Friday, June 6, 2025

                                 
ከ፡ () ደቂቅ፡ አገባብ። በስምና፡ በግብር፡ በነገርም፡ ኹሉ፡ በቦታም፡ መነሻ፡ ኹኖ፡ እየገባ፡ በቁም፡ ቀሪ፡ ይኾናል። (ማስረጃ) ከሰማይ ወረደ ።ከምድር ወጣ ።ነገር ከሥሩ፡ ውሃ ከጥሩ ።ከክፉ ተወልጄ ስፈጭ ዐደርኩ ።ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ ።ከቃጫ ወዲያ ገመድ፡ ከናት ወዲያ ዘመድ ("የለም")
ከ፡ ፲፩ኛ፡ ፊደል፡ በግእዝ፡ እልፍ፡ ቤት፡ በአበገደ፡ ይኸውም፡ በተራ፡ ቍጥር፡ ነው። በፊደልነት፡ ስሙ፡ ካፍ፡ በአኃዝነት፡ ከ፳ ("ካያ/ኻያ") ይባላል
ከ፡ በ፡ ይኾናል። ከታዘዝኸበት፡ አውለኻቸው፡ ጠላት በወሰዳቸው ።በቁም ቀሪና ሲኾን፡ ከሞት የተረፉ ከጥላ ያረፉ ።ጋራን ይዞ ሲፈታ፡ እንቅልፍ ታበዢ፡ ከነብር ትፋ ዘዢ። ወደ ሲኾን፡ የተጠማ፡ ከፈሳሽ፡ የተበደለ፡ ከነጋሽ። ይልቅን ይዞ ሲፈታ፡ ከመጠምጠም፡ መማር፡ ይቅደም። ከተማጋች፡ ታራቂ፡ ካጣቢ፡ አድራቂ። ከጄ፡ በጕንጨ። ካወደ፡ የሰበሰበ፡ (ይሻላል) እስከ ድረስን ይዞ እንዲፈታ፡ ከ፡ በግልጥ ጋራን ይዞ ይፈታል። ሔኖክ፡ ከኤልያስ ጋራ ይኖራል ።ሙሴ ከአሮን ጋራ ነበር ።ቂርቆስ ከናቱ ጋራ ሞተ ።በግእዝ መሠረቶቹ «እም/እስከ/ምስለ» ናቸው ።ያው መነሻና መድረሻ ነው
ከ፡ ዐቢይ፡ አገባብ። ከበላ፡ ብላ፡ ከሰው አትጣላ ።ይህ ጋራን ይዞ ሲነገር ነው ።ኋ ላን ይዞ ሲፈታ፡ ውሃ፡ ከፈሰሰ፡ አልታፈሠ። ዥብ፡ ካኰተኰተ፡ ሰው፡ ከተከተተ። ከመነኰሰች፡ ባሰች፡ ከቈረበች፡ አፈረሰች።
ከ፡ የኈ፡ ወራሽ፡ ከግእዝ፡ ወዳማርኛ። በኍበኈ፡ ቦከ/ቦከ።
ከ፣ የቀ፡ ወራሽ። ቀላድ፡ /ላድ።
ከ፡ የገ፡ ወራሽ፡ ወይም፡ ተለዋጭ "/ረደፈ፡ /ረተፈ። ቸን፡ እይ።
ከ፪ኛው ጠጋና ከጠገተ ሊወጣ ይችላል ("ጕራጌ ጥጃ ሲል ጠግ ይላልና ይኸውም የጀንና የገን ተወራራሽነት ያሳያል")
ከሃሊነት፡ ከሃሊ መኾን ("ቻይነት")
ከለ፡ አንድነት ጋራ ("፡ከነ")
ከለለ (ሐለለ) ዐረረ ("ጠቈረ ከሰል መሰለ ")
ከለለ (ትግ፡ ከነነ) በጣም ደረቀ ("ከዚህ የተነሣ ቀለለ ጮኸ ከሸለለን ተመ ልከት በስሯጽነት ገብቶበታል ")
ከለለ (ከልሎ ከለለ) ኣለበሰ ("ጋረደ መከተ ቀየደ ዐጠረ ቀጠረ ")
ከለለ፡ ሰወረ ("አሳወረ ማየት ከለከለ ከለለ ወሰነ የቤተ ክሲያንን ዙሪያ ገደመ ዳማ ከለለኝ እንዲሉ ")
ከለለ፡ ቈረጠ ("ሰየፈ የአሕዛብ ነገሥታት ሰማዕታትን በሰይፍ ከለሏቸው ከለለ (ትግ፡ ሐባ) ዞረ በዙሪያ ኼደ ") (መዝ. ፳፮፡ )
ከለለ፡ ከለሠ
ከለላ፡ ሸማ ("ግርዶ መከታ ዐጥር ቅጥር ከለላዬ የወንድና የሴት ስም መጋ ረጃዬ ማለት ነው ")
ከለል፡ ዝኒ ከማሁ
ከለል፡ የሚከል/የሚጮኸ
ከለልቴ ወልደ ሚካኤል፡ የንጦጦ ራጉኤል ደብተራ ("የተጕለት ተወላጅ ድምጠ መርዋ ")
ከለልቴ፡ የከለል ("ድምጣም ድምጠ ' መልካም አዝማሪ ደብተራ ጩኽቱ ከሌሎች የሚበልጥ በሩቅ የሚሰማ ")
ከለልቴ፡ ድምጣም፡ ከለለ
ከለሜዳ፡ ቀይ ግምጃ ("አይሁድ የስቅለት ለት ለጌታ ያለበሱት ")
ከለሰ (ዐረ፡ ኸለጸ) መለሰ ("መልሶ ሠራ ጥይትን ዳግመኛ ተማረ አጠና ከለሰ ጨመረ ቀላቀለ ")
ከለሠ፡ ዳግመኛ ተማረ፡ ከለሰ
ከለሰ፡ ጨረሰ ("ፈጸመ መላ ከለሰ ደቀለ ዲቃላ ወለደ ከለሰ (ትግ) ቅቤ አነጠረ ")
ከለበ (ከሊብ ከለበ) ውሻ ኾነ ("እንደ ውሻ ሮጠ ቸኰለ ቀለለ ከለፈንና ቀለ በን አስተውል ")
ከለበሰ (ለበሰ) ከነበለ፡ ቸለሰ አፈሰሰ፡ አብዝቶ፡ ጠጣ፡ ጨመረ ።ከለበሰ፡ የከበ ሰና፡ የለበሰ፡ ዘር፡ መኾኑን፡ አስተውል።
ከለባት፡ ውሾች ("የቤት አውሬዎች ከልቦች (ግእዝ)")
ከለብላባ ክልብልብ፡ የተክለበለበ፡ የሚክለበለብ፡ ከለፍላፋ፡ ክልፍልፍ። ክልብልቦች፡ ክልፍልፎች። መክለብለብ፡ መክለፍለፍ።
ከለቻ (ኦሮ) ጥፋተኛ የሙጥኝ የሚ ልበት ጣዖታዊ ብረት ("በቃልቻና በባላባት ቤት የሚቀመጥ እሱን ከጫጩ (ዛጐል) ጋራ ይዞ የኼደ ሰው ይቅርታና ዕርቅ ሰላም ይደረግለታል ")
ከለከለ (ከልከለ) ከላ ነሣ ("እገደ አቆመ አገረ ጠበቀ ሐይ አለ አጋፈረ አላስኬድ አላሳልፍ አላስገባ አላናግር አለ ") (ሐጌ. ፩፡ ፲፡ ማር. ፱፡ )
ከለወሰ) (ከዊስ ኮሰ) ንከላወሰ ("አላወሰ አንጠራወዘ ጥቂት ጥቂት አስኬደ ገገምተኛን ገመ ")
ከለው፡ የአቢስ ኹለተኛ ስም ("ትርጓ ሜው ከላኢ (ከልክሌ) ማለት ነው ከላዋ ከላባ ዕርፊተ ቢስ ቀለወን እይ ")
ከለውቱ፡ ዝኒ ከማሁ
ከለፈ (ከለበ) ሰረቀ ("ቀማ ነጠቀ እንደ ውሻ ነጥቆ በረረ ከተለፈንና ለከፈን ተመልከት ")
ከለፈ፡ ከለሰ
ከለፍላፋ/ክልፍልፍ (ፎች) የተክለፈለፈ/የሚክለፈለፍ ("ከለብላባ ክልብልብ ")
ከሉ፡ የሰው ስም ("የቀልድ ፈላስፋ ጥርስ የማያስከድን አጫዋች ሲያውቅ አበድ መሐርቡን እንደ ብራና ያጥፍና አንዳንዱን እየነጠለ ከሰማይ የወረደ መጣፍ ስሙ አቤት አቤት ለዶሮ ግት የላት ምነው የላት ያን ኹሉ ጫጩት አንተ አሳደግኸላት ለትል ጕበት የላት ምነው የላት ዐር ደኸ አየኻት ለጥንቸል ባት የላት ምነው የላት ያን ኹሉ ገመገም አንተ ሮጥኸላት ይል ነበር እብደትም በዠመረ ጊዜ በክፉ ቀን ጨርቆስ ኢየሱስ ቤተ ክሲያን ገብቶ እንጀራ ወይም እብደት ከ፪ቱ ፩ዱን ስጠኝ ብሎ ተሳለ ከዚህም በኋላ ለመቤቱ ወጥ እያወጣ ለራሱ ይበላ ዠመረ እመቤቱም እንቅልፍ ሲወስዳቸው ሽሩባቸውን ካልጋ ደንብ ጋራ አሰረው ዳግመኛም ራስ ዳርጌ ዘንድ ኼደና እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ አፍ እንደሌለው እእ አላቸው እሳቸውም ዐዝነው ዐልጋና ምንጣፍ ተሰጥቶት በማድ ቤት እንዲቀመጥና ለምሳው ነጭ መያዣ ብርሌ ጠላ ብርሌ ጠጅ ለራ ቱም እንደዚሁ እንዲሰጡት አዘዙለት ከብዙ ቀንም በኋላ የሚያውቃት ሴት እጎረቤት ነበረችና እሷ ዘንድ እየኼደ ሲጫወት ይውላል ብሎ አንድ ሰው ለራስ ዳርጌ ነገረበት ከዚህ የተነሣ ያዙና አምጡ ብለው ጊዜ ወለንጋ ቢያሳርፉበት እንደ ልማዱ እጁን ወደ ላይ ዘረጋና እእ ቢል የማይናገር ሰው ገርፌ ከፈጣሪዬ ልጣላ አሉና አሳባቂውን አጋድመው ገረፉት ይላል ከሉ የከሉ ትርጓሜ ባማርኛ ግጦሽ ወይም ለቀም ማለት ነው ")
ከሊፋ (ዐረ) (የመንግሥት/የሃይማኖት) ወኪል/እንደራሴ
ከሊፋዎች፡ ወኪሎች ("እንደራሴዎች")
ከላ (ከልአ) ነሣ ("ከለከለ (ተረት) በርጥብ ይከላ በደረቅ ያበላ ")
ከላ፡ አደረገ
ከላ፡ አራቀ ("አስወገደ (ተረት) ራብ ይከላል ባቄላ ከጥፍ ያደርሳል ነጠላ ")
ከላላ፡ የከለለ/የሚከል ("ጯኺ ዕንጨት ደወል ")
ከላሽ (ሾች) የከለሰ/የሚከልስ/የሚ መልስ ("እንደ ገና የሚሠራ የሚማር ጥይት ከሳሽ አንዲሉ ")
ከላሽነት፡ ከላሽ መኾን
ከላባ (ቦች) የከለበ/የሚከልብ (" ኵል ቀላል ጥላ ቢስ ")
ከላይ (ዮች) የከለለ/የሚከልል ("ጋራጅ ወሳኝ ቈራጭ ዲሉ ")
ከላድ፡ ቀላድ ("ቃጫ ንጣት ነጭነት ያለው ከና መወራረሳቸውን ተመልከት ")
ከላድማ፡ ቀላድማ ("ከላድ ያለው ባለ ከላድ ወገቡና ጐኑ ሆዱ ቀላድ ቃጫ የሚመስል መቀነትማ ፍየል የቀይ ከላድማ የጥቍር ከላድማ እንዲሉ ሠቅጥን አስተውል ")
ከላፋ/ከላፍ፡ የከለፈ/የሚከልፍ ሌባ
ከል (ዐረ፡ ኸል) ሖምጣጣ ' ሖም ጣጤ " ዐዞ ከል እንዲሉ
ከል (ከላኢ) የከላ/የሚከላ
ከል ለበሰ እንዲሉ
ከል፡ የሐዘን ልብስ ("የች ወገን ተድላ ደስታ እንዳያደርግ የሚከለክ እከሌ")
ከል፡ የቀለም ስም ("ከቀንጠፋና ከብረት ዐር የሚወጣ ጥቍር ቀለም ልጅ አባቱ ስለ ሞተ ልብሱን ከል ነከረ ")
ከልብ (ቦች) ውሻ ("የቤት አውሬ ከልብ የግእዝ ውሻ ያማርኛ ነው ደማብለኸ ደምን እይ ")
ከልብ፡ ቀላል ገለባ ("የተወቃ እኸል መንሽ በተባለ ጊዜ ቶሎ ይኼድና ከኵልኵል ውጭ ይገኛል ")
ከልካይ (ዮች) የከለከለ/የሚከለክል ("ሊጋባ አጋፋሪ መጨኔ ")
ከልካይ፡ ከልክሌ ("የሰው ስም ")
ከልካይነት፡ ከልካይ መኾን ("አጋፋሪነት በከልካይ የወንድና የሴት ስም ጌት ነትን እመቤትነትን ባለከልካይ መኾንን ያሳያል ")
ከልክል፡ ከልካይ ("ወይም ትእዛዝ አንቀጽ ለቅርብ ወንድ ዝንበ ከልክል እንዲሉ ")
ከልዋሳ (ሶች) የተንከላወሰ/የሚንከላ ወስ ("ጠርዋዛ ")
ከሎታ፡ ጥምጥም ("የራስ መሸፈኛ")
ከመ ቅጽበት፡ እንደ ዐይን ጥቅሻ ("ወይም ፍጥነት አለ ")
ከመ፡ ደቂቅ አገባብ
ከመ ጤፍ፡ እንደ ጤፍ ("የጤፍ ያኸል አከሌ እከሌን ከመ ጤፍ አይቈጥረ ውም ")
ከመሙ (ከሚም) ጫፍ ግፉን ቈረጠ
ከመረ (ከሚር ከመረ) ደረደረ ("ደረበ አነባበረ ዘመመ ጐቸ ቈለለ ")
ከመረ፡ ታላቅ ጥምጥም ጠመጠመ ("ደመረ ")
ከመቸ) ተከማቸ፡ ተሰበሰበ ("ታከበ ተጠናቀረ ተጠራቀመ ደለበ ") ( ነገ. ፲፡ ፪፡ ማቴ. ፳፮፡ )
ከመና ጋራ ይገጥማል "ወለል በይ ማኛ" እንዲል ጤፍ ዐጝጅ።
ከመከመ (ከመመ) ከፈከፈ ("ደመ ደሙ አስተካከለ ጠጕርን ")
ከመከመ፡ አሣቀ ("አንከተከተ")
ከመከመ፡ ከመረ
ከመዙ (ከመ ዝንቱ) እንዲሁ
ከሙን፡ የቅመም ስም ("የንስላል ዐይነት ቅመም ") (ኢሳ. ፳፰፡ ፳፯)
ከማሁ፡ እንደዚያው ("እንደ ርሱ ")
ከማመረ፡ መላልሶ ከመረ ("ደራረበ")
ከማሚ፡ የከመመ/የሚከምም ("ከርካሚ ")
ከማሪ (ሮች) የከመረ/የሚከምር (" ማሚ ቈላይ ")
ከማን አንሼ፡ ተግደርዳሪ ሰው
ከምሱር (ሮች) ከሽጕጥ/ከጠመንዣ/ ከመትረየስ/ከመድፍ/ከታንክ ቀለሕ ጋራ በስተሥር በኩል መካከለኛ ኹኖ ዐብሮ የተ በጀ ክብሪታዊ ባሕርይ ያለው ሥራ ("ታበወጋው ጊዜ እሳት ከሱ ይወጣና ባሩድን ያቃጥላል ባሩድም ዐረርን ያስነሣል ፈረን ጆች ካፕሱል ይሉታል ")
ከምሱር፡ በሠቅና/በቀበቶ ብስ ውስጥ ያለ ንሓስ ዘለበት የሚገባበት
ከምባታ፡ በጕራጌ አጠገብ ያለ እገር
ከምነዬው) ከምንጊዜው።
ከምከም፡ በጐንደር በኩል ያለ አገር
ከምካሚ፡ የከመከመ/የሚከመክም ("ጐፈሬ አሳማሪ ")
ከሞላ ጐደል) ከሙሉ ቅናሽ።
ከሰለ በከሰል አመለከተ ("ጫረ ነደፈ በገረ ሠረዘ አጠፋ ") (ገቢር)
ከሰለ፡ ከሰመ
ከሰሚ፡ የከሰመ ("የሚከስም ተካይ ቀብቃቢ ነው ከስሜ የሰው ስም ከስም ማለት ነው ካስማ (ሞች) የድንኳንን አውታር # የሚይዝ ቈላፋ ዕንጨት ወይም ብረት ") (ዘፀ. ፴፭፡ ፲፰፡ ዘኍ. ፴፮፡ ፴፪፡ ኢሳ. ፴፫፡ ፳፡ ፵፬፡ )
ከሠሠ ተማጠነከሰሰ
ከሰረ፡ ከሰሰ
ከሠረ ደኸየከሰረ
ከሠተ (ከሢት ከሠተ) ገለጠ (" ሳየ አበራ ")
ከሠተበት፡ ጕዱን/ነውሩን አወጣበት ("ገለለጠበት ") (ዮሐ. ፰፡ , , )
ከሠከሠ፡ ሰባበረ ("ከሰከሰ ኰሠኰሠ ወጋጋ ኰሰኰሰ ከሠለ፡ ጠቈረከሰለ ከሠመ መዳን ዠመረከሰመ ከሠሠ (ኀሠሠ ትግ ካሠሠ) ዐሠሠ አሰረረ በጥቂቱ አሰፋ ጋገረ እስቲበስል አቈየ ")
ከሠደ፡ ከሳ በዥማቱ ኼደ ("(ተገብሮ) ከሠደክሥዳ አወጣ (ገቢር) ከሠደ (ትግ) አቋረጠ መንገድን ከሣዳ የከሳ ከሲታ ")
ከሣቲ፡ ዝኒ ከማሁ
ከሣቴ ብርሃን፡ ቅኔየቅኔ ትምርት
ከሣቴ ብርሃን፡ ብርሃን ገላጭ ("ኢየሱስ ክርስቶስ ")
ከሣቴ ብርሃን፡ አባ ሰላማ ፍሬምናጦስ
ከሣች፡ የከሠተ/የሚከሥት ("ገላጭ ብሪ ")
ከስም ጋራ ሲጻፍ ቅጽል ይኾናል።(የታቦትዘፈን) ያባ ጠጋዛብ ልጅ የይቶት እዝጊያ፡ ትምሩኝ እንደኾን ልምጣ ወደ ኮራ።
ከስቶ፡ ተጐድቶ ("ቀጥኖ ") (ዳን. ፩፡ )
ከረረ (ከሪር ከረ ገረረ) ደረቀ ("ጠና ጠነከረ በረታ ባስ የነገር የወገብ ከረረ ተነፋ ዐበጠ ተከረበ የሆድ ከረረ ተፈተለ ተገመደ ተጠሞረ ደበነ ጥብቅ ኾነ የፈትል የገመድ የዥማት (የከረረ ' ጠጅ) የደረቀ የኖረ ከራሚ ከራሪ የሚከር ድር ሐር ከራራ የከረረ ደረቅ ድባኖ ዐጪር ድኑር ክራሪ ዝኒ ከማሁ ክራር (ሮች) የዘፈን መሣሪያ ስም በበገና " ዐይነት የተበጀ ባለ፯ አውታር T ክራር (ግጥም) እንዴት ነሽ ክራር ፮ቷ ዥማት ክፉ መካሪ እንደንጀራ እናት ")
ከረበ፡ ነፋ ("አሳበጠ ወጠረ ከረቦ ከበሮ አስመሰለ ሆድን ከረበ (ትግ) ደረቀ ቦና ኾነ ከረቦ ቅርጫት የቅርጫት ዐይነት (ግእዝ) ከረቦ ሆድ ሆዱ ቅርጫት ከበሮ ያከለ የመሰለ ሰው ከረቦ ከበሮ ባላገር ከበሮ በማለት ፈንታ ከረቦ ይላል መከረብ መንፋት ማሳበጥ አስከረበ አስነፋ አስወጠረ ማስከረብ ማሳበጥ ማስወጠር ተከረበ ተነፋ ዐበጠ ተወጠረ ክርብ የተከረበ ንፍ ውጥር አከራረብ አነፋፍ መከረብ ")
ከረበተ (ዐረ፡ ከርበጠ፡ ደባለቀ) ገለገለ ("ገለበጠ አጋደመ መከርበት መገልገል ማጋደም ተከረበተ ተገለገለ ተገለበጠ ተጋደመ ክርብት የተከረበተ ግልብጥ ጋድሚያ ጓል ሰው ")
ከረበጀ (ዐረ፡ ከርበጀ) ገረፈ (" ነቈጠ ጠበጠበ ኰርባጅ አኰርባጅ (ጆች) (ዐረ፡ ኩርባጅ) ትልቅ ዐለንጋ ጕማሬ መግረፊያ ") ( ዜና. ፲፡ ፲፩, ፲፬)
ከረባሽ፡ የሽቱ ስም ("የባሕር ሽቱ")
ከረተተ) አንከረተተ/አንከራተተ ("አዞረ አንከዋተተ አንከዋረረ አንቀ ዋለለ አንከርታች አንከራታች ያንከረተተ ያንከራተተ የሚያንከረትት የሚያንከራ ትት አዟሪ አንከርት (ቶች) የሸክላ የብረት ምድጃ ባንድ ስፍራ የማይቀመጥ አንከርት በብረት መዳመጫ ላይ የሚዞር የፈትል ዋግንቦ ቀጽ አንከርቶች አንከርት የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን እንክርት እንክርታች ዘዋሪ ቀው ሳላ ማንከርተት ማንከራተት ማዞር ማንከዋረር ማንቀዋለል ማንከርተቻ ማንከራተቻ ማዞሪያ ማንቀዋለያ ተንከረተተ ተንከራተተ ዞረ ተንከዋተተ ተንከዋረረ ተንቀዋለለ መንገድ መታው ተንከራተተ ግራ ቀኝ አየ ለማግኘት ለመቀበል ይህ ልጅ ዐይኑ ይንከራ ተታ ተንከርታች ተንከራታች የሚንከረተት የሚንከራተት ከረተት ከርታታ (ቶች) የተንከሪተተ አውታታ ቀውላላ ከርተት ቀውለል ከውተት አንድ ዓመት ከርተት አንድ ዓመት ሰርተት እንዲሉ ከርተት አለ ተንከራተተ መንከርተት መንከራተት መዞር መንከዋረር መንከዋተት መንቀዋለል ስብ ኵርችች (ኰረተ) የተሰበሰበ ስብ ኵርችች አለ ሰውነቱን ሰብስቦ ለብቻው ተቀመጠ ከሳ (ከስዐ) ተጐዳ ቀጠነ ቀለለ አነሰ ጐደለ ከውፍረት ከድንዳኔ ራቀ ከስዐ ጥንታዊ ዐማርኛ ነው ከሺ የሚከሳ ከሲታ የከሳች ብረ ሸሽ ጣጋ ክሱ የከሳ የቀጠነ ") (ኢሳ. ፳፬፡ ፲፯)
ከረተተ) ኰሳ
ከረከረ፡ ለበለበ ("ፈጀ አቃጠለ በርበሬው እሳት ስለ ገባ ጕረሮዬን ይከረክረኛል ከነከነን ተመልከት ከረከረ የጕልበት ዋጋ ቈረጠ ይህን ያኸል ' አለ ከረከረ ክርክር አበጀ በኦሪት ጥፍሩ ያልሻከረ ቀንዱ ያልከረከረ በግ መሥዋዕት ይኾናል ትግሬም ከረከረን እንደ ግእዙ ከረ ተፈ ይለዋል ወቀ ከረከረ ሞገተ ነዘነዘ ነተረከ ጨቀ ከርካሪ የከረከረ የሚከረክር መጋዥ ገዝጋዥ ማሲንቆ ክራር መቺ ያለው አከርካሪ የሽንጥ ዐጥንት ክርክር ያለው ")
ከረከረ፡ ኰረኰረ
ከረከንድ (ዶች) በመኻል 'ራሱ ላይ እንደ ተራዳ የኾነ ቀንድ ያለው ፈረስ ("ቀንደ ቍንጮ ") (መዝ. ፺፪፡ )
ከረከንድ ከረከረ
ከረየ (ከርይ ከረየ) ማሰ ቈፈረ
ከረደደ (ከርደደ) ደረቀ ("ሻከረ ጠና ጠነከረ ገረደደን አስተውል ከረደድ ከርዳዳ ክርድድ የከረደደ የሚከረድድ ደረቅ ሻካራ ቍጥርጥር ጠጕር ጠንካራ ሥጋ መከርደድ መድረቅ መሻካር መጥናት መጠንከር አከረደደ አደረቀ አሻከረ አጠና አጠነከረ አከርዳጅ ያከረደደ/የሚያከረድድ አሻ ካሪ አጠንካሪ ማከርደድ ማሻከር ማጠንከር አንከረደደ አዞረ አንቀጠቀጠ አንከርዳጅ ያንከረደደ/የሚያንከረድድ ኣዟሪ ")
ከረጢት (ቶች) በ፪ ወይም በ፫ ወገን ስፌት ያለው የገንዘብ/የሥንቅ/የልብስ/የቀላል ዕቃ መክተቻ/ማኖሪያ/መያዣ ከሸማ/ከበርኖስ/ከሸራ/ከጆንያ የተሰፋ ("(ኢሳ. ፫፡ ፳፪) በግእዝ ኸረጺት ይባላል (ግጥም) አይጣል ይሏል እንጂ ከጣለ ምን ይሏል ከከረጢት ወጥቶ ብር ይኰበልላል ኰረጆን ተመልከት ")
ከረጢት፡ ኰረኰመ
ከረፈ፡ ተመታ ("ጮለ በውስጥ እጅ አከረፈ (ዐረ፡ ከረፋህ) በጥፊ መታ አጮለ ከርፍ ጥፊ የመዳፍ በትር ከረፋ (ዐረ፡ ከረፋእ፡ አነፈነፈ ትግ፡ ከርፍሐ፡ ደረቀ፡ የቈዳ) ክፉኛ ሸተተ ተነፈገ ገማ የሽንት የፈሳሽ ጠነባ ንና ቀረናን እይ መከርፋት መተንፈግ መግማት አከረፋ አስተነፈገ አገማ ማከርፋት ማስተንፈግ ማግማት ክርፋት ክፉ ሽታ ከቁም የሚጥል ግማት ክርፋታም (ሞች) ክርፋት ያለበት የበዛበት ባለክርፋት ግማታም ክርፍት አለ ግምት ኣለ ከረፋ አከረፋፍ አተነፋፈግ መከርፋት ኰረፈ (ጐረፈ) ኩፍ አለ ቈጣ ቂም ያዘ ኰረፌ የመጠጥ ዐረፋ ፈረንጆች ሙስ ይሉታል ኵርፍ የኰረፈ የተቀየመ እከሌና እከሌ ኵርፍ ናቸው አለ ኵርፈኛ (ኞች) ዝኒ ከማሁ ቂመኛ ኵርፍ ኵርፍ አለ ኩፍ ኩፍ ኵርፊያ ቅየማ ኵርፍታ ዝኒ ከማሁ ቅያሜ ") (ዘፀ. ፲፡ )
ከረፈተ፡ ጨርሶ ከፈተ ("መክደኛን አስገለለ ጣለ ስሯጽ ነው መከርፈት መክፈት ክዳን አልባ ማድረግ ተከረፈተ ፈጽሞ ተከፈተ ከረፈት የተከረፈተ የተከፈተ ክርፍት ዝኒ ከማሁ ፍጹም ክፍት ከረፋን እይ ኰረፍታ ቍልልታ ኰረብታ ")
ከሬ፡ ኪሩብ
ከሬ፡ የአከርካሪ ሥር ("ከረከረ")
ከሬ፡ የአከርካሪ ሥር ("ከወደ ኋላ የቂጥ መጋጠሚያ ዐጥንት ይህ ልጅ እጅግ ስለ ከሳ ከሬው ይታያል ካራ ቢላዋ የቢላዋ ዐይነት መገዝገዣ መከርከሪያ ") (ምሳ. ፳፫፡ )
ከርሞ ከርሞ፡ ቈይቶ/ቈይቶ የኋላ/የኋላ
ከርሥ፡ (ከረፈፈ)
ከርሥ፡ ሆድ ("ጨጓራ ከርሥ የግእዝና ያማርኛ ሆድ ያማርኛ ብቻ ነው ከርሥ በያንዳንዱ ፊደል ጽፈት መካከል ያለ ባዶ ለምሳሌ ከርሥ አለው ማሕፀንን እይ ከርሣም ሆዳም በላተኛ ዘርጣጣ ከርሠ ሐመር የታቦት መንበር ለተኛ ክፍል ትርፍ ታቦትና መጻፍ የሚቀመጥበት ትርጓሜው የመርከብ ውስጥ ማለ ትን ያሳያል ይኸውም የመንበሩ ሥራ መርከብ ስለሚመስል ነው ")
ከርቤ (ዎች) የዛፍ ስምና መራራ ሙጫ ("የቀድሞ ሰዎች ሙጫውን ሽቱ ያደርጉታል ግብጾችም ለሬሳ ይቀቡታል ") (ዘፍ. ፴፯፡ ፳፭)
ከርክር፡ የቍስል ስም ("የእስኪትን ከርክሮ የሚቈርጥ በሽታ ጣሊያን ያመጣው (ግጥም) ፊታውራሪ ጨብጥ ቀኛዝማች ቂጥኝ ባቀኑት አገር ራስ ከርክር መጥቶ ይቈርጥ ዠመር ከርክር የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ መግዝ ዝዝግዝ ቍረጥ ክርከራ ምገዛ ግዝገዛ ማሲንቆ ምት ከርከሮ (ዎች) ዕሪያ የበረሓ 'ዐሣማ ቀንዳም ጥርሱ ጐባጣ ካራ የሚመስል ከርከሮ ያሠኘው ቀንዱ ነው ከርከሮ ዐጪር ሰው ከድንክ የሚ በልጥ ክርካር (ቅርቃር ጥኑ ' ጠንካራ ሰው ሰውነቱ የማይዝል የማይደክም ካክራን እይ ክርካር ክራይ ለከብት ጕልበት ለመሬት ለቤት የሚከፈል ሒሳብ በክርክር የሚ ወሰን ክርካረኛ ባለክራይ ክራያም የክራይ'ገንዘብ ያለበት መከርከር መገዝገዝ መመገዝ መከርከሪያ መገዝገዣ ማጭድ ጋዝ መጥረቢያ ማንኛውም ስለት አስከረከረ አስመገዘ አስገዘገዘ አስከረከረ ኣዘቀጠ አደፈረሰ አሳደፈ' አቈሸሸ አስከርካሪ ያስከረከረ የሚያስከረክር አስመጋዥ ")
ከርፈስ (ትግ) ወገል ከበሬ ዕቃ አንዱ
ከሸነ/ከሸፈ
ከሸከሸ፡ ኰሸኰሸ
ከሸፈ ጠፋ ("ተበላሸ ሳይተኰስ ሳይመታ ሳይዝ ቀረ ዐጕል ኾነ የጥይት የነገር ከሻፊ የሚከሽፍ የማይተኰስ ከሻፋ ክሽፍ የከሸፈ ብላሽ በከ ንቱ የቀረ ቀረ ከሸፋ ክሽፊያ መክሸፍ መክሸፍ መጥፋት መበላሸት መክሸፊያ የተኵስ ጊዜ አከሸፈ አጠፋ አበላሸ መና አስ አክሻፊ ያከሸፈ የሚያከሽፍ ማክሸፍ ማጥፋት ማበላሸት ")
ከሻኝ፡ የከሸነ ("የሚከሽን አሳማሪ ቀርዳጅ ከታፊ ሸንሻን ክሸና ቅርደዳ ከተፋ ሽንሸና የማሳመር ሥራ መከሸን ማሳመር መቀርደድ መክተፍ መሸንሸን መከሸኛ ማሳመሪያ መቀርደጃ መክተፊያ መሸንሸኛ ቢላዋ ሉሕ ደረገ አስከሸነ አንዲያምር እንዲሰምር አስ አስከሸነ አስቀረደደ አስከተፈ አሸ ነሸነ ማስከሸን ማስቀርደድ ማስከተፍ ተከሸነ አማረ ሰመረ ተከሸነ ተቀረደደ ተከተፈ ትክክል ኾነ ክሽን የተከሸነ ያማረ የሰመረ ትክክል ጥሩ ማለፊያ ቅርድድ ሽክፍ ጐመን ክሽን አደረገ ከሸነ ክሽን አለ ተከሸነ አከሻሸን አሰማመር መከሸን ኵሳንኵስ (ቈሳቍስ) ግስንግስ ዕቃ ግሴት ሰባራ ሥንጥር ዘሩ ኰሰኰሰ ነው ኵሳንኵስ የሳታት ጓዝ ከሌላ ክፍል መጥቶ በውስጡ እየገባ የሚነገር ቀለም ነአኵተከን ኣቡነ ዘበሰማያትን ጸሎተ ሃይማኖ ትን የመሰለ ቃል። ኵሳንኵሳም (በዓለ ቈሳቍስ) ባለብዙ የቤት ዕቃ ግስንግሳም። ኵሳንኵሳም ከታዘዘው ጸሎት በላይ ጨምሮ ጨማምሮ የሚጸልይ መነኵሴ ባሕታዊ ብዙ ጸሎትና አቍጣሮ ያለው ከሸፈ ") (ትግ፡ ከሰፈ)
ከቋት ከቋቱ ቶሎ ቶሎ መሥራት ("ከሥር ከሥሩ ")
ከበለ (ቀብለ) ጐደለ ("ጐደሎ ኾነ ከነበለን ተመልከት የዚህ ዘር ነው")
ከበለለ፡ ቍልቍል ተፈነገለ
ከበለለ፡ ድብልብል ኾነ
ከበለል/ከብላላ፡ ጠቅላላ ("በተዳፋት ስፍራ ላይ መቆም የማይችል ድብልብል ነገር")
ከበሰ (ከቢስ ከበሰ) ጠመጠመ ደመረ ከመረ ደረበ አነባበረ ሻሽን
ከበሰ፡ ሰበሰበ ("ጠመዘዘ ጠቀለለ አሰረ ጠጕርን")
ከበሰ፡ ኣሳበጠ ("አድበለበለ ሙቀጫ አስመሰለ እግርን")
ከበሰ፡ ክባስ አበጀ
ከበሠ፡ ጠመጠመ፡ ከበሰ
ከበረ (ከብረ) ታወቀ ("ተሾመ ተሸ ለመ ማዕርግ አገኘ ገነነ ሀብታም ኾነ በለጠገ ጌተየ")
ከበረ፡ ከበሮ፡
ከበሬታ፡ ከፍታ የማዕርግ ደረጃ፡ ርስዎታ አንቱታ
ከበር፡ የከበረ፡ ክብር ክቡር። እከሌ በርሻ ከበር ነው አንዲሉ። (በምሳ ከበር) ምሳ ትቶ እራት ብቻ እየበላ የከበረ ሀብታም የኾነ
ከበርቴ፡ የከሰርት ወገን ባለአዱኛ ("ኢሳ. ፫፡ ")
ከበርት ("ክቡራን/ክቡራት") የከበሩ ባለጠጎች ሀብታሞች
ከበርቶች፡ የከበር ብዢ፡ የከበሩ ጌቶች ("አስ. ፩፡ ") ከበርት የግእዝ፡ ከበርቶች ያማርኛ አካኼድ ነው
ከበሮ ("ዎች") አፍ ቂጡ በቈዳ የተለጐመ ውስጠ ክፍት ግንድ በክብረ በዓል የሚመታ፡ የደብር የከተማ ሲኾን በወርቅና በብር ይለበጣል (ተረት) ከበሮ በሰው እጅ ያምር፡ ሲይዙት ያደናግር።
ከበሮ ቤት፡ የመርከብ ጓዳ
ከበሮቤት፡ ከቅኔ ማሕሌት በግራና በቀኝ ያለ ስፍራ።
ከበበ፡ ("ከቢብ/ከበበ") ዐጀበ፡ ንደ ግድግዳ በዙሪያ ቆመ፡ የደግ። አሽከሮች ጌታቸውን ከበው ይቆማሉ
ከበበ፡ መውጫ በር መኼጃ መንገድ አሳጣ፡ የክፉ ("፪ሳሙ. ፲፩፡ ፲፯")
ከበበ፡ ክብ አደረገ፡ ነደፈ፡ በገረ፡ በዙ ሪያ ሠራ። ከተረን ተመልከት። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም፡ ይከብ/ይከባል ቢል እንጂ፡ ይከ ብብ/ይከብባል አይልም።
ከበባ፡ የመክበብ ሥራ፡ ዐጀባ። መክበብ በዙሪያ መሥራት መቀመጥ ማጀብ ("ዘዳ. ፳፰፡ ፶፭/፶፯ ።ሕዝ. ፬፡ ")
ከበተ (ከቢት ከበተ) ሰወረ (" በቀ ዐባ ደብቆ አስቀመጠ")
ከበከበ (ከብከበ) ሰርግ ደገሰ (" ጁን ወዳጁን ዘመዱን ሰረገ ዳረ")
ከበከበ፡ ክብረ በዓል አደረገ ("ዐዲሲቱ ቤተ ክሲያን ስትባረክ ዳሪ")
ከበደ (ከብደ) ተጫነ ("ጨቈነ ወደ አንድ ፊት አመዘነ ራሴን ከብዶኛል እንዲል ባላገር")
ከበደ፡ አረገዘ ("እርጕዝ ኾነ")
ከበደ፡ ከበረ ("ክቡር ኾነ የከበደ ሰው መጣ እከሌ የወለደች የከበደች ልጅ አለችው")
ከበደ፡ ኩባያ
ከበደ/ከበዴ፡ የወንድ መሪያ ስም
ከበደች፡ የሴት መሪያ ስም
ከቢር፡ መክበር ("ግእዝ") ከቢር፡ ትልቅ ("ዐረ") ዐዶን እይ። ክብራር፡ ("ሐረር") የሥራ ሹም
ከቢድ፡ ከባዳ፡ ከባድ፡ ከባጅ/በደ የሚከብድ ("ምሳ. ፳፯፡ ") ።ከባድ ሸክም እንዲሉ
ከባሪ፡ የሚከብር ("ክብር የሚያገኝ")
ከባሽ፡ የከበሰ/የሚከብስ ("ጠምጣሚ ደማሪ")
ከባቢ ("ዎች") የከበበ ' የሚከብ፡ ጃቢ፡ ሰራዊት።
ከባቢ፡ በፊደል ግራና ቀኝ የሚጻፍ የቃል ማጠሪያ ጐባጣ ምልክት ("()") ከባቢ ጦር፡ በጠላት ዙሪያ የቆመ ጭፍራ
ከባቢነት፡ ከባቢ መኾን። (ጥበ)ከበብ፡ ዝኒ ከማሁ ለከባቢ "
ከባባ፡ የመቅረዝ መብራት ማጥፊያ ("እንደ ታናሽ ዐረቄ መለኪያ ያለ")
ከባች (ከባቲ) የከበተ/የሚከብት ("ሰዋሪ ደባቂ")
ከባድመሬት፡ ጥቍር ዐፈር መረረ ።ከባድነት፤ከባድ መኾን
ከብለል ከብለል አደረገ፡ ግራ ቀኝ አየ
ከብቴ፡ ከብቴ ነኸ ("የሰው ስም")
ከብት (ቶች) የቤት እንስሳ ("በሬ ፈረስ በቅሎ አህያ ግመል በግና ፍየል") (ዘፀ. ፱፡ ፫፡ ምሳ. ፲፫፡ ፳፫)
ከብት፡ ሞኝ ("አላዋቂ ሰው")
ከብት ሰማይ ይከፍት፡ ፃነት መንግሥተ ሰማይ ያገባል
ከብት ርቢ፡ የከብት መውለድ ("መርባት መብዛት አላዋቆች ግን ከብት ርባታ ይሉታል")
ከብት፡ የገንዘብ ስም ("ቁም ከብት የሚገዛበት የሚለወጥበት ማንኛውም ገንዘብ ወርቅ ብር ሌባ እንዳይሰርቀው በሣጥን በጓዳ ተሰውሮ የሚቀመጥ") (ማቴ. ፮፡ ፳፬፡ ሉቃ. ፲፮፡ ፲፫)
ከብካቢ፡ የከሰከበ/የሚከበክብ ("ሰራጊ ዳሪ")
ከብካብ፡ ሰርግ ("ዓለም ደስታ እንግዳችንን በከብካብ ሸኘነው")
ከብዶ ትልቅ ! ራስ
ከተፈ፡ (ከቲፍ/ከተፈ) እያደቀቀ መተረ ቈረጠ አጠቀነ ሸከፈ ("(ገቢር) ከተፈ ፈጠነ ") (ተገብሮ)
ከታፊ ("(ፎች) የከተፈ የሚከትፍ ከተፎ ") (ዎች)
ከት አለ፡ ከተበ
ከቶውንም ("ጭራሹንም ከታቴ ከታች ወራሽ ከታቴው ") (ከታቹ)
ከቸለ/ከተመ
ከቸመ፡ ከተረ
ከቸረ/ከተተ
ከቸሮ፡ የከቸረ ("ክቾ አከቻማ = ለዛ ጥጤ አከቸረ እከቸቸ አከቻቸር አከቻቸች ኰቸረ ደረቀ ኰቸሮ ኾነ ኰቸሮ ደረቅ እንጀራ የተማሪ ምግብ ተወቅጦ የደቀቀውም ኰቸሮ ይባላል አኰቸረ አደረቀ ኰቸሮ አደረገ ከተተ ") (ከቲት/ከተተ)
ከነ (ምስለ፡ ከ፡ እለ፡ ጋራ፡ አንድነት) ልጄ ሆይ ከነከሌ አትግጠም ("ምድር ከነልብሱ ሰማይ ከነግሱ አንበሳው በወጥመድ ከነነፍሱ ተያዘ እነን ተመልከት ")
ከነበ (ትግ) አባያ ኾነ ("ተኛ አላ ርስ አለ ")
ከነበ (ዕብ፡ ካናብ፡ ዐረ፡ ከነበ) ጐነበ ("ሸፈነ ከተተ በውስጥ አደረገ ሰወረ ደበቀ ")
ከነበለ (ከንበለ) ጣለ ("አወደቀ ደፋ ቸለሰ ገለበጠ አፈሰሰ ")
ከነበለ፡ ከደነ ("ገጠመ")
ከነተረ (ከተረ) በዱላ መታ ("ጣለ በፍጥነት ገደለ ")
ከነቸረ፡ ከነተረ ("አደበነ ፈነቸረ ተከነቸረ ተከነተረ ደበነ ተፈነቸረ ክንችር ክንትር ፍንችር ")
ከነከነ፡ በልብ ተጕላላ ("ተመላለሰ ብን ቀነቀነ አወከ አንድ ነገር ረስቼ ልቤን ይከነክነኛል ")
ከነከነ፡ ከረከረ ("ለበለበ ፈጀ (የወሎ ቃልቻ ግጥም) በመተማ በኩል የምትጨሰው ጪስ የምትከነክን ናት የምታስነጥስ እምብዛም አትበጀው ላፄ ዮሐንስ ነና መወራረሳቸውን አስተውል አትርሳ ")
ከነወነ) ከወነ፡ ተከናወነ ("(ጣእ ጥአ ተሰልጠ) ተቃና ተሳላ ተሳካ ቀለ ጠፈ ዐለቀ ተጣጣመ ፍጹም ኾነ ") (ዘዳ. ፳፱፡ ፱፡ መዝ. ፩፡ )
ከነዘ) ቀነዘ፡ አክነዘነዘ ("ኣቅነዘነዘ ፈነዘን እይ ")
ከነዘ) ቀነዘ፡ ከፊደል መለወጥ በቀር ልዩነት የለውም ("አንድ ዘር ነው ዐረብ ግን ከነዘን አደለበ ይለዋል ፈጣሪ ")
ከነደ (ትግ) ዐጠረ ("ዐጪር ኾነ ንድ አከለ ")
ከነዳ፡ በክንድ ለካ ("መጠነ ሰፈረ ከነዳ ለዳኛ ገንዘብ ከፈለ ሰጠ ሰማኒያ ከነዳ እንዲሉ ")
ከነዳ፡ ኬንያ
ከነገ ነፃ አለ ቀን መረጠ።
ከነፈ (ከኒፍ ከነፈ) በክንፍ በረረ ("ቸኰለ ተጣደፈ ሮጠ ከነፈ አበደ ")
ከነፈፈ፡ ከኒሳ
ከነፈፈ፡ ክንፍን/እጅን መታ ("ቈረጠ ")
ከኒሳ፡ ጉባኤ ("ቤተ ክሲያን ከኒሳ (ኦሮ) ንብ የኅብረት ሥራ የሚሠራ ")
ከናንህ፡ ከነዓን
ከናፊ፡ የሚከንፍ ("በራሪ ጥዱፍ ክንፍ እንደ እጅ በግራና በቀኝ ጉን የበቀለ ባለላባ አካል በነፋስ ላይ የሚያን ዣብብና የሚሰፍ የሚኼድ ገላ ")
ከናፍር፡ ከንፈሮች
ከናፍሮ፡ የሰው ስም ("አበ ዝልጉሳን ከንፈሩን ነከሰ ተጨነቀ ቻለ ' ገሠ ጨከነ ከንፈሩን ነከሰ ዛተ አስፈራራ ")
ከንበል አለ፡ ፈሰስ አለ ("ተከነበለ ለከንበል የሬሳ በደረት መደፋት የቀረው ነው መስል ")
ከንበል፡ ደፋ ("ፈሰስ ከንበል አደረገ ደፋ አደረገ ከነበለ ፈሰስ ከንበል ያርገኝ እንዲሉ ")
ከንባላ፡ ዕንቍላል ቂጥ ("መቀመጥ መርጋት የማይችል ")
ከንባይ (ዮች) የከነበለ/የሚከነብል ("ደፊ አፍሳሽ ")
ከንተሮ፡ ቋራም ራሳም ዱላ ("ባንድ ጊዜ የሚያሳርፍ ")
ከንተብት፡ ከጐንደር ቤተ መንግሥት የተሾሙ ከንቲባዎች/ባላባቶች
ከንቱ (ከንተወ) ቅጽል ("ብላሽ የተ በላሸ ሥራ ኀጢአተኛ ሰው ባዶ መና መጥፎ የማይረባ ነገር ኹሉ እንደ እሳት እራት አኹን ታይቶ ቶሎ የሚታጣ ") (መክ. ፩፡ )
ከንቱ፡ ንኡስ አገባብ ("እንዲያው ጥቅም ኣልባ እከሌ ከንቱ መጣ ደከመ ")
ከንቱ ውዳሴ፡ ብላሽ ምስጋና ("የማይጠቅም ርባና ቢስ ከውነት የራቀ ") (ፊልጵ. ፪፡ )
ከንቱ፡ ጣዖት ("(ኤር. ፪፡ ) ከንቱዎች ብላሾች መጥፎዎች ሥራዎች ሰዎች ")
ከንቱ፡ ጧት ይበቅልና ሲመሽ ተነቅሎ የሚወድቅ ዕንጨት ("ዕፅ ከንቱ እንዲሉ ሕልምና ጥንቈላም ከንቱ ይባላሉ (ተረት) የባለጌ ኵራቱ እንዲያው በከንቱ ")
ከንቱነት፡ ከንቱ መኾን ("ብላሽነት ዐላፊ ጠፊነት ") (መዝ. ፯፡ ፲፭)
ከንቲ፡ የከንቱ ወገን
ከንቲባ (ካንተ ይግባ) ማዕርጉ ካሊጋባ በታች የኾነ ዋና የራስ ከተማ ሹምና ዳኛ/ገዢ ("የከተማው ቀረጥና የዳኝነቱ ንዘብ (ይባእ ኀቤከ) አንተ ዘንድ ይግባ ማለት ነው ይህ ስም በዘመን ብዛት ለባላባቶችና ለታላላቆች አገረ ገዦች ስለ ተሰጠ እስከ ዛሬ ድረስ የሐሳብ ባላባት ከንቲባ ይባላል ከንቲባዎች የመናገሻና የዋና ከተን ገዦች አስተዳዳሪዎች ")
ከንትር፡ የሚከነትር ("ክፉ በሽታ ፈጥኖ የሚገድል ")
ከንካኝ፡ የከነከነ/የሚከነክን ("ቀንቃኝ ክንከና ክንካኔ ቅንቀና እወካ ክንክና የበርበሬ ፍሬ መቀመጫ እንደ ተራዳ በውስጥ በመካከል የቆመ ")
ከንዋታ፡ ልዋዳ ምናውዬ ሥራ ፈት ከውታታ
ከንጂ (ጆች) የከነዳ/የሚከነዳ
ከንፈሩ፡ የርሱ ከንፈር ("የርሱ ጠርዝ ከንፈሩ ጠርዙ ጠንፉ ") (ዘፀ. ፴፯፡ ፲፪)
ከንፈራም፡ ከንፈረ ትልቅ ሰው/ዕቃ
ከንፈር፡ የሰው/የእንስሳ/የአራዊት የማንኛውም ፍጥረት አፍ መዝጊያ/መግጠሚያ ገላ ("በላይና በታች ያለ ከላይ ከንፈር ከታች ከንፈር እንዲሉ ልጅ ባለቀሰ ጊዜ ለንቦጭንና ምንጭርን ተመልከት ")
ከንፈር፡ የደገፍ ጫፍ
ከንፈር፡ ያፍ ስም ("መናገሪያ አፍ ተቀመጥ በወንበሬ ተናገር በከንፈሬ መታፈር በከንፈር እንዲሉ ")
ከንፈር፡ ዳር ("ጠርዝ ጠንፍ ") (ዘፀ. ፴፯፡ 16)
ከንፈሮች
ከንፈሯ፡ የርሷ ከንፈር ("የርሷ ጠርዝ ከንፈሯ ከንፈሪቱ ጠርዟ ጠርዚቱ ") (ዘፀ. ፴፯፡ ፲፬)
ከከ በጣም የበሰለ፡ አንጎል መሰለ፡ ዝንግልግል አለ።
ከከ፡ ደቀቀ ("ፈጽሞ አረጀ ደረቀ የጨከከች ባልቴት የጨከከች ዶሮ እንዲሉ")
ከከታም፡ ባለከከት ("እግሩ ከከት ያለበት የበዛበት ሰው ")
ከከት፡ ኰላ
ከከት፡ የተረከዝ ንቃቃት ("ሻካራ ለግ ያለው ")
ከከት፡ የተረከዝንቃቃት ("ከካ")
ከኪ (ዎች) የከካ/የሚከካ ("ፈንካች")
ከካ (ከሕክሐ/ዐረ፡ ከዕከዐ/ትግ፡ ኳዕኵዐ/ፈተገ) ሰበረ ("ፈነከተ ከፈለ ኹለት አደረገ የአበባ እኸልን ራስን ")
ከወሎ (ዎች) (ከወለ) የንጨት ስም ("ጫፉ ውልብልቢቱ ጕተና የሚመስል እሾኻም ዕንጨት በወይናደጋ የሚበቅል ")
ከወሰ (ከዊስ ኮሰ) ነቀነቀ ("በጠ በጠ ")
ከወረረ) (ከዊር ኮረ) አንከዋ ረረ ("አንቀዋለለ አዞረ ወረረን (ቀወለለ) እይ ")
ከወረር/ከውራራ፡ ቀወለል/ቀው ላላ ("ዘዋሪ ")
ከወተተ) (ወተተ) አንከዋተተ ("አንከዋረረ አንከራተተ (ከወረረ) ተመልከት")
ከወነ (ከውኖ ከወነ) ዠመረ ("አበጀ አዘጋጀ አደረገ አቀናበረ አስጌጠ አሳመረ ")
ከወከወ) (ኮከወ ከውከወ) አንከወከወ ("(አንኮከወ) አባከነ አንቀዠቀዠ አንቀወቀወ አዞረ ")
ከወከው - ከውካዋ - ገውጋዋ ዕርፊተ ቢስ ቂጡ ምድር የማይነካ/ቀዥቃዣ
ከወከው/ከውካዋ/ከውከውቱ፡ ቀዠቀዥ/ቀዥቃዣ/ቀወቀው/ቀውቃዋ/ቀውቀውቱ ("ዘዋሪ ")
ከዋ ቢስ፡ ዙረተ መጥፎ
ከዋ፡ ኰዜ
ከዋ፡ ዙረት
ከዋ ዙረት (ከወከወ) ክው አለ ("(ከዊው ከወወ) ክች አለ ደረቀ ከሸለለ ክው አለ ደነገጠ ክው አለ ተደወለ ጮኸ ከለለ ክው ማለት መድረቅ መደንገጥ መጮኸ ")
ከዋኝ፡ የከወነ/የሚከውን ("አዘጋጂ ' ሳማሪ ")
ከውር፡ አጐዶ ("ኵየት መጽሐፍ ግን በከውር ፈንታ ከቡር ይላል ስሕተት ነው") (ምሳ. ፲፯፡ ፫፡ ሕዝ. ፴፪፡ ፳፪)
ከዘራ (ዐረ፡ ከይዘራን) የበትር ስም ("ጫፈ ቀላሳ ዐጪር ምርኵዝ ከሽመል ከሌላም ዕንጨት እየታነጠ ከባሕር የሚመጣ ሲበዛ ከዘሮች ከዘራዎች ይላል ")
ከዚህ/ከዚያ፡ በቂና ቅጽል ዚህ
ከዚያ (እምህየ) ከዚያ ወዲህ ወዲያ/ከዚያዲያ/ከዚያዲያማ ("በቂና ንኡስ አገባብ")
ከየ/አከየ/ሀከየ/ሀየየ) አስ ከየ ("አከፋ አሰነፈ አስለገመ ")
ከየደ (ከዪድ) ውል አደረገ
ከይሲ፡ የእባብ ስም ("እባብ አንድስ ቅጤ ጐሚት ገና የምድር አውሬ ክፉም ሰው በግብሩ ከይሲ ይባላል ከይሲ የግእዝ እባብ ያማርኛ ነው ")
ከደነ (ከዲን ከደነ) ሰለተ ("ከፈ ከፈ ሸፈነ ከለለ አለበሰ በላይ አደረገ ገጠመ ") (ዘፀ. ፲፬፡ ፳፰፡ ዘኍ. ፱፡ ፲፭-፲፯)
ከደነ፡ ካህን
ከደና፡ የክዳን ሥራ ("ክፍከፋ")
ከደዋ (ዲባግ) የግምጃ ስም
ከዳ (ከድዐ/ዐለወ) ካደ ትቶ ኼደ ("ዐመጠ ሸፈተ አጋለጠ ለጌታው አልታዘዝ አለ ጌታውን ነከሰ ውሻው (ተረት) አፍ ሲከዳ ከሎሌ ይብሳል ")
ከዳ፡ ማር የሌለበት የንብ እንጀራ
ከዳ፡ አዳለጠ ("አንሸራተተ ጣለ አወደቀ ምድር ይክዳኝ እንዲል ማለኛ ባይከዳኝ የሰው ስም እግዜር ሰጥቶ ባይነሣኝ ማለት ነው ")
ከዳር እዳር፡ የሴት ስም ("ከጠረፍ እጠረፍ ማለት ነው")
ከዳተኛ (ኞች) የከዳት ወገን ("ሽፍታ ወንጀለኛ እያዘነጋ ሰው የሚገድል") (ሚክ. ፮፡ ፲፩)
ከዳተኛነት፡ ከዳተኛ መኾን ("ሽፍትነት")
ከዳት (ከዳዕት) የከዱ/የሚከዱ
ከዳኝ (ኞች) (ከዳኒ) የከደነ/የሚ
ከዳኝነት፡ ከዳኝ መኾን
ከዳደነ፡ ሰላለተ ("አለባበሰ ገጣጠመ")
ከዴ (ከጂ) ደመና በሰማይ ሲዞር ጤናን እየከዳ ሰውን የሚያስተኛ የሚያንቀጠቅጥ የሚመታ የወባ በሽታ
ከድን፡ አልባሽ ("ሰላች ከፍካፊ ")
ከጀለ (ኦሮ፡ ከጀሌ/ቀላወጠ) ዐሰበ ("ጓጓ ተመኘ ፈለገ ማንኛውንም ነገር ለማግኘት (የባለጌ ግጥም) ዝንጀሮ ጠባቂ ላያድር ያመሻል ብፈራሽ ነው እንጂ ልቤስ ከጅሎሻል ")
ከጂ (ከዳዒ) የከዳ/የሚከዳ ("ካጅ ከጆች ካጆች ")
ከጃይ (ዮች) የከጀለ/የሚከጅል ("በሰጡኝ ባገኘኹ ባይ ቀላዋጭ በጋልኛ ከጀልቱ ይባላል ")
ከፈለ
ከፈለ (ከፊል ከፈለ) ለየ ("ኹለት አደረገ ሙሴ የኤርትራን ባሕር ከፈለ ከፈለ የተለቃውን ከገንዘቡ ከፍሎ መለሰ ሰጠ አገባ እከሌ ብድሩን ከፈለ (በጎም ቢኾን ክፉ) ፬ኛውን እይ ዐሮም መሮም ማበሬን ከፈልኹ ከፈለ ፈተተ ቈረሰ ገመሰ ተነተነ እየብቻ አደረገ ዐደለ ሰጠ ወለለን ሠነጠቀን ተረተረን አስተውል ")
ከፈላ፡ ገመሳ ትንተና ("የመመለስ ሥራ ክፍያ መክፈል መካፈ እከሌና እከሌ በክፍያ ተጣሉ ")
ከፈረረ) ቀፈረረ፡ አንከፈረረ ("ገደለ እጅና እግርን አደረቀ አንቀፈረረ በተገብሮነትም ይፈታል እንክፍር የተንከፈረረ እንቅፍር ተንከፈረረ ሞተ ደረቀ ተንቀፈረረ ከፈረር ከፍራራ ቀፈረር ቀፍራራ ክፍርር እንክፍር ክፍርር አለ ድርቅ ቅፍርር አለ ተንከፈረረ ፍረር መንከፍረር መሞት መድረቅ መንቀ ፍረር መንከፍረሪያ መሞቻ መድረቂያ ቀፍረሪያ ")
ከፈተ፡ ኰፈተረ
ከፈተ፡ ወለለ ("በረገደ ገረገደ ገለጠ አበራ ፈታ ዘረጋ ለቀቀ አዛጋ አላቀቀ አፋ ሸገ የበር የሣጥን ያይን የባሕር የከብት ያፍ የመሰለው ኹሉ ") (ሕዝ. ፴፫፡ ፳፪፡ ዮሐ. ፱፡ ፲፬)
ከፈተረ (ቈጸረ) ፊቱን ቋጠረ ("ኰሰ ተረ ሰገጠ መከፍተር (ቈጺር) ግንባርን መቋ ጠር ")
ከፈቸረ፡ አለልክ ደረቀ ("ከቸለ ቀለዘ ከፍቻራ የከፈቸረ በጣም የደረቀ ክፍችር ዝኒ ከማሁ ፍጹም ደረቅ ክፍችር አለ ክችል አለ ከፈቸረ መከፍቸር መከቸል መቅለዝ አከፈቻቸር አከቻቸል መከፍቸር ")
ከፈነ፡ አለበሰ ("ሸፈነ ጠቀለለ ገነዘ ሰረ ሬሳን ") (ማቴ. ፳፯፡ ፶፱፡ ግብ. ሐዋ. ፭፡ )
ከፈኔ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ("የኔ ከፈን ማለት ነው (ተረት) አለ በለኝ ቀለቤን ሞተ በለኝ ከፈኔን ")
ከፈን (ሰንዱን) ዐዲስ የሬሳ ልብስ (" በፍታ መጠቅለያ መግነዝ ")
ከፈኖች፡ መጠቅለያዎች ("መገነዣዎች መከፈን መጠቅለል መገነዝ መከፈኛ መገነዣ መጠቅለያ ከፈን ከፋፈነ ገናነዘ ሸፋፈነ አስከፈነ አስጠቀለለ አስገነዘ ")
ከፈከፈ (ከፈፈ) ወፍራም አድርጎ ከደነ ("መታ አስተካከለ ክዳንን ከፈከፈ አበጠረ ከመከመ ጐፈሬን ከፈከፈ በላይ በታች አለበሰ ልብስን ለሰው ")
ከፈይ (ዐረ፡ ከፈ፡ አጐናጠፈ፡ ጠቀለለ) ቀይ/ብጫ/አረንጓዴ/ሰማያዊ ቀለም ያለው የሐር ስጋጃ/ጌጠኛ ምንጣፍ ("ጠጕራም ለምድ ካባ ቀሚስ ቆብ ኵፌትን እይ የዚህ ዘር ነው ከፈይ ወላንሳ ከፈይ የሴት ስም ከፈይ ወሌ እንዲሉ ")
ከፈፈ (አጥነፈ) ክፈፍ አበጀ/ሰፋ ("ዳሩን ዙሪያውን ፈርጁን በክፈፍ አስጌጠ የቤት የልብስ የዕቃ የሳንቃ ከፈፈ አበለጠ አላቀ ከፈፈ (ዐረ ከፈ) ሣሣ ቀለለ ከፋፊ (ዎች) የከፈፈ የሚከፍፍ ክፈፍ (ፎች) (ጥንፍ) በቀሚስ በካባ በበርኖስ በዐጽፍ በቤት ጣራ በገበታ ዙሪያ የሚሰፋ የሚደረግ የባለቀለም ሸማ ቅዳጅ የባሕር ዐረብና የነት ትልታይ ሥሥ ሉሕ ጠርብ የጫፍ የጠርዝ ተጨማሪና ተደ ራቢ ") ( ነገ. ፯፡ ፳፰, ፳፱፡ ሕዝ. ፵፫፡ 17)
ከፊለ ስም፡ የስም መክፈል
ከፋ (ላፋ) ከፋ
ከፋ (ዐረ፡ ከፋ፡ በቃ) ያገር ስም ("በጌራ አዋሳኝ ያለ አገርና ነገድ (ተረት) ከፋ ምን ይከፋ ዝናብ የማይለየው ስለ ኾነ ይመ ስላል ይህ ስፍራ መዠመሪያ ቡና የተገኘበት በመኾኑ ፈረንጆች ቡናን ከፋዊ የቱ እንደ ማለት ካፌ ይሉታል ለኑሮ የሚበ ብዙ ዐይነት ተክል ስለሚገኝበት ከፋ ተባለ በካፊያ ዘይቤም ቢፈቱት ዝናባም መኾኑን ያሳያል ")
ከፋ (ከፍአ) ባሰ ("ጠና ጨከነ መጥ ኾነ ከፋም ለማም አሩቴን ተወጣኹ እንዲሉ ")
ከፋታ፡ ያልተከደነ መክደኛ የሌለው የሸክላ ዕቃ ("ኣፉ ሰፊ የኾነ ለቃቃ አፈከፈታ እንዲሉ ")
ከፋኝ (ኞች) የከፈነ/የሚከፍን ("ገናዥ ከፈነና ከፋ ባማርኛ ይገጥማሉ። ከፋኝ (ከፍአኒ) ተቀይሚያለኹ ( ጥም) አንድ ይበቃኛል ከሞትኩ እኔ ብዙ ከፋኝ ለምኔ ")
ከፋይ (ዮች) የከፈለ/የሚከፍል ("የኹለት ዕዳ ከፋይ እንዲሉ ከፋይ ቈራሽ ገማሽ ዐዳይ ከፊል መክፈል (ግእዝ) ")
ከፋፈለ፡ ለያየ ("ቈራረሰ ገማመሰ ተናተነ እየብቻው አደረገ ") (ዘፍ. ፴፪፡ )
ከፍ፡ በለጥ ("ላቅ መብለጥ መላቅ ከፍ አደረገ ወደ ላይ ወሰደ ኣስ ቀመጠ በለጠ ከፋለ (ከፍ አለ) አደገ ረዘመ ላቀ ከፋለ የሰው ስም ከፍ ከፍ አደረገ ሌላውን ወይም ራሱን አከበረ ") (ሉቃ. ፲፰፡ , ፲፬)
ከፍ አለ፡ አደግአለ፡ ከፈፈ
ከፍ አለ፡ ከፈለ
ከፍ ከፍ አለ፡ ዐረገ ወደ ሰማይ ወጣ ("(ማር. ፲፮፡ ፲፱) ከፍታ ከፍ ማለት ከፍታ (ሉዓሌ) እድገት ርዝማኔ ልጫ ላቂያ ማዕርግ ልዕልና ") (ምሳ. ፳፭፡ )
ከፍተኛ (ኞች) ሉዓላዊ ("ከፍታ' ለው ባለከፍታ ማዕርገኛ ቁመተ ረዥም ")
ከፍታ፡ ርዝማኔ፡ ከፈፈ
ከፍታ፡ ቁመት/ርዝመት የቤት/የመ ርከብ ("(ዘፍ. ፮፡ ፲፭) ከፍታ ላይ ራስጌ ከፍታ ተራራ ኰረብታ (ኣድባር) ") ( ዜና. ፩፡ ፲፫)
ከፍታ፡ ታላቅ አደንጓሬ ("ከትንሿ የሚበልጥ ደንጐሎ ")
ከፍቶታል፡ ሆድ ብሶታል ("ተቀይማል ዐዝኗል ")
ከፍቶት፡ ብሶት ("ዐዳር መሮት አሳዝኖት ችግርና ሀዘን ጠንቶበት ከፋና ከፈተ ባማርኛ ይተባበራሉ። (የመናኝ ግጥም) እዘጋዋለኹ ቤቴን እንዳመሉ ቢጠይቋችን ከፍቶት ኼደ በሉ ")
ከፍካፊ፡ የከፈከፈ/የሚከፈክፍ ("ከዳኝ አበጣሪ ")
ኩ፡ እኔ ለሚል የአንቀጽ ዝርዝር ።ግእዝ 'ጸሐፍኩ፡ ያለውን፡ ጻፍኹ በማለት ፈንታ፡ ጻፍኩ፡ ይባላል። ኹን፡ ተመልከት።
ኩ፡ ካበ፡
ኩሊ (ዎች) ተሸካሚ ("የቀን ሠራተኛ ያተኛ ይኸውም በህንድ አገር ይነ ገራል።")
ኩሊ፡ ከለበ
ኵላሊት
ኵላሊት (ከለየ ኵሊት) በወገብ መካከል በሆድ ውስጥ ግራና ቀኝ ያለ ክብ ("እንክብል ሥጋ የደም ማጥሪያ የዘር ፈቃድ መነሻ አምላክ ኵላሊት ያጤሰውን ልብ ያሠላለሰውን ያውቃል ")
ኵላሊቶች (ኵልያት) ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ናቸው ("(ዘሌ. ፬፡ ፲፡ መዝ. ፯፡ ፲፡ ምሳ. ፳፫፡ ፲፮)")
ኵላብ (ቦች) ያፍርንጅ፡ የድቍስ፡ ያዣ፡ ቀንድ፡ ከኰልባ፡ የማይለይ።
ኵላብ በቀንድ፡ አምሳል፡ ከብረት፡ ከንወት፡ የተሠራ፡ ዕቃ፡ ማንጠልጠያ፡ በግንብ፡ በግድግዳ፡ ላይ፡ የተተከለ ።በግእዝ፡ መትከል፡ ይባላል፡ ("ዘፀ. ፴፰፡ ፲፯ ።ዕዝ. ፱፡ ።ሕዝ. ፲፭፡ ") ፈረንጆች፡ ፖርት፡ ማንቶ፡ ይሉታል።
ኵላብ በግንብ፡ በምሰሶ፡ ላይ፡ ያለ፡ የበግ፡ የፍየል፡ ቀንድ፡ ዕቃ፡ መስቀያ።
ኵላቦች መስቀያዎች፡ ማንጠልጠያዎች፡ ("ዘፀ. ፴፰፡ ፲፪, ፲፱, ፳፰")
ኵል (ኵሕል) ከመሬት የሚገኝ ሰማያዊ ማዕድን ("ላይን ጌጥና መድኀኒት የሚኾነ ") (ራእ. ፫፡ ፲፰)
ኵልል አለ፡ ጠራ ("ጥሩ ኾነ እንባና ኵል መሰለ ")
ኵልል ኵልል አለ፡ አህያን ጠራ (" አለ ")
ኵልስም፡ የተኰለሰመ ("በስተውስጥ ያለ የእግር ጣት ቍስል ሸለሊትን እይ ")
ኵልሽ፡ የተኰላሸ ("ቍላው የወጣ በሬ ፈረስ በቅሎ አህያ ግመል ድመት ዶሮ ")
ኵልትፍትፍ አለ፡  እስርስር አለ
ኵልትፍትፍ፡ የተኰለታተፈ ("እስርስር")
ኵልኵላ፡ ደንጊያ ተከላ ("ድርደራ")
ኵልኵል አለ፡ ድንኵል ድንኩል አለ ("ዶሮኛ ኼደ የልጅ ፪ቱንም አጥብቅ ኵልኵል ኵልኵል አለ ዶሮን ጠራ ነዪ አለ ")
ኵልኵል፡ የተኰለኰለ ("ያውድማ ንጊያ ")
ኵልኵልቲያም፡ ባለኵልኵልት ("ህንገቱ ላይ ኵልኵልት የወጣበት ያለበት ሰው ")
ኵልኵልት፡ ታናሽ ዕንቅርት ("እንቧይ ዕንቍላል የምታኸል ደደቆ ወዶማ በውሃ ምክንያት የሚመጣ ")
ኵልኵይ፡ የረኛ በትር
ኵሎ/ኩሎ፡ ያገር ስም ("ሸኦሮ ቤት በወላሞና በሊሙ አጠገብ ያለ አገር በግእዝ ግን (ኵሎ) ኹሉን ማለት ነው ኵሎ ኀደግነ ወተሎናከ ንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ ከኵሎ ግዛት ወደ ሌላ በተዛወሩ ጊዜ የተነገረ ቅኔ ነው ")
ኩም (ትግ፡ ጉም) ማጣት ("ማፈር ኩም አለ መልስ ዐጣ ዐፈረ ጉም ")
ኵምሽሽ አለ፡ ዕፍር አለ
ኵምሽሽ፡ ዐፋር ("ስቅጥጥ")
ኩምት፡ የዕከክ ስም ("በኵርማ ላይ ያለ ዕከክ ክምቹ ማለት ነው ")
ኵምትር አለ፡ ጭምትር አለ
ኩምትር፡ ጭምትር
ኵምትርትር አለ፡ ጭምትርትር አለ ("ተኰመታተረ ")
ኵምትርትር፡ የተጨመታተረ ("ጭምትር ትር ")
ኵምችች፡ ያጠረ/ያነሰ
ኵምኰማ፡ የመብላት/የመጠጣት ሥራ
ኩምጠጣ/ኩምጣጤ፡ የመኮምያኮጣጠጥ ሥራ ኹናቴ
ኵሳይ፡ የኵሳ ዘር ("ወይም ነገድ በግእዝ አነጋገር በጋልኛ ግን ከሴ ማለት ነው ኵሽ የሰው ስም የካም ፩ኛ ልጅ አኵስምን የቈረቈረ ኵሺ ኵሻዊ የኵሽ ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ") (ኤር. ፴፰፡ , , ፲፪)
ኵስ (ቶች) (ህቦ) ደረቅ የከብት " በት ("ሸለሸል ጥፍጥፍ ላምን እይ")
ኵስ፡ ከሰከሰ
ኵስ/ዐር፡ ኰሳ
ኵሩ (ኵሩዕ) የኰራ/የሚኰራጅንን ተጓዳጅ ("ኰፍናና ") (ኢሳ. ፲፫፡ ፲፩)
ኵሩዎች/ኵሮች፡ የኰሩ ተጓዳጆች ("( ቆሮ. ፬፡ ፲፱) ")
ኵሩዪቱ፡ የኰራች ("ጥይፍተኛዪቱ ") (ዘዳ. ፳፰፡ ፶፮)
ኵራራ፡ ያሰኑ ወዳጅ አጥባቂ ፈረስ
ኵራተኛ (ኞች) ትቢተኛ ("ኵሩ አኰራር አጀናነን መኵራት ")
ኵራት (ኵርዐት) ትቢት ("የትሕትና ተቃራኒ ኵራት እራት ነው እንዲሉ ")
ኵራት፡ የራስ መመታት
ኩሬ/ኵሬ (ኮራዊ) የቆመ ውሃ ("የማይወርድ የማይኼድ ")
ኵር፡ ቍጢጥያለ ተረተር የመሰለ ጣራ
ኵርማ፡ የኵር ባለኵር ("ሲታጠፍ ኵርነት ሾጣጣነት ያለው ክርን ")
ኵርማኒት፡ ልጆች በተረት የሚናገሯት ልጃገረድ ("ሌሊት እዛፍ ላይ ኹና በሥሩ ተሰብስበው ክፍያ የሚያደርጉትን አጋንንት በደረቅ ቈዳ አስደነገጠችና ዕቃ ውን ኹሉ ወሰደች ብለው ይተርታሉ ")
ኵርማን (ኖች) የዳቤ/ያሞሌ/የቀላድ ምድር ፬ኛ ክፍል
ኵርማን ኵርንችት
ኵርባ፡ መካከል ("(ማሕ. ፭፡ ፲፫፡ ሕዝ. ፴፰፡ ፲፪) በትግሪኛ ግን ኰረብታ ማለት ነው ")
ኵርኵም፡ ቡጢ ጡጫ
ኵርኵም፡ የተኰረኰመ ("በኵርኵም የተመታ የታጠፈ ")
ኵርድ፡ ባማርኛ ኰንታ የሚባል የፋርስ አረመኔ
ኵርፊት (ትግ፡ ሐባ፡ ከሪፍ) ዐውሎ ነፋስ
ኵርፋፍያ/ኵርፋፍቻ፡ እፍኝት ተንቀሳቃሽ ባየ ጊዜ ተቈጥቶ የመርዝ ትንፋሹን እፍ የሚል ("(ኢዮ. ፳፡ ፲፮፡ መዝ. ፻፵፡ ) አኰረፈ (ኰረፈ) ተከፋ ተቀየመ ከሰው ጋራ አልናገር አለ አኰረፈ (ንኅረ) አንቀላፍቶ ሳለበስናጉ ጮኸ ")
ኵርፍተኛ ዝኒ ከማሁ
ኵርፍታም ባለኵርፍታ
ኵሻይ ዘላን የኵሽ ወገን ማለት ይመስላል
ኵበት፡ ፦ካደ
ኵበት ወረራ፡ የዳግም ትንሣኤ ማግስት ሰኞ ቀን
ኩባክ፡ የቆቅ ጩኸት
ኵቤ/ኵብኵባዊ፡ የኵብኵባ ዐይነት ("ክንፍ የሌለው ፌንጣ")
ኩብ ("ክዑብ") ከብዙ ፈትል ተጠንጥኖ የኮበ ኮባ የመሰለ ታላቅ ሊቃቂት፡ ጥቅል ገመድ "
ኩብ የፈትል ጥቅል ፣ኮ
ኵብለላ፡ የመኰብለል/የመፈርጠጥ ሥራ ("ሽሽት ሩጫ ፍርጠጣ ሰደ ")
ኵብኵባ (ቦች) ክንፍ ያላወጣ ታናሽ አንበጣ ("ጡብ ጡብ መር መር እያለ የሚኼድ") (መዝ. ፻፭፡ ፴፬)
ኵብኵብታ፡ መርታ ዱብታ
ኩታራ ("(ሮች) ታናሽ ልጅ ማገድ መጠበቅ መታገድ የሚገባው ") (ዐማራ)
ኩት፡ የኮከብ ስም ("መልኩ ዓሣ የሚመስል የየካቲት ኮከብ ኩት ነገረ ኰትኵት እንዲሉ ኩት ውሃ የውሃ ዓሣ ይኸንንም ስም ጠንቋይ ኮከብ ቈጣሪ ለአንዳንድ ወንድና ሴት ያድለዋል ኪታ ") (ክታን)
ኩነት፡ መኾን ("ኹኔታ")
ኵነኔ፡ የጽድቅ ተቃራኒ ("ከሰማይንጉሥ በውነት የሚፈረድ ጥኑ ፍርድ የሥጋና የነፍስ ቅጣት ") (ራእ. ፲፰፡ )
ኵናማ (ሞች) በሱዳን ቈላ ያለ ገርና ነገድ
ኵንስንስ (ሶች) የተነሰነሰ ("የተሸላለመ ሽቅርቅር እመቤት ኵንስንሴ የኵንስንስ ዐይነትና ")
ኵንቢ (ዎች) በዝኆን አፍንጫ የተ ተከለ ሥጋዊ መትረብ ("አሸንዳ ዝኆኑ ውሃ ስቦ የሚጠጣበት ከዛፍ ላይ ቅጠል ቀጥፎ ወዳፉ የሚያገባበት ጠላቱን ይዞ የሚገድልበት የኀይሉ የብርታቱ የጕልበቱ መሣሪያ እጁ ")
ኵንቢ፡ ከነደ
ኵንቲ (ኵዕንታዊ) የንት ' ወይ ነት
ኵንት (ኵዕንት) የወፍ ቈሎ ("የምድር ፍሬ በዱር የሚበቅል ዐተር የሚያካ ክል ")
ኵንትሽ፡ የተኰነተሸ ("በተፈጥሮ ያጠረ ጣት ባላንድ ዐጥቅ ")
ኵንትሾች፡ ዐጫጪሮች ጣቶች ("ሰዎቹንም ያስተረጕማል ")
ኩንፈል፡ ያረመኔ ነገድ ("በቋራ በረሓ ውስጥ ያለ ")
ኵዕንት፡ የወፍ ቈሎ
ኵኩ መለኮቴ፡ ዋኔ ("የዋኔ ጩኸት ኵኩ መለኮቴ እሷ በፈሳችው በኔ ላከከችው አበ ተቈጡልኝ እመ ቈንጥጡልኝ እንዲሉ ልጆች ኵኩ የኵኵሉ ከፊል ነው ")
ኩኩ መለኮቴ፡ ዋኔ፡ ኵኩ
ኵኵሉ አለ፡ ጮኸ ("ዶሮው ኵኩ መለኮቴን እይ ")
ኵኵሉ፡ የዶሮ ጩኸት
ኵኪ (ኵኵዓዊ) የጣፊያ ዕብጠት - እንደ ኵክ መጥፎው ደም እየረጋ ከወባ ጠንቅ የተነሣ የሚመጣ በሽታ
ኵኪ፡ ዦሮ ግንድ ("ወይም ዦሮ የዙክባለኵክ እከሌ እከሌን በሽጕጥ ኵኪውን አለው ")
ኵክ (ኵኵዕ) እንደ ዝባድ በዦሮ ውስጥ ረግቶ የሚገኝ የመስሚያ ቅባት ("መራራ ሙጫ ከዦሮ ")
ኵክ ማውጫ፡ ታናሽ ጌጠኛ ማንካ ከብረት ከንሓስ ከመዳብ ከብርና ከወርቅ የተሠራ ("እንደ ሌላው ጌጥ ኹሉ ባንገት የሚደረግ ")
ኵክ ማውጫ፡ አሳባቂ
ኵክ ማውጫ፡ ዐጪር ሰው
ኵክ አወጣ (ትግ፡ ኰኵዐ) ኵክን ዛቀ ("ጠረገ ")
ኵክ፡ ኮከብ
ኵክኒ፡ ጭርት ዕከክ ኵምት
ኵክኒያም፡ ጭርታም ("ዕከካም ")
ኵዝ (ዕብ፡ ኮስ) ማሰሮ ("ጥዋ ኵስኵስት ኵዝ ካቦ እንዲሉ ኮስ ግን እንደ ዋንጫ ያለ ጥዋ ነው በምስጢር ከኵስኵስት ጋራ ይገጥማል ዚያ ")
ኵዝ፡ ከይሲ
ኵየት (ኪነት) የወርቅና የብር ማቅለጫ ማፍሰሻ መፈተኛ መጥበሻ ታናሽ ሸክላ
ኵይሳ (ሶች) የምሥጥ ዐፈር ዲብ ቍልል
ኵይስ፡ የተኰየሰ ("የተቈለለ")
ኵድኰዳ፡ የመኰድኰድ ሥራ ("ግርኘታ ")
ኩፋሌ፡ የመጻፍ ስም ("ከኦሪት የተከፈለ መጻፍ ሙሴ የጻፈው ")
ኩፋር፡ ነጭ የሐር ልብስ
ኵፌት (ዐረ ኵፈት) ቆብ ጥርቡሽ ባርሜጣ
ኩፍ አለ ብድግ አለ (ኮፈፈ)
ኩፍ ጫማ
ኩፍ ጫማ፡ እግርን እስከ ጕልበት የሚከት ባለገንባሌ ጫማ
ኩፍታ፡ መነሣት (ኮፈፈ)
ኩፍታ፡ ኩፍ ማለት ("መነሣት ኵርፍታ (ላፍ) ኩፍታ የሽንብራቂጣ ሊጡ ኩፍ ሲል የተጋገረ ጕልበቴ በርታ በርታ አበላ ኻለኹ የሽንብራ ኩፍታ እንዲሉ ልጃገረዶች ሲያጋፍቱ ")
ኩፍኝ፡ የዕከክ ዐይነት በሽታ ("አካልን የምታለብስ አንዳንድ ዘመን እመግነዝ (ከፈን) የምታደርስ ካፍንጫ ደም የምታፈስ እሷም በወጣች ጊዜ ባላገሮች ማሽላ ቈሎ ይቈሉ ላታል ያፈኩላታል። (ኰፈነነ) ኰነነ) ተኰፋነነ ጨር ቁን አፍንጫው ላይ አደረገ ኰራ (መኰንን መሰለ) ተደራራጊ ሲመስል በተደራጊነት መፈታቱን ተመልከት ")
ኵፍኵፍ አለ፡ ኵርፍ ኵርፍ አለ
ኪ፡ ቸልታ፡ ሲ።
ኪሊሊ፡ ድምጠ ቀጪን ብረት የምት ከል ' የምትዞር ("ክብ የልጆች መጫወቻ ፭ኛ ውን ከለለ እይ ልል ")
ኪሎ (መክሊት) የሚዛን ልክ ("እንደ ነጥር ያለ አንዱ ኪሎ ፲፻ ግራም ዐሥሩ ኪሎ ግራም ይኾናል ሲበዛ ኪሎዎች ይላል ( ኪሎ) የመንገድ ስም ማዚያ ፳፯ አደባባይ ( ኪሎ) የካቲት ፲፪ አደባባይ ፬ና የተባለ በዙሪያው ያለ መተላለፊያ ጐዳና ነው ፍል ")
ኪሎ ሜትር፡ የኪሎ ሜትር (" ሺሕ ክንድ ")
ኪሎ ግራም፡ የኪሎ ግራም (" ክንድ ")
ኪስ (ሶች) የልብስ ጓዳ ("ከረጢት ገንዘብና ሌላም ታናናሽ ዕቃ መክተቻ ' መያዣ ከኮትና ከሱሪ ከእጀ ጠባብ ከቀሚስ ጋራ በስተላይና በስተውስጥ ተሰፍቶ የሚታይ ኪሳም ባለኪስ ግልገሎቿን የምትይዝበት ኪስ በጐኗ ላይ ያላት የአውስትራ ልያ አውሬ ፈረንጆች ካንጉሩ ይሏታል። ካሰ (ትግ፡ ከሐሰ) ገንዘብ ከፈለ ሰጠ አስረከበ ለተሰደበና ለተመታ ለተበደለ ካሽ () የካሰ የሚክስ ካሳ ከፋይ ካሳ በደለኛ ሰው ዐጥንት ስላረከሰ አካል ስላጐደለ የሚከፍለው ፲፭ ወቄት ወርቅ በዳኛ በሽማግሌ የሚቈረጥ በደል በደሉን ወታደር በድሏል ካሳውን ግን ባላገር ሲከፍል ይታየናል ")
ኪስ፡ ኵሳ
ኪነ ጥበብ፡ የጥበብ ዘዴ ("ዐቅድ ርቀት እየተሻሻለ የሚኼድ ")
ኪን
ኪን (ከየነ) ጥልቅ ረቂቅ ብልኅት ዕውቀት ("ተንኰል ")
ኪንታሮት፡ የቍስል ስም ("በህያና በሰው ፊንጥጣ የሚበቅል የሚወጣ ቋርነት ለው ቍስል ያህያ ኪንታሮት እንዲሉ ")
ኪዳነ ማርያም፡ የማሪያም ኪዳን
ኪዳነ ምሕረት፡ በየካቲት ፲፮ኛ ቀን እመቤታችን ከልጇ የተቀበለችው የምሕረት ውል ("በዓል የበዓል ስም")
ኪዳነ ምሕረት፡ የታቦት ስም ("የመቤታችን ታቦት ")
ኪዳነ ሰላም፡ ወንጌል
ኪዳነ ቃል፡ ቃል ኪዳን "
ኪዳነ ወልድ፡ የወልድ ኪዳን (ዮሐ. ፰፡ ፶፩)
ኪዳናዪት (ኪዳናዊት) የሴት ክርስትና ስም ("ኪዳን ያላት ባለኪዳን ኪዳን የተቀበለች ማሪያም ማለት ነው ")
ኪዳኔ፡ ከዚህ በላይ ያለው ስም በከፊል ሲነገር ኪዳኔ ይባላል
ኪዳን ʾ ውል፡ ከየደ
ኪዳን፡ ውል ("መሐላ ቃል ኪዳን እንዲሉ የውል ቃል ሲሉ (ብሉይ ኪዳን) ኦሪት ነቢያት (ሐዲስ ኪዳን) ወንጌል የሐ ዋርያት መጻፍ ኪዳን ዘርፍ ይዞ እየተናበበ የተቀብዖ (የክርስትና) ስም ይኾናል ")
ኪዳን፡ የጸሎት ስም ("ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያት የነገራቸው ያስተማ ራቸው ጸሎት ይኸውም ጊዜ ነው ጠባ ለኪዳን መሸ ለቍርባን እንዲሉ መጽሐፈ ኪዳን እይ ")
(ኦሮ) ደን
ካ፲፭ ከቅርብ ቀን ወዲህ ያለ ጊዜ ("አኹን ለታ መጥቼ ዐጣኹኸ አኹን ሰው አኹን አውሬ ዐመለ መጥፎ ጠባየ ክፉ ቈጭባራ ፲፪ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ በፊደልነት ስሙ ላዊ አኃዝ ሲኾን ለ፴ ይባላል የቦታ ደቂቅ አገባብ ፍችው ወደ እከሌ አገር ላገር መንደር ለመንደር ዞረ የቀረው ነው ከመንደር ለመንደር ያሠኛል ከተናባቢ ሳድስ ቅጽል ይወጣል ታቦትን እይ ተቀባይ እየኾነ በብትን ኹሉ ገባል ላምላክ ምስጋና ይግባው ለሰው ሞት አነሰው ለሥራ ተጋ ለውነት አደላ ለወሬ አቈተመ ፍችው በቁም ቀሪ ነው በመራሕያንም ሲነገር ለርሱ ላንተ ለኛ ይላል ለኔ ከጋራ እባብ ለባብ ይተያያል በካብ ይኸውም ከምስለ የመጣ ነው ባጫፋሪነትም እባብና እባብ ተብሎ ይፈታል የየ ተወራራሽ ይን ተመልከት የረ ተለዋጭ ማረ ግላ ") ("መዓረ ግራ")
ካህነ ጣዖት፡ የጣዖት ካህን ("ቃልቻ ቃላተኛ የአረማውያን ቄስ")
ካህናተ ሰማይ፡ መላእክት ("የሰማይ ካህናት የሰማይ ቄሶች የግዜርን መንበር ' የሚያጥኑ የጽርሐ አርያም ቀዳሾች ነገደ ሱራፌል ክንፍ ያላቸው ")
ካህናተ ደብተራ፡ በድንኳን ውስጥ የሚቀድሱ የሚያወድሱ ካህናት
ካህናት፡ ዲያቆኖች ("ቄሶች ደብተሮችየቤተ ክህነት ሰዎች ማይምን ግን ካህናቶች ይላቸዋል ")
ካህን (ክህነ) ዲያቆን ("ቄስ ደብተራ በቤተ መቅደስ (በምኵራብ በቤተ ክሲ ያን በመስጊድ ያምላክ የጣዖት) አገልጋይ የሚቀድስ የሚያወድስ የሚዘምር ሳታት ' ቋሚ አወዳሽ ቀዳሽ ካህን ለመባል መደበ ኛው ቄስ ነው") (ሉቃ. ፲፡ ፴፩)
ካህንነት፡ ካህን መኾን
ካልእ (ከልአ) ሌላ ("ኹለተኛ ካልኣይ ዝኒከማሁ ትንቢት አንቀጽ ካልኢት የቅጽበት መክፈያ ")
ካም (ዕብ፡ ሐማም/ሞቀ ጋለ) የኖኅ ፪ኛ ልጅ ("የሴም ታናሽ የያፌት ላቅ ቈላ ሙቀት ወበቅ ማለት ነው ( ) ")
ካራ (ሮች) በካራ ሃይማኖት የሚያምን
ካራ ቀደደ።
ካራ፡ ቢላዋ ("ከረከረ ክር ፈትል ከረረ ኵር አለ በዦሮ ጮኸ ( ረረ) ")
ካራ የሃይማኖት ስም
ካርታ፡ ጥይት ይዞ እጠመንዣ ቀፎ የሚገባ ሥሥ ብረት
ካርታ፡ በላዩ የንጉሥና የንግሥት የአበባ ሥዕል ከፈረንጅ ቍጥር ጋራ ያለበት የቁማር መጫወቻ እንደ ብራና ያለ ዐጪር ወረቀት
ካርታ፡ ከረተሰ
ካርታ፡ የየብስና የባሕር ያገር የርስት የቦታ የከተማ የቤት የመንገድ ንድፍ ቢጋር ያለበት ጠንካራ ወረቀት ("ፈረንጆች ልጆችን በተማሪ ቤት የሚያስተምሩበት በቤታቸው የሚያኖሩት ምስክር ካርት በላዩ የይለፍና የከተማ ነዋሪነት የሠራተኛ ስም የታተመበት ወፍራም ወረቀት ሰነድ ካርቶን ወፍራምና ሥሥ ጥሩና መናኛ የወረቀት ሉሕ ቀለም የሌለውና ያለው የመጣፍ ገበታ የቤት መከታ የሚኾን ካርት ካርታ ካርቶን የፈረንጅ ቋንቋ ነው በግእዝም ክርታስ ይባላል ካሮት የተክል ስም ወጥ ጋራ እየተቀቀለ የሚበላ ጣፋጭ ተክል። ኮርቻ (ቾች) (ኮር) ባህያና በበቅሎ በፈረስና በግመል በዝኆን ዠርባ እየታሰረ በላዩ ሰው የሚቀመጥበት ከን ጩት ከቈዳ ከድብዳብ የተበጀ ኮርቻ ትክል የሱሪ ወን በር እንደ ኮርቻ የተተከለ በኮርቻ ላይ የሚያርፍ ካሮት ኮርች የዛፍ ስም እሾኻም ዕንጨት ኮርቻ የሚኾን ጎርጎ ኮርቾች ጎርጎዎች ኮረት (ሐንበለ) ኮርችን ' ጠረበ ኮርቻ አበጀ ለበደ ጫነ ከረቸመ ቸነከረ ጠቀጠቀ አገባ አጠ ጋጋ ዘጋ ዐጥርን አጥብቆ አሰረ እግርን መከርቸም መቸንከር ማግባት ማሰር ማጥበቅ ተከረቸመ ተቸነከረ ተጠቀጠቀ እግር ብረት ገባበት በጥብቅ ታሰረ አከረቻቸም አስተሳሰር መከርቸም ኰረተመ ሰበረ አሳጠረ ዕንጨትን ኰርታሚ የኰረተመ የሚኰረትም ቋሚ ቀራፊ ክም መኰርተም መስበር ማሳጠር ተኰረተመ ተሰበረ ዐጪር ኾነ ኵርትም የተኰረተመ የንጨት ኵርትም አለ ዕጥር አለ አኰረታተም አሰባበር መኰርተም ከረተፈ (ከረተ) ገረደፈ በቀላል ፈጨ እንቀት አደረገ ስንዴን ገብስን ዐጃን ቀረጠፈን አይ ከርታፊ የከረተፈ የሚከረትፍ ገር ዳፊ መከርተፍ መገርደፍ መፍጨት መከርተፊያ መገርደፊያ ወፍጮ ከረታተፈ መላልሶ ከረተፈ ተከረተፈ ተገረደፈ ተፈጯ ክርትፍ የተከረተፈ እንቅጥቃጭ ከረተሰ (ከረተ) ቈረጠመ ሰበረ ዐኘከ አደቀቀ የቈሎ ከርታሽ የከረተሰ የሚከረትስ ቈር ጣሚ መከርተስ መቈርጠም ማኘክ መከርተሻ መቈርጠሚያ ማኘኪያ መንጋጋ ተከረተሰ ተቈረጠመ ተሰበረ ታኘከ ደቀቀ ክርትስ የተከረተሰ ቍርጥም ክርታሽ ካፍ የወደቀ ጥሬ የቈሎ እንቀት ድቃቂ ስባሪ ዕኛኪ አከረታተስ አቈረጣጠም መከርተስ ክርታስ ብራና ወይም ደብዳቤ ") (ግእዝ)
ካርነት፡ የካራን ባሀል መቀበል
ካሮች ቢላዎች
ካበ፡ ("ከዐበ") ደንጊያን በደንጊያ፡ ጡብን በጡብ፡ ዕንጨትን በንጨት፡ ጓልን በጓል፡ አሞሌን ባሞሌ፡ ላይ፡ ደረሰ፡ አስቀመጠቀጠለ፡ አነባበረ
ካበ፡ አመሰገነ፡ ብዙ ምስጋና ሰጠ፡ ኰፈሰ ።አወደድ ባይ አሽከር ጌታውን ይክባል
ካቡት ("ካባዊት") ባለመካፈቻ ረዥም ቀሚስ የካፖርት ዐይነት።
ካቢ፡ ("ከዐቢ") የቅርብ ሴት ትእ ዛዝ አንቀጽ።
ካቢ ("ዎች") ("ከዓቢ") የካበ፡ የሚ ክብ፡ ካብ፡ ዐዋቂ።
ካቢ፡ ያገር ስም፡ በዜጋመል ባሻገር ያለ ቀበሌ።
ካባ ("ካፓ") እንደ በርኖስ በልብስ ላይ የሚለበስ ባለቀለም ረዥም መደረቢያ። ካፓ የመምህራን ዐማርኛ ነው። ሲበዛ ("ጥቦ")ካቦች ይላል
ካባላንቃ፡ ባለለምድመደረቢያና ባለወርቅ ጥልፍ ያለው የቀዳሽ ልብስ። ላንቃ የተባለው ለምዱ ወይም ነበልባል መስሎ የሚታየው የወርቁ ጥልፍ ነው
ካቤላ (ዎች) ኰቴው/ጫማው ወደ ላይ የተቀለሰ ቀንድ የመሰለ አረጋገጠ ጐደሎ ከብት ሰው ("በግእዝ ጸፋሕት ይባላል")
ካብ ("ቦች") የተካበ፡ የተደረበ፡ ድብርብ ንብብር ደንጊያ ("ኢሳ. ፳፪፡ ") ።ጥሬ ካብ፡ ዐፈር ቃም ካብ እንዲሉ ("እንቧይ ካብ የማይረባ የልጆች ሥራ ፈራሽ።
ካብ፡ ("ከዐብ") የቅርብ ወንድ ትእ ዛዝ አንቀጽ።
ካቦ ("ትግ፡ ካዕቦ") ቍና የሚይዝ መስፈሪያ፡ ይኸውም ክፋሎ ነው ።ካዕቦንና ክፋሎን እይ
ካቦ፡ በዋንጫና ባንኮላ ዐይነት የተሠራ ጥዋ ።ኵዝ ካቦ እንዲሉ
ካቦርት ፖርት ረዥም ቀሚስ፡
ካነ (ክህነ) አዳቈነ ("አዛቈነ ዲያቆን ካህን አደረገ (አቀሰስ) ክህነት ሰጠ ") (ዘፀ. ፳፱፡ ፳፯)
ካናዳ፡ ባሜሪካ ውስጥ ያለ አገር ("አስቀድሞ የፈረንሳይ ቅኚ የነበረ ")
ካናዶች፡ የካናዳ ተወላጆች ("እንግሊዞች ፈረንሳዮች ")
ካንቻ፡ ደን ("ደገላ ካንቻ መታ መነጠረ ")
ካንች፡ በምስማር የተመታ ሠረገላና ወፍ ባንድነት
ካንድ ዓመት በፊት ያለፈ የወዲያኛው ዓመት ቅጽል ("ካች ዓምና እንዲሉ። የኻች ምስጢር ፍጻሜና ኅልፈት ነው ኻቸው ") ("ኮሙ")
ካንጉሩ፡ ያውሬ ስም ("ቡችሎቿን በኪስ የምትይዝ የአውስትራልያ ኣውራ ")
ካንፉር፡ የመድኀኒት ስም ("ለውጋትና ለቍርጥማት መታሻ የሚኾን አብነት ዛፉ በምሥራቅ እስያ ይገኛል ")
ካዕብ (ከዐበ) ኹለት ("ኹለተኛ ደል ካዕብ ካዕብ እንዲሉ ")
ካዕቦ፡ ፬ቱን ቍና የሚያደርግ መስፈሪያ (" ክፋሎ ")
ካከመ (ኰከመ) ተጐዳ ("ታመመ ተንከፈከፈ አረግጥ አለ መርገጥ ተሳነው ጣመነን ተመልከት ግር ")
ካኪ፡ ጥብቆ ኮትና ሱሪ የሚኾን ቀለም የገባ የባሕር አገር ልብስ
ካካ፡ ዐር መጥፎ ነገር አክሽ ወደ ዐዘቅት የሚጣል ዐይነ ምድር
ካካ) (ከሕክሐ) አንካካ ("( ንከሐክሐ) ገደል ሰደደ አንከባለለ እላበጠ ")
ካካ) ሰከለ (ሰኪል/ሰከለ) አፈራ፡ ፍሬ ሰጠ (ግእዝ) "ሰነከለን" እይ።
ካካሚ፡ የካከመ/የሚካክም ("ውስጥ ")
ካካበ፡ ደራረበ፡ ቀጣጠለ። መካካብ፡ መደራረብ።
ካካቴ፡ አሪባራ የሚባል የስሜን ወፍ ("መጠኑ የርግብ ጥቍርና ዐመድማ ጭራው ነጭና ጥቍር ሲጮኸ የሣቀ ይመስላል ")
ካካቴ፡ የሚሥቅ " (ካካ)"
ካካቴ፡ የሚሥቅ ሰው
ካክራ (አድማስ) ጠንካራ ንር ብረት የማይሰበር ስለቱ የማይበርድ ሲከዛ ካክሮች ያሠኛል
ካክራ፡ ጐበዝ ሰው ("ፍንክች የማይል ")
ካውያ (ዐረ) የልብስ መተኰሻ ብረት ("የፈረንጅ ሥራ ዐጣቢዎች በውስጡ ፍም እየጨመሩ የታጠበ ልብስን ለጥ ቀጥ የሚያደርጉበት ይኸውም በቈርበት ጠቅሎ በመርገጥና በመተምተም በማለስለስ ፈንታ ነው ")
ካያ/ኻያ (ከልአ) በቁሙ ኹለት ዐሥር
ካይላ ሜዳ፡ በጐንደርና በቀሓ መካከል ያለ የካይላ ሜዳ
ካይላ፡ ባፄ ፋሲል ጊዜ የነበረ ዕቃ ጫኝ ጭፍራ
ካይላ፡ ፈላሻ ("የፈላሻ ወገን ካይላዎች ፈላሾች ጠይቦች ")
ካይንት፡ ዝዪ ("(ጐዣም)")
ካደ (ክሕደ) ፈጣሪን የለም አለ ("ሃይማኖቱን ተወ በመከራ በገንዘብ በሴት ምክ ንያት ለወጠ") (ማቴ. ፳፯፡ , ፸፪፡ ሉቃ. ፲፪፡ )
ካደ፡ መሐላን ጣሰ ("ውልን አፈረሰ ከዳ ካደ ዐማርኛ ከድዐ ክሕደ ትግሪኛና ግእዝ መኾኑን አስተውል ዳግመኛም ከድዐ ጥንታዊ ዐማርኛ ሊባል ይቻላል ")
ካደ፡ ዐደራውን ሸፈጠ ("ዐሎ አለ እንዳላየ እንዳላወቀ ኾነ")
ካዲያን (ከሓድያን) የካዱ ካጆች
ካድ፡ ዝኒ ከማሁ
ካድ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ
ካጅ (ጆች) (ከሓዲ) የካደ/የሚክድ ("ማኒ ሠራዒ መጋቢ የለም ባይ") (አርእስተ መዝ. )
ካፊር (ሮች) ከሓዲ ሃይማኖት ("የሴ ለው ነው በአረብኛ ካፍር ይባላል ")
ካፊያ (ነፍኒፍ) ረቂቅ ዝናም ("ሲዘንም የማይታይ የጉም ሽንት ") (ዘዳ. ፴፪፡ )
ካፊያ፡ ረቂቅ ዝናም፡ ካፋ
ካፋ (ትግ ካፈየ) በርቀት ዘነመ ("ወረደ ")
ካፍ (አከፈ) የፊደል ስም
ካፍር፡ የበቅሎ ከንፈር በሽታ ("ቢጋለ ብረት የሚተኰስ ከንፈራዊ ማለት ይመስላል ")
ካፓ ካፖርት ("(ካቦርት) ረዥምና ሰፊ ቀሚስ ክፍት ባላዝራር መደረቢያ በጣሊያንኛ ካፖቶ ይባላል ድኩ መጻእኩ የተባለውን በላኹ ሰገድኩ መጣኹ ይላል ") (ከአ)
ኬለ (ዔለ) ባንድ ስፍራ ዞረ ("ተሽከ ረከረ የብር የክብ ነገር ")
ኬለኛ (ኞች) የኬላ ዘበኛ ("ኬላ ባቂ ባለኬላ ")
ኬላ (ዎች) ይለፍ የሌለው ሰው እንዳይኼድበት የሚከለከል ያገር በር
ኬላ፡ ያገር በር ("፡ከላ ")
ኬልቲ፡ የማዕርግ ስም ("በግእዝ ቀኛዝ ማች ማለት ነው ")
ኬማ፡ የዶማና የማረሻ ዕላቂ ብረት
ኬንያ (ከየነ) ብልኅ ("ፈላስፋ ጥበብ ")
ኬንያ፡ ያገር ስም ("በምሥራቅ አፍሪቃ ያለ አገር በጋልኛ ኬኛ የኛ ማለት ነው ይላሉ ")
ኬክሮስ፡ ስሳ ደቂቃ
ኬደ፡ ረገጠ ("ኼደ ዐለፈ ተራመደ")
ኬደ፡ ረገጠ፡ ከየደ
ኬደ፡ ከጀለ
ኬፋ፡ ደንጊያ ዕንቍ
ክ፡ ለቅርብ ወንድ የአንቀጽ ዝርዝር
ክህለ) ቻለ ("ታገሠ (ግእዝ) ከሃሊ የቻለ የሚችል ቻይ ታገሽ ከሃሊው ጌታ እንዲሉ ")
ክህነት፡ መንፈሳዊ ሹመት ("አገልግሎት ክህነትና መንግሥት እንዲሉ ")
ክህነት ተቀበለ (ተክህነ) ተካነ ("ካህን ኾነ ካነንና ዳቆነን ተመልከት B ")
ክሕደ) ካደ/ከዳ ("(ግእዝ) ከሓዲ የካደ የሚክድ ፪ካጅ ክሕደት ክደት መካድ ")
ክለላ (ክላሌ) ቅየዳ ("ውሰና ስወራ ቈረጣ ")
ክለሳ፡ ምለሳ ("ደገማ ጭመራ ቅልቀላ ")
ክለብ (ከለብኸ፡ ትከልብ) የቅርብ፡ ወንድ፡ ትእዛዝ፡ አንቀጽ፡ ውሻ፡ ኹን፡ እንደ፡ ውሻ፡ ሩጥ፡ ማለት፡ ነው።
ክላ (ክላእ) ከልክል ("ተው ኺድ ወግድ ወዲያ በል ")
ክላሽ፡ ምላሽ ("የትምርት ድጋሚ ተካለሰ ተጫረሰ ተማላ ተካለሰ ተዳቀለ አካለሰ አንዱን ከሌላው አቀላቀለ አካለሰ ክልስ ጥይት አሣራ አካለሰ አዳቀለ ")
ክል፡ ዝኒከማሁ (ሕዝ. ፵፭፡ , , )
ክል፡ የተከለለ ("፡ከለለ ")
ክልል ' አለ፡ ከለለ
ክልል (ክሉል) የተከለለ/የተጋረደ/የተወሰነ ("ዳሩ እሳት መኻሉ ገነት የተባለ መስቀል የዞረበት ገዳም ደብር ሥጋዊ ዳኛ የማይገባበት በግእዝ ምስካይ ጸወን ይባላል ")
ክልል፡ መክለ
ክልል፡ የወሰን ደንጊያ ("ወንዝ ተራራ ወሰን ክልል እንዲሉ ")
ክልስ (ሶች) የተከለሰ ("ዳግመኛ የተሠራ ጥይት ከኹለት ዐይነት ነገድ የተወ ለደ ዲቃላ (በቅሎ) ክልስ መናኛ በርኖስ እንደ ገና በላዩ ተነድፎበት የተረገጠ ")
ክልብስ፡ የተከለበሰ ("ክንብል ችልስ ክልብስ አደረገ ችልስ ፍስስ ክን ብል ጥጥት አደረገ ")
ክልከላ (ክልካሌ ክልአት) የመከልከል የማጋፈር ሥራ ጥበቃ
ክልክል (ክልእ) የተከለከለ/የተጠ በበ ("መስክ ደን ተክል ቤት ዕርም ")
ክልውስ ክልውስ አለ፡ ጥርውዝ ጥርውዝ አለ
ክልውስ፡ ዝኒ ከማሁ
ክመማ፡ ክርከማ ("ቈረጣ")
ክመራ፡ ድርደራ ("ቍለላ")
ክምር (ሮች) የተከመረ ("ጕቾ ቍልል ዘመመን ድርብርብ ንብብር ዕቃ ") ( ዜና. ፴፩፡ )
ክምቸታ፡ ክምቹነት
ክምቹ፡ የተከማቸ/ስብስብ/እክብ ("ጥር ቅም ")
ክምቹነት፡ ስብስብነት ("ጥርቅምነት")
ክምችት አለ፡ ተከማቸ
ክምችት፡ ዝኒ ከማሁ ለክምቹ
ክምክማት፡ የጠጕር ክፍክፋት ("ትክክልነት ")
ክምክም አለ፡ ተከመከመ ("ድምድም አለ ")
ክምክም ክምክም አለ፡ ከትከት ከትከት አለ ("ባለማቋረጥ ሣቀ ተንከተከተ ")
ክምክም፡ የተከመከመ ("ክፍክፍ ትክክል ")
ክሡት፡ የተከሠተ ("ግልጥ")
ክሣድ (ትግ) የተራራና የተራራ መካከል ዐራዳ በር መተላለፊያ
ክሣድ (ዶች) የእጀ ጠባብ ("የጥብቆ የቀሚስ የኮት የካቡት የካባ ዐንገትጌ በግእዝ ግን ክሣድ ዐንገት ማለት ነው ")
ክስ ዝኒ ከማሁ
ክሥተት፡ የዜማ ስም ("ከዳዊት መዝሙርና ከነቢያት እየተወጣጣ በታላላቅ በዓል ባደራረስ ቀን ከሰኞ እስከ ቅዳሜ የሚባል ዜማ ትርጓሜው መግለጥ አገላለጥ ነው ክሥተት አርያም እንዲሉ ")
ክስት መክሳት
ክስት አለ ከሳ
ክሥዳ፡ የማዥራትና የሽንጥ ላይ ማት እየተገመደ መጻፍ መጠረዣ የሚኾን ("ክሥዶች ዥማቶች ክሥዲያም ባለክሥዳ ክሥዳው የሚታይ የከሳ ሰው ወይም ከብት ")
ክረምት የዝናም ወር ("ከሠኔ ፳፮ እስከ መስከረም ፳፭ የሚቈጠር (ተረት) ለሞኝ ሠኔ በጋው መስከረም ክረምቱ በበጋ፥ እሞኝ ቤት ተንጋጋ በክረምት እቤትኸ ተከተት ክረምት አግቢ ክረምት መግባቱን የሚያስረዳ ባለክንፍ ዐሸን ሐምሌ ሲገባ ክረምት አግቢ ከመሬት ይፈላል እሱንም ተባት ምሥጥ ይሉታል ክረምት አፈራሽ በበጋ የማይታይ እንጕዳይን ቀንድ አውጣን አሙኝትን ዐምሳ እግርን የመሰለ ነገር ኹሉ ክራሞት ኑሮ አኗኗር ከርሞ ቈይቶ ዘግይቶ ለከርሞ ለላመት ከርሞ ጥጃ ቁመቱ ከፍ የማይል የማያድግ ልጅ ")
ክራረኛ፡ ክራር ያለው ባለክራር
ክርታስ፡ የፅንስ (ሽል) መጠቅለያ ሥሥ ረቂቅ ሥጋዊ ወረቀት
ክበበትስብእት፡ የሰውነት ቅርጽ አቋም። ጌታችን ለመፍረድ በክበበ ትስብእት ይመጣል።
ክበብ ("ቦች")፤ማዘንትን ምጣድን ዐው ድማን የመሰለ ክብነት ያለው ዙሪያ ነገር። ክበብ፡ አንተ ለሚባል የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ።
ክበታ (ከበታ) ድበቃ ("ስወራ")
ክበድ፡ እርጉዝ ከብት። በግእዝ ግን ክብደት ማለት ነው፡ የሐር ገመድ የበቅሎ ክበድ እንዲሉ።
ክበድ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ፡ ክበር ማለት ነው ።ልጄ ውለጂ በጂ እንዲል መራቂ አባት "
ክበድነት፡ እርግዝና።
ክቡራን/ክቡራት፡ የከበሩ ("የሩቆችና የቅርቦች ወንዶችና ሴቶች ጌቶች እመቤቶች")
ክቡር፡ የከበረ ("የተሾመ የተሸለመ ባለማዕርግ ታላቅ ሰው ጌታ ባለጠጋ ከውርደት ከድኸነት የራቀ ችግር ደኅና ሰንብት ያለነገር ግን ክቡር በአእምሮ ለከበረ ጨዋ ኹሉ የስም ቅጽል ይኾናል ይድረስ ለክቡር አቶ እከሌ እንዲል ደብዳቤ ጻፊ ክቡር እምክቡራን ከከበሩ ይልቅ የከበረ")
ክቢ (ትግ፡ ክበብ) ክብ ("የክብ ዐይነት ከበባ")
ክቢ፡ ሰራዊት ጭፍራ ("እንዳጥር እንደ ቅጥር የኾነ ከባቢ ' ጦር በክቢ ላይ ክቢ") (፩ሳሙ. ፲፯፡ , ፳፩፡ ፳፪፡ ሚክ. ፭፡ ፩፡ ዮኤ. ፫፡ -)
ክቢ፡ ደባ ("ተንኰል እከሌ እከሌን ክቢ ሠራው")
ክባስ (ሶች) እንደ መቋሚያ ጌጠኛ ኹኖ ይቀረጽና በወጋግራና ባ፬ ማእዘን ጫፍ ተዋዶ በስተውስጥ ወይም በሰበሰብ መካበቢያን ተሸክሞ ጣራ ደጋፊ ዐጪር የማእዘን ቍራጭ (፪ዜና. ፫፡ ፲፭)
ክብ (ክቡብ) የተከበበ ("ሞላላ ማእ ዘን ያይዶለ ሥራ እንደ ዕንቍላል እንደ ኳስ ያለ ድብልብል እንክብል ወይም ቀለበት መሳይ ነገር")
ክብ፡ ከበበ፡
ክብ ካባ፡ ያንገትጌው ቅድ ክብ የኾነ ካባ ("ባለክሣድ")
ክብ፣ የተከበበ፡ ከበበ።
ክብሳት (ቶች) ያልተሠራ ያልተመ ሸጠ የሴት ጠጕር ኹናቴ ታጥፎ ተቀልብሶ ተደራርቦ ጕቾ መስሎ የሚታይ
ክብስ፡ የተከበሰ ("ትልቅ ጥምጥም በደንብ ያልኾነ ክምር")
ክብረ ሰማይ (ሕብረ ሰማይ) ከደንጊያ የተገኘ ሰማይ የሚመስል አቃጣይ የቍስል መድኀኒት
ክብረ በዓል፡ የበዓል ክብር ("ገናን ጥምቀትን ትንሣኤን ' ጰራቅሊጦስን መስቀልን ፍልሰታን ኅዳር ሚካኤልን ማዚያ ጊዮ ርጊስን ለመሰለ በዓል የሚደረግ ማሕሌት ዘፈን ንግሥ እልልታና ደስታ ሥራ አለመሥራት መንገድ አለመኼድ ")
ክብረ ነገሥት፡ የነገሥታትን ክብር የሚናገር መጻፍ ("ታሪከ ነገሥት ነብሪድ ይሐቅ የጻፈው")
ክብሩ ይስፋ፡ እግዜር በመላው ዓለም ይመስገን
ክብሪት (ቶች) ከድኝና ፎስፎር ከሚባል የዓሣ ዐጥንት ከሚገኝ ቅመም የተዘጋጀ ሲጭሩት የሚነድ በታናሽ ዕንጨት ጫፍ ያለ እሳታዊ ዐፈር
ክብሪት፡ ከበተ
ክብር (ቅጽል) ክቡር ("ሀብታም ክብር ያማርኛ ክቡር ክቡራን ክቡራት ክብ ርት የግእዝ ናቸው የክብር አካብሪኝ እንዲሉ ተረግጦ ይነበባል ")
ክብር (ጥሬ) ማዕርግ ("ሀብት ጌትነት ብልጥግና (የዱር ክብር) አዝመራ ዛፍ እንስሳ ማዕድን") (ኢሳ. ፲፡ ፲፰)
ክብር መጣጃ፡ (ግብር መጣጂ ምጣድ የሚጣድበት ሰዓት ገበረን ልከት ገና ተወራራሾች ስለ ኾኑ ግብበማለት ፈንታ ባላገር ክብር ይላል ')
ክብር ይእቲ፡ የቅኔ ስም ("፰ኛ ቅኔ ከድርገት በፊት በዕዝልና በአራራይ ዜማ የሚባል ምስጢረ መስቀል")
ክብርት፡ የከበረች ("የሩቅና የቅርብ ሴት እመቤት")
ክብርና፡ ክብርነት፡ ድንግል/ድንግልና በነፍስ በሥጋ ክብር የሚያሰጥ ስለ ኾነ ክብርና ተባለ ("ዘዳ. ፳፪፡ ")
ክብርናዎች፡ ድንግሎች
ክብርናገሰሰ፡ አጠፋ፡ ልጃገረድን ዳሰሰ ዐወቀ።
ክብት (ክቡት) የተከበተ ("ሽሽግ ስውር ድብቅ")
ክብነት፡ ክብ መኾን
ክብክብ፡ ታላቅ ጥበቃ በምግብ
ክብደት፡ መክበድ፡ ከባድነት። መክበድ መጫን መጨቈን ("፪ቆሮ. ፲፪፡ ") በክብደት ፈንታ መክበድ ይላል ("፪ሳሙ. ፲፪፡ ")
ክቱብ/ክሱብ) የተከተበ ("የተጻፈ ብጥ ሥንትር ሥንጥቅ ክትባት ") (ቶች)
ክቱብ/ክሱብ) የተከተበ ("የተጻፈ ብጥ ሥንትር ሥንጥቅ ክትባት ") (ቶች)
ክናድ፡ የሸማ እጅጌ ("የክንድ ልብስ ክናድ የእጅ ቤዛ እንደ ገንባሌ ከቈርበት የተሰፋ ባጨዳ ጊዜ ገበሬ ክንዱን የሚ ያገባበት ሲበዛ ክናዶች ይላል ")
ክን ድፎ (ዎች) ሥሥ ዳቦ ባለሰንበር ሲጋገር በወዙ የተደፋ (ተመልከት፡ ማሞ ብለኸ ማሚ ቶን)
ክንበላ፡ ግልበጣ
ክንብል አለ፡ ፍስስ አለ
ክንብል አደረገ፡ ድፍት አደረገ
ክንብል፡ የተከነበለ/የፈሰሰ/የተደፋ
ክንብንብ (ግልቡብ) የተከናነበ (" ፍንፍን ክንንብ ቢል በቀና ነበር ")
ክንብንብ (ግልባቤ) የራስ/የፊት መሸፈኛ ልብስ ("ቀጸላ አንደኛው ቅጽል ኹለተኛው ጥሬ (ስም) መኾኑን አስተውል ")
ክንችር አለ፡ ድብን አለ ("ተክነቸረ ")
ክንችር፡ ድብን ፍግም
ክንውን፡ የተከናወነ ("ያለቀ")
ክንዝንዝ፡ ቅንዝንዝ
ክንዱን ተንተራሰ፡ ዐረፈ ("ሞተ ክንዴን ሳልንተራስ ሳልሞት በሕ ይወት ሳለኹ ")
ክንዳም፡ ክንደ ረዥም
ክንዳታ፡ ምጠና ("ከፈላ")
ክንዴ፡ የሰው ስም ("የኔ ክንድ ማለት ነው ")
ክንድ (ዶች) ከብብት እስከ ጣት መጨረሻ ያለ ኹለት ሙሉ እጅ ከደረት ጋራ የሰው ቁመት መለኪያ ("ቀኝ ክንድ ግራ ክንድ እንዲሉ ")
ክንድ፡ ከኵርማ ዠምሮ ያለ የእጅ ክፍል ማንኛውንም ነገር መከንጃ መመጠኛ መስፈሪያ ("ክንድ ተስንዝር እንዲሉ ")
ክንድ፡ የክንድ ልክና መጠን ("አንድ ክንድ ኹለት ክንድ ሸማ እንዲሉ ")
ክንፉን ጣለ፡ ክንዱን ገለጠ ("አሳየ በጣም ዐዘነ አለቀሰ ")
ክንፋማ፡ ረዥም ውዥምዥም ክንፍ ያለው መልኣክ
ክንፋም (ሞች) ባለክንፍ ("ዶሮ ቆቅ አሞራ ወፍ ንብ ጥንዝዛ አንበጣ ዝንብ ትንኝ ዓሣ ጥያራ የመሰለው ኹሉ (አሞራ ክንፍ) ሰቀልኛ ቤት በዳርና በዳር ጣራው ክፍት ኹኖ የሚታይ ")
ክንፍ፡ የዛፍ ቅጥይ ("ዐጽቅ ክንፉ ክንፌ የወንድ ከፊለ ስም፡ የክርስትና ነው ዳግመኛም ክንፉ ስሙምየርሱ ክንፍ ክንፌ የኔ ክንፍ ተብሎ ይተ ረጐማል ")
ክንፍንፍ፡ የተክነፈነፈ ("ቅንዝንዝ")
ክንፎች (አክናፍ) ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ጥቂቶች ("ወይም ብዙዎች ") (ዘፀ. ፳፭፡ )
ክካም፡ ክክ ያለው ("ባለክክ ሲፈጭ የማያደቅ ክክ የሚያደርግ ")
ክክ (ኮች) የተከካ ("የባቄላና ያተር የሽንብራ የጓያ የምስር እኸል ለጒልባን ለሹሮ ለወጥ ለቅይጥ የሚኾን የገብስ እንቀት ") (፪ሳሙ. ፲፯፡ ፲፱)
ክክ አቦክ፡ የሌላት ረኸጥ ሴት ("ሳታደቅ የምታቦካ ")
ክክመታም፡ ክክመት የያዘው ("ባለክክ መት መኼድ የተሳነው መንገደኛ ")
ክክመት፡ የውስጥ እግር ጕዳት
ክወና (ክዋኔ) ብጀታ ("ድርጊት ዝግጅት ")
ክውክው አለ፡ ተንከወከወ
ክደት (ክሕደት) የእምነት ተቃ ራኒ
ክዳተኛ፡ የክዳት ሰው ("ዐመጠኛ")
ክዳት (ክድዐት/ዕልወት) ሽፍትነት (ኢሳ. ፴፡ )
ክዳን (ኖች) የጣራ ልብስ ("ሣር ብር ዐፈር ጕብጕባ መክደኛ ")
ክዳን፡ ክፍክፋት ("እድሞ")
ክድናት፡ የክዳን ኹናቴ ("አኳዃን")
ክድን (ክዱን) የተከደነ ("ስልት ክፍክፍ ")
ክድን አለ፡ ግጥም አለ ("ተከደነ")
ክድን አደረገ፡ ግጥም አደረገ ("ከደነ ")
ክጀላ፡ ምኞት ("ፍለጋ")
ክጅል፡ የተከጀለ
ክፉ (ክፉእ) የከፋ ("ደግ በጎ ያይዶለ ሰው (ተረት) ከክፉ ተወልጄ ስፈጭ ዐደርኩ ስምን እይ ")
ክፉ ልማድ፡ ስካር ("ምንዝር ሥሥት ነውር ሌብነት ክፉ ልማድ ያሰርቃል ከማድ እንዲሉ ")
ክፉ መንፈስ፡ ጋኔን ("ሰይጣን ") ( ሳሙ. ፲፰፡ )
ክፉ፡ መጥፎ ግብር ("(ኤር. ፳፬፡ ) ክፉ አድራጊ የደግ አድራጊ ተቃ ራኒ ማንኛውንም የማይገባ ነገር ያደረገ ሰው ")
ክፉ ሰው፡ ጨካኝ ("እናት አይምሬ ጠማማ ግንባሩን የሚቋጥር ፊቱን የሚያጠቍር ")
ክፉ ሥራ፡ ስርቆት ("ቅሚያ ወንጀል ነፍስ መግደል ቤት ማቃጠል ቋንዣ መቍ ረጥ ሐሰት ተንኰል የመሰለው ኹሉ ")
ክፉ ቀን፡ የረኃብ/የጦር/የልቂት መን
ክፉ ቀን) ባጤ ምኒልክ መንግሥት እኸል የጠፋበት ከብትና ሰው ያለቀበት ዘመን
ክፉ በጎ፡ መጥፎና ደግ
ክፉ ባለዳ፡ ተበድሮ የማይከፍል ("ወስዶ የማይመልስ ") (መዝ. ፴፯፡ ፳፩)
ክፉ ነገር፡ ስድብ ("ሐሜት ጭንቅ እከሌን ክፉ ነገር አግኝቶታል ")
ክፉ ዐመል፡ መጥፎ ጠባይ
ክፉ ዐሳቢ፡ ቅን የማይዶልት ("በጦርነት መሸነፍን በንግድ ማጕደልን የሚያስብ ")
ክፉ ውሻ፡ ተናካሽ ("ከዳተኛ አዘንጊአውራ መንገድ እየኼደ የሚባላ ")
ክፉነት፡ ክፉ መኾን
ክፉና ደግ፡ ጽድቅና ኀጢአት ("ጨለማና ብርሃን ")
ክፉን ችላ፡ የውሻ ስም
ክፉኛ፡ ባለክፉ ("የክፉ ወገን ክፉኛ ንኡስ አገባብ በጣም በጠና በብርቱ እከሌ ክፉኛ ")
ክፉዎች፡ የከፉ ሰዎች ("ጨካኞች")
ክፋሎ፡ የቍና አጋማሽ ("የካዕቦ ፰ኛ ስፈሪያ ")
ክፋተኛ (ኞች) ክፉ አድራጊ ("ዐመ ፀኛ እከየኛ ሀኬተኛ ልግመኛ ለሰው ጐን የማይዶልት ወደ ክፉ የሚዘነብል ")
ክፋት (ክፍአት) ክፉነት ("ጭካኔ ዐመዕ ተንኰል ") (ምሳ. ፰፡ ፯፡ ማር. ፯፡ ፳፪)
ክፋች፡ ሳይከደን ቀርቶ ስለ ነፈሰበት በመበላሸቱ የሚጣል/የሚፈስ መብል/መጠጥ
ክፋይ (ዮች) በጫፉ ፍም ያለበት ዕንጨት ("የማገዶ ክፍ ")
ክፍ (ብስ) ለድመት የሚነገር የቍጣ ቃል ("ክፉ አውሬ በቃ ኺድ ወግድ ማለት ነው ")
ክፍ ብስ፡ ከፋ
ክፍ ክፍ አለ፡ ካፊያው ዘናነመ
ክፍ ክፍ አደረገ፡ መላልሶ አካፋ
ክፍሌ፡ ከፊለ ስም ("ክፍለ ጊዮርጊስ ክፍለ ማርያም በማለት ፈንታ ክፍሌ ይባ ላል ")
ክፍሌ፡ የኔ ክፍል
ክፍል (ክፉል) የተከፈለ ("አንድ ከመ ኾን ብዛት ያገኘ ፍን ተጭነኸ አንብብ ክፍል ተከፍሎ የታደለ ዕድል ድርሻ ፈንታ መቍነን የላይኛው ቅጽል የታችኛው ጥሬ (ስም) መኾኑን አስተውል ክፍል የመጻፍ መክፈያ በአንቀጽና በምዕራፍ ውስጥ ዐልፎ ዐልፎ የሚጻፍ አንባቢና ተርጓሚ የሚያርፍበት ክፍሎች የተከፈሉ ዕድሎች ድርሻዎች ")
ክፍልፍል፡ የተከፋፈለ ("የተለያየ ልዩ ልዩ የኾነ ክፍልፋይ የክፍልፍል ዐይነት ክፍልፍል አለ ልይትይት አለ ተከ ፋፈለ ")
ክፍታፍ (ክፍት አፍ) ከንፈሩን የማይገጥም ጥርሱን የማይከድን ሞኝ ሰው
ክፍት፡ የተከፈተ ("የተለቀቀ ") (ማር. ፪፡ )
ክፍትፍት፡ የተከፋፈተ ("ግልጥልጥ")
ክፍን፡ የተከፈነ ሬሳ ("ጥቅልል ግንዝ መከፈን መጠቅለል መገነዝ መከፈኛ መገነዣ መጠቅለያ አካፈነ አጠቃለለ አጋነዘ ማካፈን ማጠቃለል ማጋነዝ አከፋፈነ አጠቃለለ አገናነዘ አስተ ሳሰረ ")
ክፍከፋ፡ የመከፍከፍ ሥራ ("ከደና ")
ክፍክፍ፡ የተከፈከፈ ("በመከፍከፊያ የተመታ ትክክልና ወፍራም ክዳን ክፍክፋት የክፍክፍ ሥራ ኣከዳደን ከደና ")
ክፎች፡ ዝኒ ከማሁ ("(መዝ. ፩፡ ፩፡ ማቴ. ፭፡ ፵፭) ")
ኮለለ፡ ዐነጠ ("ቀረጠ ኮለል አበጀ ሰነ ")
ኮለሌ (ኮለላዊ) የኮለል ዐይነት ("የሚ ዛን ዕንወት ጫፍ ")
ኮለል (ሎች) የብልትና የሞፈር ራስ ("ሰንደቅ ")
ኮለል አለ፡ ተለል አለ ("ወረደ ቅቤ ከተቀባ እግር ላይ ውሃው ዐለፈ ")
ኮለልማ፡ ኮለል ያለው ("ባለኮለ ኮለል አደረገ አወረደ አፈሰሰ ዘርን እንባን ደምን ")
ኰለሰመ፡ ከረከረ ("አቈሰለ (ጐዣም) ተኰለሰመ ተከረከረ ቈሰለ ")
ኰለሸ) አኰላሸ፡ የከብትን/የዶሮን ቍላ ቀደደ ("ሠነተረ ሰነጋ ጐነደለ አወጣ አኰላሺ ያኰላሸ የሚያኰላሽ ሰንጊ ")
ኰለሸ) ኮመጠጠ
ኰለተፈ (ከልተፈ) ጸየፈ ("ተቈለፈ ታሰረ ትክክል መናገር አቃተው ያንደበት ኰልታፋ ኵልትፍ የኰለተፈ ያፍ አንደበተ እስር ")
ኰለኰለ (ትግ፡ ኰልኰለ/ኰረኰረ) በዙሪያ ደረደረ ("ተከለ አስቀመጠ ንጊያን ሰውን ዐውድማ ለማበጀት ግብር ለማብላት ስጦታ ለመስጠት ")
ኰለኰለ፡ ዐቈረ ("ቋጠረ ዕብጠት ዠመረ ")
ኰለፈ፡ ልብስንና ማንኛውንም ዕቃ በጭቃ በወጥ በቅቤ በቀለም በእድፍ ነገር ዐልፎ ዐልፎ በከለ ("አበላሸ አጠፋ ለኰፈን እይ የዚህ ዘር ነው ከል ")
ኰላ (ትግ፡ ኰልዐ/ሐብረተ) በናስ ጭራ መታ ("እንቆቆ እንዶድ ጨምሮ ዐጠበ አጠራ ወለወለ ፈገፈገ አጠዳ የገሰ ሰውን የለቀቀውን ዐደሰ አደመቀ በኮመር ነከረ ከንሓስ ከመዳብ ከብር የተሠራውን ጌጥና ዕቃ ወይም ንሓሱን መዳቡን በብር ብሩን በወርቅ ቀባ ኮመርን ' ሰነገለን እይ ኰይ የኰላ/የሚኰላ (ጥላ) መኰላት ማጠብ ማጥራት መወል ")
ኰላለፈ፡ የኰለፈ ድርብ ("ወይም ደጊመ ቃል ")
ኰላላ፡ ዐጣጠበ ("ወላወለ ዐዳደሰ ")
ኮላሴ፡ የኮላስ ወገን
ኮላስ፡ የሰው ስም ("የነጠረ ንጥር ጥሩ ወይም መጨረሻ መደምደሚያ ማለት ይመስላል ")
ኰላሽ፡ የተራራ ስም ("በዶባ አጠገብ ያለ ሰፊ ተራራ የመራቤቴ ክፍል ዐጠበሽ አጠራሽ ዐደሰሽ ማለት ነው (ግጥም) ኰላሽ ዙሪያው ገደል በሩ በዘበኛ መቼ ይኾን የኛ መገናኛ ")
ኰላሽ፡ ያገር ስም ("፡ኰላ ")
ኰላኰለ፡ ደራደረ ("ተካከለ")
ኰላፊ፡ የኰለፈ/የሚኰልፍ ("በካይ ")
ኰልባ ቋሬ፡ በአፍኣ፡ በውስጥ፡ ፪፡ መልክ፡ ያለው፡ የዱሮ፡ ካባ፡ ባለሰንበር። ቋሬን፡ እይ።
ኰልባ፡ ከለከለ፡
ኰልባ የጐራዴ፡ የቢላዋ፡ እጀታ። ዋንጫው፡ የጋሻ፡ እንደ፡ ተባለ፡ ቢላዋውም፡ የጐ ራዴ፡ ይባላል፡ ይኸውም፡ ባለኰልባው፡ ነው። ኰልባ ከጐሽ፡ ቀንድ፡ የተበጀ፡ ሎቲና፡ ቀለበት
ኰልኝ፡ የዘንጋዳ ስም ("ቀይ ማሽላ ሚመስል ዘንጋዳ ")
ኰልኳይ (ዮች) የኰለኰለ/የሚኰለ ኵል ("ደርዳሪ ግብረ በላ ")
ኰሎፎ፡ የበርበሬ ስም ("በርበሬ ")
ኮመር (ሖመር) ባንድነት የፈላ ጨው ("ባሩድና ድኝ ጥቂት እንቆቆ ያለበት የንሓስ የመዳብ የብር ጌጥና ዕቃ መንከሪያ ማሳመሪያ ወርቅም ሲነከርበት ያገነዋል ያደምቀዋል ኮመርና ሖመር አንድ ስም ነው ኰላን አስተውል እንቆቆ በሖመር ፈንታ የገባ ነው ")
ኮመር፡ ኮምቶ
ኰመሸሸ (ከምሰሰ) አሳፈረ ("ሰቀ ጠጠ ")
ኰመተረ (መተረ) ፊቱን ቋጠረ ("ጨመደደ ጨመተረ ")
ኰመተረ፡ ከነበ
ኰመኰመ፡ እሸትንና የተክል ፍሬን ዐኘከ ("በላ ተመገበ ብዙ መጠጥ ጠጣ አደመጠ ሰማ ነገርን ቀመቀመን እይ ")
ኮመጠጠ (ሖመጠጠ) ተቈጣ ("ሸመ ጠረ እንደ ኰሽምና እንደ ቅሞ ፍሬ ኾነ እንጀራው ጠላው ማንኛውም መጠጥ መጠን ተመልከት ጨው ሲበዛ ይኮመጥጣል ኮመጠጠ የሕዝብ ሖመጠጠ የካህናት አናጋ ገር ነው ")
ኮመጠጥ፡ ኮምጣጣ ("የኮመጠጠ የሚ ኮመጥጥ ሖምጣጣ ሳማ ቅቤ ዐይብ ")
ኮማ፡ የንጨት ስም ("ጭራሽ የማያፈራ ")
ኰምሶ፡ የልብስ ስም ("የኰምሶ ቡልኮ ")
ኰምሶ፡ ያገር ስም ("በኦሮ ቤት በሲዳሞ በኩል ያለ ወረዳ በኰምሶ የነበሩ ዐዋቆች ለሞተ ሰው ጋሻ ጦር የያዘ ሐውልት ከደንጊያ እየቀረጹ በመቃብሩ ላይ ያቆማሉ ")
ኮምበል፡ ፍሬው የሚበላ ዛፍ
ኰምታራ፡ የተኰማተረ ("ጨምታራ ምዳዳ ")
ኰምታሬ፡ የኰምታራ ዐይነት ("በጣም የከረረ የቤት የባሕር ድር ሸማው እያደር የሚያጥር ")
ኮምቶ፡ የዛፍ ስፍራ
ኰምኳሚ፡ የኰመኰመ/የሚኰመም ("በዪ ጠጪ ጣት ")
ኮምጣጤ፡ የኮምጣጣ ዐይነት ("ብዙ ጊዜ የኖረ የማርና የወይን ጠጅ በግእዝ ብሕእ መፂፅ ይባላል ዐዞ ከልን እይ ")
ኰሰሰ፡ ኰሰተረ
ኰሠሠ፬ ቀጠነ፡ ኰሰሰ
ኰስኳሳ፡ ዝኒ ከማሁ ("ዝተት ሳማ ኰስኳሴ የኰስኳሳ ወገን አባ ኰስኳሲት የምትኰሰኵስ ፮፻፹፭ መኰስኰስ መሻከር መወጋጋት መቈ ስቈስ ማዥጐርጐር ኵስኵስት (ቶች) ኵዝ) ጡት ያለው የሸክላ ዕቃ ዝንጕርጕር እጅ መታጠቢያ ሰን ") (መክ. ፲፪፡ )
ኮሶ (ከዊስ ኮሰ) የዛፍ ስም ("በወይናደጋ የሚበቅል ዕንጨት ኮሶ ያሠኘው ሆድ መነቅነቁና መበጥበጡ ነው ኮሶ (ሶበርት) መራራ የኮሶ ፍሬ ሰዎች በጠጡት ጊዜ በሆዳቸው ውስጥ ያለውን ትል እየገደለ የሚያወጣ መድኀኒት ኮሶ ሸያጭ እንዲሉ ")
ኰረመተ፡ እግሩን ዐጠፈ ("ሰውነቱን ጨበጠ ኰርማች የኰረመተ የሚኰረምት ዐጣፊ ጨባጭ መኰርመት ማጠፍ መጨበጥ መኰርመቻ ማጠፊያ መጨበጫ ኰረማመተ ጨባበጠ መኰረማመት መጨባበጥ አስኰረመተ አሳጠፈ አስጨበጠ ተኰረመተ ታጠፈ ተጨበጠ ዐዘነ ኵርምት የተኰረመተ የተጨበጠ ኵርምት አለ ዕጥፍ ጭብጥ አለ ተኰራመተ ተኰረማመተ ተጣ ጠፈ ተጨባበጠ ኵርምትምት የተኰረማመተ የተጨ ባበጠ ኵርምትምት አለ ዕጥፍጥፍ ጭብጥብጥ አለ መኰራመት መኰረማመት መተጣጠፍ መጨባበጥ መኰራመቻ ታላቅ ሐዘን ዐጪርና ጠባብ መኝታ አኰራመተ አኰረማመተ አስተጣጠፈ አጨባበጠ ማኰራመት ማኰረማመት ማጨባበጥ ዳግመኛም ተኰራመተና አኰራመተ በተደራጊነትና ባድራጊነት ቢፈቱ ተኰረማ መተና ኣኰረማመተ ተደራራጊና አደራራጊ ይኾናሉ ኰርምት ዕጠፍ ጨብጥ የኰርምት (የኰርማች) ሴት - ባጠገቡ ተኝታ እያለች ሳይፈልጋት (ሳይነካት) ")
ኰረማሽ፡ በቡልጋ ክፍል ያለ ተራራ
ኰረረ) ኰረተ
ኰረብታ (ኰረፍታ) ጕባ ("ቍል ልታ ከተራራ የሚያንስ የምድር ዕንብርት ኵርቢት የትንባኾ መጠጫ ውዥሞውም ቅሉም ቃሊሙም ባንድነት ")
ኰረኰረ፡ አማሪትን መታ
ኰረኰረ፡ ከረመ
ኰረዳ (ዶች) ባል ያገባች ሴት ("ዐፍለኛ ወሲፍ ")
ኰረጃ፡ እየተጣጠፈ ባንድነት የታሰረ ብዙ ቈዳ ("ርጥብ ያይዶለ ደረቅ ጥቅል ")
ኰረጆ (ዎች) ማኅደር ("አኩፋዳ ከረጢት ከነት ከተንቤን የተበጀ የጠንቋይ የሌ ባሻይ የረኛ ኰረጆ እንዲሉ በጋልኛ ግን ቀልቀሎ ማለት ነው ")
ኮረጠ፡ አፍን ፈጀ ("ሖረጠ (ከረጠጠ) አንከረጠጠ ነፋ አንቀበደደ በተገብሮነትም ይፈታል እንክርጥ እንክርጣጭ ያንከረጠጠ የተንከረጠጠ እንቅብድ ማንከርጠጥ መንፋት ማንቀብደድ ተንከረጠጠ ተነፋ ተንቀበደደ ከረጠጥ ከርጣጣ የተንከረጠጠ ቀበደድ ቀብዳዳ ")
ኰረፈፈ) ከረረ
ኰራ (ኰሪዕ) መኵራት
ኰራ (ኰርዐ) ታበየ/ታጀረ/ተቈነነ/ተጓደደ/ተኰፋነነ ("ሰውን በንቀት ዐይን አየ እኔን ማን ያኸለኛል አለ ") (ሶፎ. ፪፡ )
ኰራ፡ ራስን በዘንግ መታ ቈረመ
ኰራ፡ ተንቋጠጠ ቤቱ
ኰራ አለ፡ ኵራት ዠመረ
ኮራ፡ የቀበሌ ስም ("በደብረ ሊባኖስ ቈላ ያለ ገጠር ትምሩኝ እንደኾን ልምጣ በግንቦት ኮራ ገዳም ያሉት ተክለ ሃይማኖት (ታቦት ዘፋኝ) ኮራ በግእዝ ጋን ጥዋ የውሃ መጠራቀሚያ ስለ ኾነ ይኸም አጥቢያ በገ ደሉ ጣቢያ ውስጥ ስላለው ጠበል ኮራ ተባለ ኾራን እይ ")
ኰራ፡ ያገር ስም ("በመራቤቴ ውስጥ ያለ ተራራ የተንቋጠጠ የተንጠራራ ኰራየወልዱ ልጅ ሞረት የጥዱ ልጅ እንዲል ዘር ቈጣሪ ")
ኮበ፡ ተጠነጠነ፡ ተደወረ፡ ተጠቀለለ፡ ፈትሉ፡ ገመዱ።
ኰበለለ፡ ከበረ
ኰበለለ፡ ወደ መጣበት ወይም ወደ ሌላ ስፍራ ተሰርቆ ኼደ ("ሮጠ ጋለበ ሸሸ ፈረጠጠ ካለበት ከነበረበት ጠፋ ታጣ ይህ ቃል የሚባለው ለወንድና ለሴት ልጅ ለከብትም ነው ላዋቂ አይነገርም ካህናት ግን ላዋቂም ይናገሩታል") (ኤር. ፴፱፡ ፬፡ ዮና. ፩፡ )
ኰበተ፡ እንደ ኵበት ኾነ ("ደረቀ")
ኰበኰበ/ጐበጐበ/ቈበቈበ) አኰ በኰበ ("ዱብ ዱብ መር መር አለ ተንደረደረ ወደ ሰማይ ለመብረር ለመውጣት ለማረግ ቈበቈበንና (ሶመሶመ) እይ ሳያኰበብ የበረረ የለም አኰሰኰበ ተንደረ ደረ ተብሎ በተገብሮነትመፈታቱ (ኰበኰበ) ስላልተለመደ ነው ")
ኮባ ("ዎች") ሙሽራው የተሸበለለ ላንፋው ርስ በርሱ የተቃቀፈ የተጠቀለለ ቅጠል የእንሰትና የሙዝ ዐይነት።
ኰብላይ (ዮች) የኰበለለ/የሚኰበልል (ዘፍ. ፬፡ ፲፪)
ኰብላይነት፡ ኰብላይ መኾን
ኰብሻም፡ ባለኰብሽ ("ዝኆን እግር ደንብን እይ ደነባ")
ኰብሽ (ሲሕ) የእግር ዕብጠት ("ከማን አንሼ ከጫማ እስከ ጕልበት የሚያድ በለብል ክባስ የሚያስመስል በሽታ ፈረንጆች ዝኆናዊ (ኤሌፋንቲያዚስ) ይሉታል ")
ኮተለከ፡ ኮተሊክ ኾነ ("ኮተሊክነት ኮተሊክ መኾን ኮትልኳል ኮተሊክ ኾኗል ኮትልኳል ኅብር ዐማርኛ ከተለፈ ") (ከለፈ)
ኰተኰተ/(ከተለ)
ኮቲባ/ኰተኰተ
ኮነ (ከዊን ኮነ) ኾነ ("ተደረገ ከወ ነንና ከነወነን እይ ")
ኰነሰ (ከነሰ) አለበሰ ("ሸለመ አስ ጌጠ ")
ኰነሰ (ኰነተረ) ጌጠ
ኰነተረ) አሽኰነተረ፡ አስጌጠ አሳመረ
ኰነተሸ፡ በጠሰ ("ቈረጠ አሳጠረ ")
ኰነነ (ኰንኖ ኰነነ) ገዛ ("ፈረደ ቀጣ ቅጣት ሰጠ ጐዳ በነፍስ በሥጋ ግእዝ የምድርንና የሰማይን ፍርድ ያስረዳል ዐማርኛ ግን የነፍስን ብቻ ያሳያል (ተረት) ሞቱ በቀረና በውል በኰነኝ ")
ኰናኝ (ኞች) የኰነነ/የሚኰንን ("እግዜር ፍራ ")
ኮንሶን (ከነሰ) መደበኛ የፈረንጅ ፊደል ኣለዋየል የሚነገር ("እኛ ግእዝ ከምንለው ፊደል ጋራ ይገጥማል ")
ኮንበል የዛፍ ስም፡ ኮምበል
ኰንበራም፡ ኰንበር ያለው ("ባለኰን በር ")
ኰንበራፍ (ኰንበር አፍ) ከንፈረ ወፍራም ሰው
ኰንበር፡ ደንዳና ከንፈር ("ሰንበርየሚ በር ")
ኰንታ፡ በከፋ አጠገብ በኩሎ ክፍል ያለ አገር ("ነገዱም ኰንታ ይባላል ዐጀምን እይ ")
ኰንኰለት፡ ጠጠራም መሬት ("ወጣ ገባ ኰንኳማ ላይኛውና ታችኛው የፊት ጥርሱ ተሰብሮ ያጠረ ዘሩ ኰመኰመ ነው በትግሪኛ ኰምኳም ይባላል ")
ኮከበ ባሕር፡ መርከበኞች የሚመለከቱት የሰሜን ኮከብ ("(ድብ)")
ኮከበ ባሕር፡ በኮከብ ዐይነት የተፈጠረ የባሕር ውስጥ ተንቀሳቃሽ
ኮከበ ብርሃን፡ አጥቢያ ኮከብ (ራእ. ፪፡ ፳፰፡ ፳፪፡ ፲፯)
ኮከበ ነጠላ፡ ዕድለ ቢስ ርባና ቢስ
ኮከበኛ (ኮከባዊ) ኮከብን የሚያስተ ውል የሚያይ
ኮከባቸው ገጠመ፡ ተፋቀሩ ("ተኳዃ ወለዱ ከበዱ ዐብረው ኖሩ አረጁ ")
ኮከብ (ቦች) የብርሃን የመብራት ስም ("የአየር ፈርጥ ሌሊት በሰማይ እንዳሸዋ ፍስስ ብሎ የሚታይ የጠፈር ፋና ከግዜር በቀር ቍጥሩን የሚያውቀው የሌለ ") (መዝ. ፻፵፯፡ )
ኮከብ ቈጠረ) ያስጠንቋይንና የናቱን ስም ፊደል ገጥሞ ባ፲፪ እየገደፈ ይቈጥርና ካ፲፪ቱ ኮከቦች ፩ዱን ላስጠንቋይ ዐደለ ሰጠ
ኮከብ ቈጣሪ (ዎች) ኮከበኛ " በሰ ማይ ያለውን ኮከብ የሚቈጥር ስም ስሙን የሚጽፍ አንዱ ኮከብ ሲወጣ ረኃብ መቅሠፍት ጦርነት ዕልቂት ይኾናል ሌላው ደግሞ ሲታይ ጥጋብ ጤና ሰላም ይመጣል እያለ የሚናገር ፈላስፋ ")
ኮከብ ቈጣሪ፡ ከመስከረም እስከ ነሐሴ አንዳንድ ወር የሚመግቡትን ፲፪ቱን ኮከቦች ባ፬ መደብ ላ፬ቱ ባሕርያት አካፍሎ ዐመልን አሰድን ቀውስን ለእሳት ("ሰውርን ሰንቡላን ጀዲን ለመሬት ገውዝን ሚዛንን ደለይን ለነፋስ ሸርጣንን ዐቅራብን ኩትን ለውሃ ይሰጥና የባልንና የሚስትን ገና ሳያጋቡ የስማቸውን ፊደል ቈጥሮ ባ፲፪ እየገ ደፈ ከዚህ በላይ ከተነገሩት ኮከቦች አዱን ለወንዱ ሌላውን ለሴቷ ዐድሎ ቸው ገጥማልና አልሚና ለሚ ስለ ኾኑ ይጋቡ ኮከባቸው ተቃራኒ ነውና አጥፊና ጠፊ ናቸው አይጋቡ እያለ የሚጠነቍል የምድር ዐዋቂ መለኛ አሳች አታላይ ያተራ የእከይ ጐተራ ")
ኮከብ፡ ኬክሮስ
ኮከብ፡ ክፉና በጎ ዕድል ("ወይም ሀብት")
ኮከብ፡ የሽልማት ስም ("በኮከብ አምሳል - ከንሓስ የተሠራ ሽልማት ላገለገለ ወታዶር ከመንግሥት የሚሰጥ ባላ፩ ባለ፪ ባለ ኮከብ እንዲሉ እነዚሁም ምክትል የ፫ አዛዥ የ፻ አለቃ ሻምበል ናቸው ኒሻን ሲኾን ለጦር አለቆችና ለመኳንንት ለወይዛዝር ለሌሎችም ባለማዕርጎች በያይነቱ ይሸ ለማል ይኸውም ከብርና ከወርቅ የተበጀ ነው ")
ኰካ (ኰኵሓዊ) ጭንጫማ ስፍራ ተራራ ባንኮበር በኩል ያለ
ኮክ (ኮክህ) የተክል ስም ("ፍሬው እየተጋጠ የሚበላ ተክል ጥጥር ውስጠ ጭንጫ ሌላም እሾኸ ያለው የባሕር ኮክ አለ በግእዝ ኆኅ ይባላል ")
ኰክ፡ የተክል ስም ("፡ኮክ ")
ኮክሃዊ) የኮክ/ኮክኛ ("እንደ ኮክ የሚጠጥር ኮክ የሚያኸል ማለት ነው ")
ኮኮ) (ኮከወ) እንኮኮ ("ጫንቃ ላይ ማድረግ (ከወከወ) እይ የዚህ ዘር ነው (ኮኮ) ቦዝ አንቀጽ ይመስላል ")
ኰኰኒያም፡ ኰኰኔ ያለው ("ባለኰኰኔ")
ኰኰኔ (ኰኰናዊ) የኰኰን ዐይነ ትና ወገን ("ዘረምቦ ")
ኰኰኔ፡ ቍንጪም ወፍ
ኰኰኔ፡ ያውራ ዶሮና የኰኰን
ኰኰን (ትግ፡ ኵክናይ/አውራ ዶሮ) ኵኵሉ ማለት የዠመረ ዶሮ
ኰኰዝ፡ ፈረንጆች ከባሕር የሚያወ ጡት የንጨት ቅቤ ("ምግብ - የሚኾን ")
ኰኳ፡ (ላዕለ ኰኵሕ ገደፈ በአለት ላይ ጣለ ")
ኰኳ፡ በደንጊያ ግንባርን መታ
ኰኳ፡ ባሪያ ሼጠ
ኰዜ፡ የምንጣፍ ስም ("ዥግርግር ምን ጣፍ ባለዘርፍ ")
ኰየሰ፡ ዐፈር ከምድር ውስጥ እያወጣ ከመረ ቈለለ ጕባ አስመሰለ
ኰየሰ፡ ኰኳ
ኰይራ፡ የነገድና ያገር ስም ("በኦሮ ቤት ያለ መኻል ግንባሩን ቍልቍል የሚ ፈቃ ሕዝብ ")
ኰደብ፡ የሰንበሌጥ ዐይነት ሣር ("ዣም ")
ኰደደ፡ ዐረሰ/ጦመ፡ ሖደደ
ኮዳ (ዕብ፡ ካድ፡ ጥዋ፡ መስቴ) የዘማች/የመንገደኛ ውሃ መያዣ ከቈርቈሮ የተሠራ
ኰድኳጅ፡ የኰደኰደ/የሚኰደድ
ኰፈሌ፡ የኰፈል ዐይነት ("ቀላል")
ኰፈል፡ እንደ ሬት/ላንፋ የቀለለ ደረቅ ዕንጨት
ኰፈል፡ ከፈፈ
ኰፈሰ (ከበሰ) ውዳሴ ከንቱ ሰብ' ካበ
ኰፈሰ፡ መየደ ("አበጠረ አጐፈረ ( ለጌ ግጥም) ራሷን በሚዶ ኰፍሳ ኰፍሳረ ልትገድለኝ ነው ልቤን ልሳ ልሳ ኰፋሽ የኰፈሰ የሚኰፍስ አጐፋ መኰፈስ ማመስገን ማበጠር መኰፈሻ ማመስገኛ ማበጠሪያ አፍ ሚዶ ")
ኰፈተረ፡ አንድነት ጠቀለለ ("ጠመዘዘ በጠ የሰበዝ ")
ኰፈኰፈ) ኰፈፈ፡ አኰፈኰፈ ("ተነሣ ሊላጥ ቀረበ የመሬት የገላ ሮጠ ")
ኰፈኰፍ፡ ኰፍኳፋ ("የተንኰፈኰፈ የሚንኰፈኰፍ ቍጡ ኵርፍተኛ ")
ኰፈፈ) አንኳፈፈ፡ ኣንካፈፈ ("ተንኳፈፈ ተንካፈፈ ሰፈፈ ብሎ ንኳፈፈ እንዲል ባለቅኔ ")
ኮፈፈ) ኰፈሰ
ኮፈፍታ፡ አለርሾ የተጋገረ እንጀራ ዐፍለኛ
ኰፊር፡ ጥንታዊ ደሴትና ከተማ ("ባጢ ምኒልክ መንግሥት ደጃች አስፋው ዳርጌና ቀኛዝማች መኰንን ወልደ ገብሬል አስገብረውታል ይባላል ዛሬም ሉክ ይሉታል አለቃ ታየ ግን ኰፊር የተባለ ኦፊር ነው ይላሉ ኦፊር የሚገኘው በእስያ ውስጥ ነው ")
ኰፍናና፡ የተኰፋነነ/የሚኰፋነን ("ኵሩ ዐውቆ ጌታ ኰፍናኔ የኰፍናና ዐይነትና ወገን መኰፋነን በልብስ መኵራት መኰፋነኛ መኵሪያ ")
ኰፍኰፍ አለ፡ ሩጭ ሩጭ አለ
አለ፡ አለ ("ድምጥ ሰጠ አለ ወለል አለ ሰማዩ ብሎ ጠርቷል ")
ኰርኳ አለ (የብሰ ነፀወ) ፈጽሞ ደረቀ ("ንቅልቅል አለ ኰረኳን ተመልከት ")
ኳለ (ኵሕለ) ቅንድብን በኵል ቀባ አስጌጠ
ኳች፡ (ኰዓቲ) የኳተ ("የሚነት ፋሪ ቈፋሪ መኳት መፋር መቈፈር ክት/የተከተተ ከተተ ክቾደረቅ፡ ከቸቸ ኮቴ፡ ሰኰና፡ ኰተኰተ ኮት ") (ክታን)
ኳንክ፡ ሥጋዊ ተሬ ዝርዝር ("ወይም ዱልዱም የተባት ምልክት በላዩ እንዝልዝል ቍንያለበት ")
ኳንክ፡ ባንገቱ ላይ ያለ የተባት ዶሮ እንጥልጥል ("ቍንጮውን የሚመስል ")
ኳንክ፡ ያውራ ዶሮ ቍንጮ ("ኰኰኔ ዱልዱም ወይም ዝርዝር ")
ኳንኳ፡ ታንኳ ("ፍልኳ")
ኳንኳ ከነፈ
ኳንኳ፡ ከነፈ
ኳንኳ፡ ያሞራ ስም ("ዋነተኛ አሞራ ይመስላል ")
ኳክ አለ፡ ጮኸ ("አትንኩኝ አለ ዶሮው ")
ኳክ፡ የዶሮ ድምጥ
ኳኳ አለ፡ ተንኳኳ ("ቋቋ አለ")
ኳኳ አደረገ፡ አንኳኳ
ኳኳ) (ትግ፡ ኳሕኵሐ/ቃሕቅሐ ጐድጐደ) አንኳኳ ("በር'መታ እንቋቋ አደረቀ ")
ኳኳታ፡ መንኳኳት
ኳኳቴ (ቋቋቴ) ሲነኩት የሚንኳኳ የቤት ዕቃ ("ቅልን የመሰለ ")
ኳኳቴ፡ ሲያርሱትኳኳ የሚል ሥሥ ("(ግርግራ) መሬት ")
ኳኳቴ፡ የሚንኳኳ ("(ኳኳ)")
ኳይ (ኰሓሊ) የኳለ/የሚኵ
ኳደሬ፡ ተወራጅ ሹም ("ጭቃ ሹምን ቱኪን የመሰለ ማዕርገ ታናሽ ገባርን እያ ዘዘ ሥራ የሚያሠራ እንግዳን ምሪት የሚመራ ለፋፊ (ተረት) ኳደሬ በንጉሥ መበ ለት በቄስ (መቅናት አይችሉም)")
 

 
ኸኝ፡ ("ከኒ") ተመልሰሽ ኸን ተመ ልከት
ኸኝ፡ ኾነ፡
ኹለተኛ ("ኞች") ተከታይ ምክትል ጡት አስጣይ ታናሽ ወንድም ።ስምዖን ለሮቤል ኹለተኛ ነው
ኹለተኛ፡ ተወራጅ፡ ተጨማሪ ኹለተኛ ቄስ ኹለተኛ ዲያቆን።
ኹለተኛ፡ የተራና የማዕርግ ቍጥር፡ የስምና የግብር ቅጽል፡ ኹለተኛ ቍጥር ኹለ ተኛ ማዕርግ ኹለተኛ ደረጃ።
ኹለተኛ፡ ዳግመኛ፡ ሌላ። ኹለተኛ እቤቴ እንዲህ ያለ ሰው ይዘኸ አትምጣ። ባለተክሊልን ሴት ኹለተኛ ወንድ አይቀርባትም ።በአኃዝ ሲጻፍ ፪ኛ ይላል
ኹለተኛው፡ የጊዜ በቂ፡ ዳግመኛው። እከሌ እቤታችን መጥቶ ሲጠይቀን ኹለተኛው ነው
ኹለተኛይቱ፡ ሌላይቱ፡ ዳግመኛይቱ።
ኹለታቸው ("ክልኤሆሙ") እነዚያ ሰዎች ወይም ሌሎች ፍጥረቶች ኹለተኞች፡ የመዠመሪያዎች ተከታዮች ("፩ዜና. ፲፩፡ ፳፩")
ኹለት ልብ) አመንቺ፡ ወላዋይ፡ ("መዝ. ፲፪፡ ")
ኹለት ሰንበት) ፲፬ ቀን ("ሳምንትን" እይ)
ኹለት ሳምንት) ዐሥራምስት (፲፭) ቀን።
ኹለት ኹለት፡ የሕፃን ርምጃ ቍጥር ጊዜ ባለ
ኹለት ፈርጅ) ነጠላ
ኹለትምላስ፡ ሐሰትና እውነት ደባላቂ፡ ቋንቋ ዐዋቂ ።ባ፩ ራስ ምላስ እን ዲሉ።
ኹለትነት፡ ኹለት መኾን ።ኹለት አፍ፡ ጠመንዣ ሰው።
ኹለትያ፡ ኹለት መቶ ድር።
ኹለትዮ፡ ኹለትነት ያለው ውስጠ፡ ብዙ
ኹለትዮሽ፡ ዝኒ ከማሁ
ኹለቶ፡ መንታ፡ ዕጥፍ፡ ድርብ።
ኹለቶች፡ መንቶች፡ ዐይንና ዦሮን ጡትን እጅን ክንፍን እግርን የመሰሉ ነገሮች
ኹለዬ ("(ኵልሄ) ኹለግዜ ዘወትር በየቀኑ ኹለመና ") (ኵለንታ)
ኹሉን ቻለ ("አገ ማሪ አካታች ያካተተ የሚያካትት አጫ ማሪ አካቶ አጫምሮ አካቶ ንኡስ አገባብ ጭራሽ ፈጽሞ ማካታት ማጋባት ማጫመር ከቶ አግብቶ - ጨምሮ ጨርሶ ከቶ ንኡስ ኣገባብ ዝኒ ከማሁ ለአ ካቶ ከቶ ምንም ቢኾን ይህን ነገር አላደርገውም ") (ኤር. ፳፫፡ ፵፡ ዮሐ. ፩፡ ፲፰)
ኹልት፡ የተኾለተ፡ ኹለት የኾነ የተ
ኹነታ/ኹናቴ/ኹኔታ ("(ክዋኔ) ተፈጥሮ አካል መልክ ቁመና አኳዃን ጠባይ ዐመል ሐሳብ ሥራ ይህ ሰው ኹኔታው አይታወቅም ኹነኛ ጠቃሚ ወዳጅ ተሰማሚ ሰው ይኹን ዕሺ በጄ ይደረግ አይኹን አይደረግ አይሠራ ኾኖ ተደርጎ ተሠርቶ ኾኖም አያውቅ ባንድ ከተማ ንጉሥ ባ፩ ዐልጋ ዐራስ ባ፩ ራስ ምላስ ኹን ተቀመጥ እዚህ ኹን እንዲሉ አኹን ንኡስ አገባብ የተዠመረ የተያዘ ጊዜ ደቂቃ ባማካይነት በመነ ሻነት ሲሰማሙት ኣኹን ባኹን ካኹን አኹን ይላል አኹን ለታ ") ("አኹን ለት")
ኾለተ፡ ኹለት አደረገ፡ ኹለት አለ
ኾነ፡ ("ኮነ") በጀ፡ ሰላ፡ ቀና፡ ረባ፡ ጠቀመ ፈየደ ተሰማማ። ይህ ልብስ ምንም ሰውን ደስ ባያሠኝ ለኔ ኾኖኛል። ይኾንልኛል ብዬ ጐሽ ጠመድኹ፡ ባይኾንልኝፈትቼ ለቀቅኹ።
ኾነ፡ ሰነበተ፡ ከረመ። ደኅና ኹን።
ኾነ፡ ባሕርዩን ሳይለቅ ሌላ መልክና አካል ገዛ ።አምላክ ሰው ኾነ፡ ሰው አምላክ ኾነ
ኾነ፡ ተለወጠ፡ ዐይነቱ፡ ጭገሬታው ጠፋ የሎጥ ሚስት የጨው ዐምድ ኾነች ደግ ኾነ ክፉ ኾነ ቢል የጠባይን መለወጥ ያሳያል
ኾነ፡ ተቀመጠ፡ ቈየ፡ ዘገየ፡ ኖረ፡ ("ዮሐ. ፲፬፡ ") ።እስከ ዛሬ ድረስ ያልጠየቅኸን የት ኾነኸ ነው
ኾነ፡ ተወለደ፡ ረባ፡ በዛ፡("ዘፍ. ፴፪፡ ")
ኾነ፡ ተደረገ፡ ተነካ። እከሌ ምን ኾነና ሞተ። የዚህ ሰው ራሱ ምን ኾነ። የኾነ ኾኖ ነገሩ በምን ዐለቀ።
ኾነ ተገባ። በኾነ ባልኾነ ከሰው አትጣላ
ኾነ ተገኘ ።የኾነውን ያኸል ላክልኝ።
ኾነ፡ ተጨበጠ፡ ተወደደ፤እኸል ነፍስ .
ኾነ፡ ተፈጠረ፡ ነበረ። እንዳልኾነ ኾነ፡ እንዲሉ
ኾነ፡ ወረደ፡ መጣ፡ ("ኤር. ፩፡ ") ።የኾነው ይኹን፡ ከዚህ በፊት የተደረገው የመጣው መከራ ይደረግ፡ ይምጣ ።ጠላት ገፍቶ ባጠቃ ጊዜ እንዲህ ይባላል ።ኾነ ብሎ፡ ዐስቦ ዐውቆ ወዶ ።ከዚ ህም በቀር ኾነ እየተመላለስ በንግግር ውስጥ ካገባብ ጋራ ይነገራል። በደን መካከል ስትኼድ ነብር የመጣ እንደ ኾነ ምን ትኾናለኸ። ሰውእንዳይኾን የለምና የቀረኹ እንደኾን እንድትጠይቀኝ ይኹን። ዕውሩ ላሜኅ ደንጊያ ወርውሮ የገደለው ሰው ይኾናል፡ ቢኾን ባይኾን ምን ተዳበጧት የመጣኸ እንደኾን ታገኘኛለኸ ።እከሌ ሰዎች ሲጣሉ የሸሸው ምስክር እንዳይኾን ይኾናል ።ሲኾን አንተ ና፡ ሳይኾን ሰው ላክ። አይኾንም እንጂ ከኾነማ ከመጋዞ፡ ላል ጕልማ። ኀላፊውን ትንቢት አንቀጽ ሲያስቀር፡ ይመጣል ኾነ ይኼዳል ኾነ ይላል ፣ፍችውም ነበረ ነው፡
ኾነ፡ ደረሰ፡ ተፈጸመ። እኔ ያልኹት ባይኾን ከምላሴ ጠጕር ይነቀል እንዲሉ።
ኾደደ ("ዐረሰ ጦመ ኾደደ ኻያ/ካያ ") (ከላ)
ዃላ፡ ጊዜና ስፍራ፡ ኋላ ("ኹለት ") (ክልኤት)
ዃኝ ("ኞች") የኾነ የሚኾን፡ ረቢ

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ