Friday, June 6, 2025

፲፭ኛ ፊደል በግእዝ ኣልፍ ቤት በአበገደ (በፊደልነት ስሙ ሠውት አኃዝ ሲኾን ይባላል - ጻፎች ግን ስሙን ንጉሡ ይሉታል - "ሸን" እይ)

ሠለሰ (ሠልሶ፣ ሠለሰ) ሦስት አደረገ

ሠለሰ፡ ሦስተኛ ዐረሰ፣ ቀሰቀሰ፣ አለሰለሰ፣ ዐየመ

ሠለሰ፡ ቅድስት ሥላሴን አመሰገነ (ሦስት ጊዜ ቅዱስ አለ)

ሠለስት፡ የቀን ሦስተኛ ሰዓት ።

ሠለስት፡ የዜማ ስም (ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ" ብሎ የሚዠምር ዜማ - ምስጢሩ ጌታችን በዚህ ሰዓት እጲላጦስ ፊት ቁሞ የሞት ፍርድ እንደ ተፈረደበት ያስረዳል ።)

ሠለቀአለዘበሠለቀ

ሠለቀ) ተሣለቀ (አላገጠ፣ አፌዘ፣ ዘበተ - ፪ዜና፡ ፴፮፥፲፮፡ ኢሳ፡ ፷፮፥፬ - ተደራራጊ ሲኾን ባድራጊነት መፈታቱን አስተውል)

ሠለቀጠ፡ ዋጠሰለቀጠ ።

ሠለጠ (ሠልጦ፣ ሠለጠ) ሠለጠነ

ሠለጠ፡ ሾለ፣ ሰላ፣ ሾጠጠ ።

ሠለጠነ፡ አለባበስና አነጋገር አሳመረ (ሰበቀለ ከባላገርነት ራቀ ፲ሥልጣንና ዕውቀት አገኘ ባለያ ኾነ ማንኛውንም ነገር መሥራት ቻለ)

ሠለጠነ፡ ዐየለ፣ በረታ (በዛ፣ አባተ፣ አሸነፈ፣ ጌተየ፣ ሰፈነ፣ በላይ ኾነ - ዘፍ፡ ፩፥፲፮፡ ኢሳ፡ ፲፬፥ ፭፡ ሰቈ፡ ፭፥፲፰፡ ሮሜ፡ ፭፥ ፲፱፣ ፲፯ - "ገደል ባለበት አገር ዝንጀሮ ይሠለጥናል ።)

ሠላሳ፡ ሦስት ዐሥር (በአኃዝ ሲጻፍ ü ይባላል)

ሠላሳ ፈሪ፡ ኻያ ዘጠኝ (፳፱) ሠላሳ ሲሞላ አንድ ቍጥር የጐደለው

ሠላሽ (ሾች) የሠለሰ፣ የሚሠልስ (አመስጋኝ - "ሠላሽ ቀዳሽ" እንዲሉ)

ሠላጢ፡ የሠለጠ፣ የሾለ፣ የሾጠጠ (በግ እዝም የሠለጠነ ተብሎ ይፈታል ።)

ሠላጢን (ኖች) ከቀጪኔ የሚበልጥ ጦር ያሣ መውጊያ (ኢዮ፡ ፵፩፥፳፩ - ሠላጢን ባለሥልጣንን ያሳያል)

ሠላጤ (ዎች) የሠላጢ ዐይነት ሕፅን ግልገል ወሽመጥ (የጥብቆ የሱሪ)

ሠላጤ፡ ሹል፣ ስል፣ ሾጣጣ (እንቆቅልኸ) - ትንሽ ወጠጤ ቀንደ ሠላጤ - (የባሕር ሠላጤ) - ልሳነ ባሕር - የዓደን የፋርስ)

ሠልስት፡ ከነግ ወዲያ (ነግ ሠልስትአትበል ቶሎ )

ሠልስትና፡ ከትላንት ወዲያ ( ምእላድ ነው" - "ትላንትናን" እይ)

ሠልጣና፡ የሠለጠነ (ዐዋቂ)

ሠልጣኝ፡ የሚሠለጥን ።

ሠመረ (ሠምረ) ወደደ፣ ፈቀደ፣ ዐቀፈ (ግእዝ)

ሠመረበጀሰመረ

ሠመር፡ በወገብ ላይ የተጠመጠመ ኹለት እጅ

ሠመር ገባ፡ ተያዘ፣ ተሸነፈ፣ ተገዛ ።

ሠመር ገጠመ፡ በትንንቅ ጊዜ ወገብን ዐነቀ፣ ያዘ (ግብግብን" እይ - "ገበገበ)

ሠማ (ሠምዐ፣ ረስነ) ሞቀ፣ ጋለ፣ ጋመ (ቀለጠ፣ ፈሰሰ - ነገር ግን በልማድ ምክንያት በሳት ይጻፋል)

ሠማ፡ አደመጠ (ሰማ)

ሠም (ሞች) (ሠምዕ) የማር ሰፈፍ ግግር ልጥልጥ (የሚቀልጥ - ኹለተኛ ስሙ ከዳ ይባላል - "ጐመጭን" አስተውል)

ሠም ረገፍ፡ ከሠሙ ተለይቶ በወርቁ ብቻ የሚነገር ቅኔ

ሠም፡ የብሉይ ምሳሌ (ፊተኛ ነገር)

ሠምና ወርቅ፡ ሠም ከወርቅ ጋራ ባንድነት

ሠምና ወርቅ፡ ብሉይና ሐዲስ ።

ሠምና ወርቅ፡ የቅኔ ስም (ዐይነተኛ ምሳሌ - ባለቤቱ ኹለት ሲኾን ባንድ አንቀጽ - ማሰሪያ - የሚነገር ቅኔ - በሠም መደብነት የፈሰሰ ወርቅ የሠሙን ቅርጽ ነሥቶ እንዲገኝ ኋለኛው ሐዲሱ ቃል ፊተኛውን ብሉዩን መስሎ ይነገራል ማለት ነው - ዕብ፡ ፱፥፩-፳፰)

ሠምና ፈትል፡ ሠም ከፈትል ጋራ ባንድነት (ጧፍ ፋና)

ሠምና ፈትል፡ ፍጹም ኅብረት ስም ምነት ያላቸው ሰዎች (ባልና ሚስት)

ሠሠተ፡ ነፈገ፣ ቤሰ፣ ቀቀተ፣ ጮቀ ()

ሠሡ፡ ያ ሠሥ (የርሱ ሠሥ)

ሠሢታ፡ የሠሠተች (የምትሠሥት)

ሠሣ፡ ዕንጨትሰሳ

ሠሣች፡ ሥሡ (መስጠት የማይወድ)

ሠሥ (ሦች) የዱር አንስሳ የፍየል ዐይነት (በገደልና በተራራ ላይ እየዘለለ የሚወረወር - አውሬ ይበላኛል ብሎ ለሕይወቱ ስለሚሣሣ ሥጋው ቀይ ሽንኵርት ይመስላል! ተባቱም እንስቱም ሠሥ ይባላል - "ሠሥና ኵላ" እንዲሉ)

ሠሥማ፡ የሠሥ ዐይነት (ሠሥ የሚመ ስል ፍየል)

ሠሥቴ፡ ሠሣች (የሠሣች ወገን)

ሠሧ፡ ያች ሠሥ (የርሷ ሠሥ)

ሠረቀ (ሠሪቅ፣ ሠረቀ) ወጣ፣ ብቅ አለ (ጨረቃው ፀሓዩ - "ሠረቀና ሰረቀ በግእዝ ልዩዎች ሲኾኑ ባማርኛ ይተባበራሉ ። ሌባው በዛ ቢተው ይተው ባይተው ግን ጀንበር በሠረቀ ቍጥር አፈርሳታ ማውጣት አንችልም (ጐንደሮች) - በዛና ቢተው ሌቦች ናቸው)

ሠረቀ፡ ባተ፣ ገባ፣ ተዠመረ ።

ሠረቀ፡ የሰው ገንዘብ ደብቆ ወሰደሰረቀ

ሠረበ (ሠሪብ፣ ሠረበ) ማገ አለ ልክ ጠጣ ደምን (ባላገር ግን ሥጋው ደሙን)

ሠረገ (ሠረመ) ወደ ውስጥ ገባ (ውስጥ ለውስጥ ኼደ - "ያዋሽ ውሃ ዐውሳ ሲደርስ ይሠርጋል - ይህ ልጅ ዐይኑ ሠርጓል ምን አገኘው" - "ሠረገላን" እይ)

ሠረገበ፡ ጠጣ፣ ጨለጠ ( ተቀጽላ)

ሠረጐደ፡ ሰበረ፣ አዘበጠ፣ አጐደጐደ፣ አ ጐደለ (ምድርን ራስን)

ሠረጸ (ትግ) ገባ፣ ተረዳ፣ ዘለቀ (ይህ ልጅ ትምርት ሠርጾታል ።)

ሠሪ (ዎች) (ሠራዒ) የሠራ፣ የሚ ሠራ (ወሳኝ ደንጋጊ አስገኚ - ዕብ፡ ፲፩፥፲ - (ተረት) - ሥራ ለሠሪው እሾኸ ላጣሪው - "ቤተ ሠሪ ነገረ ሠሪ ራሰ ሠሪ" እንዲሉ - ( ሠሪ) የቅዱስ ዲዮስቆሮስ እምነት - ( ሠሪ) የማኅበረ ኬልቄዶን ስሕተት)

ሠሪታ፡ የሠራች (ዐሻሚ ቈናኝ)

ሠራ (ሠርዐ) ወስነ፣ ደነገገ፣ ደነባ (ሕግ አቆመ - "ሥራት ሠራ" እንዲሉ)

ሠራ፡ መራ (አሰፈረ የጦር ሰራዊትን ባገር ላይ)

ሠራ፡ ሥራት አስተማረ (ሥራ ቅጣ ንዲሉ)

ሠራ፡ አደረገ፣ ፈጠረ (ካለመኖር ወደ መኖር አስገኘ አመጣ - ግብር እምግብር አበጀ አዘጋጀ አወጣ ማንኛውንም ሥራ - (ብረት ሠራ) ቀጠቀጠ፣ ጨፈለቀ፣ ቀበቀበ - (ቤት ሠራ) ዐነጠ፣ ገነባ፣ ማገረ፣ ከደነ - (ገበታ ሠራ) ዘረጋ፣ እንጀራ ጣለ፣ አቀረበ - (ግፍ ሠራ) ዐመፀ፣ በደለ ሰውን - (ወጥ ሠራ) ቀቀለ፣ አበሰለ - (ወንጀል ሠራ) ቋንዣ ቈረጠ፣ ቤት አቃጠለ - (ኀጢኣት ሠራ) ሕግን ተላለፈ፣ ሰረቀ፣ አመነዘረ - (ጠጕር ሠራ) ጐነጐነ፣ ዐሸመ፣ ቈነነ - (ጦር ሠራ) ሰራዊት ሰበሰበ፣ አሰለፈ - (ካሳ ሠራ) ቈረጠ (ይህን ያኸል ትከፍላለኸ አለ) - (መግል ሠራ) ያዘ፣ ዐቈረ - (ነገር ሠራ) ዐደመ፣ ቋጠረ፣ አሳበቀ፣ አዋሸከ፣ አጣላ - (ለሰው ይምሰል ሠራ) ግብዝ ኾነ - "ሸመነን" ተመልከት)

ሠራሽ፡ የሠራው፣ ያበጀው (ረጋ ሠራሽ ሰው ሠራሽ" እንዲሉ - የቅርብ ሴት አንቀጽ ቅጽልነት በሩቅ ወንድ መፈታቱን አስተውል)

ሠራተኛ (ኞች) የሠራት ወገን (ሕግ አውጪ - ሥራ ወዳድ ትጉህ ጠይብ ባለጅ ቀጥቃጭ አንጥረኛ - "ወርቅ ሠራተኛ ብር ሠራተኛ" እንዲሉ - ዳግመኛም ሠራ ተኛ ተብሎ ኹለት አንቀጽ ይኾናል - "ተኛን" ተመልከት)

ሠራተኛነት፡ ሠራተኛ መኾን (ትጉ ህነት)

ሠራት (ሠራዕት) የሠሩ፣ የሚሠሩ ሠሪዎች

ሠራጊ፡ የሚሠርግ፣ የሚገባ (ገቢ)

ሠራጺ፡ የመንፈስ ቅዱስ ኣካል (የሠረጸ የሚሠርጽ)

ሠርቅ፡ የወር፣ የሌሊት፣ የቀን መባቻ መዠመሪያ

ሠርቶ፡ አድርጎ፣ አዘጋጅቶ፣ አብጅቶ

ሠርቶ አፍራሽ፡ በሥልጣኑ በቃሉ ፈጥሮ የሚያሳልፍ እንዳልነበረ የሚያደርግ እግዜር (ሰውን በደዌ የሚያፈርስ በመቃብር የሚያበሰብስ - "ስለ ሠርቶ አፍራሹ" እንዲል ለማኝ)

ሠርቶ አፍራሽ፡ ያረጀውን ቤት ለማደስ ለማስፋት ለማሳመር የሚንድ ዐናጢ ' ቤተ ሠሪ

ሠርየሞፈር ቂጥ፡ ሰረረ ።

ሠርጸ ድንግል፡ በ፲፭፻፶፮ ዓ፡ ም፡ የነገሠ የሐበሻ ንጉሥ ስም (የድንግል (እመቤታችን) ቡቃያ ማለት ነው)

ሠርጽ፡ ቡቃያ፣ ብቋያ ።

ሠቀሠቀ (ሠቅሠቀ) ወጋጋ፣ በሳሳ (ለመለየት ለማላቀቅ ለማስጌጥ - "ሸቀሸቀን" እይ - የዚህ ዘር ነው)

ሠቀቀ (ሠቂቅ፣ ሠቀ - ትግ፡ ሠቀቀ ሣቀየ) ጠላ፣ ሰለቸ፣ ሰቀጠጠ ( ቅን" እይ - የዚህ ዘር ነው)

ሠቀቀናም (ሞች) ሠቀቀን ያለበት የበዛበት (ባለሠቀቀን ችጋራም ስግብግብ)

ሠቀቀን፡ በልቶ አለመጥገብ (አሲድን" እይ)

ሠቀቀን፡ ያገኙትን ያዩትን ማጣት (ከዚህ የተነሣ ምር ሐዘን ማዘን ማልቀስ)

ሠቀጠ (ቀሠጠ) አዋሸከ ' ዋሸ (ሠቀጠ" ያማርኛ "ቀሠጠ" የግእዝ ነው)

ሠቃ፡ አፋፍ (ጐዣም)

ሠቃጢ (ቀሣጢ) የሠቀጠ (የነገር ሌባ ዋሾ)

ሠቅ (ሠቂቅ፣ ሠቀ፣ ሠቅ፣ ማቅ) ውስጡ ማቅ ላዩ ግምጃ ኹኖ የተሰፋ የካህናት መታጠቂያ (በግእዝ ቅናት ይባላል - ዛሬም የከተማ ሰዎች የሐር የወርቅ ቀበቶ ይሉታል)

ሠቅሠቅ (ቆች) የተበሳሳ ዕንጨት (በሰገነት ሰበሰብ ላይ ያለ ጌጠኛ ሥራ ዐይነ ርግብ - ሕዝ፡ ፵፥፱፣ ፲፬፣ ፴፯)

ሠቅሣቂ፡ የሠቀሠቀ፣ የሚሠቀሥቅ

ሠቅጥ (ሠጥቅ) ከላድ የፍየል መልክ

ሠቅጥማ፡ ከላድማ መልከ ቀበሮ (መቀነትማ ፍየል)

ሠቆች፡ መታጠቂያዎች

ሠበጠረ (ሠበጠ) አበጀ፣ ሠራ (ቅር ጫትን ጐታን)

ሠቢ (ሠባሒ) የሚሠባ ፍሪዳ ሚኾን

ሠባ (ሠብሐ) ወፈረ፣ ደነደነ፣ ደለበ (ጮመየ ጮማ ኾነ ጥጥ መሰለ ቀለጠ - ኢሳ፡ ፳፭፥፮ - (ተረት) - አህያ ሠባ ካልታረደ ምን ረባ - (ልቡ ሠባ) - አልታዘዝ አለ ሰው ናቀ)

ሠተረ፡ ዘረጋሰተረ

ሠነቀ (ሠኒቅ፣ ሠነቀ) ቈላ፣ ፈጨ፣ ጋገረ፣ አበሰለ (ሥንቅ አበጀ አዘጋጀ)

ሠነበጠ (ሠበጠ) ሠነጠረ፣ ለበጠ (ሠነተረ ከረከረ ከፈለ) ተረር

ሠነተረ (ሠተረ) በጣ፣ ሠነጠቀ፣ ቀደደ (የታረደውን ከብት ለመግፈፍ ብልት ለማውጣት - "ሰነዘረን" ተመልከት)

ሠነታተረ፡ ቀዳደደ ።

ሠነገ፡ አፍንጫን በሳሰነገ ።

ሠነጋ፡ የፈረስን ቍላ አወጣ - ነጋ

ሠነጠረ (ሠጸረ) ለበጠ ' ሠነበጠ

ሠነጠቀ (ሠጠቀ) ሰበረ፣ አነበበ፣ ተረተረ፣ ቀደደ፣ ከፈለ (በቁመት ፈለጠ መገዘ ተረረ - "ኣቡየ ጻድቁ ገደል እንዳክርማ የሚሠነጥቁ እንዳለ ታቦት ዘፋኝ) ታሪ

ሠነጣጠቀ፡ ሰባበረ፣ ከፋፈለ ። መሠነጣጠቅ፡ መሰባበር፣ መከፋፈል

ሠናቂ፡ የሠነቀ፣ የሚሠንቅ (ጋጋሪ)

ሠኔ (ሠነየ) የወር ስም (ዐሥረኛ ወር ከመስከረም - ትርጓሜውም ሠናዪ ሠናይ ማለት ነው - የርሻን መለስለስና የዘርን መዘራት ያሳያል - (ተረት) - አላጋጭ ገበሬ በሠኔ ይሞታል - "ሠኔ ነግ በኔ" - ባ፲፱፻፶፮ ዓ፡ ም፡ ሠኔ ቀን ሰኞ የመኪና መንገድ በግራ

ሠኔ ሚካኤል (የሠኔ ሚካኤል) በሠኔ ፲፪ ቀን የሚከብር የቅዱስ ሚካኤል በዓል

ሠኔና ሰኞ፡ የመለኛ የጠንቋይ ፈሊጥ (ሠኔ ሰኞ በባተ ቍጥር ማስፈራሪያ ኾኖ ይኖራል)

ሠንበሌጥ፡ ሣርሰንበሌጥ ።

ሠንባጭ፡ የሠነበጠ፣ የሚሠነብጥ (ሠንጣሪ ለባጭ)

ሠንተራ፡ ደንጊያ ዐቃፊ የወንጭፍ ቈዳ

ሠንታሪ፡ የሠነተረ፣ የሚሠነትር (በጪ)

ሠንገር ሠንገር አለ፡ ግመልኛና ሰጐንኛ ሮጠ ።

ሠንገሮ (ሠገረ) ረዥም ቀርፋፋ ሰው

ሠንጠረዥ፡ የጨዋታ መሣሪያ - ንጠረዥ

ሠንጣሪ (ዎች) የሠነጠረ፣ የሚሠን ጥር (ሣጠራ ሠሪ) ንበጥ

ሠንጣራ፣ ሥንጣሪ፣ ሥንጥር፡ የተሠነጠረ (ልባጭ ልብጥ - በግእዝ ሥጻር ይባ ላል - ሥንጥር አለ ተሠነጠረ - ተሠነጣጠረ በብዙ ወገን ማለት ነው)

ሠንጣቂ፡ የሠነጠቀ፣ የሚሠነጥቅ (ተር ታሪ)

ሠንጣቃ ዕንጨት፡ ጭንቅ መከራ ጥብ (መውጫ ቀዳዳ የሌለው)

ሠንጣቃ፡ የተሠነጠቀ ገደል መረሬ

ሠንጥቆ፡ ተርትሮ፣ ከፍሎ (ተረት) - ባልነቃ ሠንጥቆ ባልዘነበ በርቆ)

ሠኘ) ሠነጠቀ፡ በኩል መኾኑ ቀርቶ ካ፲፱፻፴፫ ዓ፡ ም፡ በፊት እንደ ነበረ በስተቀኝ ኾነ

ሠኘ) (ሠነየ) አሠኘ (አስሠኘ) (አሠነየ) ፡ አስመለከተ፣ አሳሰበ፣ አሻ፣ አስፈለገ፣ አስወደደ (አናገረ አስባለ - (ዝም አሠኘ) አስረመመ)

ሠከተ (ሥኅተ) ቀረበ፣ ስለፈ (ጸጥ ዕክም ብሎ ለቅልውጥ)

ሠከት፡ የቀረበ፣ የሰለፈ ። ሠከቴ፡ የሠከት ወገንና ዐይነት (ሎፌ ቀላዋጭ)

ሠክሎፍሠከተ

ሠክ አለ፡ ሎፍ አለ (ተደቀነ)

ሠዊ (ሠዋዒ) የሠዋ፣ የሚሠዋ (ካህን ቃልቻ)

ሠዋ (ሦዐ) ዐረደ፣ አወራረደ ( በሰ ' አጨሰ - መሥዋዕት ወይም ቍርባን አቀረበ - ላምላክ - (ለጣዖት ጭዳ አለ) - መዝ፡ ፻፮፥፴፯)

ሠውር፡ የኮከብ ስም (ሰውር)

ሠውት፡ የፊደል ስም ( - እሸት ማለት ነው)

ሠየ (ትግ፡ ሠይአ ሻፈደ) ጐመዠ፣ ተቃረ፣ ጓጓ፣ ቋመጠ ።

ሠየመ (ሤመ) ሾመ፣ አከበረ ።

ሠየመ፡ ዐቀበ (ዐቃቢ ኾነ ፈጩ አዘጋጀ ሰፈረ መላ ለበመ በቤተ ክሲያን ምሥራቃዊ በር አደረገ አኖረ መገበሪያን - "ሰየመን" ተመልከት)

ሠየምት፡ ከበላይ ተሹመው የበታቻቸውን የሚሾሙ ባላባቶች (ከትግሬ ሠየምት ከደንቢያ ከንተብት" እንዲሉ)

ሠየረ፣ ሤረ) አሤረ (ዐደረ፣ ዐደመ ' አሳደመ ' መከረ ' ዶለተ - የክፉ፣ የበጎ)

ሠዪ፡ የሠየ፣ የሚሠይ (ጐምዢ)

ሠያሚ፡ ሿሚ (የሠየመ፣ የሚሠይም፣ ዐቃቢ )

ሠይቷል፡ ጐምዥቷል፣ ተቅሯል ።

ሠገረ (ሠፂር፣ ሠገረ) ዐለፈ፣ ኼደ፣ ተራመደ (አካኼድ አሳመረ ተቀማጩን ሳይነቀንቅ እንደ እንዝርት ሾረ ሰለከ ተሽከረከረ - ተፍለቀለቀ)

ሠገራ (ዐረ) ያይነ ምድር ጕድጓድ (ዐዘቅተ ኵስሕ)

ሠገገ፡ ረዘመ (ሠገገ)

ሠጋሪ፡ የሚሠግር፣ የሚሽከረከር ።

ሠጋር (ሮች) የሠገረ፣ የሚሠግር ( በቅሎ ስናር አህያ ፈረስ ግመል - ፩ነገ፡ ፬፥፳፰)

ሠግር፡ የወር መባቻ ቀን (እሑድ የሳተው አንድ ቀን ዐልፎ ማግሰኞ ሲብት ሠግር ይባላል)

ሠግር፡ ጳጕሜ በ፫ ዓመት ስትኾን የሚዘለለው ፮ኛ ቀን

ሠጠቀ (ሠጢቅ፣ ሠጠቀ) ከፈለ (ሣጥቅ - ቆች - ቦይ የቅብቅብ መክ ተነተነ ' ገመሰ ' ማሳን)

ሠጠጥ አለ፡ ተሠጠጠ ።

ሠጠጥ አደረገ፡ ሠጠጠ ።

ሠጣጭ (ሠጣጢ) የሠጠጠ፣ የሚሠጥ (ቀዳጅ)

ሠጥር (ሠጸረ) ያሣ ማጣበቂያ ሠንጣራ ሠንጣቃ ዕንጨት (ሠነጠረን" እይ - ሠጥር ታናሽ ጐድን - ቀጪን ሠጥር እንዲሉ)

ሡልጣን (ዐረ) ንጉሥ (በሕዝብ ላይ ሥልጣን ያለው)

ሡሠኛ (ኞች) ልማደኛ (በመለኛ)

ሡሢ፡ ባለቀለም መጠብር ነጠላ ።

ሡሥ፡ የትንባኾ የሱና ፍላጎት መሻት ክፉልማድ ዐመል (ዐይንን የሚጨፍንና የሚያዛጋ - "ሐራራን" አስተውል)

ሡካር፡ በቁሙ፡ ሱካር ።

ሢሶ መሬት፡ ቀላድ ሲጣል ለባለምድር ባላባት ከ፫ የተሰጠ

ሢሶ፡ ሦስተኛ እጅ (ዘኊ፡ ፲፭፥፮፣ ፯)

ሢሶ ዕንጨት፡ ከሦስት አንዱ ክፍል ዕንጨት የኾነ ጠመንዣ መውዜር (ከወገቡ በላይ ዕንጨቱ ዐጪር ኹኖ ብረቱ ብቻ ይታ ያል)

ሢሶ፡ ከሦስት አንድሠለሰ

ሢሶ ጠማጅ፣ ሢሶ ዐራሽ፡ ከሦስት አንድ ሊሰጥ ተዋውሎ የሰው መሬት የሚያርስ (ተጋዢ ተጠማኝ)

ሢር (ሥርው) ከተለፋ የበግና የፍየል ሌጦ በቀጪኑ ተቀዶ የወጣ የበቅሎ የፈረስ የበሬ ዕቃ መስፊያ ያገልግል መለጐ ሚያ (ሢር ያሠኘው ከመነሻ እስከ መጨረሻ ከሥር እስከ ጫፍ መድረሱ ነው)

ሢር (ሮች) የጠፍር ቅዳጅ (የጫማ ማዘቢያ መጥለፊያ - በግእዝ ቶታን ይባላል - ዮሐ፡ ፩፥፳፯)

ሢር (ዐረ) ሥር

ሢር፡ ያልተገመደ ክሥዳ ጭረት ።

ሢርባ፡ ሚጥሚጣ (የበረሓ በርበሬ በላተኛውን ብዙ ውሃ የሚያስጠጣ እንደ ሣራብ የሚለበልብ)

ሢርባን፡ ተመልከት

ሢርጋ፡ እንገር

ሢጥ፡ መጮኸ ።

ሢጥ መጮኸሠጠጠ (ሠጢጥ፣ ሠጠጠ) በፍጥ ነት ቀደደ (ልብስን)

ሢጥ ሢጥ አለ፡ ተጨነቀ ።

ሢጥ አለ፡ ባጪር ድምፅ ጮኸ (ተረት) - ዐይጥ ወልዳ ወልዳ ዥራት ሲቀር ሢጥ አለች)

ሢጥጥ ሢጥጥ አለ፡ መላልሶ ተን ሢያጠጠ

ሢጥጥ አለ፡ ብረትኛ ጮኸ ።

ሢጥጥታ፡ የስፌት አክርማና ስንደዶ ድምፅ (ሢጥጥ" ማለት - ፱ኛውን ተመልከት)

ሣለ (ሠዐለ) ነደፈ፣ በገረ፣ መሰለ (ሥዕል ምሳሌ አደረገ ነቀሰ የፈጣሪንና የፍጡርን መልክ በቀለም ገለጠ አሳየ - ሣለ ፈጠረ - ኢሳ፡ ፵፱፥፭)

ሳለ (እንዘ ሀሎ) ፡ ሳይሞት፣ ሳያልፍ ። (ተረት) "አባት ሳለ አጌጥ፡ ጀንበር ሳለ ሩጥ” ።

ሣለኡሁ ኡሁ አለሣለ

ሣልሳይ፡ ዘንድ አንቀጽ ።

ሣልስ፡ ፫ኛ ፊደል ። ( ሣልስ ሣልስ" እንዲል ተማሪ)

ሣልስ ቅጽል) ነጋሪ

ሣልስት፡ የች ፫ኛ ቀን ሦስት (ሠወስት) ከኹለት ቀጥሎ ያለ መደበኛ ቍጥር

ሣልስነት፡ ፫ኛነት ።

ሣሢት፡ የቀበሌ ስም (በተጕለት ውስጥ ያለች የኪዳነ ምሕረት አጥቢያ ገለ)

ሣሣ (ሠሥዐ) ሥሥ ኾነ፣ ረቀቀ፣ ቀ ጠነ (ኢሳ፡ ፵፥፲፱) ሣል

ሣሣ (ሠሥዖ) መሣሣት

ሣሣ፡ ሠሠተ (ምሳ፡ ፳፫፥፪)

ሣሣ፡ ተራራቀ (የዘር)

ሣሣ አለ፡ ሣሣ

ሣሣ፡ ዐዘነ፣ ራራ (እከሌ ለልጁ ይሣ)

ሣሣ አደረገ፡ አሣሣ ።

ሣሣኹ፡ ሠሠትኹ (አየን" ተመልከት)

ሣራም፡ ሣር በዝቶ የበቀለበት ስፍራ (ሣረ በል" - የቤት የዱር እንስሳ ወፍ ሣር ነጭቶ የሚበላ)

ሣራብ፡ ሳማ (አለብላቢት - ግእዝ)

ሣር (ሣዕር) በቁሙ (የመሬት ጠጕር ለእንስሳና ላውሬ ለወፍ ምግብ ለሰው ጥቅም የሚኾን - የጋዣ የገደል የመስክ የጠጅ)

ሣቀ (ሠሐቀ) ፈገገ፣ ተንከተከተ (ከሐዘን ከለቅሶ ራቀ - "አፍ ቂጡ ሣቀ" እንዲሉ - (ግጥም) - ክትክት ብላ ሣቀች ምድር ጥርስ አውጥታ አባተ ሲታሰር አብርሀ ሲፈታ - "ገበያ እንዴት ዋለ" ቢለው አንዱ ባንዱ ሲሥቅ)

ሣቀ፡ ፈካ (ማሽላ ሲያር ይሥቃል ። በሐዘን መካከል ቢሣቅ ወዶን አይሥቁ ይባላል - ወዶን ሰውየው አይሥቁ ጥርሶቹ - "ወደደ" ብለኸ "ወዶንን" ተመልከት)

ሣቀየ (ሣቅዮ፣ ሣቀየ) አስጨነቀ (መከራ አሳየ አስቻለ - መዝ፡ ፵፬፥፪)

ሣቂ (ሠሓቂ) የሣቀ፣ የሚሥቅ ።

ሣቂ ገጣጣ ጥርሰ ጣይ ሞቴ

ሣቂታ (ሠሓቂት) የሣቀች፣ የምት ሥቅ (ሣቅ የምታበዛ ሴት) ክት

ሣቃዪ፡ የሣቀየ፣ የሚሣቅይ ።

ሣቅ (ሥሒቅ) መሣቅ ።

ሣቅ ሣቅ አለ፡ ፈገግ ፈገግ አለ (መላልሶ ሣቀ)

ሣቅ ሥላቅ (ሠሐቅ ወሥላቅ) ሣቅና ሥላቅ (ሠለቀ)" እይ)

ሣቅ አለ፡ በጥቂቱ ሣቀ ።

ሣቅ፡ የፊት ፈገግታ (የደስታ ምል ክት)

ሣንሣ፡ መሎጊያሳንሳ

ሣንቃ!፡ የበርመዝጊያሳንቃ ።

ሣይ (ዮች፣ ሠዓሊ) የሣለ፣ የሚ ሥል (በእጅ በመኪና - "ሥዕል ሣይ" እንዲሉ)

ሣይንቴ (ሣይንታዊ) የሣይንት ሰው

ሣይንት፡ ያገር ስም (በበጌምድር አቅ ራቢያ ያለ አገር - "ዐማራ ሣይንት" እንዲሉ - ትርጓሜው ዘር ማለት ይመስላል - ልጅን ሽንት እንዲሉ - "ዐማራን" አስተውል) ሰው

ሣይንቶች፡ የሣይንት ተወላጆች ።

ሣጠራ፡ ከቀርክሓ፣ ከሸንበቆ የተበጀ ምንጣፍ (፪ኛ ስሙ አቴና ነው)

ሣጥን (ሣጹን) ከንጨት፣ ከብረት፣ ከደንጊያ፣ ከወረቀት፣ ከቈዳ፣ ካረግ የተበጀ ሞላላ ዕቃ (ማንኛውንም ነገር ማስቀመ፵ ማኖሪያ - የገንዘብ የልብስ የጌጥ የሬሳ ሣጥን እንዲሉ - ሲበዛ ሣጥኖች ይላል - (ቁም ሣጥን) ፡ ቁሞ የሚከፈት የቁም ሣጥን የቆመ ያልተጋደመ በውስጡ ከታች እስከ ላይ ዐልፎ ዐልፎ የዕቃ መሰደሪያ ዕርከን ያለውና የሌ ለው - (የወርቅ ሣጥን) ፡ ከወርቅ የተሠራ በወርቅ የተለበጠ የወርቅ ማስቀመጫ ማለት ነው)

ሣጥን፡ ሰይጣን ።

ሣጥን፡ በቁሙ ።

ሤረኛ (ኞች) ዐድመኛ (ነገር ቋጣሪ)

ሤረኛነት፡ ሤረኛ መኾን (ዐድመኛነት)

ሤራ፡ ርጋታ፣ አማን፣ ደኅና፣ ጸጥታ፣ ፍቅር፣ ሰላም ። (እያሙ ሤራ" እንዲል - ባላገር ለውሻው ስም ሲያወጣ - "እከሌ ግዳይ ቢያጣ ከሤራው ይገድላል" - "ባረከ" በግእዝ "መረቀ ረገመ" ተብሎ እንዲፈታ ሤራም እንደ ርሱ ነው - "መረነ" ብለኸ "መረንን" እይ)

ሤራ ቈረጠ፡ ዐድማ አደረገ ' ጨረሰ ' ማለ

ሤራ፡ ዐድማ፡ (ሠየረ፡ ሤረ)

ሴራ፡ ዐድማ (ሠየረ፡ ሤረ)

ሤራ፡ ዕድር፣ ዐድማ፣ ዱለት (ተረት) - ከምሳ የተለየ ደብተራ ያደርጋል ሤራ - በኦሮምኛ ግን ደንብ ውል ማለት ነው)

ሤራ ኾነ፡ ተሤረ፣ ተዶለተ (ጸጥ አለ፣ ረጋ አገሩ ሕዝቡ) ማለ

ሤራ ጕዱ፡ ሰላመ ቢስ ¡ ቅን የማ ይዶልት

ሥለሳ፡ ዕየማ ።

ሥሉሴ፡ ሽሩባ ።

ሥሉሴ፡ በብርና በወርቅ በንሓስ መደብ ላይ በ፫ በ፫ ረድፍ የተንጠለጠለ የበ ቅሎ፣ የግመል ዐንገት ጌጥ (ሥሥና ቀጪን አጫዋች ዐልቦ ዶቃ - መሳ፡ ፰፥፳፩ - "መረሸትን" ተመልከት)

ሥሉሴ፡ ክብ የጸናጽል ሰሌዳ፲ ጊዜ ኹኖ የሚታይ ሿሿቴ

ሥሉስ፡ ፫ ምስክር (ልማ በሥሉስ ጥፋ በሥሉስ" እንዲሉ)

ሥሉስ፡ ፫ የገበጣ ጠጠር (ሥሉስ ባይርቀኝ" እንዲል ገበጣ ተጫዋች)

ሥሉስ ቅዱስ፡ ሦስት የኾነ ቅዱስ (በአካሉ ጊዜ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ የሚመሰገን አምላክ)

ሥሉስ፡ በአካል ሦስትየኾነ አምላክ ።

ሥሉጥ፡ ሥልጡን (የጠመመውን የሚያቀና የጐደለውን የሚመላ - ሥሉጥ የግእዝ ሥልጡን ያማርኛ ነው)

ሥላሴ፡ በቅድስት ሥላሴ ስም የተቀረጸ ታቦት (ደብረ ብርሃን ሥላሴ ዐድዋ ላሴ" እንዲሉ - (የሞኝ ጥያቄ) - ሥላሴ ገዳም ታቦቱ ማነው) እይ

ሥላሴ፡ የቅኔ ስም (፩ኛ ቅኔ ዘሴን)

ሥላሴ፡ የፈጣሪ አካል ሦስትነት (ወይም ስም)

ሥላሴዎች፡ የሥላሴ ካህናት (የሥላሴ መቅደስ አወዳሾች)

ሥል (ሎች) (ሥዕል) በብራናና በወረቀት በደንጊያና በንጨት በብረት በሰው ገላ ላይ የተሣለ የተቀረጸ የተነቀሰ የሰውና የማንኛውም ፍጥረት መልክ ምሳሌ ምልክት

ሥልሳ፡ ኹለት ሠላሳ (ስድስት ዐሥር ስሳ - ስድሳ)

ሥልስ (ሞጻሕት) የወይን መጠጥ መሧዕት (ስለ ክብረ አምላክ የሚረጭ የሚፈስ - ሥልስ ከ፫ የተጣለ ጠጅ ይመስላል)

ሥልስ፡ ሦስት ዐይነት ኹኖ ባንድ ነት የተዘጋጀ (ያዋዜና የቅቤ የክትፎ ወጥ - ትግሬ ግን ሥልስ የሚለው በዘይትና በሽንኵርት የተሠራ የትማትም ወጥ ነው)

ሥልስ ወጭት፡ የሥልስ መሥሪያ ድስት (ወይም ማቅረቢያ ጣባ)

ሥልስ፡ የተሠለሰ (ሦስት የኾነ)

ሥልሶ፡ በ፫ ጣት ልክ የተደረዘ የሙ ነኵሴ ቆብ

ሥልቅ፡ ያገር ስም (በግዳድ)

ሥልጡን (ኖች) ዝኒ ከማሁ (ብልጥ ብልኅ ጮሌ ፈጣን ባለያ የከተማ ሰው ሥልጡንነት ሥልጠና)

ሥልጢ፡ ከ፯ቱ የጕራጌ ባላባቶች አንዱ (አገሩም ነገዱም ሥልጢ ይባላል)

ሥልጣኑ ተያዘ፡ እንዳይቀድስ ተከ ለከለ

ሥልጣኔ፡ ሥልጠና (ሥልጥንና ሥልጡን መኾን ዕውቀት - (ክፉ ሥልጣኔ) ተንኰል የሰይጣን ሥራ ሰውን የሚጐዳና የሚያጠፋ)

ሥልጣን (ኖች) መብት፣ ችሎት፣ ክህነት (ቅስና ድቍና - (ሥጋዊ ሥልጣን) የንጉሥ - (መንፈሳዊ ሥልጣን) የጳጳስ)

ሥልጣን ሰገድ፡ ያጤ ሱስንዮስ ስመ መንግሥት

ሥሡ (ሥሡዕ) ንፉግ፣ ጩቅ ቢስ፣ ቅቅታም፣ ሥሥታም (የባልቴት ግጥም) - እኒህ ሥሡ ለዝናም ጌታ ውሃ ነሡ)

ሥሥ (ሦች) የሣሣ (ብረ ሸሽከውፍረትና ከብዛት ከመቀራረብ የራቀ - "ሥሥ እንጀራ ሥሥ ጠጕር" እንዲሉ)

ሥሥ ቅልጥም፡ የኋላ እግር ከነቅባቱ (መቅንን" እይ - ቀና)

ሥሥ ቅልጥም) የኋላ እግር ከጕልበት በታች ከነቅባቱ መቅንን" ተመልከት ወዶ የዋጡት ቅልጥም ከብርንዶ ይጥም" እንዲሉ ።

ሥሥታም (ሞች) የሠሠተ፣ የሚሠሥት (እጁን ቢሉት ጠብ የማይለው - ፩ቆሮ፡ ፮፥፲ - (ተረት) - ከሥሥታም አንድ ይወድቀው አንድ ያንቀው)

ሥሥታምነት፡ ሥሥታም መኾን (ንፉግነት ቢስነት)

ሥሥት (ሥሥዕት) ንፍገት ' ቅት (ማቴ፡ ፳፫፥፳፭፡ ማር፡ ፯፥፳፪)

ሥሥት፡ ተንቀሳቃሽ ።  

ሥረ ብዙ፡ ሥሩ ለጕንፋን ለሳል መድኀኒት የሚኾን ቅጠል ።

ሥረ ነገር፡ የነገር ጥንት መነሻ

ሥረ ወጥ፡ ያልተሰፋ ትት ጥልፍ (መርፌና መቀስ ያልዞረበት ልብስ ቅጥል አልባ - ሥሩ እስከ ጫፉ የወጣ - በግእዝ እል ታሕ ይባላል)

ሥረ ገደል፡ በሺዋ ክፍል ያለ ቀበሌ

ሥረት (ሥር) ጠባይ፣ ባሕርይ (ተፈጥሮ ተገብሮ - የገላ ኹናቴ - ወይም በአካል ላይ የሚታይ ሥራ - በትግሪኛ ግን በዘር የሚወርድ በሽታ ይባላል)

ሥረጌ ( ሥርው) የሣርና የቅ ጠል ሥር ያለባት ምድር (የማንም ከብት ተሰብስቦ የሚውልበት ቀዬ ሜዳ ነው)

ሥሩ ተቈጣ) ዐበጠ ተነፋ

ሥሪት፡ ምሪት (በባላገር ላይ የተሠራ የጦር ሰራዊት ጭፍራ)

ሥሪት፡ ካያት - ከቅድም አያት ሲያ ያዝ የመጣ (የገባር የግንደ በል የመስቀል መሬት - "የመሬት ሥሪት" እንዲሉ)

ሥራ (ግበር) የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (እከሌ ጌታኸ ያዘዘኸን ሥራ ሥራ)

ሥራ መሪ) የሥራ ሹም (ሠራተኛን ሥራን ወደ ማወቅ ሥራውን ወደ ሠራተኛ የሚመራ ሥራ አስኪያጅ)

ሥራ ቤት፡ የሥራ ቤት ማድ ቤት (ወንድና ሴት ባሪያ)

ሥራ ያዘ፡ ረባ፣ ጠቀመ (ሥራም አይዝ አይረባም)

ሥራ ያዘ፡ እሥራ ገባ ።

ሥራ ጊዮርጊስ፡ ከካህናት በቀር ሕዝብ የማያከብረው የጊዮርጊስ በዓል (በጥር ፲፰ ቀን የሚውል)

ሥራ፡ ግብር፣ ተግባር (የጥበብ ዘዴ ውጤት - "የጽፈት የሒሳብ ሥራ" እንዲሉ - የበዓል ተቃራኒ ውሃ ዋና ሰንጠረዥ በገና ፈረስ ግልቢያ ብረት ቅጥቀጣ ጽፈት ድጕሰት)

ሥራ ፈታ፡ ተወ፣ ለቀቀ፣ ቦዘነ

ሥራ ፈት (ቶች) (ፅሩዕ) ኣለ ሥራ የሚውል ሥራ የማይወድ ቀላዋጭ ዘዋሪ

ሥራ ፈትነት፡ ሥራ ፈት መኾን (ቦዘንተኝነት - "መራ" ብለኸ "መሪን" እይ)

ሥራ፡ ፍጥረተ ዓለም ።

ሥራሥር፡ የሥር ሥር (ብዙ ዐይነት መድኀኒትና ምግብ የሚኾን የንጨት ያትክልት ሥር)

ሥራተ ቢስ፡ ሥራተ መጥፎ ዳኛ (ሕገ ውጡ)

ሥራተ ጌትነት፡ የጌትነት ክብር ማዕርግ (ሥጋ መብላት ጠጅ መጠጣት)

ሥራተኛ (ኞች) ሥራት አክባሪ (በሥራት ዐዳሪ)

ሥራት (ሥርዐት) ንጹሕ ውሳኔ (የሕግና የትእዛዝ መጠበቂያ ደንብ)

ሥራት ለበሰ፡ ዋስ ጠራ ' ተዳኘ

ሥራት ልክ ነው፡ አይለወጥም ' ይቃወስም

ሥራት፡ ሙሉ የበቅሎ ዕቃ (በቅሎ ከነሥራቷ እሰጥ" እንዲል ተጋች)

ሥር (ሥሩዕ) የተሠራ፣ የተደረገ፣ የተደነባ (ውስን ድንግግ - (የቤት ሥር) - በቤት የተሠራ ልብስ ከገበያ ያልተገዛ የባሕር ትል ያልኾነ ሸማ - (ያጤ ሥር) - ዐጤ የሠሩት ሥራት ደንብ ውሳኔ)

ሥር (ሮች) (ሠረወ፣ ሥርው) የፍጥረት የነገር ኹሉ መዠመሪያ መነሻ ወጠኛ (ወደ ታችና ወደ ላይ የሚያድግ - "ነገር ከሥሩ ውሃ ከጥሩ" እንዲሉ - የዛፍ ሥር የደም ሥር - "ሠረየ" ብለኸ "ሥረይን" እይ - በምስጢር ከዚሀ ጋራ አንድ ነው)

ሥር ሰደደ (ሠረወ) ወደ ታች ደገ ' ሥርን አረዘመ

ሥር ሰደደ፡ ተደላደለ (ዘመድ ገዛ ወገን አበጀ ገንዘብ አበዛ - "ሢርን" አስተውል)

ሥር ኵል፡ ነጭና ጥቍር የኵል ሥር

ሥር ያዘ፡ እሥር ገባ (ሳያልቅ ቀረ ነገሩ ሥር ያዘ" እንዲሉ)

ሥር፡ ግርጌ፣ ታችኛ ስፍራ፣ ጥግ (የገደል የተራራ ሥር" እንዲሉ)

ሥር ጠምዛዥ፡ ክፉ ደብተራ አስ ማተኛ ሰው ገዳይ

ሥርቻ፡ የግንብ የግድግዳ የዕቃ ሥር (የማይታይ ስፍራ)

ሥርቻ፡ የግንብ ጥግሥር

ሥርዐተ ንግሥ፡ በዘውድ በዓል የሚደረግ ጸሎትና መቀባት የመሰለው ኹሉ ።

ሥርግ ሥርግ አለ፡ ትርግ ትርግ (ርግብ ርግብ አለ" - "ተረገን" ተመልከት)

ሥርግ፡ ዝኒ ከማሁ (የሠረገ የገባ - "ሥርግ አለ ግበት አለ)

ሥርግርግ አለ፡ ተሥረገረገ ።

ሥርግርግ፡ የተሥረገረገ (የተዋጠ)

ሥርጸት፡ መሥረጽ ።

ሥቃይ፡ ጭንቅ፣ መከራ፣ ቅጣት፣ እስ ራት ' ክፉ ሕመም

ሥቅሠቃ፡ የመሠቅሠቅ ሥራ

ሥቅሥቃት፡ ቍርጥማት (ዐጥንትን የሚወጋ የሚሠቀሥቅ በሽታ)

ሥቅሥቅ አደረገ፡ ከሥር ከታች ያዘ ' ሠቀሠቀ

ሥቅሥቅ፡ የተሠቀሠቀ (የተለየ)

ሥቅሥቆ፡ በቅመም የተሠራ የሥጋ ክትፎ ወጥ (ከድስት ውስጥ በቢላዋና በማንካ ተሠቅሥቆ የሚወጣ)

ሥቅሥቆሽ፡ ሥቅሠቃ

ሥቅቅ አለ፡ ከልብ ዐዘነ፣ አለቀሰ ።

ሥቅቅታ፡ ሥቅቅ ማለት (ዕጦት ዕፍረት ሐዘን ልቅሶ ሥቃይ)

ሥባም (ሞች) ሥብ ያለው (ባለ ሥብ - መዝ፡ ፻፵፬፥፲፬) ለብ

ሥባት (ሥብሐት) መሥባት (ሥብነት ጮማነት ወፍር ድንዳኔ - (ተረት) - ካልታ ረደ አይታይ ሥባቱ ካልተናገረ አይታይ ብላቱ)

ሥባት (ጐንደር) ቦዳ ' ቀልዝ ' አረዳ መሬት (ዘፍ፡ ፳፯፥፴፱፡ ኢሳ፡ ፲፥ ፳፯፡ ሆሴ፡ ፲፪፥ ፲፩)

ሥብ (ሥቡሕ) የሠባ (ድልብ ገች ሰንጋ - "ሥብ ሊያርዱ ጕፋያ ይነዱ)

ሥብ (ሥብሕ) ጮማ (ቅልጥ ያለ ሥጋ ትርፍ)

ሥብ፡ ሞራግልገል ' ሞራ (ዘሌ፡ ፫፥፫)

ሥብነት፡ ሥብ መኾን ።

ሥብጥር (ሥብጥርጥር) የተሠባጠረ (ዝንቅ ጣልቃ)

ሥነ ሥርዐት፡ የሥርዐት ዐቅድ ኹኔታ

ሥነ ስቅለት፡ የስቅለት መልክ (ሥዕለ ስቅለት)

ሥነ ጥበብ፡ የጥበብ ዐይነት ።

ሥነ ጸዳል፡ የብርሃን ውበት ።

ሥነ ፍጥረት፡ የፍጥረት ዐይነት መልክ

ሥነቃ፡ የመሠነቅ ሥራ (ጋገራ)

ሥን (ሠነየ) መልክ፣ ውበት፣ ደም ግባት (ዐይነት - "አሥኔትን" እይ)

ሥንቀ ነፍስ፡ ሰው ሊሞት በቀረበ ጊዜ የሚቀበለው ቍርባን ። ዳግመኛም ከጣረ ሞት በፊት የሚቀምሰው እንጀራ ፉት የሚለው ውሃ ሥንቀ ነፍስ ይባላል (መሰናበቻ የነፍስ ሥንቅ ማለት ነው)

ሥንቀ ፈጅ፡ ሥንቅ ጨራሽ (ተረት) - እኼድ ባይ ሥንቀ ፈጅ)

ሥንቀን (ሥንቀነ፣ ሥንቅነ) ሥንቃችንን ሥንቃችን (ካመድ ጋራ የተቀላቀለ ትንባኾ ዱቄት - የአፍንጫ ሥንቅ ማለት ነው - ኹለተኛ ስሙ ሱረት - "ጕርፎን" እይ)

ስንቀን፡ ሱረት ሠነቀ

ሥንቄ፡ የሰው ስም ።

ሥንቅ (ቆች) የመንገደኛ መብል ምግብ መኖ ኅብስት ጭብጦ ቈሎ ዳቦ ቈሎ በሶ ድርቆሽ ጭኮ ሙልሙል ሽልጦ ሻሜት (የሚበላና የሚጠጣ መግዣ ገንዘብ - " ሥንቅ ነው የመቤቴ" እንዲል ታቦት ዘፋኝ - ከነገረኛ ሰው ሥንቅ አይደባልቁም - ሥንቅኸን ባህያ ዐመልኽን በጕያ - "ራዛ አንበጣን ሥንቃችን በልባችን አለው)

ሥንቆ፡ የቅጠል ስም (በክረምት የሚ በቅል የሜዳ ቅጠል እየተቀቀለ የሚበላ የጐመን ዐይነት í ክረምታዊ ሥንቅ መኾኑን ያሳያል - ሥንቆ በግእዝ ሥንቁን ማለት ነው)

ሥንበጣ፡ ሥንጠራ፣ ልበጣ ።

ሥንባጭ (ጮች) ሥንጣሪ ' ልባጭ

ሥንብጥ (ጦች) የመሣ እኩሌታ ኹለተኛ ክፍል ።

ሥንብጥ፡ የተሠነበጠ (ልብጥ)

ሥንተራ፡ ሥንጠቃ፣ ቀደዳ (የመሠን ተር ሥራ)

ሥንትራት፡ ብጥታት (የሥንጥቃት ይነት)

ሥንትር፡ የተሠነተረ (ብጥ)

ሥንትርትር፡ የተሠነታተረ (ባላገር ግን ሸነተረ ተሸነታተረ ይልና ሽንትርትር ይላል)

ሥንጠራ፡ ልሰጣ (ሥንበጣ)

ሥንጠቃ፡ ትርተራ (የመሠንጠቅ ሥራ)

ሥንጣቂ፡ ንቃቃት (ኢሳ፡ ፪፥፲፱፣ ፳፩፡ ፶፯፥፭)

ሥንጣቂ፡ የሥንጥቅ ቅሬታ ትራፊ (ማቴ፡ ፯፥፫፣ ፬፡ ፳፫፥፳፬)

ሥንጥርጣሪ፣ ሥንጥርጥር፡ የተሠነጣ ጠረ

ሥንጥቃት፡ ስብራት ትርትራት የመ ሠንጠቅ ኹናቴ

ሥንጥቅ አለ፡ ስብር ትርትር አለ

ሥንጥቅ ወፍ፡ ከፍተኛ ድምቢጥ (በግንባሯና በሰርኗ ላይ ቍልቍል ነጭ ያላት)

ሥንጥቅ፡ ዝኒ ከማሁ ለሠንጣቃ (ትክክል እኩሌታ ግማሽ - "እከሌ የገዛው ማር ሥንጥቅ አተረፈው)

ሥንጥቅጣቂ፡ ዐያሌ ሥንጣቂ ።

ሥንጥቅጥቅ አለ፡ ተሠነጣጠቀ ።

ሥንጥቅጥቅ፡ የተሠነጣጠቀ ግንብ፣ መሬት፣ ተረከዝ

ሥንጭሮ (ትግ) ፈፋ ' ፈረፈር ።

ሥዕለ ስቅለት፡ ጌታችን እንደ ተሰቀለ የሚያሳይ የመስቀል ሥዕል

ሥየማ፡ ሰፈራ፣ ልበማ ።

ሥየታ፡ ጕምዠታ ።

ሥዩመ እግዚአብሔር፡ እግዜር የሾመው (ንጉሥ መኰንን ዳኛ) ልብም

ሥዩም፡ የሰው ስም ።

ሥዩም፡ የተሾመ (ሹም)

ሥይማት፡ ልብማት (የመሠየም አኳ ዃን)

ሥይም፡ የተሠየመ፣ የተመላ፣ የተለበመ ዃን

ሥይት፡ የጤፍ ስም ።

ሥጉያ፡ የሥጋ መደብር (ሥጋ መሸጫ - ይህ ቋንቋ በሐረርጌ ይነገራል)

ሥጊሚጢ፡ የቅጠል ስም (በክረምት እንደ ሥንቆ እየተቀቀለ የሚበላ ቅጠል - ሥፂ በቁሙ ሚጢ መልሽ ማለት ነው)

ሥጋ ለባሲ፡ የሰው ነፍስ ።

ሥጋ ልደት (ልደተ ሥጋ) ዝም ድና ' ውልድና

ሥጋ መልከኛ፡ መልከኛ ከገባር (የሚቀበለው ታላቅ ወይም አሰጅ)

ሥጋ መልከኛ፡ የሥጋ ሹም ። (ደበ ረን" እይ)

ሥጋ ማሪያም፡ ባሕታዊ እንደ ማተብ ባንገቱ የሚያደርገው (ባሕር ዐረብ የን ጽሕና ምሳሌ)

ሥጋ በል፡ ሥጋ የሚበላ አውሬ ' አሞራ ' ሰው

ሥጋ ቤት፡ ሥጋ የሚቀመጥበት ቤት

ሥጋ ቤት፡ የሥጋ ሹምሥጋ ቤቶች፡ ጭፍሮች የሥጋ ቤት ሠራተኞች

ሥጋ ተሥጋ፡ የባላገር ንግግር (ሥጋ ከሰውነት ጋራ ይሰማማል" ማለት ነው)

ሥጋ ኾነ (ሥጋ ለበሰ) ሰው ኾነ (ዮሐ፡ ፩፥፲፬)

ሥጋ ወደሙ፡ ቍርባን (ሥጋሁ ወደሙ ለዐማኑኤል) ካለው የመጣ ነው)

ሥጋ ግብር (ግብረ ሥጋ) ሩካቤ (የወንድና የሴት መገናኘት)

ሥጋ ፈሪ፡ ፍሪዳ በታረደ ጊዜ የሚንቀጠቀጥ የሹልዳ ሥጋ (ሠጋ" ማለት ከዚህ የወጣ ይመስላል)

ሥጋማ (ጥካ) አካል ወፍራም ደንዳና

ሥጋት፡ ፍራት ሠጋ ።

ሥጋዊ (ውያን) ሥጋ ለባሽ (ዓለማዊ ሰው መንፈሳዊነት የሌለው ኣፍኣዊ)

ሥጋዎች (ግእዝ ሥጋት) ብዙዎች የሥጋ ብልቶች - ሙዳዎች ።

ሥግሪያ፡ የሠጋር አካኼድ

ሥግራ፡ የሕፃን ርምጃ (ድቅ ድቅ ድንኵል ድንል" ማለት - "አቱ ሥግራ ታቱ ሥግራ" እንዲሉ - "ዝግራን" ተመልከት - ከዚህ ጋራ አንድ ነው)

ሥግና፣ ሥጋነት፣ ሥግነት፡ ሥጋ መኾን (ዝምድና)

ሦስተኛ (ሦስተኛው፣ ሦስተኛዋ፣ ሦስተኛዪቱ) ተራ ቍጥር (ዳግመኛም ሦስተኛው ሦስተኛኸ" እያለ ጊዜን ያሳያል - "እከሌ እኛ ዘንድ ሲመጣ ሦስተኛው ነው)

ሦስተኝት፡ ሦስተኛዪቱ ክፍል ።

ሦስቲያ፡ ከሦስት አንድ (ሢሶ)

ሦስት መለኮት፡ ከቢዘን የወጣ የመናፍቃን ባህል (ባጤ ምኒልክ መንግሥት የተወገዘ)

ሦስት፡ በቁሙሠለሰ

ሦስት አደረገ፡ ሠለሰ ( ቍጥር ቈጠረ ከ፫ ከፈለ)

ሦስት ፈርጅ) ጃኖ ዝቅዝቅ ድርብ በፈርጅ በፈ ርጁ" ቢል፡ "በኩያ በኩያው ባምሳያ ባምሳ ያው" ማለት ነው ። ትግሬም ጋቢን "ፈርጊ" ለዋል ።

ሦስትነታቸው፡ ሦስት መኾናቸው (የሥላሴ ሦስትነታቸው በአካልና በአካላዊ ግብር በስም ነው)

ሦስትነት፡ ሦስት መኾን ።

ሦስትያ፡ ሦስት መቶ ድር ።

ሦስትዮሽ፡ ፯ ብስ ያለው ቀንበር ።

ሦስትዮሽ፡ ከሦስት ገመድ የተሸረበ ጅራፍ

ሦስቶ፡ በሰማይ ሦስት ኹነው የሚታዩ ኮከቦች

ሦሪት፡ የምታምር ወፍሶሪት

ሦራ፡ መጐናጸፊያሶራ ።

ሦታ (ሠወየ) የሚያምር ወጣት ፎጠና ልጅ እግር (ሦታ ጐበዝ" እንዲሉ - "ሶባን" እይ - ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ። 

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ