመጠ፡ ተሳበ፡ ተጠባ፡ ጠቢ ።
ተመጠቀ፡ መጠቀ።
ተመጠነ፡ ተለካ፡ ተመዘነ፡ ("፩ነገ. ፫፡ ፰") ።
ተመጠወተ፡ ተመጸወተ፡ ተሰጠ፡ ታደለ፡ ምጧቱ ።ተሰጠው፡ ተቀበለ፡ ሰዉ።
ተመጠጠ፡ ተሳበ፡ ተጐተተ፡ ተጠጣ፡ ተመለጠ ።
ተመጣ፡ ወደዚህ፡ ተደረሰ፡ ኾነ፡ ተደረገ፡ መምጣቱ።
ተመጣኝ፡ የሚመጠን፡ የሚለካ ።
ተመጣደቀ፡ ተመጻደቀ ።
ተመጣዳቂ፡ ተመጻዳቂ ።
ተመጣዳቂነት፡ ተመጻዳቂነት ።
ተመጣጠነ፡ ተለካካ፡ ተመዛዘነ።
ተመጣጣኝ፡ የሚመጣጠን፡ ተመዛዛኝ ።
ተመጣጭ፡ የሚመጠጥ።
ተመጥዋች፡ ተመጽዋች፡ የሚመጠወት፡ ገንዘብ፡ የሚቀበል፡ ሰው ።
ተመጨለሰ፡ ሣሣ፡ ብራ፡ ኾነቅባት፡ በነካው፡ ጊዜ፡ ተለጠሰ፡ ተኛ፡ ተለጠፈ ።
ተመጻደቀ፡ "እኔ እከሌ ' አለ" (ተገበዘ በገዛ አፉ ተመሰገነ ወይም ተመሰጋገነ ") ። በመ ምክንያት ተደራጊ፡ በጻ ምክንያት ተደራራጊ መኾኑን አስተውል ።
ተመጻደቀ፡ በገዛ አፉ ተመሰገነ፡ ጸደቀ ።
ተመጻዳቂ (ቆች)፡ የተመጻደቀ/የ ሚመጻደቅ (ግብዝ ኣፈ ጻድቅ ሰዱቃዊ ፈሪ ሳዊ ") ።
ተመጻዳቂነት፡ ግብዝነት ።
ተሙለጨለጨ፡ አልያዝ/አልረገጥ አለ።
ተሙን (ዐረ. ሱሙን)፡ የገንዘብ ስም (የዱሮ መሐልቅ አላድ ሳይመጣ የነበረ - ባንድ ብር ኹለት ይመነዘራል - የብር ስምንተኛ ማለት ነው - መሐልቅም በተሙን ፈንታ ስለ ተተካ "ተሙን" ይባላል - ማስረጃ) ።
ተሙን፡ ተቤሳ ፩ መሐልቅ ካ፩ ቤሳ ።
ተማለ፡ ኾነ/ተደረገ፡ ማለው እንዲህ ያድርገኝ/እንዲህ ይጨምርብኝ ተባለ (፩ሳሙ. ፳፭፥፳፪፡ ፩ነገ. ፲፱፥፪) ።
ተማለለ (ተማሕለለ)፡ ተረሳ/ተዘነጋ።
ተማለለ፡ ለመነ/ልመና ያዘ/ጸለየ (ሮሜ. ፩፥፲) ። "አህያ ተማሎ ዥብ አወረደ" እንዲሉ።
ተማለደ፡ ተለመነ፡ "ይቅር አለ" ተባለ፡ ምሕረት አገኘ፡ ዳነ (ኢዮ. ፳፪፥፳፱) ።
ተማላ (ተማላዒ)፡ ሲኼድ ይዞ ኻያጅ (እንደ ተማላ ወሰደው እንዲሉ) ።
ተማላ፡ ተተካከለ።
ተማላ፡ ተያያዘ፡ አንድነት ኾነ (ተኳዃነ)
ተማላይ፡ የተማለለ/የሚማለል።
ተማላጅ፡ የተማለደ/የሚማለድ፡ ተለማኝ እግዜር።
ተማመሰ (ተሓመሰ)፡ ተተረማመሰ ።
ተማመቸ (ተሓመወ)፡ ተጋባ ("ዐማ ችና ዐማት ተኳዃነ ተዛመደ" - ዕዝ. ፱፥፲፬) ።
ተማመነ፡ (ተኣመነ)፡ ተዋደደ፡ ተሰማማ፡ ተማማለ፡ አዎን፡ ተባባለ። ማለ፡ ብለኸ፡ ተማማለን፡ እይ።
ተማመፀ፡ ተበዳደለ ።
ተማሚ (ተሓማዪ)፡ የሚተማማ (ተነ
ተማሚ፡ የሚተም ("ዐማ" ብለኸ "ተማማን" አስተውል) ።
ተማማ (ተሓመየ)፡ ተነቃቀፈ ።
ተማማለ (ተማሐለ)፡ የማላ ብድር ተከፋፈለ፡ (ዛሬ አንዱ ነፃ ሌላው ማለ)፡ ሳንቃ ተዛጋ፡ በመማማል ተፈራረቀ/ተገዛዘተ (መዝ. ፻፪፥፰) ። የማይተማመን ባልንጀራ በየወንዙ ይማማላል።
ተማማለ፡ ተሢያሢያረ/ተደማደመ (፩ነገ. ፲፭፥፳፯፡ ፲፯፥፱፡ ፪ነገ. ፱፥፲፬) ።
ተማማለ፡ ክፉ እንዳይሠራ ተዋዋለ/ተማመነ (ዘፍ. ፳፮፥፴፩፡ ፩ሳሙ. ፲፰፥፫፡ ኢሳ. ፳፰፥፲፭, ፲፰) ።
ተማማረ (ተማሐረ)፡ "ይቅር ይቅር" ተባባለ።
ተማማረ (ተማሀረ)፡ ትምርትን ተቀባበለ ("ተማሪው ካስተማሪው አስተማሪው ከተማሪው ተማረ" ማለት ነው) ።
ተማማኝ፡ የሚተማመን፡ የሚዋደድ።
ተማም (ዐረ)፡ ልክ ትክክል ፍጹም ።
ተማም፡ ተመተመ፡ ባለዋሻ ።
ተማሰ፡ ተኳተ/ተቈፈረ/ታረሰ/ተጐደፈረ/ጐደጐደ (ዘዳ. ፰፥፱፡ ሉቃ. ፲፪፥፴፱) ።
ተማሰለ፡ ተገላበጠ/ተቀላቀለ/ተደባለቀ/ተዋሐደ (አንድ ኾነ) ።
ተማረ (ተምሕረ)፡ ይቅርታ አገኘ/ተተወ/ተለቀቀ።
ተማረ፡ ሲያውቅ አበደ/ዞረ። (ተረት)፡ "የተማረ ተማረ"።
ተማረ፡ ጦርነት ተዣመረ/ተፋተነ ተቈራቈሰ ("ነገር ተፈላለገ") ።
ተማረረ፡ ተጣላ/ተቋጣ/ተነፋፈረ/ተባባሰ (ነጻጸረ) ።
ተማረተ፡ ተጣላ/ተፋጀ/ተከራከረ/ተሳደበ (ፍሬ ከገለባ እንዲለይ ባሳብ በነገር ተለያየ) ።
ተማረከ (ተማህረከ)፡ እጠላት እጅ ገባ/ተያዘ/ተዘረፈ/ተበዘበዘ/ተወሰደ (ኢሳ. ፭፥፲፫) ።
ተማረክ፡ እጅህን ስጥ ተያዝ።
ተማራ፡ ተያይዞ ኼደ ("መንገዱ ይህ ነው" ተባባለ/ተጓተተ) ። "ዕውር ለዕውር ቢማራ ኹለቱም ገደል ይገባሉ"።
ተማራኪ፡ የሚማረክ።
ተማሸ፡ ጊዜው ተላለፈ።
ተማሽ፡ የሚማስ (ቦረቦር) ።
ተማተመ፡ ለታተመ ።
ተማተበ (ተማዕተበ)፡ ተመሳቀለ (ተባረከ ") ።
ተማታ፡ መታ (አድራጊ) ።
ተማታ፡ ተሸናቈጠ/ተጋፈ (ተደራራጊ) ረፍ።
ተማታ፡ ተባባለ/ተደባደበ/ተጋጨ (ናሆ. ፪፥፬) ።
ተማቹ፡ የሰው ስም።
ተማች፡ መቺ/የሚማታ (ዱለኛ) ።
ተማችነት፡ ተማች መኾን (ዱለኛነት) ።
ተማከረ፡ ከወዳጁ/ከሚስቱ ምክር ተካፈለ።
ተማከተ፡ ተካለለ።
ተማካሪ፡ የሚማከር።
ተማወቀ፡ ተጝቀ።
ተማዘነ፡ ተላካ፡ ትክክል፡ ተኳዃነ፡ ተናሣ ።
ተማዘዘ፡ ተናቀለ፡ ተዋጣ ።እከሌና፡ እከሌ፡ ተጣሉና፡ ሰይፍ፡ ተማዘዙ።
ተማዘዘ፡ ተናቀለ፡ ተዋጣ ።እከሌና፡ እከሌ፡ ተጣሉና፡ ሰይፍ፡ ተማዘዙ።
ተማዘዘ፡ ዘር፡ ተቋጠረ።
ተማዘዘ፡ ዘር፡ ተቋጠረ።
ተማዛኝ፡ የሚማዘን።
ተማገዘ፡ ተገዛገዘ ።
ተማገደ፡ ተጨመረ፡ ገባ፡ ተዶለ፡ ተጋፈጠ ።
ተማጋች (ቾች)፡ የተገተ፡ የሚገት፡ ተነጋጋሪ፡ ተከራካሪ፡ ጠበቃ፡ ነገረ፡ ፈጅ፡ የነገር፡ አባት፡ የዋስ፡ ተጋች፡ የቈማጣ፡ ፈትፋች፡ እንዲሉ ።
ተማጋችነት፡ ተጋች፡ መኾን፡ ጥብቅና ።
ተማጋጅ፡ የሚማገድ።
ተማጠ፡ ዕሕ' ተባለ፡ ወደ፡ ታች - ተገፋ ።
ተማጠነ (ተማሕፀነ)፡ ሸሸ ' ገዳም' ገባ (ተጠጋ ደወለ - ካህናት ግን ተማፀነ ይ ላሉ - ፩ነገ. ፪፥፳፰) ።
ተማጠነ ,—ተጠጋ፡ ከሰሰ' ዐጠነ፡ (ሐፀነ)
ተማጠነ፡ ተላካ፡ ተማዘነ።
ተማጠነ፡ ተጠጋ ዐጠነ ።
ተማጠነ፡ ከሰሰ ("ሰው ይማጠንኻል" እንዲሉ) ።
ተማጠነ፡ ይግባኝ ይሰማልኝ አለ ("ካህናት ግን ተማፀነ ይላሉ" - ግብ. ሐዋ. ፳፭፥፳፩) ።
ተማጠጠ፡ ከጭቃ፡ ላይ፡ ውሃን፡ ተሻማ ።
ተማጣ፡ ተሸካከመ፡ ተጋጋዘ።
ተማጣኝ፡ የተማጠነ/የሚማጠን (ተጠጊ የሙጥኝ ባይ ደዋይ ከሳሽ ") ።
ተማጣጭ፡ የተማጠጠ፡ የሚማጠጥ፡ ጥም፡ የያዘው፡ ከብት።
ተማጯ፡ ተፋቀ፡ ተፈገፈገ፡ ተጠረገ፡ ጸዳ ።
ተም፡
ተምለገለገ፡ ተሙለጨለጨ።
ተምለግላጊ፡ የሚምለገለግ።
ተምሳሊት (ተመሳሊት)፡ የምትመስል።
ተምሳሊት፡ ምሳሌ/አምሳል/አምሳያ።
ተምሳሊት ብዙ፡ አትኮኝ የለሽ።
ተምር (ሮች)፡ የዘንባባ ዐይነት ዛፍ (ጣፋጭ ፍሬ ያለው ቤቴ ዘንባባ - ዕንጨቱም ፍሬውም "ተምር" ይባላል) ።
ተምሸከሸከ፡ ተበጣጠሰ፡ (መ...ሸከ) ።
ተምሸከሸከ፡ ተበጣጠሰ/ተቈራረጠ/ተሰባበረ ("እንጀራው ከምጣድ ሲወጣ ተምሸከሸከ (ተሰባበረ)") ።
ተምተም፡ ችኰላ ፍጥነት ተፍተፍ ።
ተምተም አለ፡ ቸኰለ ፈጠነ (በብዙ ስፍራ ፈለገ ተፈተፈ - አተማተም ኣለታተም መተምተም) ።
ተምታሚ (ዎች)፡ የተመተመ/የሚ...ተመትም (ለታሚ ደምዳሚ) ።
ተምታታ፡ ተፋጀ/ተሸበረ/ተጯጯኸ።
ተምትሜ፡ የሰው ስም ።
ተምትም፡ ለትም ግጭ ።
ተምች (ቾች)፡ ጥቍር ትል (በር...ኖሴ የጤፍ ፀር) ።
ተምች፡ መታ ብዙውን ሰው እንዴ ("ተምች ባንድ ጊዜ ደበደበ ገደለ") ።
ተምነሸነሸ፡ ተሸለሙ/አጌጠ/ተጌጠ/ተሽሞነሞነ።
ተምዘገዘገ፣ ተውዘገዘገ።
ተሞለሞለ፡ ክብ ኾነ/ተጋገረ ሙልሙል።
ተሞለሰሰ፡ ተነቀለ/ተነጨ።
ተሞለቀቀ፡ ተዛቀ/ተነቀለ።
ተሞላቀቀ፡ ተናቀለ/ተጋፈፈ።
ተሞላቀቀ፡ ተንደላቀቀ/ተቀማጠለ/ተንቀባረረ (ባለገ)
ተሞላቃቂ፡ የሚሞላቀቅ (ተንቀባራሪ) ።
ተሞላጀጀ፡ ተንሰዋለለ።
ተሞላፈጠ፡ ተሞዣለጠ።
ተሞረሞረ፡ ሾለ/ሞጠሞጠ።
ተሞረሞረ፡ ተቦረቦረ (ሆዱ ባዶ ኾነ) ።
ተሞረደ፡ ተፈገፈገ/ተዘረዘረ/ተሳለ/ለዘበ።
ተሞራረተ፡ የርት ብድር ተከፋፈለ ርት።
ተሞራረደ፡ ተፈጋፈገ/ተዘራዘረ።
ተሞራጅ፡ የሚሞረድ (ተዘርዛሪ) ።
ተሞሸለቀ፡ ታጨደ/ተላጨ/ተላጠ/ተገፈፈ/ተቃጠለ/ተሰረቀ።
ተሞሸረ፡ ለመ ማዕርግ አየ (እጒላ ቤት ገባ/ተከተተ) ።
ተሞሸረ፡ ሙሽራ ኾነ/አጌጠ/ተሸለመ።
ተሞሸረ፡ ተጠቀለለ/ተሸበለለ (ውሳጣዊ/ውስጠኛ ኾነ) ።
ተሞሻሪ፡ የሚሞሸር/የሚሸበለል።
ተሞኘ፡ ተደለለ/ተታለለ/ጀለ/ቄለ/ተሸነገለ።
ተሞኛኘ፡ ተዳለለ/ተሸናገለ።
ተሞከረ (ተመከረ)፡ ተፈተነ/ተዠመረ/ተበገረ። ተመከረ ግእዝኛ ነው።
ተሞከተ፡ ተወቀጠ/ተቀጠቀጠ፡ ተቀለበ/በላ/ሠባ ሙክት ኾነ።
ተሞካሪ፡ የሚሞከር፡ ተበጋሪ።
ተሞካች፡ የሚሞከት/የሚሠባ።
ተሞካከረ፡ ተፈታተነ።
ተሞወረ፡ ተጫጫረ፡ ተቦጫጨረ፡ ተበለሻሸ፡ ጽፈቱ።
ተሞዘቀ፡ ተመታ፡ ተከረከረ።
ተሞዠቀ፡ ተወረ፡ ተጠረገ፡ ተበጠረ፡ ተፈገፈገ፡ ተዠደረገ ።
ተሞዣለጠ፡ ተላፋ፡ ተሞላፈጠ፡ ሥራ፣
ተሞዣለጠ፡ ተላፋ፡ ተሞላፈጠ፡ ሥራ፣
ተሞዳሞደ፡ ተደማደመ፡ ውስጥ፡ ለስጥ፡ ተመካከረ ።
ተሞጀረ፡ ተጨመረ፡ በዝቶ፡ ገባ፡ ተዶለ።
ተሞገተ፡ ተነዘነዘ፡ ተጨቀወቀ፡ ተነተረከ፡ ተጠየቅ፡ ተባለ ።
ተሞገደ፡ በዝቶ፡ ተማገደ፡ ተዠገደ።
ተሞገደ፡ ተወገጠ፡ ታወከ።
ተሞጋች፡ የሚሞገት፡ የሚጠየቅ።
ተሞጨለፈ፡ ተሰረቀ፡ ተነጠቀ፡ ተቀማ፡ ተወሰደ ።
ተሰለለ፡ ታየ፡ ተገመተ፡ ተመረመረ፡ ተጐበኘ።
ተሰለመጠ፡ ተዋጠ/ተሰለቀጠ።
ተሠለሰ፡ ፫ ጊዜ ታረሰ/ተቀበቀበ/ ታየመ/ለሰለሰ ።
ተሠለሰ፡ ሦስት ኾነ ተባለ።
ተሠለሰ፡ ተመሰገነ (ምስጋና ተቀበለ) ።
ተሰለቀ፡ ቀስ ብሎ ኼደ/ተቈነነ።
ተሰለቀጠ፡ ተዋጠ (ወደ ሆድ ወረደ) ።
ተሰለበ፡ በርቀት ተወሰደ፡ ዐለቀ። "ዥብ ምንም አንድ እግሩ ዐጪር ቢኾን መንገድ ይሰለብለታል።"
ተሰለበ፡ ተቈረጠ፡ ተጐመደ፡ ተጝደደ (ዘዳ. ፳፫፡ ፩).
ተሰለበ፡ ተገፈፈ፡ ተነሣ።
ተሰለቸ፡ ተጠገበ፡ ተጠላ፡ ተፈላጊ ሳይኾን ቀረ፡ ተነቀፈ ("ማር ሲበዛ ይመራል" እንዲሉ) ።
ተሰለቻቸ፡ ተጠጋገበ/ተጠላላ።
ተሰለፈ፡ ሰይፍ ታጥቆ/ወንጭፍ/ቀስት/ጠመንዣ ጨብጦ/ጋሻ አንግቦ/ጦር ይዞ ተራ መታ/ተሰደረ/ተደረደረ/ቆመ ።
ተሰለፈ፡ ተደቀነ/ተደከረ።
ተሰላ፡ ታሰበ፡ ተቈጠረ።
ተሰላለመ፡ ሰላምታ ተሰጣጠ/ተቀባበለ ("እንዴት ዐደርኸ/ዋልኸ/ሰነበትኸ?" ተባባለ/ተሳሳመ) ።
ተሰላለበ፡ ተጐማመደ።
ተሰላለፈ፡ ተቀራረበ (አንጸር ለአንጻር/ፊት ለፊት ተቋቋመ) ።
ተሰላላፊ፡ የሚሰላለፍ/የሚቀራረብ።
ተሠላሽ፡ የሚሠለስ/የሚታየም።
ተሰላቀጠ፡ ተሰለቀቀጠ/ተዋዋጠ።
ተሰላቂ፡ የሚሰለቅ (ለዛቢ) ።
ተሰላቸ፡ ተጣገበ/ተጣላ።
ተሰላይ፡ የሚሰለል (ተጐብኚ) ።
ተሰላፊ (ፎች)፡ የሚሰለፍ (ተደርድሮ የሚቆም ሐርበኛ/ቀስተኛ/ጦረኛ/ነፍጠኛ/ዘማች) ።
ተሰመለ፡ ተዠለጠ/ለፋ/ለሰለሰ፡ ተላገ/ተፋቀ/ለዘበ ።
ተሰመሰመ፡ ተቃመ/ተበላ።
ተሰመረ (ተፀመረ)፡ ተቸነከረ (በምስማር ተመታ) ።
ተሠመረ፡ ተበገረ/ተጣለ/ተነደፈ (መሥመሩ ") ።
ተሰመራ/ተሰማራ (ተረዐየ/ወፈረ)፡ ወደ ሥራ ኼደ፡ ወደ ዱር ገባ/ተሠራጨ (ሕዝ. ፴፬፡ ፲፬) ።
ተሰመራራ፡ ተሠረጫጪ።
ተሰመነ፡ ስምንት ኾነ ተባለ።
ተሰሚ፡ የሚሰማ/የሚደመጥ (ጨዋ/ሽማግሌ/ሊቅ) ።
ተሰማ (ተሰምዐ)፡ ተደመጠ (እሰው ዦሮ ገባ - ግብ. ሐዋ. ፲፡ ፴፩) ።
ተሰማ፡ የወንድ መጠሪያ ስም።
ተሰማመረ፡ ተጊያጊያጠ/ተሸላለመ።
ተሰማሚ፡ የሚሰማማ (ተደማማጭ) ።
ተሰማማ፡ ተደማመጠ፡ ተፈቃቀረ፡ ተዋደደ፡ ተዋዋለ (ምሳ. ፲፱፡ ፲፡ ማቴ. ፳፡ ፩, ፪, ፲፫፡ ግብ. ሐዋ. ፳፰፡ ፴) ።
ተሰምሪ/ተሰማሪ፡ የተሰመራ/የሚሰመር (የተሰማራ/የሚሰማራ ሰው/ከብት) ።
ተሰሰ፡ ተላሰሰ/ተነቀለ/ተጠረገ።
ተሠሠት፡ ተነፈገ/ተቀቀተ።
ተሰረሰረ፡ ተሰነፈጠ/ተበሳ/ተነደለ ።
ተሰረረ፡ ተወጣ/ተጠቃ/ተመታ (በታች ኾነ ተወጣበት) ። (ተረት)፡ "ዥብ እሰር ብሎ ተሰሮ ገባ"።
ተሰረረ፡ ተጣደ/ሰፋ/ተጋገረ ።
ተሰረረች፡ ተጠቃች/ተመታች (ቄብነቷ ቀረ) ።
ተሰረቀ (ተሰርቀ)፡ ተነሣ/ተወሰደ በሌባ እጅ ተሞጨለፈ ።
ተሠረተ፡ መሠረት ተሠራለት/ተጣለለት።
ተሰረነቀ፡ ታፈነ/ተሰነፈጠ ።
ተሰረየ (ተሰርየ)፡ ቀለለ/ተተወ/ይቅር ተባለ (ኢሳ. ፯፡ ፯፡ ሮሜ ፬፡ ፯) ።
ተሰረጀ፡ ተጠለፈ/ተሰናከለ/ተጣለ ።
ተሰረገ፡ ተደራጀ/ተደገሰ ።
ተሰረገ፡ ተጌጠ/ተሸለመ/ተኳለ/ተዳረ (ሚስት አገባ) ።
ተሠረገበ፡ ተጠጣ/ተጨለጠ።
ተሠረገበ፡ ተጠጣ/ተጨለጠ።
ተሰረገች፡ ተጌጠች/ተሸለመች/ተዳረች (ለባል ተሰጠች ባል አገባች) ።
ተሠሪ (ዎች)፡ በየመንደሩ የሚሠራ በገባር ቤት የሚቀመጥ ወታደር ምሪተኛ ።
ተሠሪነት፡ ተሠሪ መኾን ።
ተሰራ (ተሰርሐ)፡ ታረሰ/ተቈፈረ/ተገበረ/ተዘመረ/ታጨደ/ተከመረ/ተወቃ ።
ተሠራ (ተሠርዐ)፡ ታግን/ተወሰነ/ ተደነገገ/ተደነባ ።
ተሠራ፡ ሥራት ለበሰ/ለመደ/ተዳኘ ("(ግጥም)" - ፈረንጅ ወርዶ ወርዶ ማረፊያው ጅቡቴ ተሠራኹ ተቀጣኹ ማረኝ አካላቴ - "(ኹለተኛ ተሠራ)" - በጠና ታሞ ሙቶ ተነሣ - ዮሐ. ፲፩፥፵፬) ።
ተሠራ፡ ተመራ (ስፍራ ያዘ) ።
ተሠራ፡ ተሰማራ፡ (ሠረ) ።
ተሠራ፡ ታነጠ/ተገነባ (ተነገደ/ተሰፋ/ተጻፈ/ተጐነጐነ - "አይዞኸ ወንድሜ ተሠራውጋሜ" እንዲል ሐርበኛ ") ።
ተሠራ፡ ኾነ/ተደረገ/ተበጀ/ተዘጋጀ/ ተፈጠረ/ተገኘ ("(ፊልጵ. ፩፥፳፯)") ።
ተሰራረቀ፡ ተሞጨላለፈ ።
ተሰራረገ፡ ተዳዳረ ።
ተሠራራ፡ ተኳዃነ/ተደራረገ።
ተሰራጀ፡ ተጣለፈ/ተጣጣለ/ተዋደቀ ።
ተሰራጊ፡ የሚሰረግ/የሚዳር/የምትዳር ።
ተሰርሳሪ፡ የሚሰረሰር/የሚበሳ ።
ተሰርቆ ኼደ፡ ከጌታው ሳይሰናበት ተደብቆ ነጐደ ኰበለለ ።
ተሰቀለ (ተሰቅለ)፡ ተንጠለጠለ/ታበተ (ከምድር ራቀ) ሰፈረ (ዕቃው/ዶሮው/ሰዉ - አስ. ፪፡ ፳፫) ። (የባልቴት ግጥም)፡ "ዐርብ ሊሰቀል ማታውን ተሰናበታት እናቱን። እናትዬ ቈይ ታዪኛለሽ ተሰቅዬ። እኔን ይስቀለኝ ይስቀለኝ፡ ሐሰት ባንተ ዘንድ አይገኝ"።
ተሠቀሠቀ፡ ተወጋጋ/ተበሳሳ (ተለየ ተነጠለ) ።
ተሠቀቀ፡ ተጠላ/ተሰለቸ/ ተሰቀጠጠ ("ልማዱ ግን ጠላ ሰለቸ ነው" - ኢዮ. ፴፮፥፴፫፡ ዘካ. ፲፩፥፰) ።
ተሠቃቂ፡ የሚሠቀቅ/የሚሰለች።
ተሰቃይ፡ የሚሰቀል/የሚንጠለጠል (ተንጠልጣይ) ።
ተሰቈረ፡ ተበሳ/ተሸነቈረ ።
ተሠቅሣቂ፡ የሚሠቀሠቅ/የሚበሳሳ።
ተሰበሰበ (ዘፍ. ፵፱፡ ፴፫)፡ ተለቀመ፡ ተጠራቀመ፡ ታከበ፡ ተከማቸ፡ ተከተተ። "ዝንብ"ን ተመልከት።
ተሰበሰበ፡ ተሰቀጠጠ፡ ዐረፈ (ዐርፎ ተቀመጠ) ።
ተሰበረ (ተሰብረ)፡ ነከተ፡ ተቀለጠመ፡ ደቀቀ፡ ተሠነጠቀ፡ ተለበጠ (ሕዝ. ፳፯፡ ፴፬) ። "ሲሰበር ይሠንጠር" እንዲሉ።
ተሰበረ፡ ተነደለ፡ ተጣሰ፡ ፈረሰ።
ተሰበረ፡ ተደፋ፡ ዘነበለ።
ተሰበረ፡ ታጨደ፡ ተቈረጠ።
ተሰበቀ፡ ተበጠበጠ፡ ተማሰለ፡ ተምታታ፡ ታሸ።
ተሰበቀ፡ ተነከረ፡ ታለለ (ዘፀ. ፴፭፡ ፴፭) ።
ተሰበቀ፡ ተነገረ፡ ኾነ፡ ተደረገ (ሰብቁ) ።
ተሰበቀ፡ ተወዘወዘ፡ ተነቀነቀ።
ተሰበቃቀለ፡ ተቀለጣጠፈ፡ ተመሰቃቀለ።
ተሰበበ፡ ተመካኘ።
ተሰበተ፡ ሰባት ኾነ።
ተሰበተ፡ ታረሰ፡ ተገለገለ።
ተሰበከ፡ ተነገረ፡ ተወራ፡ ተባለ፡ ተሰማ (ማቴ. ፳፬፡ ፲፬፡ ሉቃ. ፳፬፡ ፵፯) ።
ተሰበከተ፡ ተገረፈ፡ ተጠጣ።
ተሰበዘ፡ ተሻጠ፡ ተሸጐጠ፡ ተጨመረ፡ ገባ።
ተሰባ፡ (ተሰብሐ)፡ ተገለጠ፡ ተረዳ።
ተሰባሰበ፡ ተጠራራ፡ ተለቃቀመ፡ ተጠረቃቀመ፡ ተከመቻቸ።
ተሰባሪ፡ የሚሰበር። "ሰውና ዕንጨት ተሰባሪ ነው"።
ተሰባቀለ፡ ተቀላጠፈ።
ተሰባቀለ፡ ተዘናፈለ፡ ተመሳቀለ (ኤር. ፮፡ ፪) ።
ተሰባበረ፡ ተቀለጣጠመ (፪ዜና. ፲፬፡ ፲፫) ።
ተሰባኝ፡ ተገለጠልኝ፡ ገባኝ።
ተሰባው፡ ተገለጠለት፡ ተረዳው፡ ገባው።
ተሠባጠረ (ተሠበጣጠረ)፡ ተዋሰበ/ተዛነቀ/ጣልቃ ገባ (አንድ ዐለፍ ኾነ ' ቆመ) ።
ተሠባጣሪ፡ የሚሠባጥር (የተጠቀጠቀና ያልተጠቀጠቀ ባለጽፈት ወረቀት ቀሪና ኻያጅ) ።
ተሰብሳቢ፡ የሚሰበሰብ።
ተሰተሰ) አንተሰተሰ፡ አነቃ ሠነ...ቀ አስፈራ ።
ተሰተስ/ተስታሳ፡ የተንተሰተሰ/የሚ...ንተሰተስ (ፈሪ) ።
ተሰተረ (ተሰትረ)፡ ተዘረጋ/ተሰጣ ።
ተሰታተረ፡ ተዘረጋጋ ።
ተሠነቀ፡ ተቈላ/ተፈጨ/ተጋገረ (ተዘ ነቅ ") ።
ተሰነቀረ፡ ተሻጠ/ተጋረጠ/ገባ ።
ተሰነቃ (ተሰንቀወ)፡ ተጠረበ/ታነጠ/ተላገ ።
ተሰነቃ፡ ተመታ/ተከረከረ/ተገረፈ (ማሲንቆ - ዎች/መሰንቆ) ። የዘፈን መሣሪያ (ሰርግና ግብር መሸታ ግብዣ ባለበት ቤት አዝማሪ እየመታ እየከረከረ እየገረፈ የሚጫወትበትና የሚያጫውትበት) ። ማሲንቆ ጥንት የቤተ ክህነት ሲኾን በዘመን ብዛት እቤተ መንግሥት ገባ ይባላል።
ተሠነበጠ፡ ተሠነጠረ/ተለበጠ (ተሠነተረ ተከረከረ ተከፈለ) ።
ተሰነባበተ፡ "ደኅና ሰንብት በደኅና ያድርስኸ ይመልስኸ፡ ኣሜን ደኅና ቈየኝ" ተባባለ/ተሳሳመ።
ተሰነባበተ፡ ተፋታ/ተላቀቀ/ተለያየ።
ተሠነተረ፡ ተበጣ/ተቀደደ/ተሠነጠቀ።
ተሠነታተረ፡ ተበጣጣ/ተቀዳደደ።
ተሰነከለ፡ ተመታ/ተጐዳ ።
ተሰነካከለ፡ ተጓጐለ/ተወለካከፈ።
ተሰነካከለ፡ ተጓጐለ/ተወለካከፈ።
ተሰነካካይ፡ የሚሰነካከል።
ተሰነካካይ፡ የሚሰነካከል።
ተሰነኰረ፡ ተዘነኰረ ።
ተሰነኰረ፡ ተዘነኰረ ።
ተሰነዘረ፡ ተለካ/ተመጠነ ።
ተሰነዘረ፡ ተሠነተረ/ተበጣ/ተሠነ...ጠቀ ።
ተሰነዘረ፡ ተቃጣ ።
ተሰነደቀ፡ ቀስ ብሎ ታቦትኛ ኼደ ።
ተሰነደቀ፡ ተቀረጸ ክብ ኾነ ።
ተሰነደቀ፡ ታሰረ ።
ተሰነደደ፡ ተሠራ/ተበጀ ስንድዱ፡ ተሰካ/ተደረደረ፡ ቀጥተኛ ኾነ።
ተሰነዳዳ፡ ተዘገጃጀ/ተደረጃጀ/ተካተተ።
ተሰነገ፡ ስናግ ገባበት።
ተሰነገ፡ ተበሳ/ተሸነቈረ፡ ገባ/ተቀረቀረ ።
ተሰነገ፡ ተነቀነቀ/ተደናቀፈ (ዘክዘክ አለ - በቅሎ) ።
ተሰነገ፡ ተጠመጠመ/ታሰረ።
ተሰነገ፡ ተጨነቀ/ተጠበበ።
ተሰነገለ፡ ተወለወለ/ጠራ/ተብለጨለጨ/ተሳለ/ሰላ (ሕዝ. ፳፩፡ ፲, ፲፩, ፲፭) ።
ተሰነጋ፡ ተኰላሸ/ወጣ/ተጐነደለ፡ ተቀጠቀጠ/ተወቀጠ፡ ታሸ/ታሰረ/ተሠነጠቀ/ፈሰሰ ።
ተሰነጠ፡ አማረ/ጌጠኛ ኾነ።
ተሠነጠረ፡ ተለበጠ/ተሠነበጠ (መክ. ፲፥፱) ። ("(ተረት)" - ሲሰበር ይሠንጠር) ።
ተሠነጠቀ፡ ተሰበረ/ነበበ/ተተረተረ/ተተረረ (ኹለት ኾነ - ኤር. ፲፫፥፬) ።
ተሠነጣጠቀ፡ ተሰባበረ/ተቃደደ ("(በብዙ ወገን ተሠነጠቀ)") ። ("እግሬ ተሠነጣጠቀና አላስኬድአለኝ") ።
ተሰነፈጠ/ተሰረነቀ/ተሰረሰረ ።
ተሰናበተ፡ "ደኅና ሰንብቱ" አለ (ነሐ. ፲፫፡ ፯) ።
ተሰናበተ፡ ተፈታ/ተለቀቀ፡ ሞተ/ተለየ።
ተሰናባች፡ የሚሰናበት (ኻያጅ መንገደኛ) ።
ተሠናተረ፡ ተባጣ/ተቃደደ።
ተሰናነፈ፡ ተናነሰ/ተበላለጠ።
"እከሌና እከሌ በሙያ ኣይሰናነፉም"።
ተሰናናፊ፡ የሚሰናነፍ (ተበላላጭ) ።
ተሰናኘ፡ ተሰማማ/ተጋጠመ/ተባበረ፡ ተላለፈ ከትውልድ ወደ ትውልድ ።
ተሰናኘ፡ ተሰማማ/ተጋጠመ/ተባበረ፡ ተላለፈ ከትውልድ ወደ ትውልድ ።
ተሰናከለ፡ ተጠለፈ/ተሰረጀ/ተጨናጐለ/ተወላከፈ/ተደናቀፈ (ዕንቅፋት መታው ጕዳት አዠኘው ታወከ) ። ኀጢአት ሠራ/በኀጢአት ወደቀ (መንፈሳዊ ሙቀቱ በረዶ ቀዘቀዘ - ምሳ. ፬፡ ፲፪፡ ኤር. ፵፮፡ ፮፡ ሮሜ. ፱፡ ፴፪፡ ፲፩፡ ፲፩) ።
ተሰናከለ፡ ተጠለፈ/ተሰረጀ/ተጨናጐለ/ተወላከፈ/ተደናቀፈ (ዕንቅፋት መታው ጕዳት አዠኘው ታወከ) ። ኀጢአት ሠራ/በኀጢአት ወደቀ (መንፈሳዊ ሙቀቱ በረዶ ቀዘቀዘ - ምሳ. ፬፡ ፲፪፡ ኤር. ፵፮፡ ፮፡ ሮሜ. ፱፡ ፴፪፡ ፲፩፡ ፲፩) ።
ተሰናካይ፡ የሚሰናከል።
ተሰናካይ፡ የሚሰናከል።
ተሰናዘረ፡ ተላካ/ተማጠነ ።
ተሰናዘረ፡ ተላወሰ/ተዛወረ/ተወላዳ ("ስንዝር ታኽል ኼደ" - ፈቀቅ አለ) ።
ተሰናዘረ፡ ተሠናተረ/ተባጣ ።
ተሰናዛሪ፡ የሚሰናዘር/የሚላካ።
ተሰናዳ፡ ገባ/ተጨመረ/ተከተተ (የሥንቅ/የዕቃ/የማንኛውም ነገር - ተደራዝ) ።
ተሰናዳና አሰናዳ፡ ተደራራጊና አደራራጊ ሲመስሉ በተደራጊነትና ባድራጊነት መፈታታቸውን አስተውል ።
ተሰናጂ፡ የሚሰናዳ/የሚዘጋጅ (ግቢ ተ...ጨማሪ) ።
ተሰናጊ፡ የሚሰነግ/የሚገባ።
ተሠናጠቀ፡ ተቃደደ/ተካፈለ/ተራከበ (ግማሽ ግማሹን ወሰደ ") ።
ተሠናጣቂ፡ የሚሠናጠቅ (ተካፋይ) ።
ተሠንታሪ፡ የሚሠነተር (ተበጪ) ።
ተሰንዛሪ፡ የሚሰነዘር (ተሠንታሪ) ።
ተሰንዳቂ፡ የሚሰነደቅ (በቀስታ የሚኼድ/የሚታሰር - ታሳሪ) ።
ተሰንጊ፡ የሚሰነጋ/የሚኰላሽ።
ተሠንጣቂ፡ የሚሠነጠቅ (ተቀዳጅ) ።
ተሠኘ፡ ተባለ/ተነገረ።
ተሠኛኘ፡ ተባባለ/ተነጋገረ።
ተሰከለ፡ ታሰረ፡ ተቈረኝ።
ተሰኪ፡ የሚሰካ/የሚሻጥ።
ተሰካ (ተሰክዐ)፡ ተሻጠ፡ ተሳገ፡ ገባ፡ ተደረደረ፡ ቆመ፡ ተገተረ። "እከሌ ዐጥር ላይ ተሰካ" እንዲሉ።
ተሰካይ፡ የሚሰከል (ዐመለኛ የጋማ ከብት) ።
ተሰወረ፡ ተሸፈነ፡ ተከለለ፡ ታባ፡ ተደበቀ፡ ተሸሸገ፡ የማይታይ ኾነ (፪ሳሙ. ፲፯፡ ዮሐ. ፰፡ ፶፱).
ተሠዊ (ተሠዋዒ)፡ የሚሠዋ (የዓመት ጥቦት ክርስቶስ) ።
ተሠዋ (ተሦዐ)፡ ታረደ (ጭዳ ተባለ ") ።
ተሰዋሪ፡ የሚሰወር/ተደባቂ/ተሸሻጊ።
ተሰዋወረ፡ ተደባበቀ።
ተሰየመ (ተሰምየ)፡ ስም ተሰጠው/ወጣለት።
ተሠየመ፡ ተሰፈረ/ተመላ/ተለበመ።
ተሠየመ፡ ተሾመ/ከበረ።
ተሰየፈ፡ ሾጠጠ (ሾጣጣ ኾነ) ።
ተሰየፈ፡ በሰይፍ ተመታ፡ ተቈረጠ፡ ተከለለ፡ ተገደለ።
ተሰያሚ፡ የሚሰየም (ስም ተቀባይ) ።
ተሰያፊ፡ የሚሰየፍ (ተገዳይ) ።
ተሰደሰ፡ ስድስት ኾነ/ተባለ።
ተሰደረ፡ ተወለደ፡ ረባ፡ ተደረደረ፡ ተመዴዴ፡ ተኵሎኰለ፡ ተራ መታ።
ተሰደረገ፡ ፈጠነ ዐለፈ ኼደ ።
ተሰደቀ (ተሰድቀ)፡ ተዘረጋ።
ተሰደቀ፡ ተቀባ፡ ተደለሰ።
ተሰደበ፡ ተወረፈ፡ ተነቀፈ፡ ተዘለፈ፡ ተዋረደ፡ አነሰ፡ ቀለለ፡ ኰሰሰ፡ ረከሰ (ሉቃ. ፲፰፡ ፴፪) ። "ሰጠን"ን እይ።
ተሰደደ (ተሰደ)፡ ግብር መሮት አገዛዝ ጸንቶበት ችግር በዝቶበት ካገር ወጣ፡ አገር ጥሎ ቈርበት ጠቅሎ ኼደ። (ተረት)፡ "ካብሮ አደግህ አትሰደድ።"
ተሰዳሪ፡ የሚሰደር/ተደርዳሪ።
ተሰዳቢ፡ የሚሰደብ፡ ተነቃፊ።
ተሰዳደበ፡ ተወራረፈ፡ ተነቃቀፈ።
ተሰዳጅ (ጆች)፡ የሚሰደድ/የሚኼድ።
ተሰዳጅነት፡ ተሰዳጅ መሆን።
ተሰገሰገ፡ ተቀራረበ፡ ተጠቀጠቀ፡ ጠበበ።
ተሰገሰገ፡ ገባ፡ ታጨቀ።
ተሰገደ፡ ኾነ/ተደረገ (ስግደቱ ለፈጣሪ ቀረበ) ።
ተሰገደደ፡ ተመለሰ፡ ተሰበሰበ፡ ተደበቀ፡ ተከለለ፡ ተሰወረ።
ተሰገጠ፡ ተሰፋ፡ ተቀመቀመ፡ ተዘመዘመ (ቅሉ/ካባው) ።
ተሰጋለበ፡ ተቻኰለ፡ ተጣደፈ ለመብላት።
ተሰጋጭ፡ የሚሰገጥ/የሚሰፋ።
ተሰግሳጊ፡ የሚሰገሰግ (በሸማ ጫፍ የተጣለ ሰፊ ጥለት) ።
ተሰጐደ፡ ተመታ፡ ተገጨ።
ተሰጐደ፡ ታጠፈ፡ ተቀነፈ፡ ጐደጐደ፡ ተደጐሰ፡ ተጐበጐበ፡ ተሸለመ፡ ተጌጠ።
ተሰጓጅ፡ የሚሰጐድ፡ ተደጓሽ።
ተሰጠ (ተሰጥወ)፡ ተቸረ፡ ተለገሰ፡ ታደለ፡ ተረከበ (ከተቀባይ እጅ ገባ) ።
ተሰጠ፡ ተነገረ፡ ተመለሰ፡ ተወሣ (ቃሉ ነገሩ) ።
ተሠጠጠ፡ ተቀደደ ።
ተሰጣ (ተሰጥሐ)፡ ተዘረጋ፡ ተዘረረ፡ ተሰተረ፡ ተበተነ።
ተሰጣሰጠ፡ ተደባደበ፡ ተጋረፈ፡ ተማታ።
ተሰጣጠ፡ ተዳደለ፡ ተቀባበለ፡ ተረካከበ።
ተሰጣጣ (ተሳጥሐ)፡ ተዘረጋጋ፡ ተሰታተረ።
ተሰጥዎ፡ መዘምራን የሚያዜሙት የቅዳሴ ጓዝ ("እግዚኦ ተሣሀለነን ምስለ መንፈስከን" የመሰለ)፡ ትርጓሜው መመለስ።
ተሰጦ (ተሰጥዎ)፡ ዕድል ።
ተሰጪ/ጭ፡ የሚሰጥ/የሚታደል ።
ተሰጪነት፡ ተሰጪ መሆን ።
ተሰፈረ፡ ቀለብ ተቀበለ (ወታደሩ) ።
ተሰፈረ፡ ተለካ/ተመጠነ (እኽሉ) ።
ተሰፈረ፡ ያበደረውን እኽል ተከፈለ።
"በሰፈሩበት ቍና መሰፈር አይቀርም"።
ተሰፊ፡ የሚሰፋ (ሸማ/ዐጥፍ/በርኖስ) ።
ተሰፋ (ተሰፍየ)፡ ተጠቀመ/ተደረዘ/ተዘመዘመ ።
ተሰፋሪ፡ ቀለብ ተቀባይ (ቀለብተኛ) ።
ተሰፋሪ፡ የሚሰፈር/የሚለካ (እኽል) ።
ተሢያሢያረ፡ ተማማለ/ተደማደመ።
ተሲያት (ተሱዓት ሰዓት)፡ ዘጠኝ ሰዓት ። ("መንገደኛው በተሲያት መጣ" እንዲሉ - "ሰዓትን" እይ) ።
ተሲያት (ተስዐ)፡ ከሠለስት በላይ ያለ ጊዜ ረፋድ ("አውራን" አስተውል) ።
ተሲያት ኾነ፡ ረፈደ ።
ተሳለ (ተሳአለ)፡ ታቦትን/ጣዖትን ተጠያየቀ፡ ተለማመነ፡ ተለማመጠ፡ ተማኰተ። ልማዱ ግን እንደ መዠመሪያው አድራጊነት ነው (መዝ. ፻፴፪፡ ፪፡ ዮና. ፩፡ ፲፮) ። "ከበሽታ ብታድነኝ፡ ከጭንቅ ብታወጣኝ፡ መከራዬን ብታቀልልኝ ጧፍ/ዕጣን/ዘይብ እሰጣለኹ፡ ግምጃ እጋርዳለኹ" አለ።
ተሳለ (ተስሕለ)፡ ተሞረደ፡ ተፈገፈገ፡ ተሰነገለ፡ እስኪሰላ ድረስ ተለመጠ (ሕዝ. ፳፩፡ ፲). (ተረት)፡ "በተሳለ ያርዷል፡ በታየ ይፈርዷል።" ተሳለ፡ ተዘረዘረ (መጋዙ/ማጭዱ - ራእ. ፲፬፡ ፲፬).
ተሳለ (ተስእለ)፡ ተለመነ፡ ተጠየቀ።
ተሣለ (ተሥዕለ)፡ ተነደፈ/ተበገረ/ ተመሰለ ።
ተሳለ (ተስዕለ)፡ ኾነ/ተደረገ ሳሉ፡ ተጐበሰተ ።
ተሳለ፡ የስለት ልጅ ኾነ፡ ለእግዚአብሔር ተሰጠ (መሳ. ፲፫፡ ፯) ።
ተሳለለ፡ ተጐበኛኘ፡ ተላላከ፡ ተጠያየቀ፡ ተነጋገረ፡ ተመራመረ፡ ተመሳጠረ።
ተሳለመ፡ ቤተ ክርስቲያን መስቀል/የቄስ እጅ ሳመ/ተባረከ/እጅ ነሣ፡ ሰላምታ ሰ... ተሰናበተ (ግብ. ሐዋ. ፳፡ ፩፡ ፩ጴጥ. ፭፡ ፲፬) ። "ተሳለመ" ተደራራጊ ሲኾን ባድራጊነትና በተደራጊነት መፈታቱን ልብ አድርግ።
ተሣለቀ፡ አላገጠ (ሠለቀ) ።
ተሳለበ፡ ተጓመደ።
ተሳለፈ፡ ተቃረበ/ተፋጠጠ ለመዋጋት/ለመጋደል።
ተሳላ፡ ተሳሰበ፡ ተፋሰሰ፡ ተቈጣጠረ።
ተሳላ፡ ተከናወነ፡ ተቃና፡ ተቀናበረ፡ ተሳካ (ማር. ፱፡ ፵፱) ።
ተሳላሚ፡ የሚሳለም (ተባራኪ) ።
ተሣላቂ፡ የተሣለቀ/የሚሣለቅ/የሚዘ ብት (አላጋጭ - ምሳ. ፳፩፥፲፩) ።
ተሳላይ፡ የተሳለለ/የሚሳለል (ተጠያያቂ/ተመራማሪ) ።
ተሣልቆ፡ መሣለቅ ("(ግእዝ)") ።
ተሳመ (ተስዕመ)፡ ተጨመጨመ።
ተሳመጠ፡ ተሳጠመ።
ተሳሚ፡ የሚሳም (መልክ ቀና ልጅ) ።
ተሳማ (ተሳምዐ)፡ ተዳመጠ ።
ተሳሰረ፡ ተንተባተበ፡ ከስካር ከበሽታ የተነሣ መናገር አቃተው። አፉ ተሳሰረ እንዲሉ።
ተሳሰረ/ተኣሰረ፡ ተያያዘ፡ ተቈራኘ።
ተሳሰበ (ተሓሰበ)፡ ተፈቃቀደ ተቈ ጣጠረ ተሳላ (ተረዳዳ ") ።
ተሳሰብ፡ ተቈጣጣሪ
ተሣሠተ፡ ተናፈገ ።
ተሳሳመ (ተሳዐመ)፡ ተጨማጨመ (አፍ ላፍ/ጕንጭ ለጕንጭ/ትከሻ ለትከሻ ተገናኘ) ። "አህያና አህያ ሲገናኝ ይሳሳማል"።
ተሳሳሚ (ተሳዓሚ)፡ የተሳሳመ/የሚሳሳም ።
ተሣሣቀ፡ በሣቅ ተፈራረቀ/ተጨዋወተ ("(ተረት)" - እንሣሣቅስ ታለሽ ነዶዬን ጥለሽ - ባላገር ዝንጀሮዋን ") ።
ተሳሳበ፡ (ተሳሐበ)፡ ተጓተተ፡ ምድርን ተለካካ በገመድ።
ተሳሳቢ (ተሓሳቢ)፡ የተሳሰበ የሚ
ተሳሳቢ፡ (ተሳሓቢ)፡ የተሳሳበ፡ የሚሳሳብ (ተጓታች) ።
ተሳሳቢ፡ የሚሳሳብ—ሳበ ።
ተሳሳቢ፡ የሚተሳሰብ (ዐሰበ) ።
ተሳሳቢነት፡ ተጓታችነት።
ተሳሳተ (ተሳሐተ)፡ ተሳከረ፡ ተደናገረ ። (ተረት)፡ "ጥጃ ቢሳሳት ከናቱ ነገር ቢሳሳት ከጥንቱ"።
ተሳሳተ፡ ተጣጣ ሳይተዋወቅ ቀረ ።
ተሳሳች፡ የሚሳሳት ወደ ስሕተት የሚያጋድል ።
ተሳረረ፡ ተዛዘለ/ተነባበረ/ተገናኘ ።
ተሳረቀ፡ ተሞጫለፈ ።
ተሣራ፡ ተዋጋ/ተማታ/ተቀራደደ።
ተሣራ፡ ተዳረገ ("እከሌና እከሌ ክፉ ተሣርተዋል!" እንዲሉ) ።
ተሣቀ፡ ኾነ/ተደረገ (ሣቁ - ሕዝ. ፴፮፥፬) ። በትና ለት ሲሰማሙት ተሣቀበት ተሣቀለት ይላል ።
ተሳቀለ፡ ተናሣ/ተንጠላጠለ/ተማዘነ ።
ተሣቀቀ፡ አይቶ አግኝቶ ዐጣ (ዐፈረ ኩም አለ) ወሰደ ።
ተሣቀየ፡ ተጨነቀ፡ ዛበረ - ተሣቀየ፡ ተጨነቀ፡ ደከመ። ረዘየ ጥንታዊ አማርኛ ነው - ረዘየ የድሮ አማርኛ ቃል ነው።
ተሣቀየ፡ ጭንቅ ተቀበለ (ተጨነቀ) ።
ተሣቃቂ፡ የተሣቀቀ/የሚሣቀቅ።
ተሳበ (ተስሕበ)፡ ተጐተተ፡ ተመዘዘ፡ ረዘመ።
ተሳበ፡ ተወጠረ፡ ተለጠጠ፡ ተገተረ።
ተሳበ፡ ተጠራ፡ መጣ፡ ቀረበ።
ተሳበ፡ ዐረገ፡ ወጣ (ግብ. ሐዋ. ፲፩፡ ፲) ።
ተሳበረ፡ ተማታ፡ ተቀላጠመ። "አህያ ላህያ ቢራገጥ ጥርስ አይሳበር"።
ተሳበረ፡ ተሸናነፈ፡ ተረታታ፡ ድል ተኳዃኑ። "ዐይን ላይን ተሳበረ" እንዲሉ።
ተሳበቀ፡ ተወዛወዘ፡ ተነቃነቀ።
ተሳበቀ፡ ተጠላለፈ፡ ተያያዘ።
ተሳቢ (ተሰሓቢ)፡ የሚሳብ፡ ተጐታች (ሞፈር፣ ፈረስ፣ በቅሎ፣ ሠረገላ፣ እባብ፣ ዘንዶ፣ ዐረግ፣ ላስቲክ፣ ቀስት) ።
ተሳቢ ቃል/ነገር፡ "ሳቢና ተሳቢ" እንዲሉ።
ተሳቢነት፡ ተሳቢ መሆን፡ ጐታችነት።
ተሳቦ ። "ቀለመ" ብለኸ "ቀለምን" እይ ። ቀንድ ዘርፍ ኹኖ ሳለ ከባለቤት ቀድሞ ሲነገር ።
ተሳቦ፡ እየተሳበ የሚኼድ ትል (ቀንዳውጣ፣ ዛጐል)፡ ልብሱ...
ተሳተ (ተስሕተ)፡ ሳይመታ ቀረ አመለጠ ዳነ ።
ተሳተ፡ ተገደፈ ታጣ ።
ተሳተረ፡ ተዘራጋ ።
ተሳተፈ፡ ተገናኘ/አንድ ኾነ/ተቋረሰ/ዐብሮ በላ/ተፋተተ/ተካፈለ ።
ተሳታፊ፡ የሚሳተፍ ።
ተሳነ፡ አቃተ (ሳነ) ።
ተሳነኝ፡ አቃተኝ (ዐቅም ዐጣኹ/ደከመኝ) ።
ተሳነው፡ አቃተው/ቸገረው ። "ለእግዜር የሚሳነው ነገር የለም"።
ተሳነፈ፡ ተዳከመ (ሰነፍ ተኳዃነ ልብና ሰውነት) ።
ተሳኝ፡ የሚሳን (አቃች) ።
ተሳከረ፡ ተሳሳተ፡ ተዛነቀ፡ ተዘባረቀ፡ ተቃወሰ (ሰው፡ አእምሮው፡ ነገሩ፡ ሥራው) ።
ተሳካ (ተሳክዐ)፡ ተዋደደ፡ ተቀናበረ፡ ተሳላ።
ተሳይ፡ ብፅዐት የሚያደርግ።
ተሳይ፡ የሚሳላ/የሚቈጣጠር (ተሳሳቢ) ።
ተሳይ፡ የሚሳል (ባለብፅዐት) ።
ተሳይ፡ የሚሳል/የሚሰነገል ።
ተሳደረ፡ ተደራደረ።
ተሳደበ (አድራጊና ተደራራጊ)፡ ሰደበ፡ ተዋረፈ፡ ተናቀፈ፡ ተኳሰሰ፡ ተራገመ (ሕዝ. ፴፭፡ ፲፪፡ ነሐ. ፱፡ ፳፯) ። ("ተሳደበ"ን "ሰደበ" ማለት የልማድ ስሕተት ነው) ።
ተሳደበ፡ ተባለ፡ ተለያየ (ልክክ ሳይል ቀረ - ግድግዳው/ግንቡ) ።
ተሳደደ፡ ተባረረ (፪ቆሮ. ፩፡ ፮)
ተሳዳቢ፡ የተሳደበ/የሚሳደብ (ሰዳቢ፡ ተራጋሚ - ዘሌ. ፳፬፡ ፲፬፡ ፩ቆሮ. ፩፡ ፲፩).
ተሳዳቢነት፡ ተሳዳቢ መሆን።
ተሳዳቢዎች/ተሳዳቦች፡ የሚሳደቡ (ሰዳቢዎች - ፩ቆሮ. ፮፡ ፲).
ተሳዳጅ፡ የሚሳደድ/የሚባረር (ተባራሪ) ።
ተሳገ/ተሳጋ፡ ተሻጠ፡ ተሰካ፡ ተጨመረ፡ ገባ።
ተሳገደ፡ ስግደትን ተቀባበለ።
ተሳጐደ፡ ተማታ፡ ተጋጨ።
ተሳፈረ፡ ተሰፋፈረ፡ ተላካ/ተለካካ ።
ተሳፈረ፡ እመርከብ/እባቡር/አይሮፕላን ላይ ወጣ ለመኼድ ።
ተሳፈረ/ተሰፋፈረ (ተዓየነ)፡ አቅጣጫ ላቅጣጫ ተቀመጠ/ተቀማመጠ (ሰራዊቱ) ።
ተሳፋሪ (ሮች)፡ የሚሳፈር (በሠረገላ/በካሚዎን የሚቀመጥ) ።
ተሴሰየ፡ ጐረሠ/በላ/ተመገበ/ተቀለበ ።
ተሤረ፡ ታደረ/ታደመ/ተመከረ/ተዶለተ (ተቈረጠ ውሳኔ አገኘ ሤራው) ።
ተስ፡ የተደራጊና የተደራራጊ አንቀጽ ባዕድ መነሻ ። ("ከረከረ - ተስከረክረ" - "ነጎደ - ተናገደ ተስተናገደ") ።
ተስለመለመ፡ ተጭለመለመ፡ ተዝለፈ ለፈ ።
ተስለከለከ፡ ተፍለከለከ፡ ተሹለከለከ (ሀልቅትኛ ገባ) ።
ተስመነመነ፡ ተድቀሰቀሰ (እንቅልፍ ተጫነው) ።
ተስማሚ፡ የሚስማማ (ተፋቃሪ) ።
ተስማማ፡ ተፋቀረ፡ ተዋዋደ፡ ጤና ኾነ፡ ጠቀመ፡ ረባ።
ተስረቀረቀ፡ ተንሠቀሠቀ፡ መላልሶ ሥቅቅ ብሎ ክፉኛ ካንዠት አለቀሰ።
ተስረቀረቀ፡ አለቀሰ፡ ረቀረቀ ።
ተሥረገረገ (ሐዘዘ)፡ ተዋጠ ' ሰጠመ ።
ተሥረገረገ (ሐዘዘ)፡ ተዋጠ ' ሰጠመ ።
ተስቦ፡ (ተስሒቦ)፡ የበሽታ ስም፡ ሰውን የሚያሳብድ፣ ዐይንን የሚያፈርጥ፣ የራስ፣ የተቅማጥ፣ የትኵሳት ሕመም። በአየር እየተሳበ ከአንዱ ወደ ሌላው ስለሚጋባ "ተስቦ" ተባለ። (ግጥም)፡ "የዚህ ዓለም ፍጥረት ኹሉ በሽተኛ፡ ተስቦ መጣና እንዲህ አረገኛ።"
ተስቦ፡ ክፉ በሽታ፡ (ሳበ) ።
ተስተስ አለ፡ የፍራት ነገር ተናገረ ።
ተስተረፈ፡ ተረፈ።
ተስተናገደ (ተአንገደ)፡ በሰው ቤት በላ/ጠጣ/ተጋበዘ እንግዳ ኹኖ።
ተስኖት፡ አቅቶት/ቸግሮት። "ምን ተስኖት" እንዲሉ። "ምንን" ተመልከት ።
ተስከረከረ፡ አደፈ፡ (ከረከረ) ።
ተስገበገበ፡ ቸኰለ፡ ተጣደፈ፡ ኹሉን ውጨው አለ።
ተስገብጋቢ፡ የሚስገበገብ።
ተስጣጣ፡ ተገላበጠ፡ ተገላለጠ።
ተስፋ (ሰፈወ)፡ አለኝታ ወደ ፊት አገኛለኹ የማለት ጽኑ እምነት ።
ተስፋ ማርያም፡ የሰውና የቀበሌ ስም (በተጕለት ውስጥ ያለ አጥቢያ) ።
ተስፋ ሰጠ፡ ይሰኻል ታገኛለ'ኸ ኣለ ።
ተስፋ ቈረጠ፡ ተበሳጨ አላገኝም አለ ።
ተስፋ አደረገ፡ ማግኘትን አመነ ።
ተስፋ ጢብኛ፡ ስለ ሞቱ ሰዎች ለካህናት የሚዘጋጅ ባቡቴ ።
ተስፋዬ፡ የወንድና የሴት ስም ("የኔ ተስፋ" ማለት ነው) ። ("በተስፋ" - ባለኝታ በተስፋ እየኖረ ደጅ የሚጠና - "ባል" ብለኸ "ባለን" ተመልከት) ።
ተስፋፋ፡ ተመቻቸ/ተደላደለ/ተሸራሸ
("ተስፋፍቶ ተቀምጧል" እንዲሉ) ።
ተረ ።
ተረ፡ ለፋ/ደከመ ("በሥራ ዛሬ ስማትር ውዬ መጣኹ") ።
ተረመመ፡ (ተረመ) ዝም ጭጭ ባለ።
ተረመሰ፡ ተወሸቀ፡ ረመሰ ።
ተረመሰ፡ ተወሸቀ፡ ተነከረ፡ ተዘፈቀ፡ ተዘፈዘፈ፡ ራሰ፡ ቀዘቀዘ።
ተረመሰ፡ ታሸ፡ ተለወሰ፡ ተቦካ።
ተረመሰ) ተተራመሰ፡ ተሸበረ ታ...ወከ ታመሰ ተፋጀ ተበጠበጠ ተመሳቀለ (ጪስ እንደ ገባው ንብ ኾነ - ዘሩ ፪ኛው ረመሰ) ።
ተረመረመ፡ ተጠቀጠቀ፡ ተረገጠ፡ ተበራየ።
ተረመደ፡ ተነካ፡ ተረገጠ፡ ተጨቈነ፡ ተተመተመ፡ ተደመደመ፡ ከንጀራ ከውስጥ እግር ጋራ ተላከከ፡ ተጣበቀ፡ ዐብሮ ተነሣ መበያው እሾኹ።
ተረመደደ፡ ተረመጠጠ።
ተረመጠ፡ ገባ፡ ተሸጐጠ፡ ተቀበረ፡ ተደፈነ፡ ተጠበሰ።
ተረመጠጠ፡ ተረገጠ፡ ተደፈጠጠ።
ተረማመደ፡ ተላለፈ፡ ተጋባ፡ ተሸጋገረ በሽታው።
ተረማማጅ፡ የሚረማመድ፡ ተላላፊ።
ተረማማጅነት፡ ተላላፊነት።
ተረማረመ፡ ተጠቃጠቀ፡ ተረጋገጠ።
ተረማሽ፡ የሚረመስ።
ተረሰና ኰሰተረ፡ አንድ ዘር ናቸው ከመዛ ወር በቀር ልዩነት የላቸውም ።
ተረሳረሰ፡ ተራራሰ።
ተረረ (ትግ)፡ ጠና ጠነከረ በረታ ።
ተረረ፡ ሠነጠቀ ከፈለ ረደፈ ደረደረ ። ("ጠረረ"
ብለኸ "ጥራርን" አስተውል) ።
ተረረ፡ ቀጥታ ኾነ ።
ተረር አለ፡ ሥንጥቅ አለ ።
ተረር፡ የቅሞ ፍሬ ዘለላው በየረድፉ የሚንጠለጠል ።
ተረሸተ፡ በዛ፡ ተጠጋጋ ብቋያው።
ተረሸነ፡ ተመታ ተገደለ ሞተ ባረር።
ተረሺ፡ የሚረሳ ።
ተረቀረቀ፡ ተመታ፡ ተደበደበ ዠርባው።
ተረበ (ሰረበ)፡ ፈሰስ ወረደ ።
ተረበ፡ ቀለደ አላገጠ አፌዘ ። ተረበ፡ ነደፈ ጠቅ አደረገ ወጋ ።
ተረበ ተረጐመ
ተረበረበ፡ ተሰደረ/ተደረደረ/ተደረበ/ተነባበረ ።"ተጣለ ወደቀ ተጋደመ ።የሰናክሬም ሰራዊት እንደ ግንድ ተረበረበ"
።
ተረበረበ፡ ተርከፈከፈ/ተረጫ ።
ተረበኛ (ኞች)፡ ተረብ ወዳድ ባለ...ተረብ ።
ተረበከ፡ ተወዘፈ/ተረፈ/ተረፈቀ ።
ተረበደ፡ ተቸኰለ ተለፈለፈ ። ዐነጠሰንና ዐነከሰን እይ፡ አካኼዳቸው ከአረበደ ጋራ አንድ ነው ። ባስደራጊውና በተደራጊው አ መታጣቱን አስተውል ።
ተረበደ፡ ተቸኰለ አረበደ ።
ተረቢ፡ የሚረባ/ተጠቃሚ ።
ተረባ፡ ተባለ/ተነገረ
("ርባታው ") ።
ተረባ፡ ተጠቀመ
("ጥቅም አገኘ ሰውየው ") ("(ኢሳ. ፴፥ ፭ ። ዮሐ. ፲፪፥ ፲፱)")
።
ተረባረበ፡ ተራዳ/ተደራረበ/ተነባበረ ።
ተረባረበ፡ ተራጨ ።
ተረባራቢ፡ የሚረባረብ/ተነባባሪ ።
ተረባባ፡ ተጠቃቀመ ።
ተረባየ፡ ተረገጠ/ተረመረመ ።
ተረብ፡ ቀልድ ለግጥ ፌዝ ።
ተረተ፡ ኾነ/ተደረገ/ተቀበረ ርት።
ተረተረ፡ ሠነጠቀ ፈነከተ (ዕንወትን ራስ ቅልን) ።
ተረተረ፡ አቀና ቀጥ አደረገ (ጐባጣን) ።
ተረተረ፡ ዕዳሪ አወጣ ጠጋ ፈለቀ ።
ተረተረ፡ ዘረዘረ ነጠለ ። "አራት ያለውን ይተረትራል" (ትርጓሜ ሕዝቅ. ፲፬፡ ፳፩) ።
ተረተር (ሮች)፡ የምድር ዠርባ የኰረብታ የተራራ መንገድ መንደርደሪያ ። የገደል ሲኾን "ሸንተረር" ይባላል ።
ተረተርማ፡ የተረተር (ባለተረተር ተረተራም ስፍራ) ።
ተረተኛ፡ ዝኒ ከማሁ (የተረት ሰው - "ተረት ተረት የላም በረት" - የተረት መቅድም ከተረት በፊት የሚባል የሚነገር) ።
ተረታ፡ ተሸነፈ፡ ድል ኾነ።
ተረታም፡ ባለተረት (የተረት ጌታ ተረት ዐዋቂ ተረተ ብዙ) ።
ተረታታ፡ ተበያየነ፡ ተሸናነፈ፡ ረቺና ተረቺ ተኳዃነ፡ የመርታትን ብድር ተመላለሰ።
ተረት፡ "መንገድ ሳለ በዱር በቅሎ ሳለ በእግር ምንም ቢጠም መንገድ ምንም ቢከፋ ዘመድ" - እግርን አውራን እይ -
ተረት (ቶች)፡ ልብ ወለድ ፈጠራ ነገር (ሉቃ. ፳፬፡ ፲፩) ። ("ተረት በምሳሌ ዜማ በሃሌ" እንዲሉ) ።
ተረት፡ ስለ ያለፈና የጊዜ ነገን እውነት አስመስሎ አወጋ ።
ተረት)፡ "ሲስማት ቀርታ ሲስቧት።" "ሰው የወለደውን ቢስሙለት የደገሰውን ቢበሉለት ይወዳል"።
ተረቺ፡ የሚረታ የሚሸነፍ።
ተረነቀ፡ አነሰ/ዐጠረ ("ተቈነ") ።
ተረንተራ (ተረን ተሪ)፡ ማፉዳ...ቦርሳ ኩፋዳ የገንዘብ መያዣ ። በግእዝ "ቍናምት" ይባላል ።
ተረኛ (ኞች)፡ ዘቡ ሥራው የርሱ...የኾነ ባለተራ ("ወርን" እይ) ።
ተረከ፡ አወጋ አወራ ያለፈ ነገርን ኣሳሰበ ("እንዲህ ነበር" አለ) ።
ተረከመ - ጠረቀመ)፡ ተተራከመ፡ ...ተሰበሰበ ተጠራቀመ ።
ተረከመ)፡ ትርንጎ
ተረከሰ፡ ቀለሰ አጐበጠ ።
ተረከረከ፡ ዕጥፍ ዘርጋ እለተወላገደ።
ተረከበ፡ ተቀበለ፡ (ረከበ) ።
ተረከበ፡ ተቀበለ፡ እጅ አደረገ።
ተረከበ፡ ካንዱ ወደ ሌላው ዐለፈ፡ ተሰጠ። (እንደ ተረከበው) እንደ ተቻለው፡ እንዳቅሙ፡ እንደ መጠኑ።
ተረከከ፡ ጠረቀቀ ሠነጠቀ ፈነከተ ።
ተረከዘ (ዐረ. ረከዘ/አቆመ የብስ ረገጠ)፡ ቀዘፈ ወደ ወደብ መርከብን...መራ ።
ተረከዘ ሎሚ፡ ተረከዙ ሎሚ የሚመስል ጫማው ንትብ ፈለግ ሥንጥቅ የሌ...ለበት ሰው ።
ተረከዘ፡ ዐጪር ።
ተረከዝ (ዞች)፡ የእግር ኋለኛ ጫፍ መርገ፵ መቆሚያ ሰኰና (ግብ. ሐዋ. ፫፡ ፯) ። ተረከዘ፡ ክት እግሯ የሚያምር ሴት ።
ተረከዝ የማይሸፍን መጫሚያ ነጠላ - ተረከዝን የማይሸፍን ቀጭን ጫማ። ዳግመኛም ረጃሌ እግርን ጕብዝናን ያስተረጕማል - በተጨማሪም ረጃሌ የእግርን ጕብዝናን ያሳያል።
ተረካቢ፡ የተረከበ፡ የሚረካብ፡ ተቀባይ።
ተረካቢነት፡ ተረካቢ መሆን፡ ተቀባይነት።
ተረካከሰ፡ ተሳሳጠ፡ ተቀባበለ።
ተረካካቢ፡ የተረካከበ፡ የሚረካከብ፡ ተቀባባይ።
ተረኰሰ፡ ሰበረ ኰሰተረ ኣለማ መብ...ራትን "
ተረወ፡ ደረሰ መጣ ።
ተረዘዘ፡ ተዘጋ፡ ተቈለፈ፡ በቤት ተቀመጠ - ተዘጋ፡ ተቆለፈ፡ በቤት ተቀመጠ። የተያዘ/የተረዘ እንዲሉ - የተያዘ/የተዘጋ እንዲሉ።
ተረደፈ፡ ተሰደረ, ተደረደረ, ተራ መታ - ተሰደረ, ተደረደረ, ተራው ደረሰ።
ተረዳ፡ ታዞ፣ ተደገፈ።
ተረዳ፡ የዘመዱን ሞት ሰማ። አጥብቆ ጠያቂ የናቱን ሞት ይረዳል።
ተረዳ፡ ፈጽሞ ዐወቀ ገባው ትምርቱ ነገሩ። (አልተረዳውም)፡ አልገባውም። ተረዳ፡ ተጠና፡ ታወቀ።
ተረዳጂ፡ የተረዳዳ፣ የሚረዳዳ፣ ተደጋጋፊ።
ተረጂ፡ የሚረዳ ሽማግሌ፣ መርዶ ሰሚ፣ ጠላት የመጣበት ሕዝብ (ኢሳ፩፡ ፫) ።
ተረገመ (ተረግመ)፡ ተለየ/ተካደ ።"ርጉም ተባለ በሌላ ወይም በገዛእፉ" ("(ዘዳ. ፳፩፥ ፳፫ ። ፩ሳሙ. ፳፭፥ ፳፪ ። ማር. ፲፬፥ ፸፩)")
።
ተረገረገ፡ ተንቀጠቀጠ, ተነቀነቀ, ተወዘወዘ ("ግፍና ጫፉ" - "ግፍና ጫፉ").
ተረገረገ፡ ታጨቀ. "መላ ተጠቀጠቀተጐደጐደ ግጥም እለ በዛ" - "መላ ተጠቀጠቀተጐደጐደ ግጥም እለ በዛ".
ተረገረገ፡ ኰራ, ተጓደደ, ተደገ.
ተረገዘ፡ ተፀነሰ ("በሆድ ቀረ ተቋጠረ ዘሩ ደሙ ልጁ ") ። (ተረት)
"የተረቱ በሆድ የዘለ በለምድ" ።
ተረገደ፡ ተጨፈረ / ተዘለለ / ተረገጠ / ተሸበሸበ
ተረገጠ (ተረግፀ)፡ በርግ፵ ተመታ/ተደበደበ ("(ነገ. ፱፥ ፵፫ ። ኢዮ. ፭፥ ፬ ። ኢሳ. ፲፬፥ ፲፱ ። ሉቃ. ፰፥ ፳)") ።"ረገጠ በማለት ፈንታ ተረ ገጠ ይላል ስሕተት ነው ። መዓርገ መላእክትን እንደ “ግማ ተረግጦ እንዲሉ መተርጕማን ።ተረገጠ ተፈረ ተዘለለ ተሸበሸበ ። እውነት ኾነ"
።
ተረገጠ/ተረገጠች፡ ተመታች/ተሰረረች ("ፈረሷ አህያዋ ") ።
ተረጋሚ፡ የሚረገም/የሚካድ ።
ተረጋገመ፡ ተካካደ/ተለያየ ።"እቀብርኸ አልደርስም እቀብሬ አትድረስ ተባባለ" ። መ
ተረጋገጠ፡ ርግጥ ("(ኾነ)")
ተኳዃኑ ተደ ላደለ ።
ተረጋገጠ፡ በእግር ተቃጠቀ/ተረማረመ ("(ሉቃ. ፲፪፥ ፩)") ። ላደለ ።
ተረጋጋ፡ ተጸናና/ተበረታታ
("(ተደራ ") ።
ተረጋጋ፡ ተጽናና/በረታ/ታገሠ/ቻለ
("(ተደራጊ)") ።
ተረጋጭ፡ የሚረገጥ ጭቃ ።
ተረግራጊ፡ የሚረገረግ/የሚወዘወዝ ("ኵሩ ተደጋጊ" - "ኩሩ ወይም ተደጋጋሚ").
ተረጐመ (ተርጐመ)፡ ከቋንቋ ወደ...ቋንቋ ገለበጠ መለሰ ፈታ ገለጠ አስረዳ (መጽሐፍ አሰማ ስለ ምን ነገረ አንድም ኣለ ዘረዘረ) ።
ተረጠበ፡ ርጥባን ተቀበለ፡ ተረዳ፡ ተገኘ ሰው።
ተረጠበ፡ ተሰጠ ገንዘቡ።
ተረጠጠ፡ ታመቀ፡ ተጨቈነ፡ ተቀመጠ፡ ተወዘፈ።
ተረጣቢ፡ የሚረጠብ፡ ተቀላች።
ተረጨ (ተረቅየ)፡ ተፈነጠቀ፡ ተበተነ፡ ተነዛ፡ ተወረወረ (ጠበሉ ጠለሸቱ) ("(ኢዮ. 41፡ 11)") - ተረጨ፡ ተበተነ
("(ኢዮ. 41፡ 11)"). የበሽተኛው ፊት በጠበል ተመታ - የበሽተኛው ፊት በጸበል ተረጨ። የኀጢአተኛው ሰውነት የጸሎት ውሃ ዐረፈበት
("(ዕዝ. 10፡ 22)") - የኀጢአተኛው ሰውነት የጸሎት ውሃ ነካው
("(ዕዝ. 10፡ 22)").
ተረጪ (ተረቃዪ)፡ የሚረጭ (ውሃ, ሽቶ, ራስ, ዕቃ) - የሚረጭ (ውሃ, ሽቶ, ራስ, ዕቃ) ።
ተረፈ (ተርፈ)፡ ዳነ ቀረ ተፈታ...ተፈወሰ ተተወ ።
ተረፈ መሧዕት፡ አኰቴት ።
ተረፈ፡ በዛ ከልክ ወለፈ ከመጠን በለ ። ("ከሀብታም ይተርፈዋል" እንዲሉ - "ተረት" - ላሳር የጣፈው ቢነግድ አይተርፈው) ።
ተረፈ ብንያም፡ የብንያም ነገድ ቅ...ሬታ (የሞት ትራፊ) ።
ተረፈ ኤርምያስ፡ የኤርምያስ መጽሐፍ (ደረቅ ትንቢት የሚናገር - ማቴ. ፳፯፡ ፱) ።
ተረፈ፡ ኾነ ደረሰ ። "ለጥኣን የወረደ ለጻድቃን ይተርፋል" ።
ተረፈሰ፡ አብዝቶ ዘግነ ዐፈሠ ተርፎ እስኪፈስ ቃመ
("ትፈረን" እይ) ።
ተረፈስ/ተርፋሳ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ተረፈረፈ፡ ተነሰነሰ፡ ተረበረበ፡ ተጐዘጐዘ።
ተረፈረፈ፡ ተጣለ፡ ወደቀ፡ ተለሸለሸ፡ ተኛ፡ ተጋደመ፡ የቍስለኛ የበሽተኛ ሽቶ።
ተረፈቀ፡ ተቀመጠ፡ ተወዘፈ፡ ተዘፈዘፈ፡ ተጨቈነ ወደ ታች ተባለ።
ተረፈጠ/ተረፈቀ፡ ተቀመጠ።
ተረፈፈ - ደረበበ)፡ አንተረፈፈ፡ መላ ቅዝ አደረገ፡ አንደረበበ ። አንተረፈፈ፡ የፈሳሽ ። አንደረበበ፡ የደረቅ ነው ።
ተረፋ) ተንተራፋ፡ ተሰበረ ተፈ...ለቀ ተጨማለቀ (ፈሰሰ ውሃው ደሙ) ።
ተረፋቂ፡ ሥራ ፈት ።
ተረፋቂ፡ የሚረፈቅ፡ ተወዛፊ።
ተረፍራፊ፡ የሚረፈረፍ፡ ሣር ቅጠል ጕዝ።
ተራ መታ፡ አተረተረ ተሰደረ ተደ...ረደረ ። ("በተራ በተራ"
- በቅደም ተከተል በረድፍ በረድፍ) ።
ተራ ሰው፡ አልባሌ ።
ተራ፡ ረድፍ፡ ተረረ ።
ተራ፡ ረድፍ ፊና ወረፋ (ዘፀ. ፳፰፡ ፲፱, ፳) ።
ተራ ቍጥር፡ ፩ኛ ፪ኛ እየተባለ...የሚጻፍ ።
ተራ፡ የሸቀጥ መደብ መደብር ስፍራ ። ("እኸል ተራ በግ ተራ ጌሾ ተራ አጣና ተራ ማእዘን ተራ ሰንጋ ተራ"
እንዲሉ) ።
ተራመመ፡ ተጠረገ፡ ተፈገፈገ፡ ታጠበ።
ተራመደ፡ ዐለፈ፡ ኼደ፡ ሠገረ፡ ተሻገረ፡ ገሠገሠ፡ ፈጠነ፡ ተደራራጊ ሲመስል በተደራ ጊነት መፈታቱን አስተውል።
ተራማሚ፡ የሚራመም፡ ተፈግፋጊ።
ተራማጅ (ጆች)፡ የተራመደ፡ የሚራመድ፡ ኻያጅ፡ ግሥጋሽ፡ ሠጋር፡ ፈጣን።
ተራማጅነት፡ ተራማጅ መኾን፡ ፈጣንነት።
ተራረመ (ተሐረመ)፡ ዕርም ተባ ባለ (ተለያየ - ተራራቀ ") ።
ተራረቀ (ተዓረቀ)፡ ተጐናበሰ ተሰ ማማ (ተወዳጀ ፥ ተፈቃቀረ ተሳሳመ ") ።
ተራረደ (ተሓረደ)፡ ተቀራደደ ።
ተራረፈ (ተዓረፈ)፡ ሸክምን ተቀባ በለ (ተረዳዳ ተጋገዘ ") ።
ተራረፈ፡ በበቅሎ የተቀመጠው በእ ግሩ ሲኼድ እግረኛው ተቀመጠ ።
ተራሪ፡ የተረረ/የሚተርር (ሠንጣቂ ደርዳሪ) ።
ተራራ ።
ተራራ፡ ረዥምና ከፍተኛ ዐምባ (ብርቱ ስፍራ የምድር ራስ) ።
ተራራማ፡ ተራራ ያለበት የበዛበት አገር (ባለተራራ) ።
ተራራም፡ ዝኒ ከማሁ ። ተራሮች፡ ዐምቦች (ዘፍ. ፬፡ ፭) ።
ተራራሰ፡ (ተራሐሰ)፡ ተራጠበ ።
ተራራቀ፡ (ተራሐቀ) ተነጣጠለ ተለያየ።
ተራራቂ/ተራሓቂ፡ የሚራራቅ የሚለያይ።
ተራቀቀ፡ ተጠበበ፡ ፈለሰፈ፡ ብልኅ ኾነ፡ ጥልቅ ነገር ተናገረ፡ ረቂቅ ተኳዃነ።
ተራቃቂ፡ የተራቀቀ፡ የሚራቀቅ።
ተራቃቂነት፡ ተጠባቢነት።
ተራቈተ (ተዐርቀ)፡ ተገፈፈ ታረዘ ባዶ ኾነ ("(ተጋፈፈ)") ።
ተራቈተ፡ ታረዘ፡ ዐረቀ ።
ተራቋች፡ የሚራቈት/የሚታረዝ ።
ተራበ፡ ባዶ ኾነ
("ችጋር ያዘው ምግብ ሻ ፈለገ ") ("(ማቴ. ፬፥ ፪ ። ፳፩፥ ፲፰)")
።
ተራቢ፡ የሚራብ ።
ተራቢ፡ የተረበ/የሚተርብ (ቀልደኛ አላጋጭ ፌዘኛ) ።
ተራባ (ተራብሐ)፡ ተዋለደ/ተባዛ ። "የረባ የራበ ተደራራጊና ተደራጊ ኀላፊ ትንቢት በጽፈት ሲገጥሙ ይራባሉ (ይትራብሑ ሀለዉ) ይራባሉ (ይርኅቡ ሀለዉ) ይላል ።ባንደኛው ራን ባን በኹለተኛው ራን ብቻ አጥብቅ" ።
ተራተረ፡ ፈታታ ለያየ ሠነጣጠቀ...ፈነካከሉ ።
ተራታ/ተራትዐ፡ ተቃና ነገሩ።
ተራች (ቾች)፡ የተረተ/የሚተርት (ጥሳ መሰል) ።
ተራከሰ፡ (ረከሰ) ተነካካ፡ ተዳደፈ፡ ርኩስ ተኳዃነ፡ ተናናቀ።
ተራከበ፡ ተቀራመተ፡ ተናጠቀ፡ ተሠናጠቀ፡ ተካፈለ፡ ተተናተነ፡ ተሻማ፡ ተቃማ። ዥቦችሌ ሊት በዱር አንድ እህያ አገኙና ተራከቡት።
ተራከበ፡ ተናኘ፡ ተጋጠመ፡ ተዳረሰ።
ተራከባ፡ (ተከተበ) ተጋባ፡ ተመሳቀለ።
ተራኪ (ዎች)፡ የተረከ/የሚተርክ (ወግ ዐዋቂ) ።
ተራክቦ፡ የጨረቃና የፀሓይ መገናኘት፡ መነጻጸር፡ በመርሐዕዉር ዐውደ አበቅቴ ይባላል፡ ፲፱ ዓመት ነው።
ተራኰተ፡ ተፋተ፡ ተናነቀ፡ ተጋፋ፡ ታገለ። ዥቦች ጥንብ ስላገኙ ዛሬ ሌሊት ሲራኰቱ አደሩ።
ተራኳች፡ የተራኰተ፡ የሚራኰት፡ ተከራካሪ ታይ።
ተራወጠ፡ ተሯሯጠ፡ ተባረረ፡ ተሽቀዳደመ - ተሯሯጠ፡ ተባረረ፡ ተሽቀዳደመ።
ተራዋጭ፡ ተሯሯጭ፡ የሚራወጥ/የሚሯሯጥ፡ ተባራሪ፡ ተሽቀዳዳሚ፡ ድፍርስ ቅራሪ - ተሯሯጭ፡ የሚባረር፡ የሚሽቀዳደም፡ ግራ የሚያጋባ።
ተራዘመ፡ ተባለጠ፡ ተበላለጠ፡ ተራራቀ፡ ተባዛ፡ ተበራከተ - ተበለጠ፡ ተራራቀ፡ በዛ፡ በራከተ።
ተራዛሚ፡ የተራዘመ/የሚራዘም፡ የሩቁን የሚያቀርብ መነጽር፡ በሩቅ የሚመታ መድፍ፡ አሸጋጋሪ - የረዘመ/የሚረዝም፡ የሩቅን የሚያቀርብ መነጽር፡ በሩቅ የሚመታ መድፍ፡ አሻጋሪ።
ተራደፈ፡ ተከታተለ, ተቀጣጠለ, ቅደም ተከተል, ተኳዃነ፡ ተደራረበ - ተከታተለ, ተቀጣጠለ, ተስተካከለ፡ ተደራረበ።
ተራዳ (ሠርዌ)፡ ተርክሓ የድንኳን ምሰሶ ዋልታ ደጋፊ ተሸካሚ።
ተራዳ ተረከከ
ተራዳ፡ ተረዳዳ፡ ተቀባበለ፣ ተፈራረቀ፣ ተራረፈ፣ ተጋዘ፣ ተደጋገፈ (፪ዜና፡ ፳፥ ፳፫) ።
ተራዳ፡ የድንኳን ምሰሶ፡ ረዳ ።
ተራድኦ፡ መራዳት (ግእዝ) ።
ተራዶች፡ ፫ ወይም ፬ የድንኳን ምሰሶዎች (ዘኍ፡ ፳፮) ።
ተራገመ፡ ረገሙ ("(ምሳ. ፳፯፥ ፲፬)")
። "ተራገመ ተደራራጊ ሲኾን አድራጊ መኾኑ በል ማድ ነው እንጂ በቋንቋው ሕግ አይዶለም ።ተራጋሚ/ረጋሚ፡ የሚራገም ጥቍር ምላስ" ።
ተራገመ፡ ተሳደበ ።
ተራገበ፡ ተጓረበ ("ነፋስ ተሰጣጠ ተቀባበለ ተናፈሰ")
ተራገጠ (ተራገፀ)፡ በርግ ተማታ/ ተላፋ/ተጫወተ/ተዛለለ ።(ተረት)፡ "አህያ ላህያ ቢራቱጥ ጥርስ አይሳበር" ።
ተራገጠ፡ ረገጠ ("(አድራጊ)")
።
ተራገጠ፡ ተዳካ/ተዋሰነ/ተካለለ ("(ተደ ራራ.)")
።
ተራገፈና/አራገፈ፡ "ተደራራጊና አደራራጊ ሲመስል በተደራጊነትና ባድራጊነት መፈታቱን አስተውል" - ተደራራጊና አደራራጊ ሲመስል በተደራጊነትና ባድራጊነት ያለውን ልዩነት አስተውል።
ተራጋ፡ ተጻና/ተበራታ ።
ተራጋጭ (ጮች)፡ የሚራገጥ ከብት ። ተራጋጭ/ረጋጭ ።
ተራጋጭነት፡ ተራጋጭ መኾን ።
ተራጋፊ፡ የሚራገፍ ("ልብስ ተራጋፊ ነው" - ልብስ የሚራገፍ ነው፡ "የጋማ ከብት መጫሚያ ተራጋፊ ነው"
- የጋማ ከብት መጫሚያ የሚራገፍ ነው).
ተራጠበ፡ ተረጣጠበ፡ ተራራሰ፡ ተሳሳጠ፡ ተቀባበለ።
ተራጨ (ተራቀየ)፡ ተፈናጠቀ, ተባተነ - ተረጨ, ተበተነ። መራራት መፈናጠቅ/መባተን - መራጨት/መበተን። መራጫ መፈናጠቂያ/መባተኛ - መርጫ። ተረጯ ተበታተነ/ተፈነጣጠቀ - ተረጩ ተበታተኑ/ተረጩ። መረጨት መፈነጣጠቅ - መረጨት/መበተን። መረጫ መፈነጣጠቂያ - መርጫ።
ተራፊ፡ የሚተርፍ/የሚቀር (ዳኝ ቀሪ ተረፍ ቅሬታ) ።
ተሬ፡ ተራማ፡ ተረረ ።
ተሬ፡ ተራዊ ተራማ (የተራ አንድ የወንድ ልጅ ሽሩባ በራስ አማካይ ከግንባር እስከ ማዥራት ያለ ዕሽም ተረተር መስሎ የሚታይ) ።
ተሬ፡ ታናሽ ጕባ ቍልልታ ። ተር፡ ቀጥ ።
ተር፡ ቀጥ ተረረ ።
ተር አለ፡ ቀጥ አለ ።
ተር አደረገ፡ ቀጥ አደረገ ።
ተርመሰመሰ፡ ተንቀሳቀሰ፡ ተነቃነቀ፡ ተላወሰ።
ተርመስማሽ፡ የሚርመሰመስ፡ ተንቀሳቃሽ፡ ተላዋሽ።
ተርመጠመጠ፡ ረመጥ ላይ ተንደባለለ፡ ተኵለፈለፈ፡ ተልከሰከሰ ሥጋው።
ተርመጥማጭ፡ የሚርመጠመጥ፡ ተልካሽ።
ተርሞጠሞጠ፡ ዝኒ ከማሁ።
ተርሴስ፡ በእስያ ክፍል ያለ አገር (መዝ. ፸፪፡ ፲) ።
ተርበተበተ፡ ተንተባተበ/ተንቀጠቀጠ ።
ተርበትባች፡ የሚርበተበት ።
ተርበደበደ፡ ፈራ/ተንበደበደ/ተንቀጠ ቀጠ ።
ተርበድባጅ፡ የሚርበደበድ ።
ተርቡት፡ ጨቅጫቃ ሴት አፈኛ ነገረኛ ያ ቢስ ።
ተርብ (ቦች)፡ የተንቀሳቃሽ ስም (በ...መርዙ የሚነድፍ በክንፉ የሚበር - "የውሻ ሳንጃን" እይ - ንብ) ።
ተርቦ፡ ጦሙን ውሎ ዐድሮ ሰንብቶ ።"ኣቶ እከሌ ተርቦ ተጠምቶ ቤት ሠራ"
።
ተርታ፡ መናኛ፡ ተረረ ። ተረተረ (ተረረ)፡ ስፌትን ጥምጥምን...ፈታ ለየ ክርን ሢርን መዘዘ በጠሰ ("ተለተለን" እይ) ።
ተርታ፡ መናኛ ትሑት ተራ መደዳ (፩ነገ. ፥ ፮፡ ፴፯፡ ፯፡ ፲፪፡ ዕብ. ፱፡ ፭) ።
ተርታ ሰው፡ ሹመት ማዕርግ የሌለው ተራ ሰው ።
ተርታ ነገር፡ ቁም ነገር ያልኾነ...ጕዳይ ።
ተርታሪ፡ የተረተረ/የሚተረትር (ሠንጣቂ ፈንካች ጨፍላቂ) ።
ተርከፈከፈ፡ ተረጨ፡ ተረበረበ፡ ተንጠባጠበ።
ተርከፍካፊ፡ የሚርከፈከፍ ውሃ፡ ሽቱ፡ መድኀኒት።
ተርካሳ፡ ቀላሳ ጐባጣ ጕብር ።
ተርካኪ፡ የተረከከ/የሚተረክክ (ጠርቃቂ ሠንጣቂ ፈንካች) ።
ተርኳሽ፡ የተረኰሰ/የሚተረስ (ኰስታሪ) ።
ተርገበገበ፡ ተንዘፈዘፈ / ተወዘወዘ / ተነቀነቀ ("ተለማመጠ ልምጥልምጥ ዕጥፍ ዘርጋ ክፍት ክድን አለ")
ተርገብጋቢ፡ የሚርገበገብ / ተለማማጭ
ተርገደገደ፡ ተንደገደ/ተፍገመገመ ።
ተርገድጋጅ፡ የሚርገደገድ ።
ተርገፈገፈ፡ ተወዘወዘ ሥጋው (ሥጋው ተወዘወዘ).
ተርጓሚ (ሞች)፡ የተረጐመ/የሚተረ...ጕም (ሊቅ የብሉይ የሐዲስ የሊቃውንት ሻህር) ። የመጽሐፈ መነኮሳት መምር ።
ተርጓሚ፡ ደርጋሚ (ንባብን በትምርጓሜ የሚያስተባብል - ፪ጴጥ.
፫፡ ፲፯) ።
ተርፋ፡ ትርሽማ
ተርፋ አለ፡ ደነገጠ ተከፈለ ዘለለ...ፈሰሰ ።
ተርፋሽ፡ የተረፈሰ/የሚተረፍስ (ዘጋኝ...ቃሚ) ።
ተርፍ፡ ድንጋጤ ዝላይ መደንገጥ መ...ዝለል (የልብ) ።
ተሸ፡ ተተኰሰ/ተቀቀለበት/ተጋገረበት (ሥራ ለመደ ሸክላው) ።
ተሸለለ፡ ተሸለተ ተሸነገለ ።
ተሸለለ፡ ተሸደሸደ ተወሰወሰ ተቶረበ ተያያዘ ተጋጠመ ተሰፋ ።
ተሸለለ፡ ኾነ ተደረገ ተባለ (ስለላው) ።
ተሸለመ፡ ሽልማት ተቀበለ (ለበስ) ።
ተሸለመ፡ ተሣለ ተነቀሰ ተመሰለ ተጌጠ ተዥጐረጐረ ።
ተሸለቀቀ፡ ተቀደደ ተላጠ ተገፈፈ (ከቈዳ ከቅርፊት ውስጥ ወጣ ተለየ) ።
ተሸለቀቀ፡ ጠበበ ቀጠነ ።
ተሸለተ (ተቀርፀ)፡ ተቀረፀ ተቈረጠ (በጉ - ዘዳ. ፲፰፡ ፬፡ ማሕ. ፬፡ ፪) ።
ተሸለተ፡ ተጠረበ ተላገ ሾለ ።
ተሸለገ፡ ታሰበ ተለካ ተሰላ ተገመተ ተገመገመ ።
ተሸለፈ፡ ሣሣ ቀለለ ።
ተሸለፈ፡ ተታለለ ተሸነገለ ።
ተሸለፈፈ፡ ተለፈፈ ተላከ ።
ተሸላለመ፡ ተጊያጊያጠ ጌጥ ተቀባበለ (የመሸለም ብድር ተከፋፈለ) ።
ተሸላለገ፡ ተጎማመተ ተገማገመ ።
ተሸላላሚ፡ የሚሸላለም/የሚጊያጊያጥ ።
ተሸላሚ፡ የሚሸለም ።
ተሸላች፡ የሚሸለት/የሚቀረፅ (ተቈራጭ) ።
ተሸላጊ፡ ሚሸለግ (ተገምጋሚ) ።
ተሸመሸመ፡ ተከረተፈ ተፈ ተሸረ...ከተ ።
ተሸመቀ፡ ተደፈጠ ።
ተሸመቀቀ፡ ተሳበ ዐጠረ (ተጨመደደ ተጠጋ ጠበበ) ።
ተሸመተ፡ ተገዛ ተሸጠ ተለወጠ (ለገዢ ተሰጠ) ።
ተሸመተረ፡ ተሸነቈጠ ተገረፈ ።
ተሸመጠጠ፡ ተሮጠ ተጋለበ ።
ተሸመጠጠ፡ ተዠመዥ ተፈተለ ተ...ሠራ (እሸቱ ፈትሉ ሽሩባው) ።
ተሸመጠጠ፡ ተጌጠ ተሸለመ ተደ...ጐሰ ።
ተሸመጠጠ፡ ተጠጣ ተለጠ ።
ተሸመጠጠ፡ ታሰለ ተዋሸ ።
ተሸመጠጠ፡ ታጠረ ተዋሰበ ።
ተሸማመቀ፡ ተደፋፈጠ ።
ተሸማመተ፡ ተገዛዛ ተሻሻ ተለዋ...ወጠ ።
ተሸማቀቀ፡ ተሳስበ ተጣበበ ተጨማ...
ተሸማች፡ የሚሸመት/የሚገዛ/የሚሼጥ ።
ተሸረሞጠ፡ ተሠረጓጐደ ።
ተሸረሸረ፡ ተበረበረ ፈረሰ ተነደለ ።
ተሸረበ፡ ተደበለ ተጠሞረ ተደረበ ተታታ ።
ተሸረከተ፡ ተቀደደ ተዘረከተ ። "ተሸረከተ እንዳገኘ ተናገረ"።
ተሸረካከተ፡ ተቀዳደደ ተዘረካከተ ።
ተሸረደመ፡ ተቈረጠመ ታኘከ በብዛት ።
ተሸረደደ፡ ታማ ተነቀፈ ተለገጠ ተ...ሾፈ ።
ተሸረጠ፡ ወጣ ተገለለ ጋኔኑ ። "ተሸርጦለታል"
- ገለል ብሎለታል።
ተሸረፈ፡ ተመነዘረ ተዘረዘረ በዛ ።
ተሸረፈ፡ ተሰበረ ተቈረሰ ።
ተሸረፈ፡ ተነቀለ ተመዘዘ ።
ተሸራሞጠ፡ ፈሳ ተጓደለ ሸሸ ተሠረጐደ (ወጣ ገባ ኾነ) ።
ተሸራረፈ፡ ተሰባበረ ተቈራረሰ ።
ተሸራሸረ፡ ተጓደለ ተቃለለ ተፈጋ ፈገ (የምግብ የሰው) ።
ተሸራሽቶ፡ ተደላድሎ ተመቻችቶ ። "ተሸራሽቶ ተቀመጠ ቆመ"
እንዲሉ ።
ተሸራከተ፡ ተቃደደ ተዘራከተ ።
ተሸራጭ፡ የሚሸራሞጥ ።
ተሸራፊ፡ የሚሸረፍ/የሚመነዘር (ሸክላ) ።
ተሸርሻሪ፡ የሚሸረሸር (ቦረቦር) ።
ተሸሸ፡ ኾነ ተደረገ ሽሽቱ ።
ተሸሸገ፡ ተደፈነ ታባተሰወረ ተደበቀ (ዘፍ. ፫፡ ፰, ፲፡ ፩ሳሙ. ፲፡ ፳፪፡ ምሳ. ፳፪፡ ፫) ።
ተሸሻጊ፡ የሚሸሸግ (ተደባቂ) ።
ተሸቀጠ፡ ተሸጠ ተለወጠ ተገዛ ።
ተሸቈረረ፡ ተጠየፈ ተሠቀቀ ።
ተሸበለለ፡ ተጠቀለለ ።
ተሸበለቀ፡ ሾለ/ገባ/ተቀረቀረ (በሽብልቅ ተወጋ) ።
ተሸበረ፡ ደነገጠ/ፈራ/ታወከ/ተበጠበጠ (ግርግር ድብልቅልቅ አለ - ግብ.ሐዋ. ፲፱፡ ፳፱) ።
ተሸበሸበ፡ ተሸነሸነ/ተጠጋጋ/ተቀራረበ ።
ተሸበበ፡ ተጠለፈ/ታሰረ (በቅሎው ፈረሱ አህያው ግመሉ ታበተ ሽቢያው ለኮው) ።
ተሸባ፡ ተበጀ/ተለጠፈ/ታሰረ ።
ተሸባለለ፡ ተጠቃለለ ።
ተሸባሪ፡ የሚሸበር ።
ተሸባቢ፡ የሚሸበብ/የሚታበት ከብት ።
ተሸብሻቢ፡ የሚሸበሸብ ልብስ ።
ተሸተረ፡ ተሸለመ ተጌጠ ተንቈጠቈጠ ።
ተሸተተ፡ ካፍንጫ ገባ ተሳበ ተማገ ።
ተሸታሪ፡ የሚሸተር ።
ተሸነ፡ ጭርቅ አለ ተለቀቀ ተንፎከፎክ ወረደ ፈሰሰ ተንዣረረ ።
ተሸነሸነ፡ ተሸበሸበ ተጠጋጋ (በመቀነት በክር) ተሠነጠቀ (በጥልቆ) ።
ተሸነቀረ፡ ተሰበሰበ ታጠፈ ተቀነፈ ተሸጐጠ ።
ተሸነቈረ፡ ተበሳ ተነደለ ተቀደደ ።
ተሸነቈጠ፡ ተገረፈ ተሸመተረ ሾጥ ተደረገ ተመታ ።
ተሸነቋቈረ፡ ተበሳሳ ተቀዳደደ ።
ተሸነተረ፡ ተበጣ ተቀደደ ።
ተሸነታተረ፡ ተበጣጣ ።
ተሸነከፈ፡ ታጠፈ ተኰረተመ ታሰሪ ።
ተሸነጠ፡ ተበለተ ተነጠለ (ተለየ ወጣ) ።
ተሸነፈ፡ ድል ኾነ ተረታ ተመታ...ተሻረ (ታከተ ደከመ) ።
ተሸነፈጠ፡ ታጠፈ ተዘቀዘቀ ።
ተሸናቈጠ፡ ተጋረፈ ተማታ ።
ተሸናነፈ፡ ድል ተነሣሣ ተረታታ ።
ተሸናፊ (ፎች)፡ የሚሸነፍ (ድል...ዃኝ) ።
ተሸንቋሪ፡ የሚሸነቈር/የሚበሳ (ተበሺ) ።
ተሸንቶ ዐደረ፡ ጥቂት መንገድ ኼዶ ሌሊቱን በውጭ አሳለፈ ።
ተሸንካፊ፡ የሚሸነከፍ (ዐመለኛ ከብት) ።
ተሸኘ፡ ከሰው ጋራ ዐብሮ ኼደ ።
ተሸኚ፡ የሚሸኝ (መንገደኛ) ።
ተሸኛኘ፡ ተሰነባበተ ።
ተሸከመ፡ ሸክም ኾነ ተያዘ ታዘለ (ል...ማዱ ግን አድራጊነት ነው) ።
ተሸከመ፡ ያዘ (ዘለ ተነ ተደበለለ ቻለ - ፬ነገ. ፰፡ ፬፡ ማቴ. ፲፩፡ ፳፱፡ ሉቃ. ፪፡ ፳፰) ።
ተሸከሸከ፡ ተሸደሸደ ተዘረዘረ ተዘከዘከ ።
ተሸከሸከ፡ ተወቀጠ ።
ተሸከፈ፡ ተተፈተፈ ጠቀነ ።
ተሸካሚ (ሞች)፡ የተሸከመ/የሚሸከም (፩ሳሙ. ፴፩፡ ፬-፭፡ ነሐ. ፬፡ ፲፯) ። "አላህ ተሸካሚ ብለምነው ሸክም አዘዘብኝ"
ተሸካከመ፡ ሸክምን ለማንሣት ተጋዝ ተረዳዳ (የማሸከም ብድር ተከፋፈለ እንኮኮ ተባባለ ተዛዘለ) ።
ተሸካከረ፡ ተቀያየመ ።
ተሸክሻኪ፡ የሚሸከሸክ (የገብስ ቈሎ) ።
ተሸያየተ፡ ዕጣ ተጣጣለ ።
ተሸያጭ፡ የሚሼጥ/የሚለወጥ (ተለዋጭ ሽያጭ - ሤጥ)፡ ዋጋ ለውጥ ። በሸቀጥና በንግድ ዕቃ ፈንታ
"ሽያጭ" ይላል (ራእ. ፲፰፡ ፲፩) ።
ተሸደሸደ፡ ተወሰወሰ/ተሸከሸከ/ተሸ...ለለ ።
ተሸዳሸደ፡ ተወሳወሰ ።
ተሸጋሸገ፡ ተፈጋፈገ/ተራራቀ፡ ወይም ተጠጋጋ/ተቀራረበ ።
ተሸጋሻጊ፡ የሚሸጋሸግ (ተራራቂ ተቀ...ራራቢ) ።
ተሸጋገረ፡ ካንዱ ግንብ ጫፍ ወደ ሌላው መደምደሚያ ተላለፈ (ተዳረሰ - ዐለፈ ደረሰ - ካመት ዓመት) ።
ተሸጋገነ፡ ተዋዋበ/ተቈነዣዠ ።
ተሸጋጋሪ፡ የሚሸጋገር (ጋድም ሠረገላ ተላላፊ በሽታ) ።
ተሸጋጋሪነት፡ ተላላፊነት ።
ተሸጐረ፡ ተወረወረ/ተቀረቀረ ።
ተሸጐበ፡ ታጠፈ/ተቀለሰ ።
ተሸጐጠ፡ ገባ/ተወተፈ/ተደበቀ/ተሸሸገ (ኢያ. ፰፡ ፬) ።
ተሸጓሪ፡ የሚሸጐር (መወርወሪያ) ።
ተሸጓጭ፡ ሰንበሌጥ ።
ተሸጓጭ፡ የሚሸጐጥ (ተደባቂ) ።
ተሸፈሸፈ፡ ታጨደ ተቈረጠ ።
ተሸፈነ፡ ለበሰ ተከለለ ተጋረደ (ተጨፈነ ዘውስጥ ኾነ ተከደነ) ።
ተሸፈጠ (ተሰፍጠ)፡ ተከዳ ተካደ...ዐሎ ተባለ ተሞኘ ተሸነገለ ።
ተሸፋኝ፡ የሚሸፈን ።
ተሸፋፈነ፡ ተከናነበ ።
ተሸፋፈጠ፡ ተከዳዳ ተካካደ ።
ተሸፋፋኝ፡ የሚሸፋፈን (ተከናናቢ) ።
ተሸፋፍኖ፡ ተከናንቦ ። "ተሸፋፍኖ በተኙ ገልጦ የሚወጋ ጌታ አለ"።
ተሹለከለከ፡ በደን በጥሻ ውስጥ ለውስጥ ዐለፈ ።
ተሻ፡ ተፈለገ/ተፈቀደ ።
ተሻለ (ኀየሰ)፡ በለጠ ተመረጠ ረባ ጠቀመ ። "ከመሞት መሰንበት ይሻላል" ። (ተረት)፡ "ከውነት የሚሻል ሐሰት ከመውጋት የሚሻል መሳት"።
ተሻለ፡ በለጠ፡ (ሻለ) ።
ተሻለው፡ በጎ ኾነ ።
ተሻለገ፡ ተጋመተ ተሳሰበ ተሳላ ።
ተሻመቀ፡ ተዳፈጠ ተዳባ (ሉቃ. ፳፩፡ 96) ።
ተሻመተ፡ ተላወጠ ።
ተሻሚ፡ የሚሻማ (ተናጣቂ ተቃሚ) ።
ተሻማ (ተማሠጠ)፡ ተጋራ ተፋለመ ።
ተሻማ፡ ተናጠቀ፡ (ጥማሻማ) ።
ተሻረ (ተስዕረ)፡ ተዋረደ (ሹመት ዐጣ ከማዕርግ ተሰናበተ - "አዝማሪ - አገራችን ደጋ እርሻው በደጃችን ያ ቢሾም ያ ቢሻር እኛ ምን ተዳችን")
።
ተሻረ፡ ዐለፈ ቀረ ።
ተሻረ፡ ጠፋ ተፈታ (ድል ኾነ ፈረሰ) ።
ተሻረከ፡ ተወዳጀ ተባበረ ተጋጠመ ።
ተሻሪ (ተሰዓሪ)፡ የሚሻር ።
ተሻራኪ፡ የሚሻረክ (ተባባሪ) ።
ተሻሸ (ተሐሰየ)፡ የማሸትን ፥ ብድር' ተከፋፈለ ተመላለሰ ።
ተሻሸ፡ ዳተኛ ዝግተኛ ኾነ (ፍጥነት ዐጣ ") ።
ተሻሻለ፡ ታደሰ ተጠገነ ተለዋወጠ አማረ ። "ተሻሻለ"
የተሻለ ድርብና ተደራራጊ መኾኑን ልብ አድርግ ።
ተሻሻጠ (ተሳሐጠ)፡ ተታከለ/ተሳካ ።
ተሻሻጠ (ተሣየጠ)፡ ተገበያየ/ተገዛዛ/ተለዋወጠ/ተቀባበለ ።
ተሻሻጠ፡ ተለዋወጠ (ሸየጠ) ።
ተሻሻጭ (ተሣያጢ)፡ የሚሻሻጥ (ተለ...ዋዋጭ) ።
ተሻበ (ተስሕበ)፡ ተመዘዘ/ቀጠነ/ተጠመጠመ ።
ተሻተተ፡ ተጣጠነ ሽታ ተቀባበለ...ተጫሰ ተነፋነፈ ።
ተሻታች፡ የሚሻተት ።
ተሻኰተ፡ ተወዳደረ/ተፈካከረ
("እገና" ተማታ ተጣፋ - ተጻፋ - ዕቃን ለመግዛትና ለመሼጥ ለመርታትና ለመረታት) ።
ተሻኳች (ቾች)፡ የተሻኰተ/የሚሻኰት (ተወዳዳሪ) ።
ተሻወተ፡ ተሻኰተ/ተቈታቸ ።
ተሻጋሪ፡ የሚሻገር/የሚያልፍ ።
ተሻጠ (ተስሕጠ)፡ ተተከለ/ተሰካ/ተሳና (ቆመ) ።
ተሻጭ (ተሰሓጢ)፡ የሚሻጥ/የሚሰካ ።
ተሻፈነ፡ ተካለለ ።
ተሼጠ (ተሠይጠ)፡ ተለወጠ (ለገዢ ተሰጠ - መዝ. ፻፭፡ ፲፯) ።
ተሽ፡ የደጊመ ቃል ተደራጊ አንቀጽና ቅጽል ባዕድ መነሻ ። ("ከረከረ - ተሸከረከረ" - "ተሽከርካሪ" - "ቈጠቈጠ - ተሽቈጠቈጠ ተሽቈጥቋጭ" - "ቀረቀረ - ተሽቀረቀረ ተሽቀርቃሪ") ።
ተሽላል፡ ግብዝ ነገር ሸፍጥ ሽንገላ ።
ተሽሎታል፡ ጤና አግኝቷል ።
ተሽመለመለ፡ መኼድ አቃታው፡ ዕጥፍ ዕጥፍ አለ እግሩ።
ተሽመለመለ፡ ተሸበለለ።
ተሽመለመለ፡ ተሸበለለ፡ (መለ) ።
ተሽመደመደ፡ ተቅመደመደ (ወገቡ ተገመደ እግሩ) ።
ተሽሞነሞነ፡ ተሸፈነ ተከናነበ ተኵ...ነሰነሰ (ተሽኰነተረ ተሸተረ) ።
ተሽሞንጝኝ፡ የሚሽሞነሞን (ተሽኰን...ታሪ) ።
ተሽረከረከ፡ ተፍረከረከ ፈረሰ (ሽርክናው ምክሩ ዐድማው ሤራው) ።
ተሽቀረቀረ፡ ተሸለመ አጌጠ ተጌጠ ።
ተሽቀርቃሪ፡ የሚሽቀረቀር (ጌጥ ወዳድ
") ።
ተሽቀነደረ፡ ተቀናጣ ቀነደረ ።
ተሽቀነደረ፡ ተደሰተ የኵራት አካኼድ ኼደ፡ ተቀናጣ ዘለለ ።
ተሽቀነጠረ፡ ተወረወረ ተጣለ ።
ተሽቀንዳሪ፡ የሚሽቀነደር (ዘላይ
") ።
ተሽቀንጣሪ፡ የተሽቀነጠረ/የሚሽቀነጠር (ተወርዋሪ
") ።
ተሽቀዳደመ፡ ተቀዳደመ ተሯሯጠ ! በ ሩጫ ተበላለጠ ።
ተሽቀዳዳሚ፡ ተቀዳዳሚ (የተሽቀዳደመ የሚሽቀዳደም
") ።
ተሽቈለቈለ፡ ተቈለቈለ ።
ተሽቈመቈመ፡ ተጠራ ተሽኰመኰመ ።
ተሽቈመቈመ፡ ፊትን መለሰ ጠመ ዘዘ ከማእድ ።
ተሽቈጠቈጠ፡ ፈራ ተንቀጠቀጠ ተለ ማመጠ ተርገበገበ ።
ተሽቈጥቋጭ፡ የሚሽቈጠቈጥ (ፈሪ ርግ ብግብ ተለማማጭ
") ።
ተሽበለበለ፡ ተባበለ ተለመነ ተገለገለ ተቈላመጠ ።
ተሽከረከረ፡ - ተንደረደረ -, (ከረ) ።
ተሽከረከረ፡ ዞረ ("ሾረ ኼደ ተንደረደረ ተንከባለለ እግዜር ዐሙስ ከባሕር ዐርብ ከየብስ በእግር የሚሽከረከሩ በክንፍ የሚበሩ ፍጥረቶች ፈጠረ እነዚሁም እንስሶችና አሞሮች (ወፎች) አውሬዎች ናቸው ተሽከርካሪ (ሮች) የሚዞር የሚሽ ከረከር እንስሳ አውሬ መኪና በያይነቱ ሽክርክር የተሽከረከረ ሽክርክር አለ ተሽከረከረ ሽክርክሪት (ቶች) ከቀጪን ዕንጨት ጋራ የተዋደደች የንዝርት ራስ ወይም ገል የልጆች መጫወቻ ሴቴ ሬት የዝንጀሮ ቂጣ፥ ክብ የመንኰራኵር ብረት ክሊሊ መሽከርከር መዞር መሾር መንከባ ለል መሽከርከሪያ እግር መንኰራኵር መሽከርከሪት ታናሽ መኪና (ቢስክሌት) ተከራከረ ተገተ ተፈካከረ በነገር ተመላለስ ነው አይዶለም ተባባለ ተፈታጨቀ እምነት ክደትን ተነጋገረ ") (ዘፍ. ፳፮፡ ፳፡ ኢሳ. ፵፩፡ ፲፩፡ ሉቃ. ፪፡ ፴፬) ።
ተሽኰመኰመ፡ ተሽቈመቈመ ("ተጠራ ተሽኰረመመ ተጫወተ ተዳራ ") ።
ተሽኰረመመ፡ ተዳራ ("ተግደረደረ ተሽኰርማሚ የተሽኰረመመ የሚሽ ኰረመም ተግደርዳሪ ወንድና ሴት እንስት ዶሮ መሽኰርመም መግደርደር መዳራት መሽኰርመሚያ መግደርደሪያ መዳ ሪያ ስፍራ ጊዜ ") ።
ተሽኰነተረ፡ አጌጠ ("ተጌጠ አማረ ባልታጠበ እጅ አትንኩኝ አለ ") ።
ተሽኰንታሪ፡ የተሽኰነተረ/የሚሽኰነ ተር ።
ተሽጐደጐደ/ተዥጐደጐደ (ዠጐደ) ።
ተሽጠጠ፡ ተባለ፡ ተነገረ፡ ኾነ፡ ተደረገ፡ ሽሙጡ፡ ተሸረደደ፡ ተቀለደበት፡ ሰውየው ።
ተሾ
ተሾለከ (ሾለከ)፡ ሳይታይ ተሰርቆ ኼደ ።
ተሾለከ፡ ታለፈ ተወጣ ሳንው ።
ተሾመ (ተሠይመ)፡ ከበረ ሥልጣን አገኘ (ስም አወጣ፡ አገር ገዛ) ።
ተሾመ፡ ተመላ ምሉ ኾነ ።
ተሾመ፡ ተበጀ ተዘጋጀ ።
ተሾመ፡ ታከበ ተሰበሰበ ።
ተሾመ፡ ዝም ጥርቅም አለ ሻረ (ሰ ዐረ) ። "ብለኸ ተሻረን" ተመልከት ።
ተሾካሾከ፡ በሹክታ ተነጋገረ ።
ተሾካሿኪ፡ የተሾካሾከ/የሚሾካሾክ ።
ተሾፈ፡ ተቀለደ ተዘበተ ።
ተሿለከ፡ በጠባብ በር ተላለፈ ።
ተሿሚ፡ የሚሾም/የሚሸለም ።
ተሿሿመ፡ ማዕርግ ተቀባበለ (ሹም ተኳዃኑ ተሸላለመ - እንደ አትናቴዎስና እንደ እንጦንስ) ።
ተሿሿሚ፡ የሚሿሿም ።
ተቀለመ—ተያዘ/ቀለበ ።
ተቀለሰ፡ ተመለሰ ጐበጠ ተቈለፈ ።
ተቀለበ፡ ተመገበ በላ ጠጣ
("(ኤር. ፭፥ ፰)") ።
ተቀለበ፡ ተያዘ ተጨበጠ ።
ተቀለበሰ፡ ከጫፍ ታጠፈ ተሸነቀረ ተቀነፈ ።
ተቀለበሸ፡ ተመለሰ ተገለበጠ ።
ተቀለተ፡ ተረጠበ ተረዳ ታገዘ ።
ተቀለደ፡ ተሾፈ ተቧለተ ተተረበ
ተቀለጠመ፡ ተመታ ተሰበረ ።
ተቀለጣጠመ፡ ተሰባበረ ።
ተቀለጣጠፈ፡ ተከነዋወነ ተጣጣመ ።
ተቀለፈፈ፡ ተቀፈፈ ተቈረጠ ።
ተቀላ (ተቀልዐ)፡ ተመታ ተለጋ ።
ተቀላ፡ ተቈረጠ (ዐንገቱ ራሱ
") ።
ተቀላለበ፡ ተመጋገበ ።
ተቀላለበ፡ ተቀባበለ ።
ተቀላለተ፡ ተረጣጠበ ።
ተቀላቢ (ዎች)፡ የሚቀለብ (ተመጋቢ ገበታ ዐቃፊ ") ። (ተረት)፡ "አብዝቶ ከማረስ ከተቀላቢው ማሳነስ" ።
ተቀላቢነት፡ ተቀላቢ መኾን ።
ተቀላች፡ የሚቀለት (ተረጣቢ
") ።
ተቀላወጠ፡ ተከጀለ ምግቡ ።
ተቀላጠመ፡ ቅልጥምን ተማታ ተሳበረ ።
ተቀላጠፈ፡ ተፋጠነ ተከናወነ/ተጨረሰ ።
ተቀልባሽ፡ የሚቀለበስ/ተቀናፊ ።
ተቀልጣሚ፡ የሚቀለጠም/ተሰባሪ ።
ተቀመመ፡ ተዘጋጀ ተቀላቀለ ተዋዋደ ኣንድነት ኾነ ።
ተቀመሰ፡ ተጣመ ተለከፈ ተበላ ተ ጠጣ በጥቂቱ ።
ተቀመረ፡ ተቈጠረ፡ ተመደበ ተለየ ተከፈለ ።
ተቀመቀመ፡ ተሰፋ ተዘመዘመ ።
ተቀመጠ፡ ቍጭ አለ ተጐለተ ነበረ፡ ኖረ ቈየ ሰነበተ
("(ዘፍ. ፯፥ ፲፬፡ መክ. ፭፥ ፲፯፡ ዳን. ፩፥ ፳፩፡ ፪፥ ፴፰)") ። "ተቀመጥ በወንበሬ፡ ተናገር በከንፈሬ"
እንዲሉ። (ተረት)፡ "የተቀመጠ ተቈ መጠ" ።
ተቀመጠ፡ በፈረስ በበቅሎ በበህያ በግመል በዝኆን ተነ ።
ተቀመጠ፡ ዐረፈ ሰፈረ
("(ዘኍ. ፱፥ ፲፰)") ።
ተቀመጠ፡ ኰሳ ቀዘነ ።
ተቀመጠለ፡ ታረደ ተጐመደ ተቀነ
ተቀመጠለ፡ ጐደለ አነሰ ።
ተቀማ (ተቀምሐ)፡ ተነጠቀ አለውድ በግድ ተወሰደ ገንዘቡ፡ ተወሰደበት ሰዉ ። (ተረት)፡ "በባባቱ ከተማ ልጁ ተቀማ" ። በቢርነት ሲፈታ፡ ገንዘቡን ተቀማ ይላል ።
ተቀማመጠ፡ ተሸካከመ፡ የመሸከም ብድር ተከፋፈለ፡ ሸክምና ተሸካሚ ተኳዃነ ።
ተቀማሚ፡ የሚቀመም ።
ተቀማቀመ፡ እንጀራ መብላት ዠመረ፡ ተላመደ ሕፃኑ ።
ተቀማጠለ - ተቀመጣጠለ (ሐንቀቀ)፡ ደኅና ጠባዩ ዐመሉ ተጓደለ፡ ተንደላ ቀቀ ተንቀባረረ፡ ተዘናፈለ ተደላደለ፡ "ዶሮ ዕለሱ ጣይ በንቅብ አግቡ" አለ ።
ተቀማጣይ፡ የሚቀማጠል (ተንቀባራሪ
") ።
ተቀማጭ (ጮች)፡ የሚቀመጥ (ነባሪ ኗሪ ") ("(ኤር. ፮፥ ፯፡ ፰፡ ፩ዜና መዋ. ፱፥ ፪፡ ሕዝ. ፴፱፥ ፳፱፡ ማቴ. ፳፪፥ ፲)") ። (ተረት)፡ "ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ" ።
ተቀማጭ ገንዘብ፡ ለብዙ ጊዜ የማይነካ የማይጐድል ወርቅና እኸል የክፉ ቀን መጠባበቂያ
("(ዘፍ. ፵፩፥ ፴፫ - ፴፬፡ ፴፭፡ ፴፮፡ ፵፰፡ ፵፱)") ። ይኸንንም ፈረንጆች
"ሪዘርብ" ይሉታል ።
ተቀማጭነት፡ ተቀማጭ መኾን ነባ ሪነት ።
ተቀምቃሚ፡ የሚቀመቀም (ተዘምዛሚ ቀሚስ በርኖስ
") ።
ተቀምጨ፡ ያገዳ እኸል ጕረንጆ ።
ተቀሠመ፡ ተለቀመ ተሰበሰበ ተመጠጠ ።
ተቀሰረ፡ ተገተረ ቆመ ።
ተቀሰቀሰ፡ ተበረበረ/ተፈተሸ ።
ተቀሰቀሰ፡ ተነቀነቀ ነቃ ተነሣ ።
ተቀሰተ፡ ተደገነ ጐበጠ ።
ተቀሠፈ፡ በዝርዝር ተቀጪ ተቀጠፈ ተገደለ ሞተ
("(ኤር. ፶፥ ፳፩)") ።
ተቀሠፈ፡ ተደገነ ጐበጠ ።
ተቀስቃሽ፡ የሚቀሰቀስ (እንቅልፋም ሰው አውሬ ቀሳ
") ።
ተቀረረ፡ ተጠለለ ተቀዳ ተመለጠ ።
ተቀረሸመ፡ ተገጨ ተሰበረ ።
ተቀረሻሸመ፡ ተሰባበረ ።
ተቀረቀረ፡ ገባ ተሸጐረ ተወረወረ ።
ተቀረቀበ፡ ታሰረ ተወደነ ተጠመረ ታረተ ተቈረኘ ።
ተቀረቀፈ፡ ተከረከረ ።
ተቀረበ፡ ሰውየውን ሌሎች ተጠጉት ።
ተቀረበ፡ ተነዳ ተወሰደ ።
ተቀረነተ፡ ታሰረ ተቀረቀበ ።
ተቀረደደ፡ ተቈረጠ ተቈረሰ ተገመሰ ።
ተቀረጠ፡ ሾለ ተበጀ ብርዑ ።
ተቀረጠ፡ ተሰጠ ተከፈለ ግብሩ
("(ዕዝ. ፬፥ ፲፫)") ።
ተቀረጠፈ፡ ተቈረጠ ጠቀነ ደቀቀ ።
ተቀረጣጠፈ፡ ተቈራረጠ ።
ተቀረጪ፡ ተነከሰ ።
ተቀረጸ፡ ተቀረጠ ተነጠጠ ተፈለፈለ ተጐበጐበ ሰመጠ ተነቀሰ ።
ተቀረፈ፡ ተላጠ ተመለጠ ተለጠጠ ተነጠለ ተነሣ፡ ተሰበረ ተፈለጠ ። "ገደል ተቀረፈና ወደቀ"
።
ተቀራመተ፡ ተቃረጠ ተተናተነ ተራ ከበ ተካፈለ ።
ተቀራማች፡ የተቀራመተ/የሚቀራመት
("ተተናታኝ ተካፋይ ") ።
ተቀራረጠ፡ ቀረጥ ተሰጣጠ ተቀባበለ ተግባበረ ።
ተቀራረፈ፡ ተሰባበረ ተሠነጣጠቀ፡ ተላ ላጠ ተመላለጠ ።
ተቀራራቢ፡ የሚቀራረብ ።
ተቀራሸመ፡ በቀንድ ተማታ ተጋጨ ተሳበረ ።
ተቀራቀበ፡ ተገተ ተከራከረ ተማ ረተ ።
ተቀራጨጨ፡ ተናከሰ ።
ተቀራጭ፡ የሚቀረጥ (ቀረጡ ያልወጣለት ሸቀጥ
") ።
ተቀራፊ፡ የሚቀረፍ ።
ተቀርቃሪ፡ የሚቀረቀር (ተሸጓሪ
") ።
ተቀርቃቢ፡ የሚቀረቀብ (ተጠማሪ
") ።
ተቀርዳጅ፡ የሚቀረደድ ።
ተቀርጣፊ፡ የሚቀረጠፍ ።
ተቀሸ፡ ኰራ ተለጠጠ ።
ተቀሸመደ፡ ተሰበረ ነከተ ።
ተቀሸረ፡ ተነፋ ተቀበተተ ።
ተቀሸረ፡ ተከሸነ አማረ ሰመረ ።
ተቀቀለ፡ ሞቀ ፈላ በሰለ ነፈረ፡ ተሠራ ወጡ ።
ተቀቃይ፡ የሚቀቀል (እኸል ጐመን ዓሣ ሌላም ምግብ
") ።
ተቀበለ፡ ቅብል ኾነ (እፈጣሪ ፊት ደረሰ ከበረ ተወደደ ") ("(ሉቃ. ፬፥ ፲፱ - ፳፪፡ ፳፬)") ።
ተቀበለ፡ ተሰጠው አገኘ እጅ አደረገ ተረከበ ("(ሉቃ. ፳፬፥ ፵፫)") ።
ተቀበለ፡ ተረከበ፡ (ቀበለ) ።
ተቀበለ፡ አማረ ደመቀ ተስማማ ። "አቶ እከሌ የለበሰው ልብስ ተቀብሎታል" ።
ተቀበለ፡ ጐረሠ ዋጠ ጠጣ (ቍርባ ንን ") ። "ቈረበን" ተመልከት ።
ተቀበረ (ተቀብረ)፡ በመቃብር ተኛ ተጋደመ (ዐፈር ቀመሰ ለበሰ ተደፈነ ") ።
ተቀበረ፡ ተጐዳ ተጨቈነ ።
ተቀበቀበ፡ ተቀጠቀጠ ታደሰ ።
ተቀበቀበ፡ ተተከለ ተቸከለ ።
ተቀበቀበ፡ ታረሰ ታየመ ለሰለሰ ።
ተቀበተተ፡ ዐበጠ ተነፋ ተወጠረ ተነረተ (ቍንጣን ያዘው
") ።
ተቀበነነ፡ ተነፋ ተወጠረ ተቀበተተ ።
ተቀበጠጠ፡ ተቀበተተ ።
ተቀቢ (ተቀባዒ)፡ የሚቀባ (ጳጳስ ንጉሥ ዝኆን ገዳይ ") ።
ተቀባ (ተቀብዐ)፡ ተላከከ ተለቀለቀ ተደለሰ (ቅቤው ራሱ ") ። ታደለ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀበለ (ካህኑ ንጉሡ ") ። ዳግመኛም በገቢርነት ሲፈታ "ቅቤን ተቀባ" ይላል ።
ተቀባ፡ የሰው ስም ።
ተቀባሪ፡ የሚቀበር/የሚደፈን ።
ተቀባበለ፡ ተሰጣጠ ተረካከሰ (ዕቃን ገንዘብን
") ("(ራእ. ፳፩፥ ፲)") ። በእንግድነት ተፈራረቀ
("(ሮሜ. ፲፭፥ ፯)") ።
ተቀባበረ፡ ተደፋፈነ (የመቅበር ብድር ተመላለሰ የችና የቋሚ ወገን
") ።
ተቀባባ፡ ተለቃለቀ ተደላለሰ ተባበሰ ተወዛዛ ።
ተቀባባሪ፡ የሚቀባበር ።
ተቀባባይ፡ የተቀባበለ/የሚቀባበል (ተ ረካካቢ ዳኛ
") ።
ተቀባይ፡ የተቀበለ/የሚቀበል (ተረካቢ ያዥ ") ። "ገንዘብ ተቀባይ እንግዳ ተቀባይ ተስጥዎ ተቀባይ" እንዲሉ ።
ተቀባይነት፡ ተቀባይ መኾን (ተረካ ") ።
ተቀባዮች፡ ዘፈን መዝሙር መላሾች ("(ዕዝ. ፪፥ ፷፭)") ።
ተቀብዖ፡ መቀባት ።
ተቀተረ፡ ተቀረቀረ/ተሸጐረ ።
ተቀተረ፡ ተነፋ ዐሰጠ ተወጠረ ተቀ በተተ ።
ተቀታተረ፡ ተወዳደረ ተገዳደረ ተከራከረ ተፈካከረ ተቋቋመ ። (ተረት)፡ "ከባለቀትር አትቀታተር (ከባለጊዜ አትፈካከር )" ። ዳግመኛም
"ባለቀትር ደሙ የፈላ" ማለትን ያሳያል ።መቀታተር፡ መወዳደር/መከራከር/መ ቋቋም ።
ተቀነሰ፡ ተነሣ ጐደለ፡ ከብዛት ከመምላት ኣነሰ ።"ከበስመ አብ ተቀንሶለት"
።"እነሰ" ሲሉት ተቀነሰ ።
ተቀነረ፡ ተነፋ ዐበጠ ።
ተቀነቀነ፡ ተመረመረ ተፈተሸ ።
ተቀነቀነ፡ ተቃኘ ተዠመረ ።
ተቀነበበ፡ ተከበበ ክብ ኾነ፡ የሥራ የጠላት ጦር ሰራዊት ።
ተቀነባበረ፡ ተዘገጃጀ ተደረጃጀ ተከነዋወነ ተቋቋመ ።
ተቀነተ፡ በወገብ ላይ ታሰረ መቀ ነቱ ቅናቱ ሠቁ ቀበቶው ።
ተቀነዘፈ፡ ታረደ ተቀነጠሰ ተመለመለ ።
ተቀነዘፈ፡ ወረደ ፈሰሰ ተንጠባጠበ ።
ተቀነደለ፡ ተበጣ ተቈረጠ ።
ተቀነደሸ፡ ተሰበረ ነከተ ።
ተቀነደበ፡ ተመታ ።
ተቀነደበ፡ ተቀነደለ ።
ተቀነደበ፡ ተጠጣ ጐደለ ።
ተቀነጠሰ - ተቀነጠበ - ተቈረጠ - ተበጠሰ ።
ተቀነጠበ፡ ከላይ ተቈረጠ ተበጠሰ ተ ቀነጠሰ ።
ተቀነጣጠሰ - ተቀነጣጠበ፡ ተቈራረጠ ተ በጣጠሰ ።
ተቀነጣጠበ፡ ተቀነጣጠሰ ።
ተቀነፈ፡ ታጠፈ ተመለሰ ተሸበለለ ተቀለበሰ ።
ተቀና፡ ተገዛ ተሼጠ ተለወጠ ።
ተቀናሽ፡ የሚቀነስ/የሚጐድል ።
ተቀናቀነ፡ ተመራመረ ።
ተቀናቃኝ (ኞች)፡ የተቀናቀነ/የሚ ቀናቀን (ተመራማሪ ") ።
ተቀናቃኝነት፡ ተመራማሪነት ።
ተቀናበረ፡ ተዘጋጀ ተደራጀ ተከናወነ ።
ተቀናባሪ፡ የሚቀናበር (ተከናዋኝ
") ።
ተቀናና፡ ተመቀኛኘ ።
ተቀናዘረ፡ ተዋሸሙ ከመጠን ተላለፈ ።
ተቀናጀ፡ ከሌላ ሰው በሬ ጋራ ተጠመደ ።
ተቀናጠሰ - ተቀናጠበ - ተባጠሰ ።
ተቀናጠበ፡ ተቀናጠሰ ።
ተቀናጣ፡ ጠገበ ወበራ ይይዘውን ዐጣ፡ ዘለለ ተላፋ ።
ተቀናፊ፡ የሚቀነፍ (ተቀልባሽ እጅጌ ሱሪ
") ።
ተቀንዳይ፡ የሚቀነደል (ተበጪ
") ።
ተቀንጣሽ፡ የሚቀነጠስ ። ቅንጥስ፡ የተቀነጠሰ (ቅንጥብ ቅንጥስ አለ ብጥስ አለ ") ።
ተቀንጣቢ፡ የሚቀነጠብ ።
ተቀኘ (ተቀንየ)፡ ዐወቀ ተናገረ ገ ለጸ ቅኔን ።
ተቀኘ፡ ተባለ ተነገረ ተሰጠ ቅኔው
("(ኢሳ. ፳፮፥ ፩)") ።
ተቀዘነ፡ ፈጥኖ ወጣ ወረደ ፈሰሰ ።
ተቀዘፈ፡ ተገፋ (ግራ ቀኝ ተባለ ተ ገለጠ ተከፈለ
") ።
ተቀየመ፡ ተጸየፈ ተከፋ ዐዘነ አኰ
ተቀየሰ፡ ተለካ ተመጠነ ተነደፈ ተበገረ ።
ተቀየረ፡ ተለወጠ ተዛወረ ።
ተቀየደ፡ ተሰከለ ታሰረ ተጋዳ ።
ተቀየደ፡ ተከፈለ ተመከተ ተጋረደ ።
ተቀየጠ፡ ተዘነቀ ተቀላቀለ ተደባለቀ ።
ተቀያሚ፡ የሚቀየም (ተጸያፊ አኵራፊ
") ።
ተቀያሪ፡ የሚቀየር (ተዛዋሪ ወታደር
") ።
ተቀያየመ፡ ቂም ተያያዘ ተኰራረፈ፡ ሆድና ዠርባ ተኳዃነ ።
ተቀያየረ፡ ተለዋወጠ/ተዘዋወረ ።
ተቀያያሪ፡ የሚቀያየር/ተለዋዋጭ/ተዘ ዋዋሪ ።
ተቀያጅ፡ የሚቀየድ (ተጋራጅ የቤት ውስጥ
") ።
ተቀያጭ፡ የሚቀየጥ (አደፍ ወይም
ተቀደመ፡ ሳይመታ ተመታ ።
ተቀደመ፡ ቀደመ (ቀዳሚ ኾነ
") ። "ተቀደመን ቀደመ" ማለት የተለመደ ስሕተት ነው ። "ረገጠ" ብለኸ "ተረገጠን" አስተውል ።
ተቀደመ፡ በቀዳማ ላይ ተሰቀለ ።
ተቀደመ፡ ወደ ኋላ ኾነ ታለፈ ።
ተቀደሰ (፪ዜና. ፴፥ ፳፯)፡ ተለየ ተባ ረከ ነጻ ከበረ፡ ተመሰገነ ምስጋና ተቀበለ ።
ተቀደደ፡ ተሸረከተ ተሠነጠቀ ተሠጠጠ (ተበሳ ተሸነቈረ
") ("(ዮሐ. ፳፩፥ ፲፩)") ። (ተረት)፡ "ካያያዝ ይቀደዳል፡ ካነጋገር ይፈረዳል" ።
ተቀደደ፡ ወሬ ነዛ ።
ተቀዳ (ተቀድሐ)፡ ወረደ ተጨመረ ተንቈረቈረ ተደነበቀ ተጠለቀ ተጨለፈ ተገለበጠ ።
ተቀዳ፡ ተጻፈ ተከተበ ።
ተቀዳሚ፡ የሚቀደም/የሚታለፍ (በሩጫ ሌላ የሚበልጠው
") ።
ተቀዳሚ፡ የሚቀድም (ቀዳሚ በኵር ግንባር ቀደም አንጋፋ
") ። "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወዲያኛው ዓለም ከአብ አለናት በዚህ ዓለም ከድንግል ማርያም አላባት በመወለዱ ተቀዳሚ ተከታይ የለውም፡ ላባቱም ለናቱም አንድ ልጅ ነው" ።
ተቀዳሽ፡ የሚቀደስ/የሚባረክ (ተመስ
ተቀዳሽነት፡ ተቀዳሽ መኾን ።
ተቀዳው፡ ብዙ እንባ ወረደው ፈሰሰው ።
ተቀዳው፡ ጋኑ ይህን ያኸል ጠጅ ወይም ጠላ ወጣው ።
ተቀዳደመ፡ ተላለፈ (ፊትና ኋላ ተኳዃነ
") ("(፩ቆሮ. ፲፬፥ ፩፡ ግብ. ሐዋ. ፲፪፥ ፲፬)") ።
ተቀዳደሰ፡ ተበራረከ ተመሰጋገነ ። "
ተቀዳደደ፡ ተሠነጣጠቀ ተሸረካከተ ተ በጫጨቀ ።
ተቀዳዳሚ፡ የሚቀዳደም ።
ተቀዳጀ (ተቀጸለ)፡ በራሱ ላይ የሐር የግምጃ ቅዳጅ ጠመጠመ አክሊል አደረገ፡ ዘውድ ደፋ፡ በአበባ ተሸለመ አጌጠ ። "የተቀዳጀ ምስጢር" አክሊሉና አበባው ከወደ ላይ ባዶ ዘውዱም ዐልፎ ዐልፎ ክፍት መኾኑን ያሳያል ።
ተቀዳጅ፡ የሚቀደድ (ጥንካሬ የሌለው ልብስና የቈዳ ዐይነት
") ።
ተቀጠለ፡ በላይ በጫፍ በቀለ ።
ተቀጠለ፡ ተጨመረ ታከለ ተቋጠረ ተሰፋ ረዘመ ።
ተቀጠረ (ተቀጽረ)፡ ታጠረ ተከበበ ።
ተቀጠረ፡ ለጌታ ለመቤት ዐደረ (ለሰው ታዛዥ ኾነ
") ።
ተቀጠቀጠ (ተቀጥቀጠ)፡ ተመታ ተደበደበ ተሰበረ ደቀቀ ("(ኢሳ. ፵፪፥ ፫፡ ኤር. ፴፰፥ ፬)") ። "በሐዘን ተቀጠቀጠ"
እንዲሉ።
ተቀጠቀጠ፡ ተሠራ ሾለ ጠፍጣፋ ኾነ ።
ተቀጠቀጠ፡ ተወቀጠ
("(ዘዳ. ፳፫፥ ፩)") ።
ተቀጠበ፡ ተከነዳ ተለካ ተመጠነ፡ ተመለከተ ምልክት ኾነበት ተደረገበት፡ ተከ ሰለ ።
ተቀጠጠ፡ ተቈረጠ ታጨደ ተሸለተ
("(መሳ. ፮፥ ፴፯)") ።
ተቀጠፈ፡ በልጅነት ሞተ ተገደለ ተቀሠፈ ተቀጨ ።
ተቀጠፈ፡ ተቈረጠ ተቀነጠሰ ተሰበረ (ጐመኑ ቅጠሉ
") ።
ተቀጣ (ተቀጽዐ)፡ ተመታ ተገረፈ እወህኒ ቤት ገባ ታሰረ ።
ተቀጣ፡ መቀጮ ከፈለ ።
ተቀጣ፡ ተሠራ ተመከረ ተገሠጸ፡ ተጠበቀ (ባሳብ በሰውነት
") ። "እኔን ያየኸ ተቀጣ" እንዲል ሌባ ሲገረፍ ።
ተቀጣ፡ እጁ ምላሱ ተቈረጠ ።
ተቀጣሪ (ሮች)፡ የሚቀጠር/የሚታ ጠር፡ እሥራ የሚገባ ።
ተቀጣቀጠ፡ ተማታ ተደባደበ ተዳቀቀ ።
ተቀጣቢ፡ የሚቀጠብ (ተመጣኝ
") ።
ተቀጣይ፡ የሚቀጠል/የሚጨመር/የሚ ታከል ።
ተቀጣጠለ፡ ተቈጣጠረ ተያያዘ ተና
ተቀጣጠለ፡ ተከታተለ ተለጣጠቀ ተገጣጠመ ።
ተቀጣጠረ፡ "እዚህ ድረስ እመጣለኹ"
በማለት ተነጋገረ ።
ተቀጣጠበ (ተቃጸበ)፡ ተጠቃቀሰ በምልክት ተያየ (ተላገደ አላገጠ ተመሳቃ ") ።
ተቀጣጣ (ተቃጽዐ)፡ የቅጣት ብ ድር ተመላለሰ ።
ተቀጣጣይ፡ የሚቀጣጠል (ተያያዥ
") ።
ተቀጣጥሎ፡ ተያይዞ ተከታትሎ
("(፪ሳሙ. ፳፩፥ ፩)") ።
ተቀጣፊ፡ የሚቀጠፍ (ብስል የተክል ፍሬ ጐመን
") ።
ተቀጥላ - ተቀጽላ፡ በወርካ በቍልቋል በማንኛውም ዛፍ ኹሉ ራስ በስንደዶ ዐናት ላይ የሚበቅል ቅጠል የጫት አምሳያ ። ባለመድኀኒቶች አብነት ያደርጉታል፡ መናኛው "ተገድራ" ይባላል ። "ገደረን" እይ ። (የማሰሮ ተቀ ጥላ)፡ ገንፎ ።
ተቀጥላ፡ በ፫ ፊደል ግስ መነሻና መድረሻ የተጨመረ ባዕድና ምእላድ ፊደል ቍጥር ፯ ተመልከት ።
ተቀጥቃጭ፡ የሚቀጠቀጥ/ተወቃጭ ።
ተቀጨ፡ ተቀሠፈ ተገደለ ።
ተቀጨ፡ ተቈረጠ ተነጨ ተገነጠለ ።
ተቀጨ፡ ዐንገቱ ታመመ (ዘወር ብሎ ማየት አቃተው
") ።
ተቀጪ፡ የሚቀጣ (ዐመፀኛ ወንጀለኛ
") ።
ተቀጸለ፡ ተቀዳጀ፡ ቀጸለ ።
ተቀጸለ፡ ተቀዳጀ ተሸለመ ተጌጠ ።
ተቀጸለ፡ ተጠና ትምርቱ ።
ተቀጸለ፡ ታማ ተነቀፈ፡ ስሙ ከፋ ።
ተቀጸል፡ ለቅርብ ወንድ የሚነገር ት እዛዝ አንቀጽ ።
ተቀጸል ጽጌ፡ ሐፄጌ ።
ተቀጸል ጽጌ፡ የበዓል ስም (በመስከረም ፲ኛ ቀን በያመቱ የሚከብር የመስ ቀል በዓል
") ። ይኸውም የጌታችን ግማደ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ የመምጣቱ መታሰቢያ ነው ።እሱንም ያስመጡት በ፲፬፻ አመተ ምሕ ረት የነበሩ ዐጤ ዳዊት ስለ ኾኑ በዓሉ ባማርኛ ዐጤ መስቀል ይባላል ። "ዐጪ" ብለኸ "ዐጤን" እይ ።
ተቀጻ (ተቀጽዐ)፡ ተቈረጠ ታፈፈ ተቀፈፈ ።
ተቀጽላ - ተቀጥላ፡ ቀጠለ ።
ተቀፈረ፡ ቆመ ተዘረጋ ተቀቀረ ።
ተቀፈቀፈ፡ ተበሳ ተሰበረ ተፈለፈለ ተወለደ ።
ተቀፈቀፈ፡ ተከረከረ ።
ተቀፈደ፡ ተበሳ ታሰረ ።
ተቀፈደደ፡ በጥብቅ ታሰረ ።
ተቀፈፈ፡ ተለመነ
("ራበኝ ጠማኝ ተባለ ") ።
ተቀፈፈ፡ ተቈረጠ ተከረከመ ተተካከለ ።
ተቍለጨለጨ፡ ከብለል ከብለል አለ ።
ተቍነጠነጠ፡ ተቅበጠበጠ ተወዘወዘ ።
ተቍነጥናጭ፡ የሚቍነጠነጥ ተወዝዋዥ ተቅበጥባጭ ።
ተቃ፡ ተጋጨ ጠጠሩ ብይው ።
ተቃለለ (ቀለለ)፡ ተናቀ ተዋረደ (ተደ
ተቃለለ፡ ተዋገደ ተገባደደ (ተደራራጊ) ።
ተቃለበ፡ ተራዳ ተማገበ ።
ተቃለተ፡ ተራጠበ ።
ተቃለደ፡ ተዋዛ በቀልድ ተነጋገረ ።
ተቃለጠ፡ ተማታ ተደባደበ፡ ደም ተፋሰሰ ።
ተቃላይ፡ የተቃለለ/የሚቃለል (ተዋራጅ
") ። "ኑ ባይ አክባሪ፡ እንቢ ባይ ተቃላይ" እንዲሉ። በልማድ ግን "ተቀላይ" ይሉታል፡ አያሠኝም ።
ተቃላጅ፡ የተቃለደ/የሚቃለድ/የሚዋዛ ።
ተቃመ (ተቅሕመ)፡ ተቓመ ተገተመ ተገፈረ ተሰመሰመ ።
ተቃመሰ፡ ተላከፈ ተዳረሰ ።
ተቃመሰ፡ ተማታ ።
ተቃሚ (ተቃማሒ)፡ የሚቃማ/የሚ ሻማ (ተናጣቂ/ተሻሚ ") ።
ተቃሚ፡ የሚቃማ/ቀማ ።
ተቃሚ፡ የሚቃም።
ተቃማ (ተቃምሐ)፡ ተናጠቀ ተሻማ ።
ተቃረ፡ ተሳለ ተፋጩ ተፈገፈገ ።
ተቃረ፡ ጐመዠ ሠየ፡ ተመኘ ፈለገ (ከብት ዐምቦን ወጥን
") ።
ተቃረመ፡ ተለቀመ፡ ተሰበሰበ።
ተቃረረ፡ ተቃዳ ተለጠ ።
ተቃረበ፡ ተናዳ ተዋሰደ ።
ተቃረበ፡ ተዳረሰ ተዋጎደ ።
ተቃረበ፡ ተጣጋ ተገናኘ፡ እዳኛ ፊት ጐን ለጐን ተቋቋመ ።
ተቃረነ፡ ተጣላ/ተዋጋ ።
ተቃረጠ፡ ተቀራመተ ተካፈለ ።
ተቃራሚ፡ የሚቃረም፡ ተለቃሚ፡ ተ ሰ ብሳቢ ።
ተቃራቢ፡ የሚቃረብ (ተገናኝ
") ።
ተቃራኒ (ዎች)፡ የተቃረነ/የሚቃረን ("ተሰማሚነት የሌለው ተጣይ ") ። "ክፉና ደግ ሞትና ሕይወት እውነትና ሐሰት ጨለ ማና ብርሃን ንፍገትና ቸርነት ፍራትና ጕብዝና የመሰለው ኹሉ"
።
ተቃራኒነት፡ ተቃራኒ መኾን ።
ተቃቀፈ (ተሓቀፈ)፡ ተቋቈረ ተደ
ተቃቃረ፡ ተሳሳለ ተፋጩ ተፈጋፈገ፡ ተመኛን ተፈላለገ ።
ተቃቃረ፡ ተሸካከረ ተቀያየመ ።
ተቃቃሪ፡ ተፈላላጊ ተቀያያሚ ።
ተቃቃፊ (ተሓቃፊ)፡ የሚተቃቀፍ ።
ተቃበረ፡ ተዳፈነ (ዐፈር ተማለሰ
") ።
ተቃበጠ፡ ተላፋ ተቈናጠጠ ተዳራ ተቈላመመ ።
ተቃበጥ፡ የቂጥኝ ስም (በፈጋራ ውስጥ የሚወጣ የቂጥኝ ምላሽ ")፡ ወይም ዕግል ። "ከሴት ሴት በመኼድ ባለማረፍ በቅብጠት ስለሚመጣ ተቃበጥ ተባለ" ።
ተቃባ (ተቃብዐ)፡ ተዳለሰ ።
ተቃባ፡ ደም ተፋሰሰ (አበ ደም ተኳ ዃነ ተጋደለ ") ። "እከሌና እከሌ ደም ተቃብተዋል" እንዲሉ ።
ተቃባጭ፡ የተቃበጠ/የሚቃበጥ (ልፊያ ") ።
ተቃተለ፡ ታገለ ተጋደለ ።
ተቃና (ተራትዐ)፡ ተሳላ ተሳካ ተ
ተቃና (ተቃንአ)፡ ተመቃኘ ።
ተቃኘ፡ ተሰለለ ተጐበኘ ታሠሠ ።
ተቃኘ፡ ተቀነቀነ ተዠመረ ተባለ ።
ተቃኘ፡ ጠበቀ ላላ ተሰማማ ተቃና ።
ተቃወመ፡ ተጣላ ተከራከረ ተገተ ።
ተቃወሰ፡ ተለያየ ተሳሳተ ተጣመመ ተሳከረ ተዋሰበ ተዘባረቀ ነገሩ ።
ተቃዋሚ፡ የተቃወመ/የሚቃወም (ተከ
ተቃዋሞች፡ የሚቃወሙ (ተማጋቾች
") ።
ተቃዋሽ፡ የሚቃወስ (ተሳሳች
") ።
ተቃደሰ፡ ተመሳገነ ።
ተቃደደ፡ ተሠናጠቀ (ቅዳጅ ተካፈለ ተ ተናተነ
") ።
ተቃዳጅ፡ የሚቃደድ (ተተናታኝ
") ።
ተቃጠረ፡ ተቀጠረ ቀጠሮ አደረገ፡ ከሴት ተነጋገረ ።
ተቃጣ፡ ተደከረ ተደቀነ ተዘረጋ ተዘጋጀ ። "ከተቃጣ መቅሠፍቱ ከወረደ ማቱ ያ ድናችኹ"
እንዲል መራቂ ሽማግሌ ።
ተቃጣሪ፡ የተቃጠረ/የሚቃጥር ።
ተቃጣይ፡ የሚቃጠል (ነዳጅ ሞራ ቅባኑግ ጋዝ ቤንዚን ነፍት
") ።
ተቃጨለ፡ ተመታ ።
ተቃጨለ፡ ተማታ ተጋጨ ።
ተቃጪ፡ ተቋረጠ ተጋደለ ።
ተቈ፡ ተጸጸተ ዐዘነ ተቈረቈረ ተቀየመ
("(መዝ. ፻፲፪፥ ፲)") ።
ተቈለለ (ተጐለለ)፡ ተደረበ ተነባበረ ተከመረ ተጐቸ ።
ተቈለመመ፡ ተቀለሰ ተዘለሰ ተዘቀዘቀ፡ ጐበጠ ተጠመዘዘ፡ ማዥራቱ ወደ ምድር ማንቍርቱ ወደ ላይ ኾነ ።
ተቈለቈለ፡ ተዘቀዘቀ፡ ቍልቍል ኼደ
ተቈለፈ፡ ተሸፈነ ተወሸለ ።
ተቈለፈ፡ ተዘጋ ተቀረቀረ ተሸጐረ ።
ተቈለፈ፡ ተያዘ ታነቀ ።
ተቈለፈ፡ ጐበጠ ተቀለሰ ታጠፈ ።
ተቈላ፡ ተወዘወዘ ተንቀሳቀሰ ።
ተቈላ፡ ተገረፈ ተመታ ።
ተቈላ፡ ታመሰ ተንጣጣ ተጠበሰ በሰለ ።
ተቈላለፈ፡ ተገነኛኘ ተጣላ ።
ተቈላላፊ፡ የሚቈላለፍ ።
ተቈላመመ፡ ተቃለሰ ተጠማዘዘ ተዳራ ።
ተቈላመጠ፡ ቍልምጫ ተቀበለ ።
ተቈላፊ፡ የሚቈለፍ (ተሸጓሪ
") ።
ተቈልማሚ፡ የሚቈለምም (ፍሪዳ ሙ
ተቈልቋይ፡ የሚቈለቈል፡ ወደ አረኸ የሚወርድ ።
ተቈመደ፡ ተደረተ ተደበደበ ተዋሰበ ተደፈነ ።
ተቈመጠ፡ ቈሰለ፡ ተቈረጠ ተጐመደ ተጐረደ ተበጠሰ፡ የእጁና የእግሩ ጣት ታጣ፡ ዐጠረ ዐጪር ኾነ ።
ተቈማመጠ፡ ተቈራረጠ ተጐማመደ ተበጣጠሰ ።
ተቈሰቈሰ፡ ተነካ ታወከ ።
ተቈሰቈሰ፡ ተጠቀሰ ተገፋ ገባ ተጨ መረ ።
ተቈሳቈሰ፡ ተዋጋ ተጋደለ ።
ተቈረመ፡ ተመታ፡ ተኰረኰመ።
ተቈረማመደ፡ ተጨባበጠ/ተኰረማመተ ።
ተቈረሰ፡ ተፈተተ ተገመሰ ተገመደለ ተቀረደደ ተከፈለ ተጐረመደ ።
ተቈረረ፡ ተጫነ ተደረበ ተነባበረ ።
ተቈረቈረ፡ ተማሰ ተቈፈረ ተበላ ተነ ደለ ተሸነቈረ ።
ተቈረቈረ፡ ተዠመረ ተመሠረተ ።
ተቈረቈረ፡ ተደፈነ ተመረገ ተጠቀጠቀ ።
ተቈረቈረ፡ ተጐረበጠ ተነካ ተወጋ፡ ቈሰለ ።
ተቈረቈረ፡ ዐሰበ ተጸጸተ ዐዘነ ተከዘ ።
ተቈረበ፡ ተቀደሰ መሥዋዕቱ ቀረበ ።
ተቈረበለት፡ ተቀደሰለት፡ ስሙ ተጠራ ።
ተቈረበተ፡ ተጐለበ ተለጐመ ።
ተቈረኘ፡ ታሰረ ተጠመደ ።
ተቈረኘተ፡ ተነፋ ተጐሰረ ።
ተቈረዘ፡ ተሸረበ ተሸፈነ ።
ተቈረጠ፡ ተለየ ተወሰነ ቀኑ ። ዳግመኛም በገቢርነት ሲፈታ
"ጠጕሩን ተቈረጠ" ይላል ።
ተቈረጠ፡ ተጐረደ ተጐመደ ተመደመደ ተሸለተ ተበጠሰ፡ ጠፋ ታጣ
("(ዘፀ. ፴፥ ፴፫ - ፴፰ ። ፪ዜና. ፯፥ ፲፰)") ።
ተቈረጠ፡ ዐለቀ ተጨረሰ፡ ጐደለ ተቀነሰ ቆመ
("(ዘፍ. ፯፥ ፪)") ።
ተቈረጠመ፡ ተጐረደመ ተሰበረ
("(በሙ ንጋጋ ወፍጮነት ተከካ ተፈጩ)") ተከረተሰ ታኘከ ተበላ ።
ተቈረጠመ፡ ተጐረደመ ተሰበረ
("(በሙ ንጋጋ ወፍጮነት ተከካ ተፈጩ)") ተከረተሰ ታኘከ ተበላ ።
ተቈረፀ፡ ተቈረጠ፡ ዐጪር ኾነ ።
ተቈረፈ፡ ተጨረፈ ተቀለበሰ ተማሰ ተከፈለ ።
ተቈራ (ተቄርሐ - ተቀርዐ - ተኰርዐ)፡ ተበጣ ተፈቃ ተጋረጠ፡ ተተኰሰ ተነ ቀሰ ታተመ ተቀባ፡ ተመታ ተቈረመ ።
ተቈራረሰ፡ ተጎማመሰ ተከፋፈለ ።
ተቈራረጠ፡ ተበጣጠሰ ተጐማመደ
("(ዳን. ፪፥ ፭)") ።
ተቈራረጠ፡ ተጠላላ ተለያየ ።
ተቈራራጭ፡ የሚቈራረጥ ።
ተቈራሽ፡ የሚቈረስ (ተፈታች
") ።
ተቈራቈሰ፡ ተፋተነ ተከራከረ ተማከረ ተዣመረ ተማታ ተዋጋ
("(፪ሳሙ. ፪፥ ፲፬)") ።
ተቈራቋሽ (ሾች)፡ የተቈራቈስ/የሚቈራቈስ (ተፋታኝ ተማች ተዋጊ እስክንድ ርን ፉዝን የመሰለ ") ።
ተቈራኘ (ተደራጊና ተደራራጊ)፡ ከባለ ደም ጋራ በሰንሰለት ታሰረ ተሳሰረ ተጣመደ ተያያዘ ።
ተቈራኘ፡ ተጠጋ ዐደረ ተዋሐደ (ጋኔን ሰውን
") ።
ተቈራኚ፡ የሚቈራኝ ።
ተቈራጭ፡ የሚቈረጥ/የሚበጠስ/የሚያልቅ/የሚቀነስ ።
ተቈርቋሪ፡ የሚቈረቈር (ዐሳቢ ዐዛኝ
") ።
ተቈርቋሪነት፡ ተቈርቋሪ መኾን፡ ዐዛኝ ነት ።
ተቈርጣሚ፡ የሚቈረጠም/የሚበላ ።
ተቈሸበ፡ ተጀጀረ፡ መብላት ኣቃተው ።
ተቈበረ፡ ተበሳጨ ተበጣበጠ ።
ተቈታቸ፡ በመብል በመጠጥ ተወራረደ
("እሰጥ አገባ ተባባለ ") ።
ተቈታቺ፡ የተቈታቸ/የሚቈታች (ተወ ራራጅ
") ።
ተቈነ፡ ተነቀለ ተጐለጐለ ዐረሙ ።
ተቈነቈነ፡ ተከተፈ ተተነተነ ።
ተቈነነ፡ ተለካ ተመጠነ ተሰፈረ ድ ርጎው ።
ተቈነነ፡ ተታታ ተጐነጐነ ተሠራ ።
ተቈነነ፡ ተጀነነ ኰራ ተቋፈ ።
ተቈነነ፡ ድርጎ ተቀበለ መነኵሴው ።
ተቈነዣዠ፡ ቍንዥናን ተሰጣጠ' ጠጕ ርን በመመሸጥና ባለባበስ ።
ተቈነደደ፡ ተገረፈ ተለቈጠጠ ።
ተቈነደደ፡ ደረቀ ሻከረ፡ ዐጪር ኾነ ።
ተቈነጠለ - ተቈነጸለ ።
ተቈነጠረ፡ ተነካ ተወጋ ተነከሰ ተማረ ።
ተቈነጠረ፡ ጥቂት ኾነ ።
ተቈነጠጠ፡ ተለመዘዝ ተቀጣ ።
ተቈነጠጠ፡ ተነከሰ ተበላ ።
ተቈነጠጠ፡ ተያዘ ተረገጠ ።
ተቈነጠጠ፡ ተጠቀለለ ተሸበለለ ተማ ገረ ።
ተቈነጣጠረ፡ ብዙ ጊዜ ተቈነጠረ
("(ተ ደራጊ)") ።
ተቈነጣጠረ፡ ተነካከሰ
("(ተደራራጊ)") ።
ተቈነጩ፡ ተለቀመ ተገደለ ቍንጫው ።
ተቈነጸለ፡ ተቈረጠ ተገነጠለ ።
ተቈነጸለ፡ ተኰሰተረ ተሰበረ ።
ተቈናቈነ፡ ተሣሠተ ተተናተነ ተንቈ ጣቈጠ ።
ተቈናቋኝ፡ የተቈናቈነ/የሚቈናቈን ።
ተቈናኝ፡ የሚቈነን (ተጓዳጅ ተቋፊ
") ።
ተቈናደደ፡ ተጋረፈ ።
ተቈናዳ፡ ተዛለለ ተቃበጠ ።
ተቈናጠረ (ፈሐለ)፡ ተናከሰ ተቍነጠ ነጠ ተፈናጠረ ዘለለ ።
ተቈናጠጠ፡ ተለማዘገ ።
ተቈናጠጠ፡ ተናከሰ ተባላ ።
ተቈናጠጠ፡ ተገናኘ ተያያዘ
("(ትዳር ዠመረ ያዘ)") ።
ተቈናጣሪ፡ የተቈናጠረ/የሚቈናጥር (ተ ናካሽ ቅብጥብጥ
") ።
ተቈናጣጭ፡ የተቈናጠጠ/የሚቈናጠጥ (ተናካሽ ዝንብ ትንኝ
") ።
ተቈንጣሪ፡ የሚቈነጠር (ድልኸ ቅቤ ሱረት ዐመድ
") ።
ተቈኘተ፡ ተታታ ተሠባጠረ ተዋሰበ ።
ተቈዘረ፡ ተጐኘረ ተነፋ ተጐሰረ ።
ተቈደሰ፡ ተቈረሰ ተከፈለ ።
ተቈጋ፡ ተገረፈ/ተቈነደደ (በቍግ
") ።
ተቈጠረ (ተቈጽረ)፡ ታሰበ ተሰላ ቍ ጥሩ ታወቀ ተነገረ፡ ከቍጥር ገባ ("(ግብ. ሐዋ. ፩፥ ፳፮፡ ሮሜ. ፬፥ ፲፫፡ ፱)") ።
ተቈጠቈጠ፡ ተቈረጠ/ተመለመለ ።
ተቈጠቈጠ፡ ተቈጠበ/ተቈነጠረ ።
ተቈጠበ፡ ወጪው አነሰ፡ ተቀመጠ በዛ በረከተ ተረፈ ተካበተ ገንዘቡ ።
ተቈጠጠ፡ ተኰሳ ታራ ።
ተቈጢታ፡ የምትቈጣ ። "የፈሲታ ተቈጢታ"
እንዲሉ።
ተቈጣ (ተቈጥዐ)፡ ገሠጸ ዘለፈ ወቀሠ ገላመጠ ። "የማይመቱት ልጅ ቢቈጡት ያለቅሳል" ።
ተቈጣ፡ ሖመጠጠ ሸመጠረ ።
ተቈጣ፡ ተናደደ ጮኸ ተበሳጨ
("(ዘዳ. ፱፥ ፰)") ። (ተረት)፡ "በባዳ ቢቈጡ በጨለማ ቢያፈጡ" ። "ፌንጣ ብትቈጣ እግሯን ጥላ ኼደች" ።
ተቈጣ፡ -ገሠጸ፡ (ቈጣ) ።
ተቈጣሪ፡ የሚቈጠር/የሚታሰብ/የሚ
ተቈጣቢ፡ የሚቈጠብ ።
ተቈጣጠረ፡ ተያያዘ ተሳሰረ ።
ተቈጣጣ፡ መላልሶ ተቈጣ (ገሣሠጸ
") ።
ተቈጣጣሪነት፡ ተቈጣጣሪ መኾን ።
ተቈጥቋጭ፡ የሚቈጠቈጥ/የሚመለመል (ተመልማይ
") ።
ተቈጪ፡ የሚቈጣ/የሚገሥጽ ።
ተቈጪነት፡ ተቈጪ መኾን ።
ተቈፈረ፡ ተማሰ ተማረ ተመነቀረ ተኳተ ጐደጐደ ።
ተቈፈነነ፡ ታጠፈ ተጨበጠ ደረቀ ።
ተቈፋሪ፡ የሚቈፈር ።
ተቈፋጠነ፡ ተዘጋጀ ተደራጀ ፍጹም ኾነ አማረ ተጌጠ ።
ተቅለሰለሰ፡ ደከመ ሰለተ ።
ተቅለሸለሸ፡ ሳይስማማ ቀረ መብል መጠጡ፡ ታወከ ሆዱ ።
ተቅለበለበ፡ ተክለበለበ ተስገበገበ፡ ቸ ኰለ ቀለብ ለመፈለግ ።
ተቅለብላቢ፡ የሚቅለበለብ/ተስገብጋቢ ።
ተቅለጠለጠ፡ ወዛ፡ ቅቤ የተቀባ መሰለ፡ ጭፍጭፍ አለ ። (ግጥም)፡ "ምንም ተቀባብተሽ ብትቅለጠለዉ ተማሪ ውድ ነው፡ የሱሪ ጨው አምጪ" ።
ተቅላላ፡ ብዙ ጊዜ ቀላ፡ ቀያቀይ ኾነ ።
ተቅመደመደ፡ ተጐተተ ዐቅም ዐጣ ተሽመደመደ ።
ተቅመድማጅ፡ የሚቅመደመድ (ተጐ
ተቅማጣም፡ ቅዘናም፡ ተቅማጥ የሚበዛበት ሰው ።
ተቅማጥ፡ ቅዘን ሻታ ብጥብጥ ዐይነ ምድር ።
ተቅረፈረፈ፡ በብዙ ወገን ተቀረፈ ተፍረከረከ ።
ተቅበዘበዘ - ተቅነዘነዘ፡ ናወዘ ባከነ ዛበረ ባዘነ ("(ኤር. ፲፬፥ ፱፡ ሆሴ. ፱፥ ፲፯፡ ዓሞ. ፰፥ ፲፪)") ።
ተቅበዝባዥ (ዦች)፡ የሚቅበዘበዝ/የሚናውዝ (ዘዋሪ ") ("(ዘፍ. ፬፥ ፲፪)") ።
ተቅበጠበጠ፡ ተቍነጠነጠ ተወራጨ ተወዘወዘ ተነቀነቀ ተበሳጨ ዐመለ ቢስ ኾነ ። "ዐመለኛ በቅሎ ሲቀመጡበት ይቅበጠበጣል" ። "ሀብታም ሰው በማእድ ጊዜ ይቅበጠ በጣል" ።
ተቅበጥባጭ፡ የሚቅበጠበጥ/የሚወ
ተቅነዘነዘ፡ ተፍነዘነዘ ተክለፈለፈ ተንቀ ዠቀዠ ።
ተቅዘመዘመ፡ ተወረወረ ተምዘገዘገ ተውዘገዘገ ።
ተቅዘምዛሚ፡ የሚቅዘመዘም በትር ።
ተቅጠለጠለ፡ ተከታተለ ተገናኘ ።
ተቅጠልጣይ፡ የሚቅጠለጠል (ተከታ
ተቅጨለጨለ፡ ብረትና ብረት ብርና ብር ተጋጨ ።
ተቅጨልይ፡ የሚቅጨለጨል ።
ተቆመ፡ መኼድ መራመድ ቀረ ተ ተወ (ቀጥ ተባለ
") ።
ተቆመ፡ ተባለ ደረሰ ተዜመ ። "ሳታቱ ዋዜማው ማሕሌቱ ተቆመ"
እንዲሉ።
ተቋለፈ፡ ተገናኘ ተያያዘ፡ አልላቀቅ አለ ።
ተቋላ፡ ተጋረፈ ተታኰሰ በጥይት ተማታ ።
ተቋላፊ፡ የሚቋለፍ (ተያያዥ
") ።
ተቋመጠ፡ በቈመጥ ተማታ ተጓመደ ።
ተቋሰለ፡ ተማታ ተዋጋ ተፈናከተ ተዳማ ።
ተቋሰለ፡ ተቀያየመ ተጣላ ተባባሰ ።
ተቋረሰ፡ ተፋተተ ተካፈለ ተሳተፈ ።
ተቋረበ፡ አንድ መጐናጸፊያ ለብሶ ።
ተቋረጠ፡ ሥራ ሊሠራ ተዋዋለ (ሥራ ውን ጨርሶ የሚያስረክብበትን ቀን ተነጋገረ ") ("(ተደራራጊ)")
።
ተቋረጠ፡ ቀረ (መምጣቱ መሰጠቱ መሠራቱ
") ("(ተደራጊ)") ።
ተቋረጠ፡ ተባጠሰ ።
ተቋረፈ፡ ተካፈለ በላ ተመገበ (ቋር ፍን
") ።
ተቋረፈ፡ አጠለቀ ተላበሰ ዳባን ።
ተቋራጭ (ጮች)፡ የተቋረጠ/የሚ ቋረጥ (ተዋዋይ መሐንድስ ") ። "ሥራ ተቋራጭ"
እንዲሉ ።
ተቋራጭነት፡ ተዋዋይነት ።
ተቋቈረ (ተዓቈረ)፡ ተቃቀፈ ።
ተቋቋ፡ ተቀፈቀፈ ተፈለፈለ ።
ተቋቋመ፡ ተነሣሣ ተቀታተረ ተከራከረ ተወዳደረ
("(መከተ)") ። "ምን ታደርጋለኸ ምን ታመጣለኸ ተባባለ" ("(ኢያ. ፲፥ ፰፡ ግብ. ሐዋ. ፲፰፥ ፮)") ።
ተቋቋመ፡ ኾነ በጀ ተሳካ ተቀናበረ ።
ተቋቋሚ፡ የሚቋቋም (ባለጋራ ሥራ
") ።
ተቋቋሞች፡ ተከራካሪዎች ተቃዋሞች
("(ሮሜ. ፲፫፥ ፪)") ።
ተቋተ፡ ተጨመረ ተደቀነ ።
ተቋተ፡ ተጨመረ ተደቀነ ።
ተቋተ፡ ተጨመረ ተደቀነ ።
ተቋደሰ፡ በገዛ አፉ ተመሰገነ ። "ተቃደሰን"
አስተውል ።
ተቋደሰ፡ ተቋረሰ ተካፈለ ተሳተፈ ።
ተቋጠረ (ተቈጽረ)፡ ተቀጠለ ታሰረ ገመዱ ጠፍሩ ድሩ ።
ተቋጠረ፡ ተቈጣጠረ፡ ተሳሰበ ተሳላ ። "ኀጢአታቸውን ይቋጠራቸዋል"
። "ከዚያ እቋጠራቸዋለኹ" ("(ሆሴ. ፱፥ ፱፡ ዮኤ. ፫፥ ፪)") ።
ተቋጠረ፡ ተፀነሰ ተረገዘ ።
ተቋጠረ፡ ዐረግ ተማዘዘ፡ "እከሌ ቢወልድ እከሌን ተባባለ"
።
ተቋጠረ፡ ዐተረ ታቈረ ጓጐለ ።
ተቋጣ (ተቋጥዐ)፡ የቍጣ ብድር ተመላለሰ (ተጋሠጸ ") ።
ተቋጣሪ - ተቈጣጣሪ (ሮች)፡ የሚቈጣጠር (ተሳሳቢ ስሌተኛ ("(ኤር. ፴፫፥ ፲፫)"))
። "ቋንቋቸውን የማያከብሩ ሰዎች ግን ኮንትሮል ይሉ ታል። ወደ ፊት፡ ቋጠረ ተቋጠረ ብለኸ ተቋጣሪን አስተውል" ።
ተቋጣሪ፡ የሚቋጠር/ተቀጣይ ። "ጐንደሮች ግን ተቈጣጣሪን ተቋጣሪ ይሉታል ። ቈጠረ ተቋጠረ ብለኸ ተቋጣሪን እይ"
።
ተቋጥሮ፡ መቋጠር ። "የተቋጥሮ ዝምድና"
እንዲሉ።
ተቋጨ፡ ተጠመዘዘ ከረረ ተገመደ ተጠመረ ተደበለ (እንደ ቈጫ (ዔሊ) ኾነ
") ።፡ ቄጆ ማለቢያ አኮሌ ግሬራ ሰ
ተቋፈ፡ ተቈነነ ዝንጀርኛ ኼደ ተዋበ ።
ተቋፊ፡ የሚቋፍ/ተቈናኝ ።
ተበለቀጠ፡ ተገለጠ ተከፈተ ።
ተበለቃቀጠ፡ ተገላለጠ ተከፋፈተ ።
ተበለተ፡ ተለየ፡ ተነጠለ፡ ተቈረጠ፡ ድኻ፡ ብቸኛ፡ ኾነ፡ ብቻውን፡ ቀረ ።
ተበለጠ፡ አነሰ፡ ዐጪር ኾነ፡ ጐደለ ። ተሞኘ ተታለለ ።
ተበለጠጠ፡ ተገለጠ ተከፈተ ።
ተበላ (ተበልዐ)፡ ተነከሰ ተጐረሠ ፥ ተገመጠ ተመሳ ታረበ ተዋጠ፡ ተቃጠለ ተቈረጠ ። (ግጥም)፡ እበላ ብዬ ተበላኹ፡ ምነው ሳልበላ በቀረኹ ። ነብርን እይ ።
ተበላለጠ፡ ተራራቀ ተላላቀ ተራ ዘመ ።
ተበላላ፡ ተነካከሰ ተጋጋጠ ተገማመጠ ።
ተበላላጭ፡ የተበላለጠ የሚበላለጥ የሚራዘም ።
ተበላቀጠ፡ ተጋለጠ ተከፈተ፡ ሴትኛ ኼደ ተራመደ ።
ተበላጩና አበላጩ፡ ሥርወ ቀለሙ ግእዝ ተከታዩ ራብዕ ስለ ኾነ በኹለት እንደ ተፈታ አስተውል ።
ተበላጪ (ተፋለጸ)፡ ተጋጩ፡ ተሠነጠቀ ተተረተረ ተለያየ፡ ተሰበረ፡ ሱፋጭ ኾነ ።
ተበሰ፡ ተጣላ ተጠላላ፡ ተቋጣ ተበጣበጠ ።
ተበሠረ (ተበሥረ)፡ ተባለ ተነገረ ተወራ የምሥራቹ ።
ተበሰበሰ (በሰበሰ)፡ ራሰ ታሸ ተገ ላበጠ ።
ተበሰከ (ተበትከ)፡ ተበተከ ተበጠሰ ።
ተበሳ፡ ተሰረሰረ ተፈለፈለ ተሸነቈረ ተነደለ ። (ኢዮ ፴ ፥ ፲፯) ።
ተበሳሰከ፡ ተበታተከ ተበጣጠሰ ።
ተበሳሳ፡ ተሸነቋቈረ ተነዳደለ ።
ተበሳበሰ፡ ተራራሰ ተጋማ፡ ተበለሻሸ ተበሻቀጠ ተለዋወጠ ።
ተበሳጨ፡ ዐዘነ ተቈጣ ተናደደ ።
ተበረቀሰ፡ ተነደለ ተበሳ ተጣሰ ወደቀ ፈረሰ ።
ተበረቃቀሰ፡ ተበታተነ ተሰባበረ ፈ ራረሰ ።
ተበረበረ (ተበርበረ)፡ ተበዘበዘ ተወረረ ተዘረፈ፡ ወሪሳ ተመታ አገሩ፡ ተገለበጠ አኺዶው ።
ተበረታታ፡ ተጠነካከረ ተደጋገፈ ተ ዛዘነ ተጋገዘ ።
ተበረኰተ፡ ተደፈነ ተረመጠ ።
ተበረዘ (ተበርዘ)፡ ተበጠበጠ ተዘ ለለ፡ በረደ በረሰ ።
ተበረገደ፡ ተከፈተ ተከፈለ ተተረተረ ተፈለጠ ።
ተበረገገ፡ ተፈነከተ ተወለለ ።
ተበራ፡ በራ ። ለተገብሮ ግስ ተደራጊ አንቀጽ የለውም ።
ተበራረከ፡ ተመሰጋገነ ተመራረቀ ተቀ ዳደሰ፡ ምርቃት ተሰጣጠ ተቀባበለ ።
ተበራረዘ፡ የተባረዘ ድርብ ።
ተበራበረ፡ ተበዛበዘ ተዛረፈ ።
ተበራታ፡ ተጠናና ተጠነካከረ፡ አይዞኸ አይዞኸ ተባባለ ።
ተበራከተ፡ ተባዛ ተራባ ተዋለደ ።
ተበራዥ፡ የሚበረዝ፡ ፍል ውሃ ማር ።
ተበራየ፡ ተኼደ ተረገጠ፡ ታሸ ።
ተበራገደ፡ ተከፋፈተ ተለያየ፡ ተበላ ቀጠ ።
ተበራገገ፡ ተደናገጠ ተደናበረ ።
ተበራገገ፡ ተፈናከተ ተሳበረ ።
ተበርባሪ፡ የሚበረበር፡ ተበዝባዥ ።
ተበሸረከ፡ ተበጠረቀ ተቀደደ ተሸረ ከተ ።
ተበሸራረከ፡ ተቀዳደደ ተሸረካከተ ።
ተበሸቃቀጠ፡ ተነቃቀፈ ተሰዳደበ ።
ተበሸተ፡ ታመመ ተደወየ ።
ተበሺ፡ የሚበሳ፡ ሞፈር ቀንበር የመሰለው ኹሉ ።
ተበሻቀጠ፡ ተራራሰ ተበሳበሰ፡ ተነ ወረ ተነቀፈ ተሰደበ ረከሰ ።
ተበሻቀጠና አበሻቀጠ፡ ተደራራጊና አደራራጊ ሲመስሉ፡ በተደራጊነትና ባድራጊ ነት እንደ ተፈቱ አስተውል ።
ተበቀለ፡ ዕዳ ብድራት ከፈለ፡ ቂምን ዶምን አወጣ መለሰ ። (መሳ ፮ ፥ ፴፩ ። ራእ ፲፰ ፥ ፮ ፥ ፲፱ ፥ ፪) ።
ተበቀበቀ፡ በጣም ታረሰ ።
ተበቀተ፡ ተነዘነዘ ተነተረከ ተወቀ ወቀ ።
ተበቃች፡ የሚበቀት ።
ተበቃይ (ዮች)፡ ቂመኛ ደም መላሽ ። (ዘዳ ፲፱ ፥ ፮ ። ናሖ ፩ ፥ ፪) ።
ተበበት፡ በብብት ተያዘ፡ ከብብት ገባ ተከተተ ።
ተበተበ
ተበተበ ተጕላላ
ተበተበ፡ ዐመ ደገመ ("አሰረ" ብለኸ "አሰርኩሽን" እይ) ።
ተበተበ፡ ወረረ ያዘ ከበበ ። ተብታቢ (ዎች)፡ የተበተበ/የሚተ...በትብ (አሳሪ አስማተኛ ጕንዳን ዕከክ) ።
ተበተበ፡ ጠመጠመ (በብዙ ወገን እሰረ አረተ አከተ) ።
ተበተበተ፡ ተቦረቦረ ተቦጠቦጠ ተፈ ለፈለ፡ ተበላ ተቃጠለ ተበገበገ ።
ተበተብ/ተብታባ፡ ኰልታፋ ለንባዳ (አፈ እስር - ወንዱን "አንቺ" ሴቷን "አንተ" የሚል መሣቂያ) ።
ተበተብኩሽ ("አሰርኩሽ ተበተብኩሽ" - "አሰረን" እይ) ።
ተበተነ፡ ተዘራ ተዘረዘረ ተለየ ተፈታተነ ነሰነሰ ። (ኢሳ ፲፩ ፥ ፲፪ ። ፴፫ - ፫ ። ያዕ ፩ ፥ ፲፪ ፥ ፲፫) ።
ተበተከ (ተበትከ)፡ ተበሰከ ተቈረጠ ።
ተበታተነ፡ ተለያየ ተሠራጨ ተወራኘ ።
ተበታተከ፡ ተበሳሰክ ተበጣጠሰ ተቈ ራረጠ ።
ተበታኝ፡ የሚበተን፡ ጉም ደመና ጭስ ዐመድ ትቢያ ዐቧራ ሰራዊት ።
ተበከለ፡ አደፈ ተበላሸ ተኰለፈ ጠፋ ቈሸሸ ።
ተበከረ (በከረ ተበኵረ)፡ በካር ኾነ፡ ወለደ ። (ምርቃት)፡ ጨምሪ ጨምሪ፡ በወንድ ልጅ ተበከሪ ።
ተበከረች (ተበኵረት)፡ መዠመሪያ ወለደች ።
ተበዘበዘ፡ ተዘረፈ ተቀማ ተበረበረ፡ ተበተነ ባከነ ። (ኤር ፱ ፥ ፲፱ ። ዮኤ ፩ ፥ ፲) ። (ተረት)፡ ላም ሲበዘበዝ ጭራውን ያዝ ።
ተበዛበዘ፡ ተዛረፈ ተቃማ ተሻማ ።
ተበዣገደ፡ ተሳሳተ ተበላሸ አእምሮው ።
ተበየነ፡ ተተቸ ተፈረደ ተለየ፡ ነገሩ ሰዉ ።
ተበየነለት፡ ተፈረደለት ። (ቅጽል) ።
ተበየነበት፡ ተፈረደበት ።
ተበየዶ፡ ተደፈነ ተመረገ ተቀባ ።
ተበያጅ፡ የሚበየድ፡ ተደፋኝ ቈርቈሮ ታኒካ ።
ተበደለ፡ ታመፀ ተገፋ ። (ተረት)፡ ድኻ ተበድሎ ማሩኝ ይላል ቶሎ ። ተለወጠ ተቀየረ ።
ተበደረ (ተበድረ)፡ ታረጠ ተለቃ ተሰጠ ገንዘቡ፡ ወይም ሰዉ ገንዘብ ወሰደ ። (ዘዳ ፳፰ ፥ ፲፪) ። አትበደር፡ ባለኸ ዕደር ።
ተበደገ፡ ተሠነጠቀ ተለየ ተከፈለ ።
ተበዳሪ (ሮች)፡ የተበደረ የሚበደር የተለቃ የተዋሰ፡ ልቆኛ ። (ምሳ ፳፱ ፥ ፲፫ ። ኢሳ ፳፬ ፥ ፪ ። ሉቃ ፯ ፥ ፵፩) ።
ተበዳይ፡ የሚበደል ። (፪ቆሮ ፯ ፥ ፲፪) ።
ተበዳደለ፡ ተማመፀ ክፉ ተሣራተ ጐዳዳ ተጨቋቈነ ።
ተበዳደረ (ተባደረ)፡ ተሰጣጠ ተቀ ባበለ ብድርን ።
ተበጀ (በጀ)፡ ተሠራ ተዘጋጀ ማለ ‰ያ ኾነ ተሻለ ።
ተበጃጀ፡ ተሰማመረ ተጊያጊያጠ ።
ተበገረ፡ ተሞከረ ተፈተነ፡ ተነደፈ ተመጠነ ተሣለ ተመለከተ ።
ተበገረ፡ ተደፈረ ።
ተበገበገ፡ ተተኰሰ ተቃጠለ ተገረፈ፡ በብዙ ቈሰለ ። ገበገበን ተመልከት፡ የበገበገ ግልባጭ ነው ።
ተበጋሪ፡ የሚበገር የሚሞከር የሚደፈር የሚነድፍ ።
ተበጠሰ፡ ተበተከ ተበሰከ፡ ተቀነጠሰ ።
ተበጠረ፡ ተነፈሰ ተንገዋለለ ተንቀረቀበ ጥሩ ኾነ፡ ቆመ ።
ተበጠረቀ፡ ተነደለ ተበሳ ተሸነቈረ ።
ተበጠበጠ፡ ተጠመቀ ተበረዘ ተደረጠ ታመሰ ደፈረሰ፡ ታወከ ።
ተበጣ (ተበጥሐ)፡ ተፈቃ ተቈራ ተተፈተፈ ተሠነተረ፡ እንደ ሻንቅላ ቈዳ ።
ተበጣሪ፡ የሚበጥር ጤፍ ጐፈሬ ።
ተበጣሽ፡ የሚበጠስ፡ ተቈራጭ ።
ተበጣበጠ፡ ተበሳጩ ተናደደ፡ ተወዛወዘ ።
ተበጣባጭ፡ የሚበጣበጥ፡ ተበሳጪ ።
ተበጣጠሰ፡ ተበላሸ፡ የወተት ።
ተበጣጠሰ፡ ተንደላቀቀ ተሞላቀቀ ፥ ተቀማጠለ ።
ተበጣጠሰ፡ ተጐማመደ ተቈራረጠ ። (ተረት)፡ ለጥምቀት ያኾልነ ቀሚስ ይበጠጣስ ።
ተበጣጠሰ፡ ተጣላ ተለያየ ።
ተበጣጠረ፡ ተገተ ተከራከረ ተነጣ ጠረ ተነጋገረ ተለያየ ።
ተበጣጣ፡ ተሠነታተረ ።
ተበጥባጭ፡ የሚበጠበጥ፡ ማር ተልባ ኑግ ሰሊጥ ሱፍ መድኀኒት ።
ተበጨቀ (ተበትከ)፡ ተሰጠሰ ፥ ተቈ ረጠ፡ ተበተከ ተበሰከ ።
ተበጫጨቀ፡ ተቈራረጠ ተበጣጠሰ ተቀዳደደ ።
ተበጯ፡ የሚበጣ ተሠንታሪ፡ ዕብጠት ።
ተቢዠ (ተቤዘወ)፡ ተዋጀ ተገዛ፡ ቤዛ አገኘ ዳነ፡ ነጻ ወጣ ተለቀቀ ። ልማዱ ግን አዳነ ነው ። መጽሐፍም በጸሓፊ ምክን ያት በተቤዠ ፈንታ ተበጀ ይላል፡ የስሕተት ስሕተት ነው ። (መዝ ፳፭ ፥ ፳፪ ። ፻፮ ፥ ፲ ። ኤር ፲፭ ፥ ፳፩ ። ሚክ ፬ ፥ ፲) ።
ተባ (በልኀ)፡ ተሞረደ ሰላ ፈጠነ ።
ተባ (ተብዐ/ጠብዐ)፡ ጨከነ ጠነ...ከረ (ወንድ ወጣው) ።
ተባለ (ተብህለ)፡ ተተነባ ተወራ ተነገረ፡ ተጠራ ተሰየመ ። (እሱ ማን ይባላል፡ አንተ ማን ትባላለኸ)፡ ስሙ ስምኸ ማነው ። (ይባላል)፡ ይወራል። (አይባልም)፡ አይወራም፡ አይነገርም ።
ተባለ፡ ተመታ ተመደወተ ።
ተባለጠ፡ ተዛነፈ ። መጽሐፍ ግን በበለጠ ፈንታ ተባለጠ ይላል ። (፪ቆሮ ፪ ፥ ፲፩) ።
ተባለጥ፡ ተዛነፍ ።
ተባላ (ተባልዐ)፡ ተናከሰ ተጋመጠ ተቧወቀ ተዘባተረ፡ (ነከሰ በላ) ። መጽሐፍ ግን ተፋጀ በማለት ፈንታ ተባላ ይላል ። (፩ሳሙ ፬ ፥ ፲፫) ።
ተባሰለ፡ ተጣላ ተማረረ ተናሸረ ።
ተባረረ፡ ተሳደደ ተሯሯጠ ተቻኰለ ። (፩ሳሙ ፬ ፥ ፲፪ ። ኢሳ ፲፫ ፥ ፲፬) ።
ተባረከ፡ መስቀል የቄስ እጅ ሳመ ተሳለመ ።
ተባረከ፡ ተመሰገነ ተመረቀ፡ ምር ቃት ተቀበለ ።
ተባረከ፡ ተቀደሰ፡ በዛ በረከተ ዘሩ ።
ተባረከ፡ ተከረከረ ታረደ ። ተባረክ፡ ዘር ይውጣልኽ ።
ተባረዘ፡ ተቀላቀለ ተደባለቀ ተካለሰ ።
ተባረደ፡ ተባረዘ ተበራረዘ፡ ተዳከሙ፡ የኀይል የጕልበት የመንፈሳዊ ሙቀት ።
ተባራሪ፡ የሚባረር፡ ጥይት ኮሶ ።
ተባራኪ፡ የሚባረክ፡ ተቀዳሽ ተመራቂ ።
ተባቀተ፡ ተነታረከ ተጨቃጨቀ ።
ተባቃ፡ ተዳከመ ተሰላቸ ተጣገበ፡ ልክ ተኳዃነ ተካከለ ።
ተባበለ (ተሓበለ)፡ ተካካደ/ተሸፋፈጠ (አልተማመነም) ።
ተባበለ፡ ተሽበለበለ ተለመነ ተቈላ መጠ ።
ተባበለች፡ በወርቅ እንክብል በሸማ ጥቅል ተለመነች ።
ተባበሰ፡ ተጠራረገ ፥ ተወዛዛ ።
ተባበረ (ተኃበረ)፡ ተመሳሰለ/ተዋሐደ/ ተሰማማ/ተጋጠመ/ተሻረከ/አንድ ተኳዃነ ("(ማቴ. ፳፫፥፴ - ግብ. ሐዋ. ፲፰፥፲፪)") ።
ተባባለ (ተባሀለ)፡ ተነጋገረ ተማ ገተ ተከራከረ ተማከረ ። (፩ሳሙ ፲ ፥ ፲፩ ። ኢዮ ፪ ፥ ፲፩) ። ውረድ እንውረድ ተባባሉና፡ አስደበደቡት አፋፍ ቆሙና ።
ተባባለ፡ ተማታ ተደባደበ ተዋጋ ።
ተባባሰ (ተባአሰ)፡ ተከፋፋ ተጣላ ተጠላላ ተናሸረ ተማረረ ። (ተረት)፡ ቀን ለተ ባባሰው ማጭድ አታውሰው ። ያጨሽ ላያገባሽ ከባልሽ ሆድ አትባባሽ ።
ተባባሪ (ዎች)፡ የተባበረ/የሚተባበር (ተሻራኪ ") ።
ተባባሪነት፡ ተባባሪ መኾን።
ተባባተ (ተባሐተ)፡ ተሳለፈ ተዋጋ ታገለ ተጋደለ፡ ተሸናነፈ ።
ተባተበ፡ ደጋገመ ።
ተባተበ፡ ጠማጠመ መላልሶ አሰረ ።
ተባት (ተባዕት)፡ ወንድ ሴትን የሚ...ያሶልድ ።
ተባት፡ ቍልፍ (ወንዴ ቍልፍ ከሴቴው ጋራ የሚገጥም - ሴቴው የሐር ቋድ ነው) ።
ተባትና እንስት (ተባዕት ወእንስት)፡ ወንዴና ሴቴ (ደንጊያ ዐፈር ውሃ ዕንጨት እንስሳ አውሬ ወፍ ሰው ወይም ሌላ ፍጥረት - ዘፍ.
፯፡ ፪፡ ማር. ፲፡ ፮) ።
ተባነነ (በነነ)፡ ተበታተነ ተጫጫሰ ።
ተባከለ፡ ተዳደፈ ።
ተባዘተ (ባዘተ)፡ ተነቀሰ ባዘቶ ኾነ ።
ተባዛ (ተባዝኀ)፡ ተዋለደ ተራባ ። (ዘፍ ፩ ፥ ፳፰) ።
ተባይ (ዮች)፡ የሚበላ የሚባላ፡ ትዃን ቍን ቅማል ጕንዳን ዘመሚት ዝንጀሮ ጦጣ ዕሪያ ዐሣማ ።
ተባደለ፡ ተለዋወጠ ተቀያየረ፡ ተለያየ ተጓዳ ኾነ ።
ተባደላ ኾነ፡ የተራራቀ የተፈራረቀ ።
ተባደላ፡ የተለዋወጠ የተለያየ ።
ተባደገ፡ ተለያየ ተከፋፈለ ተሠነጠቀ ጠቀ ።
ተባጠሰ፡ ተቋረጠ ።
ተባጣ (ተባጥሐ)፡ ተሠናተረ ።
ተቤተ፡ ታበየ/ኰራ።
ተቤተ፡ ኰራ ዐበየ ። ትቢት፡ ኵራት ዐበየ ።
ተብለጠለጠ፡ የበለጠ ድርብ፡ ላቅ ላቅ ከበር ከበር አለ፡ ተትኰረኰረ ።
ተብለጥላጭ፡ የተብለጠለጠ የሚብለጠለጥ፡ ትትኰርኳሪ ።
ተብለጨለጨ፡ የበለጩ ድርብ፡ ብልጥ ብልጭ ቦግ ቦግ ተግ ተግ አለ ።
ተብላላ፡ ተሳሳበ ተዋዋደ ። ድፍድፉ ተብላልቷል ።
ተብሰለሰለ፡ ተንገበገበ ተትከነከነ፡ በ ልብ ወጣ ወረደ ።
ተብሰከሰከ፡ ተንበሸበሸ ተቀማጠለ ።
ተብሰክሳኪ፡ የሚብሰከሰክ የሚቀማጠል ።
ተብረቀረቀ፡ ተብለጨለጨ፡ ተፍለቀለቀ ። ብልጭ ብል ፍልቅ ፍልቅ አለ ።
ተብረከረከ፡ ፈጽሞ ጕልበት ዐጣ፡ ተንቀጠቀጠ ።
ተብረዠረዠ፡ ተጨፈነ፡ ተንገደገደ ተንቦዠቦዠ ። መጽሐፍ ግን ተብረጀረጀ ይላል ። (መዝ ፻፯ ፥ ፳፯ ። ዘካ ፱ ፥ ፲፭) ።
ተብቃቃ (በቃ)፡ ፈጽሞ በቃ፡ ልክ ኾነ፡ (ተዳረሰ) ።
ተብተብ አለ፡ ቸኰለ ።
ተብተከተከ፡ ተብሰከሰከ ተቈራረጠ ተበጣጠሰ፡ አማረ ሰመረ፡ ዐይን ብቻ ኾነ ።
ተብከነከነ፡ ግራ ቀኝ አየ፡ ተቅበዘበዘ ።
ተብጠለጠለ (ተበጽለ)፡ ፈጽሞ ተቀደደ ተበተነ፡ እንደ ቀይ ሽንኵርት ተላጠ ተመለጠ ።
ተብጠሰጠሰ፡ ተንቀባረረ፡ ፈጽሞ ተበላሸ ። ወተት ሲሉት ማር፡ ማር ሲሉት ወተት ስጡኝ አለ፡ ባለግ ።
ተቦረቀ፡ ተወረበ ።
ተቦረቀ፡ ተዘለለ ጮቤ ተመታ ።
ተቦረቦረ (ተበረበረ)፡ ተጐረጐረ ባዶ ኾነ ።
ተቦቀረ፡ ተላጨ ሳዱላ ኾነ ።
ተቦተረፈ፡ ተነከሰ ተቦጨቀ ተወሰደ ሥጋው ።
ተቦደሰ፡ ተገመሰ ተጐመደ ።
ተቦደነ፡ በመቅን ታረሰ ተተለመ ።
ተቦደነ፡ በርግብግቢት ላይ ሸብ ተ ደረገ ተደገደገ ።
ተቦደነ፡ ተጠመረ ተደረበ ገጠመ ።
ተቦጠለቀ፡ ወጣ ። ሕፃኑ ነገር ተቦጠ ለቀው፡ ይቦጠለቀዋል እንዲሉ ።
ተቦጠቦጠ፡ ተበተበተ ተጐረጐረ፡ ውስጥ ውስጡ ተበላ ።
ተቦጨቀ (ተበጨቀ)፡ ተባዘተ ታወደ ተቈረጠ ታማ ።
ተቦጫቂ፡ የሚቦጨቅ፡ ታጅ ።
ተቦጫጨቀ፡ ተቀዳደደ ተበጣጠሰ ።
ተቧደነ፡ ተጣመረ ተያያዘ ተቀናጀ ተጋጠመ፡ አንዳንድ ወገን ኾነ ።
ተቧዳኝ፡ የሚቧደን ።
ተቧጠጠ፡ ተጠጠ ተጨረ ።
ተቧጣጭ፡ የሚቧጠጥ፡ ጕረሮ ለግዳ ቅምሖ ።
ተቧጨረ፡ ተወረ ተጫረ ተሰነ ዘረ ታከከ ።
ተቧጨቀ፡ ተናከሰ ተባላ ተናጠቀ ።
ተተ ፣ ተጋደለ፡ ተገዳደለ፡ ተላለቀ፡ ተጣፋ ።
ተተለመ፡ በበሽታ ተያዘ ተለከፈ ።
ተተለመ፡ ተዠመረ ታረሰ ተቦደነ ተገ...መሰ ።
ተተለተለ፡ ተቀደደ ተሠነጠቀ ተበጣ ።
ተተለተለ፡ ተፈታ ተተረተረ ተመዘዘ ተለየ ወጣ ።
ተተላሚ፡ የሚተለም (ተዠማሪ) ።
ተተመተመ፡ ተመታ ተለተመ ተገጨ...ተወጛ ።
ተተመተመ፡ ተረመደ ።
ተተመተመ፡ ተደመደመ ።
ተተማተመ፡ ተላተመ ተጋጨ ተዋጋ ።
ተተማታሚ፡ የሚተማተም (ተላታሚ...አውራ በግ) ።
ተተረማመሰ፡ ተበጣበጠ ተመሰቃቀለ ።
ተተረረ፡ ተሠነጠቀ ተከፈለ ።
ተተረበ፡ ተነደፈ ተወጋ ።
ተተረተ፡ ተመሰለ ተነገረ ተወጋ (ተወግዐ) ።
ተተረተረ፡ ቀና ቀጥ አለ (የሰውነት) ።
ተተረተረ፡ ተዘረዘረ ተነጠለ (ነገሩ) ።
ተተረተረ፡ ተፈታ ተለየ ። ተተረተረ፡ ተነጠቀ ተፈነከተ (፩ነፃ. ፲፫፡ ፭) ።
ተተረተረ፡ ዕዳሪው ወጣ ተጨፈለቀ ።
ተተረከ፡ ተወጋ ተነገረ ተወራ ።
ተተረከሰ፡ ተቀለሰ ጐበጠ ።
ተተረከከ፡ ተጠረቀቀ ተሠነጠቀ ተፈ...ነከተ ።
ተተረኰሰ፡ ተሰበረ ተኰሰተረ ለማ ።
ተተረጐመ (ተተርጐመ)፡ ተገለበጠ...ተመለሰ ተፈታ ተገለጠ ።
ተተራተረ፡ ተፈናከተ ።
ተተራከከ፡ ተፈናከተ ።
ተተራጐመ፡ ተፋታ ርስ በርሱ ።
ተተርታሪ፡ የሚተረተር (ተሠንጣቂ) ።
ተተበተበ፡ ተወረረ ተያዘ ተከበበ (ሥጋው ሰውነቱ) ።
ተተበተበ፡ ተጠመጠመ ታሰረ (ማሰሪያው ሰውየው) ።
ተተበተበ፡ ታዘመ ተደገመ (አስማቱ) ።
ተተባተበ፡ ተጠላለፈ ተጠማጠመ ተሳሰረ ተያያዘ ተወሳሰበ (ዕብ. ፲፪፡ ፩) ።
ተተብታቢ፡ የሚተበተብ ።
ተተቸ፡ ታተተ ተባለ ተነገረ (ትቹ) ።
ተተነባ፡ ተነገረ/ተባለ/ተወራ ድሞ።
ተተነተነ፡ ተለየ ተከፈለ ተመደበ ተደለደለ ተቈነነ ታደለ ።
ተተነኰለ፡ ኾነ ተደረገ (ተንኰል ልማዱ ግን እንደ መዠመሪያው አድራጊነት ነው - ዘፍ.
፴፩፡ ፯፡ ዘዳ. ፲፱፡ ፲፩) ።
ተተነኰሰ፡ ጥቂት ተመታ ላመል ተ...ለኰፈ ተነካ ።
ተተነኳኰለ፡ ተንኰል ተሠራራ ተጐ...ዳዳ ።
ተተነኳኳይ፡ የተተነኳኰለ/የሚተነኳ...ኰል ።
ተተነፈሰ፡ ጥቂት ተባለ/ተነገረ ቃሉ (ወጣ ትንፋሹ - ኢዮ. ፲፭፥፪) ።
ተተናተነ፡ ተጋራ ተካፈለ ተከፋፈለ ተዳረሰ ተዳደለ ።
ተተናታኝ፡ የሚተናተን (ተካፋይ) ።
ተተናኰለ፡ ተጣላ ጐዳ ተጠናወተ ።
ተተናኰሰ፡ ተላኰፈ ተናካ ።
ተተናኳይ (ዮች)፡ የተተናለ/የሚ...ተናኰል (ተናዋች) ።
ተተናኳይነት፡ ተተናኳይ መኾን ።
ተተናፈሰ፡ ትንፋሽ ተቀባበለ ("እፍ ተባባለ" - ተደራራጊ)
ተተናፈሰ፡ ወዳፍንጫው ነፋስን አግብቶ አወጣ ("አድራጊ") ።
ተተኛኛ፡ ተዋደቀ በግብረ ሥጋ ተገነኛኘ ተዋወቀ ።
ተተከለ፡ ቤስት ተቀበለ ።
ተተከለ፡ ተመሠረተ ጸና ለማ ።
ተተከለ፡ ተቸከለ ተቀሰቀሰ ተከሰመ...ተሻጠ ገባ ተሸጐጠ ቆመ (፩ሳሙ. ፲፯፡ ፵፱፡ ሕዝ. ፲፱፡ ፲፫፡ ሉቃ. ፲፯፡ ፯፡ ሮሜ. ፯፡ ፭) ።
ተተከተከ፡ ተጠቀጠቀ ተወጋ ተብላ ።
ተተኪ፡ የሚተካ/የሚወከል (ተወካይ) ።
ተተኪነት፡ ተወካይነት ።
ተተካ፡ ተወከለ ተሰጠ ተከፈለ ተረጠበ...ስጦታው ለሰው ሰውየው ስጦታን ።
ተተካከለ፡ ተደላደለ ፥ ተበጃጀ ፥ ተዘጋጀ፡ ተወዳደረ ።
ተተካይ፡ የሚተከል ቀዋሚ ።
ተተኰሰ፡ መላ ተፈጸመ ተጨረሰ ።
ተተኰሰ፡ ተለኰሰ ተለበለበ ተቃጠለ (ኢሳ. ፵፫፡ ፪) ።
ተተኰሰ፡ ተላከከ ተገጠመ ተቀባ ።
ተተኰሰ፡ ተካሰ ተቀበለ ።
ተተኰሰ፡ ተዳመጠ ቀጥ እለ ።
ተተኰሰ፡ ጮኸ ተሰማ (ጥይቱ) ።
ተተኰረ፡ ታየ ዐይን ተጣለበት ።
ተተኳኰሰ፡ ተለኳኰሰ ተለባለበ ።
ተተኳኰረ፡ ተፋጠጠ በትኰራ ተያየ ።
ተተወ፡ ተለቀቀ ተፈታ ተገደፈ ተጣለ ቀረ ተማረ (ነሐ. ፮፡ ፱፡ ኢሳ. ፳፯፡ ፲) ። ተው፡ ልቀቅ ጣል ።
ተተገ፡ በክፋይ መታ ወጋ አቃጠለ ("ተገተገን" እይ) ።
ተተገተገ፡ ተገረፈ ተተኰሰ ።
ተተገነ፡ ተጠጋ ተጠለለ (የሰው...) ።
ተተገነ፡ ታጠረ ተቀጠረ ተጀጐለ ተከለለ ታቀበ (የተክል ቦታ በካብና በንጨት) ።
ተተፈተፈ፡ ተበጣ ተፈቃ ተቈራ...ተቈረጠ ተሠነተረ ።
ተተፋ፡ ተቀረሸ ወጣ ተመለሰ ።
ተታለለ፡ ተደለለ ተሸነገለ ተሞኘ ቄለ ደነቈረ ዘነጋ (ኤር. ፳፡ ፯፡ ፩ጢሞ. ፪፡ ፲፬) ። ተታላይ (ዮች)፡ የሚታለል/የሚደለል...ተደላይ ።
ተታለመ፡ ተዣመረ ።
ተታላይነት፡ ተታላይ መኾን ሞኝነት ንዝህላልነት ።
ተታታ፡ ተጠፈረ ተጠለፈ ተዋሰበ ተያያዘ ።
ተታከለ፡ ርስት ተሰጣጠ ተቀባበለ ።
ተታከለ፡ ተቻከለ ።
ተታኰሰ፡ በጥይት በእሳት ተማታ ተ...ዋጋ ተቋላ ተጣበሰ ።
ተታኰሰ፡ ተላኰሰ ።
ተታጊ (ዎች)፡ የተተገ/የሚተትግ (ወጊ አቃጣይ) ።
ተታጋ (ተታግሀ)፡ ትጋትን ተሰጣጠ ።
ተትመሰመሰ፡ ተድበሰበሰ ተድመሰመሰ...ተርበተበተ መለስ ቀለስ አለ ።
ተትመከመከ፡ ተድበሰበሰ (ነገሩ እሳት ጢስ ሳይነድ እንደ መቅረት) ።
ተትመከመከ፡ ተድበሰበሰ፡ ተ...መከ ።
ተትረፈረፈ፡ የትርፍ ትርፍ ኾነ ።
ተትከነከነ፡ ተብሰለሰለ ተናደደ ።
ተትጊ (ትግ)፡ ፋደት ዐራጅ (ኢሳ. ፴፬፡ ፲፩፡ ሶፎ. ፪፡ ፲፬) ።
ተትጐለጐለ፡ እንደ ጉም በዝቶ ተጣቦ ወጣ (የጪስ የላበት) ።
ተቶረበ፡ ተሰፋ ተወሰወሰ ተሸደሸደ ተሸለለ ተሸከሸከ ።
ተቸ (ሐተተ)፡ ዐተተ (የነገር ማስረጃ እመጣ) ። ("ተረት" - ብዙ ቢተቹ ይሰለቹ) ።
ተቸለሰ፡ በማዥራት...ተኛ ተዝለሰ ።
ተቸለሰ፡ ተከነበለ ተገለበጠ ተደፋ ።
ተቸመቸመ፡ ተሠራ ተዘራ ቆመ...በዛ ።
ተቸመቸመ፡ ተቸረቸመ ጠረሰ ተደ...መደመ ።
ተቸሰረ፡ ተፈተ ተደነሰረ ።
ተቸረቸመ፡ ተሰበረ ተሸረፈ ጠረሰ ታ...ጠፈ ።
ተቸረቸረ፡ ተበተነ ተተነተነ ተዘረ...ዘረ ተሼጡ ።
ተቸረቸፈ፡ ...፡ ተቸረቸ - ፈ፡ የሙ ለውጥ ።
ተቸበቸበ፡ ተሸጠ ተለወጠ ።
ተቸበቸበ፡ ተጣለ ተመታ ተደበደበ...ተወቃ ።
ተቸበቸበ፡ ተጨበ ሬበ ።
ተቸበቸበ፡ ታረደ ተቈረጠ ።
ተቸቸረ፡ ተዝፈረ ተቃመ ።
ተቸነነ፡ ተወነገ ተወሰጠ ።
ተቸነነ፡ ተጀነነ ኰራ ተቈነነ ተዓደደ ።
ተቸነከረ፡ ተሰመረ ተወጋ ተመታ ተጣበቀ (መክ. ፲፪፡ ፲፩) ።
ተቸናኝ፡ የሚቸነን (ተጀናኝ ተጓዳጅ) ።
ተቸከለ፡ ተተከለ ተቀበቀብ እመሬት ።
ተቸኰለ (እምከመ ጐጕአ)፡ መንገደኛው ተ(ከ)ቸኰለ ቶሎ ይኺድ ። ተ በከ ሞክሼነት የተነገረ ዐቢይ እገባብ ነው እንጂ የመደረግ ልማድ አለመኾኑን አስተውል ።
ተቸገረ፡ ተጨነቀ ተራበ ተጠማ ታረሀ ፧ዐጣ ነጣ ደኸየ ግራ ገባው (ግብ. ሐዋ. ፲፡ ፲፯፡ ያዕ. ፬፡ ፱) ።
ተቸጋሪ፡ የሚቸገር (ተጨናቂ) ።
ተቸፈገ፡ ተፊተ ተጠቀጠቀ ።
ተቸፋቸፈ፡ ተዐቃቤኯ ተነዛነዙ ።
ተቺ (ዎች)፡ የተቸ/የሚተች (ሐተተኛ) ።
ተቺነት፡ ተቺ መኾን ።
ተቻለ (ተክህለ)፡ ተወሰነ ተጨረሰ ።
ተቻለ፡ ተመቸ ኾነ ደላ ተደረገ ። "ዛሬ አይቻለኝም በተቻለኝ ጊዜ እመጣለኹ" ።
ተቻቻለ (ተካሀለ)፡ ተሸካከመ ተወሳሰነ ተጣወረ ተጋገሠ (ኤፌ. ፬፡ ፪) ።
ተቻቻረ፡ ችሮታን ተቀባበለ ።
ተቻቻይ፡ የሚቻቻል ተጣዋሪ ።
ተቻቻይ፡ የቅኔ ኣገባብ ።
ተቻቻይነት፡ ተቻቻይ መኾን ።
ተቻኰለ፡ ተጣደፈ ተፋጠነ ተጐታ...ጐተ ።
ተቻኳይ፡ የሚቻኰል (ተጣዳፊ ተፋ...ጣኝ) ።
ተቻይ፡ የሚቻል።
ተነ (ከነ)፡ መነሻነትንና አንድነትን የሚያሳይ ደቂቅ አገባብ ኹኖ ከነ በገባበት ይገባል ።
ተነ፡ ተነቀለ።
ተነኋረጠ፡ ተነፋነፈ።
ተነሰነሰ፡ ተበተነ/ተዘራ/ተጐዘጐዘ።
ተነሰነሰ፡ ተወዘወዘ/ተንቀሳቀሰ።
ተነሣ (ተነሥአ)፡ ተከለከለ/ራቀ/ ተወሰደ/ተገለለ ("ዳዊት ኦርዮን ባስገደለ ጊዜ ረድኤት ተነሣው") ።
ተነሣ (ተንሥአ)፡ አፈፍ ብድግ ኩፍ አለ (ቆመ ነወር አለ ስፍራውን ተወ - "የሰውን ልጅ ተነሣ አይሉም እስኪነሣ ይጠብቋል") ።
ተነሣ፡ ብድግ አለ፡ ነሣ ።
ተነሣ፡ ተቀነሰ/ጐደለ።
ተነሣ፡ ተንሳፈፈ/ተንካፈፈ።
ተነሣ፡ ተወሣ/ተነገረ ("(እሳት ተነሣ)" - ቃጠሎ ኾነ - "(ነፋስ ተነሣ)" - በኀይል ነፈሰ ዐቧራው ቀጥ አለ - "(ጾር ተነሣበት)" - ፍት
ተነሣ፡ ተዠመረ/ተወጠነ።
ተነሣ፡ ከበረ/ገነነ።
ተነሣ፡ ወጣ/ለቀቀ።
ተነሣ፡ ዳነ/ተፈወሰ ("ታሞ የተነሣ እግዜርን ረሳ") ።
ተነሣለት፡ ብድግ አለለት።
ተነሣለት፡ ተቀነሰለት (አከበረው) ።
ተነሣሣ፡ (በክፉ ተነሣ ተገሰለ) ተ
ተነሣሣ፡ ተከላከለ።
ተነሣሽ፡ የሚነሣሣ (ተቋቋሚ) ።
ተነረተ፡ ተመታ/ተጠዘለ።
ተነረተ፡ ተነፋ/ተቀበተተ።
ተነሸጠ፡ ታሰበ ' ተነሣሣ ።
ተነሽ፡ የሚነሣ/ብድግ የሚል ሰው ዕቃ ከብት (በኀይለ ቃል የሚነገር ንባብ) ።
ተነሽ፡ ጐዳይ/ተቀናሽ ነገር ገንዘብ ቍጥር።
ተነሽ/ሺ፡ ብድግ በይ።
ተነሽናሽ፡ የሚነሰነስ (ተበታኝ ያን እንገባን ዐጡንባር) ።
ተነቀለ፡ ተመዘዘ/ነገለ/ተመነገለ/ወጣ ' ወለቀ (ሕዝ. ፲፱፥፲፪፡ ሉቃ. ፲፯፥፮)
ተነቀለ፡ ከርስቱ ተወገደ።
ተነቀሰ፡
ተነቀሰ፡ ተመሰከረ።
ተነቀሰ፡ ተሸለመ/አማረ።
ተነቀሰ፡ ተቀነሰ/ጐደለ።
ተነቀሰ፡ ተበጠረ/ተለየ/ጠራ።
ተነቀሰ፡ ተነቀለ/ወጣ ("ነገር በነገር ይጠቀሳል እሾኸ በሾኸ ይነቀሳል።")
ተነቀሰ፡ ተጠቀጠቀ/ተወጋ/ተወቀረ/ጠቈረ ("(ተረት)" - አላንድ የላትጥርስ በዘነዘና ትነቀስ) ።
ተነቀረ፡ ተጠጠ/ተጨለጠ።
ተነቀበ፡ ተበሳ/ተነደለ/ተሰፋ።
ተነቀተ፡ ተከረተፈ (ተቀቀለ እንቀት ' ኾነ ") ።
ተነቀነቀ፡ ተቀሰቀሰ/ተወዘወዘ ' (ኢሳ. ፳፬፥፳፡ ሉቃ. ፮፥፴፰) ' #1
ተነቀፈ፡ ተሰደበ/ተናቀ/ተጸየፈ/ተነወረ ' ተወቀሠ ' ተዘለፈ ።
ተነቀፈ፡ ተሰደበ/ተናቀ/ተጸየፈ/ተነወረ ' ተወቀሠ ' ተዘለፈ ።
ተነቃቀለ፡ ተመዛዘዘ/ተመነጋገለ ' ወለ ላቀ።
ተነቃቀሰ፡ ተመሰካከረ።
ተነቃቀሰ፡ ተነቃቀለ።
ተነቃቀሰ፡ ተጠቃጠቀ ("የመናቀስ ብድር ተመላለሰ ተጠቋቈረ") ።
ተነቃቀፈ፡ ተሰዳደበ/ተናናቀ።
ተነቃቀፈ፡ ተሰዳደበ/ተናናቀ።
ተነቃቃፊ፡ የሚነቃቀፍ/የሚናናቅ።
ተነቃቃፊ፡ የሚነቃቀፍ/የሚናናቅ። ን
ተነቃናቂ፡ የተነቃነቀ/የሚነቃነቅ (ተንቀ ሳቃሽ) ።
ተነቃናቂ፡ የተነቃነቀ/የሚነቃነቅ (ተንቀ ሳቃሽ) ።
ተነቃይ፡ የሚነቀል (ተመዛዥ) ።
ተነቃፊ፡ የሚነቀፍ (ተሰዳቢ) ።
ተነቃፊ፡ የሚነቀፍ (ተሰዳቢ) ።
ተነቈረ፡ ተነከሰ/ተወጋ/ተበሳ/ወጣ።
ተነቅናቂ፡ የሚነቀነቅ (ተቀስቃሽ) ።
ተነበበ፡ ተነገረ (ንባቡ/መጻፉ/ሕጉ - ነሐ. ፰፥፲፰፡ ፲፫፥፩) ።
ተነበዘ፡ ልብ ዐጣ/ተለወጠ።
ተነበዘ፡ መነቸከ/ተመረዘ።
ተነበዘ፡ ተሰለበ/ተቈረጠ።
ተነበዘ፡ ተቀማ/ተገፈፈ።
ተነበየ፡ ተነባ (ትንቢት ተናገረ - "ርሳቸውም ይነበያሉ" - ፩ሳሙ. ፲፥፭ - "ነፈሰ" ብለኸ "ተነፈሰን" እይ አካኼዱ ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ተነባ (ነባ)፡ ተለቀሰ/እንባው ፈሰሰ።
ተነባ፡ ተነበየ፡ ትንቢት ተናገረ፡ (ነበየ/ነባ) ።
ተነባ፡ ትንቢት ተናገረ፡ (ነበየ ነባ) ።
ተነባረረ፡ ባጕል ድምጥ ጮኸ/አለቀሰ/ተንዠባረረ።
ተነባበረ፡ ተደራረበ/ተረዳዳ/ተገጣጠመ (ሐጌ. ፪፥፲፭) ።
ተነባባሪ፡ የሚነባበር/የሚደራረብ ("ዐባሪ ተነባባሪ" እንዲሉ) ።
ተነባባሪነት፡ ተነባባሪ መኾን።
ተነባነበ፡ ተነዛነዘ/ተለፋለፈ።
ተነባጀለ፡ ተነኋረጠ።
ተነተሰ፡ ተነከሰ።
ተነተረፈ፡ ተረፈ።
ተነተነ (ነተነ/ተንተነ)፡ ለየ ከ...ፈለ መደበ ደለደለ ቈነነ ዐደለ ። "ተለተለንና ሰነሰነን ሸነሸነን" ተመልከት ።
ተነተፈ፡ ተነፋ።
ተነታረከ፡ ተነዛነዘ/ተጨቃጨቀ/ተባ ቀተ ።
ተነትራኪ፡ የተነተረከ/የሚነተርክ።
ተነነ (ተኒን/ተነ)፡ በነነ ጨሰ...ተበተነ ።
ተነነፍሱ፡ ሳይሞት በሕይወት ሳለ የሰከረው ዓሣ ("ተነነፍሱ ተያዘ") ።
ተነከሌ፡ ርሱ ተነከሌ አያንስም ።
ተነከሰ፡ ተዘነተረ/ተቦጨቀ/ተበላ/ ተዘከዘከ።
ተነከረ (ተነክረ/ተጠምዐ)፡ ተዘ ፈቀ/ተደፈቀ/ተዘፈዘፈ (አከል ገባ ታለለ ራሰ) ።
ተነከረ፡ ተደነቀ።
ተነከረ፡ ተጠመቀ (ሰውየው በጠበል በመድኀኒት) ።
ተነከረ፡ እውሃ ገባ ነከረ ።
ተነከረ፡ ጠነከረ ።
ተነከረ፡ ጠነከረ ተ ።
ተነከታቴው፡ ተነመጨረሻው ።
ተነከነከ፡ ተበላ።
ተነካ፡ ተዳበሰ/ተዳሰሰ (ድል ተባለ ተገጠበ ቈሰለ ተበደለ - "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" - ተረት)
ተነካሪ፡ የሚነከር (ልጥ ገመድ ዐተር ባቄላ ሽንብራ) ።
ተነካከሰ፡ ተዘነታተረ/ተቦጫጨቀ።
ተነካኪ፡ የሚነካካ።
ተነካካ፡ ተላላሰ ዶቄቱ (ተጠላላ ሰዉ) ።
ተነኰለ (ጠነቈለ)፡ መጥፎ ሠራ...አደረገ በረቂቅ (ግብ. ሐዋ. ፯፡ ፲፱) ።
ተነኰሰ (ነከሰ)፡ በቀላል መታ ነካ ።
ተነኰሰ፡ ተነተነ፡ ለኰፈ ።
ተነኰረ፡ ተገለበጠ/በሰለ (እንኩሮ ኾነ) ።
ተነኰተ (ነኰተ)፡ ተቃጠለ (ከነእን ቡጡ ተቈላ በሰለ) ።
ተነኳኰሰ፡ ለኳኰፈ ።
ተነዃለለ፡ ተደናቈረ (የሞኝ አነጋገር ተናገረ) ።
ተነወረ፡ ተደፈረ/ነውረኛ ኾነ ተባለ ስሙ ጠፋ (ኢሳ. ፲፫፥፲፮፡ ሚክ. ፫፥፯) ።
ተነዋሪ፡ የሚነወር።
ተነዋወረ፡ ነውርን ተዘካዘከ።
ተነዘረ፡ ተመታ/ጮኸ።
ተነዘረ፡ ተወረወረ/ተነደፈ።
ተነዘረ፡ ተጸፋ/ሾረ/ተፈተለ።
ተነዘነዘ፡ ተጨቀጨቀ/ተነተረከ።
ተነዛ፡ ተረጨ/ተፈነጠቀ/ተበተነ (ተረት፡ "ጌታ ያዛል ውሃ ይነዛል (ይረጫል)") ።
ተነዛነዘ፡ ተጨቃጨቀ/ተነታረከ።
ተነዛናዥ፡ የሚነዛነዝ (ተጨቃጫቂ) ።
ተነደለ (ተነድለ)፡ ተፈለፈለ/ተሸረሸረ/ተበሳ/ተሸነቈረ/ተቀደደ/ፈረሰ።
ተነደቀ፡ ተገነባ/ተናሰ።
ተነደፈ፡ ተለካ/ተበገረ።
ተነደፈ፡ ተበተነ/ተጠዘጠዘ/ተወጋ (፩ነገ. ፲፩፥፩ - ዳዊት ቤርሳቤሕን ባየ ጊዜ በሐጸ ዝሙት ተነደፈ) ።
ተነዳ፡ ተቀረበ/ተወሰደ/ኼደ (፪ዜና. ፮፥፴፰፡ ምሳ. ፯፥፳፪፡ ኢሳ. ፰፥፲፩፡ ሉቃ. ፰፥፳፱፡ ግብ. ሐዋ. ፰፥፴፪፡ ያዕ. ፫፥፬ - "ያቶ እከሌ መንጋ በወንጭፍ ይነዳል" - እጅግ በጣም ብዙ ነው) ።
ተነዳደለ፡ ተበሳሳ (ጥና) ።
ተነዳፊ፡ የሚነደፍ (ተወጊ) ።
ተነገረ፡ ተባለ/ተወራ/ተሰበከ/ተተረከ/ታወጀ/ተተነባ።
ተነገተ፡ ተያዘ ተንጠለጠለ ባንገት ።
ተነገደ፡ ተኼደ/ተመጣ (ተገዛ/ተሼጠ/ተለወጠ) ።
ተነጋሪ፡ የሚነገር ትምርት/ዐዋጅ/ትእዛዝ።
ተነጋገሠ፡ ተመሰጋገነ (ንጉሥነትን ተቀባበለ) ።
ተነጋገረ፡ ተባባለ/ተገተ/ተከራከረ።
ተነጋገረ፡ ተጫወተ/ተጨዋወተ።
ተነጋጋሪ፡ የተነጋገረ/የሚነጋገር (ተማ ጋች) ።
ተነጋጋሪነት፡ ተማጋችነት/ጠበቃነት።
ተነጐረ፡ ነጐረ።
ተነጐተ፡ ተጋገረ (ዕንጐቻ ኾነ ") ።
ተነጓለለ፡ ተደናቈረ (እንደ ነጕላ ተናገረ/ተነፋለለ) ።
ተነጠለ፡ ተለጠጠ/ተለየ (ነጠላ ኾነ ተዘረጋ) ።
ተነጠሰ፡ ኾነ ተደረገ ንጥሻው ።
ተነጠረ፡ ነጠረ።
ተነጠቀ (ተመሥጠ)፡ አፈፍ አለ (ምድር ለቀቀ ወደ ላይ ወደ ሰማይ ኼደ ዐረገ ወጣ - ፪ቆሮ. ፲፪፥፪, ፬፡ ፩ተሰ. ፬፥ ፲፯) ።
ተነጠቀ፡ ተቀማ/ተሳበ (ድንገት ተወሰደ ሰዉ ገንዘቡ ገላው - ምሳ. ፪፥፳፪፡ ኤር. ፭፥፯፡ ሕዝ. ፴፫፥፲፭) ።
ተነጠጠ፡ ተፋቀ ተሰነጠ (በሥርና በ ጫፍ ሰንበር ተደረገበት - ፬ነገ. ፮፥ ፲፰፡ ማሕ. ፯፥ ፫፡ ኤር. ፲፥ ፭) ።
ተነጠፈ (ተነጽፈ)፡ ተጣለ/ተዘረጋ/ተሰተረ/ተጸፈጸፈ ("መላእክት የስቅለት ለት በመስቀል ዙሪያ እንደ ሻሽ ተነጠፉ") ።
ተነጣቂ፡ የሚነጠቅ (ዐቅመ ቢስ ሰው) ።
ተነጣይ፡ የሚነጠል/የሚለይ።
ተነጣጠረ (ተናጸረ)፡ በአንጻር ቁሞ ከዳኛ ተያየ (ከባለጋራው ጋራ ተነጋገረ ተከራከረ ተገተ) ።
ተነጣጠረ፡ ተመሳሰለ ነገሩ።
ተነጣጠቀ፡ ተቀማማ።
ተነጣጠፈ፡ ተጣጣለ/ተዘረጋጋ።
ተነጣጣሪ (ሮች)፡ የተነጣጠረ/የሚነጣጠር (ተከራካሪ ተማጋች) ።
ተነጣጣይ፡ የሚነጣጠል (ተለያዪ) ።
ተነጣፊ፡ የሚነጠፍ (መሬት ምንጣፍ) ።
ተነጩ፡ ተፈገፈገ/ተሞዠቀ/ተላጠ/ተመለጠ (ቈሰለ - ኢሳ. ፲፭፥፪ - "ለውሽማ ሞት ፊት አይነጭለት" - ተረት)
ተነጫነጨ፡ ተበሳጨ/ተጨቃጨቀ (ዐመለ ናጫ ኾነ) ።
ተነጫጨ፡ ተነቃቀለ/ተላላጠ።
ተነጻጸረ፡ ተያየ/ተመሳሰለ።
ተነጻጻሪ፡ የተነጻጸረ/የሚነጻጸር (ተመ ሳሳይ) ።
ተነፈሰ፡ ለነፋስ/ለትንፋሽ ተሰጠ (በሰፌድ መሣሪያነት ተበጠረ ወጣ ተለየ እብቁ ገለባው - ተደራጊ) ።
ተነፈሰ፡ አለ/ተናገረ ("ውሃ ከፈሰሰ ንጉሥ ከተነፈሰ (አይመለስም)") ጣት።
ተነፈሰ፡ እፎይ አለ፡ ነፈሰ ።
ተነፈሰ፡ ካፉ ትንፋሽ አወጣ ("እፎይ አለ ዐረፈ" - አድራጊና ተደራጊ - ዘፀ. ፴፩፥፲፯) ።
ተነፈራረቀ፡ ተሠነጣጠቀ።
ተነፈነፈ፡ ተሸተተ
ተነፈነፈ፡ ተበላ/ተጋጠ/ተነጯ።
ተነፈገ (ጼአ)፡ ክፉኛ ሸተተ/ገማ (ከረፋ ራቀ ተገለለ ጥሩው መዐዛ - "ነፈሰ" ብለኸ "ተነፈሰን" እይ አካኼዱ ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ተነፈገ፡ ተሠሠተ/ተከለከለ (ምግቡ ገንዘቡ) ።
ተነፈገተሠሠተ፡ ነፈገ ።
ተነፋ (ተነፍየ)፡ ተንዘረዘረ/ወረደ ("(ጥና) አናፋ" - የመንፋትን ሥራ ረዳ ዐገዘ) ።
ተነፋ (ተነፍጎ)፡ እፍ ተባለ (ነፋስ ተቀበለ በተተ) ።
ተነፋ፡ ታበየ/ተቈጣ/አኰረፈ።
ተነፋ፡ ዐበጠ/ተቀበተተ (ዘኍ. ፭፥፳፩) ።
ተነፋለለ፡ ተደናቈረ (ቂልኛ ተናገረ) ።
ተነፋረቀ (ነፈረቀ)፡ ተላቀሰ።
ተነፋረቀ፡ ተነኋረጠ ("ከፊቴ ወዲያ ኺድ አትነፋረቅብኝ") ።
ተነፋነፈ (ትግ. አነፈ)፡ ባፍንጫው ተናገረ ' ተነኋረጠ።
ተነፋነፈ፡ ተሻተተ (ጠረን ተቀባበለ) ።
ተነፋነፍ፡ የዱሮ ዘመን ሰፊ ሱሪ (ከስፋቱ የተነሣ ነፋስ እየጠለፈ ድምጥ የሚ ሰጥ ስለ ኾነ ተነፋነፍ ተባለ - እሱን የሚታጠቁ ጥብጣባቸውን ሳይፈቱ ወደ ላይ ገል በው ይኰሳሉ) ።
ተነፋናፊ፡ ተሻታች።
ተነፋናፊ፡ የተነፋነፈ/የሚነፋነፍ።
ተነፋፈረ፡ ፈጽሞ ተጣላ/ተማረረ/ተ ባሰለ/ተባባሰ/ተዛዛተ።
ተነፋፈቀ፡ ተፈላለገ ("ባየኹት ባገኘኹት ተባባለ") ።
ተነፋፋ፡ ዐባበጠ።
ተነፋፋቂ፡ የሚነፋፈቅ (ተፈላላጊ " መነፋፈቅ" - መፈላለግ) ።
ተናሣ (ተናሥአ)፡ ተማዘነ/ተሳቀለ ("እጅ ተ ነሣሣ" እንዲሉ) ቋቋመ።
ተናረተ፡ ተማታ/ተጣዘለ።
ተናሸረ፡ ተማረረ፡ ነሸረ ።
ተናቀ ተቃማ
ተናቀ፡ ተዋረደ/ቀለለ/ተጠላ ' (ማር. ፮፥ ፴፩) ።
ተናቀለ፡ ተላቀቀ/ተለያየ/ተማዘዘ።
ተናቀሰ፡ ተመሳከረ።
ተናቀሰ፡ ተቃነሰ/ተጓደለ።
ተናቀሰ፡ ተጣቈረ።
ተናቃላ፡ ከሥራው/ከደንቡ/ከይዘታው የተለያየ ' "እከሌ እኮ ሳይቸግረው ተናቃላ ኹኖ ቀረ" ።
ተናቃነቀ፡ ተንቀሳቀሰ/ተወዛወዘ/ዋዠቀ/ተናወጠ (የንቅልፋም የጥርስ የምድር) ።
ተናቃነቀ፡ ተንቀሳቀሰ/ተወዛወዘ/ዋዠቀ/ተናወጠ (የንቅልፋም የጥርስ የምድር) ።
ተናቈረ፡ ተጣላ/ተናከሰ/ተዋጋ (የዶሮ ያሞራ የወፍ) ።
ተናበበ፡ ተዛረፈ/ተያያዘ (ዘርፍና ባለቤት ተኳዃነ) ።
ተናበበ፡ ኣንዱ መጻፍ ከሌላው ጋራ ቃሉ ትክክል መኾኑ ተመረመረ።
ተናባ (ተናብዐ)፡ ተላቀሰ።
ተናባቢ ቀለም፡ እጀ ሰብ ዐይነ ወግ ጥርሰ ገጣጣ ዐይነ ፈጣጣ መልከ ቀና እየተባለ የሚነገር ቃል (ይህ በግእዝ ሲናበብ ነው - ዘርፍና ባለቤት አንድ ቃል ሲኾን፤ገደላገደል/ወንዛወንዝ/ውርውር/ወርቃወርቅ/ጨርቃጨርቅ/ሥራሥር/ቅጠላቅጠል/ርጥባርጥብ/ብረታብረት/ጥጋጥግ/ሴታሴት እያለ በራብዕ ይናበባል - በሳድስም ሲናበብ፡ ስም አጥፊ ነገር ዐላፊ ይላል - ይኸውም በግእዝ (አጥፋኤ ስም ኀላፌ ነገር) ያሠኛል) ።
ተናባቢ፡ የተናበበ/የሚናበብ (ተያያዥ) ።
ተናተነ፡ ለያየ ከፋፈለ ።
ተናነሰ፡ ተጓደለ፡ ተቀናነሰ፡ ተከፋፈለ።
ተናነቀ (ተኃነቀ/ተቃለሰ)፡ ወገብ ለወገብ ተያያዘ (ሠመር ገባ ገጠመ ታገለ - "(ተረት)" - ስንተዋወቅ አንተናነቅ ") ።
ተናናረ፡ ተዛለለ ("አንተስ አንተስ ተባባለ") ።
ተናናቀ፡ ተጠላላ/ተኳሰሰ።
ተናናዶ፡ ፈራረሰ/ወዳደቀ።
ተናኘ፡ ተሰጠ/ታደለ/ገባ/ተሠራጨ (ተነዛ ተወራኘ ተበተነ ተዘራ) ።
ተናኘ/ተናኜ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ("አቶ ተናኘ እመት ተናኜ" እንዲሉ) ።
ተናኝ፡ የሚተን (በናኝ) ።
ተናከሰ፡ ተዘናተረ/ተባላ (ተደራራጊ) ።
ተናከሰ፡ ነከሰ (አድራጊ) ።
ተናከረ፡ ተለያየ ("ከመንገድ ወጣ ዐረፈ ሰፈረ") ።
ተናከረ፡ ተዛፈቀ/ተዳፈቀ።
ተናካ፡ ነካ (የላይኛው ተደራራጊ ይህ አትዘንጋ አድራጊ መኾኑን) ።
ተናካ፡ ድል ተባባለ/ተጣላ ("ነካና ነከተ" በአማርኛ ይተባበራሉ። - "ንጉሥ ይባረኩ ኣቡን ኣስመጥተው ካረመኔ ጋራ ተናክተው ተናክተው" - ግጥም)
ተናካሽ፡ ተናዳፊ ነዘር እባብ (ዘኍ ፳፩፥፫) ።
ተናካሽ፡ የተናከሰ/የሚናከስ ("(ዐዋጅ)" - ተዋጊ በሬኸን ተናካሽ ውሻኸን ያዝ - "(ተረት)" - ተናካሽ ውሻ የዥብ መቋደሻ) ።
ተናኰረ (ተናቈረ)፡ ተዋጋ።
ተናወረ፡ ተዋጣ ጕድን "
ተናወጠ፡ ተነዋወጠ/ተናጋ/ተነቃነቀ/ተናጠ (ኢሳ. ፳፬፥፲፱፡ ኤር. ፶፥፵፮) ።
ተናዋጭ/ተነዋዋጭ፡ የሚናወጥ/የሚነዋወጥ/የሚነቃነቅ (ተነቃናቂ) ።
ተናዘዘ፡ የጄን ለልጄ አለ (ርስቱን ገንዘቡን አወረሰ ኀጢአቱን ለቄስ ነገረ "ይህን ሠርቻለኹ ይፍቱኝ" አለ በሕይወት ሳለ ወይም በሞት ጊዜ - ማር. ፩፥፭) ።
ተናዛዥ፡ የሚናዘዝ።
ተናደ (ተንዕደ)፡ ተጐተተ/ተዘረጠጠ/ፈረሰ/ወደቀ (ክምሩ)፡ ሸሸ (የጦር ሠራዊቱ)፡ ተንከባለለ (ናዳው - ተረት፡ "የጨው ገደል ሲናድ ሞኝ ይሥቃል ብልኅ ያለቅሳል") ።
ተናደ፡ ተተረተረ/ተፈታ (ጥንጥኑ - ጥና) ።
ተናደደ፡ ተበሳጨ/ተቈጣ (በቍጣ ነደደ/ጨሰ/ተቃጠለ በገነ ዐረረ) ጀት።
ተናደደ፡ ተያያዘ/ተቀጣጠለ።
ተናደፈ (ነደፈ)፡ በመርዝ ተዋጋ/ተጠዛጠዘ (ልማዱ ግን ነደፈ ወጋ ነው - "ንቦ ንቦ ኣትናዶፊ የነከሌ ነኝ ብለሽ ዕለፊ" - ሴቶች የሰርግ ለት) ።
ተናዳ (ተናድአ)፡ ተቃረበ/ተዋሰደ።
ተናዳጅ፡ የተናደደ/የሚናደድ።
ተናዳጅነት፡ ተናዳጅ መኾን።
ተናዳፊ (ነዳፊ)፡ የተናደፈ/የሚናደፍ (ንብ/ተርብ/ጥንዝዛ/እባብ/ጊንጥ/ናዜራ/ቀስተኛ ወባ) ።
ተናዳፊነት፡ ተናዳፊ መኾን።
ተናገሠ፡ ንጉሥ ተኳዃነ (ባንድ ዘመን ነገሠ) ።
ተናገረ፡ (በግእዝ ተደራራጊ ባማርኛ አድራጊ) ቃል ሰጠ/ነገረ ("ተቀመጥ በወንበሬ ተናገር በከንፈሬ" - ግጥም፡ "ክፉ ሳይ ናገር ሞት ይፈታል አገር") ።
ተናገረ፡ ለፈለፈ/ቀባጠረ።
ተናገደ፡ ተገዛዛ/ተሻሻጠ (ንግድ ለንግድ ተለዋወጠ/ተቀባበለ) ወጥ።
ተናጋ (ተናጕዐ)፡ በጥቂቱ ተላቀቀ/ተነቃነቀ/ተናወጠ/ተለያየ (የቅልጥሙ/የሙላው መጋጠሚያ) ።
ተናጋሪ (ሮች)፡ የተናገረ/የሚናገር (ለፍላፊ አፈኛ - ኢዮ. ፴፩፥፪፡ ምሳ. ፪፥፲፪፡ ግብ. ሐዋ. ፲፰፥፳፬) ።
ተናጋሪነት፡ ተናጋሪ መኾን (አፈኛነት) ።
ተናጐደ፡ ተማታ "
ተናጠ፡ ተገፋ/ተወዘወዘ/ተነቀነቀ (ወደፊትና ወደ ኋላ ተባለ ወይም አለ) ።
ተናጠለ/ተነጣጠለ፡ ተለያየ (እየብቻ ተኳዃነ - "ተነጣጠለ ብዙ ጊዜ ፈጽሞ ለማለት ይነገራል።")
ተናጠቀ (ተማሠጠ)፡ ተቃማ/ተ ሻማ (ሕዝ. ፴፱፥፬፡ ማቴ. ፲፩፥፲፫፡ ግብ. ሐዋ. ፳፥፳፱ - "ጌታችን በሕፃንነት ሳለ ሰው ኹሉ ይናጠቀው ነበር" ይላል አረጋዊ መንፈሳዊ) ።
ተናጠበ፡ ተራገጠ/ተቅበጠበጠ።
ተናጠበ፡ ተዳፈረ/ተሳደበ።
ተናጠፈ፡ ተዘራጋ።
ተናጣ፡ ተናጻ።
ተናጣላ ኾነ፡ ከሥራ ተወገደ ራቀ።
ተናጣላ፡ የተናጠለ/የተለያየ።
ተናጣቂ (ቆች)፡ የተናጠቀ/የሚናጠቅ (ተቃሚ ተሻሚ - ፩ቆሮ. ፲፭፥፲፩) ።
ተናጣቢ፡ የተናጠበ/የሚናጠብ (ተሳዳቢ - "ዐመለኛ ክፉ ተራጋጭ ቅብጥብጥ ላም" - ሆሴ. ፬፥፲፮) ።
ተናጣቢነት፡ ተናጣቢ መኾን።
ተናጪ፡ ተበሳጨ/ተጨቃጨቀ (ዐመለ ናጫ ኾነ) ።
ተናጯ፡ ተናቀለ።
ተናጻ፡ ታጠበ/ተጣጠበ/ተለቃለቀ።
ተናፈሰ፡ ተዛወረ (ሽር ሽር አለ ነፋስ ተቀበለ ስፍራ ለወጠ ካዲስ አየር ተ ገናኘ) ።
ተናፈቀ፡ ተሻ/ተፈለገ።
ተናፈገ፡ ተነፋፈገ/ተሣሠተ/ተሻማ።
ተናፈጠ፡ እንፍ አለ (ንፍጥን አወጣ አፍንጫውን አጠራ - ተናጻ) ።
ተናፈጠና አናፈጠ፡ ተደራራጊና አደራራጊ ሲመስሉ ባድራጊነትና ባስደራጊነት መፈታታቸውን አስተውል ለገድ።
ተናፋሽ፡ የሚናፈስ (የክት ልብስ) ።
ተናፋቂ፡ የሚናፈቅ/የሚፈለግ (ተፈላጊ) ።
ተኔ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ተን፡ አን በገባበት በደጊመ ቃል ግስ መነሻ እየተነገረ የመደረግ ልማድ ይኾናል (ማስረጃ) ። በዝበዝ—ተንበዝበዝ፡ በለበለ—ተንበለበለ፡ ገደደ—ተንገደገደ፡ ነጠበ—ተንጠባጠበ፡ ደፈደፈ—ተንደፋደፈ፡ ቀጠቀጠ—ተንቀጠቀጠ (ቀለቀለ)—ተንቀለቀለ፡ ሰረሰረ—ተንሰረሰረ ። ተኛ—ተጋደመ—ተዘረጋ—ተዘረረ—ጐኑ ምድር ነካ (ሳሙ. ፫፡ ፱፡ ፩ነገ. ፲፱፡ ፭, ፮) ።
ተን፡ የጉም የጪስ ብናኝ (ግእዝ) ("ቱኒን" እይ - የዚህ ዘር ነው) ።
ተንሰለጀጀ (ሰለጀጀ)፡ ደከመ/ፈዘዘ/ተንሰዋለለ ።
ተንሰረሰረ፡ ተቀቀለ/በሰለ/ነፈረ ።
ተንሰረተተ፡ ረዘመ/ተጐተተ ።
ተንሰራፋ፡ ሰፋ/ሰፊ ኾነ፡ ተንጋለለ/ተዘረጋ/ብዙ ስፍራ ያዘ/ተንዘራፈጠ (መዝ. ፻፬፡ ፳፭) ። "አንሰራፋና ተንሰራፋ አደራራጊና ተደራራጊ ሲመስሉ ባድራጊነትና በተደራጊነት መተርጐማቸውን አስተውል"።
ተንሠቀሠቀ፡ ዕርር ምርር አለ (ተስረ ቀረቀ ባለማቋረጥ አለቀሰ ተንፈቀፈቀ በሹል ነገር በመሠቅሠቂያ እንደ ተወጋ - ፊልክ. ፭) ።
ተንሰገሰገ፡ ተስገበገበ፡ ቸኰለ (ሳያኝክ ዋጠ) ።
ተንሢያጠጠ፡ ተፋዬ (በቀጪን ድ ምፅ ጮኸ - ብረቱ እባቡ ዐይጡ) ።
ተንሳቀቀ (በቀቀ)፡ ተላቀቀ ተከፋ ፈተ፡ ልማዱ ግን ተደራጊ ነው ።
ተንሳተተ (ሰተተ)፡ ወጣ ገባ ዐባጣ ጐባጣ ከመኾን ራቀ ።
ተንሣይ (ትንሣኤ)፡ መነሣት (የታላቅ በዓል ስም በያመቱ እሑድ ለት የሚከብር በዓል - ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት ፳፯ ቀን ዐርብ ሙቶ በ፫ኛ ቀን የመነሣቱ መታሰቢያ - "ተንሣይ" ያማርኛ "ትንሣኤ" የግእዝ ነው - "(ዳግማ ተንሣይ)" - የትንሣኤ ሳምንት) ።
ተንሣይ፡ ትንሣኤ፡ ነሣ ። ተነፈገ፡ ገማ፡ ነፈገ ።
ተንሳፈፈ፡ ሰፈፈ ።
ተንሳፋፊ፡ የሚንሳፈፍ (ቀላል ነገር) ።
ተንሶለሶለ፡ ዞረ፡ ተንቀዠቀዠ፡ ተንቀለቀለ ።
ተንሶከሶከ፡ አሶከሶከ።
ተንሸረሸረ፡ ሠሠረ ተራመደ ።
ተንሸረሸረ፡ ሾረ ።
ተንሸረሸረ፡ ወደ ውጭ ኼደ ዞረ (ኣየር ለወጠ ተናፈሰ ነፋስ ተቀበለ - ጥሩ ልብስ ለብሶ አምሮ ተሸትሮ) ።
ተንሸራተተ/ተንሻተተ፡ ወደ ታች ተንፋቀቀ ወረደ ።
ተንሸራታች፡ የሚንሸራተት (ውል ለ...ቃቂ) ።
ተንሸርሻሪ፡ የሚንሸረሸር/የሚሾር ።
ተንሸቀሸቀ፡ ፈራ ራደ ተንቀጠቀጠ ።
ተንሸቅሻቂ፡ የሚንሸቀሸቅ (ተንቀጥ...ቃጥ) ።
ተንሸቅሽቋል፡ ርዷል ተንቀጥቅጧል ።
ተንሸዋረረ፡ ተጣመመ/ተንጋደደ (ወደ ጐን እየ...)
ተንሸዋራሪ፡ የሚንሸዋረር/የሚንጋደድ ።
ተንሻለለ፡ ተንፋቀቀ ተሳበ (በምሰሶ ላይ እንሽላሊትኛ ወጣ ወረደ) ።
ተንሻረረ፡ ወደ ላይና ወደ ታች ተወረወረ (በገደል በግንብ በምሰሶ ላይ ፈጥኖ ዐለፈ ተንሻለለ - ገበሎው እባቡ እንሽላሊቱ) ።
ተንሻተተ፡ ተንሸራተተ ።
ተንሻታች፡ የሚንሻተት (ተንሸራታች) ።
ተንሾካሾከ፡ ሹክታን ተመላለሰ ።
ተንሾካሿኪ፡ የተንሾካሾከ/የሚንሾካሾክ (ተሾ...ተንሾካሿኪ) ።
ተንሿሿ፡ ፈላ ገነፈለ ፈሰሰ ወረደ...ተሰማ ።
ተንቀለቀለ፡ በኀይል ነደደ ተንበለበለ ።
ተንቀለቀለ፡ አለልክ ረዘመ ።
ተንቀለቀለ፡ ዞረ ተንቀዠቀዠ ተንቀወ ቀወ ናወዘ ።
ተንቀለጠጠ፡ ተከፈተ ተገለጠ ተን ገለጠጠ ።
ተንቀላበሰ፡ ኣልብሱኝ አንተርሱኝ አለ፡ ተደገፈ ።
ተንቀላባሽ፡ የተንቀላበሰ/የሚንቀላበስ (ተደጋፊ
") ።
ተንቀልቃይ፡ የሚንቀለቀል/የሚነድ (ነዳጅ ናዋዥ
") ።
ተንቀሳቀሰ (አንሳሕስሐ - ተሐውሰ)፡ ተነቃነቀ ተላወሰ ("(ኢዮ. ፴፯፥ ፳)") ።
ተንቀሳቃሽ (ተሐዋሲ)፡ የሚንቀሳቀስ (ተነቃናቂ ተላዋሽ በእግር የሚሽከረከር በክንፍ የሚበር እንስሳ አውሬ ወፍ ") ። "ኀሙስ ከባሕር ዐርብ ከየብስ የተፈጠረ ፍጥረት ኹሉ ደመ ነፍስ ያለው"
("(ዘፍ. ፩፥ ፳)") ።
ተንቀሳቃሽ፡ በያይነቱ ፈረንጆች የሠ ሩት መኪና ።
ተንቀሳቃሽነት፡ ተነቃናቂነት/ተላዋሽ ነት ።
ተንቀሳቃሾች (ተሐዋስያን)፡ ተሽከርካሮች በራሪዎች እንስሶች አውሬዎች ወፎች መኪኖች ።
ተንቀረሰሰ - ተንቈረሰሰ፡ ቀስ ብሎ ኼደ ዘገመ ("ላዘ") አዘገመ ።
ተንቀረቀበ፡ ተንቀጠቀጠ ተናወጠ፡ ተ ወዘወዘ ተንገዋለለ ተለየ ።
ተንቀረበበ - ተንገረበበ - ተንቀረደደ - ተንከረፈፈ፡ ረዘመ ።
ተንቀረፈፈ፡ ረዘመ ተንከረፈፈ ተን ቀረበበ (ግመልኛ ኼደ
") ።
ተንቀራጨ፡ ተቈረጠመ ተንቀጫቀጨ ።
ተንቀርቃቢ፡ የሚንቀረቀብ (እንቀቱና ዶቄቱ የሚለይ
") ።
ተንቀርፋፊ፡ የሚንቀረፈፍ (ተንከርፋፊ
") ።
ተንቀሸረረ፡ ቀሸረረ ።
ተንቀበቀበ፡ ተንገበገበ ነፈገ ሠሠተ ።
ተንቀበደደ፡ አረገዘ ተነፋ ዐበጠ ።
ተንቀባረረ፡ ተቀማጠለ ተንደላቀቀ ተሞ
ተንቀባራሪ፡ የሚንቀባረር ።
ተንቀብቃቢ፡ የሚንቀበቀብ/የሚነፍግ ።
ተንቀወቀወ - ተንከወከወ - ተንቀዠቀዠ ።
ተንቀዋላይ፡ የሚንቀዋለል ።
ተንቀዠቀዠ፡ ተክለፈለፈ ተክለበለበ ።
ተንቀጠቀጠ፡ ተንጠበጠበ ተነቀነቀ ራደ ተንዘፈዘፈ ተወዘወዘ
("(ኢዮ. ፳፮፥ ፲፩፡ ፴፥ ፯)") ።
ተንቀጠቀጠ፡ ነፈገ ሠሠተ ።
ተንቀጥቃጭ፡ የሚንቀጠቀጥ (ተንዘፍ ዛፊ
("(ዘዳ. ፳፰፥ ፷፭)")) ።
ተንቀጫቀጨ፡ ተጋጩ/ተፋጩ፡ የጥ
ተንቀፈረረ፡ ረዘመ ግመል መሰለ ።
ተንቀፈደደ፡ ተንቀረደደ ።
ተንቀፍዳጅ፡ የሚንቀፈደድ ።
ተንቃቂ፡ የሚንቃቃ ።
ተንቃቃ፡ ሞቀ መጠጠ ደረቀ ቀነበረ ተጕላላ ።"ቃታን"
"ቃትን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው ።
ተንቃቃ፡ ድምፅ ሰጠ፡ ተንገጫገጨ ።
ተንቃፈፈ - ተንጋፈፈ - ተንከረፈፈ ።
ተንቈማቈጪ፡ ተነነጩ ቡችልኛ ።
ተንቈረቈረ፡ ተቈለቈለ ወረደ ወደ ታች ኼደ ከብቱ ።
ተንቈረቈረ፡ ፈሰሰ ተቀዳ ተመላ መ ጠጡ ።
ተንቈረበበ፡ ቈረበ ጐረበ ።
ተንቈረዘዘ፡ ተንጠለጠለ (ሊወርድ ሲፈስ ሲንጠባጠብ ቀረበ እንባው ደሙ ወተቱ
") ።
ተንቈረፈፈ፡ ተቈፈነነ ተወበጠ ። "ይህ ዶሮ ሊሞት ነው፡ ተንቈርፋል"
።
ተንቈራባ፡ ተንኳኳ ተንኰራፋ ።
ተንቈራጠጠ፡ ተንጐራደደ
("ከቤት ወደ ውጭ ወጣ ከውጭ ወደ ቤት ገባ ወዲያና ወዲህ አለ ") ። "ሰንጋ ፈረስ በተቀመጡበት ጊዜ ይንቈራጠጣል፡ ሴት ምጥ ሲይዛት ትንቈራጠጣለች" ።
ተንቈራጣጭ፡ የሚንቈራጠጥ (ተንጐ ራዳጅ
") ።
ተንቈራፋ - ተንኰራፋ - ተንቈራባ ።
ተንቈርቋሪ፡ በማንቈርቈሪያ/በመንቈርቈሪት የሚንቈረቈር (የሚመር ጠጅ ጠላ ማንኛውም ፈሳሽ ነገር ") ።
ተንቈጠቈጠ፡ በላይ በታች ተሸለመ አጌጠ፡ ባላበባ ቍጥቋጦ መሰለ ።
ተንቈጠቈጠ፡ ደቀቀ ተንከታከተ፡ ከሰማይ የወረደ ጭንቍላ ኾነ ።
ተንቈጣቈጠ፡ ተቈናቈነ ሠሠተ ቈጠበ ።
ተንቈፈቈፈ፡ ነፈገ ሠሠተ ።
ተንቈፈቈፈ፡ ጮኸጠራ ጩትን ።ርግጠኛው ግን ተጮኸ ተጠራ ነው ።
ተንቋቋ፡ ጮኸ ጣቱ ወገቡ ።
ተንቋጠጠ፡ ተኰሰተረ፡ ኰራ ። "እከሌ የተንቋጠጠ ቤት ሠራ"
እንዲሉ።
ተንበለበለ፡ ነደደ፡ ተንቦገቦገ፡ ተንቀ ለቀለ ።
ተንበላጠጠ፡ ተገላመጠ፡ ፈራ፡ ወዲያና ወዲህ አየ ።
ተንበላጣጭ፡ የሚንበላጠጥ፡ ጭላዳ ሌባ ነፍሰ ገዳይ ።
ተንበረበረ፡ ተበረበረ ።
ተንበረከከ፡ በረከ በረከከ፡ ሰገደ ተኛ ። (ኢዮ ፴፱ ፥ ፫ ። ኢሳ ፵፬ ፥ ፲፭) ።
ተንበረክ፡ ሥር ታች፡ መንበርከኪያ ቦታ ወንበር ።
ተንበረክ፡ ያዲስ ግንብ ልባስ ሰንበሌጥ መካከሉ በገመድና በንጨት የተማገረ ።
ተንበረክ...ባስ፡ በረከ ። ትንቡሼ፡ ድንቡሎ፡ በሸበሸ ።
ተንበሩን ያዢና እንኺድ ወደ ርሻ።
ተንበራጠጠ፡ ተቋፈ ተቈነነ፡ ተጓደደ ።
ተንበርካኪ፡ የሚንበረከክ፡ ግመል ሰጋጅ ።
ተንበርጣጭ፡ የሚንበረጠጥ የሚኰራ ። (፪ጴጥ ፪ ፥ ፲፰) ።
ተንበሸበሸ፡ ተቀማጠለ ተንቀባረረ ።
ተንበሸበሸ፡ ተንቀባረረ፡ በሸበሸ ።
ተንበሸከከ፡ ተንቀባረረ ተንበጠረረ ።
ተንበቀበቀ፡ እንደ ቅል ውሃ ጮኸ ።
ተንበከበከ (በከበከ)፡ ተንደከደከ ረጥ ረጥ አለ፡ የሹሮ የዶዮ የገንፎ ።
ተንበደበደ (በደበደ)፡ ፈራ ተንቀ ጠቀጠ ራደ ። (ኢያ ፪ ፥ ፳፬ ። ኢሳ ፳፩ ፥ ፬) ።
ተንበጠረረ (በጠረረ)፡ ተጓደደ ዳ አለ፡ ዳተኛ ኾነ ።
ተንበጥራሪ፡ የሚንበጠረር፡ ተጓዳጅ ።
ተንበጨበጨ (በጨበጪ)፡ ብ መስሎ ወረደ ። በጪን እይ ።
ተንቢ፡ የተነባ/የሚተነባ (ትንቢተኛ) ።
ተንቤኔ (ኖች)፡ የተንቤን ሰው...ንቤን ተወላጅ ትግሬ ።
ተንቤን፡ በተንቤን ውስጥ የሚሠራ...ቀይ ቈርበት (ነት) ።
ተንቤን፡ በትግሬ ክፍል ያለ አገር ።
ተንቦለቦለ፡ ቡልቅ ቡልቅ ኣለ፡ ተትጐለጐለ፡ ፈለቀ ወጣ፡ ወረደ ፈሰሰ ተንዶለዶለ፡ የጪስ የውሃ ። ቦለለን እይ፡ የ(ቦለቦለ) ሥር ርሱ ነው ።
ተንቦረቀቀ (ቦረቀቀ)፡ ሰፋ ሰፊ ኾነ፡ ተንቧለለ ።
ተንቦቀቦቀ፡ በዝቶ ወረደ ፈሰሰ ተንዶለዶለ፡ ፈራ ።
ተንቦዠቦዠ፡ ሞቅ አለው ተደሰተ፡ ተብረዠረዠ ።
ተንቦገቦገ፡ ትግ ትግ አለ፡ ዘለለ በኀይል ነደደ ። (ናሖ ፫ ፥ ፫) ።
ተንቦጫረቀ፡ በባሕር በኩሬ በጮረቃ ውስጥ ተንደፋደፈ ተንቧቸ ተንፈራገጠ ።
ተንቦጫራቂ፡ የሚንቦጫረቅ ወፍ ሕፃን ። ወንዘረጭን እይ ።
ተንቦጫቦጨ፡ ተበጣበጠ ተማታ ተፋሰሰ ።
ተንቧለለ፡ ቦላሌ ለብሶ ኼደ ። ተጫሰ፡ በዝቶ ወጣ ።
ተንቧቧ፡ ተንፋፋ ተንሿሿ፡ ወረደ ፈሰሰ ።
ተንቧቸ፡ ተንቦጫረቀ፡ ተንቻቻ ተን ጫጫ ተጫወተ፡ እንደ ልቡ ኾነ ።
ተንተሰተሰ፡ ነቃ ተሠነጠቀ ፈራ ።
ተንተረከከ፡ ሠባ ወፈረ...መከር ።
ተንተረከከ፡ በሰለ ። እኸል በጊዜ ባይሰበሰብ የእንቡጡን መፈንዳትና የባላውን መበተን ያሳያል ።
ተንተረፈረፈ፡ ተተርፈረፈ።
ተንተረፈፈ፡ ተመላ ተንደረበበ ። ቲፍ አለ ።
ተንተራሰ፡ ራሰ ተደገፈ፡ ራስ ።
ተንተራሰ፡ ቶፋ
ተንተራሰ/ተተርአሰ፡ ራሱን በትራስ ላይ አደረገ፡ ተደገፈ፡ ቀና አለ (ዘፍ፳፰፡ ፲፰። ማር፬፡ ፴፰) ። መናኝ ጤዛ ልሶ ደንጊያ ተንተርሶ ይኖራል። ከነዳ ብለኸ ክንድን አስተውል።
ተንተርፎ፡ ትርፍ።
ተንተበተበ፡ ተቈላ ።
ተንተባተበ፡ ድዳ ለንባዳ ኾነ (አንደ...በቱ ተርበተበተ) ።
ተንተባታቢ፡ የሚንተባተብ ።
ተንተከተከ፡ ሞቀ በጣም ፈላ ነፈረ...ተንጠቀጠቀ ።
ተንተገተገ፡ ተብረቀረቀ ተብለውለው ብልጭልጭ አለ በራ ።
ተንታ፡ በወሎ ክፍል ያለ አገር ።
ተንታኝ (ኞች)፡ የተነተነ/የሚተነ...ትን (ከፋይ ዐዳይ) ።
ተንትርክራኪ፡ የሚንከባለል።
ተንትርፍራፊ፡ የሚተርፈረፍ።
ተንቷቷ፡ ተበጣጠሰ ።
ተንቸሰቸሰ፡ ሰ...ተነሣ ላበቱ ወጣ ዐረፋው ።
ተንቸረፈፈ፡ ኰረፈ ("አልናገር" እለ) ።
ተንቸበቸበ፡ ተጠበሰ በሰለ ተቃጠለ ።
ተንቸከቸከ፡ ተሸነ ተንፎከፎከ ተንቸከቸከ ተበሰ ።
ተንቻረረ/ተንሻረረ/ተንሻለለ፡ ዘለለ ።
ተንቻቻ፡ ተንኩኸ ።
ተንኦሮይ፡ የሚንጋለል (በዠርባው የሚተኛ) ።
ተንከላወሰ፡ ተላወሰ ("ተንጠራወዘ ኣዘ ") ።
ተንከራ፡ ጠንካራ ዕንቍ (ግእዝ) ።
ተንከበከበ፡ ተድበለበለ ("ኳስ መሰለ") ።
ተንከባለለ (ጸድፈ)፡ ገደል ገባ ("ተገላበጠ ተንደባለለ") (፪ሳሙ. ፳፡ ፲፪) ።
ተንከባለለ፡ ተቍለጨለጩ ("ተዥገረገረ") ።
ተንከባላይ (ዮች)፡ የሚንከባለል ("ተገ ላባጭ ተንደባላይ ሀ ባይ ዐመድ ላይ ተንከባላይ እንዳለ ተማሪ") ።
ተንከብካቢ፡ የሚንከበከብ ("ተድበል ባይ ") ።
ተንከወከወ፡ ባከነ ("ተንቀዠቀዠ ተንቀወቀወ ዞረ ") ።
ተንከዋረረ፡ ተንቀዋለለ ("ዞረ") ።
ተንከዋተተ፡ ተንከዋረረ ("ተንከራተ የትም ሲንከዋተት ውሎ መጣ ተንከዋታች ተንከራታች ከወተት ከውታታ የተንከዋተተ የሚንከዋተት ከረተት ከርታታ ከውታቶች ከርታቶች ") ።
ተንከፈከፈ፡ መርገጥ አቃተው ("ተሳነው ተሠቀቀ ውስጥ እግሩ ") ።
ተንካካ፡ ገደል ገባ ("ተንከባለለ") ።
ተንካፈፈ (ጸለለ)፡ ቀለለ ("ሰፈፈ ተን ሳፈፈ በውሃ ላይ ኾነ ተቀመጠ ኼደ ተንካፋፊ የሚንካፈፍ ቀላል ነገር መንካፈፍ መንሳፈፍ መንካፈፊያ መንሳፈፊያ ") ።
ተንክ፡ ሐሩር ፈል አስራቦ ሰውን የሚነድፍበት ጊዜ ("ጠንቅን" እይ) ።
ተንክ/አተንክ፡ የውሃ ዝበሎ ።
ተንኰለ ቢስ፡ ተንኰሉ አጥፊ ጐጂ የኾነ ።
ተንኰለኛ (ኞች)፡ ጥበበኛ መሠሪ ሰው መኼጃው የማይታወቅ እባብ ።
ተንኰለኛነት፡ ተንኰለኛ መኾን ።
ተንኰሉ፡ የሰው ስም (ሴት በባሏ ቤት መኖር ሳትፈልግ ልጅ የወለደች እንደ ኾነ "ተንኰሉ" ትለዋለች - የለ ዝርዝርነት ፈጣሪን ያያል) ።
ተንኰላኰለ፡ መኼድ ዠመረ ("የሕፃን ") ።
ተንኰል፡ ክፉ ጥበብ ምክር ደባ (ማር. ፯፡ ፳፪) ።
ተንኳለለ፡ ኮለል አለ ("ፈጥኖ ፈሰሰ ተንኳላይ የሚንኳለል ባዜቃ ") ።
ተንኳሽ (ሾች)፡ የተነሳ/የሚተነ...ኵስ (ለኳፊ) ።
ተንኳሽነት፡ ተንኳሽ መኾን ።
ተንኳኳ፡ ተንቋቋ ("ደረቀ") ።
ተንዘለዘለ፡ ተንጠለጠለ/ዞረ/አለል ።
ተንዘረበበ፡ ተንጠለጠለ ።
ተንዘረዘረ፡ ተነፋ/ተነቀነቀ/ተወዘወዘ/ተንቀጠቀጠ/ዞረ/ተዘራ/ለነፋስ ተሰጠ ።
ተንዘረገገ፡ ተጐተተ ("ቀስ ብሎ ኼደ ቶሎ ቶሎ ና አትንዘርገግ") ።
ተንዘረጠጠ፡ ተንጠረዘዘ/ተንቀበደዶ/ተንገፈጠጠ/አረገዘ/ተነፋ ።
ተንዘረፈፈ፡ ዘርፍ ኾነ መሰለ ("ረዘመ ተሳበ ተጐተተ ተንቀረፈፈ") ።
ተንዘራጋ፡ ወደቀ/ተጣለ/ዟ አለ/ተንፈራገጠ ።
ተንዘራፈጠ (ዘረፈጠ)፡ እንደ ልቡ ተቀመጠ ("ተሸራሸ ሰፋ (ሰፍሐ) ተንሰራፋ ተፈረነሰ") ።
ተንዘገዘገ/ተምዘገዘገ/ተቅዘመዘመ፡ ዘግዘግ አለ ("ዘክዘክ አለ") ።
ተንዘፈዘፈ፡ ተርገበገበ/ተንቀጠቀጠ ።
ተንዘፍዛፊ፡ የሚንዘፈዘፍ ("ተርገብጋቢ") ።
ተንዛረጠ፡ ዘረጥ አለ ።
ተንዛዛ፡ በዛ/ረዘመ ("ከልክ ዐለፈ ተ ረፈ ተትረፈረፈ") ።
ተንዛዛ፡ ተንከዋረረ፡ ዞረ ።
ተንዛዛ፡ ተንከዋረረ/ዞረ ።
ተንዛፈፈ፡ ሰፋ/ተንሰራፋ/ተዘረጋ ("በዛ አደገ ረዘመ አጠላ ጥላ ኾነ") ።
ተንዠረገገ/ተንጨረገገ፡ ወረደ/ተንጠ ለጠለ ።
ተንዠቀዠቀ፡ በዝቶ ወረደ/ፈሰሰ ("ውረድ በሌ ኾነ") ።
ተንዠባረረ፡ ለገሰ/ቸረ ("ተንቀባረረ") ።
ተንዠባረረ፡ በጣም ሰከረ/ዘነጋ/ አረጀ/ዦዠ ("ከልክ ዐለፈ") ።
ተንዠዋለለ፡ ረዘመ/ተጐተተ ።
ተንዣለለ፡ ሾለቀ/ሞለለ ("ሠላጤ መ ለል") ።
ተንዣረረ፡ ተሸነ/ፈሰሰ/ወረደ ("ቀጠነ") ።
ተንዣበበ፡ ተዘረጋ ("በክንፍ በነፋስ ዞረ ሰፈፈ") ።
ተንዣዣ፡ በዛ/ተለገሰ ("ተንቻቻ") ።
ተንደላቀቀ፡ ተቀማጠለ/ተንቀባረረ/ተሞላቀቀ ("አግድሞ አደገ") ።
ተንደረሰሰ፡ ቀስ ብሎ ተራመደ ("እ ንደ ዔሊ ኼደ ተንቀረሰሰ") ።
ተንደረበበ፡ ረጋ/ጨመተ ("ጭምት ኾነ") ።
ተንደረከከ፡ በሰለ/መረተ/ተንገለጠጠ ("ፍሬው ፍሙ") ።
ተንደረከከ፡ ዐጠረ ("ዐጪር ኾነ ሰዉ") ።
ተንደረደረ፡ ከላይ ወደ ታች ሮጠ/ፈጠነ/መጣ/ኼደ ።
ተንደርዳሪ፡ የተንደረደረ/የሚንደረደር ("ቍልቍል ሯጭ") ።
ተንደቀደቀ፡ ጮኸ/ተቈጣ/ፎከረ ።
ተንደበሰሰ፡ ተንደበዘዘ ።
ተንደበዘዘ፡ የስንፍና ኣካኼድ (ቀስ ብሎ ኼደ አዘገመ ተንቀረደደ ተንቀፈደደ) ።
ተንደበደበ፡ ተጕረበረበ ("ፈረሳቤት ኾነ።" ) ።
ተንደከደከ፡ ደቅደቅ አለ/ፈላ ።
ተንደገደገ፡ ተቈላ ("ተንደቀደቀ ተንዶ ሸዶሸ") ።
ተንደፋራ/ተንደፋደፈ/ተንፈራፈረ፡ ተ ንከባለለ/ተንደባለለ ።
ተንደፋደፈ፡ ተንፈራፈረ/ተንፈራገጠ/ተንዘፈዘፈ/ተንደፋራ ።
ተንደፋዳፊ፡ የሚንደፋደፍ ("ተንፈራፋሪ") ።
ተንዳሰሰ፡ አዘገመ ("ትዃንኛ ኼደ") ።
ተንዳሰሰ፡ ደሳሳ ኾነ/ተለመጠ ።
ተንዳከከ፡ ፍጥነት ዐጣ ።
ተንዶለዶለ፡ በዝቶ ወረደ ፈሰሰ = (፪ዜና. ፴፪፡ ፬) ።
ተንዶሸዶሸ፡ ተቈላ/ተንጦሸጦሸ ።
ተንዷዷ፡ ፈነዳ/ጮኸ/ተተኰሰ ።
ተንዷዷ፡ ፈነዳ/ጮኸ/ተተኰሰ ።
ተንጃጃ፡ ተንጋጋ/ተነዳ ።
ተንገለጀጀ፡ ተንሰለጀጀ/ተንሰዋለለ/ተንቀዋለለ (የሞኝ የቂል አካኼድ ኼደ ተሞኘ ቄለ) ።
ተንገለጠጠ፡ ተንቀለጠጠ/መረተ ተገለጠ ።
ተንገላታ፡ ተጕላላ/ተጐዳ/ተበደለ/ተጠቃ/ተራበ/ተጠማ/ተራቈተ ።
ተንገላቺ፡ የሚንገላታ/የሚጐዳ/የሚጕላላ ።
ተንገላወደ፡ ሥራ አልባ ኾነ/ተንቀዋለለ ።
ተንገረበበ፡ አልጠጋ አለ ። "ተንከረፈፈ ዳር ዳር አለ።"
ተንገረገበ፡ ተጐዳ/ተጠቃ ።
ተንገረገበ፡ ፈላ/ተቀቀለ ።
ተንገረገፈ፡ ተንቀጠቀጠ/ተመታ ።
ተንገራጠጠ፡ እንቢ አለ ።
ተንገራጣጭ፡ ፈቃደኛ ያይዶለ (የማይታዘዝ እንቢተኛ) ።
ተንገርባቢ፡ የሚንገረበብ/ተንከርፋፊ ።
ተንገርጋቢ፡ የሚንገረገብ ።
ተንገሸገሸ፡ ተነቀነቀ/ተወዘወዘ/ተንገ ፈገፈ (ከመመረር ከመጥላት ከመሰልቸት የተ ነሣ) ።
ተንገበገበ፡ ተቃጠለ፡ ተሰበለበ፡ ተስገበገበ። (ተረት)፡ "ለገቢኸ ተንገብግብ።"
ተንገብጋቢ፡ የሚንበለበል፡ ተስገብጋባ።
ተንገታገተ፡ ነገር መላለሰ/ተንገዛገዘ ።
ተንገቸገቸ፡ አጋሰስኛ አህይኛ ኼደ ("ዘ ክዘክ ዘጥዘጥ አለ።") ።
ተንገቸገቸ፡ ዘክዘክ አለ፡ (ገቸ) ።
ተንገዋለለ፡ ዞረ/ተንጓለለ/ጓለበ/ለየ ።
ተንገዋላይ፡ የሚንገዋለል።
ተንገዛገዘ፡ ተንገታገተ/ለንባዳ ኾነ (ሲናገር ተርበተበተ) ።
ተንገደገደ፡ ተግተረተረ/ተርገደገደ/ተፍገመገመ ።
ተንገዳገደ፡ ተወዛወዘ/ተነቃነቀ።
ተንገድጋጅ፡ የሚንገደገድ (ተግተርታሪ) ።
ተንገጫገጨ፡ ተጋጩ/ተንቀጫቀጨ ።
ተንገፈለለ፡ ሳያፈራ ቀረ (ላንፋ ብቻ ኾነ አገዳው) ።
ተንገፈለለች፡ ልጃገረዲቱ ባል ሳታገባና ሳትወልድ ቀረች ።
ተንገፈገፈ፡ ተሠቀቀ/ተንገሸገሸ ።
ተንገፈጠጠ፡ ሰፋ/ተነፋ (ከበሮ መሰለ ተንዘረጠጠ ተንቀበደደ) ።
ተንጋለለ፡ በዠርባ ተኛ/ተንካረረ (ለመታከም ለማመንዘር ለማጥባት) ። (ተረት)፡ "ከጸደቁ አይቀር ይንጋለሉ።" "የመንታ እናት ተንኦሮ ትሞት።"
ተንጋተተ፡ ተንጋፈፈ/ተንከረፈፈ ("አባ አይረባ ኾነ።") ።
ተንጋደደ፡ ተጣመመ/ተወላገደ/ተወላገመ/ተወላቀመ ።
ተንጋዳጅ፡ የሚንጋደድ/የሚጠም (ተጣማሚ)።
ተንጋጋ፡ ተቃጠለ/ነደደ።
ተንጋጋ/ተንጃጃ፡ ረባ/በዛ፡ በብዛት ኼደ/ተነዳ።
ተንጋፈፈ፡ ተንቀረፈፈ/ተንቃፈፈ ።
ተንጐራዳጅ፡ የሚንጐራደድ (ተንቈራ) ።
ተንጐበደደ፡ ጐበደደ።
ተንጐደጐደ (አንጐድጐደ)፡ ጮኸ/ተሰማ ።
ተንጐዳጐደ፡ በቤት ውስጥ ሮጠ ወዲያና ወዲህ አለ/አተፈተፈ ።
ተንጐፈለለ፡ ረዘመ ጐፍላው ።
ተንጐፈጐፈ፡ ሩጭ ሩጭ አለ (ያሮጌ ያሮጊት) ።
ተንጐፈጠጠ፡ ጐፈጠጠ ።
ተንጓለለ፡ ተንገዋለለ ።
ተንጓሰሰ፡ ተንቋሰሰ/ተንቈረሰሰ/ተጐ ተተ ቀስ ብሎ ኼደ ።
ተንጓበበ፡ ጐበበ፡ ፍና ጫፉ ወደ ታች መካከሉ ወደ ላይ ኾነ (የሞፈር)።
ተንጓጓ፡ ጮኸ/ተሰማ (የሆድ/የድንጋይ/የደመና)።
ተንጓፈፈ፡ ደከመ/ታከተ (በቀስታ ኼደ ተንቈረሰሰ ከርጅና የተነሣ) ።
ተንጠለጠለ፡ ተሰቀለ/ተሰቀጠጠ ("ተንዘለዘለ") (ዘዳ. ፳፰፡ ፷፮፡ ፪ ሳሙ. ፳፩፡ ፲፫፡ ሰቈ. ፭፡ ፲፪) ።
ተንጠለጠለ፡ ከበደ ("ደመናው ፊቱ አረገዘ ግንቡ") ።
ተንጠላጠለ፡ ዛፍን/ገደልን/ምሰሶን/ትከሻን ወጣ ("ተወጣጣ ተዛዘለ") ።
ተንጠላጣይ፡ የተንጠላጠለ/የሚንጠላጠል ("ተዛዛይ") ።
ተንጠልጣይ (ዮች)፡ የሚንጠለጠል ("የሌት ወፍ ተሰቅጣጭ") ።
ተንጠረረ፡ ተቈረጠ።
ተንጠረበበ፡ ጠቈረ/ከበደ/ተንጠለ ጠላ ።
ተንጠረገገ፡ ተንጠረበበ ።
ተንጠረጠረ፡ ተንቀረቀበ ተለየ ።
ተንጠረጠረ፡ ተንቀጠቀጠ ተንጠበጠበ ።
ተንጠራራ፡ እደርስ እደርስ አገኝ አገኝ እይዝ እይዝ አለ ("አላቅሙ ተመኘ") ።
ተንጠቀጠቀ፡ ተንተከተከ/ተፈናጠረ ።
ተንጠቀጠቀ፡ ተንተገተጉ/ተብረቀረቀ ("ተሸለመ ተንቈጠቈጠ") ።
ተንጠቀጠቀ፡ ፈላ/በሰለ ።
ተንጠበጠበ፡ ተንቀጠቀጠ።
ተንጠባጠበ፡ መዝነብ ዠመረ (ጠብ ጠብ አለ ተንጠፈጠፈ የትም ወድቆ ቀረ - መጽሐፍ ግን በተንጠባጠበ ፈንታ ተንጠበጠበ ይላል - ሚክ. ፭፥፯) ።
ተንጠባጣቢ፡ የሚንጠባጠብ (የተክል የእኸል ፍሬ) ።
ተንጠፈጠፈ፡ ፈሰሰ ("ጠብ ጠብ አለ ተንጠባጠበ") ።
ተንጣለለ፡ ፈሰሰ/ሰፋ ("ሰፊ ኾነ ተዘረጋ ተኛ በዛ በረከተ የውሃ የቤት የድንኳን የተንጣለለ ቅቤ የተንጣለለ መሬት የተንጣለለ ምርት እንዲሉ") ።
ተንጣላይ፡ የሚፈስ/የሚንጣለል ።
ተንጣረረ፡ ተፈሳ ("ጮኸ መንጣረር መጮኸ ጠረር አለ ተንጣረረ") ።
ተንጣጣ፡ ተቈላ ።
ተንጣጣ፡ ተፈሳ/ጮኸ ("ተንጣጣ ቀባጠረ ለፈለፈ") ።
ተንጦለጦለ፡ ተንቀዠቀዠ ("ካንዱ ቤት አንዱ ቤት ኣለ") ።
ተንጦሸጦሸ፡ ጦሽ ጦሽ አለ ("ተንጣጣ") ።
ተንጦዘጦዘ፡ ተንከወከወ ("ተዚያ እዚያ ፥ አለ") ።
ተንጨረገገ፡ ተንዠረገገ/ተንጠለጠለ ።
ተንጨረገገ፡ ጠቈረ ።
ተንጨረጨረ፡ መልሶ መላልሶ እንደ እንጭራር ጮኸ ።
ተንጨረጨረ፡ እጅግ ተቈላ/ተጠበሰ ።
ተንጨረፈፈ፡ አደገ/ረዘመ/ቆመ/ደረቀ ("ተንጨፈረረ") ።
ተንጨበረረ (ጨበረረ)፡ ተቃጠለ ("ተ ንጨፈረረ") ።
ተንጨፈረረ፡ ተንጨረፈፈ ።
ተንጨፈጨፈ፡ በማጠቢያ ላይ ተ መታ/ታጠበ ።
ተንጨፈጨፈ፡ አዠ ወዛ የፊት ።
ተንጫረረ፡ ተቃጠለ/ተንጨበረረ/ዐ ረረ/ገመነ/ተኰማተረ ("ጮኸ") ።
ተንጫጫ፡ ተንቻቻ ጮኸ ("ተፋጅ ተረት ተልባ ቢንጫጫ በሙቀጫ") ።
ተንፈላሰሰ፡ ባልጋ በፍራሽ በመከዳ ላይ ተደገፈ (አንደዬ በቀኝ አንደዬ በግራ ተኛ ተጋደመ፡ በዠርባው ተንከባለለ ተገላበጠ - ከድሎት ከምቾት የተነሣ ") ።
ተንፈላሳሽ፡ የሚንፈላሰስ ("(ደም የጠ ገበ ውሻ)") ።
ተንፈሳለቀ/ተንፈላሰሰ፡ አላገጠ ።
ተንፈረከከ፡ እግሩ ተለያየ ።
ተንፈረዘዘ (ተፈርዘዘ)፡ ጠገበ ተቀ በነነ (በጥጋብ ተነፋ ዐበጠ፡ ሆዱ፡ ተደሰተ ተቀማጠለ፡ ጸጥ አለ ረጋ - ሰውየው ") ።
ተንፈረፈረ፡ ተሠራ ፈላ ተግፈለፈለ (እንፍርፍሩ ") ።
ተንፈራገጠ፡ እግሩ ተንቀሳቀሰ ታጠፈ ተዘረጋ (ከጣር ከመከራ የተነሣ ") ።
ተንፈራጠጠ፡ በስፋት ቆመ ተቀ መጠ ተንዘራፈጠ ።
ተንፈራጣጭ፡ የተንፈራጠጠ/የሚንፈ ራጠጥ ።
ተንፈራፈረ፡ ተንደፋደፈ ተንዘፈዘፈ ተንቀጠቀጠ ("(፩ ሳሙ. ፳፩፥ ፲፫)") ።
ተንፈራፋሪ፡ የተንፈራፈረ/የሚንፈራፈር ።
ተንፈጯፈጨ፡ ፈላ (እንደ ላብ መ ነ ወረዛ አዠ መረቁ ምራቁ ውሃው ") ።
ተንፋለለ፡ ረዘመ ወረደ ወደቀ ።
ተንፋሰሰ፡ ውህኛ ኼደ (በቅሎው ") ።
ተንፋሳሽ፡ የተንፋሰሰ/የሚንፋሰስ ።
ተንፋቀቀ፡ በቂጡ ኼደ ።
ተንፋቃቂ፡ የሚንፋቀቅ (በቂጡ መሬ ትን የሚፈትግ - መሬት ቂጡን የሚፈትገው በሽተኛ ሰው ") ።
ተንፋከከ፡ ተራራቀ እግሩ (ወይም ሰ ውየው ባካኼዱ ") ።
ተንፋፋ፡ ወረደ ፈሰሰ (ብዙ ድምፅ ሰጠ ") ።
ተንፎሸፎሸ፡ ወሬ ነዛ ነፋ ቀለለ ።
ተንፎከፎከ፡ ተሸነ ተንዠቀዠቀ ።
ተንፎደፎደ፡ ተንበደበደ ፈራ ።
ተኖ፡ ሰኞ (ጨሶ ተበትኖ - "ሰይጣን እንደ ጪስ ተኖ እንደ ጉም በኖ ጠፋ") ። አተናነኝ፡ አበናነን መትነን ። ትናንት፡ ትናንትና ትላንት ትላን...ትና ።
ተኖረ፡ ተቈየ/ተዘገየ/ተከረመ።
ተኗኗረ፡ በኑሮ ተባበረ።
ተኛ ።
ተኛ ።
ተኛ (ዊ)፡ በስም ጫፍ እየታከለ...ወገን ቅጽልነትን ያሳያል (ማስረጃ) ። ገበያ—ገበያተኛ፡ ዋና—ዋነተኛ፡ ያ—ያተኛ፡ ነገር—ነገረተኛ፡ ቀለብ—ቀለብተኛ ። ምስጢሩም ሲሠራ የዋለ የኖረ ማታ መጋደሙን መጨረሻ ዕረፍቱን (ሞቱን) ያሳያል ። ብዙ ጊዜም "ኛ" ከቶ እየተለየ ብቻውን ይነገራል ("ኛን" ተመልከት) ።
ተኛ፡ ዐረፈ ሞተ (፩ቆሮ. ፲፭፡ ፯, ፲፰) ። ተኛ፡ በግብር ዐወቀ ተናኘ ሴትን ። ("ግጥም - ካንተ ተኝታ ሌላ ታማራት በል ተነሣና በዱላ በላት") ።
ተኛ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (ተጋደም እንቅልፍ ይውሰድኸ - ፩ሳሙ.
፫፡ ፮, ፮, ፱) ።
ተኞች ።
ተአረማመም፡ አጨማመት፡ ማርመም።
ተዐቃቢ፡ ተጠባቂ ።
ተዐቅቦ፡ መጠበቅ ("ተጠብቆ መኖር" - "አንቀጽን" እይ ") ።
ተዓቃቢ፡ ተጠባባቂ ("ዮሐንስ ተዓቃቢ" እንዲሉ) ።
ተዓቅቦ፡ መጠባበቅ ።
ተኦሮጭ፡ የሚጋለጥ (ተራቋች) ።
ተከለ (ተኪል/ተከለ)፡ ቸከለ ቀበ...ቀበ ከሰመ እመሬት ኣገባ ሻጠ ወተፈ ሸጐጠ አቆመ (፩ቆሮ. ፫፡ ፮) ።
ተከለ፡ ቀላድ (ምድር) ሰጠ (ውርርድ ተከለ) ። "ማር እሰጥ አለ"። ("ስሙን ተከለ") አስጠራ ። ("ታቦት ተከለ") ቤተ ክሲያን ሠራ ።
ተከለ፡ አጸና መሠረተ አለማ ። "ግብር ተከለበት ሳል ተከለበት" እንዲሉ።
ተከለ፡ የግእዝ "ቸከለና ቸኰለ" ያማርኛ ናቸው ።
ተከለለ፡ ለበሰ ("ተጋረደ ተመከተ ተቀየደ ታጠረ ተቀጠረ ") ።
ተከለለ፡ ተሰወረ ("ታወረ") ።
ተከለለ፡ ተቈረጠ ("ተሰየፈ ተከለለ አክሊል ደፋ ተቀዳጀ ተከላይ የሚከለል ተጋራጅ ") ።
ተከለለ፡ ተወሰነ ("ተገደመ መማጠኛ መደወያ ኾነ ") ።
ተከለሰ፡ ተመልሶ ተሠራ ("ተጠና ተከለሰ ተፈተነ ቀለጠ'ነጠረ ") (ዘካ. ፲፫፡ ፱) ።
ተከለሰ፡ ተደቀለ ።
ተከለሰ፡ ተጨመረ ("ተቀላቀለ") ።
ተከለሰ፡ ተጨረሰ ("ተፈጸመ መላ ") ።
ተከለበሰ፡ ተከነበለ፡ ተቸለሰ፡ ፈሰሰ።
ተከለከለ (ተከልከለ)፡ ተከላ ("ታገደ ቆመ ታገረ ቀረ ተጠበቀ ሐይ ተባለ ተተወ ") (ዘፀ. ፴፮፡ ፮፡ ዘኍ. ፲፮፡ ፵፰, ፶፡ ኢዮ. ፳፱፡ ፱፡ ፵፪፡ ፪፡ ሮሜ. ፩፡ ፲፪) ።
ተከለፈ፡ ተሰረቀ ("ተቀማ ተነጠቀ ") ።
ተከላ (ተከልአ)፡ ተከለከለ ።
ተከላ/ትክሎሽ (ትክለት)፡ የመት...ክል ሥራ ።
ተከላሽ፡ የሚከለስ/የሚጨመር ።
ተከላከለ፡ ተነሣሣ ።
ተከላከለ፡ ተጠባበቀ ("እየሸሸ እያፈገፈገ ጥቂት ጥቂት ተዋጋ አልሞት ባይ ተጋዳይ ተኳዃነ ላከል ") ።
ተከላካይ (ዮች)፡ የተከላከለ/የሚከ ክል ("አትስጥ ባይ ") ።
ተከልካይ፡ የሚከለከል/የሚጠበቅ ።
ተከመረ፡ ተደረደረ ("ተደረበ ተዘመመ ተጐቸ ተቈለለ ") ።
ተከመረ፡ ወደቀ ("በላይ ኾነ ተጫነ ለመያዝ እከሌ በደን ውስጥ ሲኼድ ድንገት ነብር ተከመረበት ") ።
ተከመቻቸ፡ ተሰባሰበ ("ተጠረቃቀመ") ።
ተከመከመ፡ ተከፈከፈ ("ተተካከለ") ።
ተከማሪ (ሮች)፡ የሚከመር ("ነዶ ድር ቆሽ መጽሐፍ ግን በጕልላት ፈንታ ተከማሪ ይላል ") (፩ ነገ. ፯፡ ፲፮, ፲፯) ።
ተከሠተ (ተከሥተ)፡ ተገለጠ ("ግልጥ ኾነ ታየ በራ ") ።
ተከሳከሰ፡ ተባባለ ("ተፈናከተ ተሳበረ ተዳቀቀ ጊዜ መከሳከስ መፈናከት መሳበር መከሳከሻ መፈናከቻ መሣሪያ ስፍራ አከሳከሰ አባባለ አፈናከተ አዳቀቀ አሳበረ ባይ አከሳካሽ ያከሳከሰ የሚያከሳክስ በለው ማከሳከስ ማፈናከት ማሳበር ማከሳከሻ አከሳከስ አፈነካከት መከስከስ ከሸከሸ ቃሪያ በርበሬን ሌላውንም የተክል ፍሬ ዐኘከ በላ ሙከሽከሽ ማኘክ መብላት ከሽ ቀላል ዋዛ እከሌን ባታውቀው ነው እንጂ ከሽ አይዶለም ከሽ አደረገ በጥርሱ ሰበረ በዱላ መታ አነከተ ከሽ አለ ተሰበረ ነከተ ከሽ ከሽ አለ በመንጋጋ ውስጥ ድምጥ ሰጠ ተሰማ ከሽከሼ በሠማ ምጣድ ተንቃቅቶ የደረቀ እንጀራ ሲበሉት ከሽ ከሽ የሚል መከሽከሽ ማኘክ መብላት ተከሸከሸ ታኘከ ተበላ ክሽክሽት ጤፍ የሚያካክል የጐመን ትል ቅጠለ በላ ክሽክሽት ነጭ የዦሮ ዕከክ ክሽክሽታም ክሽክሽት ያለበት ባለክሽክሽት ጐመን ሰው ኰሰኰሰ (ኰስኰሰ) ሻከረ ሻካራ ኾነ ወጋጋ ገላን ኰሰኰሰ ኵስኵስት ሠራ አዥጐረጐረ ቈሰቈሰን እይ ኰሰኰሰ (ትግ፡ ኰስኰሰ) ኰተኰተ ቈፈረ ዳከመ ኰሰኰሰን ኰተኰተ ማለት ባረብኛ ሰና ተ ተወራራሾች መኾ ናቸውን ያሳያል ኰስኳሽ የኰሰኰሰ የሚኰሰኵስ ሻካራ ጠጕር ናጫ ") ።
ተከረ (ተከነ)፡ ተቀጨቀጠ ነዘነዘ ።
ተከረ፡ ተፋተነ፡ ተዣመረ፡ ተባባለ።
ተከበሰ፡ ተጠመዘዘ ("ተጠቀለለ ታሰረ") ።
ተከበሰ፡ ተጠመጠመ ("ተደመረ ተከመረ ተደረበ ") ።
ተከበሰ፡ ዐበጠ ("ተድበለበለ") ።
ተከበረ፡ ("ከበረ")፡ በሰው ዘንድ ወይም በገዛ አፉ ተመሰገነ ተጓደደ።
ተከበረ፡ በሹም ሥልጣን ተያዘ ተጠበቀ ርስቱ ገንዘቡ።
ተከበረ፤ታረፈ፡ በዓል ኾነ።
ተከበበ፡ ክብ ኾነ ተደረገ ።
ተከበበ፡ ዙሪያው ተያዘበት ።
ተከበተ (ተከብተ)፡ ተሸሸገ ("ተደ በቀ ታባ") ።
ተከበከበ፡ ተደገሰ ("ተሰረገ በመብል ተጠበቀ") ።
ተከበደ፡ ተጨቈነ፡ ተጨነቀ።
ተከባቢ፡ የሚከበብ ("ክብ የሚኾን") ።
ተከባባሪ፡ የሚከባበር፡ ወዳጅ፡ ባልን ጀራ ።
ተከባከበ፡ ተሰራረገ ("ተመጋገበ ተከናከነ (በየጊዜው በየሰዓቱ መገበ ዓይንፈስ ብኸ አለ ተጠንቅቆ ጠበቀ)") ።
ተከባካቢ፡ የተከባከበ/የሚከባከብ ።
ተከተለ፡ ለጠቀ፡ (ከተለ) ።
ተከተከ፡ ክፉኛ አሳለ ።
ተከተከ፡ ጠቀጠቀ ወጋ በላ ።
ተከታይ፡ ታናሽ ወንድም ("ጡት ኣስ ተከታይነት ተከታይ መኾን ተከተል የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ በስተዠርባ ኺድ ለጥቅ ቅደም ተከተል ተመልከት ዐላማኸን ተከተል አለቃ ኸን እንዲሉ ክተላ ቅጠላ ልጠቃ የመከተል ሥራ ከተል ለጠቅ ጠጋ መከተል በኋላ መኼድ መቀጠል መለጠቅ ") (፪ነገ. ፲፯፡ ፳፩፡ ኢዮ. ፴፬፡ ፳፯፡ ማቴ. ፲፮፡ ፪፳፬) ።
ተከነ፡ በገነ ነደደ ገመነ ፈላ በሰለ...ተቈጣ ።
ተከነበለ፡ ተበጀ ("አክንባሎው ተሰፋ ወስከንባዩ ") ።
ተከነበለ፡ ተከደነ ("ተገጠመ") ።
ተከነበለ፡ ወደቀ ("ተደፋ ተቸለሰ ተገለ በጠ ፈሰሰ ") ።
ተከነተረ፡ ተመታ ("ተገደለ ቶሎ ሞተ ክንትር የተከነተረ የሞተ ") ።
ተከነዋወነ፡ ተቀለጣጠፈ ።
ተከነዳ፡ ተለካ ("ተመጠነ ተሰፈረ ተከነዳ ተከፈለ ተሰጠ ") ።
ተከነዳዳ፡ ተለካካ ።
ተከናነበ፡ ተጐናነበ ("ተሸፋፈነ ") (ኤር. ፲፬፡ ፫, ፬፡ ፩ ቆሮ. ፲፩፡ ፬, ፭) ።
ተከናናቢ፡ የሚከናነብ ("ተሸፋፋኝ") ።
ተከናከነ፡ ተቀናቀነ ።
ተከናከነ፡ ተከባከበ ("ጠበቀ") ።
ተከናዋኝ፡ የሚከናወን ።
ተከናዳ፡ በክንድ ተላካ ።
ተከንባይ፡ የሚከነበል/የሚደፋ ።
ተከኪ፡ የሚከካ ።
ተከካ፡ ተሰበረ ("ተፈነከተ ተከፈለ") ።
ተከወሰ፡ ተነቀነቀ ("ተበጠበጠ") ።
ተከወነ፡ ተበጀ ("ተዘጋጀ ተደረገ ተቀ ናበረ አጌጠ አማረ ሰመረ ክውን የተከወነ ዝግጁ ክውንውን ቅንብርብር አከዋወን አቀነባበር መከወን ከነ ' 'ነን ተመልከት ") ።
ተከዘ (ተክዞ/ተከዘ)፡ ዐዘነ ተቈረ...ቈረ (ከደስታ ከፈገግታ ራቀ) ።
ተከዘ፡ አዘገመ ቈየ ። "ዐለንጋ እስቲዝ በክርን ይተክዙ"። "እራት እስቲቀርብ በጥሬ ተከዘ"።
ተከዘ፡ ፈሰሰ ወረደ (ግእዝ) ።
ተከዚ/ተከዜ፡ የዠማ ስም (ከላስታየሚነሣ ወንዝ በአትባራ ከ፪ቱ አባዮች ጋራ የሚገጥም ታላቅ ፈሳሽ - የትግሬንና የበጌምድርን ጠቅላይ ግዛቶች የሚለይ ዥረት - በግእዝ ሲናበብ "ተከዜ" ይባላል) ።
ተከየ (ተሀከየ)፡ ሰነፈ ("ለገመ ሀኬ ተኛ ልግመኛ እከየኛ ኾነ ቸል አለ ") ።
ተከየ፡ ለገመ፡ ሰነፈ፡ ቸል አለ፡ ዋሾ/ቀጣፊ/አታላይ ኾነ።
ተከየ፡ ለገመ፡ ከየ ።
ተከደነ (ተከድነ)፡ ተሰለተ ("ተከፈ ከፈ ተሸፈነ ተከለለ ለበሰ ተገጠመ ") ።
ተከዳ (ተከድዐ)፡ ታዛዥ ዐጣ ("ብቻ ውን ቀረ ባለ ") ።
ተከዳኝ፡ የሚከደን ("ጣራ ሰንበሌጥ ") ።
ተከዳደነ፡ ተሸፋፈነ ("ተለባበሰ") ።
ተከዳዳ፡ ተካካደ ።
ተከጀለ፡ ታሰበ ("ተሻ ተፈለገ ተ ላወጠ የምግብ የባለምግብ ") ።
ተከጃይ፡ የሚከጀል ።
ተከጃጀለ፡ ተፈላለገተፈቃቀደ ("ባገ ኘኹት ባገኘኹት ተባባለ በልብ ባሳብ") ።
ተከጃጃይ፡ የሚከጃጀል ("ተፈላላጊ ") ።
ተከፈለ (ተከፍለ)፡ ተለየ ("ኹለት ኾነ ለሙሴ ኤርትራ ለኢያሱና ለኤልያስ ለኤልሳዕ ዮርዳኖስ ተከፈለ ") (ዘፀ. ፲፬፡ ፳፩፡ ኢያ. ፫፡ ፲፮፡ ፪ ነገ. ፪፡ ፰ - ፲፬) ።
ተከፈለ፡ ተመለሰ ("ተሰጠ ገንዘቡ ተቀ በለ አበዳሪው ") ።
ተከፈተ፡ (፩ ነገ. ፲፮፡ ፴፬፡ ሉቃ. ፩፡ ፷፬) ተወለለ ("ተገለጠ በራ ተፈታ ተለቀቀ መናገር ተቻለው ") (ሕዝ. ፴፫፡ ፳፪) ።
ተከፈከፈ፡ ተከደነ ("ተመታ ተተካከለ ተከፈከፈ ተበጠረ ተከመከመ ተከፈከፈ ለበሰ ") ።
ተከፈፈ፡ በክፈፍ ተሠራ/ተበጀ/ተሰፋ ("ክፈፍ ኾነበት ተደረገበት ተከፋፊ የሚከፈፍ ክፍፍ የተከፈፈ ") ።
ተከፋ፡ ተቀየመ ("ዐዘነ ተከዘ ተቈቈረ ") (ኢሳ. ፲፭፡ ፬) ።
ተከፋች፡ የሚከፈት ።
ተከፋይ፡ የሚከፈል ("ለባለዳ የሚሰጥ ተከፋይ ተቀባይ ") ።
ተከፋፈለ፡ ተለያየ ("እየብቻው እየራሰ ተኳዃነ ተፈራቀቀ ተከፋፈለ ብድርን ተቀባበለ ") ።
ተከፋፈት፡ ተዘረጋጋ ("ተገላለጠ") ።
ተከፋፋይ፡ የሚከፋፈል ("የሚለያይ") ።
ተከፍካፊ፡ የሚከፈከፍ ("ቤተ ክሲያን የሀብታም ቤት ") ።
ተኵለፈለፈ፡ አደፈ፡ ኰለፈ ።
ተኵለፈለፈ፡ ጥርክርክ ኾነ ("እንዳሣማ ኵልፍልፍ የተኵለፈለፈ ኵልፍልፍ አለ ብልሽትሽት አለ መኵለፍለፍ በብዙ ወገን መበከል ") ።
ተኵላ (ሎች)፡ ያውሬ ስም (የበረሓ ውሻ የበግ ያንበሳ ጠላት ነጣቂ - "ዐይንን" ተመልከት) ።
ተኵስ፡ ከቀኝ ወደ ግራ የተሰፋ የነጠላ ጠርዝ ስፌት ("ተኵስ ስፌት" እንዲሉ) ።
ተኵስ፡ የዐይን/የከብት/የገላ ጠባሳ (የሌባ ምልክት የነፍጥ ድምጥ) ።
ተኵነሰነሰ፡ ካህንኛ/ታቦትኛ ለባበሰ ("ተሸላለመ ተሽቀረቀረ ") ።
ተኪ፡ የተካ/የሚተካ (ክፋይ ወካይ) ።
ተካ (ትግ. ተክአ)፡ በተወሰደ በጠፋ...በሞተ በኼደ ፈንታ ሌላ ስጠ መለሰ ረጠበ ከፈለ ካሰ ወከለ (ዘሌ. ፳፬፡ ፲፰) ። ተካ/ተካልኝ፡ የሰው ስም ።
ተካለለ፡ ተዋሰነ ("ተዳካ ተካላይ (ዮች) የሚካለል ተዋሳኝ ") ።
ተካለለ፡ ተገራረደ ።
ተካለበ፡ ተሯሯጠ ("ተቻኰለ ተጣደፈ") ።
ተካሠሠ (ተኃሠሠ ተፈላለገ)፡ ፈለገ ("ጠየቀ ማለደ ለመነ ተቀናቀነ ሹመት ተካሠሠ እንዲሉ መተርጕማን ") ።
ተካሪስ/አተካሪስ፡ በቀሚስ ላይ የተሰፋ ድንድን መታጠቂያ ("አባ" ብለኸ "አባ ወራን" እይ) ።
ተካራ/ተኻራ፡ አተካራ ።
ተካበ፡ ("ተክዕበ") ተደረበ፡ ተነባበረ ደንጊያ በደንጊያ ላይ ኾነ። ተካበ፡ የሰው ስም። ተካበች፡ የሴት ስም ።
ተካበበ፡ የከባቢ ተከባቢ ተኳዃነ ("ተዟረ") ።
ተካበተ (ተመክዐበ/ተካዕበተ)፡ ተጠራቀመ ("ዕጥፍ ድርብ ኾነ ደለበ ልብሱ ገንዘቡ ወርቁ ብሩ") ።
ተካበደ፡ ከበደ፡ ("ተመናዘለ")። ሸኽ አለልክ ይካበዳል።
ተካባች፡ የሚካበት ("ተጠራቃሚ በፈረንጅኛ ካፒታል ' ይባላል") ።
ተካባጅ፡ የሚከብድ፡ ("የሚካበድ")መካበድ፡ መክበድ ("መመናዘል") ተከባበደ፡ ተመነዛዘለ።
ተካተካን፡ እበን መትከን ።
ተካነ (ተክህነ)፡ ዳቈነ ("ድቍና' ተቀበለ ካህን ኾነ (ቀሰሰ) ") (ዘፀ. ፳፱፡ ፴፬) ።
ተካነ፡ ቅቤና ቅመም ገባበት ("ጣመ ጣፈጠ ወጡ ") ።
ተካነ ተኰሰ
ተካነ፡ የክህነት ሥራ ሠራ ("አገለገለ ቀደሰ ሠለሰ ") ።
ተካነ፡ ዲያቆን ኾነ፡ ካነ ።
ተካኝ (ኞች)፡ የሚካን ("ክህነት ተ ቀባይ ") ።
ተካኝ፡ ተናዳጅ ተከነ ።
ተካኝ፡ የሚተክን (ተናዳጅ) ። ተካኝ፡ የሚካን፡ ካነ ። ትክን፡ የተከነ የፈላ የበሰለ ("ትክን አለ" - እፍታ አልባ ኾነ - "ትክን ያለ ወጥ" እንዲሉ) ።
ተካከለ፡ ልክ ኾነ ፥ ሳይበላለጥ ቀረ፡ (ኢዮ ፳፰፡ ፲፱ ። ሕዝ ፴፩፡ ፰) ። ድግርና ገባር ሲተካከል ያምር እንዲሉ።
ተካከለ፡ መላልሶ ተከለ ።
ተካከለ፡ ተመሳሰለ ፥ ተነጻጸረ ፥ ተመጣጠነ ። ተከለን ተመልከት ።
ተካከለ፡ ተመደመደ ፥ ተደለደለ ።
ተካከለ፡ ትክክል ተኳዃነ፡ ከለ ።
ተካከከ፡ የማከክ ብድር ተመላለሰ ("አህያ በጥርስ ይተካከካል ") ።
ተካካበ ("ተካዐበ")፡ ተደራረበ። ተካካበ፡ ተመሰጋገነ፡ ተወዳደሰ። መካካብ፡ መመሰጋገን። መካካቢያ፡ መመሰጋገኛ።
ተካካደ (ተካሐደ)፡ ተለያየ ("ተረጋ ገመ ") ።
ተካካደ፡ ተሸፋፈጠ ("ዐሎ ተባባለ") ።
ተካኼደ፡ ተቃና ("ተቀናበረ ተፋጠነ ሥራው ተካኼደ እንዲሉ ") ።
ተካወሰ፡ ተነቃነቀ ("ተበጣበጠ") ።
ተካዥ፡ የሚተክዝ/የሚያዝን (ዐዛኝ ተቈ...ርቋሪ) ።
ተካየደ፡ ተዋዋለ ("ቃል ኪዳን ተጋባ ተማማለ ") (ዘዳ. ፳፱፡ ፩፡ ኤር. ፴፩፡ ፴፩-፴፫) ።
ተካይ (ዮች)፡ የተከለ/የሚተክል (ቸ...ካይ ከሳሚ አቋሚ - ዮሐ.
፲፭፡ ፩) ።
ተካይ፡ ነቃይ (ሰውን በክርስትና/በማዕርግ የሚተክል/የሚነቅል ባለሥልጣን) ።
ተካይነት፡ ተካይ መኾን ።
ተካደ፡ ተሸፈጠ ።
ተካደ (ተክሕዶ)፡ ልጄምአይዶል ተባለ ("ተለየ ተረገመ") (ሉቃ. ፲፪፡ ፱) ።
ተካደነ፡ ተሻፈነ ("ተላበሰ") ።
ተካዳ (ተካድዐ)፡ አላውቅኸም ተባለ ።
ተካዳ፡ ተናከሰ ("ተባላ") ።
ተካጀለ፡ ተፋቀደ ("ተፋለገ") ።
ተካጅ፡ የሚካድ/የሚረገም ።
ተካፈለ፡ ተጋራ ("ተፋለመ ግማሽ ግማ ሹን ድርሻ ድርሻውን ወሰደ ተራከባ ተናተነ ") (ማቴ. ፳፯፡ ፴፭) ።
ተካፈተ፡ አፍ ላፍ ተጋለጠ ("ክፉ በጎ ተነጋገረ ተመላለሰ ") ።
ተካፋይ (ዮች)፡ የሚካፈል ("ምንዝር ባላንጣ ዝሞት ") (፩ ቆሮ. ፲፡ ፳) ።
ተካፋይነት፡ ተካፋይ መኾን ("ባላንጣነት") ።
ተኬደ፡ ታለፈ "
ተኬደ፡ ተኼደ ("ተረገጠ") (ኢሳ. ፳፰፡
ተክለ ሃይማኖት፡ ፲፻ ዓ.ም...ገሠ (የላስታ ንጉሥ) ።
ተክለ ሃይማኖት፡ በ፯፻ ዓ.ም. የነበሩ የኢትዮጵያ ሐዋርያ ጻድቅ ።
ተክለ ሃይማኖት፡ በ፱፻ ዓ.ም. የነ...በሩ ዕጨጌ ።
ተክለ አልፋ፡ በ፲፰፻ ዓ.ም. ከደብረ ሊባኖስ ተይዘው ስለ ሃይማኖት በፍየል ዐምባ ተገርፈው ምላሳቸው ተቈርጦ በውሃ ጥም የሞቱ መናኝ ሊት መምር ።
ተክለፈለፈ፡ ተክለበለበ ("እዚያም እዚያም ተገኘ ከኹሉ ኣለኹ አለ ") ።
ተክሊል አደረገ፡ ሞላ ("ሥርዐቱን ፈጸመ በተክሊል አገባ ") ።
ተክሊል፡ የሕግ ጋብቻ ሥርዐት፡ ከለለ ።
ተክሊል፡ የክርስቲያን ጋብቻ ሥነ ሥር ዐት ("ሙሽራውና ሙሽራዪቱ አክሊል ተቀዳጅተው አበባ ይዘው አንድ መጐናጸፊያ ለብሰው የተባረከ ቀለበት አድርገው ቃል ኪዳን የሚገቡበት ሥጋውንና ደሙን የሚቀ በሉበት መንፈሳዊ ሕግ እስከ ሞት ድረስ አለመፋታትንና አለመለያየትን የሚሰብክ የሚያስተምር ለሥጋም ለነፍስም ጥቅም የሚ ኾን ጸሐፈ ብለኸ መጽሐፍን እይ ") ።
ተክሌ፡ ከፊለ ስም ("የኔ ተክል" ተብሎም ይተረጐማል) ።
ተክል ("ከታቢ ") (ዎች) ።
ተክል (ሎች)፡ ቡቃያ ችግኝ ፍሬው...የሚበላና የማይበላ ዕንወት የሽቱ ቅጠል ።
ተክልዬ፡ "የኔ ተክለ ሃይማኖት" ("ሰነቃ" ብለኸ "ሳንቃን" እይ) ።
ተክበሰበሰ፡ ተጐተተ ("ተግበሰበሰ ታቦትኛ ኼደ ትት ") ።
ተክታኪ፡ የተከተከ/የሚተከትክ (ጠቅ...ላጭ) ።
ተክነዘነዘ፡ ተቅነዘነዘ ።
ተክነፈነፈ፡ ተወዘወዘ ("ተርገበገበ ተቅ ነዣ ") ።
ተኰለኰለ፡ ዐበጠ ("ጠጠረ") ።
ተኰለፈ፡ ተበከለ ("ተበላሸ ጠፋ ") ።
ተኰላ፡ ታጠበ ("ጠራ ተፈገፈገ ተወለወለ ' ታደሰ እኮመር ገባ የተኰላ ወርቅ እንዲሉ ") ።
ተኰላ፡ ከለበ
ተኰላ፡ የሰው ስም ።
ተኰላሸ፡ ተቀደደ ("ተሠነተረ ተሰነጋ ተጐነደለ ከብቱ ቍላው ") ።
ተኰላተፈ/ተኰለታተፈ፡ ተንተባ ተበ ("ተሳሰረ ") ።
ተኰልኰሎ (ዎች)፡ ታናናሽ ልጆች' በማዘንት ዙሪያ ተኰልኵለው የሚታዩ ("ተልኰሎ ውሰጠ ብዙ ነው ንጊያ ") ።
ተኰልኰሎ፡ ሕፃናት ኰለኰለ ።
ተኰልኰሎዎች፡ ኰልኰሌ ("ቅራቅንቦ") ።
ተኰልኳይ፡ የሚኰለኰል ("ተደርዳሪ") ።
ተኰመሸሸ፡ ዐፈረ ("ተሰቀጠጠ ዕፍረት ያዘው ") ።
ተኰመተረ፡ ተቋጠረ 'ቋጣራ ኾነ ("ተ ጨመተረ ") ።
ተኰመታተረ፡ ተጨመታተረተጨመ ዳደደ ።
ተኰመኰመ፡ ታኘከ ("ተበላ ተጠጣ ") ።
ተኰማተረ፡ ዐረረ ("ተጨማደደ ተጨማተረ ተጨባበጠ ያንዠት የዥማት የፈት ተኰማታሪ የሚኰማተር የግርሽጥ እ ንቡጥ ") ።
ተኮማጠጠ፡ ተሸማጠረ ("ተበሳጨ አሳዛኝ ነገር ተናገረ ") ።
ተኰሰ፡ ለኰሰ ለበለበ አቃጠለ ፈጀ (ቤትን ደንን ድምርን አፍን የዐይን ሥርን ክንድን የሌባን ግንባር ዐዲስ ቍስልን ዕባጭን ሸሐኝን) ።
ተኰሰ፡ መላ ፈጸመ ጕዳይን (ገቢር) ።
ተኰሰ፡ ሞቀ ወበቀ ፀሓዩ (ተገብሮ - ዘፍ.
፲፰፡ ፩፡ ፩ሳሙ. ፲፩፡ ፱, ፲፩) ።
ተኰሰ፡ ሰፋ (ነጠላን ቅጥልጥል ደቦሎን) ።
ተኰሰ፡ ነደደ ተቃጠለ እሳቱ ቍጣው (ኢዮ. ፵፪፡ ፯) ።
ተኰሰ፡ ኣሰማ...ድም (አደረገ ጠመንዣን መድፍን ሽጕጥን) ።
ተኰሰ፡ ካሰቀቅ ከፈለ (ላቈሰለው ሰው) ።
ተኰሰ፡ የግንብን ደንጊያ መጋጠሚያ በኖራ በስሚንቶ ላከከ ቀባ ገጠመ ።
ተኰሰ፡ ዳመጠ ቀጥ ለጥ አደረገ አስተካከለ (የታጠበ ልብስን) ።
ተኰሰኰለ፡ ተደረደረ ("ጐን ለጐን ተ ተከለ ተቀመጠ ") ።
ተኰረ፡ ለበመ አስተዋለ ዐይኑን ጣለ (ትክ ብሎ እየተመለከተ ዐወቀ አነጣጠረ) ። ተኳር (ሮች)፡ የተኰረ/የሚተኵር (ል...በኛ ለባሚ ኦስተዋይ አነጣጣሪ) ። ተኳርነት፡ ተኳር መኾን ። ትኰራ፡ ምልከታ ።
ተኰረኰመ፡ ተጨበጠ/ተመታ/ተገጨ/ተሰበረ/ተሸረፈ/ታጠፈ ።
ተኰራ (ተኰርዐ)፡ ራሱን በበትር ተመታ ("ተቈረመ ") ።
ተኰራ (እምከመ ኰርዐ)፡ ከኰራ/ከተጓደደ ሰው ተኰራ መዋረዱ አይቀርም ።
ተኰርኳሚ፡ የሚኰረኰም ("ተሰባሪ") ።
ተኰነ፡ ኾነ ተገኘ ተፈጠረ (የትዃን) ። ትዃን (ኖች)፡ የተባይ ስም...በቤት ውስጥ በጣራ በግድግዳ ባልጋ በማንኛውም መኝታ ላይ ኹኖ የሰውን ገላ የሚቀነቅን የሚበላ የሚልጥ የሚያቃጥል የሚያንገበግብ ግማታም ፍጥረት ። ("ተረት - እኔን ቢወዱኝ ወዳፍንጫቸው ወሰዱኝ አንቺን ቢጠሉሽ አጥመዝምዘው ጣሉሽ" አለቻት ትዃን ቍንጫን - "የቤቴ መቃጠል ለትዃኑ በጀው") ።
ተኰነተሸ፡ ተበጠሰ ("ተቈረጠ ዐጪር ኾነ ") ።
ተኰነነ፡ ከጽድቅ ራቀ ("ተፈረደበት ተቀጣ ተጐዳ ዘብጥያ ውህኒ ቤት ገባ ሲኦል ገሃነመ እሳት ወረደ ሥቃይ ተቀበለ መከ ራውን አየ ") (ዮሐ. ፫፡ ፲፰) ።
ተኰናኝ (ኞች)፡ የሚኰነን ("ኀጢአ ") ።
ተኰኳ፡ ተመታ ("ተፈነከተ") ።
ተኰኳ፡ ተሼጠ ("ተለወጠ") ።
ተኰኳ፡ ተጣለ ("ወደቀ") ።
ተኰየዕ፡ ተከመረ ("ተቈለለ") ።
ተኰደኰደ፡ በደዌ ተያዘ ("ሆዱ እስ ኪያብጥ እስኪነፋ") (ሉቃ. ፲፬፡ ፪) ።
ተኰደኰደ፡ ተገረኘ ("ታሰረ") ።
ተኰፈሰ፡ ከንቱ ውዳሴ ተቀበለ ("ተመ ተኰፈሰ ተመየደ ተበጠረ ጐፈረ ኵፍስ የተኰፈሰ የተመሰገነ ብጥር ጐፈሬ ") ።
ተኰፋነነ፡ ኰራ፡ (ኰፈነነ) ።
ተኳለ (ተኵሕለ)፡ ኵልና መድኀኒት ተቀባ ("ተጌጠ") (ራእ. ፫፡ ፲፰፡ ፪ነገ. ፱፡ ፴) ።
ተኳለፈ፡ ተባከለ ።
ተኳሳ፡ ሙቀታም ወበቃም ስፍራ (የሚፋጅ የሚያቃጥል በርበሬ ሰናፍጭ ፌጦ የመሰለውኹሉ) ።
ተኳሽ (ሾች)፡ የተኰሰ/የሚተኩስ (የማ...ይስት አነጣጣሪ ለኳሽ አቃጣይ - "ፍጥም አፍ ራሽ ቤተ ክሲያን ተኳሽ" እንዲሉ) ።
ተኳሽነት፡ ለኳሽነት ።
ተኳኳለ (ተኳሐለ)፡ ኵል ተቃባ ("ተቀባባ ") ።
ተኳዃነ፡ ተጠማመረ ("ተደራረገ ተፋቀረ ተዋደደ ተሰማማ አቶ እከሌና እመት እከሊት አልተኳዃኑም ") ።
ተኳይ፡ የሚኳል/የሚቀባ ።
ተኸሬ፡ በመረሬ የሚዘራ ስንዴ ስም ።
ተኹለደሬ፡ በወሎ ክፍል ያለ አገር...ስም ።
ተኾለተ፡ ኹለት ኾነ፡ ኹለት ተባለ።
ተኾነ፡ ("ከኾነ")፡ ከተደረገ ከበጀ ።ገ ብለኽ ' መጋዞን እይ ።
ተኾነ የሰው ስም ።
ተወ፡ ለቀቀ ባለ ፈታ ገደፈ ርግፍ አደረገ ማረ (ሉቃ. ፭፡ ፳፰) ። "ተውኸ ተዉ ተዋችኹ ተወች ተውሽ ተውኹ ተውን" እያለ ይዘረዝራል ። ("ተረት - ያምራል ብሎ ከተናገሩት ይከፋል ብሎ የተዉት") ።
ተወሓሐደ፡ ተዋዋደ/ተለወሰ/ተገነ ኛኘ/ተዛመደ/ተሰማማ/ተኳዃነ ።
ተወለለ፡ ተከፈለ/ተሠነጠቀ/ተከፈተ ።
ተወለማመጠ፡ የተወላመጠ ድርብ ።
ተወለቀ፡ ታሸ/ተበጠበጠ/ተመታ ።
ተወለቃቀመ፡ ተወለጋገመ ።
ተወለከፈ፡ ታጐለ/ተሰነከለ/ታወከ ።
ተወለካከፈ፡ ተሰነካከለ/ተደነቃቀፈ ።
ተወለወለ፡ ተመታ/ተጠፈጠፈ/ቀለጠ ።
ተወለወለ፡ ተጠረገ/ታሠሠ/ታበሰ/ታ ደፈ/ተሰነገለ/ጠራ ።
ተወለደ፡ ተዘመደ ።
ተወለደ፡ ከማሕፀን (ከጨለማ ወደ ብ ርሃን ከጠባብ ወደ ሰፊ) ወጣ/መጣ/ወረደ/ተገኘ ።
ተወለደ፡ ጠበቃ ኾነ/ተወከለ ።
ተወለጋገመ፡ ተወለቃቀመ ።
ተወለጋገደ፡ ተወለጋገመ ።
ተወላለደ፡ ተዘማመደ ።
ተወላመመ፡ ተጣመመ/ተዛወረ ።
ተወላመጠ፡ ተዘዋወረ ።
ተወላቀመ፡ ተወላገመ ።
ተወላከፈ፡ ተሰናከለ/ተደናቀፈ ።
ተወላወለ፡ በጥፊ ተማታ/ተቃለጠ/ተጠፋጠፈ ።
ተወላወለ፡ ተወዛወዘ ።
ተወላዲ፡ የወልድ አካል የስም ግብር ("ትርጓሜው ተወላጅ") ።
ተወላዳ፡ የዠግንነት ሥራ ሠራ ("ወ ንድ ወጣው በሥራ ታወቀ ተወናወነ ተዛ መረ ተፈናፈነ ተዋጋ ተጋደለ") ።
ተወላጅ፡ የተወለደ/የሚወለድ ("የ፫ ያ፬ ቤት ዘመድ") ።
ተወላገመ፡ ተጣመመ/ተወላቀመ ።
ተወላገደ፡ ተወላገመ ።
ተወሰነ፡ ተደነገገ/ተደነባ/ታገገ/ተገ ደበ/ተጠበቀ/ተከለከለ/ተከለለ ።
ተወሰከ፡ ተጨመረ/ተነሣ ።
ተወሰወሰ፡ ተሰፋ/ተሸደሸደ/ተሸከ ሸከ/ተሸለለ ።
ተወሰወሰ፡ ተዋኘ ("ውስጥ ለውስጥ ታለፈ") ።
ተወሰደ፡ ተይዞ ኼደ/ተጋዘ/ተነዳ/ተቀማ/ተነጠቀ/ጠፋ (ገላ. ፪፡ ፲፡ ፲፫) ።
ተወሰጠ ("ተወነገ ገባ") ።
ተወሣ (ተወሥአ)፡ ታሰበ/ተመለሰ ("ተባለ ተነገረ ተሰጠ መልሱ") ።
ተወሳሰበ፡ ተጠላለፈ/ተጠማመረ/ተ ወታተበ/ተተባተበ ።
ተወሳሰነ፡ ተደናጋገገ/ተደነባባ ።
ተወሳሰደ፡ ተቀማማ/ተነዳዳ/ተጋጋዘ ።
ተወሳሳኝ፡ የሚወሳሰን ።
ተወሳኝ፡ የሚወሰን/የሚከለል ።
ተወሳወሰ፡ ተሸዳሸደ ።
ተወሳወሰ፡ ተወዛወዘ/ተነቃነቀ/ተዛ መረ/ተወላዳ/ተፈናፈነ ።
ተወሳዋሽ፡ የተወሳወሰ/የሚወሳወስ ("ተነቃናቂ") ።
ተወሳጅ፡ የሚወሰድ/የሚኼድ ።
ተወረ, ተጫረ፡ ተቧጨረ።
ተወረሰ፡ ተገኘ/ተያዘ/ተወሰደ ("በቃል ያለ ይረሳል በመጣፍ ያለ ይወረሳል") ።
ተወረስ፡ ንብረቱ የተወረሰበት ሰው ("ዘምቶ ተወረስ” እንዲሉ) ።
ተወረረ፡ ተከበበ/ተዘረፈ/ተበዘበዘ/ተ በረበረ/ተማረከ ("የተናቀ ከተማ ባህያ ይወ ረራል” እንዲሉ) ።
ተወረበ፡ ተባለ/ተዜመ ወረቡ ።
ተወረበ፡ ታጨደ/ተላጨ ("ሣሩ ጠ ጕሩ") ።
ተወረወረ፡ ተለቀቀ/ተነደፈ ።
ተወረወረ፡ ተሸጐረ/ተቀረቀረ/ተቈለፈ ።
ተወረወረ፡ ተጓነ/ተጣለ ።
ተወረወረ፡ ገባ/ጠለቀ/ዐረበ ።
ተወረደ (ወረደ)፡ ፈጸመ/ጨረሰ ("እከሌ ዕዳውን ተወረደ” እንዲሉ) ።
ተወረደ፡ አነሰ/ተቀነሰ/ዐጸጸ/ጐደለ ።
ተወረደ፡ ወረደ ("ተዋረደ ተዋረሰ") ።
ተወረደ፡ ዝቅ ተባለ ("ቍልቍል ተ ኼደበት ዛፉ ገደሉ") ።
ተወረፈ፡ ተሰደበ/ተፀረፈ ("አንተ እን ዲህ ተባለ") ።
ተወረፈ፡ ተወረበ/ተዘለለ/ታለፈ ።
ተወራ፡ ተነገረ/ተባለ ።
ተወራረሰ፡ ተገነዛዘበ/ተቈላለፈ ("ውርስ ተቀባበለ") ።
ተወራረሰ፡ ተገዳደለ ።
ተወራረደ፡ ተበለተ/ተጠባ/ተቈረጠ ሥጋው ።
ተወራረደ፡ ተገተ/ተከራከረ/ተቈ ታቸ/ተወዳደረ ("እምነት ክደት ተነጋገረ እሰጥ አገባ ተባባለ እንወራረድ አህያ እን ረድ” እንዲል እረኛ ሰጠን ተመልከት) ።
ተወራረፈ፡ ተሰዳደበ ።
ተወራራሽ (ሾች)፡ የተወራረሰ/የሚ ወራረስ ("ተያያዥ ተገነዛዛቢ") ።
ተወራራሽ፡ ገ ከ ቀ ተለዋዋጭ ማለት ነው ("ቍጥር ፲፱ እይ") ።
ተወራራጅ፡ የሚወራረድ ("ተማጋች ጠ በቃ ነገረ ፈጅ") ።
ተወራሽ፡ የሚወረስ ("ርስት ሥራ ጥ በብ መንግሥተ ሰማይ") ።
ተወራሽነት፡ ተወራሽ መኾን ።
ተወራቢ፡ የሚወረብ/የሚታጨድ/የ ሚላጭ/የሚዜም ።
ተወራወረ፡ ተጓጓነ/ተጣጣለ ("ውርወ ራን ተመላለሰ") ።
ተወራጅ (ጆች)፡ አነስተኛ ሰው ("ዝቅተኛ ምክትል ሹም ወይም ሌላ ነገር") ።
ተወራጅ፡ የሚወርድ ።
ተወራጨ፡ ተቅበጠበጠ/ተባጣበጠ ("ጸ ጥታ ዐጣ ተበሳጨ የጣርና የጋር የጭንቅ እንቅስቃሴ ተንቀሳቀሰ") ።
ተወርዋሪ፡ የሚወረወር ("ዋነተኛ ኮከብ ዐይን እባብ") (ኢሳ. ፴፬፡ ፲፭) ።
ተወሸለ፡ ተሸፈነ ("በውስጥ ኾነ") ።
ተወሸለ፡ ተወከለ/ተወተፈ ("ገባ") ።
ተወሸመ፡ ውሽማ ኾነ ።
ተወሸቀ፡ ተጨመረ/ገባ/ተሸጐጠ/ተረፈቀ/ተወዘፈ/ተቀመጠ ።
ተወሸጋገረ/ተወነጋገረ/ተወነካከረ፡ ውሽግርግር/ውንግርግር/ውንክርክር ።
ተወሻሸመ፡ ውሽማ ተኳዃነ ("ተገነኛኘ") ።
ተወቀሠ፡ ተገሠጸ/ተዘለፈ/ተመከረ/ተነቀፈ ።
ተወቀረ (ተወቅረ)፡ ተነቀሰ/ተጠቈረ/ ተጠረበ/ሰላ/ሻከረ/በጀ/ተሰመረ/ተጠረቀ (ዘዳ. ፬፡ ፲፮፡ ፪ ነገ. ፲፪፡ ፲፪፡ ፪ ዜና. ፴፫፡ ፯) ።
ተወቀጠ፡ ተመታ/ተቀጠቀጠ ።
ተወቀጠ፡ ተወጋ/ተፈተገ/ተሸከሸከ/ተደለዘ ።
ተወቂ፡ የሚወቃ እኽል ።
ተወቃ፡ ተጣለ/ተመታ/ተደበደበ ("ተኼደ ተፈለፈለ") ።
ተወቃሪ፡ የሚወቀር/የሚነቀስ ("ወፍጮ ጥርስ") ።
ተወቃሽ፡ የሚወቀሥ ("ወቀሣ ተግ ሣጽ ቍጣ ተቀባይ") ።
ተወቃቀሠ፡ ወቀሣን ተነጋገረ ("ተመ ላለሰ") ።
ተወቃጭ፡ የሚወቀጥ ("ከብት እኸል") ።
ተወበረ፡ ተሳሳተ/ተደናገረ ።
ተወተረ፡ ተሳበ/ተገተረ/ተወጠረ/ተ ለጠጠ ።
ተወተበ፡ ተወሸለ/ተጠመጠመ ።
ተወተወተ፡ ተነዘነዘ/ተጐተጐተ ።
ተወተፈ፡ ተሸጐጠ/ተከደነ ።
ተወት፡ ለቀቅ ።
ተወት አደረገ፡ ለቀቅ አደረገ ።
ተወነባበረ፡ ተደነጋገረ ።
ተወነነ፡ ተወነገ/ተወሰጠ ("ያውሬ") ።
ተወነነ፡ ኰራ/ተጀነነ ("የሰው") ።
ተወነካከረ፡ ተወነጋገረ ።
ተወነዘፈ፡ ተለበሰ ።
ተወነጀለ፡ ወንጀለኛ ተባለ ("ተከሰሰ ተያዘ") ።
ተወነጃጀረ፡ ተወነጋገረ/ተፈነጃጀረ ("ተራራቀ") ።
ተወነገ/ተሻጠ/ተወነጠ/ተወሰጠ/ተወነነ/ተወዘወዘ፡
ተወነገረ፡ ተደነቀረ ።
ተወነጋገረ፡ ተወነካከረ ።
ተወነጠ/ተወነገ/ተወዘወዘ፡
ተወነጨፈ (ተወፅፈ)፡ ተወረወረ/ቴ ለቀቀ/ተሰደደ ።
ተወነጨፈ፡ ፈጥኖ ኼደ/ዐለፈ/ተረ መደ/ቀለጠፈ ።
ተወናቀፈ፡ ተወላከፈ/ተደናቀፈ ።
ተወናበደ፡ ተሳሳተ/ተናጠቀ ፥ ተቃማ ።
ተወናበደ፡ ተደናበረ/ተሯሯጠ ዞረ ።
ተወናከረ፡ ተለያየ/ተራራቀ ("የግድግዳ የጣራ") ።
ተወናከረ፡ ወዲያና ወዲህ ረገጠ ("ተ ውተረተረ") ።
ተወናወነ፡ ተወዛወዘ/ተወላወለ/ተወሳ ወሰ/ተወላዳ ።
ተወናደመ (ተኣኀወ)፡ ወንድም ተኳ ዃነ ("ወንድሜ ወንድሜ ተባባለ ካንድ ኹ ለት ኾነ ተቀናጀ ተጓደነ") ።
ተወናጀለ፡ በወንጀል ተካሰስ/ተከራ ከረ/ተገተ/ተነጋገረ ("ወንጀለኛ ተባባለ ጕድ ለጕድ ተዋጣ ተጐላጐለ") ።
ተወናጀረ፡ ተወናገረ/ተፈናጀረ ።
ተወናጀበ፡ ተወላከፈ/ተደናቀፈ ("ሰክሮ") (ኤር. ፳፭፡ ፲፮) ።
ተወናገረ፡ ተወናከረ ።
ተወናጨፈ፡ በወንጭፍ ተወራወረ ("ጦ ርነት አደረገ ተማታ") ።
ተወናጨፈ፡ ተላለፈ/ተረማመዶ በፍ ጥነት ።
ተወናፈለ፡ ጕልበት ተበዳደረ/ተራዳ/ተጋዘ ("በሥራ ተፈራረቀ") ።
ተወናፋይ፡ የሚወናፈል ("ተጋጋዥ") ።
ተወንጫፊ፡ የሚወነጨፍ ።
ተወከለ፡ ታመነ/ተተካ ("ምትክ ኾነ በሰው ፈንታ ሠራ") ።
ተወከወከ፡ ተጐተጐተ ።
ተወካይ፡ የሚወከል/የሚታመን/የሚ ተካ ("ተተኪ") ።
ተወዘመ፡ ተባለ/ተቆመ ("ዜማው ዘነ በለ ራሱ") ።
ተወዘረ፡ ተጌጠ/ተሸለመ ።
ተወዘተ፡ ተጫነ/ተቀመጠ/ተረፈቀ ።
ተወዘወዘ፡ ተናጠ/ተሰበቀ/ተነቀነቀ (ተነዘነዘ)/ተንገሸገሸ ("ባንገት ወረደ ናቃ") ።
ተወዘገ፡ ተፈተለ/ተመዘዘ/ተሳበ/ተጐ ተተ/ቀጠነ/ረዘመ/ከረረ ።
ተወዘፈ፡ ተወዘተ/ተረበከ/ተረፈቀ/ተጐለተ/ተቀመጠ/ተጋደመ ("ታጐለ") ።
ተወዛች፡ የሚወዘት ("በረመጥ ላይ ተቀ ማጭ") ።
ተወዛወዘ፡ ተነቃነቀ/ተናጋ/ተወላወለ/ ተንቦጫቦጨ/ተነዋወጠ ።
ተወዛዋዥ፡ የሚወዛወዝ ("ተነቃናቂ") ።
ተወዛዛ፡ ተባበሰ ("በቀላል ተቀባባ እጁና ፊቱ") ።
ተወዛፊ፡ የሚወዘፍ ("ተረፋቂ") ።
ተወዝዋዥ፡ የሚወዘወዝ ("እስክስተኛ") ።
ተወዣበረ፡ ተሳሳተ/ተደናገረ ።
ተወያየ፡ ተዛዘነ ("ዐዘንን ትካዜን ተነ ጋገረ ተካፈለ") ።
ተወደለ፡ በወዴላ ላይ ተጫነ/ተጨመረ ።
ተወደሰ፡ ቀረበ ተባለ ("ምስጋናው") ።
ተወደሰ፡ ተመሰገነ ("እግዜሩ ሰዉ ተወደሰ ተቆመ ተደገመ ተዜመ መወድሱ ሳታቱ ዳዊቱ") ።
ተወደስ፡ ዝኒ ከማሁ ። (ተመልከት፡ ደንደስን እይ) ።
ተወደረ፡ ተገመደ/ተጠመረ ።
ተወደረ፡ ታሰረ/ተጋዳ ።
ተወደረ፡ እሰጥ ተባለ ።
ተወደበ፡ ተበጀ ("ወደብ ኾነ") ።
ተወደነ፡ ተቦደነ/ተደገደገ ።
ተወደነ፡ ታሰረ/ተቈረኘ/ተቀረቀበ ።
ተወደወደ፡ ተደበደበ/ተማሰለ/ተወከ ወከ ።
ተወደደ፡ ተከበበ/ታገደ/ተከለከለ/ተመለሰ ።
ተወደደ፡ ተከፈለ/ተሠነጠቀ/ተቈረ ።
ተወደደ፡ ተፈቀረ/ተፈቀደ/ታመነ ("የሰው") ።
ተወደደ፡ እሳት ኾነ ("ተጨበጠ የገበያ") ።
ተወዳሪ፡ የሚወደር ።
ተወዳሽ፡ የሚወደስ ("ተመስጋኝ (ጥወ) መወደስ መመስገን መወደሻ መመስገኛ ተወዳደሰ ተመሰጋገነ መወዳደስ መመሰጋገን መወዳደሻ መመሰጋገኛ አዋደሰ አመሳገነ") ።
ተወዳደረ፡ ተሳሰረ/ተቈረኛኘ ።
ተወዳደረ፡ ተተካከለ ("ሳይበላለጥ ቀረ") ።
ተወዳደረ፡ ተፈካከረ/ተላለከ/ተገተ ተከራከረ/ተወራረደ ።
ተወዳዳሪ (ዎች)፡ የሚወዳደር ("ተፈ ካካሪ") ።
ተወዳዳሪነት፡ ተፈካካሪነት ።
ተወዳጀ፡ ተዋደደ ("ወዳጅ ተኳዃነ") ።
ተወዳጅ፡ የሚወደድ/የሚፈቀር ።
ተወጃወጀ፡ ተወጋወገ ።
ተወጃጀ፡ ተገዛዛ/ተለዋወጠ ("ተሻሻጠ") ።
ተወገረ፡ በደንጊያ ተመታ/ተደበደበ (ዘፀ. ፳፩፡ ፳፰፡ ፩ ነገ. ፳፩፡ ፲፬) ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ሰረቀ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ሠራ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ሸለመ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ሸለመ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ሸተተ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ቈረጠ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ በዛ/አበዛ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ተሠራ/ተደራጀ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ተቈረጠ/ተለየ/ራቀ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ተናገረ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አመሰገነ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አመነ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አበበ/ፈካ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አከበረ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አደገ/ሰፋ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ አገኘ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ከፈለ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ወደደ ።
ተወገነ (ተውገነ)፡ ፈቀደ ።
ተወገነ (ተውገየ)፡ ተደገፈ/ተማመነ ።
ተወገነ፡ ወገን ተባለ ("ተዘመደ") ።
ተወገዘ፡ ተገዘተ ("ውጉዝ ተባለ ተለየ ተወገደ") ።
ተወገደ (ተወግደ)፡ ተለየ/ተወገደ ("ተወገድ ተባለ") ።
ተወገደ (ተወግደ)፡ ተለየ/ተገለለ/ራቀ (መክ. ፰፡ ፫) ።
ተወገጠ፡ ተቸገረ/ተጨነቀ/ተወጠረ ።
ተወገጠ፡ ተወቀጠ ።
ተወጊ፡ የሚወጋ አገር ("ጠላት") ።
ተወጋ (ተወግአ)፡ ተለተመ/ተሸቀ ሸቀ/ተዘረከተ/ተጠቈመ ።
ተወጋ (ተወግዐ)፡ ተነገረ - ተባለ ወጉ ።
ተወጋ፡ ተጠላ/ተመረዘ/ተነቀፈ ።
ተወጋ፡ ተጻፈ/ተመለከተ ("ምልክት ተደረገበት") ።
ተወጋሪ፡ የሚወገር ("ተደብዳቢ") ።
ተወጋወገ፡ ዋጋ ተነጋገረ ("ውጣ ው ረድ ተባባለ") ። (ተመልከት፡ ወጀወጀን እይ ገና ጀ ይዋ ረሳሉ) ።
ተወጋዥ፡ የሚወገዝ/የሚለይ ።
ተወጋጅ፡ የሚወገድ/የሚርቅ ።
ተወጋገዘ፡ ተገዛዘተ ("ተለያየ") ።
ተወጠረ፡ ተነፋ/ተቀበተተ/ተዘረጋ/ተሳበ/ተለጠጠ/ተገተረ ።
ተወጠረ፡ ተጠየቀ/ተወገጠ ።
ተወጠረ፡ ኰራ/ተቈነነ/ተቋፈ ።
ተወጠነ (ተወጥነ)፡ ተዠመረ/ተፈ ለመ/ተቀደመ/ተሠራ (መዝ. ፻፴፱፡ ፲፭) ።
ተወጠወጠ፡ ተሠራ/ተቈላ/ተጠበሰ/ተቀቀለ/ተማሰለ ።
ተወጠጠ፡ ተወጠረ/ተገተረ ።
ተወጠጠ፡ ኰራ/ታጀረ ።
ተወጣ፡ ሠራ/አደረገ/ወረሰ/ፈጸመ ።
ተወጣ፡ ተወጣበት ("ተኼደ ታለፈ ዳ ገቱ ዐቀበቱ ታረገ ሰማዩ") ።
ተወጣሪ፡ የሚወጥር/የሚለጠጥ ("ተለ ጣጭ የሚኰራ ኵሩ ቀስ ብሎ ኻያጅ") ።
ተወጣኝ፡ የሚወጠን ("ተዠማሪ") ።
ተወጣጠረ፡ ተሳሳበ/ተዘረጋጋ ("ርስ በርሱ") ።
ተወጣጠነ፡ ተዠማመረ/ተፈላለመ ።
ተወጣጣ፡ አንዱ ባንዱ ላይ ወጣ ("ተቀማመጠ ተቀማጭነትን ወይም መቀመ ጫነትን ተፈራረቀ") ።
ተወጣጣ፡ ከዚያም ከዚያም ተሰባሰበ/ተጠራቀመ ("የሰው የገንዘብ") ።
ተወጫመደ፡ ዕጥፍ ዕጥፍ ውትር ው ትር አለ ("ግራና ቀኝ ረገጠ ተውተረተረ") ።
ተዋሐደ፡ አንድ ኾነ ("ከመንታነት ከኹለትነት ራቀ (ሥጋ ለበሰ)") ።
ተዋሓጅ፡ የሚዋሐድ ("አንድ ዃኝ") ።
ተዋሕዶ፡ የሃይማኖት ስም ("የቃልን ሥጋ መልበስና አንድ አካል አንድ ልጅ") ።
ተዋሕዶዎች፡ በተዋሕዶ ሃይማኖት የሚያምኑ ("ደብረ ሊባኖሶች አንኮበሮች ኣዘዞ ዎች ዲሞች ዋልድቦች አኵስሞች ማኅበረ ሥላሴዎች እነዚሁም ቤተ ተክለ ሃይማኖት ናቸው") ።
ተዋለ፡ ቀኑ ታለፈ/ተፈጸመ ("መሸ") ።
ተዋለ፡ ውል ፥ ተደረገ/ታሰረ/ተቋጠረ ።
ተዋለቀ፡ ተሳደበ/ተዋጋ/ተጋደለ ።
ተዋለቀ፡ ተናቀለ/ተፋለሰ ።
ተዋለደ፡ ተራባ/ተዛመደ ("የወንድ ወ ገን ከሴት የሴት ወገን ከወንድ በዘር ተቀ ላቀለ አባትና ልጅ ተኳዃነ") (ሕዝ. ፴፩፡ ፮) ።
ተዋሰ (ተውሕሰ)፡ ዕቃ ወሰደ/ተበ ደረ (፪ ነገ. ፬፡ ፫) ።
ተዋሰ፡ ለሰው ተሰጠ ("ከብቱ ዕቃው በዋስ ኣለዋስ") ።
ተዋሰ፡ ዋስ ኾነ/ተያዘ ("እዋሳለኹ ኣለ") ።
ተዋሰበ፡ ተዋተበ/ተጣለፈ/ተጣመረ/ተሳሰረ ("የድር የገመድ የመጫኛ የሹራብ") ።
ተዋሰነ፡ ወሰን ተራገጠ/ተዳካ/ተካ ለለ/ተላካ ("ተደናገገ ተደናባ") ።
ተዋሰደ፡ ተቃማ/ተናዳ/ተቃረበ ።
ተዋሣ (ተዋሥአ)፡ ተመላለሰ ("መ ልስ ተሰጣጠ") ።
ተዋሳቢ፡ የሚዋሰብ ("ተጣማሪ") ።
ተዋሳኝ (ኞች)፡ የተዋስነ ("የሚዋ ሰን ተካላይ") ።
ተዋረሰ፡ ተያያዘ/ተገናዘበ/ተገናኘ/ተ ቋለፈ ።
ተዋረደ፡ ተሻረ/ከሰረ/ዐጣ/ነጣ ("ባልንጀራው በለጠው ደኸየ ከክብር ከማዕ ርግ ' ወደቀ ከጌትነት ራቀ ጐሰቈለ") ።
ተዋረደ፡ ተዋረሰ ("ደከመ") ።
ተዋረደ፡ ትሑት ኾነ/ታዘዘ ።
ተዋረድ፡ ትሕትናን ገንዘብ አድርግ ።
ተዋረድ፡ ዝቅታ ደረጃ ("በተዋረድ በዝቅታ በላይና በታች") ።
ተዋረፈ፡ ተሳደበ/ተፃረፈ ("ቢዋደዱ ጦም ገደፉ ቢጣሉ ተዋረፉ") ።
ተዋራሽ፡ የሚዋረስ ("ተገናዛቢ") ።
ተዋራጅ፡ የሚዋረድ ።
ተዋራጅ፡ የሚዋረድ ("ታዛዥ ዕሺ ባይ") ።
ተዋርዶ፡ መዋረድ ("ርን ተጭነኸ አን ብብ") (ግእዝ) ።
ተዋርዶ፡ ዝቅ ብሎ (ዐማርኛ) ("ተዋ ርዶ ከማግኘት ኰርቶ ማጣት” እንዲሉ) ።
ተዋሸመ፡ በውሽምነት ተገናኘ ("ል ብስ ተጋፈፈ ተዋደቀ") ።
ተዋሽ፡ ዕቃ የሚወስድ ።
ተዋሽ፡ የሚዋስ ("ዋስ የሚኾን") ።
ተዋቀሠ፡ ተቋጣ/ተከራከረ ("በደል ለበደል ተገላለጠ") ።
ተዋቀረ፡ ተቋጠረ/ተጠረቀ/ተዠመረ ("ጣራው") ።
ተዋቀረ፡ ተናቀሰ/ተጠቃጠቀ/ተጣረበ ።
ተዋቀጠ፡ ተፋተግ/ተቀጣቀጠ/ተማታ/ተደባደበ ።
ተዋቃ፡ ተማታ/ተደባደበ ።
ተዋቃ፡ ተነቃነቀ/ተሳደበ ።
ተዋቃሽ፡ የሚዋቀሥ ("ተከራካሪ") ።
ተዋበ (ተውህበ)፡ ተሰጠ ("ተሰጭ ኾነ") ።
ተዋበ (አደመ ሠነየ)፡ አማረ ፥ ቈ ነዠ (ናሖ. ፫፡ ፬) ።
ተዋበ፡ ኰራ ("አካኼድ አሳመረ በቀ ስታ ኼደ መጣ") ።
ተዋበች (ተውህበት)፡ ለማማር ተ ሰጠች ("ማማር ተሰጣት ዋና ምስጢሩ' ለባል ተሰጠች ማለት ነው") ።
ተዋበች (አደመት ሠነየት ቀደ ወት)፡ የሴት ስም ("አማረች ቈነዠች ምን ትዋብ” እንዲሉ) ። (ተመልከት፡ ምንን) ።
ተዋኔ (ተዋናዪ)፡ የፈላስፋ ስም ("በጐዣም አውራጃ የነበረ ታላቅ ሊቅ ቅኔን የፈጠረ ባሕረ ምስጢሩን ዋኝቶ የመረመረ ! ቁም ነገር ባለው ፍልስፍና ከደቀ መዛሙርቱ ' ጋራ ሲጫወት የኖረ") ።
ተዋኔ/ፈላስፋ፡ ዋኘ ።
ተዋኘ፡ በዋና ተሞከረ/ተደፈረ ("ተወ ሰወሰ የውሃ ምላት") ።
ተዋወቀ (ተዓወቀ)፡ ተላመዱ/ተለ ማመደ ።
ተዋወከ (ተሃወከ)፡ ተበጣበጠ ተተራመሰ ።
ተዋዋለ (ተዋዐለ)፡ በግብር በነገር ተሰማማ ("ይህን ብታደርግ ይህን አደርጋለኹ ተባባለ ተጻጻፈ ተፈራረመ ቃል ኪዳን ተጋባ") ።
ተዋዋሰ፡ ተበዳደረ ዕቃ ተሰጣጠ/ተ ቀባበለ ።
ተዋዋሰ፡ ዋስ ተጠራራ ("ሥራት ገባ ተጋባ") ።
ተዋዋሽ፡ የሚዋዋስ ።
ተዋዋቂ፡ የተዋወቀ/የሚተዋወቅ ።
ተዋዋበ (ተዋሀበ)፡ ውበትን ተሰ ጣጣ ("ተሸጋገነ") ።
ተዋዋይ (ዮች)፡ የተዋዋለ/የሚዋዋል ("ተሰማሚ") ።
ተዋዋጠ፡ ተባላ/ተበላላ/ተሰለቃቀጠ ።
ተዋውዶ/ተዋሕዶ፡ የባላገር ዘዬ ነው ።
ተዋዛ፡ ዋዛ ተናገረ/ተነጋገረ/ተቃ ለደ ("ቈሎ ተጓረሠ") ።
ተዋየ፡ ተጮኸ/ታዘነ/ተቈዘመ/ተለ ቀሰ ("ዋይ ተባለ") ።
ተዋደረ፡ ተጋመደ/ተጣመረ ።
ተዋደቀ፡ ተጣጣለ ("ከድኸነት ጋራ ተዋደቀ ተገዳደመ ተተኛኛ ተነባበረ ተደራረበ ሬሳ በሬሳ ላይ ተኳዃነ") (ዘሌ. ፳፮፡ ፴፯) ።
ተዋደደ፡ ተሰማማ/ተፋቀረ/ተማመነ (ዮሐ. ፲፫፡ ፴፬፡ ሮሜ. ፲፪፡ ፲) ።
ተዋደደ፡ ተሳካ/ተጋጠመ ።
ተዋዳጅ፡ የሚዋደድ ("ተፋቃሪ") ።
ተዋጀ፡ ተገዛ/ተለወጠ ።
ተዋገረ፡ ተማታ/ተደባደበ ።
ተዋገነ፡ ተዛመደ ("ወገን ተኳዃነ") ።
ተዋገዘ፡ ተጋዘተ ።
ተዋገደ፡ ተገባደደ/ተቃለለ ፥ ተቃረበ ("ሥራው") ።
ተዋጊ (ወጊ)፡ ከብትን/ሰውን የሚ ዋጋ ክፉ በሬ (ዘፀ. ፳፩፡ ፳፱, ፴፰) ።
ተዋጊዎች/ተዋጎች፡ ጦረኞች/ሐር በኞች (ዘፀ. ፲፬፡ ፯፡ ዘዳ. ፪፡ ፲፬, ፲፮፡ ኢሳ. ፬፡ ፭) ።
ተዋጋ (ተዋግአ) (ወጋ)፡ ተላተመ/ ተተማተመ/ተዳሰመ ("በቀንድ በጦር በሰይፍ በጠመንዣ ተማታ ተጋጩ ተሸቃሸቀ") (፪ ዜና. ፲፩፡ ፬፡ ፲፯፡ ፲፡ ያዕ. ፬፡ ፪) ።
ተዋጋ (ተዋግዐ)፡ ወግን ተነጋገረ ("ዋጋን ተሳሰበ") ።
ተዋጋ፡ መዝጊያ እንዳይከፈት ከወደ ውስጥ ወግቶ ተደግፎ የሚይዝ አጕራ ።
ተዋጠ፡ ተበላ/ተሰለቀጠ ("እሆድ ገባ") (ኤር. ፴፡ ፲፯፡ ፩ ቆሮ. ፲፭፡ ፶፬) ።
ተዋጠ፡ እባሕር ጠለቀ ("በረግረግ ሠ ረገ ሰጠመ") ።
ተዋጠ፡ ጠብቆ ተነገረ/ተጐረደ/ቀረ ("የፊደል የቀለም") ።
ተዋጠረ፡ ተዘራጋ ።
ተዋጠነ፡ ተዣመረ/ተፋለመ ።
ተዋጣ፡ ተከረ/ተፋተነ/ተባባለ ("የጕ ልበትን ልክ ተዋወቀ") ።
ተዋጣ፡ አማረ/ሰመረ ("ሥራው") ።
ተዋፅኦ፡ መዋጮ፡ ወጣ ።
ተው፡ ዕንክ በሬን ካንድ ነገር ላይ ለመከልከል የሚነገር ቃል ("ዕንካን" ተመልከት) ።
ተው፡ የቅርብ ወንዶችና ሴቶች (በርስዎታም የቅርብ ወንድና ሴት ትእዛዝ አንቀጽ - "ተዪ/ተይ ልቀቂ ጣዪ") ። "ትቶት ጥሎት"።
ተውለቀለቀ፡ የወላለቀ ድርብ ("ተነ ቃቀለ") ።
ተውለበለበ፡ ተወዘወዘ/ተነቀነቀ ("ለፈ ለፈ") ።
ተውለብላቢ፡ የሚውለበለብ ("ሰንደቅ ዐላማ") ።
ተውሳከኛ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ተውሳካም፡ በሽተኛ ("የበሽታ ጐሬ ጤና ቢስ") ።
ተውሳክ፡ ብዙ ዐይነት በሸታ ወረ ርሽኝ ።
ተውሳክ፡ ተጨማሪ ቍጥር ("ለቀንና ለጦም ለበዓል የሚነገር") ።
ተውሶ፡ ዝኒ ከማሁ ("መዋስ ገንዘብ የተውሶ ጠፋ ተጨርሶ ለሩቅ ወንድ ቦዝ አ ንቀጽ ሲኾን እከሌ መሣሪያ ተውሶ አመጣ ይላል") ።
ተውረከረከ፡ ተብረከረከ ።
ተውረገረገ፡ ተረገረገ ።
ተውሸለሸለ፡ ተውተፈተፈ ("ጥብቅነት ዐጣ") ።
ተውተበተበ፡ ተውሸለሸለ/ተውተፈ ተፈ ።
ተውተፈተፈ/ተውሸለሸለ/ተውተበ ተበ፡ ውትፍትፍ ("የተውተፈተፈ ውሽልሽል ውትብትብ የማይረባ ሥራ") ።
ተውዘገዘገ፡ ተምዘገዘገ/ተቅዘመዘመ ።
ተውዠለዠለ፡ ተጐተተ/ተሳበ/ተው ዠመዠመ ።
ተውዠመዠመ፡ ረዘመ ("ተሳበ ተጐ ተተ") ።
ተውጠነጠነ፡ ታሰበ/ተጕላላ ።
ተዘለለ፡ ተበለጠ/ተተወ/ታለፈ ።
ተዘለለ፡ ተዘረረ/ዐረፈ ("ዐሳቡን ጣለ ምን አለብኝ አለ") ።
ተዘለለ፡ ተጠመቀ/ተበጠበጠ/ተቦካ ።
ተዘለለ፡ ተጨፈረ/ተረገደ ።
ተዘለሰ፡ ተቈረጠ/ተመነጠረ/ተኛ/ተጋ ደመ ።
ተዘለቀ፡ ተነበበ/ተወጣ/ታለፈ ("ከንጨት ዕንጨቱ ተጨረሰ መጻፉ") ።
ተዘለነ፡ ጐዦ ነቀለ/ደሳ ጠቀለለ/ስ ፍራ ለቀቀ/ተጐዳኘ/ተዛወረ ።
ተዘለዘለ፡ ተሠነጠቀ/ተሸነሸነ/ቀጠነ/ ረዘመ ።
ተዘለዘለ፡ ተነከሰ/ተዘነተረ ።
ተዘለጐሰ፡ ተዘለለ/ተገደፈ/ተበላሸ ።
ተዘለፈ፡ ተዘለሰ/ዘነበለ ።
ተዘለፈ፡ ተገሠጸ/ተወቀሠ/ተመከረ/ተነቀፈ/ተሰደበ (ዘፍ. ፳፡ ፲፮) ።
ተዘላለቀ፡ ተከራረመ/ተኗኗረ ።
ተዘላሽ፡ የሚዘለስ ።
ተዘላኝ፡ የሚዘለን ("ተዛዋሪ") ።
ተዘላዘለ፡ ተሠናጠቀ/ተሸናሸነ ።
ተዘላዘለ፡ ተናከሰ/ተዘናተረ ።
ተዘላይ፡ የሚዘለል/የሚታለፍ ("ጕድባ ፈረፈር") ።
ተዘልዛይ፡ የሚዘለዘል ።
ተዘመመ፡ ተሠራ ("ገባ ዝማሙ") ።
ተዘመመ፡ ተዘነበለ/ተዜመ/ተባለ ("ተደረገ ዝማሜው") ።
ተዘመመ፡ ተደረደረ/ተጐቹ ተከመረ ("በሞላላው") ።
ተዘመረ፡ ተሠራ/ታረሰ/ታጨደ ።
ተዘመረ፡ ተዜመ/ተመሰገነ/ተዘፈነ ("ተደረደረ ተመታ በገናው") ።
ተዘመተ፡ ተኼደ/ተገሠገሠ ("ተዘረፈ ተቀማ") ።
ተዘመዘመ፡ ተሰፋ/ተጠቀመ/ተቀመ ቀመ/ተጠለፈ/ተጌጠ ።
ተዘመደ፡ ተወለደ/ዘመድ ኾነ/ተወገነ ።
ተዘማመደ፡ ተገነኛኘ/ተያያዘ/ተገና ዘበ ።
ተዘምዛሚ፡ የሚዘመዘም ("ተቀምቃሚ") ።
ተዘምዶ፡ ዝምድና (ግእዝ) ።
ተዘረረ፡ ተዘለለ/ተዘረጋ/ተሰጣ/ተሰተረ ("ተኛ ተጋደመ") ።
ተዘረነቀ፡ ተበላሸ/ተዘባረቀ ።
ተዘረነቀ፡ አያገባው ገባ/ተጨመረ/ተዶለ/ተነከረ ።
ተዘረከተ፡ ተቀደደ/ተዘረገፈ ።
ተዘረከተ፡ ተነፋ ("(ተነፍን)")
።
ተዘረካከተ፡ ተቀዳደደ/ተሸረካከተ ።
ተዘረኰተ፡ ተዘለጐሰ/ተገደፈ/ተጣለ/ ወደቀ/ተዘለለ ።
ተዘረዘረ፡ ተመነዘረ/ተሸረፈ ።
ተዘረዘረ፡ ተሞረደ/ተፈገፈገ/ተሳለ ።
ተዘረዘረ፡ ተሸከሸከ/ተዘከዘከ/ሣሣ/ ተራራቀ ።
ተዘረዘረ፡ ተበተነ/ተለየ ።
ተዘረዘረ፡ ገባ/ተመለሰ ("ፊደሉ") ።
ተዘረገፈ፡ ወጣ/ፈሰሰ ("ስፍራውን ለ ቀቀ") (ሰቈ. ፪፡ ፲፩) ።
ተዘረጋ፡ ተሰተረ/ተሰጣ/ተዘረረ/ተጠፈጠፈ/ሣሣ ("ተጋደመ ተገለጠ ተወጠረ ተነጠፈ") ።
ተዘረጋጋ፡ ተሰታተረ ።
ተዘረጠጠ፡ ተሳበ/ተጐተተ ።
ተዘረጠጠ፡ ተናደ/ፈረሰ ።
ተዘረጠፈ፡ ተሰደበ/ተፀረፈ ።
ተዘረፈ፡ ተወረረ/ተበዘበዘ/ተቀማ/ ተነጠቀ/ተወሰደ ።
ተዘራ (ተዘርዐ)፡ ተበተነ/ ተነሰነሰ/ተሸነ ("ጠብ ጠብ አለ") (ሕዝ. ፴፮፡ ፱ TM ማቴ. ፲፫፡ ፲፱, ፳, ፳፪, ፳፫) ።
ተዘራ (ተዘርወ)፡ ተንቀረቀበ/ተነቀ ነቀ ("ለነፋስ ተሰጠ ተለየ") ።
ተዘራ ወርቅ፡ ዝኒ ከማሁ ("ወርቅ ተፀነሰ ተረገዘ ማለት ነው") ።
ተዘራ፡ የሰው ስም ።
ተዘራረፈ፡ ተቀማማ/ተነጣጠቀ ።
ተዘራከተ፡ ተቃደደ/ተዘራገፈ ።
ተዘራዘረ፡ ተለያየ ("እየብቻ ተኳዃነ") ።
ተዘራዘረ፡ ተረደ/ተፈጋፈገ/ተሳሳለ ።
ተዘራገፈ፡ ተቃደደ/ተሸራከተ/ተዘራ ከተ ።
ተዘራጋ፡ ተሳተረ (ኢዮ. ፫፡ ፲፫) ።
ተዘራጠጠ፡ ተናናደ/ተሳሳበ/ተጓተተ ።
ተዘራፊ፡ የሚዘረፍ ("ተነጣቂ") ።
ተዘርዛሪ፡ የሚዘረዝር ("ዐጋዥ ማጭድ") ።
ተዘርጊ፡ የሚዘረጋ ("ተወጣሪ") ።
ተዘርጋፊ፡ የሚዘረገፍ/የሚወጣ ።
ተዘርጣጭ፡ የሚዘረጠጥ/የሚናድ ("ጕቾ ዘመመን") ።
ተዘቀዘቀ፡ ተቈለቈለ/ፈሰሰ/ተደፋ ("ቍልቍል አመራ ወረደ የሌት ወፍ እንደ ጃን ጥላ ተዘቅዝቃ ትሰቀላለች ትሰፍራለች (ትተኛለች)") ።
ተዘቃዘቀ፡ ቍልቍል ተሳቀለ ።
ተዘቅዛቂ፡ የሚዘቀዘቅ ("ኮከብ ዋነተኛ") ።
ተዘበለለ፡ ታራ/ተኰሳ/ተዘፈዘፈ ።
ተዘበራረቀ፡ ተደበላለቀ/ተዘናነቀ/ተ ቀያየጠ ።
ተዘበተ፡ ተቈለለ/ተከመረ ።
ተዘበተ፡ ተዛተ/ተፎከረ ።
ተዘበተ፡ ኾነ/ተደረገ ("ለግጡ ተዘበተ") ።
ተዘበተረ፡ ተዘነተረ ።
ተዘበዘበ፡ ተነዘነዘ/ተነተረከ/ተቀ ጨቀ ("በዛ ተጐተተ ነገሩ") ።
ተዘበጠረ፡ ተሠባጠረ ።
ተዘባረቀ፡ ተቃወሰ/ተሳሳተ/ተዛወረ ("አለስፍራው ገባ የግራው በቀኝ የቀኙ በግራ የዳሩ በመኻል የመኻሉ በዳር የኋላው በፊት የፊቱ በኋላ ኾነ") ።
ተዘባረቀ፡ ተደባለቀ/ተቀላቀለ ።
ተዘባበተ፡ ተዛዛተ/ተፎካከረ ።
ተዘባዘበ፡ ተነዛነዘ/ተነታረከ/ተጨ ቃጯቀ ።
ተዘተዘተ፡ ተነከሰ/ተበጣጠሰ/ተገተገተ ።
ተዘነቀ፡ ተቀየጠ/ተቀላቀለ/ተደባለቀ ።
ተዘነበለ (ዘነበለ)፡ ተጐነበሰ ።
ተዘነተረ፡ ተነከሰ/ተዘበተረ/ተቦጨቀ/ ተቦተረፈ ።
ተዘነኰረ/ተዘነከረ፡ ተበላሸ ("ፍሬ ፈርስኪ ኾነ") ።
ተዘነኳኰረ፡ ተበለሻሸ ።
ተዘነደበ፡ ረዘመ/ወጣ ።
ተዘነጀረ፡ ታሰረ ("፪ ፍንጅና ጠገግ ባለው እግረ ሙቅ ተገጠመበት") (፪ ሳሙ. ፫፡ ፴፬) ።
ተዘነጋ፡ ተረሳ/ታጣ/ጠፋ ።
ተዘነጋጋ፡ ተረሳሳ/ተጣጣ ።
ተዘነጓጐለ፡ ተለያየ/ተበለሻሸ ።
ተዘነጠለ፡ ተነፋ ወፈረ ("ቦርጭ አወጣ") ።
ተዘነጠለ፡ ተፈነቀለ/ተነደለ ።
ተዘነጠለ፡ አላገባብ ተነበበ ።
ተዘነጠፈ፡ ረዘመ ("ረዥም ኾነ") ።
ተዘነጠፈ፡ ረገፈ/ወረደ (ሐ.፮፡ ፪፡ ፳፪) ።
ተዘነጣጠለ፡ ተበሳሳ/ተቀዳደደ ("ተሸ ረካከተ") ።
ተዘናበለ፡ ተጐናበሰ/ተደናቀፈ/ተጣመመ (ሰቈ. ፬፡ ፲፬) ።
ተዘናተረ፡ ተናከሰ/ተዘባተረ/ተባላ ።
ተዘናነፈ፡ ተበላለጠ ።
ተዘናጐለ (መዝጐለ ተመዝጐለ)፡ ተቃወመ/ተከራከረ ("ስምምነት ዐጣ ተለየ ተበላሸ") ።
ተዘናጠለ፡ ተፈናቀለ/ተቃደደ ("ተዋጋ ተሸራከተ") ።
ተዘናፈለ፡ ተንፈላሰሰ/ተፈረነሰ/ተጋደመ ("ተቈላዘመ ተጐናዘለ ሣሩ ጤፉ መኰንኑ") ።
ተዘንባይ፡ የሚዘነበል ።
ተዘንጎች፡ በትሮች/ምርኵዞች (ዘፀ. ፳፯፡ ፲፩) ።
ተዘንጣይ፡ የሚዘነጠል ("ተቀዳጅ") ።
ተዘከረ (ዘከረ)፡ ዐሰበ/ፈረደ ።
ተዘከረ፡ ለድኻ/ለለማኝ ሰጠ ("ርግጠኛው ግን ተሰጠ ነው") ።
ተዘከረ፡ ተጸለየ/ተባረከ/ተቈረሰ ።
ተዘከዘከ፡ ተነቀነቀ/ተሰነገ ።
ተዘከዘከ፡ ተነከሰ/ተበላ/ተቦተረፈ ።
ተዘከዘከ፡ ተዘረዘረ/ተሸከሸከተ/ተቀደደ ።
ተዘከዘከ፡ ተዘቀዘቀ/ተዘረገፈ/ወጣ/ ፈሰሰ ።
ተዘካሪ፡ የሚዘከር/ሰጪ ።
ተዘካዘከ፡ ተዘራዘረ/ተሸካሸከ/ተቃደደ ።
ተዘካዘከ፡ ተዘራገፈ/ተዋጣ ።
ተዘክሮ፡ ማሰብ ።
ተዘክሮ፡ ዐስቦ ሰጥቶ (ዐማርኛ) ።
ተዘወረ፡ መዘውር ኾነ/ዞረ/ተጠመዘዘ ።
ተዘወተረ፡ ዘወትር ተሠራ/ኾነ/ተደ ረገ ።
ተዘዋተረ፡ ተዘወታተረ፡ ተመላለሰ፡ ነገሩ፡ ጕዳዩ ።
ተዘዋተረ/ተዘወታተረ፡ ተመላለሰ ነገሩ/ጕዳዩ ።
ተዘዋወረ፡ ተዟዟረ/ተጠማዘዘ ("መዘውር ተኳዃነ ተለዋወጠ ተቀያየረ") ።
ተዘዋዋሪ፡ የሚዘዋወር ("ተጠማዛዥ ተ ላላፊ መኪና በሽታ") ።
ተዘውታሪ፡ የሚዘወተር ።
ተዘውታሪ፡ የሚዘወተር ። ዝውትር፡ የተዘወተረ ።
ተዘዘ፡ ተመናቸከ።
ተዘዘ፡ ተመናቸከ።
ተዘዘ፡ ታሰበ ታወሰ ። በትግሪኛ ግን "ዘነበለ" ማለት ነው ።
ተዘየረ፡ ተጐበኘ/ተደረሰ/ሰላም ተባለ ("ምስጋና ተቀበለ") ።
ተዘየነ፡ ተሸለመ/ተጌጠ ።
ተዘገበ፡ ተሰበሰበ/ተጠራቀመ/ተከማቸ ።
ተዘገነ፡ ተጠረኘ ("ጥርኝ ኾነ ተቃመ") ።
ተዘገጃጀ፡ ተደረጃጀ/ተሰነዳዳ/ተቀነ ባበረ ።
ተዘጊ፡ የሚዘጋ/የሚገጠም ።
ተዘጋ፡ በተዘጋ ቤት ተቀመጠ ("በውስጥ ኾነ") (ሕዝ. ፫፡ ፳፬) ።
ተዘጋ፡ ተገጠመ/ተከደነ/ተደፈነ ("ል ክክ እለ ወለነ") (፬ ነገ. ፮፡ ፴፬፡ ኢሳ. ፳፬፡ ፪, ፲) ።
ተዘጋቢ፡ የሚዘገብ ("ደላቢ") ።
ተዘጋጀ (ተዘጋደየ)፡ ተደራጀ/ተ ሰናዳ/ተበጃጀ/ተቀናበረ (ተደራጊ) ።
ተዘጋጋ፡ ተገጣጠመ/ተደፋፈነ ።
ተዘጠረ፡ ምሉ ኾነ ("ተነፋ ተወጠረ ዐ በጠ") ።
ተዘጠነ፡ ዘጠኝ ኾነ ("ተባለ") ።
ተዘጠነ፡ ዘጠኝ፡ ኾነ፡ ተባለ ። ዝጥን፡ የተዘጠነ፡ ዘጠኝ፡ የኾነ ። አዘጣጠን፡ ዝጠና፡ መዘጠን ። ዘጠረ፡ (ዘተረ)፡ ውሃና፡ ጨው፡ ሞጀረ፡ ኣበዛ፡ መላ፡ ነፋ፡ ወጠረ፡ ሆድን ።
ተዘፈቀ፡ ተደፈቀ/ተነከረ/ጠለቀ/ሰ ጠመ ።
ተዘፈነ፡ ተዜመ/ተገጠመ/ተዘለለ/ተጨፈረ ("ተጨበጨበ (አንዳንድ ጊዜ በዋልድባ ይዘፈናል) ዐዳኞች ዝኆንና አንበሳ ገዳዮች ባጠገቡ ይዘፍኑበታል") ።
ተዘፈዘፈ፡ ተነከረ/ራሰ ።
ተዘፈዘፈ፡ ታራ/ተወዘፈ ።
ተዚያ (ከዚያ)፡ ተዚያ ወዲያ በቂ ።
ተዚያ፡ ከዚያ፡ ዚያ ።
ተዚያዚያመ፡ ተጯጯኸ/ተቀባበለ ።
ተዛለለ፡ ተላለፈ/ተረማመደ ።
ተዛለለ፡ ተናናረ/ተፈረ/ተጨፋፈረ ።
ተዛለለ፡ ተገተ/ተከራከረ ("እሰጥ አ ገባ ተባባለ ተሯከረ ተወዳደረ") ።
ተዛለቀ፡ ተካረመ/ተቻቻለ ("ዐብሮ ኖረ") ።
ተዛለፈ፡ ተናቀፈ/ተሳደበ ።
ተዛመተ፡ ተላለፈ/ተዋራ ።
ተዛመደ፡ ተቀላቀለ/ተዋሐደ/ተዋለደ/ተዋገነ ("ዘመድ ተኳዃነ ጡት ተጣባ") (ነሐ. ፲፫፡ ፬) ።
ተዛረፈ፡ ቅኔ ተነጋገረ/ተመላለሰ ("እንደ ዕቡይ ካሳና እንደ አለቃ ዶሪ") ።
ተዛረፈ፡ ተበዛበዘ/ተቃማ/ተናጠቀ ።
ተዛረፈ፡ ዘርፍ ተኳዃነ/ተያያዘ/ተና ተዛረፈ ።
ተዛራ፡ ተፋሰሰ/ተለያየ ።
ተዛቀ፡ ተጠረገ/ተጋፈ/ተሰበሰበ/ተ ተዛቂ ("የሚዛቅ የሚጠረግ ቦይ") ።
ተዛበተ፡ ተቃለደ/ተዋዛ ።
ተዛበተ፡ ተፋከረ ።
ተዛባ፡ ተላመጠ ("ተቃወሰ ተሳሳተ የነገር") ።
ተዛተ፡ ኾነ/ተደረገ/ተነገረ ("ዛቻው ተፎከረ") ።
ተዛነቀ፡ ተቃየጠ/ተሠባጠረ/ተደባለቀ ።
ተዛነበ፡ ተፋሰሰ/ተራጩ ።
ተዛነብ፡ ተፋሰስ ("መዛነቢያ") (ሕዝ. ፵፡ ፳፪) ።
ተዛነፈ፡ ተባለጠ/ተራዘመ ።
ተዛነፍ፡ የተዛነፈ/የተባለጠ ("ዝንፋት ተዛነፍ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ እንቀጽ ተባለጥ") ።
ተዛና (ተዝያነወ)፡ ተዳራተጫወተ/ ተቃበጠ ።
ተዛና፡ ተሸራሸ/ተደላደለ/ተመቻቸ ።
ተዛናፊ፡ የሚዛነፍ/የሚባለጥ ።
ተዛወረ፡ ተላለፈ/ተላወጠ/ተቃየረ ሥ ራን/ስፍራን ።
ተዛወረ፡ ተገለበጠ/ተጋባ ("በሽታው ዕ ቃው") ።
ተዛወቀ፡ ተዛነቀ/ተዘባረቀ/ተሳሳተ ።
ተዛዋሪ፡ የሚዛወር ።
ተዛዘለ (ተሐዘለ)፡ ተሸካከመ/ተደ ራረበ/ተነባበረ ("የሸክም ሸክም ተኳዃነ ") ።
ተዛዘለ፡ ግራና ቀኝ ተባለ/ተነገረ (ተፈራረቀ ተመላለሰ - ዳዊቱ ዜማው ") ።
ተዛዘበ (ተሓዘበ)፡ ተገናዘበ/ተገ ነዛዘበ/ተጠላለፈ ።
ተዛዘበ፡ በትዝብት ተያየ (ተጠራጠረ ተናናቀ ተነቃቀፈ ") ።
ተዛዘነ (ተሐዘነ)፡ ተላቀሰ/ተወያየ/ ተራረፈ/ተረዳዳ/ተካፈለ/ተዳረሰ ("አባት ልጆ ቹን ተዛዝናችኹ ብሉ" እንዲል) ።
ተዛዘነ፡ ተከፋፋ ("(ያዕ. ፭፥፱)") ።
ተዛዘዘ፡ (ተኣዘዘ)፡ የማዘዝ፡ ብድር፡ ተመላለሰ፡ ርስ፡ በርሱ።
ተዛዛተ፡ ተፋከረ/ተዘባበተ/ተወዳደረ ("በጠብ ተነጋገረ አንተ አንተ ተባባለ") ።
ተዛዛኝ፡ የተዛዘነ/የሚተዛዘን (የሚረ ዳዳ ያገኘውን ተካፍሎ የሚበላ ") ።
ተዛዛይ፡ የሚተዛዘል (አንበጣ ፌንጣ የመሰለው ኹሉ ") ።
ተዛገመ/ተዘጋገመ፡ ተጓጓዘ ።
ተዛጋ፡ ተወራኘ/ተቃረበ/ተጣበበ/ተ ጋጠመ ("ተማማለ") ።
ተዛፈቀ፡ ተዳፈቀ/ተሳጠመ ።
ተዜመ፡ በዜማ ተባለ/ተነገረ/ተቃኘ/ተዘመረ/ተቀደሰ/ተወደሰ ።
ተዝለሰለሰ፡ ተዝለፈለፈ/ተቅለሰለሰ/ ተ ለሸለሸ ።
ተዝለገለገ፡ ተምለገለገ/ተሳበ/ተጐተተ ("የለሐጭ ተንሸራተተ የእባብ") ።
ተዝለፈለፈ፡ ተጥመለመለ/ደከመ ("ባለ አልነሣ አለ ተስለመለመ") ።
ተዝረ (ተገዝረ)፡ ተገረዘ/ተቈረጠ/ተቀነጠበ ።
ተዝረበረበ፡ ተንጠባጠበ/ተዝረከረከ ።
ተዝረከረከ፡ ልብሱንና ሰውነቱን አልሰበስብ አለ ("ከርጅና ከሞኝነት የተነሣ") ።
ተዝረከረከ፡ በብዙ ስፍራ ተወራ ።
ተዝረከረከ፡ ተዝረፈረፈ/ተጣለ/ወደቀ/ተገደፈ ።
ተዝረጠረጠ፡ ተዝረከረከ ወደ ኋላ ቀረ ።
ተዝረፈረፈ፡ ተዝረከረከ/ወደቀ/ተቈናዘለ ("የሣር የጠጕር") (ማሕ. ፭፡ ፲፩) ።
ተዝበደበደ፡ ፈራ/ተርበደበደ ።
ተዝቦቀቦቀ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ተዝቦጠቦጠ፡ ተበጠበጠ/ተደባለቀ/ተቀላቀለ ("ወፈረ") ።
ተዝናና፡ ብዙ ተናገረ/ተቅበጠበጠ ።
ተዝካረ በቀል፡ የበቀል መታሰቢያ ("በጦርነት ለሞቱ ሰዎች የተሠራ ሐውልት ፈረንጆች ሞኒማ ይሉታል") ።
ተዝካር (ሮች)፡ የሞተ መታሰቢያ ድግስ ("ሰው በሞተበት ቀን በያመቱ የሚ በላና የሚጠጣ") ።
ተዝካር አወጣ፡ የሞተ ስም አስጠራ ("አስቈረበ ለካህናት አበላ አጠጣ ለ ድኾች መጸወተ") ።
ተዞረ፡ ተከበበ/በዙሪያ ተኼደ/ታ ወደ ("ዑደት ተደረገበት ቤተ ክሲያኑ ድምሩ") ።
ተዟዟረ፡ ዙረትን ተመላለሰ ("ተላለፈ") ።
ተዠለጠ፡ ተረገጠ/ለፋ ("ተዘቀዘቀ") ።
ተዠመረ፡ ተወጠነ/ተፈለመ/ ተቀደመ ።
ተዠመገገ፡ ተሸመጠጠ/ተዠረገገ/ተ ሳበ/ተጐተተ ።
ተዠማመረ፡ ተወጣጠነ/ተፈላለመ ።
ተዠማሪ፡ የሚዠመር ("ተፈላሚ") ።
ተዠረገደ፡ ረዘሙ/ቁመታም ኾነ ።
ተዠረገደ፡ ተመታ/ተደበደበ ።
ተዠረገደ፡ ተወለደ/ተፈለፈለ ።
ተዠረገገ፡ ተዠመገገ/ተበጠሰ ።
ተዠነቀ፡ ተጨመረ/ገባ ።
ተዠነጠፈ፡ ተቈረጠ/ተዠመገገ ።
ተዠገደ፡ ተማገደ/ተሞጀረ ።
ተዣመረ፡ ተዋጠነ/ተፋለመ ።
ተዥበረበረ፡ ተንጸባረቀ/ተጥበረበረ ("ቅር ግር አለው") ።
ተዥገረገረ፡ ዥግራ መሰለ/ጠቃጠቆ ኾነ ("ተንከባለለ ነጩና ጥቍሩ ታየ ነገር") ።
ተዥጐረጐረ፡ ነብር መሰለ/ነጣ/ጠ ቈረ ("የዝናም የደመና") ።
ተዥጐደጐደ፡ በዝቶ መጣ/ገባ ("ዠደድ አለ ተነቀ") ።
ተየከሰ፡ ተጠየቀ ።
ተየካሽ፡ የተየከሰ ("ተጠያቂ ለጉባኤውም ለተየካሹ ምነው ቢገቡ ኾነ ምላሹ") (ኪ. ወ. ክ) ።
ተያዘ (ተእኅዘ)፡ ተጨበጠ/ተገታ ።
ተያዘ፡ ተዋሰ ("በጐደለ እመላለኹ በጠፋ እተካለኹ አለ (ቤቱ ተያዘ) በዳኛ እጅ ኾነ") ።
ተያዘ፡ እወጥመድ ገባ ።
ተያዡ፡ የሚያዘው ("የርሱ ተያዥ ያ ተያዥ") ።
ተያዢ/ዥ (ዦች)፡ የሚያዝ/የሚ ጨበጥ ("ዋስ መድን ኀላፊ ተጠያቂ") ።
ተያዥ ኾነ፡ መድን ኾነ ("ተዳነ") ።
ተያዥነት፡ ተያዥ መኾን ("ዋስትና") ።
ተያዧ፡ የርሷ ተያዥ ("ያች ተያዥ") ።
ተያየ፡ (ተራአየ)፡ ተነጻጸረ፡ አኳያ ላኳያ ተኳዃነ፡ ተፋዘዘ፡ (ዘፀ፳፭፡ ፳)። እባብን ተመልከት ።
ተያያዘ (ተኣኀዘ)፡ ተጣመረ/ተቈላ ለፈ/ተጣበቀ/ተቀጣጠለ/ነደደ/ተጣላ ("ግብ ግብ አለ ታገለ ተናነቀ") (ማቴ. ፲፭፡ ፲፬) ።
ተያያዥ፡ የሚያያዝ/የሚታገል።
ተይዟል፡ ለሰው ተረክቧል ("ዕቃው ገንዘቡ ቤቱ ተያዥ ኹኗል ዋሱ") ።
ተይዟል፡ በጠና ታል
ተደለለ፡ ተሞኘ/ተታለለ/ተሸነገለ ("ከቍጣ ተመለሰ ላይ") ።
ተደለሰ፡ ተላከከ/ተመረገ/ተቀባ ።
ተደለቀ፡ ተመታ/ተደሰቀ/ተጐሰመ ።
ተደለቀ፡ ተቈነነ ("በቀስታ ኼደ") ።
ተደለኸ፡ ተወቀጠ/ተደለዘ/ተፈጨ/ላመ/ላቈጠ/ተለወሰ ፥ ተዘጋጀ ።
ተደለዘ፡ ተመረገ፡ ተቀባ/ሰነ፡ ተለቀለቀ፡ ተቀላቀለ።
ተደለዘ፡ ተመረገ/ተበየደ/ተደፈነ ።
ተደለዘ፡ ተወቀጠ/ተወገጠ ።
ተደለደለ፡ ተመላ ' ተጨመረ/ትክ ክል ኾነ ።
ተደለደለ፡ ተከፈለ/ተመደበ ("ምድር ሲደለደል ለማሳ ሲታል” እንዲሉ) ።
ተደለደለ፡ ተገደበ/ታገደ/ተከተረ ።
ተደለደለ፡ ዐበጠ/ተቀበጠጠ ።
ተደለፈሰ፡ ተዛቀ/ተሰረረ ።
ተደላ (ደላ)፡ ጠመመ/ጐደለ ብይኑ ።
ተደላለስ፡ ተቀባባ ።
ተደላቂ፡ የሚደለቅ ("ተቈናኝ") ።
ተደላይ፡ የሚደለል ("ተሸንጋይ ተታ") ።
ተደላደለ፡ ተተካከለ/ቆመ/ተመቻቸ/ጌተየ/ተሰማማ/ተካፈለ ።
ተደላዳይ፡ የሚደላደል/የሚመቻች ።
ተደልዳይ፡ የሚደለደል ("ተከታሪ") ።
ተደመመ፡ ተቀበረ/ተደፈነ/ተስጣጣ ።
ተደመመ፡ ተደነቀ/ተገረመ ("ዝም አለ") ።
ተደመመን፡ አደነቀ ("ማለት ልማዳዊ ስሕተት ነው") ።
ተደመሙ፡ አደነቀ/አነከረ ።
ተደመሰሰ፡ ተፋቀ/ተፈገፈገ/ጠፋ/ተ በላሸ ("እንዳልነበረ ኾነ") ።
ተደመረ፡ ተሰበሰበ/ታከበ/ተከማቸ/አንድነት ኾነ/ተደረገ/ቆመ/ተጠመጠመ ።
ተደመደመ፡ ተረገጠ/ተተካከለ ።
ተደመደመ፡ ተጨረሰ/ተፈጸመ/ተቈ ረጠ ።
ተደመደመ፡ ደነዘ/ዶለዶመ ።
ተደመጠ (ደምፀ)፡ ተሰማ ("እዦሮ ገባ") ።
ተደማመጠ፡ ተሰማማ ("ድምጥ ተቀ") ።
ተደማሚ፡ የሚደመም ("ተደፋኝ") ።
ተደማሪ፡ የሚደመር ("ዝርዝር አኃዝ") ።
ተደማደመ፡ ውስጥ ለውስጥ አሤረ ዐድማ አደረገ ("በሰውር መከረ ተመሳጠረ ተሞዳሞደ ሰው አይስማ ተባባለ") ።
ተደማጭ፡ የሚደመጥ ("ተሰሚ") ።
ተደምሳሽ፡ የሚደመሰስ ("ጠፊ") ።
ተደምዳሚ፡ የሚደመደም ።
ተደሞ፡ መደነቅ/ማድነቅ ።
ተደሰመ፡ ተገጨ/ተለተመ/ተተመተመ ።
ተደሰመ፡ ታጠረ/ተዘጋ/ተደፈነ ።
ተደሰቀ፡ ተመታ/ተደቃ ።
ተደሰተ፡ ተድላ ደስታ አደረገ ("ፈነ ደቀ") ።
ተደሳች፡ የሚደሰት ።
ተደረመሰ፡ ተደረባ/ፈረሰ/ተናደ/ወደቀ/ሠረገ ።
ተደረሰ፡ ተቀረበ/ተነካ ።
ተደረሰ፡ ተነገረ/ተባለ ("ስብከቱ ድ ርሰቱ") ።
ተደረሰበት፡ ተለጠቀ ።
ተደረበ፡ ተካበ/ተጨመረ/ተጫነ/ዐበረ/ገጠሙ/አንድ ኾነ (፬ነገ. ፩፡ ፩) ።
ተደረበ፡ ተዳበለ ("የታቦት") ።
ተደረባ፡ ተናደ/ተንሸራተተ/ወረደ/ወደቀ/ተወረወረ ።
ተደረተ፡ ተደበደበ/ተጠቃቀመ ("እንደ ደረት ኾነ") ።
ተደረነቀ፡ ታመቀ/ተረጠጠ ።
ተደረዘ፡ ደርዝ ኹኖ ተሰፋ/ተለጐመ ።
ተደረደረ፡ ተመታ በገናው (ሆሴ. ፲፪፡ ፲፩) ።
ተደረደረ፡ ተሰደረ/ተኰለኰለ/ተደከነ ("ደንጊያው ነዶው") ።
ተደረደረ፡ ተራ መታ ("ተሰለፈ ሰዉ") ።
ተደረጃጀ፡ ተዘገጃጀ/ተቀነባበረ/ተሰ ነዳዳ ።
ተደረገ (ተገብረ)፡ ተሠራ/ተበጀ/ኾነ/ተከወነ/ተፈጸመ (ሉቃ. ፭፡ ፲፪) ።
ተደረገመ፡ ገባ/ተጠረቀመ ("እሾኹ") ።
ተደረገመ፡ ጠፋ/ወደመ ("ዐይኑ መብ ራቱ") ።
ተደረጠ፡ ተበጠበጠ/ታወከ/ተነቀ ነቀ ።
ተደረጠ፡ ታሸ/ተመታ ።
ተደራ፡ ተሰበቀ/ተነቀነቀ ።
ተደራ፡ ተተረተረ/ተዘረጋ ("ድር ኾነ ከዚህ እስከ ደራ አንዠትኸ ይደራ” እንዲሉ ልጆች) ።
ተደራሰመ፡ ተገራሰመ/ተደናበረ/ተ ደናቀፈ ።
ተደራረሰ፡ ተቀራረበ/ተነካካ ።
ተደራረበ፡ ተነባበረ/ተለባበስ/ተጣ ነባባሪ ።
ተደራረገ፡ ተሠራራ/ተበጃጀ/ተኳዃነ ።
ተደራረገ፡ ድርጎ ተሰጣጠ/ተቀባበለ/ተለዋወጠ ("አንተ ይኸን ውሰድ እኔ ያንን እወስዳለኹ ተባባለ") ።
ተደራራቢ፡ የሚደራረብ ("ተነባባሪ") ።
ተደራራጊ፡ ፩ኛ ዐምድ ("ተሳሳቢ አን ቀጽ ተጋደለ ተገዳደለ የሚደራረግ ፪ አካል ተጋዳይ ተገዳዳይ") ።
ተደራራጊ አደራራጊ ፥ አንቀጾች (ወይም ግሶች ") ።
ተደራራጊ፡ የሚደራረግ/የሚሠራራ ።
ተደራቢ (ዎች)፡ የሚደረብ ("ዐባሪ ተጨማሪ") ።
ተደራች፡ የሚደረት ("ዐዲስ ወይም አ ሮጌ ሸማ") ።
ተደራደረ፡ ተሰማማ/ተዋዋለ ("ለመታ ረቅ") ።
ተደራደረ፡ ተሳደረ/ተኰላኰለ ።
ተደራጀ፡ ተዘጋጀ/ተቀናበረ/ተደገሰ/ተሰናዳ ("ተደራጊ") ።
ተደራገመ፡ ጕንጭን ተማታ/ተጣፋ ።
ተደራጊ፡ ፫ኛ ዐምድ ("ተሳቢ አንቀጽ ተገደለ ተሠሪ አካል ተገዳይ") ።
ተደራጊ፡ የሚደረግ/የሚሠራ ።
ተደራጊነት፡ ተሠሪነት/ብጁነት ።
ተደርዳሪ፡ የሚደረደር ("ተሰዳሪ ተኰል ኳይ") ።
ተደርዳሪ፡ የተንቤን ሽብሽቦ ("በዝናር ላይ የተሰፋ የጥይት ቤት") ።
ተደርጎ፡ ተሠርቶ/ኹኖ ።
ተደቀለ/ተዴቀለ፡ ተወለደ ("ዲቃላ ኾነ") ።
ተደቀቀ (ደቀቀ)፡ ኢሳይያስ ፶፫፡ ቍ፭ "ደቀቀ" በማለት ፈንታ "ስለ ኀጢአታችን ተደቀቀ" ይላልና ስሕተት ነው ። "ደቀቀ ዐጕል ግስ ስለ ኾነ ተደቀቀን አይሻም።"
ተደቀነ፡ ቀረበ/ተጠጋ/ተቋተ/ተደ ከረ ።
ተደቀደቀ፡ ተወቀጠ/ተወጋ/ተጠቀጠቀ/ተጠረገ/ተወለወለ/ተከረና ።
ተደቂ፡ የሚደቃ ("መሬት ዠርባ") ።
ተደቃ፡ ተመታ/ተወጋ ።
ተደቃኝ፡ የሚደቀን ("ተደካሪ") ።
ተደቈሰ፡ ተመታ/ተዳመጠ ።
ተደቈሰ፡ ተፈጨ/ደቀቀ/ላመ/ለዘበ ።
ተደቅዳቂ፡ የሚደቀደቅ ("ጠመንዣ") ።
ተደቋሽ፡ የሚደቈስ ("ላሚ ለዛቢ") ።
ተደበለ፡ ተጨመረ/ተደረበ/ተሸረበ/ተጠሞረ ።
ተደበሰ፡ ተጐበጐሰ/ተቀላቀለ ።
ተደበረ፡ ደብር ኾነ/ተገደመ/ከበረ/በለጠ ("ሳታትና መወድስ ተቆመበት ካመት እስካመት ተቀደሰበት") ።
ተደበቀ፡ ተከተተ/ተሸጐጠ/ታባ/ተ ሰወረ/ተሸሸገ ።
ተደበበ፡ ተሠራ/ተበጀ/ተዘረጋ/ተወ ጠረ/ተገተረ/ጠየመ ።
ተደበተ፡ ተጨቈነ ("እንቅልፍ ተጫነው ደበተው") ።
ተደበተረ፡ ተዘረጋ/ተጻፈ ("እደብተር ገባ ደብተራ ኾነ") ።
ተደባሪ፡ የሚደብር (ደብር የሚኾን) ።
ተደባቂ፡ የሚደበቅ (ተሸሻጊ) ።
ተደባበቀ፡ ተሰዋወረ ።
ተደባቢ፡ የሚደገብ (ተወጣሪ) ።
ተደባየ፡ ተረገጠ ("በደባያት ሞተ።") ።
ተደነሰ፡ ተዘለለ/ተጨፈረ ("ኾነ ተደ ረገ ዳንሱ") ።
ተደነሰረ፡ ተሸራሸ/ተመቻችቶ ቍጭ ።
ተደነቀ (አደነቀ)፡ አነከረ (ኤር. ፬፡ ፱፡ ዕን. ፩፡ ፭፡ ማቴ. ፰፡ ፲) ።
ተደነቀ (ደነቀ)፡ ድንቅ ኾነ ("ዕጹብ ተባለ ተገረመ ተደመመ ነገሩ ሰዉ") ።
ተደነቀረ፡ ቆመ/ተሸጐረ/ተቀረቀረ/ተ ደገፈ/ተለገደ/ተጋረጠ/ተተከለ/ተሰካ ገባ ። "አንድ ሰው በጨለማ ሲኼድ በውስጥ እግሩ እሾኸ ተደነቀረበት" ።
ተደነቀፈ፡ ተወለከፈ ("ሰንካላ ኾነ") ።
ተደነቃቀፈ፡ ተሰነካከለ/ተወለካከፈ ።
ተደነቈለ፡ ተጠነቈለ/ተወጋ/ተዛቀ/ተነቈረ ።
ተደነበቀ፡ ተቀዳ/ተጠለቀ ።
ተደነባ፡ ታነጸ/ተጠረበ ።
ተደነባ፡ ታገገ/ተወሰነ/ታወጀ ።
ተደነባበረ፡ ተለካካ/ተወሳሰነ ።
ተደነባበረ፡ ተወነባበረ/ተወነባበደ ።
ተደነከረ፡ ተዘለለ/ተረገደ ።
ተደነጀ፡ ተደነገገ/ተወሰነ ።
ተደነገለ፡ ተጠበቀ ("ድንግል ኾነ") ።
ተደነገገ፡ ተሠራ/ተወሰነ/ተደነባ/ታ ገገ/ተጠነቀቀ ።
ተደነጋገረ፡ ተሳሳተ/ተረሳሳ ።
ተደነጋገገ፡ ተወሳሰነ ።
ተደነጐረ፡ ተደደቀ/ተቈፈረ/ተፈነቀለ/ተገለበጠ ።
ተደነፋ፡ ተዘለለ/ተጨፈረ/ተፎከረ ("ዘራፍ ያንተ ኣሽከር ተባለ") ።
ተደነፋፋ፡ ተፎካከረ ።
ተደናቀፈ፡ ተወላከፈ/ተሰናከለ ።
ተደናቂ፡ የሚደነቅ ።
ተደናቈለ፡ ተዘናቈለ/ተናቈረ ።
ተደናቈረ፡ ነገር ለነገር ሳይዳመጥ ቀረ ("ተጯጯኸ ተለፋለፈ") ።
ተደናበረ፡ ተዋሰነ/ተዳካ ።
ተደናበረ፡ ተጠናበረ/ቀኝና ግራ ረ ገጠ ("ተሳሳተ በደ") ።
ተደናነቀ፡ ተገራረመ ("ጕድ ተሠኛኘ ተባባለ እንደ አቢብና እንደ እንጦንስ") ።
ተደናከረ (ተደናገረ)፡ ተወላገደ/ተ ደናቀፈ ።
ተደናገረ፡ ተሳተ/ታጣ/ተረሳ ።
ተደናገገ፡ ተዋሰነ ።
ተደናገጠ፡ ተፋራ/ተዛዘነ ።
ተደናፋ፡ ተፋከረ ።
ተደንጋጊ፡ የሚደነገግ ("ተወሳኝ") ።
ተደንጓሪ፡ የሚደነጐር ("ተደዳቂ") ።
ተደከመ፡ ተጣረ/ተለፋ ("ተሠራ ሥራው ኾነ ተደረገ ድካሙ ይህ ሥራ እጅግ ተደክሞበታል") ።
ተደከረ፡ ተደቀነ/ተገተረ/ቆመ/ቀረበ ("ተሰለፈ") ።
ተደከነ፡ ተሰደረ/ተደረደረ/ተነባበረ/ተደራረበ ።
ተደካ፡ ተለካ/ተረገጠ/ተወሰነ ።
ተደካሪ፡ የሚደከር (ተደቃኝ) ።
ተደወለ፡ ተቃጨለ/ተመታ/ተጠዘለ/ተመደወተ ።
ተደወረ፡ ዞረ/ተዘወረ/ተጠነጠነ/ተ ጠቀለለ ።
ተደዋሪ፡ የሚደወር ግራ ።
ተደዋይ፡ የሚደወል (ተመቺ) ።
ተደዘደዘ፡ ተመታ/ተጠዘለ ።
ተደገለ፡ ተቀየመ ።
ተደገለለ፡ ተጠቀለለ/ተጠመጠመ/ታ ።
ተደገመ፡ ተነበበ/ተጸለየ/ተመለሰ ።
ተደገመ፡ ታከለ/ተጨመረ ።
ተደገሰ፡ ተቈላ/ተፈጨ/ተዘጋጀ/ተደ ራጀ/ተሰናዳ/ተቀናበረ/ተጠመቀ/ተጋገረ ።
ተደገነ፡ ጐበጠ/ታሰረ/ተዘጋጀ/ተቀ ሰተ/ተቀሠፈ/ተደከረ ("ጐረሠ ታለበ") ።
ተደገደገ፡ ታሰረ/ተሸነፈጠ/ዞረ/ተጠ መጠመ/ተቦደነ ።
ተደገገ፡ ባነጋገር ታበየ/ኰራ/ታጀረ/ተገደረ ("አንተ እኔን ኣታኸለኝም ኣል ጡር መስቃ ተናገረ") ።
ተደገፈ፡ ታቀበ/ተያዘ/ተጠጋ/ተመ ረኰዘ/ተንተራሰ (ኢሳ. ፴፩፡ ፫) ። "መጽሐፍ ግን በተደገፈ ፈንታ ተገደፈ ይላል ስሕተት ነው" (ዮሐ. ፲፫፡ ፳፭) ።
ተደጋሽ፡ የሚደገስ/የሚዘጋጅ ።
ተደጋደገ፡ ተበሳቈለ/ተለዋወጠ/ተጣ ቈረ ።
ተደጋገመ፡ ተናበበ/ተመላለሰ ።
ተደጋገፈ፡ ተያያዘ/ተጠጋጋ/ተጋጠመ/ተቃረበ/ተቀራረበ ።
ተደጋጊ፡ የሚደገግ (ኵሩ ሰው ናቂ) ።
ተደጋጋፊ (ፎች)፡ የሚደጋገፍ ("ተከ ታትሎ ች") ።
ተደጋፊ፡ የሚደገፍ (ተመርኳዥ) ።
ተደጐመ፡ ታገዘ/ተረዳ/ተደገፈ ("ኣገኘ ተቀበለ") ።
ተደጐሰ፡ ነት ለበሰ/ተጌጠ/ተሸለመ ።
ተደጓሽ፡ የሚደጐስ/የሚሸለም ።
ተደፈረ፡ በዛ/ተቈለለ ። "ምርቱ ተደ ፍሯል" እንዲሉ ።
ተደፈረ፡ ተሰደበ/ተነጠበ/ተናቀ/ተዋ ረደ ።
ተደፈረ፡ ተነካ/ተደረሰበት ።
ተደፈቀ፡ ተዘፈቀ/ተነከረ/ገባ ።
ተደፈቀ፡ ተዳጠ/ተፈጪ/ላመ ።
ተደፈነ፡ ተቀበረ/ተመረገ/ተጠቀጠቀ ።
ተደፈደፈ፡ ተለጠፈ/ተቀባ/ተመረገ ።
ተደፈደፈ፡ ታሸ/ተለወሰ ("ድፍድፍ ኾነ") ።
ተደፈጠ፡ ተሰካ/ተዋደደ ("መደፈጫው ደፋጣ ዶባቃ ስፍራ") ።
ተደፈጠ፡ ተሸመቀ ("ኾነ ተደረገ ደፈ") ።
ተደፈጠጠ፡ ተረገጠ/ተዳመጠ/ተወ ቈነ ("ዐዳ ኾነ") ።
ተደፊ፡ የሚደፋ ("ተከንባይ") ።
ተደፋ፡ ባፍ ጢሙ በግንባሩ ወደቀ ።
ተደፋ፡ ፈሰሰ/ተገለበጠ/ተዘቀዘቀ/ተዘረገፈ/ተጋገረ ።
ተደፋሪ፡ የሚደፈር ።
ተደፋቂ፡ የሚደፈቅ ።
ተደፋኝ፡ የሚደፈን ("ተመራጊ") ።
ተደፋፈረ፡ ተሰዳደበ/ተነጣጠበ ።
ተደፋፈጠ፡ ተሸማመቀ ።
ተደፍ፡ የሸማኔ መምቻ ("በጥርስ ላይ የሚዋደድ የሚደፋ በመደፈ ብል") ።
ተደፍዳፊ፡ የሚደፈደፍ ("ተለዋሽ") ።
ተዳለለ፡ ተሸናገለ ("ሰምቶ እንዳልሰማ ሲያውቅ እንደማያውቅ ተኳዃነ") ።
ተዳለሰ፡ ተቃባ ።
ተዳለቀ፡ ተዳሰቀ/ተጓሰመ/ተጫወተ ።
ተዳላ፡ ተመቻቸ/ተሰማማ ።
ተዳሎ፡ የውሻ ስም ("ተሞኛኝቶ ተሸ ናግሎ ማለት ነው") ።
ተዳመጠ (ተደራራጊ)፡ ተሳማ ("ባበለ") ።
ተዳመጠ (ተደራጊ)፡ ተረገጠ/ተዳጠ/ተደፈጠጠ/ተለሰቀ ("ትክክል ኾነ") ።
ተዳማ፡ ተዋለደ ("በዘር ተቀላቀለ") ።
ተዳማ፡ ደም ተፋሰሰ ።
ተዳማጭ፡ የሚዳመጥ ("የሚሳማ") ።
ተዳማጭ፡ የሚዳመጥ ("ፍልቅቅ ' መን") ።
ተዳሰ፡ ተፈጨ/ደቀቀ ።
ተዳሰመ፡ ተጋጩ/ተላተመ/ተተማተመ ።
ተዳሰሰ፡ ተነካ/ተዳበሰ ።
ተዳሳሽ፡ የሚዳሰስ ("ተዳባሽ") ።
ተዳረ፡ ተሰረገ/ሚስት አገባ/ተሞሸረ ።
ተዳረሰ፡ ተቃረበ ("ዝር ተባባለ") ።
ተዳረሰ፡ ተካፈለ/ተዳደለ ("ትክክል ተሰጠ ተሰጣጠ") ።
ተዳረሰ፡ ተዋገደ/ተገባደደ ("ሊያልቅ ቀረበ") ።
ተዳረቀ፡ ተነዛነዘ/ተጨቃጨቀ ።
ተዳረቀ፡ ደረቅ ተኳዃነ ።
ተዳረች፡ ከአባት ከናቷ ቤት ወጣች ("ለባል ተሰጠች") (፩ሳሙ. ፲፰፡ ፲፱) ።
ተዳረገ፡ ተለካ/ተሰፈረ/ተመጠነ/ተቈ ነነ/ተሰጠ ("ድርነው ተቀበለ ሰውየው") ።
ተዳረገ፡ ተሣራ ።
ተዳረገ፡ ተፈቀደ/ታዘዘ ።
ተዳሪ፡ የሚዳር/የምትዳር ("ተሰራጊ የተዳረ የተሰረገ ሚስት ያገባ ጕል ማሳ") ። (ተመልከት፡ ኳለ ብለኸ የተኳለን እይ) ።
ተዳራ (ተማሐዘ)፡ ተዛና/ተቃበጠ/ተዋዛ/ተጫወተ/ተላፋ/ተዳለቀ/ተዳሰቀ ("ኀ ፍረት ለኀፍረት ተገላለጠ ተቈላመመ") (ዘፍ. ፳፮፡ ፰) ።
ተዳራ፡ ድር ተቀባበለ ።
ተዳራጊ፡ የሚሣራ ።
ተዳራጊ፡ የተዳረገ/የሚዳረግ ("ሰው ወ ይም ድርጎ") ።
ተዳቀለ፡ ተራከበ/ተገናኘ ("የተክልና የተክል") ።
ተዳቀለ፡ ተዋለደ/ተዛመደ ("የሰውና የ ሰው") ።
ተዳቀቀ፡ ተሳበረ/ተሳለቀ/ተዳከመ ("ዐ ቅም ዐጣ") ።
ተዳቃ፡ በኰቴ ተማታ ።
ተዳቈሰ/ተደቋቈሰ፡ ተዳቀቀ/ተማታ/ተደባደበ ።
ተዳበለ (ተደበለ)፡ ደባል ኾነ (በሰው ቤት ተቀመጠ ኖረ) ።
ተዳበሰ፡ ተዳሰሰ ፥ ተነካ/ተፈለገ ።
ተዳባ፡ ተሻመቀ/ተዳፈጠ ።
ተዳባሽ፡ የሚዳበስ (ተዳሳሽ) ።
ተዳባይ፡ የሚዳበል ።
ተዳነ (ተድኅነ)፡ ተዋሰ ("መድን o ተ ያዥ ኾነ") ።
ተዳኘ፡ ለዳኛ ታዘዘ/ተከሰሰ ("ሥራት ለበሰ በግራ ቆመ ተፈረደበት ተሠራ ተቀጣ") ።
ተዳከመ፡ ተሰላቸ/ተሳነፈ ("ወደ መሸ ነፍና ወደ ሞት ተቃረበ") ።
ተዳካ (ተዳወለ)፡ ምድርን ተራገጠ/ተላካ/ተዋሰነ/ተካለለ ።
ተዳኸ፡ በጕንብስ ተኼደ ።
ተዳኺ፡ የሚዳኸ መታደያ ። "ባለቅኔዎች ግን ቤተ ልሔም ይሉታል" ።
ተዳወለ፡ ተማታ/ተጣዘለ ፥ ተመዳወተ ። (ተመልከት፡ ደካን እይ) ።
ተዳወረ፡ ተደወረ ።
ተዳደለ (ተዓደለ)፡ ተሰጣጠ/ተቀባ በለ (ድርሻን ፈንታን ") ።
ተዳደሰ (ተሓደሰ)፡ ዐዲስ ተኳዃነ (ተጠጋገነ ") ።
ተዳደረ (ተኃደረ)፡ ተኳዃነ/ተሰማማ/ ተኗኗረ ።
ተዳደነ፡ ተፈላለገ/ተገዳደለ ።
ተዳደፈ፡ ተጓደፈ ተራከሰ ተረካከሰ ተባከለ ተጨመላለቀ ።
ተዳዳረ፡ ተሰራረገ ።
ተዳጠ፡ ተረገጠ/ተደፈጠጠ ።
ተዳጠ፡ ተፈጪ/ላመ ።
ተዳጭ፡ የሚዳጥ (ፌጦ ተልባ) ።
ተዳፈረ፡ ተሳደበ/ተናጠሰ/ተጋፋ ።
ተዳፈቀ፡ ተዛፈቀ/ተናከረ/ተሳጠመ/ተሳመጠ ።
ተዳፈነ (ተደራራጊ)፡ ተቃበረ ("ሰው ለሰው") ።
ተዳፈነ (ተደራጊ)፡ ተደፈነ/ተቀበረ/ተሸሸገ ።
ተዳፈነ፡ ቀረ/ታጐለ ("ግብሩ ቅዳሴው") ።
ተዳፈጠ፡ ተሻመቀ/ተዳበቀ ።
ተዳፋ፡ ተፋሰሰ/ተዋደቀ/ተቻኰሰ/ተ ጋፋ/ተጋደለ ።
ተዳፋሪ፡ የተዳፈረ/የሚዳፈር ("ተሳዳቢ ተናጣሲ") ።
ተዳፋት፡ ዘቅዛቃ ስፍራ ።
ተድላ፡ ምቾት ለሰውነት የሚሰማማ መብል መጠጥ ("ማለፊያ ኑሮ ሐዘን ቅ ት ችግር ጕድለት የሌለበት") ።
ተድላ ሥጋ፡ የሥጋ ተድላ ("ኀላፊ") ።
ተድላ ነፍስ፡ የነፍስ ተድላ ("የማያ ልፍ") ።
ተድላ ደስታ፡ የደስታ ምቾት ።
ተድላ፡ ድሎት ደላ ።
ተድላ ገነት፡ የገነት ተድላ ("አዳምና ሔዋን ከስሕተት በፊት የነበሩበት በግእዝ ገነተ ተድላ ይባላል የተድላ ገነት ማለት ነው") ።
ተድመሰመሰ፡ ተትመሰመሰ/ተልከሰከሰ ።
ተድመነመነ፡ ጠቋቈረ/ጨላለመ ።
ተድረመረመ፡ ተጕረመረመ ።
ተድረምራሚ፡ የሚድረመረም ("ተጕረ ምራሚ") ።
ተድረቀረቀ፡ መብረቅኛ ጮኸ ።
ተድቀሰቀሰ፡ በንቅልፍ ዛለ/ደከመ/ሰለተ ("ሰውነቱ ደቀቀ ዐቅም ዐጣ መነሣት አቃታው") ።
ተድበለበለ፡ ተርበተበተ ።
ተድበለበለ/ተድቦለቦለ፡ ተንከበከበ (ክብ ኾነ ዐበጠ ተነፋ) ።
ተድበሰበሰ፡ ተደናገረ/ተሳሳተ ("ዐረም" ።
ተድበስባሽ፡ የሚድበሰበስ (ተደናጋሪ) ።
ተድበረበረ (ተድበለበለ)፡ ተድፈ ነፈነ ("ደንበር ደንበር እለ") ።
ተድበከበከ፡ ወፈረ ።
ተድጐለጐለ፡ ወፈረ ("መልክ ዐጣ ቅ ንቡርስኛ ኼደ ተላወሰ") ።
ተድፈነፈነ፡ ተጭፈነፈነ ("ዳፍንታም ኾነ") ።
ተድፈጠፈጠ፡ ተፍረጠረጠ ።
ተዶለ፡ ተጨመረ/ተከተተ/ገባ/ተሰ ።
ተዶለተ፡ ተሰበሰበ/አንድነት ኾነ ("ታ ደመ ተመከረ ተሤረ ተቋጠረ") ።
ተዶለተ፡ ተዶለ/ተጨመረ/ተቀላቀለ ።
ተዶረረ፡ ኰራ/ተመካ/ተቈጣ/አኰ ረፈ ።
ተዶራሪ፡ የሚዶረር ("ትምክተኛ") ። (ተመልከት፡ ሰራ ንን እይ) ።
ተዶገዶገ፡ ተጨረ/ተሞጫጨረ/ቀ ጠነ/አነሰ/ደቀቀ ።
ተጀቦነ፡ ለበሰ/ታጀለ/ተሸፈነ ።
ተጀነነ (ዐረ. አበደ)፡ ኰራ/ታበየ ("በዕለተ ፍጥረት የዲያብሎስን አለማመስገን ያሳያል") ።
ተጀነጀነ፡ ገባ/ተጨመረ/መላ ተረገ ረፃ/ተጐዘጐዘ ።
ተጀናኝ፡ የሚጀነን/የሚኰራ ።
ተጀጀረ፡ ከምግብ ተከለከለ ("ቍሽቢ ያም ኾነ") ።
ተጀጐለ (ተጨጐለ)፡ ተካበ/ታጠረ/ተቀጠረ/ተማገረ/ተሸመጠጠ ።
ተጅመለመለ፡ እንደ ግመል ተቀጣ ጥሎ ኼደ ።
ተጅአይጡ፡ የበሬ ስም፡ ዐጣ ። ታደገ፡ አዳነ ተመለሰ ዐደገ ።
ተገለለ፡ ተለየ/ተወገደ/ፈቀቅ አለ (ብቻውን ኾነ ለዕርቅ ለጸሎት) ።
ተገለለ፡ ታጨደ/ተቈረጠ/ተነቀለ/ተጠራቀመ ።
ተገለማመጠ፡ ተገራመመ ።
ተገለሰሰ፡ ተለፈፈ/ተገለጠ ።
ተገለበጠ፡ ተቀዳ/ተጨመረ/ተጋባ (ማር. ፪፡ ፳፪) ። "ፈሰሰ ተከነበለ።"
ተገለበጠ፡ ተተረጐመ ተመለሰ ቋንቋው/ብራናው ።
ተገለበጠ፡ ተኛ/ተፈነደሰ ። "ያንን ለከት ውጨ ውጨ እንድክ ዐልጋ ተገልብጨ" እንዲሉ ልጆች ።
ተገለበጠ፡ ከዳ ወደ ጠላት ኼደ ።
ተገለበጠ፡ ውስጠኛው ላይኛ ኾነ/ተዛወረ (ምሳ. ፲፩፡ ፲፩፡ ፳፮፡ ፳፯) ።
ተገለደመ፡ ታሰረ/ተሸረጠ ።
ተገለገለ፡ ተለመነ/ዕሺ አለ/በላ/ጠጣ ።
ተገለገለ፡ ተነቀለ/ተወሰደ ።
ተገለገለ፡ ተገመሰ/ታረሰ ።
ተገለገለ፡ ታገዘ/ተረዳ (አገልግሎትን ተቀበለ) ።
ተገለጠ፡ ተገለበ/ተገፈፈ/ተከፈተ/ተራቈተ (ታየ/ተረዳ/ተከሠተ) (ዘፀ. ፫፡ ፲፯፡ ኢሳ. ፵፱፡ ፱) ። "አምላክ በሥጋ ተገለጠ።" (ተመልከት፡ ገመነ ብለኸ ገመናን) ።
ተገለጠጠ፡ ተዛቀ/ተሣቀ ።
ተገለጸ፡ ተገለጠ/ተከሠተ ።
ተገለፈጠ፡ ተሣቀ/ተገለፈፈ ።
ተገለፈፈ፡ ተላጠ/ተላፈ/ተገፈፈ/ተፋቀ ።
ተገለፈፈ፡ ተሣቀ/ተገለጠ (የከንፈር) ።
ተገላለጠ፡ ተከፋፈተ/ተገላለበ/ተጋፈፈ (ነገር ለነገር ተዋጣ) ።
ተገላላጭ፡ የሚገላለጥ ።
ተገላመጠ፡ ቀኝና ግራ ፊትና ኋላ ዝንጀርኛ እየ (አድራጊ) ።
ተገላመጠ፡ ተተኰረ/ተገሠጸ (ተደራጊ) ።
ተገላማጭ፡ የሚገላመጥ ።
ተገላበጠ፡ ተንከባለለ/ተዛወረ/ስፍራ ለወጠ (ዘፍ. ፫፡ ፳፬፡ ሉቃ. ፩፡ ፵፩) ። (ተረት)፡ "ያልተገላበጠ ያራል።"
ተገላባጭ፡ የሚገላበጥ (ተንከባላይ) ።
ተገላተመ፡ ተቻኰለ/ተጣደፈ/ተጋጨ/ተላተመ ።
ተገላገለ፡ ተላቀቀ/ተለያየ/ታረቀ/ተሰማማ ።
ተገላገለች፡ ወለደች (ከምጥ ተለያየች) ።
ተገላጋይ፡ የሚገላገል (ታራቂ) ።
ተገላጭ፡ የሚገለጥ (መጋረጃ ወይም) ።
ተገልባጭ፡ የሚገለበጥ (ተለዋጭ ወረ) ።
ተገልጋይ፡ የሚገለገል/የሚታረስ መሬት (የሚታገዝ/የሚረዳ ሰው) ።
ተገመለ፡ ተለበለበ (ግመል መሰለ) ።
ተገመሰ፡ ተተለመ/ታረሰ/ተቈረሰ/ተከፈለ/ተፈነከተ ።
ተገመተ፡ ተሰላ/ታሰበ/ተገመገመ ።
ተገመደ፡ ከረረ/ተሸረበ/ተደበለ ።
ተገመደለ፡ ተቈረሰ/ተገመሰ ።
ተገመደለ፡ ጐደለ/ተቀመጠለ ።
ተገመገመ፡ ተያያዘ (ገመገም መስሎ ቆመ) (፩ሳሙ. ፲፬፡ ፭፡ ነሐ. ፫፡ ፳፮) ።
ተገመገመ፡ ተገመተ/ተሸለገ/ታሰበ/ተሰላ (ዘሌ. ፭፡ ፲፭) ።
ተገመጠ፡ ተነከሰ/ተቈረሰ/ተሰበረ/ተሸረፈ/ተበላ ።
ተገመጠጠ፡ ተነቀፈ/ተናቀ ።
ተገማመሰ፡ ተፈነካከተ ።
ተገማመተ፡ ተሳላ/ተዋጋ (ተዋግዐ)/ተሳሰበ/ተገማገመ/ተሸላለገ ።
ተገማመጠ፡ ተነካከሰ/ተቈራረሰ/ተሰባበረ/ተሸራረፈ ።
ተገማሽ፡ የሚገመስ (ተተላሚ) ።
ተገማች፡ የሚገመት (ሀብት ግምት ተቀባይ ወሳጅ) ።
ተገማጅ፡ የሚገመድ (ሣር ልጥ ጭረት) ።
ተገማገመ፡ ተገማመተ/ተሳላ/ተሻለገ/ተሸላለገ/ተሳሰበ ።
ተገማጋሚ፡ የሚገማገም (ተሳይ) ።
ተገማጠጠ፡ ተነቃቀፈ/ተንገራጠጠ/እንቢ አለ ።
ተገማጣጭ፡ እንቢተኛ/ተንገራጣ ።
ተገማጭ፡ የሚገመጥ (ተሸራፊ) ።
ተገምዳይ፡ የሚገመደል (ተቈራሽ) ።
ተገምጋሚ፡ የሚገመገም (ተሸላጊ) ።
ተገሰለ (ተአርወየ)፡ ተነሣሣ/ተቈጣ/ተናደደ/ጮኸ ።
ተገሰሰ (ተገሰ)፡ ጠፋ/ተደመሰሰ/ተዳ በሰ/ተዳሰሰ ።
ተገሰሰ፡ ረባ/በዛ ።
ተገሰሰ፡ ተሻረ/ተለወጠ/ተገለበጠ ።
ተገሠጠ፡ ተሳለ/ተነጠሰ ።
ተገሠጠ፡ ተገሠጸ ።
ተገሠጸ፡ ተዘለፈ (ቍጣ መጣበት ወረደበት ተሠራ ተቀጣ ተመከረ) ።
ተገሳሽ፡ የሚገሰስ (ተለዋጭ) ።
ተገረ፡ ተቈጣ ግልፍተኛ ኾነ ገፈ ።
ተገረ፡ ነገደ ወጥቶ ወርዶ ("ቸገረን" ተመልከት) ።
ተገረ፡ ወደ ዛፍ ወይም ወደ ሌላ...ነገር ላይ ወጣ ።
ተገረመ፡ ተደነቀ ("ዕጹብ ድንቅ ተባለ ልማዱ ግን አደነቀ አነከረ ነው") ።
ተገረመመ፡ ተገላመጠ ።
ተገረሰሰ፡ ተነቀለ/ፈለሰ/ወደቀ/ተ ጋደመ ።
ተገረበደ፡ ፈጽሞ ተከፈተ/ተወለለ ።
ተገረኘ፡ ታሰረ/ተኰደኰደ ።
ተገረዘ፡ ተቈረጠ/ተቀነጠበ ።
ተገረደ፡ ተጦለ/ተለየ/ተቀጠረ (ግርድ ገረድ ኾነ) ።
ተገረደመ፡ ተገመጠ/ተሰበረ/ነከተ/ደቀቀ/ተበላ ።
ተገረደደ፡ ጠረሰ/ተቸረቸመ ።
ተገረደፈ፡ ተፈጨ/ተከረተፈ (ጕርሃ) ።
ተገረገመ፡ ተሠራ/ተበጀ ግርግሙ ።
ተገረገመ፡ ተሸረፈ/ተሰበረ ጥርሱ ።
ተገረገረ፡ ተቀረቀረ/ተተከለ ።
ተገረገረ፡ ታወከ/ታገረ/ታገደ ።
ተገረፈ፡ ቀና ዕርሻ ለመደ ።
ተገረፈ፡ ተሸለመ/ተተኰሰ ።
ተገረፈ፡ ተቈነደደ/ተሸመተረ/ተሸነ ቈጠ/ተቀጣ/ተጠበጠበ (፪ቆሮ. ፲፩፡ ፳፬) ።
ተገሪ፡ የሚግራ/የሚፈተን ።
ተገራ (ተረየፀ/ገርሀ)፡ ሥግሪያን ተማረ/ለመደ (ሰውን ተሸክሞ ኼደ ተሠራ ተቀጣ ተፈተነ) ።
ተገራመመ፡ ተገለማመጠ (በክፉ ዐይን ተያየ) ።
ተገራሰመ፡ ተጋጨ/ተገላተመ/ተደና ቀፈ/ተወላከፈ ።
ተገራረመ፡ ተደናነቀ (እንደ እንጦንስና እንደ አቢብ) ።
ተገራረደ፡ ተካለለ/ተመካከተ ።
ተገራዥ፡ የሚገረዝ ወንድ ልጅ (ተቀንጣቢ ሸለፈት) ።
ተገራደመ፡ ተጋመጠ/ተሳበረ ።
ተገራፊ፡ የሚገረፍ (ጥፋተኛ ሰው) ።
ተገርማሚ፡ የተገረመመ/የሚገረመም ።
ተገርዳፊ፡ የሚገረደፍ (ተከርታፊ) ።
ተገሸለጠ፡ ተላጠ/ተመለጠ/ተገፈፈ ።
ተገሸለጠ፡ ተሣቀ/ተገለፈጠ/ተገለፈፈ ።
ተገሸረ፡ ተቀመጠ/ተረፈቀ ።
ተገሸረ፡ ተተወ/ቈየ ።
ተገሻሪ፡ የሚገሸር (ተቀማጭ) ።
ተገበ (ጠገበ)፡ ወለስ ዐፈነ (ዝናሙ ከፋ ኣካፋ ችፍችፍ አለ) ።
ተገበረ (ተጸብሐ)፡ ተሠራ፡ ታረሰ፡ ተዘመረ፡ ታረመ፡ ታጨደ ። "መምህራን ግን ተገበረን እንደ ገበረ 'ሠራ' ብለው ይተረጕሙታል።"
ተገበረ፡ ተቀረጠ፡ ተከፈለ፡ ተሰጠ ግብሩ ።
ተገበረ፡ ተቀበለ፡ እጅ አደረገ፡ ወሰደ ሹሙ።
ተገበዘ
ተገበዘ፡ ግብዝና ተሾመ፡ ዝበዝ ኾነ።
ተገበየ፡ ተገዛ፡ ተለወጠ፡ ተሸጠ፡ ተወደደ ።
ተገበያየ፡ ተገዛዛ፡ ተለዋወጠ፡ ተሻሻጠ፡ ተቀባበለ፡ ተሰጣጠ።
ተገበደ፡ ተፈለጠ፡ ተተረተረ፡ ተሠነጠቀ።
ተገበጠ፡ ተመታ፡ ተለየ፡ ተከመረ/ተከማቸ ።
ተገቢ፡ የሚገባ ። ተገቢ ነገር ተገቢ ሥራ እንዲሉ ።
ተገባ (ደለወ)፡ ኾነ በጀ ተመቸ ተወደደ ቀና ።
ተገባ፡ መግባት ተቻለ ።
ተገባ፡ በቃ ተዘጋጀ ። እከሌ ነፍስ መግደሉ ስለ ተመሰከረበት ለሞት ተገባ ።
ተገባ፡ ተተካ ተወከለ ።
ተገባበዘ፡ ተጠራራ፡ በላ/ጠጣ ተባባለ፡ የግብዣ ብድር ተከፋፈለ፡ ተጐራረሠ።
ተገባባ፡ ተዳዳረ ተዘማመደ ተሰጣጠ፡ ተደማመጠ ተሰማማ ። (ተረት)፡ ባይገባቡ በደጃፍ ይገቡ ።
ተገባዥ፡ የሚገበዝ፡ ግብዝ የሚኾን።
ተገባደደ፡ ተዋገደ፡ ተቃረበ፡ ተዳረሰ።
ተገብሮ፡ "ን" የሌለበት ቃል፡ መደረግ። (ማስረጃ)፡ "አሞራውም በረረ፡ ቅሉም ተሰበረ።"
ተገብሮ፡ መሠራት፡ ሥራ/ዐመል። "ተፈጥሮን ተገብሮ አይመልሰውም" እንዲሉ።
ተገተ፡ በፍርድ፡ ቤት፡ ተነጋገረ፡ ተከራከረ ። (ተረት)፡ በኹለት፡ በትር፡ አይማቱ፡ በኹለት፡ ዳኛ፡ አይገቱ።
ተገተመ፡ ተቃመ/ተቻመ ።
ተገተረ፡ ተሳበ/ተለጠጠ/ተወጠረ/ተወተረ (ሕዝ. ፵፩፡ ፲፮, ፳፮) ። "ቆመ ተቀሰረ ተደከረ።"
ተገተነ፡ ተነጨ/ተቦጨቀ/ተዘነተረ/ተበላ/ተዋጠ ።
ተገተገ (ተተገ)፡ ገረፈ በእሳት ተ...ኰሰ ።
ተገተገተ፡ ተነከሰ/ታኘክ ።
ተገታ (ተገትዐ)፡ ተያዘ/ተወሰነ/ታገደ/ቆመ ።
ተገታሪ፡ የሚገተር (ተለጣጭ ተወጣሪ) ።
ተገቺ፡ የሚገታ (አጥባቂ ያይዶለ) ።
ተገነ (ጸቈነ)፡ ዐጠረ ቀጠረ ጀጐለ ጋረደ ከለለ ዐቀበ ("ጠገነን" እይ) ።
ተገነበለ (ተገንጰለ)፡ ተገለበጠ/ተጋደመ ።
ተገነኛኘ፡ ተቀራረበ/ተገጣጠመ/ተወሳሰበ/ተገናዘበ ።
ተገነዘ (ተገንዘ)፡ ተከፈነ/ተሸፈነ/ተጠቀለለ/ለበሰ/ታሰረ/ተቋጠረ ።
ተገነዘበ፡ ታሰበ/ታወሰ/ተጤነ/ልብ ተባለ (ልማዱ ግን ዐሰበ አስታወሰ ነው) ።
ተገነደሰ፡ ተሰበረ/ወደቀ/ተጣለ/ተጋደመ (ግንዱ እንደ ግንድ ተኛ ሰው) ።
ተገነጠለ፡ ተሳበ/ተቈረጠ/ተበተነ/ተለየ/ተበላሸ ።
ተገነጣጠለ፡ ተለያየ/ተበጣጠሰ/ተበታተነ/ተበለሻሸ ።
ተገነፈለ፡ ገነፈለ ።
ተገነፋ፡ (ተመልከት፡ ነፋን እይ) ።
ተገናኘ (ተራከበ)፡ ተቃረበ/ተያየ/ተዋወቀ/ተሳሳመ (ዘፍ. ፳፱፡ ፲፩, ፴፩፡ ፵፭) ።
ተገናኘ፡ ተጋጠመ/ተጣመረ/ተያያዘ/ተዋሰበ/ተደረበ/አንድ ኾነ ።
ተገናኘች፡ ላም ጥጃዋን አጠባች/ታለባች ።
ተገናኝ፡ የሚገናኝ (ግጥሚያ መግጠም አንድነት) ። (በተገናኝ) በመግጠም ።
ተገናዘበ፡ ገንዘብ ለገንዘብ ተሰጣጠ/ተዋረሰ/ተወራረሰ/ተገናኘ/ተጣመረ/ተያያዘ/ተቋለፈ ።
ተገናዛቢ፡ የሚገናዘብ (ተያያዥ ሜንጦ አዝራር) ።
ተገናዥ፡ የሚገነዝ (የሰው በድን ሬሳ) ።
ተገናጠለ፡ አንዱም አንዱም ገንጥሎ ሰብሮ ወሰደ (ተባጠሰ) ።
ተገኔ፡ የሰው ስም ("የኔ ተገን" ማለት...ነው) ።
ተገን (ጸቈን)፡ ጀጐል ዐጥር ቅጥር ከለላ (በተን ውስጥ ያለ ሞቃት ስፍራ - "ዓለም ጥበብ ጨለማ ተገን" እንዲሉ) ።
ተገን፡ ግንብ ከፍተኛ ምድር ።
ተገንዛቢ፡ የሚገነዘብ (ታሳቢ ዐሳቢ) ።
ተገንጣይ፡ የሚገነጠል (ዕንወት ሽጉጥ) ።
ተገኘ (ተረክበ)፡ ተፈጠረ/ተወለደ/መነጨ/ተገለጠ/ታየ ።
ተገኘ፡ መጣ/ቀረበ/ገባ/ታወቀ/ተረዳ (ኤር. ፴፩፡ ፱፡ ፊልጵ. ፪፡ ፰) ።
ተገኘ ወርቅ፡ የሰው ስም ።
ተገኛ፡ መጠጊያ መከለያ ተገን ።
ተገኝ፡ የመጠሪያ ስም "ልጅ ተገኘ ማለት ነው።"
ተገዘመ፡ ተናቀ/ተነቀፈ/ተሸነፈ/ተዋረደ/ተገዛ/ተገረዘዘ ።
ተገዘተ (ተወግዘ)፡ በቄስ ሥልጣን ተያዘ/ታሰረ/ተከለከለ/ተለየ ። "ቃልዎ ይድረሰኝ አላደረግኹም ባደርግም አይለምደኝም አለ ማለ።" "ተወገዘ ራቀ።"
(ተረት)፡ "የተገዘተች ነፍስ የተለጐመች ፈረስ።"
ተገዘዘ (ተገዘ)፡ ተጀጐለ/ታጠረ/ተቀጠረ/ተጋረደ/ተከለለ ። "ትግሬም 'ዘዘ' ብሎ በንጉሥ አለ አማጠነ አዳኘ ይላልና ከለለ ካለው ይገባል።"
ተገዘገዘ (ተገዘ/ተገዝዐ/ተወሠረ)፡ ተከረከረ/ተመገዘ/ተከረከመ ።
ተገዘገዘ፡ ደከመ/ሰለተ።
ተገዛ (ተገዝአ)፡ ተገበየ/ተሸመተ/ለገዢ ተሰጠ ።
ተገዛ፡ ገበረ/ዜገ/ታዘዘ/ታዛዥ ኾነ (ሕዝ. ፳፱፡ ፳፡ ኤፌ. ፮፡ ፭, ፯) ። "ሲገዙ ይገዙ" እንዲሉ። "ዐጤ ቴዎድሮስ ደጃች ውቤን ድል ባደረጉ ጊዜ (አዝማሪ)፦ ሰብአ በጌምድር ወልቃይት ጠገዴ ስሜን አርማጭሆ ለኀይለኛው ንጉሥ ተገዛን እንሆ።"
ተገዛሪ፡ የሚገዘር።
ተገዛች፡ የሚገዘት (በክሕደት/በነውር የተጠረጠረ መናፍቅ ወይም ሌላ ሰው) ።
ተገዛዘተ (ተዋገዘ)፡ ተዋገዘ/ተወጋገዘ/ተለያየ ።
ተገዛዛ (ተጋዝአ)፡ ተገበያየ/ተሻሻጠ/ተለዋወጠ ።
ተገዛገዘ፡ ተማገዘ ።
ተገዥ (ዦች)፡ ገባር/ዜጋ/ቅኝ።
ተገዥነት፡ ገባርነት/ዜግነት/ቅኝነት ።
ተገደለ (ተገድለ/ተቀትለ)፡ ተመታ/ተደበደበ/ተወጋ/ታረደ/ሞተ/ጠፋ/ዐለፈ/ተቀተለ (ማር. ፲፡ ፴፪) ።
ተገደረ (ገደረ)፡ ጡር መስቃ ተናገረ/ሰደበ/ነቀፈ/ናቀ/አቀለለ/ተላገደ (ኣድራጊ) ።
ተገደረ፡ መጻተኛ ኾነ/ተለገጠበት።
ተገደረ፡ ምስጋና ቢስ ኾነ/ተሰደበ/ተነቀፈ ።
ተገደረ፡ ተቀጠለ/በላይ ወጣ/በቀለ ። (ተመልከት፡ ቀጠለን) ።
ተገደረ፡ ዐጣ/ተቸገረ ። (ተረት)፡ "ደግ አድራጊ አበደረ ክፉ አድራጊ ተገደረ።"
ተገደበ፡ ኃደረ ዕድሩ።
ተገደበ፡ ተከተረ/ተወሰነ/ተደለደለ/ታገደ (፪ነገ. ፲፱፡ ፳፬) ።
ተገደደ፡ ግድ ተባለ፡ በግድ ታዘዘ።
ተገደገደ፡ ተተከለ/ቆመ/ተወጠረ። (ተረት)፡ "ሲገደገድ ያልበጀው ሲዋቀር እሳት ፈጀው።"
ተገደፈ (ተገድፈ)፡ ተተወ/ተሻረ/ተፈሰከ/ተበላ ።
ተገደፈ፡ ተጣለ/ተዘለለ/ተረሳ/ጐደለ/ወደቀ/ቀረ/ጠፋ/ታጣ ።
ተገዳቢ፡ የሚገደብ (ተከታሪ/ታጋጅ)።
ተገዳይ፡ የሚገደል (ተደብዳቢ)።
ተገዳደለ፡ የተጋደለ ድርብ መላልሶ ተጋደለ/ተላለቀ ።
ተገዳደረ፡ ተጠቃቀሰ/ተነቃቀፈ።
ተገዳደረ፡ ተፈካከረ/ተወዳደረ/ተከራከረ/ተገተ "እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ተባባለ"/ተቀታተረ/ተቋቋመ ።
ተገዳዳሪ (ሮች)፡ የሚገዳደር (ተቻቻይ/ተወዳዳሪ/ተፈካካሪ/ተቃዋሚ) ።
ተገዳጅ፡ የሚገደድ (ባሪያ/ገባር)።
ተገድራ፡ በዛፍ ላይ የበቀለ ብዙ ተቀጽላ/ጀፍጀፎ ። "ቀ ለገ ጸ ለደ ለ ለረ እንደ ተለወጠ አስተውል።"
ተገድራ/ተቀጽላ፡ ገደረ ።
ተገጠመ፡ ተዘጋ/ታተመ/ልክክ አለ/ታሸገ ።
ተገጠመ፡ ተዘፈነ (ኾነ/ተደረገ ግጥሙ) ።
ተገጠበ፡ ተነካ/ቈሰለ/ተመለጠ/ተላጠ/ተላፈ/ተጋጠ ።
ተገጠገጠ፡ በዝቶ ተሠራ ቤቱ/ተተከለ ድንኳኑ ።
ተገጠገጠ፡ ተቀጠቀጠ/ተላጠ/ተለጠ/ተመነጠረ ።
ተገጣሚ፡ የሚገጠም (ተዘጊ) ።
ተገጣበረ፡ ተናቀ/ተነቀፈ/ተሰደበ/ተዋረደ/ተገጠጠ ።
ተገጣጠመ፡ ተቀናበረ/ተቀነባበረ/ተከናወነ/ተከነዋወነ/ተገናዘበ/ተገነዛዘበ ።
ተገጣጠበ፡ ተቋስለ/ተላላጠ/ተመላለጠ ።
ተገጣጣሚ፡ የሚገጣጠም (ተቀናባሪ/ተከናዋኝ/ተገናዛቢ) ።
ተገጨ፡ ተመታ/ተለተመ/ተኰረኰመ ።
ተገጨረ፡ ተቋፈ/ቀስ ብሎ ኼደ ።
ተገጨረ፡ ተደነሰረ/ተጐበለ ። "በመካከል ተገጭሮ ትርጓሜ ሕዝቅኤል (ገጽ ፫)።"
ተገፈተ፡ ተገፈፈ/ተቀመሰ/ተጠጣ/ተዠመረ ።
ተገፈተረ፡ ተገፋ ።
ተገፊ፡ የሚገፋ ሰው ወተት ።
ተገፋ (ተገፍዐ)፡ ዕልፍ አለ (ቦታውን ለቀቀ) ።
ተገፋ፡ ተበደለ (ግፍ ተቀበለ) ።
ተገፋ፡ ተናጠ/ተወዘወዘ ። (ተመልከት፡ ለቀቀ ብለኸ ለቃቃን እይ) ።
ተገፋተረ፡ ተጋፋ ።
ተገፋፋ (ተጋፍዐ)፡ ግፍ ተቀባበለ ።
ተጕለቴ (ቶች)፡ የተጕለት ሰው ።
ተጕለቴ፡ የተጕለት ዜማ ።
ተጕለት፡ ተገተገ
ተጕለት፡ ያገር ስም (ለመልከኛ ለባለል የተሰጠ አገር በወግዳ ሰሜን ያለ) ።
ተጕለት፡ ያገር ስም፡ ጐለተ ።
ተጕላላ፡ ተራበ/ተጠማ/ተጐዳ/ተቸገረ/ጕልሕ መከራ ተቀበለ/ተንቃቃ/ተበደለ ።
ተጕላላ፡ ተንገላታ፡ ጐላ ። ፲፪፻፶፪
ተጕላላ፡ ወጣ ወረደ ። "ሣር እሥቃለኹ እንደ ማሽላ ነገር በሆዴ እየተጕላላ" (ክራር መቺ) ።
ተጕመተመተ፡ ተድረመረመ ።
ተጕመጠመጠ፡ ታጠበ/ጠዳ ። "ልማዱ ግን ዐጠበ ነው።"
ተጕመጥማጭ፡ የሚጕመጠመጥ (በሽተኛ ኮሶኛ) ።
ተጕማማ፡ በስውር በድብቅ ተወራ/ተነገረ ።
ተጕማማ፡ ውስጥ ለውስጥ ተ...ወራ (ጐማ)
ተጕረመረመ፡ ተድረመረመ/ተቈጣ ።
ተጕረምራሚ፡ የሚጕረመረም (ቍጡ) ።
ተጕረፈረፈ፡ ተዝረከረከ/ተዝረፈረፈ (ተጣለ ወደቀ) ።
ተጊ፡ የሚተጋ/የሚያስብ (ተጣጣሪ) ።
ተጊያጊያጠ፡ ተላበሰ/ተሸላለመ/ተሰማመረ ።
ተጋ (ተግሀ)፡ ሠጋ እንቅልፍ ዐጣ...ነቃ ዐሰበ (ከሰንፍና ራቀ) ።
ተጋለለ፡ ተለያየ/ተራራቀ ።
ተጋለበ፡ ኾነ/ተደረገ ግልቢያው (በፈረስ ተሮጠ ሜዳው) ።
ተጋለጠ፡ ኀፍረቱ ታየ/ተዋረደ/ብቻውን ኾነ/ተጋለበ/ተራቈተ (አባት እናት ሚስት ሞቱበት አደባባይ ዋለ ደረቱን ጣለ) ።
ተጋመሰ፡ ተካፈለ/ተጋራ/ተፈናከተ (እኩሌታ ኾነ) ።
ተጋመጠ (ገመጠ)፡ ተናከሰ/ተዘናተረ/ተባላ ።
ተጋማ፡ ተበሳበሰ/ተበለሻሸ ።
ተጋማጭ፡ የተጋመጠ/የሚጋመጥ (ተናካሽ ነካሽ ጋማ ከብት) ።
ተጋሰሰ፡ ተዳፈረ ።
ተጋረደ (ተንጦልዐ)፡ ተጣለ/ተዘረጋ/ተለቀቀ መጋረጃው ።
ተጋረደ፡ ተከለለ/ተጠለለ/ተሰወረ/ተመከተ ሰዉ ቤቱ ።
ተጋረጠ፡ ተሰካ/ተተከለ ጋሬጣው ። "ተፈቃ ተበጣ ግንባሩ።"
ተጋረፈ፡ ተማታ/ተቈናደደ/ተለቋጠ/ተሸማተረ ("(ገረፈ)")
።
ተጋረፈው፡ ምች መታው/አሳከከ/ኣሳበጠው/አቈሰለው ።
ተጋሪ፡ የሚጋራ/ተፋላሚ ።
ተጋራ፡ ተካፈለ/ተካፍሎ ወሰደ/ተፋለመ ። "ይህን ዕንጨት ባትጋራኝ" እንዲል እረኛ ።
ተጋራ፡ ተዳረሰ ።
ተጋራጅ፡ የሚጋረድ (መንበር ዕልፍኝ ግምጃ) ።
ተጋራጭ፡ የሚጋረጥ (ተፈቂ) ።
ተጋበሰ፡ ተሰበሰበ/ተከማቸ።
ተጋበዘ፡ ሰውን "ልምታ/ልደብድብ" አለ፡ ተከለከለ።
ተጋበዘ፡ ተራ በላ/ጠጣ/ተመገበ።
ተጋቢ፡ የሚጋባ፡ ተላላፊ ዕመም ።
ተጋባ (ተጋብአ)፡ ተዛመደ ተዳረ፡ ለሚስት ተሰጠ፡ ባል ኾነ ። (ሉቃ ፲፯ ፥ ፳፯) ።
ተጋባ፡ ተገለበጠ ተዛወረ ተላለፈ ባዶ ኾነ ።
ተጋባች፡ ተዳረች፡ ሚስት ኾነች ። (ኢሳ ፷፪ ፥ ፬) ።
ተጋባዥ (ዦች)፡ የሚጋበዝ፡ በዪ ።
ተጋቦት (ተጋብኦት)፡ መዛወር ማ ለፍ፡ የበሽታ የሌላውም ኹሉ።
ተጋተ (ተግዕተ)፡ በጥርኝ ጠጣ/ተጐነጨ ።
ተጋች፡ የሚጋት (ሕፃን በሽተኛ) ።
ተጋነነ፡ ተከባበረ/ተመሰጋገነ/ተባዛ ።
ተጋኘ፡ የፀሓይ ሙቀት/የነፋስ ግጭት/ኀይል/ቅዝቃዜ እሰው አካል ተጋባ/ተናኘ ።
ተጋኝ፡ የተገነ/የሚተግን (ጀጓይ) ።
ተጋዘ (ተግዕዘ)፡ ተወሰደ/መጣ ።
ተጋዘ (ተግእዘ)፡ ተጠላ/ተነቀፈ/ተሻረ/ተዋረደ/ታሰረ/ተቀጣ ።
ተጋዛ፡ ተጠመነ (የሰውን መሬት በርቦ አፍሳሽነት ወይም በጕልበት በእኩል ዐራሽነት ተዋዋለ) ።
ተጋዢ (ዦች)፡ ተጠማኝ (የሰው ምድር ዐራሽ) ።
ተጋዢነት፡ ተጠማኝነት (ርቦ አፍሳሽነት) ።
ተጋዥ፡ የሚጋዝ/የሚወሰድ/የሚታሰር ።
ተጋደለ (ተጋደለ/ተቃተለ)፡ ተሳለፈ/ተጋጠመ/ታገለ/ተናነቀ/ተዋጋ/ተተናነቀ (ሉቃ. ፲፫፡ ፳፬) ።
ተጋደረ (ገደረ)፡ አላገጠ/አፈዘዘ (ማር. ፱፡ ፴፪) ።
ተጋደደ፡ ለጊዜው ተበደረ/ተዋሰ።
ተጋደደ፡ ተደባበቀ፡ ተካለለ።
ተጋደደ፡ ተጣመመ/ተጠማዘዘ። "በሮቹ ሊዋጉ ተጋደዋል።"
ተጋደደ፡ ታየ/ተጣባ ። "ኮሶ ተጋደደው" እንዲሉ።
ተጋዳ፡ ታሰረ/ተወደረ/ታገደ/ተከለ ።
ተጋዳይ (ተጋዳሊ/ተቃታሊ)፡ የተጋደለ/የሚጋደል (ጦረኛ/ሐርበኛ/ሰልፈኛ/ተዋጊ/የጦር ገበሬ/ሰማዕት/ጻድቅ)። (ተረት)፡ "ኣልሞት ባይ ተጋዳይ።"
ተጋዳዮች፡ የተጋደሉ/የሚጋደሉ (ኢሳ. ፴፬፡ ፫) ።
ተጋገሠ (ተዓገሠ)፡ ተቻቻለ (ዝም ተባባለ - እንዳላየ እንዳልሰማ ተኳዃነ) ።
ተጋገረ፡ በሰለ (እንጀራው/ዳቦው ረጋ/ጠና)፡ በረዶው/ውርጩ/ዐመዳዩ።
ተጋገረ፡ ዝም አለ፡ ሳይናገር ቀረ።
ተጋገሻ፡ መቻቻያ።
ተጋገተ (ተዓገተ)፡ ተካሰበ/ተያያዘ ("ተቀባበለ ዕግትን ") ።
ተጋገዘ (ተሓገዘ)፡ ተቀባበለ ፥ ተረዳዳ ፥ ተፈራረቀ ተራረፈ ።
ተጋጋለ፡ ብርቱ ጥል ተጣላ/ተፋጅ/ተነሣሣ ።
ተጋጋለ፡ ተጋጋመ/ተቀጣጠለ ።
ተጋጋመ፡ ተፋፋመ/ተጋጋለ/ተቀጣጠለ (እሳቱ ጠቡ ጦርነቱ) ።
ተጋጋሪ፡ የሚጋገር/የሚረጋ ሊጥ።
ተጋጋዥ (ተሓጋዚ)፡ የተጋገዘ/የሚ ተጋገዝ (የሚረዳዳ ተቀባባይ ") ራረፍ ።
ተጋጠ (ተግሕጸ)፡ ተላጠ/ተመለጠ/ተነፊ/ተገጠበ/ተብላ/ታማ ።
ተጋጠመ፡ ተቃረበ/ተገናኘ/ተሳካ/ተዋደደ/ተሰማማ/ተያያዘ (የጠባይ/የግብር/የክፉና የበጎ) ።
ተጋጠመ፡ ተጣላ/ተዋጋ (የበሬ/የጦረኛ) (ዘዳ. ፩፡ ፵፬) ።
ተጋጠጠ፡ ተቈረጠ/ተገፈፈ/ተጠረገ/ተደደ/ተማጠጠ ።
ተጋጣሚ፡ የተጋጠመ/የተገናኘ (የሚጋጠም/የሚገናኝ ተቃራቢ ተገናኝ) ።
ተጋጨ፡ ተጣላ/ተላተመ/ተተማተመ (ጥቂት ጦርነት አደረገ) (ኢሳ. ፶፱፡ ፲፡ ሕዝ. ፫፡ ፲፫) ።
ተጋጪ፡ የሚጋጭ (ደንጊያ/ብረት) ።
ተጋጭ፡ የሚጋጥ (ዐጥንት ዐምቦ) ።
ተጋፈ (ተግሕፈ)፡ ታፈሠ/ተጠረገ/ተጠጣ ።
ተጋፈጠ፡ ቀረበ/ገባ (ሰው ከጦርነት) ።
ተጋፈፈ (ተደራጊ)፡ ታጨደ/ተጠረገ/ተሰባሰበ/ተያዘ (ገርሣው ልሻው ዘኬው ዓሣው) ።
ተጋፈፈ፡ ልብስን ተቃማ ገፈፈ ።
ተጋፊ (ዎች)፡ የሚጋፋ (ኀይለኛ) ። "በልማድም ገፊ ተብሎ ይተረጐማል።"
ተጋፋ (ተጋፍዐ)፡ ግፍ ተሣራ/ተባደለ/ተዳፈረ (ሚል. ፫፡ ) ።
ተጋፋ፡ ተጣበበ/ተነቀ ።
ተጋፋ፡ ገፋ (ዘሌ. ፲፱፡ ፴፫) ።
ተጋፋጭ፡ የሚጋፈጥ (ተማች ተዋጊ አይፈር ለፊቱ ጐበዝ) ።
ተጋፍቼ፡ የጋን ማቶት ጠላ ሲቀዱ ጋኑን የሚገፉበት ዐሸት የሚያደርጉበት ።
ተጌጠ፡ ተሸለመ/ተሽኰነተረ/ኣማሪ ሰውየው ። "ጌጠኛ ኾነ ተለበሰ ልብሱ።"
ተግ ተግ አለ/ቦግ ቦግ አለ ።
ተግ አለ/ቦግ አለ፡ በራ ቆመ ።
ተግ/ቦግ/ብል፡ ቆመ ።
ተግ/ቱግቦግ፡ ተገተገ ።
ተግመነመነ፡ የገመነ ድርብ (ተትከነከነ ተናደደ) ።
ተግማማ፡ የገማ ድርብ (መላልሶ ገማ) ።
ተግሣጽ፡ ዘለፋ/ቍጣ (የምክር ኀይለ ቃል ቅጣት) ።
ተግበሰበሰ፡ ተጐተተ/ተክበሰበሰ/ታቦትኛ ኼደ ።
ተግበሰበሰ፡ የተጋበሰ ድርብ (በጅጉ ተሰበሰበ)።
ተግባረ ሥጋ፡ ሥጋዊ ሥራ (ዕርሻ/ቍፋሮ/ጸናጽል/ከበሮ/ውሃ ዋና/ሰንጠረዥ በገና/ፈረስ ግልቢያ/ጥፈት/ድጕሰት/ንግድ የመሰለው ኹሉ።)
ተግባረ ነፍስ፡ የነፍስ ሥራ (ጾም/ጸሎት/ስግደት/ፍቅር/ትሕትና/ትዕግሥት/ምጽዋት የመሰለው ኹሉ።)
ተግባረ እድ፡ የእጅ ሥራ ።
ተግባረ ፈት፡ ሥራ ፈት/ሰነፍ/ማጋጣ/ምናውዬ/በዋል ፈሰስ (ምሳ. ፳፮፡ ፲፮)።
ተግባር፡ ሥጋዊና መንፈሳዊ ሥራ።
ተግባባ፡ ተስማማ፡ ነገርን ተቀባበለ ።
ተግብ፡ ነፋስና ብርድ ውሽንፍር ያለው ወሊስ ዐፈና ።
ተግብ ኾነ፡ ቀዘቀዘ በረደ ተጫነ ከበደ (ክረምቱ) ።
ተግተለተለ፡ ተያያዘ/ተቅጠለጠለ/ተ ።
ተግተመተመ፡ ተምታታ/ተገላተመ/ተጋጨ (ሰው ከዕቃ ጋራ) ።
ተግተረተረ፡ የተገተረ ድርብ (ተው ተረተረ ተንገደገደ) ። "ዕንቅፋት መታኝና ልወ ድቅ ተግተርትሬ ዳንኹ።"
ተግተርታሪ፡ የሚግተረተር (ተንገድጋጅ) ።
ተግታ/ቦግታ፡ መቆም ። ቱግ ተግ ።
ተግታጊ፡ የተተ...የሢተትግ (ገራፊ) ። ትግተጋ፡ ገረፋ ትኰሳ ።
ተግዠለዠለ፡ ረዘመ/ተሳበ/ተጐተተ ።
ተግደረደረ፡ ኰራ/ታበየ/ተግበዘበዘ "ሳይኖረው ያለው መሰለ በአፍ በልብስ ከበረ ሲፈልግ አልፈልግም አለ ወላወለ።"
ተግደርዳሪ (ሮች)፡ የሚግደረደር "ያለው መስሎ የሚታይ ከማን አንሼ።"
ተግደርዳሪነት፡ ኵራት/ኵሩነት ።
ተግዳር፡ ሮት (በዋሉት ውለታ ሰውን መውቀሥ) ።
ተግዳሮት፡ ትቢት/ኵራት/ጡር/ሽሙጥ/ቅጥጥብ (ለግጥ/ለግድ ስድብ/ውርደት) ።
ተግጀለጀለ፡ ተጐተተ (ገዠለ) ።
ተግፈለፈለ፡ ጨዋታ አበዛ ።
ተግፈለፈለ፡ ፈላ/በሰለ/ተሠራ ።
ተግፈጠፈጠ፡ ጨሰ/ተጫሰ/ነደደ ።
ተጐለለ፡ ተሠራ/ተጫነ በላይ ኾነ ጕልላቱ (ዐለቀ ተፈጸመ ክዳኑ) ።
ተጐለመ፡ ተከፈለ/ተቈረጠ/ተሰጠ ።
ተጐለሰሰ፡ ተሸነፈ/ደከመ/ተጨቈነ (ዐውቆ በቀላል ወደቀ ከድካም የተነሣ) ።
ተጐለበ፡ ተለበደ/ተጠፈረ/ተሸፈነ/ተለጐመ ።
ተጐለበ፡ ተጠረጠረ (አሹቁ ሽንብራው) ።
ተጐለተ፡ ቆመ/ተጠመዘዘ/ተተከለ/ተከለለ/ተሰጠ/ተቀመጠ/ተረፈቀ ።
ተጐለደመ፡ ተናጋ/ተለየ/ታጠፈ/ፈነገጠ/ወጣ ።
ተጐለጐለ፡ ተቈነጯ/ተለቀመ ።
ተጐለጐለ፡ ተናደ/ተፈታ/ተተረተረ/ተበላሸ ።
ተጐለጐለ፡ ወጣ/ተዘረገፈ ። "አርዮስ አንዠቱ ንስጥሮስ ምላሱ ተጐልጕሎ ሞተ።"
ተጐለጐለ፡ ፈጠጠ/ጐረጠ ።
ተጐለፈጠ፡ ተጐለፈፈ ።
ተጐለፈፈ፡ ተጐለሰሰ ።
ተጐላመሰ፡ ተዳራ/ተበራታ/ተቃበጠ ።
ተጐላቢ፡ የሚጐለብ (ተለባጅ) ።
ተጐላች፡ የሚጐለት መሬት ።
ተጐላይ፡ የሚጐለል የቤት ቍንጮ ።
ተጐላጐለ፡ ተዋጣ/ተዘካዘከ ። "እከሌና እከሌ ጕድ ለጕድ ተጐላጐሉ።"
ተጐላጐለ፡ ተፋጠጠ/ተጓረጠ ።
ተጐመረ፡ ተነፋ/ዐበጠ/ክምር መሰለ (ኰራ) ።
ተጐመተ፡ ተጐመደ/ተቈረጠ/ተከፈለ ።
ተጐመደ፡ ተቈረጠ/ተበጠሰ/ተሰለበ ።
ተጐማለለ፡ ተቈነነ ጐመለለ ።
ተጐማለለ፡ ተቈነነ/ተኰፋነነ (የኵራት ርምጃ ተራመደ) ።
ተጐማመደ፡ ተቈራረጠ/ተበጣጠሰ ።
ተጐማሪ፡ የሚጐመር/የሚነፋ/የሚያብጥ/የሚኰራ ።
ተጐማጅ፡ የሚጐመድ (ተቈራጭ) ።
ተጐሰመ፡ ተመታ/ታወከ "እህ አለ" ።
ተጐሰረ፡ መላ ተጠቀጠቀ/ታመቀ/ተነፋ/ተወጠረ/ተከረበ ።
ተጐሰጐሰ፡ ተጐረሠ/ተበላ/ተጠቀጠቀ ገባ/ተከተተ ።
ተጐሳቈለ (ጐሰቈለ)፡ ተዋረደ (የ ቀይ ጥቍር የረዥም ዐጪር የወፍራም ቀጪን ኾነ ከቈሉበት የጋፉበት መሰለ ተጣቈረ) ።
ተጐረመመ፡ ተቈረጠ/ተፎነነ ።
ተጐረመደ፡ ተገመሰ/ተቈረሰ/ተቈረጠ/ተፈተተ ።
ተጐረሠ፡ ተበላ ምግብ ኾነ (ተከረ ተፈ ተሸመሸመ ተፈጨ) ።
ተጐረበጠ፡ ተነካ/ተቈረቈረ ።
ተጐረተ፡ ተጐራ/ተከመረ ።
ተጐረደ፡ ቀረ/ታጣ/ተዋጠ (አልተ ነገረም ፊደሉ) ።
ተጐረደ፡ ተጐመደ/ተቈረጠ/ተሰበረ/ተጐነደበ/ዐጠረ/ተቀየደ/ተከፈለ/ተፈተገ ። "በውስጥ እግሬ እሾኽ ተጐረደብኝ (ተሰበረ ብኝ)" ።
ተጐረደመ፡ ተቈረጠመ/ተሸረደመ ።
ተጐረጐመ፡ ወለቀ/ተነቀለ ።
ተጐረጐረ፡ ተኰረኰረ/ተበረበረ/ተጓጐጠ/ተሻ/ተፈለገ ።
ተጐረፈ፡ ጐረፈ ።
ተጐራ፡ ተሰበሰበ/ተከማቸ/ተከመረ/ተነባበረ/ተደራረበ/ተቈለለ ።
ተጐራረሠ፡ ተመጋገበ (ጕርሻ ተመላ) ።
ተጐራረደ፡ ተቈራረጠ/ተበጣጠሰ ።
ተጎራባች፡ የሚጎራበት ።
ተጐራጅ፡ የሚጐረድ (ተቈራጭ) ።
ተጐራጐረ፡ ተፋተሸ/ተበራበረ ።
ተጐርጓሪ፡ የሚጐረጐር (ተፈታሽ) ።
ተጐሸመ፡ ተደሰቀ/ተደሰመ/ተጐጐመ ።
ተጐሸመጠ፡ ተነካ/ተጐነጠ ።
ተጐሻመጠ፡ ተናካ/ተጓነጠ/ተናጠበ ።
ተጐበለ፡ ቍጭ አለ፡ ተቀመጠ።
ተጐበኘ፡ ተፈቀደ ። ተጠያቂ፡ የሚጠየቅ፡ ሊቅ፡ መምር፡ ሽ
ተጐበኘ፡ ታወጠ፡ ታየ፡ ተፈቀደ፡ ተሰለለ ።
ተጐበኛኘ፡ ተጠያየቀ፡ ተፈቃቀደ።
ተጐበጐበ፡ በቡሖው አብሲት ተመረበት።
ተጐበጐበ፡ በቡጢ/በጕሽም ተመታ።
ተጐበጐበ፡ ተጌጠ፡ ተሸለመ፡ ተደጐሰ።
ተጐባ፡ ተደገፈ፣ ተገፋተነሣ።
ተጐባ፡ ጕቦ ተቀበለ፣ ተበሰተ፣ በላ።
ተጐባባ፡ ተሰጣጠ፡ ተቀባበለ ጕቦን፡ ተረዳዳ፡ ተደጋግፈ በጕቦ።
ተጐባኘ፡ ተፋቀደ፡ ተሳለለ።
ተጐባጐበ፡ በቡጢ ተማታ፡ ተጓሸመ።
ተጐብኚ፡ የሚጐበኝ፡ ተሰላይ።
ተጐተተ፡ ተሳበ (በደረት በልብ ኼደ ምድር አበሰ አዘገመ) (ምሳ. ፯፡ ፳፪) ። "ረ ዘመ ተጠራ ቀረበ።"
ተጐተጐተ፡ ተነቀነቀ/ተጣደፈ/ተወ ተወተ ።
ተጐታች፡ የሚጐተት (ተሳቢ) ።
ተጐታጐተ፡ ተቻኰለ/ተነዛነዘ/ተዘባ ዘበ ።
ተጐቸ፡ ተከመረ/ተዘመመ/ተቈለለ ።
ተጐነበሰ፡ ጐነበሰ/ሰገደ (ዘፍ. ፵፫፡ ፳፰፡ ዳን. ፰፡ ፲፰፡ ማር. ፩፡ ፯፡ ፊልጵ. ፪፡ ፲) ።
ተጐነደለ፡ ተነደለ/ተቀደደ/ተሰነጋ/ተኰላሸ/ተበጠሰ ።
ተጐነጐነ፡ ተታታ/ተቈነነ/ተጠመረ (ዕጥፍ ድርብ ኾነ) (ዘፀ. ፳፯፡ ፬) ።
ተጐነጐነ፡ ተደፈደፈ/ተለወሰ/ተዋዋደ ።
ተጐነጠ፡ ተደፈረ/ተነካ/ተገፋ/ተነቀነቀ ።
ተጐነጨ፡ በጕንጭ ተያዘ/ተጠጣ ። "ልማዱ ግን ያዘ ጠጣ ነው በተ የሚነሣ ያ፬ ፊደል ግስ ተደራጊነት እንጂ አድራጊነት እንደሌለው አልተመረመረም ።" (ተመልከት፡ ገረመንና ደመመን ደነቀን እይ) ።
ተጐነጨፈ፡ ተዠመገገ ።
ተጐነፈ፡ ታጠበ/ታጀለ/ተቀረጸ/ተደ ።
ተጐናበሰ፡ ታረቀ/ተራረቀ (ይቅር ተባባለ ተሰማማ) ።
ተጐናባሽ፡ የሚጐናበስ (ታራቂ) ።
ተጐናተረ፡ ተቈናጠረ/ተበሳጨ/ተቈጣ ።
ተጐናነበ፡ ተከናነበ/ተጐናጸፈ/ተጀቦነ (በላይ በታች ለበሰ) ።
ተጐናዘለ፡ ተቈላዘመ/ተዘናፈለ/ተመሳቀለ/ተጠጋጋ (ሰብል በነፋስ) ።
ተጐናጣፊ፡ የሚጐናጠፍ (ቄስ ታቦት) ።
ተጐናጸፈ፡ የካህናት ። "ተጐናጠፈ የሕዝብ ነው ።"
ተጐናፊ፡ የሚጐነፍ/የሚታጀል/የሚደጐስ ።
ተጐንጓኝ፡ የሚጐነጐን (ልጥ ሐር የመሰለው ኹሉ) ።
ተጐኘረ፡ ተመላ/ታጨቀ/ተጐሰረ ።
ተጎዘመ፡ ተቈረጠ/ተከፈለ/ታመመ (ሥራው ዐጨዳው) ።
ተጐዘጐዘ፡ ተበተነ/ተመነዘረ/ተነሰነሰ/ተመቻቸ/ተነጠፈ (ሣሩ ቅጠሉ) ። "ተቀመጠ ሰውየው።"
ተጐዛጐዘ፡ ተደላደለ/ተሸራሸረ ።
ተጐዝጓዥ፡ የሚጐዘጐዝ (ተበታኝ ቀጤማ) ።
ተጐደበ፡ ተማሰ/ተቈፈረ/ተቈረጠ/ታረደ/ጐያጐደ ።
ተጐደጐደ፡ ገባ/ተከተተ/ተረገረገ/ተቀበረ።
ተጐደፈረ (ተጐጽፈረ)፡ ተጫረ/ተመነቀረ/ተማሰ/ተቈፈረ/ተዛቀ/ተበተነ ።
ተጐዳ (ተጐድዐ)፡ ተመታ/ተሰበረ ።
ተጐዳ፡ በዋጋ ተበለጠ።
ተጐዳ፡ ዐጣ። "አከሌ ልጁን ተጐዳ" እንዲሉ።
ተጐዳ፡ ከሳ/ተጠነ/መነመነ፡ "የተይ ጥቍር የረዥም ዐጪር የወፍራም ቀጪን ኾነ" (ምሳ. ፳፪፡ ፫) ።
ተጎዳሪ፡ አላጋጭ/ነቃፊ።
ተጐዳቢ፡ የሚጐደብ (ተቈፋሪ)።
ተጐዳኘ (ገሐሠ)፡ ወደ ቤት ገባ/ጐራ አለ ።
ተጐዳዳ፡ ተሰዳደለ ።
ተጐጂ፡ የሚጐዳ/የሚርበው/የሚጠማው/የሚቸግረው ።
ተጐጂነት፡ ራብተኛነት/ችጋረኛነት።
ተጐጐመ፡ ተለተመ/ተወጋ።
ተጐጠረ፡ ተጐሰረ/ተወጠረ ።
ተጐጠጐጠ፡ ተመዘዘ/ተነቀለ ።
ተጐጠጐጠ፡ ተወጋ/ወጣ/ተቦጠቦጠ ።
ተጐፈጨረ፡ ተጨቈነ/ተጫረ/ተመረረ ።
ተጓመተ፡ ተቋረጠ/ተካፈለ ።
ተጓመደ፡ በዱላ ተማታ/ተደባደበ ።
ተጓመደ፡ ተጓረደ/ተሳለበ ።
ተጓረሠ፡ መብል ተሰጣጠ (ባፍ ተቀ ባበለ) ።
ተጓረበ፡ ተራገበ/ተጨማደደ ።
ተጓረደ፡ ተቋረጠ (በዱላ ተማታ) ።
ተጓረጠ፡ ተፋጠጠ/ተሞጫጨረ ።
ተጓሸመ፡ ተዳሰቀ/ተዳሰመ ።
ተጓበጠ፡ ተቃለሰ፡ ተዛባ ።
ተጓተተ፡ ተሳሳበ/ተዋሰደ ።
ተጓታች፡ የተጓተተ/የሚጓተት (ተሳሳቢ) ።
ተጓዘ (ግዕዘ)፡ ዘገመ/ዝግ ብሎ ኼደ ።
ተጓዥ፡ የሚጓዝ (ዘምተኛ/መንገደኛ/ቤተ ሰብ) ።
ተጓደለ፡ ተናነሰ/ተቀናነሰ ወይም ጐደለ/ቆመ/ተቋረጠ (ሥራው/ስጦታው) ።
ተጓደደ (ጓደደ)፡ ኰራ/ተደገገ/ታበየ/ታጀረ (ዘኍ. ፲፭፡ ፴፡ ዘዳ. ፰፡ ፲፬፡ ኢሳ. ፴፡ ፲፭፡ ሮሜ. ፪፡ ፳፫) ።
ተጓደደ፡ ካለ ጓዴ አለ፡ በጓደኛው ተመካ ።
ተጓደፈ፡ ተዳደፈ/ተቋሸሸ/ተራከሰ (ጕድፋም ተኳዃነ መሬቱና ፍጉ ተባላ) ።
ተጓዳ (ተጓድዐ)፡ ተባደለ ።
ተጓዳኝ፡ የሚጓደን (ተዘላኝ)።
ተጓዳጅ፡ የሚጓደድ (ኵሩ/ተደጋጊ) (ምሳ. ፳፩፡ ፳፬) ።
ተጓዳጆች፡ የሚጓደዱ (ተደጋጎች) (ሮሜ. ፩፡ ፴)።
ተጓጐለ (ተሃጐለ)፡ ተጣፋ ተጠፋፋ፡ ተሰናከለ ተሰነካከለ ። (፪ዜና ፲፮ ፥ ፭) ።
ተጓጐጠ፡ ተወጋ/ተሸቀሸቀ/ተቈሰቈሰ ።
ተጓጓዘ (ተጋዐዘ)፡ ተዛገመ/ተዘጋገመ ።
ተጠለለ (ተጸለለ)፡ ከዝናም በቤት በዋሻ ከፀሓይ በጥላ በዛፍ ሥር ተጠጋ/ዐረፈ ("ተከለለ ተጋረደ ተሸፈነ ሚካኤል ሚካኤል ባንተ ጥላ ልጠለል እንዲል ታቦት ዘፋኝ") ።
ተጠለለ (ጠለለ)፡ ላይ ላዩ ተቀዳ ("ተጨለፈ") ።
ተጠለቀ ("ተደገ ደገ ታሰረ ተቦደነ ተለባሽ የሚለበስ ' የሚጠለቅ ") ።
ተጠለቀ፡ ተለበሰ ።
ተጠለቀ፡ ተመረመረ ።
ተጠለቀ፡ ተገባ/ተገባበት ።
ተጠለቀ፡ ተጠቀሰ/ተጨለፈ/ተቀዳ ።
ተጠለቅ፡ ተመርመር ።
ተጠለፈ፡ ተሰረጀ/ተሰናከለ ("ተያዘ") ።
ተጠለፈ፡ ተሣለ/ተመሰለ/ተጌጠ/ተሸለመ/ተዘመዘመ ።
ተጠለፈ፡ ተነጠቀ/ተወሰደ ።
ተጠላ (ተጸለለ)፡ ተወጠረ/ተዘረጋ ("ጥላው ተከለለ ተጋረደ ፀሓዩ ሰዉ በጥላ") ።
ተጠላ (ተጸልአ)፡ ተነቀፈ ፥ ተጸየፈ ተሰለቸ/ረከሰ ።
ተጠላለፈ፡ ተወሳሰበ/ተያያዘ/ተቈላ ለፈ ።
ተጠላላ፡ ተነቃቀፈ/ተቈራረጠ/ተበጣ ጠሰ ።
ተጠላላፊ፡ የሚጠላለፍ ("ተወሳሳቢ") ።
ተጠላፊ፡ የሚጠለፍ ("ተዘምዛሚ") ።
ተጠመለለ (ተጠብለለ)፡ ታጠፈ/ተ ቈለመመ ።
ተጠመሰሰ፡ ተጣሰ/ተለጠሰ/ተኛ ።
ተጠመረ (ተፀመረ)፡ ተደረበ/ተደ መረ/ተቀረቀበ ።
ተጠመቀ፡ ተነከረ/ታጠበ/ጠበለተ ኛው ።
ተጠመቀ፡ ተጠመዘዘ ("ሸማው") ።
ተጠመቀ፡ ተጨመቀ ("ጥሩ ኾነ ማሩ ዘይቱ ወይኑ") (ዘሌ. ፳፬፡ ፪) ።
ተጠመቀ፡ ክርስትና ተነሣ ("ሕፃኑ አረመኔው") (ማር. ፩፡ ፱) ።
ተጠመቀ፡ ውሃ ተመላበት/ተበጠበጠ/ ተዘለለ ("ተሾመ ጠላው") ።
ተጠመነ፡ ተጋዛ ("የርሻ ውል ተዋዋለ") ።
ተጠመዘዘ፡ ዞረ/ተመለሰ/ተገመደ/ ከረረ ።
ተጠመደ፡ ተበጀ/ተዘጋጀ/ተሸሸገ ' ወጥመዱ ።
ተጠመደ፡ ተጠላ/ተመረዘ ።
ተጠመደ፡ እቀንበር ገባ ("ዐንገቱ ታሰረ ተገዛ አገለገለ") ።
ተጠመደ፡ ጥይት ጐረሠ ("ተለጐመ") ።
ተጠመጠመ፡ ተሸበለለ/ተጠቀለለ/ተ ደመረ/ተከበሰ ("ገመዱ ጠፍሩ ጠጕሩ") (፪ ሳሙ. ፲፰፡ ፱፡ ኢዮ. ፰፡ ፲፯) ።
ተጠሚ፡ የሚጠማ ።
ተጠማ (ተጠምዐ)፡ ተነከረ ("ራሰ") ።
ተጠማ (ጠማ)፡ በጥም ተያዘ ("አፉ ደረቀ ኵበት ኾነ (ተረት) የተጠማ ከፈሳሽ የተበደለ ከነጋሽ") ።
ተጠማለለ፡ ተጣጠፈ/ተቈላመመ ።
ተጠማመረ፡ ተገነኛኘ/ተጠማመደ ።
ተጠማመደ፡ ተቈረኛኘ/ተጠላላ ።
ተጠማሪ፡ የሚጠመር ("ተቀርቃቢ") ።
ተጠማቂ፡ የሚጠመቅ ("ጠላ ሰው ተጠምዛዥ ልብስ") ።
ተጠማኝ፡ ተጋዢ ("የሰው መሬት ዐ ራሽ (ተረት) ተጠማኝ ቢሰነብት ባለርስት ይኾናል") ።
ተጠማዘዘ፡ ተዘዋወረ/ተጣመመ/ተጋ መደ ።
ተጠማጅ፡ የሚጠመድ ("በሬ አሽክላ አይጠመድም አይገኝም አይያዝም") ።
ተጠማጠመ፡ በ፪ እጁ የሰውን ወገብ ዐንቆ ያዘ (ማሕ. ፫፡ ፬) ።
ተጠማጠመ፡ ተሸባለለ/ተጠቃለለ ("የመጠምጠም ብድር ተከፋፈለ") ።
ተጠምዛዥ፡ የሚጠመዘዝ ።
ተጠምጣሚ፡ የሚጠመጠም ("እባብ ዘ ንዶ") ።
ተጠሞረ፡ ተደረበ/ተሸረበ ("ተሸርቦ ተከረረ ተደወረ") ።
ተጠሰቀ፡ ተመታ/ተደሰቀ ።
ተጠሰቀ፡ ተወጠቀ/ተጠቀጠቀ ።
ተጠረመሰ፡ ተሰበረ/ተፈጩ ።
ተጠረረ፡ ጥሩር አጠለቀ/ለበሰ ("ጦር እንዳይወጋው ቀስት እንዳይነድፈው (ገቢር) ተጠረረ ተጠለቀ ተለበሰ ጥሩሩ (ተገ ብሮ)") ።
ተጠረቀ፡ ተወጋ/ተሰመረ/ተቸነከረ ("ብረት ለበሰ") (ኣስቴ. ፰፡ ፲፬) ።
ተጠረቀመ፡ ገባ ("ጥብቅ ኾነ ታሰረ ተዘጋ") ።
ተጠረቃቀመ፡ ተሰባሰበ/ተከመቻቸ ።
ተጠረበ (ተጸርበ)፡ ታነጠ/ተሸለተ ሾለ/ሣሣ/ቀጠነ/ጠፈጠፈ ።
ተጠረነቀ፡ ታሰረ ("ጥብቅ ኾነ ድርጭት መሰለ") ።
ተጠረኘ፡ ተከፈለ/ተዘገነ/ተያዘ ("ጥርኙ እኸሉ ውሃው በጥርኝ") ።
ተጠረኘ፡ ጥርኝ ኾነ ።
ተጠረገ፡ ተዛቀ/ተማጠጠ ።
ተጠረገ፡ ታደፈ/ታበሰ/ተወለወለ ("ጠዳ ጠራ (ተረት) ቍንጫ የተጠረገ ለት ባለጌ የተመከረ ለት") "
ተጠረገ፡ ታጨደ/ተቈረጠ/ተመነጠረ ።
ተጠሪ (ዎች)፡ የሚጠራ ("ወኪል ቶፋ ምትክ የሌላ ሰው ንብረት ጠባቂ") ።
ተጠሪነት፡ ወኪልነት/ቶፍነት ።
ተጠራ፡ ተወከለ/ተተካ ።
ተጠራ፡ ተጮኸ ("ና ተባለ ለግብዣ ለሰርግ ለዕድር ለሌላም ጕዳይ ቃል'ዐለፈ ለት") ።
ተጠራረገ፡ ተባበሰ/ተወዛዛ ።
ተጠራራ፡ ተጯጯኸ ("ና ተባባለ") ።
ተጠራቀመ፡ ተጠናቀረ/ተሰበሰበ/ተዘ ገበ/ተከማቸ ("ገንዘቡ ሰዉ ውሃው") ።
ተጠራቂ፡ የሚጠረቅ ።
ተጠራቃሚ፡ የሚጠራቀም ።
ተጠራቢ፡ የሚጠረብ/የሚታነጥ ።
ተጠራጊ፡ የሚጠረግ ።
ተጠቀለለ፡ ተሰበሰበ/ተኰሰተረ/ተሸበለለ/ተጠመጠመ ("ክብ ኾነ ዐረጉ ልጡ ገመዱ ድንኳኑ ወረቀቱ ብራናው ቍርበቱ") (ሕዝ. ፪፡ ፱) ።
ተጠቀለለ፡ ተፈጸመ/ተጨረሰ ።
ተጠቀመ (ተጠቅበ)፡ ተሰፋ/ተጣፈ/ተደረተ/ተለገበ (ኢያ. ፱፡ ፭) ።
ተጠቀመ፡ ጠኀበ/ረካ/ጥቅም አገኘ/ተረባ (ኢሳ. ፵፯፡ ፲፪) ።
ተጠቀሰ፡ በምልክት ተጠራ ።
ተጠቀሰ፡ ተባለ/ተነገረ ጥቅሱ ።
ተጠቀሰ፡ ተነካ/ተሳበ/ተጐተተ/ቀ ረበ ("ተማረ") ።
ተጠቀሰ፡ ተኰሰተረ/ተተረኰሰ ።
ተጠቀሰ፡ ገባ/ተነከረ ("እንጀራው ተጠ ለቀ ወጡ") ።
ተጠቀጠቀ፡ ባ፭ ጣት ተወጋ ("ታ ተመ ድፎው ጥፍጥፉ ተነቀሰ ጥርሱ") ።
ተጠቀጠቀ፡ ተረገጠ/ተረመረመ ።
ተጠቀጠቀ፡ ተበላ/ተወጠቀ ።
ተጠቀጠቀ፡ ተደፈነ/ተዘጋ/ጨለመ ።
ተጠቀጠቀ፡ ተጠጋጋ/ተቃረበ ።
ተጠቂ፡ የሚጠቃ ("ጥቃተኛ") ።
ተጠቃ (ች)፡ ተወጋ/ተሰረረ ("የሚ ነገረው ለጊደር ነው") ።
ተጠቃ፡ ተገፋ/ተበደለ/ተሸነፈ/ተዋረደ/ተጐዳ/ተጨቈነ (ምሳ. ፲፪፡ ፱፡ ኢሳ. ፪፡ ፲፩፡ ሰቈ. ፩፡ ፲፩፡ ፪ ቆሮ. ፲፫፡ ፯) ።
ተጠቃለለ (ተጠቀለለ)፡ ተፈጸመ/ ተከናወነ ("ጣጣው ዐለቀ") ።
ተጠቃለለ፡ ተሸባለለ/ተጠማመተ ።
ተጠቃለለ፡ ዐረፈ/ሞተ/አንድ ወገን ኾነ ("ተከፈነ ተገነዘ") ።
ተጠቃሚ፡ የሚጠቀም/የሚረባ ("ተረቢ") ።
ተጠቃሚነት፡ ተጠቃሚ መኾን ።
ተጠቃሽ፡ የሚጠቀስ/የሚባል/የሚነገር ("የሚጠራ") ።
ተጠቃቀመ፡ ተሰፋፋ/ተጣጣፈ ።
ተጠቃቀመ፡ ተረባባ ("ጥቅም ተሰጣጠ ተቀባበለ") ።
ተጠቃቀሰ፡ ተነካካ ("በምልክት ተነገረ ዐይን ላይን ተገናኘ ተቀጣጠበ (ተረት) በዕውር ይጠቃቀሱበታል በደንቈሮ ይሾካሾኩበታል") ።
ተጠቃቃሚ፡ የሚጠቃቀም ።
ተጠቃጠቀ፡ ተረጋገጠ/ተረማረመ ።
ተጠቃጠቀ፡ ተበሳሳ/ተነቃቀሰ ።
ተጠቃጠቀ፡ ተደፋፈነ/ተደባበቀ ።
ተጠቈመ፡ ላመል ተወጋ ("ተጫረ ታ ድሩ") ።
ተጠቈመ፡ ምልክት ተቀበለ ።
ተጠቈመ፡ ተሳበ/ታረቀ/ተተካከለ ("ባይ") ።
ተጠቈረ (ጠቈረ)፡ ተነቀስ/ተወቀረ ጥርሱ ።
ተጠቈረ፡ በመርፌ/በሾኸ ተሣለ ("ታ ተመ ገላው") ።
ተጠቈረ፡ ተጐነፈ ("ዘንጋዳው") ።
ተጠቅላይ፡ የሚጠቀለል ("ተሸብላይ") ።
ተጠቅጣቂ፡ የሚጠቀጠቅ ("ተደፋኝ ተረ ምራሚ") ።
ተጠቋሚ፡ የሚጠቈም ("ምልክት ተቀ ባይ") ።
ተጠቋቈረ፡ ተነቃቀሰ ።
ተጠበሰ፡ በጥይት ተመታ ።
ተጠበሰ፡ ተተኰሰ/ተቃጠለ ።
ተጠበሰ፡ ፈላ/በሰለ/ተቈላ/ተንቃቃ ደረቀ ።
ተጠበረ፡ ተሠራ/ተጌጠ/ተሸለሙ አ ማረ ።
ተጠበቀ (ተዐቅበ)፡ ተከለከለ/ታገደ/ተወሰነ ("ከክፉ ነገር ራቀ ተጠነቀቀ") (ዘዳ. ፬፡ ፳፫፡ ሕዝ. ፴፫፡ ፭) ።
ተጠበቀ፡ ቈየ/ዘገየ/ተመደበ/ተወሰነ ("ኀጢአተኛ ለክፉ ቀን ይጠበቃል") (ኢዮ. ፳፩፡ ፴) ።
ተጠበቃዬ፡ የሳምንት ቀጠሮ ("ከጠበቃዬ ጋራ ማለት ነው") ።
ተጠበቅ (ተዐቀብ)፡ ተጠንቀቅ ("ከ ኀጢአት ተወገድ ራቅ") (ዘዳ. ፰፡ ፲፩) ።
ተጠበበ (ጠበበ)፡ ተተንኰለ/ተንኰል አደረገ (ዘፀ. ፩፡ ፲፡ አስቴ. ፰፡ ፫) ።
ተጠበበ፡ ተለቀመ/ተዋሰበ/ተሠባጠረ ("ተጣለ ተሠራ ጥበቡ ተፈለሰፈ") ።
ተጠበበ፡ ተጨነቀ/ተቸገረ ።
ተጠበበ፡ ተጨነቀ/ተቸገረ.
ተጠበበ፡ ዐወቀ/ተራቀቀ ("ፈላስፋ ብልኀተኛ ኾነ") ።
ተጠበጠበ (ተጠብጠበ)፡ ተገረፈ/ ተሸነቈጠ/ተመታ ።
ተጠበጠበ፡ ተበለተ/ተጠባ ።
ተጠበጠበ፡ ተቸኰለ/ተገሠገሠ ።
ተጠቢ (ተጠባሒ)፡ የሚጠባ/የሚ በለት ።
ተጠቢ (ተጠባሒ)፡ የሚጠባ/የሚ በለት.
ተጠባ (ተጠብሐ)፡ ተበለተ/ተቈ
ተጠባ (ተጠብሐ)፡ ተበለተ/ተቈ
ተጠባ (ተጠብወ)፡ ተሳበ/ተጐተተ/ተመጠጠ/ተመጠመጠ/ተመገመገ/ ተ ጠጣ ።
ተጠባሪ፡ የሚጠበር ("ተሸላሚ") ።
ተጠባሽ፡ የሚጠበስ/የሚቈላ ።
ተጠባቂ፡ የሚጠበቅ ዕቃ/ሰው ።
ተጠባበቀ (ተዓቀበ)፡ ተከላከለ/ተ ከታተለ ("የሚያደርገውን የሚናገረውን አየ ሰማ") (ማቴ. ፱፡ ፲፯፡ ሉቃ. ፭፡ ፴፰) ።
ተጠባበቀ፡ ተዋሰነ/ተወሳሰነ ።
ተጠባባቂ፡ ተከታታይ/ሰላይ ("ነገር አቀባይ") ።
ተጠባባቂነት፡ ሰላይነት ("የክፉ የበጎ") ።
ተጠባጠበ፡ ተጋረፈ/ተሸናቈጠ ።
ተጠብጣቢ፡ የሚጠበጠብ ("ተገራፊ") ።
ተጠቦ፡ ተጨንቆ/ተቸግሮ ።
ተጠቦ፡ ተጨንቆ/ተቸግሮ. "እከሌ ቤቱን ተጨንቆ ተጠቦ ሠራ እንዲሉ".
ተጠነሰሰ (ተፀንሰ)፡ ተበጠበጠ ("ጥን ስስ ኾነ") ።
ተጠነሰሰ፡ ተፀነሰ/ተረገዘ ("በሆድ ቀረ ተቋጠረ") ።
ተጠነቀለ፡ ተቈነጠረ ("ላመል ተወሰደ") ።
ተጠነቀቀ፡ ተዘጋጀ/ተኰሰተረ/ተከ ወነ/ተፈጸመ/ተጨረሰ ።
ተጠነቀቀ፡ ተጋ/ተጠበቀ ።
ተጠነቈለ፡ ተረተ/ተደረገ ("ጥንቈላው") ።
ተጠነቈለ፡ ተወጋ/ተደነቈለ/ተነቈረ ።
ተጠነቋቈለ፡ ተነቋቈረ ።
ተጠነበፈ፡ ተገደለ ' ወደቀ ' ተጣለ ("ጥ ንብ መሰለ") ።
ተጠነባበረ፡ ተደነባበረ ።
ተጠነካከረ፡ ተጠናና/ተበረታታ (ሕዝ. ፳፩፡ ፲፮) ።
ተጠነገደ፡ ሞተ/ተጨረሰ/ዐለቀ ("ሽቅ አለ እንደ ሰናክሬም ሰራዊት") ።
ተጠነጠነ (ተጸንጸነ)፡ ተጠቀለለ/ ኮበ/ተደወረ/ተዳወረ ።
ተጠነፈፈ፡ ውሃው ከንፍሮ ውስጥ ፈሰሰ/ተንጠፈጠፈ ("ንፍሮው ከውሃ ተለየ") ።
ተጠና፡ ታወቀ ("ልብ ተደረገ በቃል ተያዘ ትምርቱ") ።
ተጠናቀረ፡ ተጠራቀመ/ተሰበሰበ/አንድነት ኾነ ("ተከማቸ") ።
ተጠናቀቀ፡ ተከናወነ ።
ተጠናቈለ፡ ተናቈረ/ተተናኰለ/ተጋፋ/ተጠነቋቈለ ("የጥንቈላ ብድር ተከፋ ፈለ") ።
ተጠናበረ፡ ተደናበረ ።
ተጠናና፡ ተበረታታ ።
ተጠናከረ፡ ተጣና/ተበራታ ("ጠንካራ ተኳዃነ") ።
ተጠናወተ፡ ወረደ (ጠነወተ) ።
ተጠናወተ፡ ዘወትር ዐመመ ("ጨነገፈ ወረደ በምች በክፉ ሽታ") ።
ተጠናወታት፡ ወረዳት ("ፅንሱ ሽሉ") ።
ተጠናገረ፡ ተጠናበረ ።
ተጠንቀቅ፡ ዕወቅ/ተጠበቅ/ትጋ/ንቃ/ ኰስተር በል ።
ተጠንቃቂ፡ የሚጠነቀቅ ።
ተጠወረ (ተጸውረ)፡ ሸክም ኾነ ("ተያዘ ተወሰነ ተቻለ ተለመደ") ።
ተጠወረ፡ ተጦረ ።
ተጠዋለገ፡ ተለዋወጠ/ተጣቈረ ።
ተጠዋሪ (ዎች)፡ የሚጦር ("በሰው ትከሻ የሚኖር ጡረተኛ") ።
ተጠዋሪነት፡ ተጠዋሪ መኾን ("ጡረተኛነት") ።
ተጠዘለ፡ ተመታ/ተመደወተ ("ተጠዘለ ደነደነ ወፈረ") ።
ተጠዘጠዘ፡ ተነደፈ/ተወጋ ("ተጠዘጠዘ ተነዘነዘ ተነዘረ") ።
ተጠዛጠዘ፡ ተናደፈ/ተዋጋ ።
ተጠየረ፡ ሠገረ/በረረ/ከነፈ ("ተጠየረ ተዘጋጀ ተደራጀ ተጠየረ አለመጠን ኰራ ምድርን ለመርገጥ ተጸየፈ") ።
ተጠየቀ፡ ተመረመረ፡ የሚኾነውን፡ ንገ ረኝ፡ ተባለ፡ ነቢዩ፡ ጠንቋዩ፡ (ሕዝ፳፡ ፫፡ ፴፩) ። ተጠየቀ፡ ተሞገተ፡ ተጠየቅ፡ ተባለ ።
ተጠየቅ፡ የጠያቂ፡ ሙግት፡ አዝማች ወይም፡ መነሻ ። (ግጥም)፡ ተጠየቅ፡ ጠይቀኝ፡ ማር፡ እሰጥ፡ አገባ፡ እንዴት፡ ይዘለቃል፡ የጎረ ቤት፡ ሌባ ። ተጠየቅ፡ ተጠለቅ፡ እንዲሉ ።
ተጠየቅታ፡ ተጠየቅ፡ ማለት፡ ጥያቄ፡
ተጠየተ፡ በጥይት ተመታ/ተገደለ ("እንደ አቡነ ጴጥሮስ") ።
ተጠየተ፡ ተሠራ/ተበጀ ("ጥይቱ ተጠየተ ተሰበሰበ ታሰረ - ዛላው እ ሸቱ") ።
ተጠየፈ፡ ተጠላ፡ ተነቀፈ ። ልማዱ፡ ግን፡ እንደ፡ ኹለተኛው፡ አጠየፈ፡ ጠላ፡ ነቀፈ፡ ነው ። ተጠያፊ፡ የሚጠየፍ፡ ነቃፊ ። ጥዩፍ፡ ጥይፍ፡ የተጠየፈ፡ ሸቍራራ፡ ንቁፍ፡ የነቀፈ ።
ተጠያሪ፡ የሚጠየር ("ሠጋሪ በራሪ") ።
ተጠያቂ፡ ተሞጋች፡ ተየካሽ ።
ተጠያየቀ፡ ተጐበኛኘ፡ ተፈቃቀደ ። ተጠያያቂ፡ የተጠያየቀ፡ የሚጠያየቅ፡
ተጠጀ፡ ተጣለ/ተበጠበጠ ።
ተጠገረ፡ ለጠገራ ተለወጠ/ተሼጠ ።
ተጠገረረ፡ ተደበለለ/ተሸከመ ("ተጠገረረ በሸክም ተያዘ") ።
ተጠገበ፡ በቃ/ተሰለቸ/ተተወ ("የሰው ገንዘብ አይጠገብም እንዲሉ") ።
ተጠገተ፡ ታለበ ("ላሙ ጡቱ ወተቱ") ።
ተጠገነ፡ ታሰረ/ተጠቀለለ/ታከመ/ተፈ ወሰ/ዳነ/ታደሰ ።
ተጠገነ፡ ታገዘ/ተረዳ ።
ተጠጊ፡ የሚጠጋ ("ቀራቢ") ።
ተጠጋ፡ ቀረበ ("በጥግ ቆመ ተቀመጠ ተደገፈ ተማጠነ") (፪ ሳሙ. ፬፡ ፫) ።
ተጠጋኝ፡ የሚጠገን ("ታዳሽ") ።
ተጠጋገነ፡ ተሳሰረ/ተጠቃለለ/ተዳደ ።
ተጠጋገነ፡ ተረዳዳ/ተጋገዘ ።
ተጠጋጊ፡ የሚጠጋጋ ("ተደጋጋፊ") ።
ተጠጋጋ፡ ተቀራረበ/ተደጋገፈ ።
ተጠግቶታል፡ ቀርቦታል/ዐድሮበታል ("ሰይጣን ተጠግቶታል እንዲሉ") ።
ተጠጠ፡ ተጠረገ፡ ተጨረሰ፡ ዐለቀ።
ተጠጠተ (ተጸጸተ)፡ ተቈጨ/ዐዘነ/ ተቈረቈረ (፩ ሳሙ. ፲፭፡ ፴፭፡ ማቴ. ፳፩፡ ፳፱) ።
ተጠጣ፡ ፉት ተባለ ("ተማገ ተጨለጠ ወደ አንዠት ወረደ ገባ መጠጣት ጕንጭ መባል") ።
ተጠጣች፡ የሚጠጠት ("ዐዛኝ") ።
ተጠፈረ (ተጸፍረ)፡ ተቈረጠ/ተከረ ከመ ጥፍሩ ።
ተጠፈረ፡ በጠፍር ታሰረ/ተተበተበ/ተገረፈ ("ተታታ ተማገረ ተጐለበ") ።
ተጠፈነ (ተጸፍነ)፡ ተጠለፈ/ታሰረ/ ተዘጋ ።
ተጠፈነነ፡ ተጀነነ/ኰራ ።
ተጠፈጠፈ (ተጸፍጸፈ)፡ ተዘረጋ/ ሣሣ/ተነጠፈ/ተለበጠ ።
ተጠፈጠፈ፡ በጥፊ ተመታ/ተወለወለ ።
ተጠፋ (ተጠፍሐ)፡ በጭን ላይ ተ ነዘረ ።
ተጠፋ፡ ተጨበጨበ ።
ተጠፋጠፈ፡ በጥፊ ተማታ/ተወላወለ ።
ተጠፋፈጠ፡ ተጣጣመ ።
ተጠፋፋ፡ ተገዳደለ/ተተ ማተ ።
ተጠፍጣፊ፡ የሚጠፈጠፍ/የሚሣሣ ።
ተጣለ (ተጽዕለ/ተጥሕለ)፡ ተወረወረ/ተገደፈ/ወደቀ/ተተወ (፪ ዜና. ፲፰፡ ፲፬፡ ኢሳ. ፲፩፡ ፲፪፡ ፴፬፡ ፫፡ ዳን. ፫፡ ፮፡ ራእ. ፲፪፡ ፱, ፲፫) ።
ተጣለ፡ ተናደ/ተዘረጠጠ ("ተጣለ ተኛ ተጋደመ ተጣለ ተጨመረ ገባ ተዶለ ተጣለ ተበጠበጠ ታሸ ማሩ") ።
ተጣለፈ፡ ተሰራጀ/ተዋሰበ/ተቋለፈ ።
ተጣላ (ተጻልአ)፡ ተፃረረ/ተቃረነ/ተቃወመ ("ሰላም ዐጣ ሳይስማማ ቀረ (ተረት) ሳይጣሉት የተጣላ ሲርብ ያበላ አይረሳም የቀረው ነው አህያ የለኝም ከዥብ አልጣ ላም (ውሻ አይበላሽ ጥል ተጣላ) በምድር ድንበር በሴት ከንፈር ስለ ተገናኘ ዕርቅ አልባ ኾነ (ከፈሱ የተጣላ) እብድ") ።
ተጣመ (ተጥዕመ)፡ ተቀመሰ ።
ተጣመመ፡ ተጠማዘዘ/ተንጋደደ/ተወ ላገደ ።
ተጣመረ (ተፃመረ)፡ ተገናኘ/ተጣ መደ/ተዋደደ/ተያያዘ ("ድርና ማግ ኾነ የተባትና የእንስት") ።
ተጣመደ፡ ተቈራኘ/ተጣላ ።
ተጣማ፡ ተቀላቀለ/ተደባለቀ/ተያያዘ ።
ተጣማሚ፡ የሚጣመም ("ተንጋዳጅ") ።
ተጣማሪ፡ የሚጣመር ("ተያያዥ") ።
ተጣማጅ፡ የሚጣላ ።
ተጣማጅ፡ የሚጣመድ ("ትክክል የሚ ያርስ የሚስብ በሬ") ።
ተጣሰ፡ ተወደደ/ተሰበረ/ተረገጠ/ተኛ/ተነደለ/ተቀደደ/ፈረሰ ።
ተጣሰ፡ ተፈጨ ።
ተጣረ፡ ተተጋ/ተለፋ/ተደከመ ።
ተጣረሰ፡ ተሳሳተ/ተበላሸ/ተቃወሰ ("የሙግት የክርክር የነገር") ።
ተጣረሰ፡ ተጋጨ ጥርሱ ።
ተጣረረ (ተፃረረ)፡ ተጣላ ("ጥል እበ ቀለ") ።
ተጣረገ፡ ተጫጨደ/ተመናጠረ ።
ተጣሪ፡ የሚጣራ ("ጠሪ") ።
ተጣራ (ተጣርአ/ተጻርሐ)፡ ጠራ ።
ተጣራ (ተጻረየ/ተናጽሐ)፡ ተናጻጥሩ ኾነ ("ተኳዃነ") ።
ተጣራ፡ ፈጽሞ ተሼጠ ።
ተጣራሪ (ተፃራሪ)፡ የሚጣረር ተጣይ ("የማይሰማማ እሳትና ውሃ ዐይንና ፈር የመሰለው ኹሉ") ።
ተጣቀመ፡ ተያያዘ/ተማላ ።
ተጣቀሰ፡ በቅንድብ/በከንፈር ተጣራ ።
ተጣቀሰ፡ ተናካ/ተሳሳበ ።
ተጣቈሰ፡ ተደገመ ("ዘሩ") ።
ተጣቈሰ፡ ተጐሸመጠ/ተደፈረ ።
ተጣቈረ፡ ተናቀሰ ።
ተጣቈረ፡ ተጐሳቈለ/ተዳደፈ ።
ተጣበሰ፡ በጥይት ተቋላ/ተማታ ።
ተጣበሰ፡ ተጋረፈ/ተሸናቈጠ ።
ተጣበቀ፡ ተላከከ/ገጠመ/ተሰማማ/ ተያያዘ ("አልላቀቅ አለ ደገደገ") (፪ ነገ. ፭፡ ፳፯፡ ፲፰፡ ፮) ።
ተጣበበ፡ ተጠጋጋ/ተጫነቀ ("እንደ ሮ ማን ኾነ") ።
ተጣበበ፡ ተጠጋጋ/ተጫነቀ ("እንደ ሮ ማን ኾነ").
ተጣባ (ተጣበወ)፡ ተመጋመገ/ተ ማጠጠ ።
ተጣባ (ተጻብሐ)፡ የጧት ሰላምታ ተሰጣጠ ("እንዴት ዐደርክ ተባባለ") (፪ ነገ. ፬፡ ፳፱) ።
ተጣባ (ተጻብአ)፡ ተጣላ/ተዋጋ ።
ተጣባ፡ እመስከረም ተቃረበ (ደረሰ) ።
ተጣባቂ፡ የሚጣበቅ ("ተላካኪ") ።
ተጣና፡ ተበራታ/ተጠናከረ ።
ተጣወረ (ተጻወረ/ተካሀለ)፡ ተቻ ቻለ/ተላመደ ("እከሌ ይህን ሥራ ተጣውሮታል") ።
ተጣዘለ፡ ተማታ/ተመዳወተ/ተጣረዘ ።
ተጣይ (ተጸዓሊ/ተጠሓሊ)፡ የሚ ጣል ("ወዳቂ") ።
ተጣይ (ተጻላኢ)፡ የሚጣላ/ተፃራሪ ("ተቃራኒ") ።
ተጣይ፡ የሚጣላ፡ ጠላ ።
ተጣይ የሚጣል፡ ጣለ ።
ተጣደ፡ ተሰረረ/በላይ ኾነ/ተነ ።
ተጣደ፡ ዐለፈ/ተሰጠ/ቀረበ/ተደቀነ ።
ተጣደፈ፡ ተቻኰለ/ተዋከበ ።
ተጣዳፊ፡ የተጣደፈ/የሚጣደፍ ("ጥዱፍ") ።
ተጣዳፊነት፡ ችኩልነት ።
ተጣገበ፡ ተባቃ/ተሰላቸ ።
ተጣጋ (ተጣግዐ/ተፃግዐ)፡ ደረቀ/ተቃረበ/ልጥቅ አለ ("የሆድ የምላስ") (ኢዮ. ፳፱፡ ፲፡ መዝ. ፳፪፡ ፲፭፡ ፵፬፡ ፳፭) ።
ተጣጠረ (ተሓጸረ)፡ ተካበበ/ተካለለ ።
ተጣጠቀ (ተዓጠቀ)፡ የትጥቅን ብ ድር ተመላለሰ ተጠማጠመ ("(ለባበሰ ጠማጠመ)") ።
ተጣጠበ (ተኃፀበ)፡ ተሻሸ/ተለቃ ለቀ/ተናጻ ።
ተጣጠነ (ተዓጠነ)፡ የዕጣንን ጪስ ተሰጣጠ (ተቀባበለ - "(እንዳጠነ ታጠነ)" - ተጫ ሰ ") ።
ተጣጠፈ (ተዓጸፈ)፡ ተኰራመተ ።
ተጣጣ (ተኃጥአ)፡ ሳይገናኝ ሳይተ ያይ ቀረ (ተረሳሳ ተራራቀ - "አፍና እጅ አይ ተጣጣም" እንዲሉ - "ጠጣን" ተመልከት ") ።
ተጣጣ (ጣእጥአ)፡ ተከናወነ/ተቻ ።
ተጣጣ ተረሳሳ፡ ዐጣ ።
ተጣጣ፡ ጥዋ ተቀባበለ ("ማኅበር ተከፋፈለ (ማኅበር ተጣጣ) ተዋደደ ተሰማማ ተፋቀረ") ።
ተጣጣለ፡ ተዋደቀ/ተወዳደቀ/ተገዳደመ ("የመጣልን ብድር ተከፋፈለ") ።
ተጣጣለ፡ ዕጣ ዕጣ ("ለዚህ ጌታ ይውጣ ተባባለ") ።
ተጣጣለ፡ ካንዱ አገር ወደ ሌላው ተላለፈ ።
ተጣጣመ (ተጣዐመ)፡ ተጠፋፈጠ/ ተፋቀረ/ተሰማማ ።
ተጣጣመ፡ ዐለቀ/ተጨረሰ/ተከናወነ ("ሥራው") ።
ተጣጣረ (ተጻዐረ)፡ ተጨናነቀ ("(ተጋ ታተረ)")
(ሮሜ. ፰፡ ፳፪, ፳፫፡ ፪ ቆሮ. ፭፡ ፱) ።
ተጣጣሪ፡ የተጣጣረ/የሚጣጣር ("ትጉህ ታታሪ") ።
ተጣጣቢ፡ ርስ በርሱ የሚተጣጠብ የሚናጻ ።
ተጣጣፈ፡ ተጋጠመ/ተገናኘ/ተሰማማ/ተኳዃነ ("የባልና የሚስት") ።
ተጣጣፈ፡ ተጻጻፈ ("ጥፈትን ተረዳዳ በደብዳቤ ተዋዋለ ተነጋገረ ተላላከ") ።
ተጣጣፊ፡ የሚጣጣፍ ("ተጻጻፊ ተዋዋይ") ።
ተጣፈ፡ ተጠቀመ/ተሰፋ/ተለጠፈ ።
ተጣፈ፡ ተጻፈ/ተከተበ ።
ተጣፈረ (ተጻፈረ)፡ ጥፍር ተቋረጠ ።
ተጣፈረ፡ በቃሪያ ጥፊ ተማታ ።
ተጣፈጠ (ጣፈጠ)፡ ጣፋጭ ኾነ ("በ ሰው ዘዴ") ።
ተጣፊ (ተጣፋኢ)፡ የሚጣፋ ("ተጋ ዳይ") ።
ተጣፋ (ተጣፍሐ/ተጻፍዐ/ተመላትሐ)፡ በጥፊ ተጠፋጠፈ ።
ተጣፋ (ተጣፍአ)፡ ተጋደለ/ተተ ማተ ።
ተጣፋ፡ ሽው አለ ("ዐይንን አሳበጠ") ።
ተጣፋ፡ ተሻኰተ/አገና/ተማታ ("ኣጥ ፋኝ አላጥፋኸ ተባባለ የገዢና የሸያጭ") ።
ተጤነ፡ ታሰበ ("ልብ ተባለ ተመረመረ") ።
ተጥለቀለቀ፡ ተንጣለለ ("ውሃ ለበሰ ተሸፈነ") ።
ተጥመለመለ፡ ተዝለፈለፈ/ተሽመደ መደ ("እንደ ጠፍር ኾነ") ።
ተጥመዘመዘ፡ ተፍተለተለ/ታመመ ።
ተጥረበረበ፡ ተሽቈጠቈጠ/ተለማመጠ ("ተርገበገበ ሰውን ለመጋበዝ") ።
ተጥረከረከ፡ ተጕደፈደፈ/ተኵለፈለፈ ።
ተጥበረበረ፡ ተብረቀረቀ ፡ አልታይ አለ ።
ተጥባበ ነገር፡ የነገር መልስ ዘዴ ።
ተጥባብ፡ ክፉ ምክር ።
ተጥናና፡ ተረጋጋ ።
ተጥወለወለ፡ ተናወጠ/ዞረ ("የነፋስ የልብ የራስ ዞር") ።
ተጦለ፡ ተጠረገ/ተገፈፈ/ተለየ/ተወገደ ።
ተጦመ፡ ሳይበላ ሳይጠጣ ቀረ ("ዋለ ጦም ኾነ ጊዜው") ።
ተጦረ (ተጸውረ)፡ ታዘለ ("ተጠዋሪ ኾነ ተቻለ ታገዘ ተረዳ") ።
ተጧሪ (ዎች)፡ የሚጦር ("የሚታገዝ የሚረዳ ሽማግሌ") ።
ተጧጧረ (ተጻወረ)፡ ተዛዘለ/ተሸ ካከመ ("ተረዳዳ ተጋገዘ ያሮጌና ያሮጊት") ።
ተጨለጠ፡ ተጨረሰ/ተነቀረ ።
ተጨለፈ፡ ተጠለቀ/ተቀዳ ("ከሰታቴ ከአፍላል ወጣ") ።
ተጨላፊ፡ የሚጨለፍ/የሚቀዳ ።
ተጨመላለቀ፡ የተጨማለቀ ("ድርብ በብዙ ወገን በፊት በኋላ በቀኝ በግራ ተዳደፈ") ።
ተጨመረ (ተፀመረ)፡ ገባ/ተላ/ተከተተ/ተሰናዳ (ማቴ. ፭፡ ፳፭) ።
ተጨመረ፡ ታከለ ("አንድ ኾነ ወረ") ።
ተጨመቀ፡ ተጨቈነ/ተጠመዘዘ/ተንጠፈጠፈ ("ውሃው ጥሩው ወለላው ወረደ") ።
ተጨመተረ/ተኰመተረ፡ ተጨመደደ ።
ተጨመታተረ/ተኰመታተረ፡ ተ መዳደደ ።
ተጨማለቀ፡ ነገር አበዛ ("ችክ ምን ችክ አለ ለፈደደን ተመልከት") ።
ተጨማመ፡ ተሳሳመ ።
ተጨማመረ፡ ተባበረ/ተነባበረ/ተደ ራረበ ።
ተጨማማሪ፡ የሚጨማመር ("ተነባባሪ") ።
ተጨማሪ፡ የሚጨመር/የሚታከል ! ("ተጨማሪ ዲያቆን እንዲሉ ኹለተኛ")
።
ተጨማሪነት፡ ተጨማሪ መኾን ("ዐባ ሪነት") ።
ተጨማተረ/ተኰማተረ፡ ተጨማደደ ።
ተጨምሮ፡ ታክሎ ።
ተጨረመደ፡ ተበላ ።
ተጨረማመተ፡ ተጨመዳደደ ።
ተጨረሰ፡ ተፈጀ/ተገደለ/ተፈጸመ/ዐለቀ ("ተከወነ ተደመደመ") (ኢዮ. ፴፪፡ ፲፭) ።
ተጨረገደ፡ ተቈረሰ/ተገመጠ ("ተበላ") ።
ተጨረገደ፡ ታጨደ/ተቈረጠ ።
ተጨረፈ፡ በቀላል በጥቂት ዥል ተመታ/ተቈረጠ ።
ተጨሪመተ/ተጨማተረ/ተጨማደደ ።
ተጨራመመ፡ ተጣመመ ።
ተጨራመደ፡ ተወጫመደ ።
ተጨራገደ፡ ተማታ/ተደባደበ ("በበሎታ") ።
ተጨራገደ፡ ተጫጨደ/ተቋረጠ ።
ተጨቀጨቀ፡ ተነዘነዘ/ተነተረከ ።
ተጨቀጨቀ፡ ተወቀጠ ።
ተጨቀጨቀ፡ ተጠቀጠቀ/ተደፈነ ።
ተጨቃጨቀ፡ ተነዛነዘ/ተነታረከ ።
ተጨቃጫቂ (ቆች)፡ የተጨቃጨቀ/የሚጨቃጨቅ ("ተነዛናዥ") ።
ተጨቃጫቂነት፡ ተጨቃጫቂመኾን ።
ተጨቈነ፡ ተረጠጠ/ታመቀ ("በታች ኾነ ተቸገረ ተጨነቀ") (ሉቃ. ፮፡ ፴፰፡ ዓሞ. ፪፡ ፲፫) ።
ተጨቈነ፡ ተጨፈቀ/ተለሰቀ ።
ተጨቋቈነ፡ ተጠጋጋ/ተወፋፈቀ ።
ተጨቋኝ፡ የሚጨቈን ("ተጨፋቂ ተለ ሳቂ") ።
ተጨበጨበ፡ ኾነ/ተደረገ ("ጭብጨ ባው እከሌ ስብቅል ነገር ስለ ተናገረ ጨበጨበለት") ።
ተጨነቀ (ተጽዕቀ)፡ ተጠበበ/ተቸገረ/ታወከ ("ግራ ገባው") (ዘፍ. ፮፡ ፮) ።
ተጨነቈረ፡ ደከመ/አነሰ ("ሊከደን ሊገ ጠም ጥቂት ቀረው ሸፋሽፍቱ") ።
ተጨነባበሰ፡ ተጫጫሰ 31
ተጨነገፈ፡ ተመለመለ/ረገፈ ።
ተጨነጓጐለ፡ ተጓጐለ/ተሰነካከለ ።
ተጨናቂ (ቆች)፡ የተጨነቀ/የሚጨ ነቅ (መክ. ፬፡ ፩) ።
ተጨናቈረ፡ ባንድ ዐይን ተያየ ("በ፪ኛው' አልተያየም") ።
ተጨናበረ፡ ተሳሳተ/ተደናገረ ።
ተጨናነቀ፡ ተጠጋጋ/ተቀራረበ/ተንታ በረ/ተደራረበ ።
ተጨናጐለ፡ ታጐለ/ተሰናከለ ("ሳይዋጣ ባጓጕል ቀረ") ።
ተጨከነ፡ ኾነ/ተደረገ ("ጭካኔው ተጨካከነ ሳይተዛዘን ቀረ") ።
ተጨወየ፡ ጨው/ጨዋ ኾነ ("ከ ተነሰነሰበት") ።
ተጨዋወተ፡ ተነጋገረ ("ጨዋታ ተመላለሰ ተለዋወጠ") ።
ተጨጐለ፡ ተጀጐለ ("ተከበበ ተጋረደ ተሸፈነ ተጌጠ ተሸለሙ አማረ ሰመረ ተንቈጠቈጠ") ።
ተጨፈለቀ፡ ተሠራ/ተቀጠቀጠ ("ጠገ ራው") ።
ተጨፈለቀ፡ ተረገጠ/ተዳጠ/ተደፈ ጠጠ ።
ተጨፈለቀ፡ ታረሰ/ተተረተረ/ተሠነጠቀ ዕዳሪው ።
ተጨፈላለቀ፡ ተዳዳጠ/ተደፋጠጠ/ተ ጨመላለቀ ።
ተጨፈረ፡ ተዘለለ/ተረገደ "
ተጨፈቀ፡ ተጠጋጋ/ተጠቀጠቀ/ተቸ ፈገ ("በዛ") ።
ተጨፈቀ፡ እንክብል ኾነ ("ተድበለበለ") ።
ተጨፈቀ፡ ደንጊያ ተጫነበት ("ተለሰቀ ቀጥ አለ") ።
ተጨፈነ፡ ተከደነ/ተደፈነ/ተሸፈነ (ኢሳ. ፳፱፡ ፱፡ ፴፪፡ ፫) ።
ተጨፈገ፡ ተፈቀ/ተቸፈገ ።
ተጨፈገገ፡ ተቋጠረ/ጠቈረ ።
ተጨፈጨፈ፡ ተቈራረጠ/ተተፈተፈ ።
ተጨፈጨፈ፡ ታለፈ/ተሻረ ነገሩ ።
ተጨፋለቀ፡ ተጨማለቀ/ተቀጣቀጠ ።
ተጨፋቂ፡ የሚጨፈቅ ።
ተጨፋኝ፡ የሚጨፈን ።
ተጨፋጨፈ፡ በሰይፍ ተማታ/ተቈራ ረጠ ።
ተጨፋፈቀ፡ ተጠጋጋ/ተጨቋቈነ ።
ተጨፋፈነ፡ ዐይንን ተከዳደነ/ተሸፋ ፈነ ።
ተጨፍላቂ፡ የሚጨፈለቅ ዕዳሪ/ብረት ።
ተጨፍጫፊ፡ የሚጨፈጨፍ ቅጠል ።
ተጫለጠ፡ ተጫረሰ/ተቃዳ/ተረረ ።
ተጫሚ፡ የሚጫማ ።
ተጫማ (ተሥእነ)፡ ጫማ ለü ፡ አጠለቀ ("ኹለት እግሩን ከጫማ አገባ") (ኤፌ. ፮፡ ፲፭) ።
ተጫረ (ተጽሕረ)፡ ተወረ/ተቈ ፈረ/ተኳተ/ተፋረ/ተጐደፈረ/ተበተነ ።
ተጫረ፡ ተዛቀ/ተወሰደ ፍሙ ።
ተጫረ፡ እሳትን ተበዳደረ ።
ተጫረሰ፡ ተጋደለ/ተላለቀ ።
ተጫረተ፡ ተፈካከረ/ተበላለጠ ("ባ፲ ፭ በ፻ ፶ እሰጥ አክል እምር ተባባለ በግዥ ዋጋ ተለያየ") ።
ተጫራች (ቾች)፡ የተጫረተ/የሚጫ ረት ("ተበላላጭ ተፈካካሪ") ።
ተጫቈነ፡ ተጫጫነ/ተፈቀ ።
ተጫነ (ተጽዕነ)፡ ጭነትን ኮርቻን ተሸከመ ።
ተጫነ፡ በሸክምነት በላይ/በተሸካሚነት በታች ኾነ ("ተከመረ ጨቈነ ከበደ እከን እርጅና እንቅልፍ ተጭኖታል እንዲሉ (ተረት) ሰው ይውደድኸ ድንጋይ ይጫንኸ") ።
ተጫነ፡ በከብት በማንኛውም ነገርተቀ መጠ ።
ተጫነ፡ ባጋሰስ ዠርባ መጣ/ኼደ እኸሉ ዕቃው ።
ተጫነ፡ ተሸካከመተካበደ ።
ተጫነቀ (ተጻዐቀ)፡ ተጣጋ/ተጣ ረረ ("ተፋተገ ተጋፋ") ።
ተጫናቂ (ተጻዓቂ)፡ የሚጫነቅ ("ተጣ ባቢ ተጋፊ") ።
ተጫን፡ የሰው ስም ("ጠላትን ቍን ክበድ ማለት ነው") ።
ተጫኝ፡ የተጫነ/የሚጫን ("ኀይለኛ") ።
ተጫወተ (ተጻወተ)፡ ሥጋዊና መንፈሳዊ ነገር ተናገረ ("ተላፋ ዘፈነ አዘመረ አላገጠ እከሌ በእከሌተጫወተበት እንዲሉ የሀብታም ልጅ ሲጫወት የድኻ ልጅ ይሞት") ።
ተጫዋች (ቾች)፡ የተጫወተ/የሚጫ ወት ("ዘፋኝ አዝማሪ አማሪት ገንቦኛ አረኾ") ።
ተጫጨደ፡ ተቋረጠ/ተጣረገ ።
ተጫጫሰ፡ ተፋፋመ/ተያያዘ/በዛ ("በረታ ጠቡ") ።
ተጫፈረ፡ ተዛለለ ("ተቃረበ í ተያያዘ ተቀናጀ") ።
ተጫፈቀ፡ ተጣጋ/ተጫቈነ ።
ተጫፋሪ፡ የሚፈር ("ተያያዥ ንግግር ") ።
ተጭቈነቈነ፡ እንደ ጭቍኝ ቅጠል ኾነ ("ተጣበበ") ።
ተጭበሰበሰ፡ አላይ/አልነድ አለ ("በሽ ተኛ ዐይን ርጥብ ዕንጨት") ።
ተጭበረበረ፡ እንደ ጕጕትና እንደ ሌት ወፍ ኾነ ("ብርሃን ማየት አቃተው ተሳነው") ።
ተጭበረበረ፡ እውነት እያለው የሌ ለው መሰለ ("ተሳሳተ ተደናገረ") ።
ተጭፈነፈነ፡ ተጭበሰበሰ ።
ተጮኸ፡ ቍቁ ውይ ተባለ ("ድረሱልኝለማለት ለማልቀስ እንባ ለማፍሰስ (ጥጮ) ቢጮኸ ኦሮ እንዲሉ") ።
ተጯጯኸ፡ ጩኸትን ተቀባበለ ("ተ ፋጀ") ።
ተጰጰሰ፡ ጳጳስ ኾነ ተሾመ ።
ተፀረረ፡ ተሠራ ተለበሰ ፅሩሩ ።
ተፀረረ፡ ተጠረረ ፅሩር ለበሰ ሰዉ ።
ተፀነሰ (ተፀንሰ)፡ ተጠነሰ ተጠነሰሰ፡ በሆድ ቀረ ታቈረ ተቋጠረ ተረገዘ ።
ተጸናና (ተጻንዐ)፡ ተበረታታ ።
ተጸጸተ፡ ተጠጠተ ተቈጪ ዐዘነ ። "ም ነው ባልሠራኹት ' አለ" ።
ተጸፋ (ተጸፍዐ - ተጠፍሐ)፡ በጥፊ ተመታ ፊቱ (ተዜመ ተባለ - ጽፋቱ ") ።
ተፃረረ፡ ተጣላ ።
ተፃራሪ፡ የተፃረረ/የሚፃረር (ተጣይ ") ።
ተጻብኦ (ጸብአ/ተጻብአ)፡ ሕልመ ሌሊት ሶፍያ...ትርጓሜው መጣላት መዋጋት ሩካቤ ሕልም ።
ተጻብኦ፡ ሕልመ ዝሙት ("የፍትወት ጦርነት ሶፍያ") ።
ተጻጻፈ (ተጻሐፈ)፡ ደብዳቤ ተመላ ለሰ ተላላከ ተቀባበለ (በወረቀት ተነጋገረ ") ።
ተጻፈ ("ተጣፈ ተሠነተረ ተሠነጠቀ ክንዱ ተቈረጠ ዐጽቁ ጫፉ ተጋባ ተገናኘ ተራከባ ተቀላቀለ ተዛመደ አንድ ኾነ ብት ተከታቢ የሚከተብ ልጅ ተክል ከ ቶች ተከታቢዎች የሚከተቡ ልጆች ከብ ክትብ ") (ቦች) ።
ተጻፈ ("ተጣፈ ተሠነተረ ተሠነጠቀ ክንዱ ተቈረጠ ዐጽቁ ጫፉ ተጋባ ተገናኘ ተራከባ ተቀላቀለ ተዛመደ አንድ ኾነ ብት ተከታቢ የሚከተብ ልጅ ተክል ከ ቶች ተከታቢዎች የሚከተቡ ልጆች ከብ ክትብ ") (ቦች) ።
ተጻፈ (ተጽሕፈ)፡ ተጣፈ ተከተበ ታተመ ።
ተጽናና፡ ሐዘኑን ተወ ተረጋጋ ተጥ ናና ።
ተፈለመ፡ ተቀደመ ተዠመረ (አስቀድሞ ተወጋ ቈሰለ ") ።
ተፈለሰ፡ ፈለሰ ተመነቀረ ፈረሰ ።
ተፈለሰፈ፡ ተጠባበ ተራቀቀ (ተፈተነ ተመረመረ ተዘጋጀ ተከወነ ተደረገ ") ። ጐላ ተረዳ ወጣ ጥበቡ ብልኀቱ ።
ተፈለቀ፡ ተቀደደ ተሠነጠቀ ።
ተፈለቀቀ፡ ላላ ተከፈተ ።
ተፈለቀቀ፡ ተፍታታ ተበተነ ።
ተፈለገ፡ ተሻ ተፈቀደ ("(ኢሳ. ፷፭ - ፩)") ።
ተፈለገ፡ ተከፈለ ተሠነጠቀ ።
ተፈለጠ (ተፈልጠ/ተፈልጸ)፡ ተሠ ነጠቀ ተሠነጠረ ተሰበረ ተፈነከተ ተሸነሸነ ።
ተፈለፈለ፡ ተማሰ ተፈረፈረ ።
ተፈለፈለ፡ ተቀረጸ ተሰረሰረ ተበሳ ተነደለ ።
ተፈለፈለ፡ አማረ ሸበረቀ (የመልክ ") ።
ተፈለፈለ፡ ከአንቍርባ ከቂንድ ተለየ (ተቀፈቀፈ ወጣ፡ ተወለደ ") ።
ተፈላለመ፡ ተቀዳደመ ተዠማመረ ።
ተፈላለገ፡ ተፈቃቀደ ።
ተፈላለጠ፡ ተሠነጣጠቀ ተፈነካከተ ።
ተፈላላጊ፡ የሚፈላለግ (ተፈቃቃጅ ") ።
ተፈላሚ፡ የሚፈለም (ተዠማሪ ") ።
ተፈላቀቀ፡ ተለያየ ተፈራቀቀ ተላቀቀ ።
ተፈላጊ (ዎች)፡ የሚፈለግ (ልብስ ጕ ርሥ፡ ሌላም ነገር - ፈረስ ለጦርነት፡ በቅሎ ለጌትነት፡ በሬ ለስበት፡ ጥገት ለወተት ። ያደን ለት ውሻ፡ የሽብር ለት ጋሻ ተፈላጊ ነው ") ። በዘመናችን ግን "ተፈለገ" "ተፈላጊ" በማለት ፈንታ ' "አስፈለገ" "አስፈላጊ"፡ "ይህ ነገር ለኔ አስፈላጊዬ ነው"፡ "አስፈላጊ መስሎ ስለ ታ የኝ" እየተባለ በስሕተት ይነገራል ይጻፋል ።
ተፈላጊነት፡ ተፈላጊ መኾን ።
ተፈላጭ፡ የሚፈለጥ (ግንድ ደንጊያ ") ።
ተፈልቃቂ፡ የሚፈለቀቅ ።
ተፈልፋይ፡ የሚፈለፈል ።
ተፈሰከ፡ ፋሲካ ኾነ (ተተወ ' ጦሙ ተበላ ሥጋው ") ("(፪ ነገ. ፳፫፥ ፳፪)") ።
ተፈሰፈሰ፡ ተመታ ተደበደበ ።
ተፈሳ፡ ቱስ አለ (ተንጣጣ ተንጣረረ ተንዛረጠ ") ።
ተፈረመ፡ ተጻፈ ተደረገ (ፊርማው ም ልክቱ ") ።
ተፈረቀ፡ ተለየ ተከፈለ ።
ተፈረቀቀ፡ ተፈነቀለ ተፈለቀቀ ተሠነ ጠቀ ተለየ ራቀ ።
ተፈረነሰ፡ እንደ ልብ ተኛ ተጋደመ ተዘረረ ተፈነደሰ ።
ተፈረከሰ፡ ተሰበረ ደቀቀ ።
ተፈረካከሰ፡ ተሰባበረ ።
ተፈረደ፡ ተበየነ ታደለ (ፍርዱ እው ነቱ ከሐሰት ተለየ ") ።
ተፈረደ፡ ፍርድ ተቀበለ ("(፩ ቆሮ. ፪፥ ፲፭)") ።
ተፈረደለት፡ ተበየነለት ።
ተፈረደበት፡ ተበየነበት "
ተፈረደኝ፡ ተበየነልኝ "
ተፈረደኝ፡ የሰው ስም "
ተፈረጀ፡ ከሴቱ ወጣ (አገር ለወጠ ያላየውን አየ፡ የደጋ ወይም የቈላ አየር ተቀበለ ") ።
ተፈረፈረ፡ ተፈለፈለ ተማሰ ተቈፈረ ።
ተፈረፈረ፡ ደቀቀ ጠቀነ ።
ተፈሪ መኰንን፡ የቀዳማዊ ዐጤ ኀይለ ሥላሴ ባማርኛ መጠሪያ ስም ። "ዐሰበ" ብለኸ "ዐስብን" ተመልከት ።
ተፈሪ በር፡ "የተፈሪ በር" (በውጋዴ ክፍል ያለ ቀበሌ ") ።
ተፈሪ፡ የሰው ስም ።
ተፈሪ፡ የተፈራ/የሚፈራ/የሚታፈር (ኀይለኛ ጐበዝ ") ።
ተፈሪነት፡ ተፈሪ መኾን ።
ተፈሪዎች፡ የሚፈሩ/የሚከበሩ ሰዎች ።
ተፈራ (ተፈርሀ)፡ ተጠረጠረ (ታፈረ - ከበረ - አልተደፈረም ") ("(ኤር. ፪፥ ፮)") ።
ተፈራ (ተፈርየ)፡ ተፈጠረ ተፀነሰ ተገኘ ተወለደ (ፍሬው ልጁ ") ።
ተፈራ ወርቅ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ተፈራ፡ የሰው ስም ።
ተፈራ፡ የሰው ስም ።
ተፈራሚ፡ የሚፈረም መልክት ።
ተፈራረቀ (ተባረየ)፡ ተረዳዳ ተጋ ገዘ ተራረፈ (ተለዋወጠ ተዘዋወረ ") ።
ተፈራረደ፡ ተበያየነ ("(ግብ. ሐዋ. ፳፭፥ ፱ - ፲፥ ፳)") ።
ተፈራሪ፡ የተፈራራ/የሚፈራራ (ጕል በተ እኩል "(ትክክል)") ።
ተፈራራ፡ ተፋፈረ ።
ተፈራራሚ፡ የሚፈራረም/የሚጻጻፍ ።
ተፈራራቂ (ዎች)፡ የተፈራረቀ " የሚ ፈራረቅ (ተለዋዋጭ ተዘዋዋሪ - ሌሊትና መዓ ልት በጋና ክረምት መናዝል ሐዘንና ደስታ ሹመትና ሽረት ማጣትና ማግኘት፡ የመሰለው ኹሉ ") ።
ተፈራቀቀ፡ ተላቀቀ ተለያየ ተራራቀ ።
ተፈራቃቂ፡ የሚፈራቀቅ (ተለያዪ ") ።
ተፈራከሰ፡ ተሳበረ ተዳቀቀ ።
ተፈርፋሪ፡ የሚፈረፈር ።
ተፈቀረ (ተፈቅረ)፡ ተወደደ ወዳጅ ኾነ ።
ተፈቂ፡ የሚፈቃ (ተበጪ ") ።
ተፈቃ (ተፈቅዐ)፡ ተቈራ ' ተበጣ ተሠነጠቀ ተጋረጠ ።
ተፈቃሪ፡ የሚፈቀር/የሚወደድ ።
ተፈቃቀረ፡ ተሰማማ ተኳዃነ ።
ተፈቃቃሪ (ዎች)፡ የተፈቃቀረ/የሚ ፈቃቀር (ተሰማሚ ") ።
ተፈቃቃሪነት፡ ተሰማሚነት ።
ተፈተለ፡ ተጠፋ ተወዘገ ተመዘዘ ተሳበ (ተጠመረ ተገመደ ተጠመዘዘ ") ።
ተፈተለከ፡ ተፈታ ሾለከ ወጣ አመ ለጠ ።
ተፈተረ፡ ታነቀ ተጨነቀ ተወጠረ ።
ተፈተሸ፡ ተቀነቀነ ተመረመረ ተበረ በረ ።
ተፈተተ፡ ተቈረሰ ተገመሰ ተከፈለ ተተነተነ ።
ተፈተነ (ተፈትነ)፡ ተሞከረ ተፈ ተሸ ተመረመረ ተጠየቀ፡ ተጠበሰ ቀለጠ ፈሰሰ፡ መከራ ተቀበለ ። "ኢዮብ ፯ ዓመት ተፈ ተነ" ።
ተፈተገ፡ ተላጠ ተመለጠ ።
ተፈተገ፡ ተወቀጠ ተሸከሸከ ታሸ ታጨደ ።
ተፈተፈ (ፈተፈተ)፡ በጣ ፈቃ ቈራ ሠነተረ (ላይ ላዬን በቅርብ በቅርብ ቈረጠ በፍጥነት) ።
ተፈተፈተ፡ ራሰ (በጣት ደቀቀ ") ። "ጠለቀ" ብለኸ "ተጠለቀን" አስተውል ።
ተፈታ፡ ቀረ ተወገደ ግዝቱ ።
ተፈታ፡ ተለቀቀ ተተወ ።
ተፈታ፡ ተባረታ አንደበቱ ("(ሉቃ. ፩፥ ፷፬)") ።
ተፈታ፡ ተተረተረ ተከፈተ ።
ተፈታ፡ ተፈቀደ ("(ዘሌ. ፲፩፥ ፳፩)") ።
ተፈታ፡ ጠፋ ፈረሰ ተሻረ ተበተነ ተበላሸ ("(ዮሐ. ፲፥ ፴፭)") ።
ተፈታሪ፡ የሚፈተር/የሚጨነቅ/የሚ ወጥር ።
ተፈታሽ፡ የሚፈተሽ (ተመርማሪ ") ።
ተፈታተነ፡ ተመራመረ ፈተና ተቀ ባበለ (በተንኰል ተከታተለ ተገዳደረ ተወዳ ደረ ") ። "ይቻላል አይቻልም ተባባለ" ("(ዘፀ. ፲፯፥ ፯፡ ሚል. ፫፥ ፲፭)") ።
ተፈታተገ፡ ተመላለጠ ።
ተፈታታ፡ ደሙ ተበታተነ ።
ተፈታታኝ፡ የተፈታተነ/የሚፈታተን (ተመራማሪ ተከታታይ ") ።
ተፈታች፡ የሚፈተት í ተቈራሽ ።
ተፈታኝ፡ የሚፈተን (ተመርማሪ ") ።
ተፈታይ፡ የሚፈተል (ንድፍ አምልማሎ ") ።
ተፈታጊ፡ የሚፈተግ/የሚወቀጥ ።
ተፈትሖ፡ መፈታት መጽነን ። "እመቤታ ችን በዚህ ዓለም ያለተፈትሖ ኖረች" ።
ተፈች፡ የሚፈታ/የሚሸነፍ (ድል ዃኝ ") ።
ተፈነ፡ ተካደነ/ተሻፈነ ።
ተፈነቀለ፡ ተገለበጠ ተለየ ተቀረፈ ("(ናሖ. ፩፥ ፳)") ።
ተፈነቃቀለ፡ ተገለባበጠ ተለያየ ።
ተፈነተወ፡ ተጠረገ ተገለጠ ጠራ ።
ተፈነቸረ፡ ተጣለ ወደቀ ተገደለ ሞተ አለ ።
ተፈነከረ፡ ፈጽሞ ተገለጠ ተከፈተ ተዘረጋ (መጻፉ ") ።
ተፈነከተ፡ ተፈለጠ ተከፈለ ተገመሰ ተሰበረ ተተረረ ።
ተፈነካከረ፡ ተገላለጠ ተከፋፈተ ።
ተፈነካከተ፡ ተፈላለጠ ተገማመሰ ተ ሰባበረ ።
ተፈነደሰ፡ ተኛ ተጋደመ ።
ተፈነጃጀረ፡ ተወለጋገደ ተወነጋገረ ።
ተፈነገለ፡ ተጣለ ወደቀ ተገለበጠ ።
ተፈነጋገለ፡ ተጣጣለ ተገለባበጠ ("(በ ቀኝ በግራ በፊት በኋላ ተፈነገለ)")፡ ሥሩ ተቃረበ ጫፉ ተራራቀ ።
ተፈነጠረ፡ ተለየ ወጣ ዘለለ ("(ዓሞ. ፫፥ ፭)") ።
ተፈነጠቀ፡ ተረጨ ተነዛ ተበተነ (ዐ ልፎ ዐልፎ ወደቀ ተዘራ ") ።
ተፈነጠዘ፡ ተለበሰ ተጌጠ (ኾነ ተደ ረገ - ደስታው ፈንጠዝያው ") ።
ተፈነጣጠቀ፡ ተረጫጩ ተበታተነ ።
ተፈና፡ ተዛለለ ።
ተፈናቀለ፡ ተገላበጠ ተለያየ ። "አቶ እ ከሌ ሰካር ስለ ኾነ ከሥራው ተፈናቀለ" ።
ተፈናቃይ፡ የሚፈናቀል (ተገላባጭ ") ።
ተፈናጀረ፡ ተለያየ ተራራቀ ተጣመመ ።
ተፈናገለ፡ ተዋደቀ ።
ተፈናጠረ፡ ተሳቀለ ተንጠላጠለ ።
ተፈናጠረ፡ ተዛለለ ፥ ተወራወረ ።
ተፈናጠረ፡ ተዛራ ተባተነ ።
ተፈናጠቀ፡ ተራጩ ("(ተፈነጠቀ)") ።
ተፈናጠጠ፡ ከዳራ በስተኋላ በወዴላ ላይ ተቀመጠ ።
ተፈናጣቂ፡ የሚፈናጠቅ ("(ተፈንጣቂ)") ።
ተፈናጣጭ፡ የተፈናጠጠ/የሚፈናጠጥ '
ተፈናፈነ፡ ተነፋነፈ (ተወላዳ ተዛመረ ") ።
ተፈንቃይ፡ የሚፈነቀል (ተገልባጭ ዞ ብጥ ") ።
ተፈንካች፡ የሚፈነከት (ተፈላጭ ") ።
ተፈንጋይ፡ የሚፈነገል/የሚወድቅ (በተ ቀመጠበት የማይረጋ ") ።
ተፈንጣቂ፡ የሚፈነጠቅ (ተረጪ ") ።
ተፈከረ/ተፎከረ፡ ተገለጠ ተነገረ ተ ቈጠረ (ሞያው ግዳዩ ") ። ተደነፋ ።
ተፈካከረ/ተፎካከረ (ተቃሐወ)፡ ተወዳደረ ተከራከረ ተቀታተረ ("ማን ከማን አንሶ" ተባባለ ") ።
ተፈካካሪ/ተፎካካሪ (ዎች)፡ የተፈ ካከረ/የተፎካከረ/የሚፈካከር/የሚፎካከር (ተ ወዳዳሪ ተከራከሪ ") ።
ተፈወሰ፡ ታከመ ዳነ (ፈውስ አገኘ - ሉቃ. ፲፫፥ ፲፬) ።
ተፈዋሽ፡ የሚፈወስ (ድኅነት ፈላጊ ") ።
ተፈየደ፡ ተረባ ተጠቀመ ።
ተፈደነ፡ ታሰረ ተወደነ ተቀፈደደ ።
ተፈዳፈዶ፡ ተባዛ ተባለጠ ።
ተፈጀ፡ ተጨረሰ ዐለቀ ተጠነገደ ተገ ደለ ("(ዘዳ. ፴፪፥ ፳፬)") ።
ተፈጃጀ፡ ተወራረሰ ተላለቀ ።
ተፈገመ፡ በግንባሩ ወደቀ ተደፋ ።
ተፈገፈገ፡ ተፋቀ ተጠረገ ።
ተፈጋፈገ፡ ተሸጋሸገ ተራራቀ ።
ተፈጋፈገ፡ ተፋፋቀ ተጣረገ ።
ተፈጋፋጊ፡ የሚፈጋፈግ (ተሸጋሻጊ ") ።
ተፈጠመ (ተፈጸመ/ተፈፅመ)፡ በዚህ ቀን እቀርባለኹ ወይም ኹለተኛ አልደርስም ("ንጉሥ ይሙት" በማለት ነገሩ ተጨረሰ ዐለቀ ተዘጋ ") ።
ተፈጠረ፡ ተገኘ ተሠራ ተደረገ ተወ ለደ ።
ተፈጠረቀ፡ ፈነዳ ' ወጣ ።
ተፈጠፈጠ፡ ተፈነከተ ቈሰለ ("(፪ዜና. ፳፭ - ፲፪፡ ሆሴ. ፲፥ ፲፬፡ ፲፫ - ፲፮)") ።
ተፈጣሚ፡ የሚፈጠም (የሚዘጋ ") ።
ተፈጣጠመ፡ ተቃጠረ ። "ልጄ እከሊትን ለእከሌ ልጅ ሰጠኹ፡ እኔም ተቀበልኹ፡ ንጉሥ ይሙት ተባባለ፡ ተዋዋለ" ።
ተፈጣጠረ፡ ተሠራራ ተደራረገ ። "ማን ፈጠረን"፡ "ርስ በርሳችን ተፈጣጠርን" እንዳሉ መላእክት ("(ሥነ ፍጥረት)") ።
ተፈጣጣሚ፡ የሚፈጣጠም (ተዋዋይ ") ።
ተፈጥሮ፡ መፈጠር (ባሕርያዊ ግብር ") ። "ተፈጥሮን ተመክሮ አይመልሰውም" ።
ተፈጨ (ተፈጽሐ)፡ ተከካ ተከረተፈ ተሸመሸመ (ደቀቀ ተሰለቀ ተዳሰ ") ።
ተፈጸመ፡ በቃ ብቃት አገኘ ።
ተፈጸመ፡ ዐለቀ ተጨረሰ (መላ ሞላ ደረሰ ") ።
ተፈጻሚ፡ የሚፈጸም/የሚጨረስ ።
ተፊ (ተፋኢ)፡ የተፋ/የሚተፋ (አስ...ዋኪ) ።
ተፊታ፡ የምትተፋ ሴት ።
ተፊያፊያጠ፡ ተቃለደ ።
ተፋ (ተፍኦ)፡ ምራቁን በምድር ላይ አሳረፈ (አክ እንትፍ አለ ከሆድ አውጥቶ ጣለ - ዮና.
፪፡ ፲፩) ።
ተፋ፡ ቀረሸ አወጣ አስታወከ አስመለሰ ። ("ተረት - አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል" - "ምድር ተፋችው" - አሽቀነጠረችው ሽቅብ ወረወረችው - "ምን ምድር ተፋኸ" - አወጣኸ) ።
ተፋለመ፡ ተጋራ ተካፈለ ።
ተፋለሰ፡ ተሳሳተ ተቃወሰ ተዛወረ ተዛነቀ ተዘባረቀ ተለዋወጠ ።
ተፋለሰ ተጣላ ተገተ ተከራከረ (ተማታ ተዋለቀ ") ።
ተፋለቀ፡ ተፋሰሰ ተገናኘ ተዘዋወረ ተላለፈ ።
ተፋለገ፡ ተፋቀደ ።
ተፋለጠ፡ ተፈናከተ ። በግእዝ ግን ተለ ያየ ማለት ነው ።
ተፋላሚ፡ የተፋለመ/የሚፋለም (ተጋሪ ተካፋይ ") ።
ተፋሰሰ፡ ተሳሰበ ተሳላ (በባቄላ ") ።
ተፋሰሰ፡ ተንጠባጠበ ።
ተፋሰሰ፡ ተከናበለ (የደም ብድር ተከፋ ፈለ ") ። "እከሌና እከሌ ደም ተፋሰሱ" ።
ተፋሳሽ፡ የተፋሰሰ/የሚፋሰስ (የሚተሳ ስብ የሚሳላ ") ።
ተፋረ (ተፍሕረ)፡ ተጫረ ተቈፈረ ተማሰ ተጐደፈረ ።
ተፋረመ/ተፈራረመ፡ ፊርማ ተጻጻፈ ተቀባበለ (በፊርማ ተዋዋለ ") ።
ተፋረሰ፡ የሽያጭን ንግግር ተከዳዳ ።
ተፋረደ፡ ተባየነ ("(ኢሳ. ፵፫፥ ፳፮፡ መክ. ፮፥ ፲፡ ሕዝ. ፳፥ ፴፮፡ ማቴ. ፲፪፥ ፵፩፥ ፵፪)") ።
ተፋራ (ተፋርሀ)፡ ተጠራጠረ ።
ተፋራጅ፡ የተፋረደ/የሚፋረድ (ባለ ደም የች ወገን ") ።
ተፋቀ (ተፍሕቀ)፡ ተወ ተጠረገ ተፈገፈገ (ተለየ ተወገደ፡ ተላገ ለዘበ፡ ከሳ ") ("(ዘሌ. ፲፬፥ ፵፫)") "
ተፋቀረ፡ ተዋደደ ተስማማ ።
ተፋቂ፡ የሚፋቅ (ተላጊ ") ።
ተፋቃሪ፡ የተፋቀረ/የሚፋቀር (ተዋ ዳጅ ") ።
ተፋተለ፡ ተቃጠረ ተገናኘ ።
ተፋተለ፡ ተጣመረ ተጋመደ ።
ተፋተረ፡ ተናነቀ ተጫነቀ ።
ተፋተተ፡ ተቋረሰ ተካፈለ ተተናተነ ተሳተፈ ።
ተፋተነ፡ ተከረ ተፋተግ ታገለ (ጕልበት ለጕልበት ተያየ ") ።
ተፋተገ፡ ተላፋ ተሻሸ ተላላጠ ።
ተፋታ (ተፋትሐ)፡ ተለያየ ተላቀቀ ።
ተፋታ፡ ተተራጐመ ።
ተፋታች፡ ተለያየች ተላቀቀች ("(ከባሏ ቤት ወጣች)") ።
ተፋታጊ፡ የተፋተ/የሚፋተግ (ልፊያ ወዳድ ") ።
ተፋቺ፡ የሚፋታ/የሚለያይ (ዐብሮ የ ማይኖር ባል ") ።
ተፋከረ/ተፋከረ፡ ተደናፋ ተቋጠረ ተመላለሰ ግዳይን ።
ተፋዘዘ፡ ፊት ለፊት ተኳዃነ ተያየ ተነጻጸረ (ዐይንን ከዐይን ለማሳበር ") ። "(ተረት)" - እንቅልፍ ታበዢ ከነብር ትፋዘዢ ።
ተፋዛዥ፡ የተፋዘዘ/የሚፋዘዝ ።
ተፋጀ፡ ፈጀ (ተጨቃጨቀ ተጯጯኸ ተዋካ ") ።
ተፋጂ፡ የሚፈጅ/የሚፋጅ (አቃጣይ ") ።
ተፋጠረ፡ ተሣራ ።
ተፋጠነ፡ ተቻኰለ ተጣደፈ ።
ተፋጠጠ፡ ተጓረጠ ተሳለፈ ተፋዘዘ (ተቻኰለ ተጣደፈ ") ።
ተፋጣኝ፡ የሚፋጠን (ሠራተኛና ሥራ ") ።
ተፋጣጭ፡ የተፋጠጠ/የሚፋጠጥ ።
ተፋጨ (ተፋጽሐ)፡ ተፈጋፈገ ተሳ ሳለ ተንቀጫቀጨ ።
ተፋጯ (ተፋጸየ)፡ ኾነ ተደረገ ፉጨቱ ።
ተፋፈረ (ተኃፈረ)፡ ተፈራራ ተከባ
ተፋፈገ፡ ተከመቻቸ ፥ ተነባበረ፡ ተጠጋጋ፡ ተደራረበ፡ ተጨናነቀ ።
ተፋፋመ (ተፋሐመ)፡ ተበራታ ተቃ ረበ ።
ተፌ፡ ፈጣን ቀልጣፋ ሰው ።
ተፌ፡ ፈጣን ተፈተፈ ።
ተፌዘ፡ ኾነ ተደረገ ፌዙ (ተቧለተ ተፊያፊያዘ ተዋዛ ተላገጠ ") ።
ተፌጠ፡ ተቀለደ ተቈጠ ተለገጠ ተፌዘ ።
ተፍለቀለቀ፡ ሠገረ ተንሸረሸረ (በሠጋር ኼደ ") ።
ተፍለቀለቀ፡ ተብለጨለጨ ተብረቀረቀ ።
ተፍለቀለቀ፡ ፈላ ተንተከተከ ዘለለ ጨፈረ ።
ተፍለከለከ፡ ተንቀሳቀሰ ተስለከለከ ("ል ውጣ ልውጣ አለ" ዐልቅቱ ዓሣው የመሰለው ኹሉ ") ።
ተፍሳሳ፡ መላልሶ ተፈሳ፡ ልማዱ ግን ፈሳ ነው ።
ተፍረመረመ፡ ተወዘወዘ ተነከሰ ተበላ ተጋጠ ተነፈነፈ ።
ተፍረመረመ፡ ተጋ ተጣጣረ ተፍጨረ ጨረ ።
ተፍረመረመ፡ -ተፍጨረጨረ፡ ፈ...ረመ ።
ተፍረምራሚ፡ የሚፍረመረም (ተጣጣሪ ተፍጨርማሪ ") ።
ተፍረቀረቀ፡ ተሰባበረ (በብዙ ወገን ") ።
ተፍረቀረቀ፡ ነፈረቀ መገለ ተፍረጠ ረጠ ።
ተፍረከረከ፡ ተፈረፈረ ተሸራረፈ ፈራረሰ ተቅረፈረፈ ።
ተፍረገረገ፡ ተቅዘመዘመ ተረገረገ ተወ ዘወዘ ።
ተፍረጠረጠ፡ ተድፈጠፈጠ ።
ተፍተለተለ፡ ቅሌን ጨርቄን አለ (ሰበብ አበዛ በቀስታ ኼደ ፍጥነት ዐጣ ተጐ ተተ ") ።
ተፍተለተለ፡ ታሸ ወጣ ተጥመለመለ እድፉ ።
ተፍተልታይ፡ የሚፍተለተል ተጐታች ።
ተፍተፍ አለ፡ ፈጠን ፈጠን አለ ። አተፈተፈ፡ ቸኰለ ፈጠነ ተክተፈተፈ ።
ተፍተፍ፡ ፍጥነት ችኰላ ።
ተፍታታ፡ ተበተነ ተዘረዘረ (የደም ነገር ") ።
ተፍታፊ፡ የተፈተፈ/የሚተፈትፍ (በጪ...ቈራጭ) ።
ተፍነከነከ፡ ተደሰተ በደስታ ተወዘወዘ ።
ተፍነዘነዘ፡ ተቅነዘነዘ ተክነፈነፈ ፥ ተ ክለፈለፈ ተወዘወዘ ታወከ ሮጠ ።
ተፍጃጀ፡ በብዙ ወገን ወጪ ኾነ (እጅ በዛበት ") ።
ተፍገመገመ (ተንተነ)፡ ተንገደገደ ' ተርገደገደ ።
ተፍገመገመ፡ ተንገደገደ፡ ፈ...ገመ ።
ተፍገመገመ፡ ቶራ
ተፍገምጋሚ፡ የሚፍገመገም (ተንገድ ጋጅ ") ።
ተፍገረገረ፡ ተጠንቅቆ ሠራ (ተጣጣረ ተትኰረኰረ ጫተረ - ከችግር ለመውጣት ለመ ዳን ተፍጨረጨረ ") ።
ተፍገረገረ፡ ተጣመረ ተዋሰበ ።
ተፍገርጋሪ፡ የሚፍገረገር (ተዋሳቢ ") ።
ተፍጨረጨረ፡ ፈጽሞ ተጋ ታተረ ተ ትኰረኰረ ።
ተፍጨርጫሪ፡ የሚፍጨረጨር/የሚ
ተፎ ፌጥ፡ በፉጨት ተጣራ ተጠራራ ።
ተፎነነ፡ ተሠነጠቀ ተቈረጠ ተጐረደ (ዐጪር ኾነ ") ።
ተፎናኝ፡ የሚፎነን (ተቈራጭ ተጐራጅ ") ።
ተፎጠረ፡ ታሰረ ተሸበበ ።
ቱ ተባ
ቱ፡ እንስትን ከተባት ለመለየት የሚ...ነገር ዝርዝር ("ፈረስ ፈረሲቱ በግ በጊቱ ፍየል ፍየሊቱ") ። በራብዕና በኃምስ በሳብዕ በሚጨርስ ስም ግን "ዪቱ" ይላል ("ቷን ቀን" ተመልከት) ።
ቱሊ፡ ተረፈ ኵስሕ ("ቱኒን" እይ) ።
ቱሊያም፡ ቱሲ ያለበት ባለቱሊ ።
ቱልቱላ፡ ተመመ፡ በጣ ።
ቱልቱላ፡ ከተንድ ከንሓስ የተበጀ ናሽ የድምፅ መሣሪያ (ውስጠ ክፍት ሰው መጥሪያ መሰብሰቢያ) ።
ቱልት (ቶች)፡ የቅጠል ስም (ሥሩ...ዐለንጋ የሚመስል ማላጋ ቅጠል - ጠንቋዮች "የምድር ዐለንጋ" ይሉታል) ።
ቱማታ፡ የብዙ ሰው ጩኸት ፍጅት ውካታ መጫጝ} ።
ቱማታ፡ የጨበጣ ውግ ወግቶ ማሽቀንጠር ።
ቱማታ፡ ገዳይ (በቱማታ የሚገድል ሐርበኛ እንዳቶ በዛብኸ ያለ ጨካኝ ጐበዝ) ።
ቱምቢ፡ የግንብ ጠርዝና ማእዘን (ያዲስ ሕንጻ ማስተካከያ ብረት ወይም ርሳስ ፉ...በቀጪን ገመድ የተያዘ) ።
ቱስ አለ፡ ተፈሳ በታች ተተነፈሰ ። ("ቱስ ያለ ዘረጥ ሳይል አይቀርም" እንዲሉ) ።
ቱስ አለ፡ ተፈሳ፡ ቶሰቶሰ ።
ቱስኪያም፡ ፈሳም ።
ቱስክ አለ፡ ቶሰከ ።
ቱስክ፡ ድምፅ የለሽ ፈስ ።
ቱረባ፡ ውስወሳ ሽድሽዳ ።
ቱሪናፋ (ተረፋ)
ቱሪናፋ፡ የማይረባ ወታደር ሰነፍ ። ("ሽለላ" - ቱሪናፋ ቱሪናፋ በጦር ሜዳ እትገኝ ከቀለቡ ኣትጠፋ) ።
ቱር (ሰሪር/ነጺሕ)፡ መብረር መን...ጻት ።
ቱር አለ (ሰረረ)፡ ተነሣ በረረ ።
ቱር አለ፡ እጅግ ነጣ ጸዐዳ ኾነ...ራዛ መሰለ ።
ቱርብ፡ የተቶረበ (ውስውስ ሽድሽድ ሽልልሽክሽክ መናኛ ስፌት ከጥብቅ ስፌት ቀዳሚ) ።
ቱርክ (ኮች)፡ የነገድ ስም (በታናሽ...እስያና ባውሮጳ በግሪክ አገር የሚኖር ሕዝብ) ።
ቱርክ ባሻ (የቱርክ ባሻ)፡ በምጥዋ...የነበረ የቱርክ ጦር ሰራዊት አዛዥ ሻለቃ ባጤ ሠርጸ ድንግል ዘመን ዮናኤል የሚባል ሐርበኛ በሾተል ወግቶ የገደለው ከዚህ በ ኋላ ይህ ስም ወደ ቤተ መንግሥት የገባ ይመስላል ። "ፓሻንና ባሻን" ተመልከት ።
ቱርክ ባሻ ማዕርጋቸው፡ ታምሬ ስማቸው ።
ቱርክ ባሻ ታምሬ፡ ያጤ ምኒልክ ጋሻ ዣግሬ ።
ቱርክኛ፡ የቱርክ ቋንቋ ።
ቱቢት (ዐረ. ቱቤት)፡ ጥቍር የሐ...ሀን ልብስ ሥራ ካባ (ከባሕር የመጣ) ።
ቱባ (ዐረ. ቱባዕ)፡ ክልስ ያይዶለ (ጥሩ ጥይት) ።
ቱባ፡ ሙሉ የባሕር ድር ማግ ጥለት ሐር (ጕድለት የሌለበት) ።
ቱቦ፡ ከስሚንቶና ከአሸዋ የተበጀ አሸንዳ (ሰፊና ጠባብ ቦምባ የውሃ መውረጃ ፉካ - "ቱቦ" ጣሊያንኛ ነው) ።
ቱኒ፡ ፈስ (ዘሩ "ተነነ" ነው) ።
ቱኒ፡ ፈሪ በከን ።
ቱኒያም፡ የቱኒ ባለቱኒ ፈሳም ።
ቱንቢ፡ አድማስ ቱምቢ ።
ቱኪ (ኳደሬ)፡ የጭቃ ሹም ተወራጅ ተከታይ ዕግት ተሸካሚ ።
ቱኪ፡ የጭቃ ሹም ተወራጅ (ቶ ከቶከ) ።
ቱግ አለ፡ በፍጥነት ነደደ ተቈጣ ።
ቱግታ፡ የችቦ አበራር ። ትግ/ብልጭ ።
ቱፌ፡ የወተት መና ቀዳዳ ውታፍ (በነቀሉት ጊዜ በነፋስ ኃይል ወተት ወይም ቅቤ የሚተፋ) ።
ቲ፡ ምእላድ ("ፀጕል ፀጕለቲ ፉን ፉነቲ") ።
ቲርማ፡ ጅር የዝንጀሮ ጓዝ ።
ቲቲቲ አለ፡ በጎችን...ለውጊያ አዘዘ ።
ቲቲቲ፡ አውራ በግን ለማዋጋት እረኛ የሚያሰማው ድምፅ ።
ቲክ (ተየከ)፡ መምላት መንተርፈፍ ("ቲክ አለ" - ጢም እለ መላ) ።
ቲውሽ (ተው ወሽ)፡ አህያን ለማገ...ድና ለመከልከል የሚባል ቃል። "እንቱሽን አስተው"።
ቲፍ፡ መተንፈስ መምላት (ሲተነፍሱ ባፍንጫ ርጥበት ማውጣት) ።
ቲፍ አለ፡ መላ ጢም አለ ተርፎ እስኪፈስ ("ቴፈን" እይ) ።
ቲፍ አለ፡ በትንፋሽ ድምፅ አሰማ ተጠነቀቀ (ፍየሉ) ።
ታ (ትግ. ሐባ)፡ የሩቅ ሴት ነባር አንቀጽ ናት/ነች ። "ተኣምራትስ ይህታ ሰን በትን መሻር ይህታ" እንዲሉ የሐዲስ ተርጓሞች ። ዳግመኛም "ይህች ናት" ተብሎ ይተረጐማል ።
ታ፡ ምእላድ ("ፍችው ማለት - እግዚኦ እግዚኦታ ሃሌ ሃሌታ አወን አወንታ አል ኣሉታ ይሉኝ ይሉኝታ") ።
ታ፡ በሣልስ ቅጽል መጨረሻ እየገባ አንዳንድ ጊዜ ለሴት መለዮ ቅጽል በቂ ይኾናል ("የፈሲታ ተቈታ ጠፍር በሊታ ብትኼድ ልጓም በሊታ መጣች - ሣቂታ ሰፊታ" እንዲሉ) ። የሳቢ ዘርም ምእላድ ሲኾን "ረሳ ርሳታ ረዳ ርዳታ ዘነጋ ዝንጋታ ቸለለ ቸልታ ቀረ ቅርታ ዋለ ውለታ ቀደደ ቅዴታ ሰማ ስሞታ" እያለ ይነገራል ።
ታ፡ በራብዕ በሚጨርስ የ፪ና የ፫ ፊደል ግስ ለሩቅ ሴት የቦዝ ዝርዝር ("በላ በልታ ቀና ቀንታ ሠራ ሠርታ ዘነጋ ዘንግታ ዘረጋ ዘርግታ") ። መጨረሻው ራብዕ ባልኾነ ግስ ሲገባ "ሰጠ ሰጥታ ቀረ ቀርታ" ይላል ።
ታ ቻቻታ ።
ታለ፡ አይሰጥ (የሀብታም ንፉግ የሰረ ስር ዐጥንት) ።
ታለለ (ተዐለለ/ተሤረየ)፡ ቀለም ገባ ተነከረ ("(በደም ታለለ)" - ተዘፈቀ ተለወሰ ") ።
ታለለ (ዕብ. ታላል)፡ አታለለ
ታለለ፡ በደም ተነከረ፡ ሀለለ ።
ታለመ (ተሐልመ)፡ ታየ ተገለጠ ዕልሙ ።
ታለመ (ተዐልመ)፡ ጠፋ ወደመ (ታባ ተሰወረ ") ።
ታለበ (ተሐልበ)፡ ተሳሰ/ተጐተተ ጡቱ ፲ ወጣ ፈሰሰ ወተቱ ።
ታለበ (ተዐለመ)፡ ኾነ (ተደረገ ተጨመረ ምልክቱ ") ።
ታለበች (ተሐልበት)፡ ተገናኘች (ወተቷ ለላቢ ተሰጠ ") ።
ታለፈ፡ ተኼደ ተዘለለ (መንገዱ ሰው
ታላላቆች፡ ዓሦች፣ ዓሣ፡ ነባሪዎች ("ዘፍ. ፩፡ ፳፩") ።
ታላቄ፡ የታላቅ፡ ወንድምና፡ እት፡ መጥሪያ፡ የኔ፡ ታላቅ፡ ማለት፡ ነው፡
ታላቅ፡ ትልቅ የበለጠ ላቀ ።
ታላቅ፣ የሥጋ፡ ስም፡ የኋላ፡ እግር።
ታላቅነት፣ ታላቅ፡ መኾን፡ ከፍተኛነት።
ታላቢ፡ የሚታለብ/የምትታለብ ጡቷ ።
ታልማ ፣ የወተት፡ አንዠትናመገናኛ፡ ታናሽ፡ አንዠት፡ ጥቅል ።
ታልማ፡ ታናሽ አንዠት ለማ...ትሎማ ።
ታልማው፡ ፈሰሰ፡ እንዲሉ።የታልማ፡ ትርጓሜ፡ ታለምልም፡ ታብራ፡ ማለት፡ ነው ።
ታመመ (ሐመ)፡ በደዌ ዳኛ ባልጋ ቍራኛ ተያዘ (ታማሚ ኾነ ተበሸተ - ፩ነገ. ፲፭፥፳፫፡ ፊልጵ. ፪፥፳፯ - ባ፲፱፻፶፬ ዓ ም በግን ቦት ወር የሰው ኹሉ ቀኝ ዦሮ ታመመ ") ።
ታመመ፡ (ተአመመ)፡ ተዠመረ፡ ተሠራ፡ ዐረሙ፡ ዕዳው፡ ቍፋሮው።
ታመመ፡ ተበሸተ፡ ዐመመ ።
ታመመ፡ ዐዘነ ተቈረቈረ ።
ታመሰ (ተሐመሰ)፡ ሞቀ ተንቃቃ ።
ታመሰ (ተኀመሰ)፡ ዐምስት ኾነ ተ ።
ታመሰ፡ ጪስ እንደ ገባው ንብ ታ ወከ ተተራመሰ ።
ታመረ፡ (ተአመረ፡ ተአምረ)፡ ምልክት፡ ኾነ፡ ታየ፡ ታወቀ ።
ታመቀ፡ ታበቀ ተረጠጠ ።
ታመተ (ተሐመተ)፡ ነደደ ተቃጠለ ከሰለ (ዐመድ ኾነ ") ።
ታመተ፡ ተመተረ ተከተፈ ።
ታመተ፡ ተጠበሰ ።
ታመተ፡ ዐማት ኾነ ተባለ (ኾነች ተባለች ") ።
ታመቸ፡ ዐማች ኾነ ተባለ ።
ታመነ፡ (ተአመነ)፡ አመነ፡ ወደደ። ጌታ፡ አሽከሩን፡ ታመነ፡ (ዘዳ፳፰፡ ፷፮። ኢሳ፳፮ ፲፬። ፊልጵ፫፡ ፫)። ታመነን፡ አመነ፡ ብሎ፡ መተርጐም፡ ልማዳዊ፡ ስሕተት፡ ነው።
ታመነ፡ (ተአምነ)፡ ተወደደ፡ ከበረ፡ ተወከለ፡ አሽከሩ፣ ሎሌው።
ታመነ፡ ተዘለነ፡ ተዘለለ፡ ሐሳቡን፡ ጣለ፡ ምን፡ አለብኝ፡ አለ ።
ታመደ/ታመተ፡ ዐመድ ኾነ (ተቈረጠ "(ጥም)"
ታመገ (ተሐምገ)፡ ተሰበሰበ ተከ ማቸ ተመሰገ ("ጅብ' አለ ") ።
ታመፀ፡ ተከዳ ተገፋ ተበደለ ።
ታሚ፡ የሚታማ (ስሙ በክፉ የሚነሣ ") ።
ታማ (ተሐምየ)፡ ተነቀፈ ተሰደበ ("(ተረት)" - ባልንጀራኸ ሲታማ "የኔ" ብለኸ ስማ ") ።
ታማ፡ ሻገተ በሰበሰ ሸተተ ገማ ("ደነ በሸን" እይ ") ።
ታማለች፡ አርግዛለች ፀንሳለች ("(ዘፍ. ፫፥ ፲፮)") ።
ታማሚ (ሐማሚ)፡ የታመመ/የሚታመም (ዕመምተኛ ጤና ቢስ - ፩ሳሙ. ፴፥፲፫፡ ማቴ. ፮፥፳፫) ።
ታማቂ፡ የሚታመቅ (ተረጣጭ ") ።
ታማኝ፡ (ኞች)፡ የታመነ፡ የሚታመን፡ የተወከለ፡ እውነተኛ፡ ጻድቅ፡ የማይጠረጠር። (የማይታመን)፡ ወስላታ፡ ሰው፡
ታማኝነት፡ እውነተኛነት፡ ርግጠኛነት።
ታምረ፡ ማሪያም፣ የማሪያም፡ ታምር፡ ወይም፡ መጽሐፍ።
ታምረኛ፡ ባለታምር፡ ጕደኛ፡ ድንቀኛ።
ታምረየስ፡ (ተኣምረ፡ ኢየሱስ)፡ የጌታችን፡ የኢየሱስ፡ ታምር፡ የመጽሐፍ፡ ስም።
ታምር፡ (ራት)፡ ጕድ፡ ድንቅ፡ ምልክት፡ ታይቶ፡ ተሰምቶ፡ የማይታወቅ፡ ነገር፡ ሙት፡ ማንሣት፡ ዕውር፡ ማብራት ።በግእዝ፡ ተኣምር (ተኣምራት)፡ ይባላል ።
ታምር፡ ድንቅ፡ አመረ ።
ታምሮች፡ ታምራት፡ ጕዶች፡ ድንቆች።
ታሞ፡ በመርሐ ቤቴ ውስጥ ያለ ተራራ ።
ታሞ ተራራ፡ ተመመ ።
ታሞ፡ ተበሽቶ ዐዝኖ ።
ታሞ አይድኔ፡ ች ።
ታሠሠ (ተኀሠ)፡ ተዞረ ተሻ ተፈ
ታሠሠ፡ ተጠረገ ተወለወለ ታበሰ ም ጣዱ ።
ታሠረ (ተዐሠረ)፡ ዐሥር ኾነ ተ ባለ ።
ታሰረ (ተአስረ)፡ ተያዘ ተጋዘ ። ታቈረኘ/ተአኵተ ተቈረኘ፡ ተተበተበ፡ በፍቅር አንድ ኾነ ጸና (፩ሳሙ፡ ፲፰፡ ፩) ። (እግር ተወርች ታሰረ) እግሩ ከእጁ ጋራ ባንድነት ተቀፈደደ። (የፊጥኝ ታሰረ) ፪ እጁ የኋሊት ተገረኘ።
ታሰቀ፡ ተጠለፈ ተጌጠ ተዥጐረጐረ ።
ታሰበ (ተሐሰበ)፡ ተጤነ ታወሰ ትዝ አለ ("(ኢሳ. ፷፭፥ ፲፯፡ ግብ. ሐዋ. ፳፥ ፴፩)") ።
ታሳሪ፡ የተያዘ የሚታሰር።
ታሳቢ (ተሐሳቢ)፡ የሚታሰብ የሚ ታወስ ።
ታረመ (ተሐርመ)፡ ተተወ ተከለ ከለ (ተለየ ተቀደሰ - ዘሌ. ፳፯፥ ፳፩)
ታረመ፡ ተቈረጠ ተሰጠ መሬቱ "
ታረመ፡ ተነቀለ ተኰተኰተ (ተወገደ ጸያፉ ስሕተቱ ግድፈቱ ") ።
ታረሰ (ተሐርሰ)፡ ተተለመ ተገመሰ ተገለገለ ተሰበተ ታየመ ለሰለሰ ("(ሕዝ. ፴፮፥ ፱)") ። "(ተረት)" - በዱሮ በሬ አይታረስም ።
ታረሰች (ተኀረሰት)፡ ተመገበች ' ተቀለበች (በሚገባ በላች ጠጣች ") ።
ታረረ (ተአረ)፡ ታጨደ ተሰበሰበ ተለቀመ ፲ ተጠቀለለ ።
ታረቀ (ተዐርቀ)፡ ቀና ቀጥ " አለ፡
ታረቀ፡ ጐበጠ ተቀለሰ ተለመጠ ።
ታረቀ፡ ጥልን ተወ ተስማማ ። ፱ኛ ውን ወይ እይ ።
ታረበ (ተደረ)፡ ተበላ ወደ ሆድ ገባ ወረደ እራቱ ("(ተደራጊ)") ።
ታረበ (ተደረ)፡ ተበላ ወደ ሆድ ገባ ወረደ እራቱ ("(ተደራጊ)") ።
ታረበ፡ በላ ተመገበ ተጋበዘ ("(ኣድ ራጊ)") ።
ታረበ፡ በላ ተመገበ ተጋበዘ ("(ኣድ ራጊ)") ።
ታረተ፡ ታከበ፡ ተከበበ፡ ተጐረሠ፡ ተበላ። ተቀረቀበ፡ ታሰረ፡ ተወደነ፡ ተወቃ።
ታረተ፡ አራት ኾነ ተባለ ።
ታረዘ (ተዐረዘ/ለበሰ)፡ ልብስ ፥ዐረ ረበት (ተራቈተ - ኢዮ. ፳፬፥ ፲፡ ማቴ. ፳፭፥ ፴፰) ።
ታረደ (ተሐርደ)፡ ተገዘገዘ ተከረከረ ተቈረጠ ተቀረደደ ማንቍርቱ ። "(ተረት)" - ያባያ እናት አትታረድም ።
ታረደ፡ ተማሰ ተጐደበ ጐደጐደ ።
ታረገ፡ ተወጣ ወደ ላይ ተኼደ ("ተኼ ደበት ") ።
ታረገ፡ ተወጣ ወደ ላይ ተኼደ ("ተኼ ደበት ") ።
ታረገ፡ ኣቡነ ዘበሰማያት ተባለ ተጸ
ታረገ፡ ኣቡነ ዘበሰማያት ተባለ ተጸ
ታረፈ፡ ተቈረጠ ("ዕራፊ ኾነ ") ።
ታረፈ፡ ኾነ ተደረገ ዕረፍቱ (ቍጭ ') ።
ታሪከ ሙሴ፡ የሙሴ ታሪክ (ሙሴ ያደረገው ታምር የጻፈው መጽሐፍ) ።
ታሪከ ነገሥት፡ የንጉሦች ታሪክ...የነገሥታትን ትውልድና ዘመን አገዛዛቸውን ሥራቸውን ዕድሜያቸውን በጊዜያቸው የኾነውን የተደረገውን የሚናገር መጽሐፍ (ክብረ ነገሥት) ።
ታሪከ ዓለም፡ የዓለም ታሪክ (ጊዮርጊስ ወልደ ሐሚድ በግእዝ ቋንቋ የጻፈው) ።
ታሪከኛ (ኞች)፡ ዝኒ ከማሁ ታሪክ...ያለው ባለዝና ስመ ጥር ።
ታሪካም፡ ባለታሪክ (ታሪክ የሠራ የሚያወራ) ።
ታሪክ (ኮች)፡ ዜና ያለፈ ነገር በ...ቃል በመጽሐፍ ሲያያዝ የመጣ ።
ታራ፡ ተኰሳ ተዘበለለ ወደቀ ።
ታራ፡ የሰው ስም (የአብርሃም አባት) ።
ታራሚ፡ የሚታረም የሚነቀል ።
ታራቂ (ተዐራቂ)፡ ቀጥ የሚል (ተ ቀላሽ ") ።
ታራቂ፡ የሚታረቅ (ተፋቃሪ - ያዕ. ፫፥ ፲፯) ። "(ተረት)" - ካጣቢ ' አድራቋ (ከተጋች ታራቂ ") ።
ታራጅ፡ የሚታረድ (ሙክት ፍሪዳ ") ።
ታራጅ፡ የአየር ("የትንፋሽ") ወደ ሳንባ መመላለሻ ሥጋዊ ውዥሞ (ቀጪን ጕረሮ - ፈረንጆች ፋረንክስ ይሏታል ") ።
ታሸ (ተሐስየ)፡ ተለወሰ ለፋ ተዳ መጠ (ዞረ - ተጠመዘዘ - ተደረጠ ") ።
ታሸለ፡ ተጨመረ ታከለ፡ ቀላ ነጣ፡ ተለካ ተከነዳ ተቀጠበ ።
ታሸመ፡ ተሠራ ተጐነጐነ ተደበለ ።
ታሸገ ።
ታሸገ፡ በጥብቅ ተዘጋ ተመረገ ተደፈነ፡ ተፈረመበት ታተመ ።
ታሻሚ፡ የሚታሸም ጠጕር ራስ ።
ታቀበ (ተዐቅበ)፡ ተጠበቀ (ተመላ ተሠየመ ") ።
ታቀበ፡ ተጠጋ ተደገፈ (ተሸፈነ ተከ ለለ ") ።
ታቀደ (ተዐቅደ)፡ ተለካ ተወሰነ ።
ታቀፈ (ሐቀፈ)፡ ዐቀፈ ያዘ ("(፪ነገ ፬፥ ፲፮)") ። "ታቀፈን" "ዐቀፈ" ማለት የስሕተት ልማድ ነው ። "ዐደገ (ኀደገ)" ብለኸ ፪ኛውን ታደገ ፥ ተመልከት ።
ታቀፈ (ተሐቅፈ)፡ ተያዘ ታቈረ በ ክንድ በክንፍ ።
ታቃፊ፡ የታቀፈ/የሚታቀፍ (ዐቃፊ ሕፃን ፥ ያዥ ") ።
ታቈረ (ተዐቍረ)፡ ተቋጠረ ታቀፈ ።
ታበለ (ተሐብለ)፡ ተዋሸ (ውሸት ኾነ ተቀጠፈ - "(የማይታበል)" - ከውነት በቀር ሐሰት የማይኾን - ተነግሮ ሳይፈጸም የማይቀር - አይደርስም ተብሎ የማይጠረጠር ያምላክ ቃል) ።
ታበሰ፡ ተጠረገ ፥ ተወለወለ ።
ታበቀ፡ ተወጋ ።
ታበቀ፡ ደቀቀ ፥ ታመቀ (ተመሪ ተሪ) ።
ታበበ፡ ትዝብትን ፈራ (አ...በበ) ።
ታበተ፡ ተጠለፈ ታሰረ ተንጠለጠለ ።
ታበዘ (ተኀብዘ)፡ ተጋገረ።
ታበየ (ተዐበየ)፡ ተቢተ/ከፋ/ ተመካ/ ተደገገ ፥ ተጓደደ (ልቡ ዐበጠ ተነፋ በኵራት - እኔን ማን ያኸለኛል አለ - ራሱን ከፍ አደ ረገ ኰፈሰ ፥ ኤር. ፵፰፥፳፱) ።
ታበየ፡ ተደገገ ዐበየ ።
ታባ፡
ታባ (ተኀብአ)፡ ተሸሸገ/ተሰወረ ' ተ ደበቀ ።
ታባቢ፡ የታበበ ፥ የሚታሰብ ፥ ባለይሉኝታ ።
ታቦር፡ ጌታችን የአምላክነቱን ክብር ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ተራራ (በምድረ እስራኤል ያለ) ።
ታቦተ ሕግ፡ በውስጧ ሕግ ያለባት...ታቦት ።
ታቦተ ሙሴ፡ የሙሴ ታቦት ።
ታቦተ ጽዮን፡ በዳዊት ዐምባ የነበረች ታቦት ። "ነብሪድ ይሥሓቅ ግን አኵስም መጥታለች" ይላል ።
ታቦቲቱ፡ ታቦቷ ያች ታቦት (፪ዜና. ፭፡ ፬, ፭) ።
ታቦት (ቶች)፡ ዐሠርቱ ቃላት የተጻፉባቸው ኹለት ጽላቶች (በውስጧ ያሉባት ሣጥን በወርቅ የተለበጠች - ጽላቱ ከእብነ በረድ ታቦቲቱ ከማይነቅዝ ዕንጨት ነው የተቀረጹት - ኹሉም የሙሴ ሥራዎች ናቸው - ጽላት እንደ መጣፍ ታቦት እንደ ማኅደር - ኢያ.
፫፡ ፲፬, ፲፯) ።
ታቦት፡ ቁመቱ አንድ ክንድ ተስንዝር ጐኑ አንድ ክንድ ውፍረቱ ሦስት ጣት የኾነ የክርስቲያን ጽላት ("ታቦት" መባልን ከሣጥኑ ወስዷል) ። ስመ አምላክ አልፋ ወዖ የመልአክ የነቢይ የቅድስት ማርያም የሐዋርያ የጻድቅ የሰማዕት ስም "ታቦተ እገሌ" እየተባለ በላዩ ይጻፍበታል ። በየማእዝኑ ጫፍ የአርባዕቱ እንስሳ ሥዕል ይቀረጽበታል ። ከግብጽ መጥተው በአኵስም የነበሩት መዠመሪያዎቹ ታቦቶችም "ታቦተ ማርያምና ታቦተ ሚካኤል" ናቸው ።
ታቦት፡ በራስ ላይ የተሣነ እጅ በሸኩቻ ጊዜ መዶሻን የሚረታ ትርፍ ተምሳሊት ።
ታቦት ተሸካሚ፡ በራሱ ላይ ታቦት የሚይዝ ቄስ መነኵሴ ።
ታቦት ተቀረጸለት)፡ በቃ ጻድቅ ቅዱስ ኾነ፡ ስሙ በጽላት ላይ ተጻፈ፡ ቤተ ክሲያን ታነጸለት ።
ታቦት አነገሠ፡ በወረብ በዘፈንና በ...ልልታ በከበሮ በጸናጽል በጭብጨባ አከበረ (በቤተ ክሲያን ዙሪያ ሦስት ጊዜ አዞረ) ።
ታቦት ወጣ፡ ነገሠ ዑደት ተደረገ ።
ታቦት ዘፋኝ፡ ለ...ስለ የቀረው ነው (ለታቦት ስለ ታቦት የሚዘፍን የታቦት ዘፋኝ) ።
ታቦት ዘፋኝ)፡ "ተክልዬ ተክልዬ ተክለ ሃይማኖት ሳንቃው መከፈቻው የሚካኤል ለት፡ ትምሩኝ እንደኾን ልምጣ በግንቦት"። ብረትና መስተዋትም ሉሕና መዝጊያ ይኾናሉ።
ታቦት ዘፋኝ)፡ "ያች እምዬ ማሪያም የሴት አፈቻላ ግምጃ ትካሳለች ከሰው ስትጣላ" ። "አፈቻላነቷም ስለ ኃጥኣን ነፍሳት ነው" ።
ታቦት፡ ጌታ መኰንን ባለቤት ("ታቦተ መልካም ዐጸደ ክፉ" እንዲሉ - ዐጸድ የተባለ ቤተ ሰብ ነው) ።
ታቦትኛ፡ የታቦት አካኼድ ።
ታተመ (ተኀትመ)፡ ማኅተም ተደረ ገበት (በመኪና ተጻፈ ") ።
ታተረ፡ ተጋ ጣረ ለፋ ።
ታተበ (ተዐትበ)፡ ተቈረጠ ።
ታተተ (ተአተተ)፡ ተወገደ ራቀ ተገለለ ተለየ ።
ታቱ (ታሕቱ)፡ ታቹ ሥሩ ። የቱ ዝርዝርነት አባትን ያያል ።
ታቱ፡ ሥግራ አለ ። (ትግ፡ ታተ)፡ የልጅን እጅ ይዞ መንገድን መራ መኼድን አስተማረ ። ዳግመኛም ታቱ (ተእቱ)፡ "ትገባለኸ" ተብሎ ይተረጐማል ("አቱን" አስተውል) ።
ታታ (ተወተ - ትግ፡ ተትዐ)፡ ወን...ፊትን መረብን ሥራ ዐልጋን ጠፈረ ጠለፈ አዋሰበ አያያዘ ፫ቱን ክር ወይም ገመድ ጐነጐነ ። ("የተፈተለ ከኹለት የተታታ ከሦስት" እንዲሉ) ።
ታታ፡ ቲቲቲ ።
ታታሚ፡ የሚታተም መልክት ማንኛ ውም ' ጽሑፍ ።
ታታሪ (ዎች)፡ የታተረ/የሚታትር (ጣሪ ትጉህ) ።
ታታሪነት፡ ትጉህነት ።
ታቼ፡ የዚህ ከፊል ነው ።
ታች (ታሕት/ተሐተ)፡ ንኡስ አገ...ባብ ጥግ ሥር ዝቅታ ግርጌ ። ("በና ከ ሲሰማሙት" "በታች" "ከታች" ይላል) ። ("የሰው በታች" - ሞኝ ወራዳ) ። ("የበታች በታች" - መጨረሻ ታች ስፍራ ጭፍራ) ።
ታች በላቸው፡ ከብቶቹን ካፋፍ ወዳረኸ አውርዳቸው ።
ታች በላቸው፡ ጠላቶቻችንን አዋርዳቸው ("አንተ የበላይ እነሱ የበታች ይኹኑ" ማለት ነው) ።
ታች በሌ፡ የሰው ስም ("ታች በል") ።
ታች ቤት፡ በታች ያለ ቤት (በጐንደር የበኣታ' ኣጥቢያ የሐዲስ መምህራን የነበሩበት) ።
ታች አለ፡ ወደ ታች ነዳ ቍል...ቍል ወሰደ ።
ታችኛ (ኞች)፡ የታች የቈላ በታች የሚኖር ። "ታችኛው ታችኛዋ ታኛዪቱ ታችኞቹ" እያለ ይዘረዝራል ።
ታችኞች፡ ቈለኞች አጋንንት ኀጢአ...ተኞች ።
ታቾች፡ ጥጎች ሥሮች ግርጌዎች ። ታቼ፡ የሰው ስም ("ታች" የሚል) ።
ታነቀ (ተኀንቀ)፡ በገመድ በጠፍር ዐንገቱ ታሰረ ተፈተረ ተሰቀለ ተንጠለ ጠለ ሲል አለ (በገዛ እጁ ወይም በሌላ ሰው እጅ ") ።
ታነቀ፡ በምግብ ተዘጋ ጕረሮው ። ("(ተ ረት)" - ሥሡ ሲበላ ይታነቃል - ሐሰተኛ ሲና ገር ይታወቃል ") ።
ታነደ፡ አንድ፡ ኾነ፡ አንድ፡ ተባለ።
ታነጠ፡ ተሠራ ቤቱ ።
ታነጠ/ታነጸ (ተሐንጸ)፡ ተጠረበ ተላገ ተፈለፈለ ተቀረጸ ተበሳ ።
ታኒካ (ዎች)፡ ጋዝ ዘይት ፍት ቤንዚን ሌላም ቅባት በያይነቱ ከውጭ እገ...የሚመጣበት ሥሥ ቈርቈሮ ("ትንሹ ጣሳ" ይባላል) ።
ታኒካ፡ የወርቅ ሰሌዳ (ዘፀ. ፳፰፡ ፴፮, ፴፰) ። ታንኳ (ዎች)፡ ከቀርክሓና ከሸንበቆ ከደንገል የተበጀ የባሕር መንገደኛ...በላዩ ተቀምጦ የሚሻገርበት (ማቴ. ፬፡ ፳፩, ፳፪) ። "ፍልኳንና ጀልባን" አስተውል ።
ታናሹ፡ የርሱ፡ ታናሽ፡ ያ፡ ታናሽ።
ታናሼ፡ የኔ፡ ታናሽ፡ የበታቼ ።
ታናሽ፡ (ሾች)፡ በቁሙ፡ በዕድሜ፡ በመጠን፡ በማንኛውም፡ ነገር፡ ከሌላው፡ ያነሰ፡ ዝቅ፡ ያለ ።ታናሽ፡ ወንድም፡ አባተ፡ ታናሽ፡ እንዲሉ ።
ታናሽ፡ ትንሽ፡ በቁሙ፡ አነሰ ።
ታናሽ፡ የሥጋ፡ ስም፡ ከታወቁት፡ ብልቶች፡ አንዱ፡ ዋነኛው ። (ግጥም)፡ ታናሽ፡ ታላቅ፡ በላን፡ ከርካ፡ አደባባይ፡ ክርስቲያን ' ሆይ፡ አለልብ፡ ሥጋ፡ ይጣፍጣል፡ ወይ። ዐጤ፡ ዮሐንስ፡ በግድ፡ ቍረብ፡ ያሉት፡ እስላም፡ የገጠመው፡ ነው፡ ይባላል።
ታናሽ/ትንሽ/ያነሰ፡ አነሰ ። ተረን፡ የሚዛን ቈዳ በገመድ የተንጠ...ለጠለው ቋቱ ። ድንጋዩም "ተረን" ይባላል (፻፲፫ ተኩል ግራም ያነሣል - ፪ አበት ፩ ተረን ነው) ።
ታናሽነት፡ ታናሽ፡ መኾን፡ ሕፃንነት፡ ልጅነት፡ (መዝ፻፳፱፡ ፩፡ ፪)።
ታናሿ ታናሽቱ፡ ያች፡ ታናሽ፡ የታላቅ፡ እት፡ ተከታይ፡ ሴት፡ ልጅ፡ (ዘፍ፲፱፡ ፴፩)።
ታናሿ፡ የርሷ፡ ታናሽ።
ታናቂ፡ የሚታነቅ ።
ታናናሽ፡ (ሾች)፡ ውስጠ፡ ብዙ፡ ጥቃቅን ። ታናናሾች፡ ልጆች።
ታንቆ ሞተ፡ ዐንገቱን አስሮ ተንጠ ልጥሎ በገዛ እጁ ማለት ነው ("(፪ሳሙ. ፲፯፥ ፳፫፡ ማቴ. ፳፯፥ ፭)") ።
ታንከኛ (ኞች)፡ ታንክ ነጂ ባለታ...ንክ ተኳሽ ።
ታንክ (ኮች)፡ የጦር መሣሪያ...ኪና በጦርነት ሰዓት ብዙ ጥይት የሚተስ የሀረር ጋን ። ባ፲፱ኛው ሴክል በትልቁ ጦርነት ጊዜ ያወጡት እንግሊዝና ፈረንሳይ ናቸው ይባላል ።
ታንጕት፡ የሴት ስም ።
ታኘከ (ተሐንከ)፡ ተቈረጠመ ተመ ሰኳ ተበላ (ቈሎው ንፍሮው ዐጥንቱ ሣሩ ቅጠሉ ") ።
ታከለ፡ ተጨመረ ፥ ተደገመ፡ ልክ ኾነ ። እታከል ከግመል ከግዜር ጋራ ሞተኸ፡ ትቀረው የለሞይ እሑድ ተለይተኸ (ኣልቃሽ) ።
ታከለ፡ ታከለች፡ የወንድና የሴት ስም ።
ታከመ (ተሐክመ)፡ ታገመ (ሰውነቱ ታሸ ተጠገነ ") ።
ታከረ፡ ተለወጠ፡ ቈየ፡ ዘገየ፡ ታደሰ።
ታከበ፡ ተሰበሰበ ፥ ተከማቸ ።
ታከተ (ተከተ)፡ ለፋ ደከመ ሰነፈ ሰለቸ (ሳሙ. ፯፡ ፰) ።
ታከተ፡ ተሰበሰበ፡ ተከማቸ፡ ታረተ ።
ታከተ፡ ታረተ፡ አከተ ።
ታከተ፡ ደከመ፡ ታከተ፡ (ተ)
ታከከ (ተሐከከ)፡ ተፈገፈገ/ተጠ ቈመ/ተጫረ ።
ታከከ፡ ቀረበ ተጠጋ ።
ታከከ፡ ተላገ ተፋቀ ።
ታካሚ፡ የሚታከም (ሕመምተኛ በሽተኛ ") ።
ታካታ፡ ዝኒ ከማሁ (ለታካች ደካማ) ።
ታካችነት፡ ታካች መኾን ስንፍና ደ...ካማነት ።
ታካኪ፡ የሚታከክ (ተጠጊ ") ።
ታኰተ፡ (ተአኵተ)፡ ተመሰገነ ' ተባረከ፡ ተጸለየ፡ ኾነ፡ ተደረገ፡ ጸሎቱ።
ታኰተ/ተአኵተ፡ ተመሰገነ፡ ተባረከ፡ ተጸለየ ኾነ ተደረገ ጸሎቱ።
ታወሰ (ተሐውሰ)፡ ታሰበ (ትዝ ") ።
ታወረ (ፆረ)፡ ዐይኑ ጠፋ/ፈሰሰ/ዕውር ኾነ ("(ኢሳ. ፳፱፥፱፡ ሮሜ. ፲፩፥፯)") ።
ታወረ፡ ጥፍሩ ረገፈ/ጐለደፈ ("የጣት ") ።
ታወቀ (ተዐውቀ)፡ ተለመደ/ተለየ ("(ተረት)" - የወፍ ወንዱ የሰው ሆዱ አይታ ወቅም ") ።
ታወቀ ተረዳ ("ተለበመ ተሰፈረ ተመላ ተሠየመ ልብም የተለበመ የመገበሪያ ዶቄት የመላበት ጕብ ሸክላ ልብማት ዕውቀት ምሉነት ") ።
ታወከ (ተሀውከ)፡ ፈራ ደነገጠ፡ ተናወጠ ተነቃነቀ ተበጠበጠ፡ ተነሣሣ፡ ተሸበረተ ተራመሰ ። (፪ነገ ፮ ፥ ፲፩ ። መዝ ፮ ፥ ፪ ፥ ፫ ። ዮሐ ፮ ፥ ፲፰) ። (ዐይኑ ታወከ)፡ አላይ አለ፡ ማየት ተሳነው ።
ታወደ፡ ተዞረ (ቤተ ክሲያኑ ኾነ ተደረገ ዑደቱ ") ።
ታወጀ፡ ተነገረ/ተለፈፈ (ዐዋጁ ") ።
ታወገ (ተዐወገ)፡ አላገጠ/አለመጠ ።
ታዊ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ታዋቂ፡ የሚታወቅ/የሚለመድ ።
ታዋኪ፡ የሚታወክ የሚሸበር ።
ታዋጊ (ጎች)፡ አላጋጭ/አልማጭ ("(፩ጢሞ. ፭፥፲፫)") ።
ታው፡ ስመ ፊደል "ተ" (ትርጓሚው መ...ፈረሻ ማለት ነው) ።
ታዘለ (ተሐዝለ)፡ በዠርባ ተለጠፈ/ ተደረበ/ተያዘ (ሸክም ኾነ - ተፈናጠጠ - "የታ ዘለ - በለምድ - የተረገዘ - በሆድ" እንዲሉ) ።
ታዘበ (ተሐዘበ)፡ አየ/ተመለከተ/ መሰከረ (ዐሰበ ጠረጠረ - ናቀ ነቀፈ - "የማታደር ገውን አደርጋለኹ ብትል ሰው ይታዘብኻል ") ።
ታዘበ፡ ተጐነጐነ/ተበጀ/ተሠራ ("ታዘብኩሽ ቂጤ ናቅኹሽ ነቀፍ ") ።
ታዘበ፡ ተጠለፈ/ተቈለፈ ።
ታዘበ፡ ጠረጠረ፡ ዐዘበ ።
ታዘነ (ተሐዝነ)፡ ተተከዘ/ተለቀሰ (ኾነ ተደረገ ሐዘኑ ") ።
ታዘዘ፡ (ተአዘዘ)፡ (ዘፍ፳፱፡ ፲፰፡ ፳) ሰማ፡ ተቀበለ፡ በጄ፡ ይኹን፡ ዕሺ፡ በጎ፡ አለ፡ ተገዛ፡ አገለገለ።
ታዘዘ፡ ተነገረ፡ ሥራው፡ ግብሩ። (የክራር፡ መቺ፡ ግጥም)፡ አዙረኸ፡ አዙረኸ፡ አገሬ፡ መልሰኝ፡ በሹም፡ የታዘዘ፡ ዐፈር፡ አታልብሰኝ፡
ታዛ፡ ከምድራኸ ቀጥሎ ግራና ቀኝ በሰበሰብ ያለ ቅይድ ።
ታዛ፡ የምድራኸ ቅይድ፡ ዘለ ።
ታዛቢ (ቦች)፡ የታዘበ/የሚታዘበ (የማኅበረተኛ ተመልካች ምስክር - ታዛቢ ነሽ የሴት ስም ") ።
ታዛቢነት፡ ታዛቢ መኾን (ተመልካች ነት ምስክርነት ") ።
ታዛዥ፡ (ዦች)፡ ተአዛዚ)፡ የሚታዘዝ፡ ተላላኪ፡ አሽከር፡ አገልጋይ፡ ሎሌ፡ ዕሺ፡ ባይ፡ ፈቃደኛ፡ ገር፡ ትሑት።
ታዛዥነት፡ ትሑትነት፡ ፈቃደኛነት፡ ታዛዥ፡ መኾን።
ታዛይ፡ ተማሪ ቤት፡ ዐዘለ ። ተዣረ ኰራ (ዣረ) ። ትሑት (ተሐተ)፡ ቅን ገር ታዛዥ...ተዋራጅ ።
ታዛይ ከል፡ ተፈናጣጭን ከልካይ የወዴላ ዘለበት ።
ታዛይ፡ ከቤት ግንብና ግድግዳ በስ ተውጭ ተለጥፎ የተሠራ ጓዳ ።
ታዛይ፡ የሚታዘል (ሕፃን ሙጫሊ ተፈ ናጣ ") ።
ታየ፡ (ተርእየ)፡ ተገለጠ ፥ ታወቀ ፥ ተረዳ ፥ (፩ጢሞ ፫፡ ፲፮) ። ለልጅ ይታየዋል እንዲሉ።
ታየ፡ የሰው ስም ።
ታየረ፡ ተቀላቀለ/ተደባለቀ/ተዋዋደ ።
ታየበት፡ ተፈረደበት ፥ ተበየነበት፡ ተረታ ።
ታየች፡ የሴት ስም ።
ታደለ (ተዐድለ)፡ ተፈረደ ።
ታደለ፡ በተራ ተሰጠ (መብሉ መጠጡ ልብሱ ገንዘቡ - አስ. ፩፥፯ - ዕድል ተቀበለ ሰዉ - "(ተረት)" - ያልታደለ ከንፈር ሳይሳም ያረጃል - "አማረን" እይ ") ።
ታደመ፡ ተሤረ/ተመከረ (ክፉው ") ።
ታደመ፡ ተጠራ/ተቀጠረ/ተሰበሰበ።
ታደመ/ታደመች፡ የወንድና የሴት ስም ።
ታደረ፡ ሌሊቱ ተፈጸመ/ነጋ ።
ታደረ፡ ተኖረ ።
ታደረ፡ ታገገ ፥ ተደነባ ጸና ።
ታደበ፡ ተሠራ ተደነገገ ተቀጣ ።
ታደነ፡ ተፈለገ/ተሻ/ተያዘ (እወጥመድ ገባ - ተወጋ ተገደለ ") ።
ታደገ (ተኀድገ)፡ ተተወ í ከመከራ ወጣ ዳነ ።
ታደገ (አኅደገ)፡ አስተወ/አስጣለ/አ ስለቀቀ (አዳነ ተቤዠ ራሱን ለውጦ በታሰረ ፈንታ ታስሮ ተይዞ ወባት ገብቶ - ዘዳ. ፳፪፥፳፯፡ ፪ሳሙ. ፲፱፥፱ - "ታደገን አዳነ ማለት የልማድ ስሕተት አፈታት ነው ") ።
ታደገ፡ ተቈረጠ/ተመለሰ (ቀና ቀጥ አለ ") ።
ታደገ፡ አካለ መጠን ካደረሰ ከጐለመሰ ።
ታደገ፡ አደገ ።
ታደገ፡ አዳነ ፥ —ዐደገ ።
ታደገ፡ የሰው ስም ።
ታደፈ (ተኀደፈ)፡ ታሠሠ/ተጠረገ/ ተወለወለ ።
ታዲያ/ታዲያስ፡ ንኡስ አገባብ ኀይለ ቃል። "ተዚያ ወዲያ" ማለት ነው ("ታዲያ ምን ትለኛለኸ ታዲያስ ምን ታደርገኛለኸ") ።
ታዳሚ፡ የሚታደም (ወደ ሰርግ ቤት ተጠሪ ") ።
ታዳኝ፡ የሚታደን (ተገዳይ እውሬ ") ።
ታዳይ (ዮች)፡ የሚታደል (ተሰጪ ገንዘብ ተቀባይ ሰው ") ።
ታዳጊ (አኅዳጊ)፡ የታደገ/የሚታደግ (የተቤዠ አዳኝ - ፪ነገ. ፲፫፥፭፡ ምሳ. ፳፫፥፲፩ - "ስለ ታዳጊው ጌታ" እንዲሉ) ።
ታዳጊ አልባ፡ አዳኝ የሌለው ("(መዝ ፯፥፪)") ።
ታዳጊ፡ አዳኝ ፥ —ዐደገ ።
ታዳጊ፡ አዳጊ፡ የሚያድግ፡ ለግላጋ ወጣት ።
ታዳጊ፡ የሚቈረጥ/የሚመለስ/የሚገዛ (ጐባባ ዕንጨት ") ።
ታዳጊ፡ የሚያድግ —አደገ ።
ታዳጊነት፡ አዳኝነት ።
ታዳጎች፡ የታደጉ/የሚታደጉ (አዳኞች - ሕዝ. ፴፪፥፳፩) ።
ታጀለ፡ ተሸፈነ/ለበሰ/ተጠቀለለ/ለሰ ለሰ ።
ታጀረ፡ ኰራ ዐጀረ ። ቲሃ (ተዪህ/ቴሀ)፡ ችቦ ዳቦት ሽጕ...የጭራሮ መብራት ።
ታጀበ፡ በፊት/በኋላ/በቀኝ/በግራ ተ ከበበ ።
ታጀበ፡ ተሰበሰበ/ታከበ/ተከማቸ/ተመሰ ገነ/ታወቀ ።
ታጃቢ፡ የሚታጀብ (ባለጭፍራ) ።
ታጅ፡ የሚታጨድ ሣር እኸል ።
ታገለ (ተዐገለ)፡ ተጫረ/ተኰተኰተ ።
ታገለ፡ ተመለሰ/ታደሰ ።
ታገለ፣ ተናነቀ።
ታገለ/ተናነቀ፡ ዐገለ ።
ታገለ/ተጋገለ (ተዓገለ/ተቃለሰ)፡ ተናነቀ (ለመጣል ለመቀማት - ዘፍ. ፴፪፥፳፬) ።
ታገመ (ተሐግመ)፡ ተሳበ/ተጠባ/ ተመጠጠ/ተመጠመጠ ("ድምቢጥን" እይ) ።
ታገሠ (ተዐገሠ)፡ ቻለ/ጸና/ዝም አለ ("(ሮሜ. ፱፥፳፪)" - ነገር ግን "(ዐገሠ)" ቻለ ታገሠ ተቻለ ተብሎ ቢተረጐም በቀና ነበር) ።
ታገሠ፡ ቻለ (ዐገሠ)
ታገሥ (ተዐገሥ)፡ ቻል/ጽና/ዝም በል ።
ታገረ፡ ታወከ ተመከተ ተረዳ ታገዘ ።
ታገሻ፡ ተቋተ/ተደቀነ ("ጥሬው ቅይጡ ") ።
ታገተ (ተዐግተ)፡ ተያዘ/ተወሰደ (ዋሱ ገንዘቡ ") ።
ታገዘ (ተሐግዘ)፡ ተረዳ/ዐረፈ።
ታገደ፡ ተገታ ተከለከለ ተከተረ ተወ ሰነ ቆመ ቀጥ አለ ተጠበቀ ።
ታገገ (ተሐገገ)፡ ተወሰነ/ተደነገገ ፥ ተ ሠራ ሕጉ ።
ታጋመደ፡ ተጣመረ/ተጠማጠመ/ተጠማዘዘ/ተዋሰበ ።
ታጋሚ (ተሐጋሚ)፡ የሚታገም (በሽተኛ ሕመምተኛ) ።
ታጋሽ (ሾች)፡ የታገሠ/የሚታገሥ (ቻይ - መክ. ፯፥፰፡ ናሆ. ፩፥፫) ።
ታጋሽነት፡ ታጋሽ መኾን (ቻይነት) ።
ታጋች፡ የሚታገት ሰው ።
ታጋዥ (ተሐጋዚ)፡ የሚታገዝ/የሚ ረዳ ።
ታጋይ (ተዓጋሊ)፡ የታገለ/የሚታገል ።
ታጋጅ፡ የሚታገድ ተከታሪ ።
ታግዳ፡ የሴት ስም፡ ቶሎ ያልተወለደች ልጅ ።
ታጐለ (ተሀጕለ)፡ ጠፋ ፥ ቀረ ፥ ተዳ ፈነ ፥ ተቋረጠ ግብሩ ቅዳሴው ። (ነሐሴ ፫) ።
ታጐረ፡ ተሰበሰበ ተከማቸ ታጀበ ተዘጋ ።
ታጠረ (ተሐጽረ)፡ ተከበበ/ተከለለ/ ተቀጠረ/ተጀጐለ/ተገረገረ/ተማገረ/ተሸመ ጠጠ (ተገነባ ተካበ ") ።
ታጠረ (ተዐጽረ)፡ ተጠመቀ/ተጨ መቀ ።
ታጠረ፡ ተሸጠ (ተለወጠ ተሸቀጠ ") ።
ታጠረ፡ ተገበረ/ተከፈለ/ተቀረጠ ።
ታጠቀ፡ በወገቡ አሰረ (ዐጠቀ) ።
ታጠቅ፡ ያጤ ቴዎድሮስ የፈረስ' ስም ("(ግጥም)" - ታጠቅ ብሎ ፈረስ ካሳ ብሎ ስም - ዐርባርብ ይሸበራል ኢየሩሳሌም ") ።
ታጠበ (ተኀፅበ)፡ ተረገጠ/ተንጨፈ ጨፈ/ታሸ/ጐረፈ/ተለቀለቀ/ጠራ/ጸዳ/ነጣ ።
ታጠነ (ተዐጥነ)፡ የዕጣንን የሎሚን ቅርፊት የማንኛውንም የጣፋጭ ዕንጨትና የመድኅኒት ጪስ ተቀበለ (ዘገበ - ልብሱ ሰዉ ቀፎው - "ኅዳርን" ተመልከት ") ።
ታጠፈ (ተዐጽፈ)፡ ዕጥፍ ኾነ (ተመለሰ ተቀለበሰ ተኰረመተ - ቈርበቱ እንጀ ራው ልብሱ ምንጣፉ እግሩ - ኢሳ. ፴፬፥፬) ።
ታጠፈ፡ አቅጣጫውን ትቶ ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ተመልሶ ኼደ ።
ታጣ (ተኀጥአ)፡ ተገደፈ/ተረሳ/ጠፋ ("(ሕዝ. ፴፫፥፳፰)") ።
ታጣ፡ ጠፋ፡ ተተወ፡ ቀረ። (ተረት)፡ በቃል፡ ያለ፡ ይረሳል፡ በመጣፍ፡ ያለ፡ ይወረሳል ።
ታጣሪ፡ የሚታጠር ስፍራ ።
ታጣቂ (ዐጣቂ)፡ የታጠቀ/የሚታ ጠቅ (አደግዳጊ - "(ግጥም)" -መይሳው ካሳ ባጪር ታጣቂ - ዘመድ ከዘመድ አደባላቂ ") ።
ታጣቢ፡ የሚታጠብ ልብስ/ዕቃ/ሰው ("ታጥቦ ጭቃ" - የሪያ ዕጥበት ") ።
ታጣኝ፡ የሚታጠን (ታቦት ሥዕል መ ቅደስ - የወተት የጠጅ የጠላ ዕቃ ") ።
ታጣፊ (ዎች)፡ የሚታጠፍ ጣት (ባለማጠፊያ ዕቃ ጌጥ ") ።
ታጨቀ (ተዐጽቀ)፡ ገባ/ተጨመረ/ ተከተተ/ታጀበ ።
ታጨች፡ ባል መጣላት (ሀብቷ ቀና ") ።
ታጨደ (ተዐጽደ)፡ ተቈረጠ/ተቦ ጨቀ ("(ራእ. ፲፬፥፲፮)") ።
ታጪ፡ ለሹመት ለማዕርግ ታሰበ ተ ፈለገ ።
ታጸፈ፡ ታጠፈ ተመለሰ ።
ታፈረ፡ ተፈራ ተከበረ ።
ታፈረ ደጁ፡ የውሻ ስም ("ደጁ ተ ፈራ" ማለት ነው ") ።
ታፈገ፡ ታጀበ ተከማቸ፡ ተመሰገ ።
ታፈፈ፡ ተከረከመ ተቀፈፈ ተከመመ ተቈረጠ ።
ታፋ፡ ከጭን በላይ ከቂጥ አጠገብ በስተጐን ያለ ጥላ (ሠርጓዳው የሙሓይት ካከ - አንቀጹ "ተፈተፈ" ነው) ።
ታፋሪ፡ የሚታፈር/የሚከበር ።
ታፋፊ፡ የሚታፈፍ ።
ታፌ፡ ያ፲ ቀን ቀጠሮ፡ ኦፌን ይዤ ማለት ነው ።
ቴ፡ ምእላድ ("ምናምን ምናምንቴ") ።
ቴሃ ።
ቴምብር፡ ማኀተም የማኀተም ሥዕል (የዓለም ነገሥታት በደብዳቢ ማኅደር ላይ የሚ...ለጥፉት - "ቴምብር" ፈረንሳይኛ ነው) ።
ቴምብሮች፡ ኹሉትና ከኹለት በላይ...ያሉ ብዙዎች ።
ቴዎድሮስ፡ ዐምስቱን ጠቅላይ ግዛቶች...አንድ ያደረጉ የሐበሻ ንጉሥ ።
ቴዎድሮስ፡ የሰው ስም (ምሥራቃዊ ስማዕት - ስንክ.
ጥር ፲፪) ። በጽርእ "ቴዎዶሮስ" "የግዜር ስጦታ" ማለት ነው ይላሉ ።
ቴፈ (ተየፈ)፡ መላተነሣ ተንሳፈፈ ተንካፈፈ ። "ቴፈና ተፋ" በምስጢር ይገጥማሉ ። የቴፈ ሥር በግእዝ "ተፈየ" ነው ።
ት፡ ለቅርብ ወንድ ለቅርብ ሴትና ለሩቅ ሴት ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የኀላፊ ትንቢት መነሻ ይኾናል ("ትጥ ፋለኸ ትጥፊያለሽ ትጥፋለች ትጥፋላችኹ") ።
ት፡ በራብዕ ለሚጨርስ ግስ የዘር ምእላድ ("ገባ መግባት ዘጋ መዝጋት ዘረጋ መዘርጋት ቀባ መቀባት ዘራ መዝራት") ። አንዳንዶዬም በግእዝ በሚወርስ ግስ ምእላድ ሲኾን "እየ ማየት ደረጀ መደርጀት ሰጠ መስጠት" ይላል ።
ት፡ በትንቢት መነሻ እየገባ በቂ ይኾናል ("ትለብሰው የላት ትከናነበው አማራት" - ይኸውም በ"የም" ፈንታ የተነገረ ነው) ። ት፡ ለሩቅ ሴት የአንቀጽ ዝርዝር ("እሱ እሷን ዐወቃት") ።
ት፡ ጥሬነት ባለው ስም ፵ፍ እየተጨመረ ለሴት ዝርዝር ይኾናል ("ማሞ ማሚት ልጅ ልጅት ወንድ ወንዲት ዐጅሬ ሀጅሪት ዝንጀሮ ዝንጀሪት") ።
ትሕትና/ትሑትነት፡ ዝቅታ የፈቃድ...ውርደት ።
ትሕትናም፡ ባለትሕትና ኵራት አልባ ።
ትኋን፡ ተከለ፡
ትኋን፡ ያልጋ ተባይ፡ ተኰነ ። ታኅሣሥ (ኀሠሠ)፡ የወር ስም ፬ኛ...ወር ከመስከረም። ምስጢሩ ጌታን ለመፈለግና ያለበትን ለመመራመር ወደቤተ ልሔም የሰብአ ሰገልን መምጣት ያሳያል ። ባላገርም "ትሣሥ" ይለዋል ።
ትለም፡ ሚት ዕርፍና ጭ...የሚኾን ዕንጨት (ወንዴና ሴቴ ሳራሽ መሰ) ።
ትለም፡ የቅርብ ወንድ (ትእዛዝ አንቀጽ) ።
ትሉ (ትብሉ)፡ ትናገሩ ("እናንተ እንዲህ ትሉ የለምን") ።
ትሉ፡ የማያንቀላፋ እሳቱ የማይጠፋ ገሃነመ እሳት ።
ትሉ፡ ያ ትል የርሱ ትል ።
ትሊ፡ መዠመሪያ የመጣ ሥሥ አቡጀዲ ።
ትላም፡ ትል ያለበት የበዛበት (ባለትል አመንዝራ) ።
ትላበራ (ትግ. ሚሕ)፡ ትል እበራ...ሌሊት የሚያበራ ትል (ኤሌትሪክ ያለው ሀፍም ያበራል) ።
ትላት ።
ትላትል፡ የትል ትል (ብዙ ዐይነት ትል) ።
ትላንትትናንት (ትማልም)፡ ንኡስ አገባብ (የጊዜ ስም - የዛሬ ተቀዳሚ ቀን) ።
ትላንትና/ትናንትና፡ ዝኒ ከማሁና ምእላድ ነው ። ("ግጥም - ትላንትና ማታ ዛሬ ሌሊት በልሜ ምሰሶው ተሰብሮ እባሕር ላይ ቆሜ") ። ከ መነሻ ኹኖት በዘርፍነት ሲነገር "ከትላንት በስቲያ" "ከትላንት ወዲያ" ይላል ("እስተን" ተመልከት) ።
ትል ።
ትል (ሎች)፡ ብል ነቀዝ ተምች...ግንደ ቈርቀር ቅንቡርስ መሰክ ሸሽ ኮሶ እኝት የመሰለው ኹሉ። የሥጋ ትል የሀመድ ጥል ። "እበት ትል ይወልዳል" እንዲሉ ።
ትልልቅ፡ ታላላቅ፡ ረዣዥም፡ ውስጠ፡ ብዙ፡ ከፍ፡ ከፍ፡ ያለ፡
ትልልቆች ፣ ታላላቆች፣ ረዣዥሞች ' ዐዛውንቶች፡ ሽማግሎች፡ ከበርቴዎች፡ ጌቶች #
ትልልፍ፡ ድፍረት ("(፪ዜና. ፴፮፥፲፬)") ።
ትልም፡ የተተለመ...ዥምር ፈር ቡደን ("ትልሞች" - ፈሮች የርሻ ውጥኖች - ኢዮ.
፴፰) ።
ትልቁ፡ ትልቂቱ፡ ታላቋ፣ ታላቂቱ፡ ቷ፡ በል፡ ("ዘፍ. ፲፱፡ ፴፩ ። ዳን. ፬፡ ፴") ።
ትልቅ፣ ታላቅ፡ ከፍ፡ ያለ፡ በመጠን፡ የረዘመ፡ በማዕርግ፡ የበለጠ፡ ዕዛውንት። ወንድናሴትን፡ ለመለየት፡
ትልተላ፡ ትርተራ ልየታ ሥንጠቃ ።
ትልታይ፡ ከድር የወጣ (ማግ ከማግ የተለየ ድሮ) ።
ትልት፡ መትላት ።
ትልት አለ፡ ተላ ።
ትልትላት፡ ብጥታት ሥንጥቃት ።
ትልትል፡ የተተለተለ (ትርትር ሸማ ብጥ ቅድ ሥንጥቅ ") ።
ትልዝ፡ የተለዘ የደከመ ("ትልዝ አለ" - ድክም አለ ነዲዱ...ራቱ) ።
ትሎማ፡ የላ ስምና ነገድ ።
ትሎት (ተለወ/ትልወት)፡ መዳሪያ...ሴት ልጅ ስትዳር አባቷ የሚሰጣት አሽከር ገረድ ወንድና ሴት አልጋይ ከብት ተከትሏት ስለሚኼድ "ትሎት" ተባለ (ትርጓሚውም "መከተል" ነው) ። ("የፈርዖን ዐዋጅ" - ወንድ ወንዱ ለሞት ሴት ሴቱ ለትሎት) ።
ትማትም (ሞች)፡ የተክል ስም...ክብ እንክብል ቀይ ፍሬ ወጥ የሚኾን ዐረግማ ተክል (ኹለተኛ ስሙ "ያቡን ወጥ" ነው) ።
ትም አለ፡ ቍልቍል ሮጠ ተ...መመ ።
ትም አለ፡ ቍልቍል ኼደ ወረደ ሮጠ ።
ትም አደረገ፡ በፍጥነት ፈጸመ ጨረሰ (እኸልን ገንዘብን) ።
ትምህርተ ኅቡኣት፡ የመጻፍ ስም (እንደ ክታብ በደረት የምትያዝ በቅዳሴ ጊዜ የምትነበብ ከመጽሐፈ ኪዳን የተከፈለች ታናሽ መጻፍ) ። "የመንፈሳውያት ምስጢሮች ትምህርት" ማለት ነው።
ትምርት ቤት፡ ትምርት የሚነገርበት የትምርት ቤት።
ትምቡሼ፡ ልዝብ፡ ትንቡሼ ።
ትምተማ፡ ልተማ ድምደማ ።
ትምትም፡ በልጥፍና በልስን መካከል ያለ የምርግ ሥራ ("ጕርዖን" እይ) ።
ትምትም አደረገ፡ ድም ድም አደ...ረገ ።
ትምትም፡ የተተመተመ ልትም ።
ትምክ አለ፡ ሥርጕድ አለ ወደ ውስጥ ገባ ትክክልትን ወጣ ።
ትምክ፡ የተመከ ልል ስጕድ ሥርጕድ ።
ትምክምክ፡ የተተመከመከ።
ትምክምክ፡ የተትመከመከ ድብስብስ ("ትምክምክ አለ" - ተትመከመከ) ።
ትምክተኛ (ምኩሕ)፡ የተመካ፡ የሚመካ፡ ኵሩ።
ትምክት፡ (ትምክሕት); መመካት።
ትሰሚ/ትሰሜ፡ ትሰሚያለሽ (የሴት ስም - ትደመት/ትደመጫለሽ ማለት ነው) ።
ትሣሥ፡ ፬ኛ ወር ከመስከረም (የጥ ያቄ የመመራመር ወር ማለት ነው - ማቴ. ፪፥ ፪) ። በግእዝ ታኅሣሥ ይባላል ።
ትሣሥ፡ የወር ስም (ታኅ...ሣሥ) ።
ትስብእት (ሰብእ)፡ ሰውነት ሰው መኾን ።
ትስብእት፡ ጌታችን ያለዘር የተፀነሰበት ሥጋ የለበሰበት መጋቢት ፳፱ ቀን ።
ትረባ፡ መተረብ ።
ትረካ፡ መተረክ ።
ትሩፋት፡ የሴቶች ሳድስ ቅጽል ።
ትሩፋት፡ የበዙ የተረፉ የነፍስ ሥራዎች (በቂ) ። ባላገር ግን "ትሩፋቶች" ይላል ። "ተረፍ ትራፍ ትሩፍ ትሩፋን ትሩፋት" የግእዝ ናቸው ።
ትሩፋን፡ ቅሬቶች ።
ትሩፋን፡ ዕዝራ ሱቱኤል ያያቸው መ...ፍጹማን በፍጻሜ ዘመን የሚገለጹ ።
ትሩፋን፡ የተረፉ/የቀሩ (ወደ ኢየሩሳሌም ያልተመለሱ ከእስራኤል ተለይተው በፋርስ የኖሩ) ።
ትሩፍ፡ ሃይማኖቱ የጸና ምግባሩ የቀና ትርፍ የጽድቅ ሥራ የሠራ ሰው (በግእዝ "ትሩፍ" ይባላል - ፍጹም ማለት ነው) ።
ትሩፍ፡ በፋርስ በባቢሎን ከሰባ ዘመን መከራና ሞት የቀረ የእስራኤል ወገን ።
ትሩፍ፡ የይሁዳ ነገድና የብንያም ትሬታ ካሥሩ ነገድ ጋራ ያልተማረከ (ነሐ. ፩፡ ፪, ፫) ።
ትራስ፡ በቃል መጨረሻ የሚገባ ፊደል ሽ ኒ። ውጦሽ ጢሎሽ ግመኒ ጥንበኒ።
ትራስ፡ የራስ ድጋፍ (ራሰ ራስ) ።
ትራስ/ትርኣስ፡ የራስ ድጋፍ መከዳ ብርኳኔ።
ትራፊ (ትራፍ)፡ የተረፈ/የቀረ (ኢሳ. ፲፩፡ ፲፩) ።
ትር ማን፡ ትርጁማን ተርጓሚ አስ...ተርጓሚ ።
ትርምስ፡ ሽብር ፍጅት ሁከት ብጥ...ብጥ ።
ትርምስ/ብጥብጥ፡ (ተረመሰ) ።
ትርምስምስ፡ ብጥብጥ ምስቅልቅል ።
ትርምስምስ አለ፡ ምስቅልቅል አለ ።
ትርር፡ የተተረረ ሥንጥቅ ።
ትርሽማ፡ የወታደር ድንኳን ዐሯ...ትንሿ ። ጕይዲ ግን ባለመደረቢያ የንጉሥ ድንኳን ጌጠኛ ይለዋል ።
ትርተራ፡ ልየታ ፍንክታ ጭፍለቃ ።
ትርታሮ፡ ጭፍልቅ ።
ትርትር አለ፡ ሥንጥቅ እለ ። ትርታሪ፡ ከስፌት የተፈታ ክር ።
ትርትር አለ፡ ርግብ ርግብ አለ...ተንቀጠቀጠ ።
ትርትር፡ የተተረተረ (የተፈታ ሥንጥቅ ፍንክት ጭፍልቅ) ።
ትርንጎ (ዎች)፡ የተክል...ስም (ጣዕም ከመዐዛ ያለው ተክል - ዛፉም ፍሬውም "ትርንጎ" ይባላል) ።
ትርከካ፡ ሥንጠቃ ፍንከታ ።
ትርኪ ምርኪ፡ ቅባጥርሴ ቅራቅንቦ የማይረባ ውጥንቅጥ ምናምን ነገር ("ትርኪ" ከተረከ "ምርኪ" ከማረከ ይወጣል።)
ትርክም፡ የተሰበሰበ ጥርቅም ።
ትርክምክም፡ ብዙ ትርክም ።
ትርክክ አለ፡ ሥንጥቅ አለ (ተተረ...ከከ) ።
ትርክክ፡ የተተረከከ (ጥርቅቅ ሥንጥቅ...ፍንክት) ።
ትርክዛ (ኀዳፍ)፡ መቅዘፊያ የውሃ...መግፊያ የባሕር ላይዳ ።
ትርኰሳ፡ ሰበራ ስተራ የጠለስ ።
ትርኳሽ ሾ፡ የተተረኰሰ ኵስታሪ (ዘካ. ፫፡ ፪) ።
ትርው አለ፡ ዝር አለ ።
ትርው፡ ዝር መድረስ ።
ትርውአትበል፡ አትድረስ ።
ትርጁማን (ዐረ. ተርጁማን)፡ አስተ...ርጓሚ ።
ትርጉም ፡ ረጃ (ዐረ፡ ረጀወ, ተመለስ) - ሁለተኛ ተመልሶ የፈላ ቡና (ሁለተኛ ጊዜ ተመልሶ የፈላ ቡና).
ትርጕም (ትርጉም)፡ የተተረጐመ የ...ተፈታ የተገለበጠ የተıለ ግልጥ ንግግር ።
ትርግ ትርግ አለ፡ ሥርግ ሥርግ አለ (የልብ የርግብ ግቢት) ።
ትርጐማ፡ የመተርጐም ሥራ ግልበጣ ምለሳ ።
ትርጓሜ፡ ዝኒ ከማሁ ፍች ስለ ምን ።
ትርፈሳ፡ ዘዝና ዐፈሣ ።
ትርፌ፡ የወንድና የሴት ስም ("የኔ ትርፍ" ማለት ነው) ።
ትርፍ (አንትርፎ/አንተርፎ)፡ ትርፍ።
ትርፍ (ፎች)፡ ዝኒ ከማሁ ከስፍር ከቍጥር ውጭ የኾነ እኸል ገንዘብ ፋይዳ ጥቅም (ሰው በድካሙ የሚያገኘው - ዘዳ.
፳፰፡ ፲፫፡ መክ. ፩፡ ፫) ። ("ተረት" - ካላረፉ መከራ ነው ትርፉ) ።
ትርፍ፡ የጋራ ትርፍ (ያበዳሪና የተበዳሪ ነው ከኹለት ይከፈላል) ።
ትርፍራፊ፡ ፍድፋጅ ። ትርፍርፍ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ትርፍርፍ አለ፡ ተትረፈረፈ ። አተራረፍ፡ አዳዳን መትረፍ ።
ትርፍነት/ትርፍቻ፡ ትርፍ መኾን (ሮሜ. ፫፡ ፪) ።
ትቢተኛ (ኞች)፡ ኵራተኛ (ጨርቁን አፍንጫው ላይ አድርጎ ሰውን የሚንቅ - ባለትቢት ትቢታም የማይታዘዝ - ዘዳ. ፳፩፥፲፰፡ ፪ጢሞ. ፫፥፬) ልበት ።
ትቢተኛነት፡ ኵራተኛነት።
ትቢት (ትዕቢት)፡ ኵራት።
ትቢያ፡ ወቧራ ብናኝ ደቃቅ ዐፈር አሸዋ (ኢዮ. ፴፰፡ ፴፰፡ መዝ. ፩፡ ፬) ። በግእዝ "ተቤሳ ጸበል" ይባላል ።
ትባት (ትብዕ)፡ ስለት ሹለት ጥን...ካሬ ፍጥነት ።
ትቤ፡ ያዢ ስም ።
ትቤት፡ በሺን አገር በሂማልያ አጠ...ገብ ያለ ረዥም ተራራ (የመነኮሳት መኖሪያ ደብር - ቅዱስን የመሰለ) ። "ጌታችንም በ፲፪ ዓመቱ በዚህ ስፍራ እንዳስተማረ የሚያስረዳ በሺን ቋንቋ የተጻፈ የብራና ጽፈት በገዳሙ...ይገኛል" ይባላል ።
ትብ (ትቡዕ)፡ የተባ ስል ፈጣን ጠንካራ (ቢላዋ መጥረቢያ ማንኛውም) ። መሪያ አንደበት ።
ትብተባ፡ ጥምማ እሰራ ።
ትብትባት/ትብትቦሽ፡ ጥምጥማት እስራት ።
ትብትብ፡ ዝዝዝብ ነገር (፪ኛው "ት" ይጠብቃል) ።
ትብትብ፡ የተተበተበ ጥምጥም ውስብስብ እስርስር እርት እክት (ግብ. ሐዋ. ፰፡ ፳፫) ።
ትብትብ፡ ያረቄ አሸንዳ ።
ትተጋ፡ የእሳት በጣ ውግ ።
ትት (ቶታን)፡ የተታታ ጥፍር ውስ...ብስብ ጥልፍልፍ ቍልፍልፍ (የስንደዶ የክር ገመድ ጠፍር) ።
ትት፡ የወፍ ቤት ።
ትቻ፡ ዘጠነኛ የቀባርዋ ምት ።
ትች፡ የተተቸ (ከፈራጅ ሽማግሌ ከዳኛ አንደበት የሚወጣ የፍርድ የነገር ማስረጃ) ። "ሰው ፊት አይቶ ይፈርዳል እግዜር ግን ልብን ይመረምራል - ሰው አየ እግዜር እየ - እግዜር መንግሥትን ይጠብቅ ዐመፀኛን ያውድቅ ሐሰተኛን ያርቅ ፍት ርት ይጠንቅቅ ማማለጃ ተቀብለው ፍርድ አድልተው በልተው ጠጥተው ከብረው ብታያቸው አትቅናባቸው" እንደ ማለት ። የጠበቃ ትች "ውርድ" ይባላል ።
ትችት፡ ዝኒ ከማሁ መጨረሻው ት ምእላድ ነው ። "ትች" ቅጽልና ጥሬ "ትችት" ግን ጥሬ ብቻ ይኾናል ።
ትናጋ፡ ላንቃ (የአፍ ውስጥ ላይኛው ክፍል - ኢዮ.
፳፡ ፲፫፡ መዝ. ፻፴፯፡ ፯፡ ሰቈ. ፬፡ ፬፡ ሕዝ. ፫፡ ፳፮) ።
ትናግ (ስናግ/ስናቅ - ትግ. ትንሐግ)፡ ኵጕረሮ (ወደ ሰርን የትንፋሽ መ...ው፵ ኹለት ቀዳዳ - "ቀና ሰ ገና ቀ" መወራሳቸውን ልብ አድርግ) ።
ትን፡ ባፍንጫ መውጣት
ትን አለ፡ ብን አለ ወደ ስናቅ ወጣ ሰረነቀ ዐነዘዘ (ትንፋሹ መጠጡ) ።
ትንሣኤ፡
ትንሣኤ ሙታን፡ የሞቱ ሰዎች መንቃት ከመቃብር መውጣት።
ትንሣኤ ዘጉባኤ፡ የጉባኤ ሰዎች ኹሉ መነሣት (ጉባኤ የተባለ ይህ ዓለም ነው) ።
ትንሹ፡ ያ፡ ትንሽ።
ትንሹ፡ ጥፍር መቍረ፵ ብር እርሳስ መቅ ረ መሰነ...
ትንሽ ።
ትንሽ፡ (ኅዳጥ)፡ የቍጥር፡ ንኡስ፡ ብዙ' ያይዶለ፡ ጥቂት፡ እከሌ፡ ትንሽ፡ ገንዘብ፡ ሰጠኝ።
ትንሽ፣(ንኡስ)፡ ያነሰ ፣ሕፃን፡ ብላቴና ።ትንሽ፡ ልጅ፡ እንዲሉ ።ወንድና፡ ሴትን፡ ለመለየት፡
ትንሽም ትልቁም ዛፍ ። "ተክል" ዘርፍ ይዞ "ተክለ ጊዮርጊስ ተክለ ሚካኤል ተክለ ማርያም ተክለ ሥላሴ ተክለ ጻድቅ" እያለ የክርስትና ስም ይኾናል ።
ትንሽነት፡ ሕፃንነት፡ ለጋነት፡ ጥቂትነት።
ትንሿ ትንሽቱ፡ ያች፡ ትንሽ፡ ያሠኛል ።
ትንቡሼ፡ የትንቡሽ ወገን፡ ድንቡጨ ድንቡሎ ። ትንቡሼ ገላ፡ ነዪ እንዳለ ዘፋኝ ።
ትንቡሽ፡ ወፍራም ድልድል ለስላሳ ።
ትንቡሽቡሽ፡ ቅምጥል እንቅብር፡ የደላው የተመቸው ሰውነት ።
ትንቢተኛ (ትንቢታዊ)፡ ትንቢት ተናጋሪ ባለትንቢት ንግረኛ ("አገኛለኹ እሾማለኹ" ባይ) ።
ትንቢተኞች፡ ባለንግሮች ንግርተኞች።
ትንቢት፡ ሳይኾን ሳይደረግ ሳይመጣ ይኾናል ይደረጋል ይመጣል ተብሎ በምሳሌና እለምሳሌ በነቢይ አፍ የተነገረ ንግር ("ደረቀ" ብለኸ ደረቅን እይ) ።
ትንቢት ተናገረ፡ ወደ ፊት እንዲህ ይኾናል ኣለ።
ትንቢት፡ ንግርት፡ (ነበየ)፡ ተነበየ ።
ትንቢት አንቀጽ፡ ያኹንና የቅርብ የቈየ የዘገየ ኀላፊ ግስ ("ይገድል/ይገድላል/ይገድል ነበር" እየተባለ የሚነገር) ።
ትንቢት፡ ከኢሳይያስ እስከ ሚልክያስ ያለ የነቢያት መጻፍ።
ትንቢት፡ የረኛ ዘፈን።
ትንባኾ፡ የተክል ስም (ሰው ኹሉ ልጥልጡን ባፉ የሚገርመው ሥንተኑን ባፍንጫው የሚምናው ጪሱን የሚጠጣው ቅጠል - ባረብኛ "ትንባክ" ይባላል) ።
ትንባዃም፡ ትንባኾ ጠጪ (ባለትንባኾ ሱረም - አምልኮ ባዕድ ከሌለበት ትንባኾ መጠጣት አያስኰንንም) ።
ትንቧለል፡ የሴት ስም (ቦለለ) ።
ትንቧለል፡ የሴት ስም፡ እንዳሳቧ በሰፊው ትኑር ማለት ነው ።
ትንተና፡ ልየታ ከፈላ ምደባ ።
ትንታ/ብንታ፡ ንዛዥ ።
ትንታግ (ጎች)፡ ክፋይ ቍጡ ኀይለኛ ተናጋሪ ሰው (ምሳ. ፳፮፡ ፲፰) ።
ትንታግ፡ ክፋይ፡ ተገተገ ።
ትንትናት፡ የመተንተን ኹኔታ ።
ትንትን፡ የተተነተነ የተከፈለ ክፍል...ፍል ።
ትንትግ፡ ትንትግ አለ (ቶሎ ሎቶ ለጭ) ።
ትንንሽ፡ (ሾች)፡ ውስጠ፡ ብዙ፡ ታናናሽ፡ ጥቃቅን። የኛማ፡ ልጆች፡ ትንንሾቹ፡ ይናደፋሉ፡ እንደ፡ ንቦቹ ።ታናሽና፡ ትንሽ፡ ታናናሽና፡ ትንንሽ፡ አንዳንድ፡ ወገን፡ ናቸው ።
ትንንቅ/ትንቅንቅ፡ ግብግብ ትግል " ትንቅንቅ መነቃነቅንም ያሳያል ።
ትንንን አለ፡ እንደ ትንኝ ሮጠ ሕ...ፃኑ ።
ትንኝ (ኞች - ትንንያ)፡ የተንቀሳ...ቃሽ ስም (ሲኼድ በክንፍ የሚተን ቍጭ የሚያኸልና ከዚያም የሚበልጥ - ማቴ.
፳፫፡
ትንኵስ፡ የተተነኰሰ (የተለኰፈልኵፍ - "ትንኵስ አደረገ" - ተነኰሰ) ።
ትንኰላ፡ የተንኰል ሥራ ክፋት ።
ትንኰሳ፡ ልኰፋ ንክሻ ።
ትንኳሽ (ሾች)፡ የቈላ ቍጭ በ...ነከሰ ጊዜ እንደ እሳት የሚያንበግብ ።
ትንግርተኛ (ኞች)፡ ታሪከኛ/ድንቅ አድራጊ።
ትንግርት፡ ጕድ/ድንቅ ታሪክ ("በግእዝ ንክርት ይባላል") ።
ትንፋሽ፡ ከሰው ከእንስሳ ከወፍ ካውሬ አፍ የሚወጣ ሕይወታዊ ነፋስ (ላበ ትም ትንፋሽ ይባላል) ።
ትንፋገን፡ ወረዘት (የርጥበት ሽታ) ።
ትንፋገን፡ ወረዘት ╔፡ ነፈገ ።
ትንፋጋም፡ ባለትንፋግ (ግማታም) ።
ትንፋግ፡ መጥፎ ሽታ (የፍግ የሽንት ያይነ ምድር) ።
ትንፋግ፡ መጥፎ ሽታ፡ ነፈገ ።
ትንፍስ ትንፍስ አለ፡ ቶሎ ቶሎ ተነፈሰ።
ትንፍስ፡ የተነፈሰ/የተተነፈሰ።
ትንፍሽ፡ መተንፈስ (ካፍ ነገርን ማው ጣት) ።
ትንፍሽ አለ፡ ጥቂት ተናገረ።
ትኝት፡ ረብ ጋደም ።
ትኝት አለ፡ ውድቅ አለ (ተኝቶ ተጋድሞ ተዘርሮ) ። ("ተረት - የሰው በልቶ አያድሩም ተኝቶ") ።
ትእዛዝ፡ አንቀጽ፡ ከዘንድ፡ ቀጥሎ፡ ለቅርብ፡ ወንድ፡ የሚነገር፡ ግስ። ዕወቅ፡ ተጠንቀቅ ።
ትከሻ (ተኬሳ)፡ ንቃ ዕድል ። "ትከሻ ወረደው" ተቀ...ታመው ።
ትከሻም፡ ዕድላም ክቡር ክባድ ሰው ።
ትከዛ፡ ዐዘና መሬት ቍርቈራ ።
ትኩ (ትግ. ትኩእ)፡ የሰው ስም ("ምትክ" ማለት ነው) ።
ትኩሳታም፡ ወባም ንዳዳም ትኩሳተ...ብዙ ።
ትኩሳት፡ ወበቅ ሙቀት ሐሩር ንዳድ (የወባ - የምች በሽታ - ፍ፰፡ ፳፪፡ መዝ. ፪፡ ፭፡ ኤር. ፲፯፡ ፰) ።
ትኵስ ቅቤ፡ ዐዲስ ለስታ ለጋ ቅቤ ።
ትኵስ/ትኩስ፡ የተተኰሰ (ሙቅ ላበት እንፋሎት ያልተለየው - ፩ሳሙ. ፳፩፡ ፮) ። "ትኵስ እንጀራ ትኵስ በድቍስ ትኵስ ዳቦ ትኵስ ዶም" እንዲሉ ።
ትኵር፡ የተተኰረ (ባለማቋረጥ የታየ - "ትኵር ብሎ አየ" - ተኰረ) ።
ትካር፡ ዝኒ ከማሁ (አሳዛኝ ነገር) ።
ትካት፡ ፊት ቀድሞ ዱሮ ጥንት ("ሰብአ ትካት" እንዲሉ) ።
ትካዜ፡ ዐዘን ዐሳብ እህህታ ቍዘማ የለቅሶ ዜማ (ሕዝ. ፬፡ ፲፮፡ ፩ጴጥ. ፭፡ ፯) ። አተካከዝ፡ አስተዛዘን መተከዝ ።
ትክ (ሰኪው)፡ መተኰር (ዐይንን አለ...መንቀል) ።
ትክ ብሎ አየ (ሰከወ)፡ ተኰረ ባለማቋረጥ አስተዋለ ።
ትክለኛ (ኞች)፡ ባለመሬት ቀላድ ያ...ለው ።
ትክል (ትኩል)፡ የተተከለ የቆመ የ...ጸና ("ትክል ድንጋይ" እንዲሉ) ።
ትክል አለ፡ መሬት ቆመ (ባፍጢሙ ወደቀ ተደፋ) ።
ትክትክ (ስም)፡ የሕፃን ጕንፋን ሳል ("ትክትክ አለ" - ሳለ ኡሁ ኡሁ አለ) ።
ትክትክ (ቅጽል)፡ የተተከተክ (ጥቅጥቅ...ውግ) ።
ትክቶ፡ ግዳጅ (በየወሩ ከሴቶች የሚፈስ ደም) ። "ትካትና ትክቶ" የግእዝ ቃል ነው ።
ትክክለኛ፡ የተካከለ ፥ የተመሳሰለ፡ አንድ ዐይነት ልከኛ፡ እውነተኛ ፥ ሐቀኛ ።
ትክክለኛነት፡ ተመሳሳይነት ፥ ርግጠኛነት ፥ እውነተኛነት ።
ትክክለኞች፡ የተካከሉ ፥ ድልድሎች ፥ ሰዎች፡ እውነተኞች ፥ ሐቀኞች ።
ትክክል፡ ልክ ፥ እኩያ ፥ አምሳል ፥ ወደር ፥ አቻ ፥ ድልድል ።
ትክክል አደረገ፡ አላጐደለም፡ አላበለጠም ።
ትክክል ኾነ፡ አልተበላለጠም፡ አልተናነሰም ።
ትክክልነት፡ እኩያነት ።
ትክክሎች፡ እኩዮች ፥ አቻዎች ።
ትክክሏ፡ የሴት ስም ።
ትክዝ (ትኩዝ)፡ የተከዘ ያዘነ ።
ትክዝ አለ፡ ዕዝን አለ ዐዘን ገባው ።
ትኰሳ፡ ልብለባ ዳመጣ ።
ትዃናም፡ ትዃን ያለበት የበዛበት ቈጥ...ምንጣፍ ።
ትዋብ፡ ታምር/ትመር/ትኵራ ።
ትውልድ፡ የሰው ወገን/ነገድ/ጐሣ (መክ. ፩፡ ፬) ።
ትውልድ፡ የተወለዱበት የዘር አገር ።
ትውስ (ተሐውሶ)፡ መታወስ ።
ትውስ አለው፡ ታሰበው ።
ትውስታ፡ ትዝታ/ዕስብታ/ዐሳብ ።
ትውስት፡ ሊመልሱ መውሰድ ።
ትዛዝ፡ (ትእዛዝ)፡ የጌታ፡ የፈጣሪ፡ ቃል፡ አታድርግ፡ የሚል፡ ከሥራ፡ አስቀድሞ፡ የሚሰጥ፡ የሚጻፍ፡ የሚነገር፡ አትስረቅ፡ አታመንዝር፡ በሐሰት፡ አትመስክር
"
ትዛዝ፡ በቁሙ፡ አዘዘ ።
ትዝ፡ መታሰብ ።
ትዝ አለው፡ ታሰበው ታወሰው ።
ትዝቢ (ዎች)፡ ሌባ ቀጣፊ ሰው የሚታዘበው ።
ትዝብተኛ (ኞች)፡ ባለትዝብት (ጠር ጣሪ ናቂ ") ።
ትዝብት (ትሕዝብት)፡ ጥርጥር/የፍ ራት ዐሳብ (ንቀት ነቀፋ ") ።
ትዝታ፡ ዕስብታ ትውስታ ።
ትያትር (ትያጥሮን)፡ የተምሳሊት...ዋታ ።
ትይዩ፡ የተያየ ፥ የተነጻጸረ፡ አንጻር ፥ አፍዛዣ ፥ አቅጣጫ ፥ ስፍራ ፥ ፊት ለፊት፡ (፩ነገ ፰፡ ፵፬ ፥ ፵፰ ። ዳን ፯፡ ፬) ።
ትደነቂያለሽ፡ የሴት ስም ።
ትዳር፡ ኑሮ/ንብረት (ጐዦና ጕልቻ ሀብት ") ።
ትዳር፡ ዐዳር፡ ዐደረ ።
ትድግ፡ ለውጥ (የመከራ ምትክ) ።
ትድግና፡ ለውጥነት/ምትክነት (ማዳን) ።
ትድግና፡ ማዳን፡ ዐደገ ።
ትጉ (ጎች/ዎች) (ትጉህ)፡ የተጋ/የሠጋ (ሥግ ንቅ ሀሳቢ - ምሳ. ፲፫፡ ፬) ።
ትጕልጕል አለ፡ ተትጐለጐለ/ተጫነቀ/ተጣበበ ።
ትጕልጕል፡ የተትጐለጐለ/የተጣበበ (ማሕ. ፫፡ ፮ ትርጓሜ) ።
ትጕልጕል፡ የተጣበበ (ጐለጐለ) ።
ትጕልጕልታ፡ የጥበት አወጣጥ ።
ትጉነት/ትጉህነት፡ ትጉ መኾን ።
ትጋት (ትግሀት)፡ ንቃት እንቅልፍ ማጣት (ኢሳ. ፳፩፡ ፯፡ ሉቃ. ፪፡ ፰) ። ሲበዛ "ትጋቶች" ይላል (መዝ. ፷፫፡ ፮) ።
ትግ ትግ አለ፡ ተንተገተገ ።
ትግ/ብልጭ፡ ተገተገ ።
ትግል/ትግያ/ትግልት (ትዕግ ልት)፡ ግብግብ/ትንንቅ ።
ትግሥተኛ (ኞች)፡ ታጋሽ ልበ ሰፊ ነገር ዐላፊ ሰው ።
ትግሥተኛነት፡ ትግሥተኛ መኾን።
ትግሥት (ትዕግሥት)፡ የሥቃይ የመከራ ችሎታ ዝምታ ርጋታ ጸጥታ ።
ትግሪተኛ፡ ዝኒ ከማሁ (ቍጡ ወፈ...ፍተኛ) ።
ትግሪታም (ቲግራዊ)፡ ቍጣም ወፈ...ፍታም ።
ትግሪት፡ ቍጣ ወፈፍታ ።
ትግሪት፡ ዛር ክፉ መንፈስ ወዶ...ከቢር ።
ትግሪት፡ የበረሓ ሠሥ ዲግዲግ እንሸ ።
ትግሪኛ (ትግራይ)፡ የቋንቋ ስም
ትግሪዳ (ታ)፡ መንገድገድ መፍገምገም ፍግምግምታ ።
ትግሬ (ቲግራ)፡ በጤግሮስ ወንዝ ዳር የሚኖር ታላቅ ነብር (ቍጡ ኀይለኛ) ። ባላገርም በበረሓ ትግራ የምትባል አውሬ ኣለች እያለ ያወራል።
ትግሬ፡ ከሐማሴን ቀጥሎ ያለ ያገርና የነገድ ስም (ቈላ ምድር ሐባብ በመረብ ግራና ቀኝ ከምጥዋ እስከ ተከዚ የሚ፹ኝ ወረዳ ኹሉ) ። የነገድ ስም ሲኾን ነጋዴ ማለት ነው ይላሉ ። ባላገሮቹም ታችኛውን ትግረ ላይኛውን ትግራይ ይሉታል ። በግእዝ ግን ደጋውም ቈላውም ባንድነት ትግሬ ይባላል ። "ትግሬ የትግራና የትግራይ ሰው" (ዐማ...ርኛ)
ትግሬ፡ የቋንቋ ስም (ግእዝን መደብ ኣድርጎ ከወረብና ከዕብራይስጥ ከሱርስትየሚስጥም - የሐባብ ልሳን) ።
ትግሮች፡ የትግራ አገር ሰዎች (የትግሬ ተወላጆች ትግሪኛ የሚናገሩ ነገዶች ደገኞችና ቈለኞች) ።
ትግትግ፡ የተተገገ/የተገረፈ (ግርፍ) ።
ትግን፡ የተተነ/የተጀጐለ ።
ትጥቅ (ዕጠቅ)፡ የወገብ ጌጥ (የሆድ' ድጋፍ - ድግ እስራት ጥምጥማት ") ።
ትፋሕ፡ ፍሬው ክብ እንክብል የኾነ ጣፋጭ ተክል (ምሳ. ፳፭፡ ፲፩፡ ማሕ. ፪፡ ፳) ። በግእዝ "ኮል" ይባላል ።
ትፋታም፡ ባለትፋት (ቅርሻታም) ።
ትፍ (ትፉእ)፡ የተተፋ ።
ትፍተፋ፡ የመብጣት የመቈራት ሥራ ።
ትፍታ፡ አክታ ምራቅ ።
ትፍትፋት፡ ብጥታት ፍቅታት ቍር...ታት ።
ትፍትፍ፡ በኩታና በቀሚስ ዳር የተጣለ ጥቍርና ብ፵ ጥለት ።
ትፍትፍ፡ የተተፈተፈ (ብጥ ፍቅ የሰው ፊት ብርንዶ) ።
ቶ፡ መጨረሻው ራብዕ በኾነና ባልኾነ የ፪ና የ፫ ፊደል ግስ ለሩቅ ወንድ የቦዝ ዝርዝር ("ገባ ገብቶ ወጣ ወጥቶ በላ በልቶ ጠጣ ጠጥቶ ሸኘ ሸኝቶ ስጠ ስጥቶ ዘነጋ ዘንግቶ ዘረጋ ዘርግቶ") ።
ቶሎ (ተለወ)፡ ንኡስ አገባብ (ፈጥኖ...ቸኵሎ - "ቶሎ መጣ ቶሎ ኼደ") ። "በደለ" ብለኸ "ተበደለን" እይ ።
ቶሎ ቶሎ፡ ፈጥኖ ፈጥኖ ወዲያው...ወዲያው ።
ቶመቶመ)፡ አቶመቶመ፡ እጕረመ...ረመ አጕተመተመ ።
ቶማስ፡ የሰው ስም (ካሥራ ኹለቱ ሐዋርያት አንዱ) ።
ቶሜ፡ ጐረጐማ ።
ቶሰቶሰ፡ በድብቅ ሳያሰማ ፈሳ ("ቶሰከን" እይ) ።
ቶሰቶስ/ቶስቷሳ፡ ፈሳም ፈሪ ነገር የማይችል ።
ቶሰከ፡ ሳይሰማ ተፈሳ ።
ቶረበ፡ አራርቆ ወጋ (ተርታ ስፌት ሰፋ ወሰወሰ ሸደሸደ ሸለለ ሸክሸክ) ።
ቶራ (ሶር)፡ የበረሓ እንስሳ የዱር...ቶራ...ላም ያጋዘን ወገን ï ተባቱም እንስቱም ቶራ ይባላል ።
ቶራ (ግእዝ)፡ ኹለቱ ቀንዶቿ ባለ...ብዙ ባላ ባልቾ የኾኑ የበረዶ እንስሳ ወተታም የወሊያ ወገን (ዘዳ. ፲፬፡ ፭) ።
ቶራ መስክ፡ ቀድሞ ዘመን ቶራ ይሰማራበት የነበረ...መስክ (ባ፲፱፻፱ ዓ.ም.) ።
ቶራ ፈረስ (ሶር. ወፈረስ)፡ እ...ንደ ቶራ ኹለት ቀንድ እንደ ፈረስ ጋማና ጭራ ያለው የዱር እንስሳ (ፈረንጆች "ግኑ" ይሉታል) ። ("የጥቍሪት ጊዜ አዝማሪ" - እመቤቴ የቀረዎ አንድ ነገር ቶራ ፈረስ መስረር) ።
ቶራቢ፡ የቶረበ/የሚቶርብ (ሸድሻጅ...ሸክላኪ) ።
ቶሮች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ...ብዙዎች ።
ቶፋ (ፎች)፡ ሸክላ ባሬታ (ሴቶች ትና ማታ ግብር ውሃ ይዘው የሚወጡ...በት - አንቀጹ "ወተፈ" ነው - "ቻለ" ብለኸ "አይቻልን" አስተውል) ።
ቶፋ፡ ወኪል ምትክ ተጠሪ ገባሪ ።
ቷ አለ፡ ቦግ ቧ አለ ቶሎ በራ ።
ቷ አለ፡ ተበጠሰ (ቷቷ)
ቷ አለ፡ ዉ አለ ተበጠሰ ። ቷ አለ፡ ፈጥኖ ወጣ ፈሰሰ (የሴት...ደም) ።
ቷ፡ የሩቅ ሴት ዝርዝር ("ላሚቷ በገቷ") ።
ቷቷ) አንቷቷ፡ በጣጠሰ ("ታታን" ተመልከት) ።
No comments:
Post a Comment