ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ሠ ፡ ፲፭ኛ ፊደል በግእዝ ኣልፍ ቤት በአበገደ
(በፊደልነት ስሙ ሠውት አኃዝ ሲኾን ሠ—፰ ይባላል
- ጻፎች ግን ስሙን ንጉሡ ሠ ይሉታል
- "ሸን" እይ) ። 
ሠለሰ (ሠልሶ፣ ሠለሰ) ፡ ሦስት አደረገ ። 
ሠለሰ፡ ሦስተኛ ዐረሰ፣ ቀሰቀሰ፣ አለሰለሰ፣
ዐየመ ። 
ሠለሰ፡ ቅድስት ሥላሴን አመሰገነ
(ሦስት ጊዜ ቅዱስ አለ) ። 
ሠለስት፡ የቀን ሦስተኛ ሰዓት ። 
ሠለስት፡ የዜማ ስም (ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ" ብሎ የሚዠምር ዜማ - ምስጢሩ ጌታችን በዚህ ሰዓት እጲላጦስ ፊት ቁሞ የሞት ፍርድ እንደ ተፈረደበት ያስረዳል ።)
ሠለቀ —አለዘበ—ሠለቀ ። 
ሠለቀ) ፡ ተሣለቀ (አላገጠ፣ አፌዘ፣ ዘበተ - ፪ዜና፡ ፴፮፥፲፮፡ ኢሳ፡ ፷፮፥፬ - ተደራራጊ ሲኾን ባድራጊነት መፈታቱን አስተውል) ። 
ሠለቀጠ፡ ዋጠ —ሰለቀጠ ። 
ሠለጠ (ሠልጦ፣ ሠለጠ) ፡ ሠለጠነ ። 
ሠለጠ፡ ሾለ፣ ሰላ፣ ሾጠጠ ። 
ሠለጠነ፡ አለባበስና አነጋገር አሳመረ
(ሰበቀለ ከባላገርነት ራቀ ፲ሥልጣንና ዕውቀት አገኘ ባለያ ኾነ ማንኛውንም ነገር መሥራት ቻለ) ። 
ሠለጠነ፡ ዐየለ፣ በረታ
(በዛ፣ አባተ፣ አሸነፈ፣ ጌተየ፣ ሰፈነ፣ በላይ ኾነ - ዘፍ፡ ፩፥፲፮፡ ኢሳ፡
፲፬፥ ፭፡ ሰቈ፡ ፭፥፲፰፡ ሮሜ፡ ፭፥ ፲፱፣ ፲፯
- "ገደል ባለበት አገር ዝንጀሮ ይሠለጥናል ።) ። 
ሠላሳ፡ ሦስት ዐሥር (በአኃዝ ሲጻፍ ü ይባላል) ። 
ሠላሳ ፈሪ፡ ኻያ ዘጠኝ (፳፱) ሠላሳ ሲሞላ አንድ ቍጥር የጐደለው ። 
ሠላሽ (ሾች) ፡ የሠለሰ፣ የሚሠልስ
(አመስጋኝ - "ሠላሽ ቀዳሽ" እንዲሉ)
። 
ሠላጢ፡ የሠለጠ፣ የሾለ፣ የሾጠጠ (በግ እዝም የሠለጠነ ተብሎ ይፈታል ።)
ሠላጢን (ኖች) ፡ ከቀጪኔ የሚበልጥ ጦር ያሣ መውጊያ
(ኢዮ፡ ፵፩፥፳፩ - ሠላጢን ባለሥልጣንን ያሳያል) ። 
ሠላጤ (ዎች) ፡ የሠላጢ ዐይነት ሕፅን ግልገል ወሽመጥ (የጥብቆ የሱሪ) ። 
ሠላጤ፡ ሹል፣ ስል፣ ሾጣጣ (እንቆቅልኸ) - ትንሽ ወጠጤ ቀንደ ሠላጤ - (የባሕር ሠላጤ) - ልሳነ ባሕር - የዓደን የፋርስ)
። 
ሠልስት፡ ከነግ ወዲያ (ነግ ሠልስትአትበል ቶሎ ና) ። 
ሠልስትና፡ ከትላንት ወዲያ (ና ምእላድ ነው" - "ትላንትናን" እይ) ። 
ሠልጣና፡ የሠለጠነ (ዐዋቂ) ። 
ሠልጣኝ፡ የሚሠለጥን ። 
ሠመረ (ሠምረ) ፡ ወደደ፣ ፈቀደ፣ ዐቀፈ (ግእዝ) ። 
ሠመረ —በጀ—ሰመረ ። 
ሠመር፡ በወገብ ላይ የተጠመጠመ ኹለት እጅ ። 
ሠመር ገባ፡ ተያዘ፣ ተሸነፈ፣ ተገዛ ። 
ሠመር ገጠመ፡ በትንንቅ ጊዜ ወገብን ዐነቀ፣ ያዘ (ግብግብን" እይ - "ገበገበ) ። 
ሠማ (ሠምዐ፣ ረስነ) ፡ ሞቀ፣ ጋለ፣ ጋመ
(ቀለጠ፣ ፈሰሰ - ነገር ግን በልማድ ምክንያት በሳት ሰ ይጻፋል)
። 
ሠማ፡ አደመጠ (ሰማ) ። 
ሠም (ሞች) (ሠምዕ) ፡ የማር ሰፈፍ ግግር ልጥልጥ (የሚቀልጥ - ኹለተኛ ስሙ ከዳ ይባላል
- "ጐመጭን" አስተውል) ። 
ሠም ረገፍ፡ ከሠሙ ተለይቶ በወርቁ ብቻ የሚነገር ቅኔ ። 
ሠም፡ የብሉይ ምሳሌ (ፊተኛ ነገር) ። 
ሠምና ወርቅ፡ ሠም ከወርቅ ጋራ ባንድነት ። 
ሠምና ወርቅ፡ ብሉይና ሐዲስ ። 
ሠምና ወርቅ፡ የቅኔ ስም (ዐይነተኛ ምሳሌ - ባለቤቱ ኹለት ሲኾን ባንድ አንቀጽ
- ማሰሪያ - የሚነገር ቅኔ - በሠም መደብነት የፈሰሰ ወርቅ የሠሙን ቅርጽ ነሥቶ እንዲገኝ ኋለኛው ሐዲሱ ቃል ፊተኛውን ብሉዩን መስሎ ይነገራል ማለት ነው - ዕብ፡ ፱፥፩-፳፰) ። 
ሠምና ፈትል፡ ሠም ከፈትል ጋራ ባንድነት (ጧፍ ፋና) ። 
ሠምና ፈትል፡ ፍጹም ኅብረት ስም ምነት ያላቸው ሰዎች (ባልና ሚስት)
። 
ሠሠተ፡ ነፈገ፣ ቤሰ፣ ቀቀተ፣ ጮቀ (ነ) ። 
ሠሡ፡ ያ ሠሥ (የርሱ ሠሥ) ። 
ሠሢታ፡ የሠሠተች (የምትሠሥት) ። 
ሠሣ፡ ዕንጨት—ሰሳ ። 
ሠሣች፡ ሥሡ (መስጠት የማይወድ)
። 
ሠሥ (ሦች) ፡ የዱር አንስሳ የፍየል ዐይነት (በገደልና በተራራ ላይ እየዘለለ የሚወረወር
- አውሬ ይበላኛል ብሎ ለሕይወቱ ስለሚሣሣ ሥጋው ቀይ ሽንኵርት ይመስላል! ተባቱም እንስቱም ሠሥ ይባላል - "ሠሥና ድ ኵላ" እንዲሉ)
። 
ሠሥማ፡ የሠሥ ዐይነት (ሠሥ የሚመ ስል ፍየል) ። 
ሠሥቴ፡ ሠሣች (የሠሣች ወገን)
። 
ሠሧ፡ ያች ሠሥ (የርሷ ሠሥ) ። 
ሠረቀ (ሠሪቅ፣ ሠረቀ) ፡ ወጣ፣ ብቅ አለ (ጨረቃው ፀሓዩ - "ሠረቀና ሰረቀ በግእዝ ልዩዎች ሲኾኑ ባማርኛ ይተባበራሉ ። ሌባው በዛ ቢተው ይተው ባይተው ግን ጀንበር በሠረቀ ቍጥር አፈርሳታ ማውጣት አንችልም (ጐንደሮች) - በዛና ቢተው ሌቦች ናቸው)
። 
ሠረቀ፡ ባተ፣ ገባ፣ ተዠመረ ። 
ሠረቀ፡ የሰው ገንዘብ ደብቆ ወሰደ—ሰረቀ ። 
ሠረበ (ሠሪብ፣ ሠረበ) ፡ ማገ አለ ልክ ጠጣ ደምን (ባላገር ግን ሥጋው ደሙን) ። 
ሠረገ (ሠረመ) ፡ ወደ ውስጥ ገባ (ውስጥ ለውስጥ ኼደ - "ያዋሽ ውሃ ዐውሳ ሲደርስ ይሠርጋል - ይህ ልጅ ዐይኑ ሠርጓል ምን አገኘው" - "ሠረገላን" እይ) ። 
ሠረገበ፡ ጠጣ፣ ጨለጠ
(በ ተቀጽላ) ። 
ሠረጐደ፡ ሰበረ፣ አዘበጠ፣ አጐደጐደ፣ አ ጐደለ
(ምድርን ራስን) ። 
ሠረጸ (ትግ) ፡ ገባ፣ ተረዳ፣ ዘለቀ (ይህ ልጅ ትምርት ሠርጾታል ።) ። 
ሠሪ (ዎች) (ሠራዒ) ፡ የሠራ፣ የሚ ሠራ (ወሳኝ ደንጋጊ አስገኚ - ዕብ፡ ፲፩፥፲
- (ተረት) - ሥራ ለሠሪው እሾኸ ላጣሪው - "ቤተ ሠሪ ነገረ ሠሪ ራሰ ሠሪ" እንዲሉ - (፩ ሠሪ) የቅዱስ ዲዮስቆሮስ እምነት - (፪ ሠሪ) የማኅበረ ኬልቄዶን ስሕተት) ። 
ሠሪታ፡ የሠራች (ዐሻሚ ቈናኝ)
። 
ሠራ (ሠርዐ) ፡ ወስነ፣ ደነገገ፣ ደነባ
(ሕግ አቆመ - "ሥራት ሠራ" እንዲሉ) ። 
ሠራ፡ መራ (አሰፈረ የጦር ሰራዊትን ባገር ላይ) ። 
ሠራ፡ ሥራት አስተማረ (ሥራ ቅጣ እ ንዲሉ) ። 
ሠራ፡ አደረገ፣ ፈጠረ
(ካለመኖር ወደ መኖር አስገኘ አመጣ - ግብር እምግብር አበጀ አዘጋጀ አወጣ ማንኛውንም ሥራ - (ብረት ሠራ) ቀጠቀጠ፣ ጨፈለቀ፣ ቀበቀበ - (ቤት ሠራ) ዐነጠ፣ ገነባ፣ ማገረ፣ ከደነ - (ገበታ ሠራ) ዘረጋ፣ እንጀራ ጣለ፣ አቀረበ
- (ግፍ ሠራ) ዐመፀ፣ በደለ ሰውን - (ወጥ ሠራ) ቀቀለ፣ አበሰለ
- (ወንጀል ሠራ) ቋንዣ ቈረጠ፣ ቤት አቃጠለ - (ኀጢኣት ሠራ) ሕግን ተላለፈ፣ ሰረቀ፣ አመነዘረ - (ጠጕር ሠራ) ጐነጐነ፣ ዐሸመ፣ ቈነነ - (ጦር ሠራ) ሰራዊት ሰበሰበ፣ አሰለፈ - (ካሳ ሠራ) ቈረጠ (ይህን ያኸል ትከፍላለኸ አለ) - (መግል ሠራ) ያዘ፣ ዐቈረ - (ነገር ሠራ) ዐደመ፣ ቋጠረ፣ አሳበቀ፣ አዋሸከ፣
አጣላ - (ለሰው ይምሰል ሠራ) ግብዝ ኾነ - "ሸመነን" ተመልከት) ። 
ሠራሽ፡ የሠራው፣ ያበጀው (ረጋ ሠራሽ ሰው ሠራሽ" እንዲሉ
- የቅርብ ሴት አንቀጽ ቅጽልነት በሩቅ ወንድ መፈታቱን አስተውል) ። 
ሠራተኛ (ኞች) ፡ የሠራት ወገን (ሕግ አውጪ - ሥራ ወዳድ ትጉህ ጠይብ ባለጅ ቀጥቃጭ አንጥረኛ - "ወርቅ ሠራተኛ ብር ሠራተኛ" እንዲሉ
- ዳግመኛም ሠራ ተኛ ተብሎ ኹለት አንቀጽ ይኾናል - "ተኛን" ተመልከት)
። 
ሠራተኛነት፡ ሠራተኛ መኾን (ትጉ ህነት)
። 
ሠራት (ሠራዕት) ፡ የሠሩ፣ የሚሠሩ ሠሪዎች ። 
ሠራጊ፡ የሚሠርግ፣ የሚገባ
(ገቢ) ። 
ሠራጺ፡ የመንፈስ ቅዱስ ኣካል
(የሠረጸ የሚሠርጽ) ። 
ሠርቅ፡ የወር፣ የሌሊት፣ የቀን መባቻ መዠመሪያ ። 
ሠርቶ፡ አድርጎ፣ አዘጋጅቶ፣ አብጅቶ ። 
ሠርቶ አፍራሽ፡ በሥልጣኑ በቃሉ ፈጥሮ የሚያሳልፍ እንዳልነበረ የሚያደርግ እግዜር (ሰውን በደዌ የሚያፈርስ በመቃብር የሚያበሰብስ
- "ስለ ሠርቶ አፍራሹ"
እንዲል ለማኝ) ። 
ሠርቶ አፍራሽ፡ ያረጀውን ቤት ለማደስ ለማስፋት ለማሳመር የሚንድ ዐናጢ ' ቤተ ሠሪ ። 
ሠርየሞፈር ቂጥ፡ ሰረረ ። 
ሠርጸ ድንግል፡ በ፲፭፻፶፮ ዓ፡ ም፡ የነገሠ የሐበሻ ንጉሥ ስም (የድንግል
(እመቤታችን) ቡቃያ ማለት ነው) ። 
ሠርጽ፡ ቡቃያ፣ ብቋያ ። 
ሠቀሠቀ (ሠቅሠቀ) ፡ ወጋጋ፣ በሳሳ (ለመለየት ለማላቀቅ ለማስጌጥ - "ሸቀሸቀን" እይ - የዚህ ዘር ነው) ። 
ሠቀቀ (ሠቂቅ፣ ሠቀ - ትግ፡ ሠቀቀ ሣቀየ) ፡ ጠላ፣ ሰለቸ፣ ሰቀጠጠ (ሆ ቅን" እይ - የዚህ ዘር ነው) ። 
ሠቀቀናም (ሞች) ፡ ሠቀቀን ያለበት የበዛበት
(ባለሠቀቀን ችጋራም ስግብግብ)
። 
ሠቀቀን፡ በልቶ አለመጥገብ (አሲድን"
እይ) ። 
ሠቀቀን፡ ያገኙትን ያዩትን ማጣት
(ከዚህ የተነሣ ምር ሐዘን ማዘን ማልቀስ) ። 
ሠቀጠ (ቀሠጠ) ፡ አዋሸከ ' ዋሸ (ሠቀጠ"
ያማርኛ "ቀሠጠ" የግእዝ ነው) ። 
ሠቃ፡ አፋፍ (ጐዣም) ። 
ሠቃጢ (ቀሣጢ) ፡ የሠቀጠ (የነገር ሌባ ዋሾ) ። 
ሠቅ (ሠቂቅ፣ ሠቀ፣ ሠቅ፣ ማቅ) ፡ ውስጡ ማቅ ላዩ ግምጃ ኹኖ የተሰፋ የካህናት መታጠቂያ (በግእዝ ቅናት ይባላል - ዛሬም የከተማ ሰዎች የሐር የወርቅ ቀበቶ ይሉታል) ። 
ሠቅሠቅ (ቆች) ፡ የተበሳሳ ዕንጨት (በሰገነት ሰበሰብ ላይ ያለ ጌጠኛ ሥራ ዐይነ ርግብ
- ሕዝ፡ ፵፥፱፣ ፲፬፣ ፴፯) ። 
ሠቅሣቂ፡ የሠቀሠቀ፣ የሚሠቀሥቅ ። 
ሠቅጥ (ሠጥቅ) ፡ ከላድ የፍየል መልክ ። 
ሠቅጥማ፡ ከላድማ መልከ ቀበሮ
(መቀነትማ ፍየል) ። 
ሠቆች፡ መታጠቂያዎች ። 
ሠበጠረ (ሠበጠ) ፡ አበጀ፣ ሠራ (ቅር ጫትን ጐታን) ። 
ሠቢ (ሠባሒ) ፡ የሚሠባ ፍሪዳ የ ሚኾን ። 
ሠባ (ሠብሐ) ፡ ወፈረ፣ ደነደነ፣ ደለበ
(ጮመየ ጮማ ኾነ ጥጥ መሰለ ቀለጠ - ኢሳ፡ ፳፭፥፮ - (ተረት)
- አህያ ሠባ ካልታረደ ምን ረባ - (ልቡ ሠባ) - አልታዘዝ አለ ሰው ናቀ) ። 
ሠተረ፡ ዘረጋ—ሰተረ ። 
ሠነቀ (ሠኒቅ፣ ሠነቀ) ፡ ቈላ፣ ፈጨ፣ ጋገረ፣ አበሰለ (ሥንቅ አበጀ አዘጋጀ) ። 
ሠነበጠ (ሠበጠ) ፡ ሠነጠረ፣ ለበጠ
(ሠነተረ ከረከረ ከፈለ)
ተረር ። 
ሠነተረ (ሠተረ) ፡ በጣ፣ ሠነጠቀ፣ ቀደደ
(የታረደውን ከብት ለመግፈፍ ብልት ለማውጣት - "ሰነዘረን" ተመልከት)
። 
ሠነታተረ፡ ቀዳደደ ። 
ሠነገ፡ አፍንጫን በሳ—ሰነገ ። 
ሠነጋ፡ የፈረስን ቍላ አወጣ
-ሰ ነጋ ። 
ሠነጠረ (ሠጸረ) ፡ ለበጠ ' ሠነበጠ ። 
ሠነጠቀ (ሠጠቀ) ፡ ሰበረ፣ አነበበ፣ ተረተረ፣ ቀደደ፣ ከፈለ (በቁመት ፈለጠ መገዘ ተረረ
- "ኣቡየ ጻድቁ ገደል እንዳክርማ የሚሠነጥቁ እንዳለ ታቦት ዘፋኝ) ታሪ ። 
ሠነጣጠቀ፡ ሰባበረ፣ ከፋፈለ ። መሠነጣጠቅ፡ መሰባበር፣ መከፋፈል ። 
ሠናቂ፡ የሠነቀ፣ የሚሠንቅ
(ጋጋሪ) ። 
ሠኔ (ሠነየ) ፡ የወር ስም (ዐሥረኛ ወር ከመስከረም - ትርጓሜውም ሠናዪ ሠናይ ማለት ነው - የርሻን መለስለስና የዘርን መዘራት ያሳያል
- (ተረት) - አላጋጭ ገበሬ በሠኔ ይሞታል - "ሠኔ ነግ በኔ" - ባ፲፱፻፶፮ ዓ፡ ም፡ ሠኔ ፩ ቀን ሰኞ የመኪና መንገድ በግራ፡ 
ሠኔ ሚካኤል (የሠኔ ሚካኤል) ፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የሚከብር የቅዱስ ሚካኤል በዓል ። 
ሠኔና ሰኞ፡ የመለኛ የጠንቋይ ፈሊጥ
(ሠኔ ሰኞ በባተ ቍጥር ማስፈራሪያ ኾኖ ይኖራል) ። 
ሠንበሌጥ፡ ሣር—ሰንበሌጥ ። 
ሠንባጭ፡ የሠነበጠ፣ የሚሠነብጥ
(ሠንጣሪ ለባጭ) ። 
ሠንተራ፡ ደንጊያ ዐቃፊ የወንጭፍ ቈዳ ። 
ሠንታሪ፡ የሠነተረ፣ የሚሠነትር
(በጪ) ። 
ሠንገር ሠንገር አለ፡ ግመልኛና ሰጐንኛ ሮጠ ። 
ሠንገሮ (ሠገረ) ፡ ረዥም ቀርፋፋ ሰው ። 
ሠንጠረዥ፡ የጨዋታ መሣሪያ -ሰ ንጠረዥ ። 
ሠንጣሪ (ዎች) ፡ የሠነጠረ፣ የሚሠን ጥር (ሣጠራ ሠሪ) ንበጥ ። 
ሠንጣራ፣ ሥንጣሪ፣ ሥንጥር፡ የተሠነጠረ
(ልባጭ ልብጥ - በግእዝ ሥጻር ይባ ላል - ሥንጥር አለ ተሠነጠረ - ተሠነጣጠረ በብዙ ወገን ማለት ነው) ። 
ሠንጣቂ፡ የሠነጠቀ፣ የሚሠነጥቅ
(ተር ታሪ) ። 
ሠንጣቃ ዕንጨት፡ ጭንቅ መከራ ጥብ (መውጫ ቀዳዳ የሌለው) ። 
ሠንጣቃ፡ የተሠነጠቀ ገደል መረሬ ። 
ሠንጥቆ፡ ተርትሮ፣ ከፍሎ (ተረት) - ባልነቃ ሠንጥቆ ባልዘነበ በርቆ) ። 
ሠኘ) ፡ ሠነጠቀ፡ በኩል መኾኑ ቀርቶ ካ፲፱፻፴፫ ዓ፡ ም፡ በፊት እንደ ነበረ በስተቀኝ ኾነ ። 
ሠኘ) (ሠነየ) ፡ አሠኘ (አስሠኘ) (አሠነየ)
፡ አስመለከተ፣ አሳሰበ፣ አሻ፣ አስፈለገ፣ አስወደደ (አናገረ አስባለ - (ዝም አሠኘ) አስረመመ)
። 
ሠከተ (ሥኅተ) ፡ ቀረበ፣ ስለፈ (ጸጥ ዕክም ብሎ ለቅልውጥ) ። 
ሠከት፡ የቀረበ፣ የሰለፈ ። ሠከቴ፡ የሠከት ወገንና ዐይነት (ሎፌ ቀላዋጭ)
። 
ሠክ —ሎፍ—ሠከተ ። 
ሠክ አለ፡ ሎፍ አለ (ተደቀነ)
። 
ሠዊ (ሠዋዒ) ፡ የሠዋ፣ የሚሠዋ
(ካህን ቃልቻ) ። 
ሠዋ (ሦዐ) ፡ ዐረደ፣ አወራረደ
(ጠ በሰ ' አጨሰ
- መሥዋዕት ወይም ቍርባን አቀረበ - ላምላክ - (ለጣዖት ጭዳ አለ) - መዝ፡ ፻፮፥፴፯)
። 
ሠውር፡ የኮከብ ስም (ሰውር)
። 
ሠውት፡ የፊደል ስም (ሠ - እሸት ማለት ነው) ። 
ሠየ (ትግ፡ ሠይአ ሻፈደ) ፡ ጐመዠ፣ ተቃረ፣ ጓጓ፣ ቋመጠ ። 
ሠየመ (ሤመ) ፡ ሾመ፣ አከበረ ። 
ሠየመ፡ ዐቀበ (ዐቃቢ ኾነ ፈጩ አዘጋጀ ሰፈረ መላ ለበመ በቤተ ክሲያን ምሥራቃዊ በር አደረገ አኖረ መገበሪያን - "ሰየመን" ተመልከት) ። 
ሠየምት፡ ከበላይ ተሹመው የበታቻቸውን የሚሾሙ ባላባቶች (ከትግሬ ሠየምት ከደንቢያ ከንተብት"
እንዲሉ) ። 
ሠየረ፣ ሤረ) ፡ አሤረ (ዐደረ፣ ዐደመ ' አሳደመ
' መከረ ' ዶለተ - የክፉ፣ የበጎ)
። 
ሠዪ፡ የሠየ፣ የሚሠይ
(ጐምዢ) ። 
ሠያሚ፡ ሿሚ (የሠየመ፣ የሚሠይም፣
ዐቃቢ ት) ። 
ሠይቷል፡ ጐምዥቷል፣ ተቅሯል ። 
ሠገረ (ሠፂር፣ ሠገረ) ፡ ዐለፈ፣ ኼደ፣ ተራመደ
(አካኼድ አሳመረ ተቀማጩን ሳይነቀንቅ እንደ እንዝርት ሾረ ሰለከ ተሽከረከረ
- ተፍለቀለቀ) ። 
ሠገራ (ዐረ) ፡ ያይነ ምድር ጕድጓድ (ዐዘቅተ ኵስሕ) ። 
ሠገገ፡ ረዘመ (ሠገገ) ። 
ሠጋሪ፡ የሚሠግር፣ የሚሽከረከር ። 
ሠጋር (ሮች) ፡ የሠገረ፣ የሚሠግር
( በቅሎ ስናር አህያ ፈረስ ግመል - ፩ነገ፡ ፬፥፳፰)
። 
ሠግር፡ የወር መባቻ ቀን (እሑድ የሳተው አንድ ቀን ዐልፎ ማግሰኞ ሲብት ሠግር ይባላል) ። 
ሠግር፡ ጳጕሜ በ፫ ዓመት ፭ ስትኾን የሚዘለለው ፮ኛ ቀን ። 
ሠጠቀ (ሠጢቅ፣ ሠጠቀ) ፡ ከፈለ (ሣጥቅ - ቆች - ቦይ የቅብቅብ መክ ተነተነ ' ገመሰ
' ማሳን) ። 
ሠጠጥ አለ፡ ተሠጠጠ ። 
ሠጠጥ አደረገ፡ ሠጠጠ ። 
ሠጣጭ (ሠጣጢ) ፡ የሠጠጠ፣ የሚሠጥ
(ቀዳጅ) ። 
ሠጥር (ሠጸረ) ፡ ያሣ ማጣበቂያ ሠንጣራ ሠንጣቃ ዕንጨት (ሠነጠረን"
እይ - ሠጥር ታናሽ ጐድን - ቀጪን ሠጥር እንዲሉ) ። 
ሡልጣን (ዐረ) ፡ ንጉሥ (በሕዝብ ላይ ሥልጣን ያለው)
። 
ሡሠኛ (ኞች) ፡ ልማደኛ (በመለኛ) ። 
ሡሢ፡ ባለቀለም መጠብር ነጠላ ። 
ሡሥ፡ የትንባኾ የሱና ፍላጎት መሻት ክፉልማድ ዐመል
(ዐይንን የሚጨፍንና የሚያዛጋ
- "ሐራራን" አስተውል) ። 
ሡካር፡ በቁሙ፡ ሱካር ። 
ሢሶ መሬት፡ ቀላድ ሲጣል ለባለምድር ባላባት ከ፫ ፩ የተሰጠ ። 
ሢሶ፡ ሦስተኛ እጅ (ዘኊ፡ ፲፭፥፮፣ ፯) ። 
ሢሶ ዕንጨት፡ ከሦስት አንዱ ክፍል ዕንጨት የኾነ ጠመንዣ መውዜር (ከወገቡ በላይ ዕንጨቱ ዐጪር ኹኖ ብረቱ ብቻ ይታ ያል) ። 
ሢሶ፡ ከሦስት አንድ—ሠለሰ ። 
ሢሶ ጠማጅ፣ ሢሶ ዐራሽ፡ ከሦስት አንድ ሊሰጥ ተዋውሎ የሰው መሬት የሚያርስ (ተጋዢ ተጠማኝ)
። 
ሢር (ሥርው) ፡ ከተለፋ የበግና የፍየል ሌጦ በቀጪኑ ተቀዶ የወጣ የበቅሎ የፈረስ የበሬ ዕቃ መስፊያ ያገልግል መለጐ ሚያ (ሢር ያሠኘው ከመነሻ እስከ መጨረሻ ከሥር እስከ ጫፍ መድረሱ ነው) ። 
ሢር (ሮች) ፡ የጠፍር ቅዳጅ (የጫማ ማዘቢያ መጥለፊያ - በግእዝ ቶታን ይባላል - ዮሐ፡ ፩፥፳፯)
። 
ሢር (ዐረ) ፡ ሥር ። 
ሢር፡ ያልተገመደ ክሥዳ ጭረት ። 
ሢርባ፡ ሚጥሚጣ (የበረሓ በርበሬ በላተኛውን ብዙ ውሃ የሚያስጠጣ እንደ ሣራብ የሚለበልብ) ። 
ሢርባን፡ ተመልከት ። 
ሢርጋ፡ እንገር ። 
ሢጥ፡ መጮኸ ። 
ሢጥ መጮኸ፡ ሠጠጠ
(ሠጢጥ፣ ሠጠጠ)
፡ በፍጥ ነት ቀደደ (ልብስን)
። 
ሢጥ ሢጥ አለ፡ ተጨነቀ ። 
ሢጥ አለ፡ ባጪር ድምፅ ጮኸ (ተረት) - ዐይጥ ወልዳ ወልዳ ዥራት ሲቀር ሢጥ አለች)
። 
ሢጥጥ ሢጥጥ አለ፡ መላልሶ ተን ሢያጠጠ ። 
ሢጥጥ አለ፡ ብረትኛ ጮኸ ። 
ሢጥጥታ፡ የስፌት አክርማና ስንደዶ ድምፅ (ሢጥጥ" ማለት
- ፱ኛውን ያ ተመልከት)
። 
ሣለ (ሠዐለ) ፡ ነደፈ፣ በገረ፣ መሰለ
(ሥዕል ምሳሌ አደረገ ነቀሰ የፈጣሪንና የፍጡርን መልክ በቀለም ገለጠ አሳየ - ሣለ ፈጠረ
- ኢሳ፡ ፵፱፥፭) ። 
ሳለ (እንዘ ሀሎ) ፡ ሳይሞት፣ ሳያልፍ
። (ተረት) ፡ "አባት ሳለ አጌጥ፡ ጀንበር ሳለ ሩጥ” ። 
ሣለ —ኡሁ ኡሁ አለ —ሣለ ። 
ሣልሳይ፡ ዘንድ አንቀጽ ። 
ሣልስ፡ ፫ኛ ፊደል ። (ኢ ሣልስ ቢ ሣልስ" እንዲል ተማሪ) ። 
ሣልስ ቅጽል) ፡ ነጋሪ ። 
ሣልስት፡ የች ፫ኛ ቀን ሦስት (ሠወስት)
ከኹለት ቀጥሎ ያለ መደበኛ ቍጥር ። 
ሣልስነት፡ ፫ኛነት ። 
ሣሢት፡ የቀበሌ ስም (በተጕለት ውስጥ ያለች የኪዳነ ምሕረት አጥቢያ ገለ) ። 
ሣሣ (ሠሥዐ) ፡ ሥሥ ኾነ፣ ረቀቀ፣ ቀ ጠነ (ኢሳ፡ ፵፥፲፱) ሣል ። 
ሣሣ (ሠሥዖ) ፡ መሣሣት ። 
ሣሣ፡ ሠሠተ (ምሳ፡ ፳፫፥፪) ። 
ሣሣ፡ ተራራቀ (የዘር) ። 
ሣሣ አለ፡ ሣሣ ። 
ሣሣ፡ ዐዘነ፣ ራራ (እከሌ ለልጁ ይሣ) ። 
ሣሣ አደረገ፡ አሣሣ ። 
ሣሣኹ፡ ሠሠትኹ (አየን" ተመልከት)
። 
ሣራም፡ ሣር በዝቶ የበቀለበት ስፍራ (ሣረ በል" - የቤት የዱር እንስሳ ወፍ ሣር ነጭቶ የሚበላ) ። 
ሣራብ፡ ሳማ (አለብላቢት - ግእዝ)
። 
ሣር (ሣዕር) ፡ በቁሙ (የመሬት ጠጕር ለእንስሳና ላውሬ ለወፍ ምግብ ለሰው ጥቅም የሚኾን - የጋዣ የገደል የመስክ የጠጅ) ። 
ሣቀ (ሠሐቀ) ፡ ፈገገ፣ ተንከተከተ
(ከሐዘን ከለቅሶ ራቀ - "አፍ ቂጡ ሣቀ" እንዲሉ - (ግጥም) - ክትክት ብላ ሣቀች ምድር ጥርስ አውጥታ አባተ ሲታሰር አብርሀ ሲፈታ - "ገበያ እንዴት ዋለ" ቢለው አንዱ ባንዱ ሲሥቅ) ። 
ሣቀ፡ ፈካ (ማሽላ ሲያር ይሥቃል ። በሐዘን መካከል ቢሣቅ ወዶን አይሥቁ ይባላል
- ወዶን ሰውየው አይሥቁ ጥርሶቹ - "ወደደ" ብለኸ "ወዶንን" ተመልከት) ። 
ሣቀየ (ሣቅዮ፣ ሣቀየ) ፡ አስጨነቀ (መከራ አሳየ አስቻለ - መዝ፡ ፵፬፥፪) ። 
ሣቂ (ሠሓቂ) ፡ የሣቀ፣ የሚሥቅ ። 
ሣቂ ገጣጣ ጥርሰ ጣይ ሞቴ ። 
ሣቂታ (ሠሓቂት) ፡ የሣቀች፣ የምት ሥቅ (ሣቅ የምታበዛ ሴት) ክት ። 
ሣቃዪ፡ የሣቀየ፣ የሚሣቅይ ። 
ሣቅ (ሥሒቅ) ፡ መሣቅ ። 
ሣቅ ሣቅ አለ፡ ፈገግ ፈገግ አለ (መላልሶ ሣቀ) ። 
ሣቅ ሥላቅ (ሠሐቅ ወሥላቅ) ፡ ሣቅና ሥላቅ (ሠለቀ)ን" እይ) ። 
ሣቅ አለ፡ በጥቂቱ ሣቀ ። 
ሣቅ፡ የፊት ፈገግታ (የደስታ ምል ክት) ። 
ሣንሣ፡ መሎጊያ—ሳንሳ ። 
ሣንቃ!፡ የበርመዝጊያ—ሳንቃ ። 
ሣይ (ዮች፣ ሠዓሊ) ፡ የሣለ፣ የሚ ሥል (በእጅ በመኪና - "ሥዕል ሣይ" እንዲሉ)
። 
ሣይንቴ (ሣይንታዊ) ፡ የሣይንት ሰው ። 
ሣይንት፡ ያገር ስም (በበጌምድር አቅ ራቢያ ያለ አገር - "ዐማራ ሣይንት"
እንዲሉ - ትርጓሜው ዘር ማለት ይመስላል
- ልጅን ሽንት እንዲሉ
- "ዐማራን" አስተውል) ሰው ። 
ሣይንቶች፡ የሣይንት ተወላጆች ። 
ሣጠራ፡ ከቀርክሓ፣ ከሸንበቆ የተበጀ ምንጣፍ (፪ኛ ስሙ አቴና ነው) ። 
ሣጥን (ሣጹን) ፡ ከንጨት፣ ከብረት፣ ከደንጊያ፣ ከወረቀት፣ ከቈዳ፣ ካረግ የተበጀ ሞላላ ዕቃ (ማንኛውንም ነገር ማስቀመ፵ ማኖሪያ
- የገንዘብ የልብስ የጌጥ የሬሳ ሣጥን እንዲሉ
- ሲበዛ ሣጥኖች ይላል
- (ቁም ሣጥን) ፡ ቁሞ የሚከፈት የቁም ሣጥን የቆመ ያልተጋደመ በውስጡ ከታች እስከ ላይ ዐልፎ ዐልፎ የዕቃ መሰደሪያ ዕርከን ያለውና የሌ ለው - (የወርቅ ሣጥን) ፡ ከወርቅ የተሠራ በወርቅ የተለበጠ የወርቅ ማስቀመጫ ማለት ነው) ። 
ሣጥን፡ ሰይጣን ። 
ሣጥን፡ በቁሙ ። 
ሤረኛ (ኞች) ፡ ዐድመኛ (ነገር ቋጣሪ)
። 
ሤረኛነት፡ ሤረኛ መኾን (ዐድመኛነት) ። 
ሤራ፡ ርጋታ፣ አማን፣ ደኅና፣ ጸጥታ፣ ፍቅር፣ ሰላም ። (እያሙ ሤራ" እንዲል - ባላገር ለውሻው ስም ሲያወጣ
- "እከሌ ግዳይ ቢያጣ ከሤራው ይገድላል" - "ባረከ" በግእዝ
"መረቀ ረገመ" ተብሎ እንዲፈታ ሤራም እንደ ርሱ ነው - "መረነ" ብለኸ
"መረንን" እይ) ። 
ሤራ ቈረጠ፡ ዐድማ አደረገ ' ጨረሰ
' ማለ ። 
ሤራ፡ ዐድማ፡ (ሠየረ፡ ሤረ) ። 
ሴራ፡
ዐድማ (ሠየረ፡
ሤረ) ። 
ሤራ፡ ዕድር፣ ዐድማ፣ ዱለት (ተረት) - ከምሳ የተለየ ደብተራ ያደርጋል ሤራ - በኦሮምኛ ግን ደንብ ውል ማለት ነው) ። 
ሤራ ኾነ፡ ተሤረ፣ ተዶለተ
(ጸጥ አለ፣ ረጋ አገሩ ሕዝቡ) ማለ ። 
ሤራ ጕዱ፡ ሰላመ ቢስ ¡ ቅን የማ ይዶልት ። 
ሥለሳ፡ ዕየማ ። 
ሥሉሴ፡ ሽሩባ ። 
ሥሉሴ፡ በብርና በወርቅ በንሓስ መደብ ላይ በ፫ በ፫ ረድፍ የተንጠለጠለ የበ ቅሎ፣ የግመል ዐንገት ጌጥ (ሥሥና ቀጪን አጫዋች ዐልቦ ዶቃ - መሳ፡ ፰፥፳፩ - "መረሸትን" ተመልከት)
። 
ሥሉሴ፡ ክብ የጸናጽል ሰሌዳ፲ ፪ ጊዜ ፫ ኹኖ የሚታይ ሿሿቴ ። 
ሥሉስ፡ ፫ ምስክር (ልማ በሥሉስ ጥፋ በሥሉስ" እንዲሉ)
። 
ሥሉስ፡ ፫ የገበጣ ጠጠር (ሥሉስ ባይርቀኝ" እንዲል ገበጣ ተጫዋች) ። 
ሥሉስ ቅዱስ፡ ሦስት የኾነ ቅዱስ
(በአካሉ ፫ ጊዜ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ የሚመሰገን አምላክ) ። 
ሥሉስ፡ በአካል ሦስትየኾነ አምላክ ። 
ሥሉጥ፡ ሥልጡን (የጠመመውን የሚያቀና የጐደለውን የሚመላ - ሥሉጥ የግእዝ ሥልጡን ያማርኛ ነው) ። 
ሥላሴ፡ በቅድስት ሥላሴ ስም የተቀረጸ ታቦት (ደብረ ብርሃን ሥላሴ ዐድዋ ሥ ላሴ" እንዲሉ - (የሞኝ ጥያቄ) - ሥላሴ ገዳም ታቦቱ ማነው)
እይ ። 
ሥላሴ፡ የቅኔ ስም (፩ኛ ቅኔ ዘሴን)
። 
ሥላሴ፡ የፈጣሪ አካል ሦስትነት
(ወይም ስም) ። 
ሥላሴዎች፡ የሥላሴ ካህናት (የሥላሴ መቅደስ አወዳሾች) ። 
ሥል (ሎች) (ሥዕል) ፡ በብራናና በወረቀት በደንጊያና በንጨት በብረት በሰው ገላ ላይ የተሣለ የተቀረጸ የተነቀሰ የሰውና የማንኛውም ፍጥረት መልክ ምሳሌ ምልክት ። 
ሥልሳ፡ ኹለት ሠላሳ (ስድስት ዐሥር ስሳ - ስድሳ)
። 
ሥልስ (ሞጻሕት) ፡ የወይን መጠጥ መሧዕት
(ስለ ክብረ አምላክ የሚረጭ የሚፈስ - ሥልስ ከ፫ ፩ የተጣለ ጠጅ ይመስላል) ። 
ሥልስ፡ ሦስት ዐይነት ኹኖ ባንድ ነት የተዘጋጀ (ያዋዜና የቅቤ የክትፎ ወጥ - ትግሬ ግን ሥልስ የሚለው በዘይትና በሽንኵርት የተሠራ የትማትም ወጥ ነው) ። 
ሥልስ ወጭት፡ የሥልስ መሥሪያ ድስት
(ወይም ማቅረቢያ ጣባ) ። 
ሥልስ፡ የተሠለሰ (ሦስት የኾነ)
። 
ሥልሶ፡ በ፫ ጣት ልክ የተደረዘ የሙ ነኵሴ ቆብ ። 
ሥልቅ፡ ያገር ስም (በግዳድ)
። 
ሥልጡን (ኖች) ፡ ዝኒ ከማሁ (ብልጥ ብልኅ ጮሌ ፈጣን ባለያ ፥ የከተማ ሰው ሥልጡንነት ሥልጠና)
። 
ሥልጢ፡ ከ፯ቱ የጕራጌ ባላባቶች አንዱ (አገሩም ነገዱም ሥልጢ ይባላል) ። 
ሥልጣኑ ተያዘ፡ እንዳይቀድስ ተከ ለከለ ። 
ሥልጣኔ፡ ሥልጠና (ሥልጥንና ሥልጡን መኾን ዕውቀት - (ክፉ ሥልጣኔ) ተንኰል የሰይጣን ሥራ ሰውን የሚጐዳና የሚያጠፋ) ። 
ሥልጣን (ኖች) ፡ መብት፣ ችሎት፣ ክህነት
(ቅስና ድቍና - (ሥጋዊ ሥልጣን) የንጉሥ - (መንፈሳዊ ሥልጣን) የጳጳስ) ። 
ሥልጣን ሰገድ፡ ያጤ ሱስንዮስ ስመ መንግሥት ። 
ሥሡ (ሥሡዕ) ፡ ንፉግ፣ ጩቅ ቢስ፣ ቅቅታም፣ ሥሥታም (የባልቴት ግጥም) - እኒህ ሥሡ ለዝናም ጌታ ውሃ ነሡ) ። 
ሥሥ (ሦች) ፡ የሣሣ (ብረ ሸሽከውፍረትና ከብዛት ከመቀራረብ የራቀ
- "ሥሥ እንጀራ ሥሥ ጠጕር" እንዲሉ)
። 
ሥሥ ቅልጥም፡ የኋላ እግር ከነቅባቱ (መቅንን" እይ - ቀና) ። 
ሥሥ ቅልጥም) ፡ የኋላ እግር ከጕልበት በታች ከነቅባቱ” ። መቅንን" ተመልከት” ። ወዶ የዋጡት ቅልጥም ከብርንዶ ይጥም" እንዲሉ
። 
ሥሥታም (ሞች) ፡ የሠሠተ፣ የሚሠሥት
(እጁን ቢሉት ጠብ የማይለው - ፩ቆሮ፡ ፮፥፲
- (ተረት) - ከሥሥታም አንድ ይወድቀው አንድ ያንቀው) ። 
ሥሥታምነት፡ ሥሥታም መኾን (ንፉግነት ቢስነት)
። 
ሥሥት (ሥሥዕት) ፡ ንፍገት ' ቅ ቅት (ማቴ፡ ፳፫፥፳፭፡ ማር፡
፯፥፳፪) ። 
ሥሥት፡ ተንቀሳቃሽ ።  
ሥረ ብዙ፡ ሥሩ ለጕንፋን ለሳል መድኀኒት የሚኾን ቅጠል ። 
ሥረ ነገር፡ የነገር ጥንት መነሻ ። 
ሥረ ወጥ፡ ያልተሰፋ ትት ጥልፍ
(መርፌና መቀስ ያልዞረበት ልብስ ቅጥል አልባ
- ሥሩ እስከ ጫፉ የወጣ - በግእዝ እል ታሕ ይባላል)
። 
ሥረ ገደል፡ በሺዋ ክፍል ያለ ቀበሌ ። 
ሥረት (ሥር) ፡ ጠባይ፣ ባሕርይ
(ተፈጥሮ ተገብሮ - የገላ ኹናቴ - ወይም በአካል ላይ የሚታይ ሥራ - በትግሪኛ ግን በዘር የሚወርድ በሽታ ይባላል) ። 
ሥረጌ (ጌ ሥርው) ፡ የሣርና የቅ ጠል ሥር ያለባት ምድር (የማንም ከብት ተሰብስቦ የሚውልበት ቀዬ ሜዳ ነው) ። 
ሥሩ ተቈጣ) ፡ ዐበጠ ተነፋ ።
ሥሪት፡ ምሪት (በባላገር ላይ የተሠራ የጦር ሰራዊት ጭፍራ) ። 
ሥሪት፡ ካያት - ከቅድም አያት ሲያ ያዝ የመጣ
(የገባር የግንደ በል የመስቀል መሬት
- "የመሬት ሥሪት" እንዲሉ)
። 
ሥራ (ግበር) ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (እከሌ ጌታኸ ያዘዘኸን ሥራ ሥራ) ። 
ሥራ መሪ) ፡ የሥራ ሹም (ሠራተኛን ሥራን ወደ ማወቅ ሥራውን ወደ ሠራተኛ የሚመራ ሥራ አስኪያጅ)
። 
ሥራ ቤት፡ የሥራ ቤት ማድ ቤት (ወንድና ሴት ባሪያ) ። 
ሥራ ያዘ፡ ረባ፣ ጠቀመ (ሥራም አይዝ አይረባም)
። 
ሥራ ያዘ፡ እሥራ ገባ ። 
ሥራ ጊዮርጊስ፡ ከካህናት በቀር ሕዝብ የማያከብረው የጊዮርጊስ በዓል (በጥር ፲፰ ቀን የሚውል)
። 
ሥራ፡ ግብር፣ ተግባር
(የጥበብ ዘዴ ውጤት
- "የጽፈት የሒሳብ ሥራ" እንዲሉ - የበዓል ተቃራኒ ውሃ ዋና ሰንጠረዥ በገና ፈረስ ግልቢያ ብረት ቅጥቀጣ ጽፈት ድጕሰት)
። 
ሥራ ፈታ፡ ተወ፣ ለቀቀ፣ ቦዘነ ። 
ሥራ ፈት (ቶች) (ፅሩዕ) ፡ ኣለ ሥራ የሚውል ሥራ የማይወድ ቀላዋጭ ዘዋሪ ። 
ሥራ ፈትነት፡ ሥራ ፈት መኾን
(ቦዘንተኝነት - "መራ" ብለኸ "መሪን"
እይ) ። 
ሥራ፡ ፍጥረተ ዓለም ። 
ሥራሥር፡ የሥር ሥር (ብዙ ዐይነት መድኀኒትና ምግብ የሚኾን የንጨት ያትክልት ሥር) ። 
ሥራተ ቢስ፡ ሥራተ መጥፎ ዳኛ (ሕገ ውጡ) ። 
ሥራተ ጌትነት፡ የጌትነት ክብር ማዕርግ
(ሥጋ መብላት ጠጅ መጠጣት) ። 
ሥራተኛ (ኞች) ፡ ሥራት አክባሪ (በሥራት ዐዳሪ) ። 
ሥራት (ሥርዐት) ፡ ንጹሕ ውሳኔ (የሕግና የትእዛዝ መጠበቂያ ደንብ)
። 
ሥራት ለበሰ፡ ዋስ ጠራ ' ተዳኘ ። 
ሥራት ልክ ነው፡ አይለወጥም ' አ ይቃወስም ። 
ሥራት፡ ሙሉ የበቅሎ ዕቃ (በቅሎ ከነሥራቷ እሰጥ" እንዲል ተጋች) ። 
ሥር (ሥሩዕ) ፡ የተሠራ፣ የተደረገ፣ የተደነባ (ውስን ድንግግ - (የቤት ሥር) - በቤት የተሠራ ልብስ ከገበያ ያልተገዛ የባሕር ፈ ትል ያልኾነ ሸማ - (ያጤ ሥር) - ዐጤ የሠሩት ሥራት ደንብ ውሳኔ) ። 
ሥር (ሮች) (ሠረወ፣ ሥርው) ፡ የፍጥረት የነገር ኹሉ መዠመሪያ መነሻ መ ወጠኛ (ወደ ታችና ወደ ላይ የሚያድግ
- "ነገር ከሥሩ ውሃ ከጥሩ" እንዲሉ
- የዛፍ ሥር የደም ሥር - "ሠረየ" ብለኸ
"ሥረይን" እይ - በምስጢር ከዚሀ ጋራ አንድ ነው) ። 
ሥር ሰደደ (ሠረወ) ፡ ወደ ታች አ ደገ ' ሥርን አረዘመ ። 
ሥር ሰደደ፡ ተደላደለ (ዘመድ ገዛ ወገን አበጀ ገንዘብ አበዛ - "ሢርን" አስተውል)
። 
ሥር ኵል፡ ነጭና ጥቍር የኵል ሥር ። 
ሥር ያዘ፡ እሥር ገባ (ሳያልቅ ቀረ ነገሩ ሥር ያዘ" እንዲሉ)
። 
ሥር፡ ግርጌ፣ ታችኛ ስፍራ፣ ጥግ (የገደል የተራራ ሥር" እንዲሉ) ። 
ሥር ጠምዛዥ፡ ክፉ ደብተራ አስ ማተኛ ሰው ገዳይ ። 
ሥርቻ፡ የግንብ የግድግዳ የዕቃ ሥር (የማይታይ ስፍራ)
። 
ሥርቻ፡ የግንብ ጥግ—ሥር ። 
ሥርዐተ ንግሥ፡ በዘውድ በዓል የሚደረግ ጸሎትና መቀባት የመሰለው ኹሉ ። 
ሥርግ ሥርግ አለ፡ ትርግ ትርግ (ርግብ ርግብ አለ" - "ተረገን" ተመልከት)
። 
ሥርግ፡ ዝኒ ከማሁ (የሠረገ የገባ - "ሥርግ አለ ግበት አለ) ። 
ሥርግርግ አለ፡ ተሥረገረገ ። 
ሥርግርግ፡ የተሥረገረገ
(የተዋጠ) ። 
ሥርጸት፡ መሥረጽ ። 
ሥቃይ፡ ጭንቅ፣ መከራ፣ ቅጣት፣ እስ ራት ' ክፉ ሕመም ። 
ሥቅሠቃ፡ የመሠቅሠቅ ሥራ ። 
ሥቅሥቃት፡ ቍርጥማት
(ዐጥንትን የሚወጋ የሚሠቀሥቅ በሽታ) ። 
ሥቅሥቅ አደረገ፡ ከሥር ከታች ያዘ ' ሠቀሠቀ ። 
ሥቅሥቅ፡ የተሠቀሠቀ (የተለየ) ። 
ሥቅሥቆ፡ በቅመም የተሠራ የሥጋ ክትፎ ወጥ (ከድስት ውስጥ በቢላዋና በማንካ ተሠቅሥቆ የሚወጣ) ። 
ሥቅሥቆሽ፡ ሥቅሠቃ ። 
ሥቅቅ አለ፡ ከልብ ዐዘነ፣ አለቀሰ ። 
ሥቅቅታ፡ ሥቅቅ ማለት (ዕጦት ዕፍረት ሐዘን ልቅሶ ሥቃይ) ። 
ሥባም (ሞች) ፡ ሥብ ያለው (ባለ ሥብ - መዝ፡ ፻፵፬፥፲፬) ለብ ። 
ሥባት (ሥብሐት) ፡ መሥባት (ሥብነት ጮማነት ወፍር ድንዳኔ - (ተረት)
- ካልታ ረደ አይታይ ሥባቱ ካልተናገረ አይታይ ብላቱ) ። 
ሥባት (ጐንደር) ፡ ቦዳ ' ቀልዝ ' አረዳ መሬት (ዘፍ፡ ፳፯፥፴፱፡ ኢሳ፡
፲፥ ፳፯፡ ሆሴ፡ ፲፪፥ ፲፩) ። 
ሥብ (ሥቡሕ) ፡ የሠባ (ድልብ ገች ሰንጋ - "ሥብ ሊያርዱ ጕፋያ ይነዱ) ። 
ሥብ (ሥብሕ) ፡ ጮማ (ቅልጥ ያለ ሥጋ ትርፍ)
። 
ሥብ፡ ሞራግልገል ' ሞራ (ዘሌ፡ ፫፥፫)
። 
ሥብነት፡ ሥብ መኾን ። 
ሥብጥር (ሥብጥርጥር) ፡ የተሠባጠረ (ዝንቅ ጣልቃ)
። 
ሥነ ሥርዐት፡ የሥርዐት ዐቅድ ኹኔታ ። 
ሥነ ስቅለት፡ የስቅለት መልክ (ሥዕለ ስቅለት) ። 
ሥነ ጥበብ፡ የጥበብ ዐይነት ። 
ሥነ ጸዳል፡ የብርሃን ውበት ። 
ሥነ ፍጥረት፡ የፍጥረት ዐይነት መልክ ። 
ሥነቃ፡ የመሠነቅ ሥራ (ጋገራ)
። 
ሥን (ሠነየ) ፡ መልክ፣ ውበት፣ ደም ግባት (ዐይነት - "አሥኔትን" እይ) ። 
ሥንቀ ነፍስ፡ ሰው ሊሞት በቀረበ ጊዜ የሚቀበለው ቍርባን ። ዳግመኛም ከጣረ ሞት በፊት የሚቀምሰው እንጀራ ፉት የሚለው ውሃ ሥንቀ ነፍስ ይባላል (መሰናበቻ የነፍስ ሥንቅ ማለት ነው) ። 
ሥንቀ ፈጅ፡ ሥንቅ ጨራሽ (ተረት)
- እኼድ ባይ ሥንቀ ፈጅ) ። 
ሥንቀን (ሥንቀነ፣ ሥንቅነ) ፡ ሥንቃችንን ሥንቃችን (ካመድ ጋራ የተቀላቀለ የ ትንባኾ ዱቄት
- የአፍንጫ ሥንቅ ማለት ነው - ኹለተኛ ስሙ ሱረት - "ጕርፎን" እይ) ። 
ስንቀን፡
ሱረት ሠነቀ ። 
ሥንቄ፡ የሰው ስም ። 
ሥንቅ (ቆች) ፡ የመንገደኛ መብል ምግብ መኖ ኅብስት ጭብጦ ቈሎ ዳቦ ቈሎ በሶ ድርቆሽ ጭኮ ሙልሙል ሽልጦ ሻሜት (የሚበላና የሚጠጣ መግዣ ገንዘብ - "ስ ሥንቅ ነው የመቤቴ" እንዲል ታቦት ዘፋኝ - ከነገረኛ ሰው ሥንቅ አይደባልቁም
- ሥንቅኸን ባህያ ዐመልኽን በጕያ - "ራዛ አንበጣን ሥንቃችን በልባችን አለው) ። 
ሥንቆ፡ የቅጠል ስም (በክረምት የሚ በቅል የሜዳ ቅጠል እየተቀቀለ የሚበላ የጐመን ዐይነት í ክረምታዊ ሥንቅ መኾኑን ያሳያል
- ሥንቆ በግእዝ ሥንቁን ማለት ነው) ። 
ሥንበጣ፡ ሥንጠራ፣ ልበጣ ። 
ሥንባጭ (ጮች) ፡ ሥንጣሪ ' ልባጭ ። 
ሥንብጥ (ጦች) ፡ የመሣ ፥ እኩሌታ ኹለተኛ ክፍል ። 
ሥንብጥ፡ የተሠነበጠ (ልብጥ) ። 
ሥንተራ፡ ሥንጠቃ፣ ቀደዳ
(የመሠን ተር ሥራ) ። 
ሥንትራት፡ ብጥታት
(የሥንጥቃት ዐ ይነት)
። 
ሥንትር፡ የተሠነተረ (ብጥ) ። 
ሥንትርትር፡ የተሠነታተረ (ባላገር ግን ሸነተረ ተሸነታተረ ይልና ሽንትርትር ይላል) ። 
ሥንጠራ፡ ልሰጣ (ሥንበጣ) ። 
ሥንጠቃ፡ ትርተራ (የመሠንጠቅ ሥራ) ። 
ሥንጣቂ፡ ንቃቃት (ኢሳ፡ ፪፥፲፱፣ ፳፩፡
፶፯፥፭) ። 
ሥንጣቂ፡ የሥንጥቅ ቅሬታ ትራፊ
(ማቴ፡ ፯፥፫፣ ፬፡ ፳፫፥፳፬) ። 
ሥንጥርጣሪ፣ ሥንጥርጥር፡ የተሠነጣ ጠረ ። 
ሥንጥቃት፡ ስብራት ትርትራት የመ ሠንጠቅ ኹናቴ ። 
ሥንጥቅ አለ፡ ስብር ትርትር አለ ። 
ሥንጥቅ ወፍ፡ ከፍተኛ ድምቢጥ (በግንባሯና በሰርኗ ላይ ቍልቍል ነጭ ያላት) ። 
ሥንጥቅ፡ ዝኒ ከማሁ ለሠንጣቃ
(ትክክል እኩሌታ ግማሽ
- "እከሌ የገዛው ማር ሥንጥቅ አተረፈው)
። 
ሥንጥቅጣቂ፡ ዐያሌ ሥንጣቂ ። 
ሥንጥቅጥቅ አለ፡ ተሠነጣጠቀ ። 
ሥንጥቅጥቅ፡ የተሠነጣጠቀ ግንብ፣ መሬት፣ ተረከዝ ። 
ሥንጭሮ (ትግ) ፡ ፈፋ ' ፈረፈር ። 
ሥዕለ ስቅለት፡ ጌታችን እንደ ተሰቀለ የሚያሳይ የመስቀል ሥዕል ። 
ሥየማ፡ ሰፈራ፣ ልበማ ። 
ሥየታ፡ ጕምዠታ ። 
ሥዩመ እግዚአብሔር፡ እግዜር የሾመው (ንጉሥ መኰንን ዳኛ) ልብም ። 
ሥዩም፡ የሰው ስም ። 
ሥዩም፡ የተሾመ (ሹም) ። 
ሥይማት፡ ልብማት (የመሠየም አኳ ዃን) ። 
ሥይም፡ የተሠየመ፣ የተመላ፣ የተለበመ ዃን ። 
ሥይት፡ የጤፍ ስም ። 
ሥጉያ፡ የሥጋ መደብር (ሥጋ መሸጫ - ይህ ቋንቋ በሐረርጌ ይነገራል) ። 
ሥጊሚጢ፡ የቅጠል ስም (በክረምት እንደ ሥንቆ እየተቀቀለ የሚበላ ቅጠል - ሥፂ በቁሙ ሚጢ መልሽ ማለት ነው) ። 
ሥጋ ለባሲ፡ የሰው ነፍስ ። 
ሥጋ ልደት (ልደተ ሥጋ) ፡ ዝም ድና ' ውልድና ። 
ሥጋ መልከኛ፡ መልከኛ ከገባር (የሚቀበለው ታላቅ ወይም አሰጅ)
። 
ሥጋ መልከኛ፡ የሥጋ ሹም ። (ደበ ረን" እይ) ። 
ሥጋ ማሪያም፡ ባሕታዊ እንደ ማተብ ባንገቱ የሚያደርገው (ባሕር ዐረብ የን ጽሕና ምሳሌ) ። 
ሥጋ በል፡ ሥጋ የሚበላ አውሬ
' አሞራ ' ሰው ። 
ሥጋ ቤት፡ ሥጋ የሚቀመጥበት ቤት ። 
ሥጋ ቤት፡ የሥጋ ሹምሥጋ ቤቶች፡ ጭፍሮች የሥጋ ቤት ሠራተኞች ። 
ሥጋ ተሥጋ፡ የባላገር ንግግር (ሥጋ ከሰውነት ጋራ ይሰማማል" ማለት ነው) ። 
ሥጋ ኾነ (ሥጋ ለበሰ) ፡ ሰው ኾነ (ዮሐ፡ ፩፥፲፬)
። 
ሥጋ ወደሙ፡ ቍርባን (ሥጋሁ ወደሙ ለዐማኑኤል) ካለው የመጣ ነው) ። 
ሥጋ ግብር (ግብረ ሥጋ) ፡ ሩካቤ (የወንድና የሴት መገናኘት) ። 
ሥጋ ፈሪ፡ ፍሪዳ በታረደ ጊዜ የሚንቀጠቀጥ የሹልዳ ሥጋ (ሠጋ" ማለት ከዚህ የወጣ ይመስላል)
። 
ሥጋማ (ጥካ) ፡ አካል ወፍራም ደንዳና ። 
ሥጋት፡ ፍራት ሠጋ ። 
ሥጋዊ (ውያን) ፡ ሥጋ ለባሽ (ዓለማዊ ሰው መንፈሳዊነት የሌለው ኣፍኣዊ) ። 
ሥጋዎች (ግእዝ ሥጋት) ፡ ብዙዎች የሥጋ ብልቶች
- ሙዳዎች ። 
ሥግሪያ፡ የሠጋር አካኼድ ። 
ሥግራ፡ የሕፃን ርምጃ (ድቅ ድቅ ድንኵል ድንል" ማለት - "አቱ ሥግራ ታቱ ሥግራ" እንዲሉ
- "ዝግራን" ተመልከት - ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ። 
ሥግና፣ ሥጋነት፣ ሥግነት፡ ሥጋ መኾን (ዝምድና) ። 
ሦስተኛ (ሦስተኛው፣ ሦስተኛዋ፣ ሦስተኛዪቱ) ፡ ተራ ቍጥር (ዳግመኛም ሦስተኛው ሦስተኛኸ" እያለ ጊዜን ያሳያል - "እከሌ እኛ ዘንድ ሲመጣ ሦስተኛው ነው) ። 
ሦስተኝት፡ ሦስተኛዪቱ ክፍል ። 
ሦስቲያ፡ ከሦስት አንድ (ሢሶ) ። 
ሦስት መለኮት፡ ከቢዘን የወጣ የመናፍቃን ባህል (ባጤ ምኒልክ መንግሥት የተወገዘ) ። 
ሦስት፡ በቁሙ—ሠለሰ ። 
ሦስት አደረገ፡ ሠለሰ (፫ ቍጥር ቈጠረ ከ፫ ከፈለ)
። 
ሦስት ፈርጅ) ፡ ጃኖ ዝቅዝቅ ፥ ድርብ” ። በፈርጅ በፈ ርጁ" ቢል፡ "በኩያ በኩያው ባምሳያ ባምሳ ያው" ማለት ነው ። ትግሬም ጋቢን
"ፈርጊ" ይለዋል ። 
ሦስትነታቸው፡ ሦስት መኾናቸው (የሥላሴ ፥ ሦስትነታቸው በአካልና በአካላዊ ግብር በስም ነው) ። 
ሦስትነት፡ ሦስት መኾን ። 
ሦስትያ፡ ሦስት መቶ ድር ። 
ሦስትዮሽ፡ ፯ ብስ ያለው ቀንበር ። 
ሦስትዮሽ፡ ከሦስት ገመድ የተሸረበ ጅራፍ ። 
ሦስቶ፡ በሰማይ ሦስት ኹነው የሚታዩ ኮከቦች ። 
ሦሪት፡ የምታምር ወፍ—ሶሪት ። 
ሦራ፡ መጐናጸፊያ—ሶራ ። 
ሦታ (ሠወየ) ፡ የሚያምር ወጣት ፎጠና ልጅ እግር (ሦታ ጐበዝ" እንዲሉ
- "ሶባን" እይ - ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ። 
 
No comments:
Post a Comment