ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ቀ ፡ ፲፱ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ። በፊደልነት ቆፍ፡ በአኃዝነት 100 ይባላል ።
ቀ ጠሮ አፈረሰ)፡ ተቃጥሮ ሳይመጣ ቀረ ።
ቀሃ፡ የወንዝ ስም ። ቀሓ ።
ቀሓ፡ ያገር የወንዝ ስም (በበጌምድር ውስጥ ያለ ዠማ ") ። "የውሃ የውሃ ምን አለኝ ቀሓ" እንዲሉ።
ቀህረማን (ዐረ)፡ ቈርበት ካሪም ።
ቀለ - ቃለ፡ ቀንዳ - ቀንድ፡ ቃለ ደረቅ ማለት ነው ።
ቀለ፡ ተለጠፈ/ታዘለ/አቀለ፡ ለጠፈ/ዐዘለ (በዠርባ ወይም በደረት በጐን ያዘ) ።
ቀለሔ፡ የቀለሕ ዐይነት ባዶ፡ ፍሬ የሌለው እኸል ። "ቀለኸን" እይ ።
ቀለሔ፡ የኔ ቀለሕ ።
ቀለሕ (ሖች)፡ በቂጡ ከምሱር በው ስጡ ባሩድ በፉ ዐረር የሌለበት ውስጠ ክፍት ንሓስ ።
ቀለሕ ምላሽ፡ የርሳስ መምታት የቀለሕ መመለስ (መቅረት) ።
ቀለለ (ቀሊል ቀለ)፡ ("(ዘፍ. ፰፥ ፫)") ከክብደት ከክብር ከብዛት ከብርታት ራቀ አነሰ ጐደለ ። (ግጥም)፡ "እንዴት አደርጋለኹ ብዬ ስጨነቅ፡ እያደር ይቀላል ዐባይና ሥንቅ" ።
ቀለል፡ መቅለል ።
ቀለል አለ፡ አነስ ጐደል አለ ።
ቀለልተኛ፡ ቀላልነት ያለው ከመክበድ
ቀለመ (ቀሊም ቀለመ)፡ ቀለም እዘጋጀ ኣቦካ ዐሸ ።
ቀለመ፡ ምድር ሳያስነካ ያዘ፡ ቀ
ቀለመ፡ ነካ ነበዘ አሳደፈ ።
ቀለመ፡ ዐረደ ቈረጠ ከረከመ፡ ዐንገትን ሥጋን ቀሠምን ።
ቀለመ፡ አጠቀሰ ጻፈ ጣፈ፡ ቀለምን (ቃልን) በብራና በወረቀት ላይ አሳረፈ ።
ቀለመ ወርቅ፡ የወርቅ ቀለም፡ የወንድና የሴት ስም።
ቀለመ ጠጥ፡ ዐይነ ባርማምጠ ።
ቀለመው፡ ቀለሙ ልብሱን ነበዘው አሳደፈው፡ ልብሱ ቀለሙን ሠረበው ጠጣው ተዋሐደው ።
ቀለመጠ - ቀመጠ ለመጠ)፡ አቀላመጠ፡ በምላስ ሙሬነት ወይም አማካይነት አፉን ጠረገ አጮኸ፡ ምራቁን ዋጠ አጣጣመ ።
ቀለማት፡ ቀለሞች ሕብሮች ። "፯ቱ ቀለማት" እንዲሉ።
ቀለም (ሞች)፡ ከስንዴ ዐራራና ከአሜራ ሥር ከአውጥ ፍሬ የተበጀ ጥቍርና ቀይ ልጥልጥ ወይም ፈሳሽ ("(ኤር. ፴፮፥ ፲፰)") ።በጥቍሩ ሙጫ በቀዩ ከርቤ ይገባበታል ። ነጭ ብጫ ሰማያዊ አረንጓዴ ወይን ጠጅቀለም የመሰለው ኹሉ ።"እፍራንን ዶልንና ነድን" እይ፡ "ዶለ ነደደ" ።
ቀለም (ዐረ)፡ ከጐሽ መቃ የተቀረጸ ብር መጻፊያ ። ይኸንንም ፵፬ኛው የግእዝ መዝ ሙር (ቀለመ ጸሓፊ) በማለቱ ያስረዳል።
ቀለም፡ ቀሠም ቀጪን መቃ ።
ቀለም ቀባ፡ ላከከ በቀለም ሸፈነ አለበሰ ።
ቀለም ቀንድ፡ ቀለም ያለበት የቀለም ቀንድ ። (ግጥም፡ ተማሪ በሞተ ጊዜ)፡ "ዐፈር መልሱ እንጂ ደንጊያ ለምናችኹ፡ የቀለም ቀ ንድ ነው፡ ትሰብሩታላችኹ" ።
ቀለም፡ ትምርት ቃለ እግዚአብሔር ። (ግጥም)፡ "ይማርልኝ ብዬ በጌምድር ሰድጄ ቀለም ገባው አሉ፡ እሳት ኾነ ልጄ" ። "ዐጤ ቴዎድሮስ ልጇን ያቃጠሉባት ሴት" ።
ቀለም አገባ፡ ነከረ ዐለለ ።
ቀለም አግቢ፡ ዐላይ ("(ኢሳ. ፴፮፥ ፪)") ።
ቀለም፡ ደም ግባት ውበት ላሕይ ። (ግጥም)፡ "ሥራ ፈቶ ዋለ ትላንት ሸማኔው ! ያ ቀለምሽ ነወይ የተበላሸው" ።
ቀለም ገባው፡ ምሁር ኾነ፡ ትምርት ዐወቀ ።
ቀለም፡ ጐሽ መቃ ከቅጥነቱና ከውስጠ ድፍንነቱ በቀር መቃ የሚመስል ።
ቀለምሽሽ (ምሸሽ)፡ ርቦ ከቀለም (ጐሽ መቃ) የተሠራ ።
ቀለምጺጽ፡ የሠማ የጋለ፡ ምጣድ ድስት ማሰሮ ጀበና ቂጥ ብልጭልጭታ ።
ቀለምጺጽ፡ የእሳት ፍንጣሪ ብራሪ (ግእዝ) ።
ቀለሰ (ቀሊስ ቀለሰ)፡ መለሰ አጐበጠ አደገነ ቈለፈ ።
ቀለሰ፡ አለቍንጮ ቅስትኛ ሠራ ። "ጐዦ ቀለሰ" እንዲሉ።
ቀለሰ፡ አቀረቀረ ። "ዐንገቱን ቀለሰ" እንዲሉ።
ቀለሰ፡ ኣረ ከቀኝ ወደ ግራ አዞረ ።
ቀለሳ - ቅለሳ፡ የመቀለስ/የማጕበጥ ሥራ ።
ቀለስ፡ መለስ ።
ቀለስ አለ፡ መለስ አለ ።
ቀለሸ - ቀለበሸ)፡ አቅለሸለሸ፡ አጥ ወለወለ ልውጣ ልውጣ አለ ።
ቀለሸ)—ቀማ ።
ቀለቀለ - ቀልቀለ)፡ አንቀለቀለ (አ ንቀልቀለ)፡ ባለማቋረጥ አነደደ አንበለበለ ።
ቀለቀል - ቀልቃላ (ሎች)፡ የተንቀለ ቀለ/የሚንቀለቀል (ዘዋሪ ቀዥቃዣ ቀውቃዋ ") ።
ቀለቀንዳ፡ አፈኛ ተናጋሪ ለፍላፊ ወንድ ወይም ሴት ።
ቀለበ (ቀሊብ ቀለበ ቀለጰ)፡ ረዳ መገበ ኣበላ አጠጣ ("(፪ሳሙ. ፲፱፥ ፴፪፡ ፴፫)") ።
ቀለበ (ገለወ)፡ ሸፈነ በውስጥ አደረገ ።
ቀለበ፡ ቀለጠፈ ሰበቀለ ።
ቀለበ፡ የተወረወረ ነገርን ምድር ሳያስነካ ያዘ ተቀበለ ጨበጠ እጅ አደረገ ። "ቀለመን" እይ ።
ቀለበሰ፡ ከጫፍ ወደ ውስጥ ወይም ወደ ውጭ ዐጠፈ ሸነቀረ ቀነፈ ።
ቀለበሸ፡ መለሰ ገለበጠ፡ የውስጡን በላይ አደረገ፡ አቅለሸለሸ ።
ቀለበተ፡ ቀለበት ሠራ፡ አከበበ ።
ቀለበታም፡ ቀለበት ያለው ባለቀለበት ሰው ዕቃ ።
ቀለበት (ቀለበ)፡ ከብርና ከወርቅ ከንሓስ ከመዳብ የተሠራ የጣትና ያንገት ክብ ጌጥ ("(ዘፍ. ፴፰፥ ፲፰)") ። (ተረት)፡ "በዋስ ያለ ከብት፡ በጣት ያለ ቀለበት" ። ሲበዛ ቀለበቶች ያሰኛል ። ቀለበት በጣት የሚያዝ ጣት ቀለቡ ማለትን ያሳያል ።
ቀለባ - ቅልቢያ - ቅልቦሽ (ቍላቤ)፡ መቅለብ ።
ቀለብ፡ ሠራተኛ በየወሩ የሚቀበለው ጥሬ እኸል ጥሩ ታደፍ ("(፩ነገ. ፩፥ ፯)") ። ባመት ሲኾን ምንዳ ይባላል ።
ቀለብላባ - ቅልብልብ (ቦች)፡ የተቅለበለበ (ክልብልብ ስግብግብ ችኩል ") ። (ተረት)፡ "ለቅልብልብ ዐማት ሢሶ በትር አላት" ።
ቀለብተኛ (ኞች)፡ ቀለብ ተቀባይ ባለቀለብ ቀለብ ተሰፋሪ በቀለብ ዐዳሪ ሎሌ ገረድ አሽከር ወታደር ።
ቀለተ (ትግ)፡ ረጠበ ዐገዘ ረዳ፡ በጠፋ ተካ ሰጠ ።
ቀለተኛ፡ የቀለት ወገን ባለቀለት ።
ቀለተኞች፡ ቀለት ፈላጎች ተቀባዮች ።
ቀለታ፡ ዕገዛ ርዳታ ስጦታ ።
ቀለት፡ ርጥባን ።
ቀለኸ (ቀለሕ)፡ ዝነበበ ፍሬ አልባ ቀረ፡ የብር ያበባ ያገዳ እኸል ።
ቀለወ፡ ከለበ ።
ቀለዋ፡ የዛፍ ስም፡ ፍሬው ለዕከክና ለኮሶ መድኀኒት የሚኾን አነስተኛ የወይናደጋ ዕንጨት ።
ቀለው ቀለው አለ፡ ክልብ ክልብ አለ ። (ግጥም)፡ "ካንዱ ቤት አንዱ ቤት ስትይ ቀለው ቀለው አንዱ የነደደው ማዥራትሽን ባለው" ።
ቀለዘ፡ ኣለልክ ደረቀ ከቸለ ጨለኸ ።
ቀለደ (ቀሊድ ቀለደ)፡ አሾፈ ተረበ አቧለተ ዋዛ ፈዛዛ ተናገረ፡ አላገጠ አፌዘ አፌጠ አሌጠ ።
ቀለጠ፡ ተመታ ። "በጥፊ ቀለጠ" ።
ቀለጠ ነጠረ (ደከመ ጠፋ ") ("(ሚክ. ፭፥ ፲፭)") ። "እኸሉ ፈሰሰ"፡ "እንባው ፈሰሰ"፡ "ቅቤው ፈሰሰ"፡ "ልቡ ፈሰሰ"፡ "ዐይኑ ፈሰሰ" እንዲሉ ። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም "ይፈስ ይፈሳል" እያለ ጠብቆ ይነገራል እንጂ፡ "ይፈስስ ይፈስሳል" አይልም ። (ተረት)፡ "ውሃ ከፈሰሰ አልታፈሠ" ።
ቀለጠ፡ ወፈረ ደነደነ በጣም ሠባ ።
ቀለጠ፡ ደመቀ አማረ ። "ዘፈኑ ቀለጠ፡ እልልታው ቀለጠ" ።
ቀለጠ፡ ጝ ፈሰሰ፡ ተናደ ወደቀ ፈረስ ("(መዝ. ፳፪፥ ፲፬፡ ኢሳ. ፲፫፥ ፯)") ። (ተረት)፡ "እንደ ፈንታሌ ትቀልጣለኸ" ።
ቀለጠ፡ ጠፋ ። "ገንዘቤን ለማንም አበደርኹና የትም ቀልጦ ቀረ" ።
ቀለጠመ (ትግ ቀልጸመ)፡ ቅልጥም አወጣ፡ ቅልጥማም ኾነ ።
ቀለጠመ (አንጕዐ)፡ ቅልጥም መታ ሰበረ፡ ቅልጥም አሳክሎ ቈረጠ ። "ገለፀመን" እይ፡ የዚህ ሞክሼ ነው ።
ቀለጠመ፡ ቅልጥም በሚያኸል ሽክና ጠጣ፡ ዥው አደረገ ጨለጠ ። "ገበሬው ቀን ከዱር እቤት በገባ ጊዜ ጠላውን ባንኮላ ቀለጠመው" ።
ቀለጠጠ - ገለጠጠ)፡ አንቀለጠጠ፡ ከፈተ፡ ፈጽሞ ገለጠ፡ አንገለጠጠ ። በተገብሮነትም ይፈታል ።
ቀለጠጥ - ቀልጣጣ - ቅልጥጥ፡ የሚንቀለጠጥ፡ እንቅልጥ ከለላ አልባ ።
ቀለጣጠመ፡ ሰባበረ ኰረታተመ ("(፪ነገ. ፲፰፥ ፬፡ ሆሴ. ፲፥ ፪)") ።
ቀለጤ፡ በዋል ፈሰስ፡ ወፍራም ሰው ።
ቀለጦ፡ እንኵሮ በተነኰረ ጊዜ ከገበር ምጣድ ላይ ተለጥጦ የሚወጣ ሥሥና ደረቅ የንኵሮ ቅሬታ ።
ቀለፈፈ፡ ገለፈፈ ቀፈፈ ቈረጠ ።
ቀለፋ - ቈለፈ - ቀፈለ)፡ አንቀላፋ፡ ተኛ ተጋደመ ዐይኖቹን ጨፈነ ከንፈሩን ገጠመ ሰውየው ("(ዘፍ. ፪፥ ፳፩፡ ኢሳ. ፵፫፥ ፲፯፡ ሉቃ. ፰፥ ፳፫)") ።
ቀሊል፡ የቀለለ (ላባ ገለባ ላንፋ የመሰለው ኹሉ ") ። "ረከበን" እይ ።
ቀሊል የግእዝ፡ ቀላል ያማርኛ ነው ።
ቀሊል፡ ድበላ አደፍ ያበባ እኸል ። "ብስል ተቀሊል" እንዲሉ።
ቀላ (ቀልዐ ዕብ. ቃላዕ)፡ መታ
ቀላ (ቀዪሕ)፡ መቅላት ።
ቀላ (ቄሐ)፡ ደም መሰለ ("(ምሳ. ፳፫፥ ፴፩)") ።
ቀላ፡ ቈረጠ ። ፩ኛው ቀላና ይህ ፪ኛው ቀላ ባማርኛ ሲተባበሩ (ግጥም)፡ "የታጠቅ ጐራዴ፡ ብረት የነበረ፡ እየቀላ ኼደ ደም እየመሰለ" ።
ቀላ አለ፡ ቀላ ።
ቀላል (ሎች)፡ የቀለለ/የቀለለች (የተ ሙን ተቤሳ ዶሮ ") ። "አገረ ብለኸ እግርን ወገብን" ተመልከት ።
ቀላል መሬት፡ አሸዋማ ስፍራ ።
ቀላል ሴት፡ ቁም ነገር የሌላት ።
ቀላመደ (ቃለ ዐመፀ)፡ ዋሸ ዘላበደ ቀሣፈተ፡ በቃል በደለ ቃሉን ከዳ ።
ቀላሚ፡ የሚቀልም (ነባዥ አሳዳፊ ") ።
ቀላማ ።
ቀላማ (ሞች)፡ ወላድ ፈረስ እንስት ።
ቀላማጅ (ጆች)፡ የቀላመደ/የሚቀላምድ (ዘላባጅ ቀሣፋች ") ።
ቀላሳ፡ ጐባጣ መላሳ ።
ቀላሽ፡ አሪ በሬ (ጐዣምና ጐንደር) ።
ቀላሽ፡ የቀለሰ/የሚቀልስ (መላሽ አጕ
ቀላቀለ፡ ደባለቀ ቀየጠ ዘነቀ ።
ቀላቃይ፡ የቀላቀለ/የሚቀላቅል (ደባላቂ ቀያጭ ") ።
ቀላቢ (ላል)፡ የሚቀልብ፡ ከላይ ከሰማይ ተቀባይ ያዥ ጨባጭ ። "ኳስ ቀላቢ" እን ዲሉ።
ቀላቢ (ዎች)፡ የቀለበ/የሚቀልብ (አብሊ አጠጪ ረድ መጋቢ ገረድ ") ።
ቀላች (ቾች)፡ የቀለተ/የሚቀልት (ረ
ቀላወጠ፡ ከጀለ አፈጠጠ ። (ተረት)፡ "የወደዱትን ሲያጡ የጠሉትን ይቀላውጡ" ።
ቀላዋ (ከላዋ)፡ ከላባ ።
ቀላዋጭ (ጮች)፡ የቀላወጠ/የሚቀላውጥ (አፍጣጭ ") ። (ተረት)፡ "ወጥን ማን ያው ቃል ቢሉ፡ ቀላዋጭ" ።
ቀላዋጭነት፡ ቀላዋጭ መኾን፡ አፍጣጭነት ።
ቀላያት፡ ጥልቆች ውቅያኖሶች ።
ቀላይ (ቀለየ ጠለቀ)፡ ጥልቅና ሰፊ ባሕር ውቅያኖስ ("(ዘፍ. ፩፥ ፪)") ።
ቀላይ፡ የሚቀል የማይከብድ ።
ቀላይ—ቈለለ ።
ቀላድ (ዶች)፡ ከቃጫ/ከንሰት/ጭ ረት የተገመደ ገመድ ።
ቀላድ፡ በቀላድ የተለካ አንድ ጋሻ መሬት ። በግእዝ "ሐብለ ርስት" ይባላል ("(መዝ. ፻፭፥ ፲፩)") ።
ቀላድ ጣለ፡ መሬትን ለመለካት ቀላድን በምድር ላይ ዘረጋ፡ የረዘመውን በገመድ ያጠረውን በክንድ ለካ መጠነ ።
ቀላድ ጣይ (ዮች)፡ ቀላድ የሚጥል (የሚዘረጋ) ምድርን የሚለካ ።
ቀላጅ (ጆች)፡ የቀለደ/የሚቀልድ (አላጋጭ ") ።
ቀላጤ (ቃለ ሐፄ)፡ የንጉሥ ቃል።
ቀላጤ (ዎች)፡ የንጉሥ/የዳኛ ቃል ነጋሪ መልክተኛ ። "ዐጤን ይበልጡ ቀላጤ፡ ሙክትን ይሻል ወጠጤ" እንዲሉ።
ቀላጤ ዋሻ፡ ቀላጤ ካዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሲኼድ የሚያድርበት ዋሻ ስፍራ ።
ቀላጤ—ቀለጠጠ ።
ቀላጥም (ሞች)፡ በቅልጥም ልክ የተሰበረ (የተቈረጠ) የቃሬዛና የመሰላል አግዳሚ ዕንጨት ።
ቀላጥቤ፡ ተናጋሪ ለፍላፊ፡ ወሬ አማቂ ።
ቀላጭ፡ የሚቀልጥ/የሚማ (ፈሳሽ ፈራሽ ሠም ሞራ ተራራ ") ።
ቀላጭ፡ ጌታ ባለጠጋ ሀብታም ሰውነቱ የሚያምር ጭፍጭፍ የሚል ።
ቀላጭቱ፡ እመቤቲቱ ወይዘሮዪቱ ("(ኢሳ. ፵፯፥ ፩)") ።
ቀላጮች፡ ጌቶች መኳንንት ባለጠ ጎች ("(፩ቆሮ. ፮፥ ፱)") ።
ቀሌን - ቀርን፡ ዥ፥ዝኆን ።
ቀሌንጅ (ዥ)፡ ታናሽ የዝኆን ጥርስ ።
ቀልማዳ፡ ዝኒ ከማሁ፡ ዋሾ ።
ቀልቀል (ትግ)፡ ኵስ ዐይነ ምድር በዐዘቅተ ኵስሕ አፋፍ ኹኖ የሚጣል።
ቀልቀል፡ አፋፍ ገደል (ግእዝ) ።
ቀልቀልቱ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀልቀሎ (ዎች)፡ የወጠጤ ስልቻ ። ኦሮ ግን ትንሿን ኰረጆ ትልቁን ቀልቀሎ ይለዋል።
ቀልበ ቢስ (ሶች)፡ ልበ ቢስ፡ ቀልበ መጥፎ ።
ቀልበ ደረቅ፡ የጋኔን ስም፡ ለዛ ሙጥጤ ።
ቀልበ ጮሬ፡ ሾላካ የማይጠመድ ። "ጮሬን" እይ ።
ቀልባ - ቅልብጭ፡ የቀለበጪ፡ ቀል ጣፋ ቅልጥፍ ስብቅል ።
ቀልባሳ፡ የታጠፈ ቀናፋ ።
ቀልባሽ፡ የቀለበሰ/የሚቀለብስ (ቀናፊ ") ።
ቀልባጣ (ቀልብ ዐጣ)፡ ቀባጣሪ፬ አፉ እንዳመጣ የሚናገር ።
ቀልባጣ፡ ቀባጣሪ፡ ቀልብ ።
ቀልቤ፡ ጫፉ ደረቅ አከቻማ ።
ቀልብ (ኦሮ)፡ ልብ፡ የልብ ዕውቀት ።
ቀልብ—ቀለበሰ ።
ቀልዝ፡ ፍልማ መሬት (ጐዣም) ።
ቀልደኛ (ኞች)፡ ቀልድ ወዳድ ቧልተኛ ፌዘኛ ዋዘኛ ።
ቀልድ፡ ከውነት የራቀ ጨዋታ ተረብ ቧልት ፌዝ ወዘበሬታ ።
ቀልጠፍ አለ፡ ፈጠን አለ፡ ቀለጠፈ ።
ቀልጠፍ፡ ፈጠን ።
ቀልጣሚ፡ የቀለጠመ/የሚቀልጥም (ቅልጥም መቺ ሰባሪ ") ።
ቀልጣማ፡ ሰባራ ቶሎ የሚሰበር ።
ቀልጣፊ - ቀልጣፋ (ፎች)፡ የሚቀለ ጥፍ፡ ከዝብዝብ የራቀ ፈጣን ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፲፯)") ።
ቀልጣፋነት፡ ቀልጣፋ መኾን ።
ቀልጥፍ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ፡ ፍጠን፡ መር በል ("(ማሕ. ፯፥ ፲፬)") ።
ቀመ፡ አመለጠ ጠፋ ታጣ (ተገ) ብሮ ።
ቀመለ (ቀሚል ቀመለ)፡ ቅማል አበጀ ያዘ፡ ኣፈራ ወለደ ።
ቀመለ፡ ለቀሙ በጥፍር ዳጠ ገደለ ።
ቀመመ፡ ቅመምን መድኀኒትን ሰበሰበ ፈጨ አላመ አዘጋጀ፡ ደባለቀ ቀላቀለ አንድነት አደረገ መጠነ ።
ቀመሰ (ቀሠመ)፡ ጣመ ለከፈ በጥቂቱ በላ ጠጣ ዋጠ፡ ("(ኢዮ. ፲፪፥ ፲፩)") ። "አቶ እከሌ መድኀኒት ስለ ቀመሰ እቤት ዋለ" ። "አብነትን" እይ ።
ቀመሰ፡ ተመታ ተደበደበ ።
ቀመሰ፡ ተቀበረ ። "ዐፈርን" ተመልከት ።
ቀመሳ - ቅምሻ፡ የመቅመስ ድርጊት ።
ቀመስ፡ መቅመስ ።
ቀመስ አደረገ፡ ቀመሰ ።
ቀመስ፡ የበላ ። "ፈረንጅን" እይ ።
ቀመረ (ቀምሮ ቀመረ)፡ ቈጠረ፡ መደበ ለየ ከፈለ ።
ቀመር (ዐረ)፡ ጨረቃ ።
ቀመር (ገመር)፡ የዥብ ንጉሥ ወቸገል መልኩና ጨፈረር ጠጕሩ ከዥብ ኹሉ የተለየ፡ ዥቦች ፈርተው ይሸሹታል፡ ትራፊውንም ይበላሉ ።
ቀመር፡ ቍጥር፡ የቍጥር መደብ ወይም ክፍል፡ ዐውድ ሰንጠረዥ ።"
ቀመር፡ ዋልታ በዙሪያው ከላይ እስከ ታች ባለክፍል ብስ ያለው (ግእዝ) ።
ቀመር፡ ፍሬው ትንንሽ የኾነ አደንጓሬ ።
ቀመቀመ (ከመከመ)፡ ጫፍ ጫፉን ሰፋ ዘመዘመ ።
ቀመቀመ፡ ብዙ ጊዜ ጠጣ ።
ቀመቀመ፡ ወጣ በቀለ ቀነቀነ ።
ቀመት፡ የሚዛን ልክ ፪ ተረን ፩ ቀመት ነው ።
ቀመኛ (ቀበኛ)፡ ልብስ የሚበላ ከ ብት የልብስ ቀማኛ ።"
ቀመደ - ገመደ)፡ አቅመደመደ፡ እባብኛ አስኬደ፡ እንደ ገመድ ጐተተ ዐቅሙ ቢስ አደረገ፡ አሽመደመደ ።
ቀመድማዳ - ቅምድምድ - ቅምድማጅ፡ የተቅመደመደ (ጕትት ሽምድምድ ") ።
ቀመጠ)፡ "ተቀመጠ" ብለኸ "ተቀማጭን" አስተውል ። በ የ ከ ለ መነሻ እየኾኑት ሲነገር፡ "በቅርብ የቅርብ ከቅርብ ለቅርብ" ይላል ።
ቀመጠ)፡ (ቀምጦ ቀመጠ)፡ አስ ቀመጠ)፡ ቍጭ አደረገ አሳረፈ ጐለተ፡ እነበረ ኣኖረ አቈየ አሰነበተ ("(ዘፍ. ፪፥ ፲፭፡ ፩ነገ. ፭፥ ፭፡ ሉቃ. ፱፥ ፲፬፡ ፲፭)") ። "ረፈቀን" አስተውል ። አስቀመጠ አስደራጊ ሲኾን ባድራጊነት መተ ርጐሙ (ቀመጠ) በዘመን ብዛት ስለ ተረሳ ነው ። (ዐወሰ) ብለሽ አስታወሰን ተመልከት ።
ቀመጠ) ብለኽ ተቀመጠን እይ ።
ቀመጠለ (ገመደለ)፡ ፈጽሞ አጐደለ አሳነሰ ።
ቀመጠለ፡ ዐረደ ጐመደ ቀነጠሰ ።
ቀሚ (ቀማሒ ቀማዒ)፡ የቀማ/የሚቀማ ።ሲበዛ "ቀሚዎች" ይላል ።
ቀሚሳዊ፡ አንደ ቀሚስ፡ የሰውን ገላ የሚያጠልቅ ።
ቀሚሴ (ቀሚስየ)፡ የኔ ቀሚስ ።
ቀሚሴ፡ የቂጥኝ ስም ።
ቀሚስ (ሶች)፡ በ፫ ወገን የተሰፋ የሴት ልብስ፡ ልኩ ፮ ዘንግ ፳፬ ክንድ ነው ።
ቀሚስ ለበሰ፡ ረዥም የግምጃ እጀ ጠባብ ዐብደላ ካኒ ተሸለመ አጠለቀ ።
ቀሚስ፡ ቀና
ቀሚስ፡ እጀ ሰፊ የቄስ የመነኵሴ ልብስ፡ ረዥም ጥብቆ የሸማ የሐር የዳባ ("(ዘፍ. ፴፯፥ ፳፫፡ ፴፪)") ።
ቀሚስ፡ ዋና ዲያቆን የሱቲ ቀሚስ ለብሶ "ተንሥኡ ጸልዩ" የሚል ።
ቀሚስ፡ የመሶብ ልብስ ።
ቀሚስ፡ የበቅሎ የፈረስ ኮርቻ ልብስ ።
ቀማ (ቀምሐ ትግ ቀምዐ)፡ ነጠቀ ወሰደ ("(ሚክ. ፪፥ ፪)")፡ ሸክሙን ካናቱ ሱሪውን ከባቱ ። (ተረት)፡ "ዥብ የኔ ስለው ወናፌን ቀማኝ" ። "ዘረፈን" እይ ።
ቀማ፡ መጥፋት መታጣት ።
ቀማመሰ፡ ለካከፈ ።
ቀማሚ (ዎች)፡ የቀመመ/የሚቀምም (ሰብሳቢ አዘጋጂ ") ። "መድኀኒት ቀማሚ" እንዲሉ።
ቀማማ፡ ነጣጠቀ ።
ቀማሪ፡ የቀመረ/የሚቀምር (ቈጣሪ መዳቢ ") ።
ቀማሽ (ሾች)፡ የቀመሰ/የሚቀምስ (ቀን ከሕዝብ አስቀድሞ በቤተ መንግሥት የሚበላ የሚጋበዝ መኰንን ባለማዕርግ ") ። "እንወራረድ አህያ እንረድ እኔ ጠ ባሽ፡ አንተ ቀማሽ" እንዲሉ እረኞች ።
ቀማሽነት፡ ቀማሽ መኾን ።
ቀማኛ (ኞች)፡ ዝኒ ከማሁ፡ ነጣቂ ዳንዴ ወንበዴ ሽፍታ ነጥቆ በረር ።
ቀማኛነት፡ ቀማኛ መኾን፡ ነጣቂነት ።
ቀማይ (ዮች)፡ የቀመለ/የሚቀምል ( ቅማል ገዳይ ") ።
ቀምሶ፡ ጥሞ ። "ቀምሶ ሰጠ" እንዲሉ።
ቀምቀሞ፡ እጅግ በጣም ዐጪር ጠጕር በራስና ባገጭ ላይ በቅሎ የሚታይ ።
ቀምቃሚ (ዎች)፡ የቀመቀመ/የሚቀመቅም (ሰፊ ዘምዛሚ ") ።
ቀምበር፡ የበሬ ዕቃ ። —ቀነበረ ።
ቀምቶ በላ፡ እየነጠቀ የሚበላ ።
ቀምቶ፡ ነጥቆ ።
ቀምጣላ - ቅምጥል፡ የተቀመጠለ (ጐ
ቀምጣይ፡ የቀመጠለ/የሚቀመጥል (አ ጐዳይ ") ።
ቀሰመ ። አቀሣሠም፡ አለቃቀም/መቅሠም ።
ቀሠመ (ቀሢም - ቀሠመ)፡ አበባን ደምን ርጥበት ያለውን ነገር ኹሉ ለቀመ ሰበሰበ መጠጠ ።
ቀሰመ፡ ለቀመ/ቀሠመ ።
ቀሰመ፡ ቀመመ እጣፈጠ ("(ግእዝ)") ።
ቀሰመ፡ ቀሰቀሰ ።
ቀሠማ፡ ለቀማ ስብሰባ መጠጣ ።
ቀሠም (ሞች - ቀሠብ)፡ የቀጪን መቃ ቍራጭ የማግ መደወሪያ ። "ቀለምን" እይ፡ "ቀለመ" ።
ቀሰም፡ ቀጪን መቃ ።—ቀሠመ ።
ቀሠም፡ የወርቅ የብር ጥብጣብ ።
ቀሰሰ (ቀሲስ - ቀሰ)፡ ቅስና ተቀበለ ። (ተረት)፡ "ያልተሾመ እያዝ፡ ያልቀሰሰ አይናዘዝ" ።
ቀሰሰ፡ ቀዘዘ ፈዘዘ ።
ቀሰስ (የፈዘዘ ") ።
ቀሰስተኛ (ኞች)፡ ፈዛዛ ።
ቀሰረ ። ቅሣር፡ ጭረት ።
ቀሰረ (ቀተረ)፡ ገተረ/አቆመ ።"ቀና'ገ'ሰና ተ ተወራራሽ መኾናቸውን" አትዘንጋ ።
ቀሰረ ።ቀሠተ፡ ደገነ ። ቀሰተ ።
ቀሠረ፡ ገተረ ።
ቀሰቀሰ (ትግ ቀስቀሰ - አወከ)፡ ነቀ ነቀ አነቃ አስነሣ ።
ቀሰቀሰ፡ ቀሰረ ።
ቀሰቀሰ፡ በረበረ ፈተሸ ። "ሌባ በተያዘጊዜ ዘበኞች ኪሱን ይቀሰቅሱታል" ።
ቀሠብ (ዐረ ቀጸብ)፡ መቃ ውስጠ ክፍት ዕንጨት ወይም ብረት ("(ማሕ. ፬፥ ፲፬)") ።
ቀሰብ፡ ባሕረ ጃን ።—ቀሠብ ።
ቀሠብ፡ ባሕረ ጃን የበቅሎ ዕቃ ጌጥ ዐልፎ ዐልፎ ብስ ነዳላ የሚታይበት፡ በያይነቱ ቀለም ያለው ወረቀት ።
ቀሠብ፡ ውድ የሬት ሽቱ ። በግእዝ "ዐልው" ይባላል ።
ቀሰተ (ቀስተወ)፡ ደገነ አጐበጠ ።
ቀሰተ፡ (ቋተ)፡
ቀሰተ፡ (ቋተ)፡
ቀሠጠ (ቀሢጥ - ቀሠጠ)፡ በስውር ከፍሎ ሰረቀ ወሰደ፡ ዐበለ ።
ቀሰጠ፡ ሰረቀ/ቀሠጠ ።
ቀሠፈ (ቀሢፍ - ቀሠፈ)፡ መዓት አመጣ፡ ዕድሜ አሳጠረ፡ ቀጪ ቀጠፈ፡ በድንገት ገደለ አጠፋ ባጪር አስቀረ ዐፍለኛን ("(ዘዳ. ፭፥ ፲፩ ። ፪ሳሙ. ፮፥ ፯)") ።
ቀሠፈ፡ ሰቀዘ ወጠረ አስጨነቀ፡ ጐን በስ ቀና አላሠኝ አለ ።
ቀሠፈ፡ ደገነ አጐበጠ ።
ቀሲስ፡ ቄስ ።"አቡነ ቀሲስ" እንዲሉ ።
ቀሳ (ዕብ ቃጻህ - ለየ)፡ ብቻ ብቻነት (ልዩነት ") ። ፈረንጆች "ካራንቴን" ከሚሉት ጋራ ይሰማማል ።
ቀሳ ወጣ፡ ከቤት ወደ ዱር ኼደ፡ በደን ተቀመጠ ተኛ ታመመ፡ ከቤተ ሰቡ ተለየ (የሚጋባ በሽታ ተስቦ ስለ ያዘው ") ።
ቀሣሚ፡ የቀሠመ/የሚቀሥም (ለቃሚ ሰብሳቢ ንብ ጥንዝዛ ጣዝማ ዝንብ ብራብሮ ወፍ ") ።
ቀሳሪ፡ የቀሰረ/የሚቀስር (ገታሪ ") ።
ቀሳራ - ቅስር፡ የተቀሰረ (ገታራ ግትር ") ።
ቀሳሽ (ሾች)፡ የሚቀስ (ቄስ የሚኾን ") ።
ቀሳቀሰ፡ በራበረ ።
ቀሳቀሰ፡ አነቃቃ ።
ቀሳች፡ የቀሰተ/የሚቀስት (ደጋኝ አጕ ባጭ ") ።
ቀሣጢ፡ የቀሠጠ/የሚቀሥጥ (ዐባይ ሌባ ") ። "ቀሣጢ ሌባ" እንዲሉ ።
ቀሣጢነት፡ ቀሣጢ መኾን (ሌብነት ዐባይነት ") ።
ቀሣፈተ፡ ቀላመደ ዐበለ ዋሸ ወላ ወለ ዘላበደ ቀባጠረ ቀባዠረ፡ ቅሥፈት የሚያመጣ ነገር ተናገረ ።
ቀሣፊ፡ የቀሠፈ/የሚቀሥፍ (ገዳይ አጥፊ መልአከ ሞት ") ።
ቀሣፋች፡ የቀሣፈተ/የሚቀሣፍት (ዐ ባይ ወላዋይ ቀባዣሪ ") ።
ቀሣፋችነት፡ ወላዋይነት ቀባዣሪነት ።
ቀስ አለ፡ ዝግ አለ ።
ቀስ አለ፡ ዝግ አለ ።—ቀሰሰ ።
ቀስ፡ ዝግ ። "ቀስ በል !" "ቀስ ብሎ እን ዲሉ" ። (ተረት)፡ "ሴትና ቄስ ቀስ" ።
ቀስ፡ ዝግ ።—ቀሰሰ ።
ቀስመን፡ የልብ ቃታ፡ ዘሩ ቀሰመ ነው ።
ቀስመን፡ ግድ ግዴታ ።
ቀሥም፡ አዝመራ ("(ግእዝ)") ።
ቀስር፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀስቃሽ (ሾች)፡ የቀሰቀስ/የሚቀሰቅስ (ነቅናቂ አስነሽ፡ በርባሪ ፈታሽ ") ።
ቀስቅስ፡ የልዑል ራስ ካሳና የልዑል ራስ እምሩ ፈረስ ስም (ነቅንቅ አንቃ አስነሣ ማለት ነው ") ።
ቀስተ ደመና፡ የደመና ደጋን (ባላ፬ ሕብር የማሪያም መቀነት ") ። "በበልግ ዝናም ጊዜ ጫፍና ፉ በሰሜንና በደቡብመካከሉ ወደ ላይ ወደ ሰማይ ኹኖ ይታያል ። ከላይ ወደ ታች አረንጓዴ ቀይ ብጫ ሰማያዊ ቀለም አለው" ።
ቀስተ ደመና፡ የደመና ደጋን (ባላ፬ ሕብር የማሪያም መቀነት ") ። "በበልግ ዝናም ጊዜ ጫፍና ፉ በሰሜንና በደቡብመካከሉ ወደ ላይ ወደ ሰማይ ኹኖ ይታያል ። ከላይ ወደ ታች አረንጓዴ ቀይ ብጫ ሰማያዊ ቀለም አለው" ።
ቀስተኒቻ፡ የንጨት ስም (ለቀስት ለወስፈንጠር የሚኾን ጕብጠት የሚስማማው ዕን ጨት ") ። ኹለተኛ ስሙ "ሰሪቴ" ይባላል ። "መቃን" ተመልከት ።
ቀስተኛ (ኞች)፡ በቀስት የሚዋጋ ባለ ቀስት (አውሬ የሚያድን ነዳፊ ") ("(ዘፍ. ፳፩፥ ፳)") ።
ቀስተኛ (ኞች)፡ በቀስት የሚዋጋ ባለ ቀስት (አውሬ የሚያድን ነዳፊ ") ("(ዘፍ. ፳፩፥ ፳)") ።
ቀስቱን ለጠጠ፡ ሳበ ወጠረ ገተረ አ ዘገበ ።
ቀስቱን ለጠጠ፡ ሳበ ወጠረ ገተረ አ ዘገበ ።
ቀስታ፡ ዝግታ ። በግእዝ "ድቡት ጽሚት" ይባላል፡ ንኡስ አገባብ ነው ። "ታቦት የተሸከመ ቄስ በቀስታ ይኼዳል" ።
ቀስት (ቶች)፡ የወስፈንጠር/የፍላጻ መወርወሪያ ደጋን (የጦር መሣሪያ ") ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፬)") ።
ቀስት (ቶች)፡ የወስፈንጠር/የፍላጻ መወርወሪያ ደጋን (የጦር መሣሪያ ") ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፬)") ።
ቀሥፋታ፡ ዝኒ ከማሁ ለቀሣፋች ።
ቀረ (ቀረየ)፡ ተረፈ ዳነ ተተወ ("ሳይያዝ ሳይገደል ቀረ ") ።
ቀረ፡ ቈየ ዘገየ፡ ተቀመጠ ። "ሳይኼድ ሳይመጣ ቀረ፡ እቤት ቀረ" ።
ቀረ፡ ቆመ ተከለከለ ። "በኤልያስ ዘመን ዝናም ቀረ" ። ለእስራኤል የሚወርድ መና በፊንቆን ቀረ ።
ቀረ፡ ተለወጠ ዐለፈ ።
ቀረ፡ አነሰ ጐደለ ። "ሳይመላ ቀረ" ።
ቀረ፡ ዐጣ ነጣ ባዶ እጅ ኾነ ። መና ቀረ ።
ቀረመተ (ቀሪም - ቀረመ)፡ ከፈለ ተነተነ ("ሥጋን ዐጥንትን ") ።
ቀረመት - ቅርምት - ቅርጫን፡ የሙዳ ክፍል ።
ቀረሰሰ - ቀሰሰ)፡ አንቀረሰሰ፡ (ጥ፱) አዘገመ በቀስታ አስኬደ ወሰደ ። ትግሬ ሐባብም "ቀርሰሰ" ብሎ ከሳ ይላል ።
ቀረሰስ - ቀርሳሳ፡ የተንቀረሰሰ (ዝግተኛ ዘገምተኛ ") ።
ቀረረ (ቈሪር - ቈረ)፡ ጠለለ ጠራ ጥራት አገኘ (ቅራሪው አተላው በታች ጥሩው በላይ ኾነ ") ።
ቀረረ፡ የጦር ግጥም ገጠመ (አጕራራ ") ።
ቀረራ፡ የርሾ ጥላይ ።
ቀረርቱ፡ ሽለላ የጦር ዘፈን ።
ቀረሮ፡ የዛፍ ስም ።
ቀረሸ፡ ምግብን ከሆዱ ጥቂት ፍልቅ አደረገ አወጣ፡ አስታወከ አፈሰሰ ሕፃኑ ።
ቀረሸመ፡ ገጨ ሰበረ ።
ቀረሻሸመ፡ ሰባበረ ።
ቀረሻሽምቦ፡ ቅጠል ።—ቀረሸመ፡
ቀረሻሽምቦ፡ በቀላል የሚሰበር ዕንጨት (አገዳው ውስጠ ክፍት የኾነ ") ። "የጨቆ የረግረግ ቅጠል፡ መሽረብ ውሃ መምጠጫ መጠጫ ዕፅ" ።
ቀረሽ፡ የቀረው/የጐደለው ። "ዱላ ቀረሽ ላባ ቀረሽ" እንዲሉ ።
ቀረቀረ (ቀቀረ)፡ አገባ ሸጐረ ለገደ ወረወረ ።
ቀረቀረ (ትግ ቀርቀረ)፡ ከረከረ፡ አ ሳጥሮ ቈረጠ ።
ቀረቀረ፡ ጐረሠ በላ ። (ተረት)፡ "ጦም ከማደር ዳቦ ቀርቅር" ።
ቀረቀረ፡ ጥይትን ለጠመንዣ አጐረሠ ።
ቀረቀበ (ቀረበ)፡ ኹለት ሸክምን ጭ ንትን ባንድነት አሰረ ወደነ ጠመረ ቈረኘ አረተ ።
ቀረቀፈ፡ ከረከረ ።
ቀረበ (ቀርበ)፡ ቅርብ ኾነ (ለጠቀ ተጠጋ ") ("(ዘፍ. ፳፱፥ ፲)") ።
ቀረበ፡ ነዳ ወሰደ ከብትን ።
ቀረበ፡ እሰው ፊት ተቀመጠ ገበታው ።
ቀረበበ - ገረበበ)፡ አንቀረበበ፡ እንገረበበ፡ አንቀረደደ አንከረፈፈ ።በተገብሮነትም ይፈታል ።
ቀረበጠ)፡ አንቀራበጠ፡ ካንዱ ስፍራ ወደ ሌላው አዛውሮ አስቀመጠ ።
ቀረባ (ኦሮ)፡ ወረንጦ (ጫፍና ጫፉ በመቃረብ እሾኸን ሥንጥርን ቈንጥጦ ከእግር ከገላ የሚነቅል መሣሪያ መቈንጠግና መዘ ንጠያ ") ።
ቀረባ፡ የመንዳት ሥራ/መቅረብ ።
ቀረብ (ቀሪብ)፡ ጠጋ ለጠበቅ ።
ቀረብ አለ፡ ጠጋ አለ፡ ቀረበ ።
ቀረት አለ፡ ቅዝዝ አለ፡ ጥቂት ጐ ደለ ስፍሩ ።
ቀረት፡ አነስ ጐደለ ።
ቀረነ (ቀሪን - ቀረነ)፡ ቀንድ አወጣ፡ ጠላ ወጋ ።
ቀረነተ፡ በቅራና አጥብቆ አሰረ ቀረ ቀበ ።
ቀረና (ትግ - ቀርንዐ)፡ ቀንድ ቀንድ አለ፡ ሸተተ ገማ ። "ጐረናን" እይ ።
ቀረንደላ፡ የተቃጠለ እኸል ።
ቀረንጠሎ፡ ባሪያ (የባሪያ ወገን ወይም ልብሱ ") ።
ቀረዋ፡ ከወደ ጫፉ ቀና ያለ ጐራዴ ።
ቀረዋ፡ የብረት ቍና (በሐረርጌ የሚገኝ ") ። አንዳንድ ሰዎች "ቀረዋ" የሚባል ፈረንጅ ስላመጣው በርሱ ስም "ቀረዋ" ተባለ ይላሉ፡ እውነት መኾኑን እንጂ ።
ቀረዘ (ቀረጸ)፡ ያዘ እነሣ ተሸከመ ።
ቀረደደ (ቀረፀ)፡ ቈረጠ ቈረሰ ገመሰ (ጐመንን እንጀራን ምድርን ") ።
ቀረጠ (ቀረፀ - ጸ)፡ ቈረጠ አሾለ ።
ቀረጠ፡ ዕዳሪ አወጣ ።
ቀረጠ፡ ወደ ገበያ መጥቶ ከሚሼጥ ነገር ላይ አነሣ ወሰደ ("(ማር. ፪፥ ፲፬)") ። ወይም በዚህ ፈንታ አሞሌ ብር አላድ ሩብ መሐለቅ ተቀበለ ።፫ኛውን ዐጠረ ባ፭ኛ ተራ ተመልከት፡ "ቀረጸን" እይ ።
ቀረጠፈ (ቀረጠ - ቀጠፈ)፡ የጌሾን ቀንበጥና ቅጠል በቅርብ በቅርብ እየመታ ቈረጠ አጠቀነ አደቀቀ ። "የጐመንና የሥጋሲኾን ቀረደደ ከተፈ o ያሠኛል" ።
ቀረጠፈ፡ ሰውነትን ዐመመ ።
ቀረጣ፡ መቅረጥ ።
ቀረጣጠፈ፡ ቈራረጠ አጠቃቀነ አደ ቃቀቀ ።
ቀረጣጠፈ፡ ዐማመመ ።
ቀረጥ (ቀረፅ)፡ ካሥር አንድ ዐሹራ ።
ቀረጥ (ጦች)፡ ያነስተኛ ዛፍ ስም (ሰዎች እየቀረጹ የጭራ የጅራፍ የማማሰያ የማንካ የወስፌ ዕንወት ያደርጉታል።")
ቀረጨመ)፡ ተቀራጪመ፡ ተሰበሰበ ተጠራቀመ ተቀናበረ ።
ቀረጪ)፡ አንቀራጩ፡ ቈረጠመ አንቀጫቀጨ (ቈሎን አፋጩ ጥርስን ") ።
ቀረጪጪ፡ አጥብቆና አጥልቆ ነከሰ ጐዳ አሳመመ (እስካጥንት ድረስ ") ።
ቀረጸ (ቀሪጽ - ቀረጸ)፡ ቀረጠ ዐነ ጠጠ ፈለፈለ ጐበጐበ አሰመጠ አሰነበረ ነቀሰ ።
ቀረፈ (ቀሪፍ - ቀረፈ)፡ ላጠ መለጠ ለጠጠ (ቅርፊትን አስወገደ ") ። ሰበረ ፈለጠ ነጠለ አነሣ ።
ቀረፈ፡ ተወ አጠፋ ።"ቂሙን ቀረፈ" እንዲሉ ።
ቀረፈፈ - ከረፈፈ)፡ አንቀረፈፈ፡ አረዘመ አንከረፈፈ አንቀረበበ ። በተገብሮነትም ይፈታል ። "ቀረደደ" ብለኸ "ኣንቀረደደን" እይ ።
ቀረፈፍ - ቀርፋፋ - ከረፈፍ - ከርፋፋ፡ ቂል ።
ቀረፋ፡ መቅረፍ ።
ቀረፋ፡ ሽቱነትና ቅመምነት ያለው ቅርፊት (ከባሕር የመጣ ") ("(ዘፀ. ፴፥ ፳፫ ። ኢሳ. ፵፥ ፳፬ ። ራእ. ፲፰፥ ፲፫)") ። በግእዝ "ቀንሞን" ይባላል ።
ቀሪ (ዎች)፡ የቀረ/የሚቀር (ተለዋጭ ዐላፊ የማይፈለግ ነገር ") ።
ቀሪ፡ አባት እናቱን ቀብሮ ሳይሞት የሚቈይ (ቋሚ ") ።
ቀሪቦ፡ ሞኝ ሰው ብርታት የሌለው ።
ቀሪቦ፡ ወዲያው ተበጥብጦ የሚጠጣ የዳር አገር ጕሽ ።
ቀሪነት፡ ቀሪ መኾን (ዐላፊነት ") ።
ቀራ፡ ሌሊት ከብትን ጠበቀ ("(ጐዣም)") ። ዘሩ በግእዝ "ቀርዐ" ነው ።
ቀራረመ፡ ለቃቀመ፡ ሰባሰበ።
ቀራረፈ፡ መቀራረፍ፡ መመላለጥ መላላጥ መፈ ላለጥ ።
ቀራቅር፡ በጠገዴ ወረዳ የሚገኝ ተማ ።
ቀራቢ (ዎች)፡ የሚቀርብ/የሚነዳ/የሚጠጋ (ነጂ ") ።
ቀራንዮ፡ በኢየሩሳሌም ውስጥ ያለ ቦታ ("የራስ ስፍራ" ማለት ነው ") ።
ቀራውሎ፡ ሞኝ ቂል።
ቀራጭ (ጮች)፡ የቀረጠ/የሚቀርጥ (እሿይ ዐጣሪ የገበያ ግብር ተቀባይ ") ("(ማቴ. ፱፥ ፲ - ፲፩ ። ሉቃ. ፫፥ ፲፪)") ።
ቀራጭነት፡ ቀራጭ መኾን ።
ቀራፊ (ዎች)፡ የቀረፈ/የሚቀርፍ/የሚ ልጥ/የሚመልጥ (ሰባሪ ፈላጭ ") ። "የሙጋድ ዕንጨት አቅራቢ" ።
ቀራፎ (ዎች)፡ የቅል ስባሪ ፋጋ፡ ቂል ሰው ።
ቀርም፡ የፍሬ፡ ለቀም፡ (ግእዝ) ።ሰው፡ እንዳቅሙ፡ እኸል፡ እንደ፡ ቀርሙ፡ እንዲሉ።
ቀርቀም፡ ቈረቈረ ።
ቀርቀም፡ በውሃ ዳር የሚበቅል ታናሽ ቅጠል ።
ቀርቀሬ (ቀልቀላዊ)፡ የቀርቀር (ቈላ ጐድጓዳ የታች ታች ") ።
ቀርቀር (ቀልቀል)፡ ገደል ተራራ ።
ቀርቀቦ፡ ማንቀርቀቢያ ሰፌድ ።
ቀርቃሪ፡ የቀረቀረ/የሚቀረቅር (አግቢ ሸጓሪ ") ።
ቀርቃሬ፡ ቀባ መሪ ወፍ ("(ጐንደር)") ።
ቀርቃቢ፡ የቀረቀበ/የሚቀረቅብ (ኣሳሪ ወዳኝ ") ።
ቀርቃባ (ቦች)፡ በኹለት ወገን የታ ሰረ መንታ ጭነት ።
ቀርቃባ፡ ጠፍር፡ ካንዳንድ በኩል ጫፉ እየታጠፈ የተሰፋ ቅራና ("የቀርቃባ ጠፍር ") ።
ቀርበብ - ቀርባባ፡ የተንቀረበበ/የሚንቀረበብ (ቀርደድ ቀርዳዳ ከረፈፍ ከርፋፋ ዦሮ ትልቅ ሰው ") ።
ቀርበቦ (ዎች)፡ በጋን ቂጥ የተበጀ የበሬ ግንባር ቈዳ ሚዛን ቍና ። "እስላም በመንደሯ በቀርበቦ ትማታለች" እንዲሉ ።
ቀርበታ፡ ሆድ (ሆደ ትልቅ ") ።
ቀርበታ፡ የውሃ አቍማዳ ።
ቀርበታ፡ የውሃ ኣቍማዳ ።
ቀርቦታል፡ ተጠግቶታል ። "ደጉን ሰው መንፈስ ቅዱስ ቀርቦታል፡ ክፉውን ሰው ሰይጣን ቀርቦታል" እንዲሉ ።
ቀርነ በግዕ፡ የበግ ቀንድ ("እሱን የሚመስል የድጕስ መሣሪያ ") ።
ቀርን (ግእዝ)፡ ቀንድ ።
ቀርካሓ፡ ቀርክሓ፡ (ከርካዕ)፡ የዛፍ፡ ስም፡ ውስጠ ክፍት፡ ዕንጨት ።እንዝርት፡ ተራዳ፡ ሣጠራ፡ ይኾናል፡ ለቤት፡ ሥራም፡ ያገለግላል ።
ቀርዱ፡ የአራራት ተራራ ።
ቀርዳጅ፡ የቀረደደ/የሚቀረድድ (ቈራጭ ገማሽ ") ።
ቀርጠሙሽ፡ የቀድሞ ዘመን የጋሻ ጌጥ ። "የሙሽ ቅርጥ" ማለት ይመስላል ። "ቅርጫንቀረመት ቀረጠ" ።
ቀርጣ፡ ዕዳሪ በማረሻ መስቀልኛ የሚ
ቀርጣፊ፡ የቀረጠፈ/የሚቀረጥፍ ።
ቀርጥ፡ የርሻ ክፍል መዛሮ ።
ቀሸ፡ አኰራ ለጠጠ ባነጋገር ።
ቀሸመደ፡ በፍጥነት ሰበረ አነከተ ።
ቀሸመድ - ቀሽማዳ - ቅሽምድ፡ የተቀ ሸመደ (ሰባራ ስብር ደካማ ") ።
ቀሸማመደ፡ ሰባበረ አነካከተ ።
ቀሸረ (ቀተረ)፡ ከሸነ/አሳመረ ።
ቀሸረ፡ ነፋ ቀበተተ ሆድን ።"ገሸረን" እይ ።
ቀሸረረ፡ ከሳ ደረቀ ።"ከሸለለን" ተመልከት ።
ቀሸረር - ቀሽራራ፡ የከሳ የደረቀ/ደረቅ ።
ቀሸቀሸ - ከተከተ)፡ ተንቀሻቀሸ፡ ተሰባበረ ተንከታከተ ።
ቀሻሪ፡ የቀሸረ/የሚቀሽር (ከሻኝ አሳማሪ ") ።
ቀሽመሪ፡ ሠቅጌጠኛ መታጠቂያ ።"መሪ ቄስ" ማለት ይመስላል ።
ቀቀለ፡ አሞቀ አፈላ አበሰለ አነፈረ (እኸልን ሥጋን ")፡ ወጥ ሠራ ("(ዘፀ. ፴፬፥ ፳፮ ። ፪ነገ. ፮፥ ፳፱ ። ሰቈ. ፬፥ ፲ ። ዘካ. ፲፬፥ ፳፩)") ።
ቀቀረ (ጸለወ)፡ ዦሮውን መለሰ ጣለ (ለመስማት ለማድመጥ ") ።
ቀቀበ፡ ነፈገ ሠሠተ ሰገበ ።
ቀቀበታም፡ ሥሥታም ንፉግ ስግብግብ ("ስገባ በል (ዮሴፍ)") ።
ቀቀበት (ቀቀባ - ሰገባ)፡ ንፍገት ሥሥት ።
ቀቀተ (ቄቀየ)፡ ነፈገ ጮቀ ቤሰ ሠሠተ ።
ቀቀት - ቅቅት፡ ንፍገት ሥሥት ።
ቀቃ - ቍቁ (ከካ)፡ መታ አቈሰለ ነደለ ፈነቀለ ። "ቃቃንን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው ።
ቀቃሪ፡ የቀቀረ/የሚቀቅር ።
ቀቃይ (ዮች)፡ የቀቀለ/የሚቀቅል (አፍሊ አንፋሪ ወጠ ሠሪ ") ። "ንፍሮ ቀቃይ ዶዮ ቀቃይ" እንዲሉ ።
ቀቅ፡ ትንሽ ካሳ ለቈሰለ የሚሰጥ ።
ቀቅ፡ ዋግ ብትን ድልኸ የሚመስል የእኸል በሽታ ስንዴን የሚመታ ቀጭ ብርድ ።
ቀበለ) አቀበለ፡ እጅ በጅ ሰጠ አስረከበ እሲያዘ ("(ነሐ. ፲፫፥ ፴፩)") ።
ቀበሌ (ዎች)፡ ገደማ/ዘንድ(ዳ)/ጋ ።
ቀበሎ፡ ድር ሲቋጠር በስተጥርስ በኩል ተቀምጦ መቀበል ።
ቀበረ (ቀቢር ቀበረ)፡ ራስን ወደ ምዕራብ እግርን ወደ ምሥራቅ አድርጎ ሬሳን አንጋለለ በዠርባ አስተኛ፡ በድንን ማን ኛውንም ነገር ዐፈር አለበሰ ሸፈነ፡ በጕድጓድ ውስጥ ደፈነ ደበቀ ሸሸገ ።
ቀበረ፡ ሰውን ጐዳ ጨቈነ (እንዳይታወቅ እንዳይከብር እንዳይጠቀም አደረገ ") ። (አዝማሪ)፡ "የወዲያ ሰዎች ክፋታቸው ሬሳ አስቀምጠው መብላታቸው" ። "የ.........ሰው መልካም ወንድሙን ሳይቀብር አይበላም" ("(ጦቢ. ፩፥ ፲፯፡ ፪፥ ፯)") ።
ቀበረረ) አንቀባረረ፡ አቀማጠለ አንደላቀቀ አሞላቀቀ (የልጅን ጠባይ አበላሸ ") ። በተገብሮነትም ይፈታል።
ቀበረር - ቀብራራ፡ የተንቀባረረ (እንቅ ብር ቅምጥል፡ አያት ያሳደገው ልጅ ") ።
ቀበራ፡ ደፈና (የመቅበር ሥራ ዐፈር ") ።
ቀበራርት፡ ዝኒ ከማሁ (የካህናት ዐማርኛ ") ።
ቀበር፡ የቀበረ ። (ተረት)፡ "ማን ይንገር የነበር፡ ማን ያርዳ የቀበር" ።
ቀበርቾ፡ መድኀኒትነት ያለው ዕንጨት፡ ሥሩ ወፍራምና ሞላላ ነው ። ሰው ትኵሳት በያዘው ጊዜ ይታጠነዋል፡ ትኵሳትንም በላብ የሚያጠፋና የሚቀብር ስለ ኾነ ቀበርቾ ተባለ ።
ቀበርቾ፡ የዕፅ ስም ። ቀበረ ።
ቀበሮ (ዎች)፡ ያውሬ ስም (የተኵላ ወገን የዱር ውሻ የበግ ጠላት ") ። (ተረት)፡ "ቀበሮ የበሬ ቍላ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ት ውላለች" ። "ቀበሮ" ማለት በቈፈረው ጕድጓድ ውስጥ ተቀብሮ ገላውን መደበቁን ያሳያል ። ተባቱም እንስቱም ቀበሮ ይባላል ። ኹለቱን ለመለየት ነው ።
ቀበሮች፡ ቀበሮዎች ("(ሕዝ. ፲፫፥ ፬)") ።
ቀበሮዋ - ቀበሮዪቱ፡ ያች ቀበሮ ።
ቀበሮው፡ ያ ቀበሮ ።
ቀበቀበ (ገበገበ)፡ ኹለተኛ በርጥብ ዐረሰ ዐየመ ኣለሰለሰ ።
ቀበቀበ፡ ተከለ ቸከለ ።
ቀበቀበ፡ እንደ ገና ብረትን ቀጠቀጠ ዐደሰ አሾለ አሰላ ።
ቀበቀበ፡ ደጅ መታ ቍር ቍር አደ
ቀበቀብ - ቀብቃባ፡ ገበገብ/ገብጋባ (ንፉግ ሥሥታም ") ።
ቀበተተ፡ አሳበጠ ነፋ ወጠረ ነረተ ። "የነፋሽ ፥ የቀበተተሽ" እንዲል ኵስኵስት ተጫዋች ። "ቀበጠጠን" እይ፡ የዚህ ለውጥ ነው ።
ቀበታ፡ የባጥ ገበታ ዋልታ ። "ቀና ገ" መወራረሳቸውን አስተውል ።
ቀበቶ (ዎች)፡ ባንድ ወገን በጫፉ ላይ ዘለበት ያለበት ሰፊ ወይም ጠባብ ከነት ከተንቤን የተበጀ መታጠቂያ (የሱሪ የቀሚስ የጐራዴ የሽጕጥ መያዣ ") ።
ቀበነነ (ትግ. ሐባ ቀበነ በሰና)፡ ነፋ/ወጠረ ቀበተተ ።
ቀበና (ኦሮ)፡ ቀዝቃዛ ውሃ፡ ወይም ሌላ ነገር ።
ቀበና፡ በአዲስ አበባ ውስጥ በስተምሥራቅ ያለ ወንዝ፡ ቀበሌውም በወንዙ ስም ቀበና ይባላል ።
ቀበኛ (ቀማ)፡ ልብስ የሚበላ ከብት (በሬ ላም አህያ በቅሎ ") ። "የልብስ ቀማኛ" ማለት ነው ። ሲበዛ "ቀበኞች" ያሠኛል ።
ቀበዘ - ቃበዘ፡ ወዲያና ወዲህ ዐይኑን ወረወረ፡ ዦሮውን ጣለ (የጠፋውን ለመሻት ወሬ ለመስማት ዞረ ዛበረ ባዘነ ") ።
ቀበዝባዛ - ቅብዝብዝ፡ የተቅበዘበዘ (ቅንዝንዝ ባካና ") ።
ቀበዞ፡ የቀበዘ (ፊትና ኋላ የሚሮጥ የሚያይ የሚመለከት እግረ ቀላል ") ።
ቀበያውበጠ፡ ቀላወጠ ።"የቅኔ ' ቤት ' ዐማርኛ ' ነው" ።
ቀበደደ (ቀበተተ)፡ መታ ደበደበ ሰረረ ። "ቀበጠጠን" አስተውል ።
ቀበደድ - ቀብዳዳ - እንቅብድ -
ቀበጠ (ቀብጸ)፡ ጨዋነትን ጭምት ነትን ዐጣ (ተወዘወዘ ተነቃነቀ ዘለለ ፈነደቀ ተጫወተ ") ። (ተረት)፡ "የቀበጡ ለት ሞት አይገኝም" ። "ወበራን" እይ ።
ቀበጠጠ (ቀበለ)፡
ቀበጠጠ፡ ቀበተተ ።
ቀበጢና፡ የቀበጠች (ዕረፍት አልባ ") ። ፫ኛውን "ቅብጢ" ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀበጣጠረ፡ ለፋለፈ መላልሶ ተናገረ ።
ቀበጥ (ጦች)፡ እብድ ዐይነት (ልጅ አይሉት ዐዋቂ ከፈሱ የተጣላ ሰው አፍ ቂጡ የሣቀ ") ።
ቀበጥባጣ - ቅብጥብጥ፡ የተቅበጠበጠ (ቍንጥንጥ ብስጩ ") ።
ቀቢ (ዎች - ቀባዒ)፡ የቀባ/የሚ ቀባ (ለቅላቂ ደላሽ ") ። "ቀለም ቀቢ" እንዲሉ ። "ቅቤ"፡ ከተናጠ ወተት የሚገኝ ውጤት ። የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል። "ለጋ ቅቤ" "ለስታ ቅቤ" እንዲሉ ።
ቀባ (ስም)፡ ማጓ (በዋሻ በፍርኵታ በገደል ንቃቃት በውስጠ ክፍት ዛፍ መካከል ያለ ንብ ከነማሩ ") ።
ቀባ (ቀብዐ)፡ ላከከ ለቀለቀ ደለሰ ቅቤን ። የሕፃንን ሕዋሳት ሜሮን አስነካ፡ በራስ ላይ ዘይት አፈሰሰ፡ አከበረ ሾመ ሥልጣን ሀብት መብት ችሎት አሳደረ ዐደለ ሰጠ፡ ካህን ነቢይ ንጉሥ አደረገ ። (ተረት)፡ "አልቀባም ብትል ትመስክር" ።
ቀባ፡ ኀጢአተኛ በደለኛ አስመሰለ፡ ስም አሳደፈ ።
ቀባ መሪ፡ ሰውን ወደ ቀባ የምትመራ ወፍ ። በቡልጋ "ቡሊ"፡ በመራቤቴ "ባቲ"፡ በጐንደር "ቀርቃሬ" ትባላለች ።
ቀባ ቈራጭ፡ እዱር ኼዶ ቀባ የሚቈርጥ ሰው ።
ቀባ፡ ኰላ ዐደሰ (ጌጥን በወርቅ ቤትን በቀለም በበረቅ ") ።
ቀባሪ (ዎች)፡ የቀበረ/የሚቀብር (ዐፈር መላሽ ደፋኝ ") ። (ተረት)፡ "ቀባሪ በፈጣሪ" ። "ደኸየ" ብለኸ "ድኻን" እይ ።
ቀባሪ፡ የጐዳ/የሚጨቍን ። "ድኻ ቀባሪ" እንዲሉ ።
ቀባሪነት፡ ቀባሪ መኾን ።
ቀባርዋ፡ በወልቃይት የሚደረግ የዱላ ምክት ። በመርሐ ቤቴና በዜጋመል ቈላ አ ባት ልጁን አጋም ሥር አቁሞ የዱላ ምክት ያስተምረዋል ። በመቺና በመካች መካ ከል ወደ ላይ አሳይቶ እግርን፡ ወደ ታች አመልክቶ ትከሻን በማለት ታላቅ ቅልጥፍና ይታያል ። ይኸንንም ትምርት ያወቀ አንድ ሰው ዐሥር ሰው ሊመታ ይችላል ። የቀባርዋ ምስጢር ሸማን በግራ እጅ ላይ ጠቅሎ ራስን መከለል መጋረድ ነው ። በመቺና በተ መቺ (በመካች) መካከል ያለውንም ያመታት ስም አንቷን ዳባዲ እስካሥር ይቈጥረዋል ።
ቀባሮች፡ የቀበሩ/ቀባሪዎች ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፬ - ፲፭)") ።
ቀባበረ፡ መላልሶ ቀበረ ደፋፈነ ።
ቀባባ፡ መላልሶ ቀባ ደላለሰ አባበሰ ።
ቀባዠረ፡ ቃዠ ወዣበረ ዘባረቀ (የኾነ ያልኾነውን ተናገረ ") ። "ቀባዠረን" ተመልከት ።
ቀባዣሪ (ዎች)፡ የቀባዠረ/የሚቀባ ዥር (ወዣባሪ ዘባራቂ ") ።
ቀባጠረ፡ አገኝ ዐጣውን የባጥ የቈ ውን ተናገረ (ለፈለፈ ዘበዘበ ") ። "ቀባዠረን" ተመልከት ።
ቀባጣሪ (ሮች)፡ የቀባጠረ/የሚቀባ ጥር (ተናጋሪ ለፍላፊ ") ።
ቀባጣሪ፡ አማጭ (የጋብቻ መካከለኛ ") ። "ገለገለ" ብለኸ "ግልገልን" እይ ።
ቀባጣሪነት፡ ቀባጣሪ መኾን (ለፍላ ") ።
ቀባጭ (ጮች)፡ የቀበጠ/የሚቀብጥ ።
ቀብር፡ መቃብር (የሬሳ ማጋደሚያ ") ። (ግጥም)፡ "ቀብር ቀብር አሉ፡ ቀብር ምናለበት፡ ደግ ሥራ ሠርቶ ገብቶ ቢተኙበት" ። ቀበሮ (ቀበረው - ግእዝ) ።
ቀብር፡ ሥርዐተ መቃብር (ለቅሶ ") ። "እቀብር ውዬ መጣኹ" እንዲሉ።
ቀብቀብ አለ፡ ተንቀበቀበ ።
ቀብቃቢ፡ የቀበቀበ/የሚቀበቅብ (ዐራሽ ቀጥቃጭ ቸካይ ") ።
ቀብቃባነት፡ ቀብቃባ መኾን (ገብጋ ") ።
ቀብታች፡ የቀበተተ/የሚቀበትት (ነፊ አሳባቹ ") ።
ቀብዣራ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀብዥር፡ የነጋሪት ድምጥ ። "አብጅርን" አስተውል ።
ቀብድ - ቃብዱ (ኦሮ)፡ መያዣ (ዕቃን ከመግዛት በፊት ለሸያጩ የሚሰጥ ገንዘብ ") ። በግእዝ "ዐረቦን" ይባላል ።
ቀተለ (ቀቲል - ቀተለ)፡ ገደለ (ነፍስ አሳለፈ ") ። "ጕራጌ እግዜር ይማርኸ ቢሉት፡ ይቀትለኝ ማን ኹኖ እንዳለ" ።
ቀተረ (ቀቲር - ቀተረ)፡ ፮፻ሰዓት ኾነ፡ ፀሓይ ወይም ጮራው በሰማይ መካከል በራስ አንጻር ታየ፡ ከዚህ የተነሣ ጥላ ታጣ ።
ቀተረ፡ ቀረቀረ/ሸጐረ ።"ገተረንና ቀሰ ረን" ተመልከት ። "ገና ቀ'ሰና ተ ይወራረሳሉና፡ ፫ቱ ኹሉ በምስጢር አንድ ናቸው" ።
ቀተረ፡ ነፋ አሳበጠ ወጠረ ቀበተተ ።"የቂል በትር ሆድ ይቀትር" እንዲሉ ።"ቀሸ ረን" አስተውል ።
ቀተራ፡ ርኤም፡
ቀተራ፡ በኀይል ጮኸ አገሣ ጐደራ ።
ቀታሪ፡ የቀተረ/የሚቀትር (ቀርቃሪ
ቀታሪ፡ የቀተረ/የሚቀትር (ቀርቃሪ ሸጓሪ ነፊ ወጣሪ ") ።
ቀትረ ቀላል፡ ቅርጠ ቀላል ("ወፍ ራም ያይዶለ ሰው ") ።
ቀትር፡ ቁመና ("የሰውነት ቅርጥ ቀጥ ያለ ") ።
ቀትር፡ እኩለ ቀን ("አውራ ተሲያት ሙቀት የሚጸናበት ጊዜ ") ። "ጌታችን በቀትር ተሰቀለ" ።
ቀነ ጐደሎ
ቀነሰ (ነቀሰ)፡ ነሣ አጐደለ አሳነስ ። "ሴትዮ የተመላው ጠላ እንዳይፈስ ቀንሺው"
ቀነሠ፡ አጐደለ ። ቀነሰ ።
ቀነረ፡ ነፋ አሳበጠ ።
ቀነቀነ (ቈንቈነ)፡ ነቀዘ ጠነጠነ ("(ኢዮ. ፵፩፥ ፲፱)") ።
ቀነቀነ፡ መረመረ ፈተሸ ። (ተረት)፡ "ለንጉሥ የቀነቀነ ወርቅ ለግዜር የቀነቀነ ጽድቅ" ።
ቀነቀነ፡ ሠሠተ ነፈገ ።
ቀነቀነ፡ ቃኘ ዜማ ዠመረ ዘፈን አወረደ ።
ቀነቀነ፡ ቅንቅን አፈራ በርቀት በላ አሳከከ ።
ቀነቀነ፡ በቀለ ቀመቀመ ።
ቀነበረ፡ ደረቀ ጠና በእሳት በፀሓይ ተንቃቅቶ ።
ቀነበበ፡ ከበበ ክብ አደረገ ። "ጨደደን" ተመልከት ።
ቀነባ፡ ሰበረ ቀለጠመ ("(ሕዝ. ፲፯፥ ፬)") ።
ቀነተ (ቀኒት - ቀነተ)፡ በወገቡ ላይ ጠፍርን መቀነትን ጠመጠመ ታጠቀ አሰረ ሸብ አደረገ ።
ቀነኛ፡ የቀን ምሳ ዱማች በቀትር የሚበላ ።
ቀነወረ፡ ደረቀ ጠነከረ ከረረ ጨመረ፡ ዐጪር ኾነ ቈረቈዘ ።
ቀነዘ (ፈነዘ)፡ ከለፈ ከነፈ ። "ከነዘን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀነዘረ፡ አመነዘረ ሴሰነ ባንዲት ሴት የማይረጋ የማይወሰን ኾነ ሰውየው ።
ቀነዘረ፡ ፈጥኖ አደገ ረዘመ ከሌላው በለጠ እኸሉ ።
ቀነዘፈ (ቀዘፈ)፡ ዐረደ ቀነጠሰ፡ ባንድ ጊዜ ከወገብ ቈረጠ፡ መለመለ ።
ቀነዘፈ፡ እንባ አወረደ ዱብ ዱብ አ ደረገ አንጠባጠበ ።
ቀነዝናዛ - ቅንዝንዝ፡ የተቅነዘነዘ/የሚ ቅነዘነዝ (ፍንዝንዝ ክልፍልፍ ") ።
ቀነደለ፡ ቀነደበ በጣ ቈረጠ ቅንድብን፡ መጥፎ ጠጕርን ከሥሩ ለመንቀል ለማጥፋት ።
ቀነደረ (ቀነጠረ)፡ ቄደረ ኰራ ።
ቀነደሸ፡ ሰበረ አነከተ ቀንድን ሌላው ንም ። "ገነደሰን" እይ ።
ቀነደሸ፡ አረጀ ጐበጠ ። "የቀነደሸ ሽማ ግሌ" እንዲሉ።
ቀነደበ፡ ቀንድን ዐናትን መታ በቀንድ ወይም በሌላ ።
ቀነደበ፡ ቅንድብን ቀነደለ ።
ቀነደበ፡ በዋንጫ ጠጣ አጐደለ ።
ቀነዳ፡ እንደ ቀንድ ደረቀ ከረረ ። እ ከሌ ወገቡ ቀንድቶ ጐንበስ ቀና ማለት አቅቶታል ።
ቀነጀ፡ ተነጠለ (ነጠላ አንድ ብቻ ኾነ ") ።
ቀነጠሰ፡ ቀነጠበ ቈረጠ በጠሰ ጐመ ንን ሳማን ዐንገትን ።
ቀነጠረ - ቀጠረ - ነጠረ)፡ አሽቀነ ጠረ፡ አርቆ በኀይል ወረወረ ጣለ ።
ቀነጠበ (ቀንጠበ)፡ ከፍ ቈረጠ በ ጠሰ ቀነጠሰ ።
ቀነጣ ። ቀኖና፡ ሕግ ሥርዐት ደንብ ።
ቀነጣ ። ቅንጦት፡ ጥጋብ ።
ቀነጣ (ቀንጠወ - ቀነጸ ። ትግ ቀን ጥአ)፡ ታበየ ራሱን ከፍ አደረገ፡ ርስዎ ያ ለውን አንተ አለ፡ ነቀፈ አዋረደ፡ አላገጠ መስቃ ተናገረ ።
ቀነጣ፡ አንደዬ ወደ ላይ አንደዬ ወደ ታች - አለ ።
ቀነጣጠሰ፡ ቀነጣጠበ ቈራረጠ በጣጠሰ ።
ቀነጣጠበ፡ ቈራረጠ በጣጠሰ ቀነጣጠሰ ።
ቀነጨበ (ትግ ቀንጨበ - አነቀረ)፡ በጥቂቱ ተማረ ቈነጠረ ቈንጥሮ ወሰደ ።
ቀነጨበ፡ የገበጣ ጨዋታ ዠመረ ።
ቀነፈ፡ ዐጠፈ መለሰ ቀለበሰ ሸበለለ የልብስን ጫፍ ።
ቀነፌ (ቀነፋዊ)፡ የሰው ስም (ጠ ላትን ዕጠፍ መልስ ማለት ነው ") ።
ቀነፌ፡ የኔ ቀነፍ ።
ቀነፍ፡ ዝኒ ከማሁ (ሸብላይ ") ።
ቀና (ቀኒእ)፡ መቅናት ።
ቀና (ቀንአ ሐመመ)፡ ተመቀኘ፡ ምቀኛ ኾነ ። "መቀኘን" እይ፡ ከዚህ ወጥቷል ። መዠመሪያው የደግ፡ ይህ የክፉ ነው ። (ግጥም)፡ "አጐንብሼ መኼድ አላውቅ ብዬ እንደ ሰው፡ እቀና ብዬ ነው ቤቴ የፈረሰው" ።
ቀና (ቀንአ ረትዐ)፡ ቀጥ ኣለ፡ ቀጥታ ኾነ ።
ቀና (ተቀንየ)፡ ተገዛ ዕርሻ ተማረ ለመደ ሰላ ወይፈኑ ።
ቀና፡ ለማ ሰመረ በጀ ደኑ በረሓው ።
ቀና፡ ቀጥታ እውነት ። "ቀናውን ተና
ቀና፡ ታዘዘ ዕሺ በጎ አለ፡ ቅን ኾነ አሽከሩ ።
ቀና፡ ታጠቀ ገበረ አገሩ ።
ቀና አለ፡ ወደ ላይ አየ ።
ቀና፡ አላቀረቀረም ("(ዮሐ. ፰፥ ፯፡ ፲)") ።
ቀና አደረገ:ራስን ደገፈ አንተራሰ ።
ቀናሽ (ሾች):የቀነሰ/የሚቀንስ (አ ጕዳይ ") ።
ቀናተኛ (ኞች) (ቀናኢ)፡ ("(ናሆ. ፩፥ ፪)")፡ በገንዘቡ በሰው የቀና/የሚቀና (ምቀኛ ") ። (ተረት)፡ "የሙት ቀናተኛ ሚስቴን ዐደራ" ይላል ።
ቀናት - ቀኖች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች ።
ቀናት (ቀናእት)፡ የቀኑ/የሚቀኑ (ምቀኞች ") ።
ቀናነሰ፡ ነሣሣ አጐዳደለ ።
ቀናው ቀንቶታል፡ ኾነለት ኾኖለታል፡ ገባው ታወቀው፡ ጕዳዩ ተፈጸመለት ። "ግዳይ ቀናው" እንዲሉ።
ቀናፊ፡ የቀነፈ/የሚቀንፍ (ዐጣፊ ቀል ባሽ ") ።
ቀናፋ - ቅንፍ፡ የተቀነፈ የተመለሰ (የተቀለበሰ ምልስ ቅልብስ ክፈፍ ") ።
ቀኔ፡ ዘገር አበታ ጦር ("(ዘኍ. ፳፭፥ ፯ - ፰)") ።
ቀን (መዓልት)፡ የብርሃን ስም፡ ከጧት እስከ ማታ ያለው ጊዜ፡ ፲፪ የብርሃን ሰዓት ("(ዘፍ. ፩፥ ፭)") ። "ቀን ለሰራዊት፡ ሌሊት ለአራዊት፡ ቀንና ሌሊት" እንዲሉ። (ግጥም)፡ "መሸ መሰለኝ ሲጨልም፡ እንደ ቀን ጣይ የለም" ። ደቂቅ አገባቦች በ "የ" "ከ" "ለ" "ወደ" በመነሻ እየተጨመሩበት ሲነገር፡ "በቀን" "የቀን" "ከቀን" "ወደ ቀን" "ለቀን" ይላል ።
ቀን (ቀነየ)፡ ፳፬ ሰዓት (ሌሊትና መዓልት ") ።በግእዝ "ዕለት" ይባላል ። "አንድ ቀን ኹለት ቀን" ። "ቀንና ጨርቅ እንደ ምንም ያልቅ" እንዲሉ። ዕለትን ቀን ማለት በፀሓይ ነው፡ በጨረቃ ግን ሌሊት ይባላል ። ዳዊት ("(ይውዕል ወይትቀነይ እስከ ይመሲ)") ይላልና ("(መዝ. ፻፫፥ ፳፫)") ።የቀን ምስጢር ሥራ መሥሪያነትን ያሳያል ።
ቀን (ቀን)፡
ቀን ባላ ።
ቀን አያውቁ፡ ዓለማውያን ሰዎች የሚሞቱበትን ቀን አያውቅም ።
ቀን ኾነ፡ በጣም ረፈደ ። ቀን መቍጠሪያ፡ ያ፲፪ቱን ወር ዝር ዝር ከአ፩ እስከ ፴ የሚቈጥር ሰሌዳ ወይም ሰንጠረዥ ። በግእዝ "ዐውደ ዕለት" ይባላል ።
ቀን ወጣ፡ ክረምት ዐለቀ ። "ቀን ወጣ ብር ነጣ" እንዲሉ።
ቀን ወጣ፡ ክፉ ጊዜ ዐልፎ ደግ ዘመን መጣ ።
ቀን ወጣለት፡ ሀብታም ኾነ ከበረ ። ቀን ጣለው፡ ተዋረደ ተቸገረ ዐጣ ነጣ ።
ቀን ጐደለበት፡ አደጋ ወደቀበት ሙ ከራ አገኘው ።
ቀን) ብለኽ ቅኔን አስተውል።
ቀንሪ፡ የሚቀነጭር ።
ቀንቃኝ (ኞች)፡ የቀነቀነ/የሚቀነ ቅን (መርማሪ ፈታሽ፡ ዘፈን ዠማሪ ") ("(ዕዝ. ፪፥ ፷፭)") ።
ቀንቃኝነት፡ ቀንቃኝ መኾን (መርማ ሪነት ዠማሪነት ") ።
ቀንበር ።
ቀንበር - መንቈር ። ቀንበር ("(ግብ. ሐዋ. ፲፭፥ ፲)") ።
ቀንበር - ቀምበር (በረ ቀን - በረ ቀምሕ)፡ የቀን የፍሬ በር እየተባለ ይተረ ጐማል ።
ቀንበር (ሮች)፡ ሳይቈረጥ በቁሙ ተልጦ ላይ ላዩ የደረቀ በርሻ ጊዜ በበሬ ትከሻ የሚውል ጥኑ ጠንካራ ዕንጨት፡
ቀንበር ሰበር፡ ዳንዴ ወንበዴ ሕግ አፍራሽ ።
ቀንበጥ (ቀነጠበ)፡ ለጋ እንቦቀቅላ ለምለም ጫፍ ያልጠና ቅጠል ከነዕንጨቱ ።
ቀንበጦች፡ ለጎች ለምለሞች ።
ቀንባራ - ቅንብር፡ የቀነበረ (ደረቅ እን ጀራ ") ።
ቀንቧ አለ፡ እንደ ቅንቦ በፍጥ ነት ተሰበረ ተቀለጠመ ።
ቀንዛሪ (ዐረ ኸንዚር)፡ በልቶ የማ ይጠግብ ዐሣማ ።
ቀንዛሪ፡ የቀነዘረ/የሚቀነዝር (እንዳሣማ በቃኝ የማይል ") ።
ቀንዛፊ፡ የቀነዘፈ/የሚቀነዝፍ (ዐራጅ መልማይ አፍሳሽ ") ።
ቀንዛፋ - ቅንዛፊ፡ የተቀነዘፈ ምልማይ ።
ቀንደ መለከት፡ ከቀንድ የተበጀ የቀንድ መለከት፡ "ቀንዳ መለከትም" ይባላል ።
ቀንደ ገላላ፡ ቀንዱ ወደ ጐን የኼደ ።
ቀንደ ጐዳ፡ ቀንዱ ወደ ዦሮው የወረደ የተጠመዘዘ በሬ ።
ቀንደኛ (ኞች)፡ የሕዝብ መሪ ዋና አል ጉባኤ ተጠሪ ተናጋሪ ።
ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ምድር አበስ፡ ዐይቦ የሚባል በሬ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክና ሰው ።
ቀንዲል ።
ቀንዲል፡ የማብሪያ ስም፡ የፈትል የዘይት የቅባኑግ የሻማ (የሞራ) መደብ ከሸክላ ወይም ከብረት የተሠራ፡ ጌጠኛ መቅረዙ ከጠ ንካራ ዕንጨት የተቀረጸ ("(ኤር. ፶፪፥ ፲፱)") ። ይህ
ቀንዲሎች፡ ማብሪያዎች ("(ዘፀ. ፴፥ ፬፡ ፳፭)") ።
ቀንዲት፡ የእንስት በግ ስም ።
ቀንዳ ቀንዳ አለ፡ እፊት እፊት እ በልጥ እበልጥ አለ ባነጋገር ባካኼድ ።
ቀንዳ፡ ቀንድ ። "ቀንዳ መለከት" እንዲሉ።
ቀንዳላ - ቅንድል፡ የተቀነደለ ተቈርጦ የወደቀ ።
ቀንዳማ፡ ዝኒ ከማሁ (ባለቀንድ ") ።
ቀንዳም (ሞች)፡ ቀንደ ረዥም በሬ ዶባ አጋዘን ሳላ ።
ቀንዳሻ፡ የተቀነደሸ (ሰባራ ") ።
ቀንዳሽ፡ የቀነደሸ/የሚቀነድሽ (ቀንደ ሰባሪ ") ።
ቀንዳቢ፡ የቀነደበ/የሚቀነድብ (መቺ ") ።
ቀንዳውጣ (ቀንድ አውጣ)፡ የተ ንቀሳቃሽ ስም፡ በበጋ ደርቆ ይሞትና በክረምት ታድሶ ቀንድ የሚያወጣ ዛጐል ልብሱ
ቀንዳይ፡ የቀነደለ/የሚቀነድል (በጪ ቈራጭ ") ።
ቀንድ (ቈንደየ ቀርን)፡ በአንስሳትና በአራዊት ራስ ላይ የበቀለ፡ ሥጋዊ ጦር ጸብት ዋንጫና ዋጋምት መለኪያ የንዝርት ራስ የሚኾን ። አራዊት የተባሉ የዱር እንስሳት ናቸው ። "አውሬን" አስተውል ።
ቀንድ ከብት፡ ቀንድ ያለው የቀንድ ከብት (በሬ ላም የቤት እንስሳ ") ።
ቀንዶ፡ ያጋዘን ዐይነት የዱር እንስሳ ። በ፪ቱ ቀንዶቹ ላይ ብዙ የቀንድ ዐጽም አ ለው፡ ዕድሜው በቀንዱ ብዛት ይቈጠራል ። ዐይነቱ ብዙ ስለ ኾነ በግእዝ ድስክን ርኤም ሀየል ይባላል ። ልጆችም በተረታቸው ሰባት ቀንዶ ይሉታል ። ይኸውም ምሳሌ ከራእየ ዮሐንስ የመጣ ነው ። እንደዚሁም ብዙ ቀንድ ያለው ዋሊያ የፌቆ ዐይነት በስሜን ተ ራራ ይገኛል ።
ቀንዶች፡ የንስሳና የአውሬ ጦሮች የበዳ ጸብቶች ።
ቀንጃ፡ አጣማጅ የሌለው በራ ። "ጥንድ ከቀንጃ" እንዲሉ።
ቀንጠልባ (የቀን ተልባ)፡ ጥልቅ ብዬ ለፍላፊ ።
ቀንጠፋ፡ ስምና አንቀጽ ይኾናል ። ጌታ ችን የተሰቀለ ለት ቀን ጠፋ ("(ማቴ. ፳፯፥ ፵፭)") ።
ቀንጠፋ፡ በቈላ የሚበቅል እሾኻም ዕን ጨት ።
ቀንጣ ቀንጣ አለ፡ ፈጠን ፈጠን አለ ።
ቀንጣሽ (ሾች)፡ የቀነጠሰ/የሚቀነጥስ (ቀንጣቢ በጣሽ ") ።
ቀንጣቢ፡ የቀነጠበ/የሚቀነጥብ (ቈራጭ በጣሽ ቀንጣሽ ") ።
ቀንጣባ - ቅንጣቢ - ቅንጥብ፡ የተቀነጠበ (ብጥስ ቅንጥስ ") ።
ቀንጫራ - ቅንጭር፡ የቀነጨረ (ጠን ካራ ጥንክር ዐጪር ") ።
ቀኖት፡ ችንካር ምስማር (ግእዝ) ።
ቀኖና፡ ንስሓ የኀጢአት ቅጣት ።
ቀኖና ያዘ፡ ንስሓ ገባ በሱባዔ ተቀ መጠ ።
ቀኘ - ቀነየ)፡ አስቀኘ፡ ቅኔ እሳ ወቀ አሰጠ ። "ገኘ"ን እይ፡ አካኼዱ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀኛዝማች (ቾች) (ቀኝ አዝማች)፡ የቀኝ አዝማች (ከሻለቃው በስተቀኝ ስፍራ ጭፍራውን የሚያዘምት የጦር መሪ ") ። "ግራዝማችን" ተመልከት ።
ቀኛዝማች አሻግሬ)፡ የደጃች ባልቻ በዥሮንድ ። በአዲስ አበባ ወይም በሲዳሞ ወንድና ሴት ልጅ በወለዱ ጊዜ ሕፃናቱን ወደ ወግዳ ይልካሉ፡ ወንዱንም ኾነ ሴት ልጃቸውን ለባላገር ይድራሉ።
ቀኛዝማችነት ተሾመ፡ ቀኛዝማች ተባለ፡ ማዕርግ አገኘ ።
ቀኝ (ኞች) (ቀናዪ - መቅንዪ - የማን)፡ በግራ አንጻር ያለ ስፍራ ወይም እጅ ። "ጌታ በፍርድ ቀን ጻድቃንን በቀኝ ኃጥኣንን በግራ ያቆማቸዋል" ። ቀኝ ከስም አስቀድሞ እየገባ በዘርፍነት ይነገራል፡ ቅጽልም ይኾናል ።
ቀኝ እጅ፡ የቀኝ እጅ (በቀኝ በኩል ያለ፡ ኀይለኛ ፈጣን ") ።
ቀኝ፡ ድር ዝሓ፡ ጥንካሬውን ያሳያል ። እውነተኛው የቀኝ ትርጓሜ ቅን ማለት ነው ።
ቀኝ ጌታ፡ የቀኝ ጌታ (በደብር አለቃ ቀኝ የሚቆም ባለማዕርግ ካህን ") ።
ቀወለለ - ገወለለ) ተንቀዋለለ (ተንገዋለለ)፡ ዞረ ተንከዋረረ ተንሰዋለለ (አደገ ረዘመ ") ። "ዱር ለዱር ስንቀዋለል ውዬ የጠፋብኝን በግ አገኘኹት" ። "ወስፋቴ ስለ ሞተ የጐረ ሥኩት እንጀራ ባፌ ተንቀዋለለ" ። "ይህች ልጃገረድ ባል ሳታገባ፡ ቁመቷ ተንቀዋለለ" ።
ቀወለል - ቀውላላ (ሎች)፡ የተንቀ ዋለለ (ዘዋሪ ") ።
ቀወመ)፡ ቆመ ተነሣ ቀጥ አለ ተገተረ ታገደ ተገታ ቀረ ታጐለ ተግ አለ ።
ቀወሰ፡ አጐበጠ ደገነ ቀውስ አበጀ ።
ቀወቀወ - ከወከወ - ጎገወ) አንቀወቀወ (አንጎገወ) አንከወከወ አንቀዠቀዠ ።
ቀወቀወ)፡ ቃዠ ።
ቀወቀው - ቀውቃዋ፡ የተንቀወቀወ/የሚንቀወቀው ።
ቀዊ፡ የቀዋ/የሚቀዋ ቍራ ።
ቀዋ (ቀዊዕ ቆዐ)፡ ፍሬ ለቀመ ቀሠመ አወለበ ጠረጠረ ።
ቀዋሚ (ዎች)፡ የቆመ/የሚቆም (ጸ ንቶ የሚኖር ዐምድ ሐውልት ") ።
ቀዋሚ ነገር፡ ደንበኛ ውለኛ ሥራ ።
ቀውሰኛ (ኞች)፡ በነገር ተቃራኒ (ከሕዝብ ከማኅበር የማይስማማ ") ።
ቀውስ (ዐረ)፡ ቀስት ።
ቀውስ እሳት፡ የእሳት ቀስት፡ ጠንቋይ የናትና የልጅን ስም ገጥሞ ባ፲፪ እየገደፈ ይቈጥርና ለአንዳንድ ሰው "ኮከብኸ ፥ ቀውስ እሳት ነው" ይለዋል።
ቀውስ፡ የነገር መሳሳት አለመግጠም ።
ቀውስ፡ የኮከብ ስም (ቀስት ይዞ የሚታይ የኅዳር ኮከብ ቀስተኛ ") ።
ቀውቀውቱ፡ ዝኒ ከማሁ (ከውከውቱ ") ።
ቀውጢ (ዐረ. ቀውሲ)፡ ቀስተኛ የ
ቀውጢ ቀን፡ ሽብረኛ ሁከተኛ ጦረኛ ብላ ተባላ ቀን ። "ቀውጢ ቀን በመጣ ጊዜ ጌቶቹ አንድ ጋን ጠጅና ዐምስት እብድ አያጡም" ("(ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ)") ።
ቀዎት፡ በይፋት ውስጥ ያለ አገር ።
ቀዎቶች፡ የቀዎት ሰዎች (የቀዎት ተ ወላጆች ") ።
ቀዘመ - ገዘመ) አቅዘመዘመ፡ ወረወረ እምዘገዘገ አውዘገዘገ ።
ቀዘቀዘ (ቀዘዘ)፡ በረደ ከሙቀት ራቀ (ሰንሰለት ኾነ ") ።
ቀዘባ፡ ርጥብ ለጋ ለምለም ስንዴና ገብስ ። (የዘፈን አዝማች)፡ "የማነሽ ቀዘባ፡ አንች ዐይነ ሌባ" ። "ቀዘባ ማለት በጥር መታጨድ ይገባው የነበረ የካቲት ላይ ሲያልፍ ነው" ።
ቀዘነ፡ ቶሎ ቶሎ ዕዳሪ ወጣ ተቀመጠ፡ ብጥብጥ ዐይነ ምድር በፍጥነት ለቀቀ ሿ አደረገ ። (ግጥም)፡ "ፍየል ከቀዘነ ዲያቆን ከዘፈነ አይድንም ይሞታል እየመነመነ" ።
ቀዘነ፡ ፈራ ተንበደበደ ።
ቀዘዘ (ገዘዘ)፡ ፈዘዘ (አልመላም ") ።
ቀዘዝ አለ፡ ቀረት አለ (የስፍር ") ።
ቀዘዝተኛ፡ ቀሰስተኛ ደካማ ።
ቀዘፈ (ቀዲፍ ቀደፈ)፡ ግራናቀኝ ባሕርን ገፋ ገለጠ ከፈለ፡ የመርከብ መንገድ አበጀ መራ ።
ቀዘፋ፡ ገለጣ ከፈላ (የመቅዘፍ ሥራ ") ።
ቀዛኝ፡ የቀዘነ/የሚቀዝን (ኮሶኛ ሆደ በሽተኛ ") ።
ቀዛዛ፡ የቀዘዘ (ፈዛዛ ") ።
ቀዛፊ፡ የቀዘፈ/የሚቀዝፍ (መርከብ መሪ ቋትለኛ ") ። በግእዝ "ኖትያ ኀዳፍ" ይባላል ።
ቀዛፎች፡ የቀዘፉ/የሚቀዝፉ ("(ሕዝ. ፳፯፥ ፳፮)") ።
ቀዝቃዛ፡ ዝኒ ከማሁ (የቀዘቀዘ በራድ ") ። ወንድና ሴትን ለመለየት፡
ቀዝቃዛነት፡ ቀዝቃዛ መኾን ።
ቀዝቃዛዋ - ቀዝቃዛዪቱ፡ ያች ቀዝቃዛ ("(ኤር. ፲፰፥ ፲፬)") ።
ቀዝቃዛው፡ ያ ቀዝቃዛ ።
ቀዝቃዥ፡ የሚቀዘቅዝ (በራጅ ውርጭ ውሃ አየር ") ።
ቀዠቀዠ)፡ አንቀዠቀዠ (አክለፈለፈ አክለበለበ ") ።
ቀዠቀዥ - ቀዥቃዣ (ዦች)፡ የተንቀዠቀዠ/የሚንቀዠቀዥ (ክልፍልፍ ") ።
ቀዣበረ፡ ዘባረቀ ቀባዠረ ።
ቀየመ ቄመ)፡ አጠቈረ አቀጨመ ኣከፋ ።
ቀየሰ (ዐረ)፡ ለካ መጠነ ነደፈ በገረ ።
ቀየረ (ዐረ)፡ ለወጠ ሌላ አደረገ፡
ቀየረና ቀየሰ፡ በከተማ እንጂ፡ በባላገር አይነገርም ።
ቀየደ፡ መናገር ከለከለ (ለንባዳ አደረገ ") ።
ቀየደ፡ ሰከለ አሰረ ጋዳ ። (ተረት)፡ "እንዳትበላ ለጐት፡ እንዳትኼድ ቀየዷት" ።
ቀየደ፡ ከፈለ መከተ ጋረደ ከለለ ።
ቀየጠ (ትግ. ቀየጸ ፎከረ)፡ ዘነቀ ቀላቀለ ደባለቀ ።
ቀዩት፡ ቀይ ብራብሮ እንስት ።
ቀያ፡ በመንዝ ክፍል ያለ አገር ።
ቀያሪ፡ የቀየረ/የሚቀይር (ለዋጭ አዛ
ቀያሽ (ሾች)፡ የቀየሰ/የሚቀይስ (ነዳፊ በጋሪ ") ።
ቀያቀይ፡ የቀይ ቀይ ።
ቀያቴ፡ ቀይ ጠመኔና ቀይነት ያለው አበባ ።
ቀያቴቀይ አበባ
ቀያየረ፡ ለዋወጠ ።
ቀያየጠ፡ መላልሶ ቀየጠ ።
ቀያይ፡ የውስጠ ብዙ ቀይ ቅጽል ።
ቀያዮች፡ ቀዮች ። ዐረቦች ቀያዮች ና
ቀያጅ (ጆች)፡ የቀየደ/የሚቀይድ (መካች ጋራጅ አሳሪ ") ።
ቀያጭ (ጮች)፡ የቀየጠ/የሚቀይጥ (ዘናቂ ቀላቃይ ደባላቂ ") ።
ቀያፋ፡ የሰው ስም፡ ጌታችንን ያስ ቀለ ሊቀ ካህናት ።
ቀዬ (ኦሮ)፡ ደጅ ካጥር ውጭ የሚገኝ ስፍራ ።
ቀይ (ቀይሕ)፡ የቀላ (ደም ጁኅ ጃዊ እንድኪ ፍሕሶ ነት ዐረብ አንቀልባ የሱፍ አበባ ") ።
ቀይ መልክ አይገፋም፡ እጅግ አያ ምርም፡ ደመ ግቡ አይኾንም ።
ቀይ መስቀል፡ በዓለም ኹሉ የተወደደ የበጎ አድራጎት ማኅበር፡ ሥራውም በጦርነት ጊዜ ጠላትና ወዳጅ ሳይለዩ ቍስለኛን ማንሣትና ማከም ማስታመም ነው፡ እንደ አውሮጳ አቈጣጠር ነሐሴ ፳፪ ቀን ፲፰፻፷፱ ዓ. ም. በዠኔብ ተዠመረ ።
ቀይ ሥር፡ የተክል ስም ።
ቀይ በሬ፡ ሶረን ።
ቀይ፡ በቁሙ ቀላ ።
ቀይ በግ፡ ዳንግሌ ።
ቀይ፡ አርእስቱ በቀይ ቀለም የሚጻፍ ከዳዊት መዝሙሮች አንዱ ። "ቀይ" ከስም አስቀድሞ እየገባ በቅጽልነት ይነገራል ።
ቀይ ዐፈር፡ ቦረቦር ሸክላ ።
ቀይ ዳማ፡ በጠይምነትና በቀይነት መካከል ያለ ሰው፡ ጠይምነቱ ወደ ቅላት የሚያደላ ። "ዳማ" በጋልኛ ቀይ ፈረስ ማለት ነው ።
ቀይ ዶሮ፡ ሶረኔ መልክ ።
ቀይ ግምጃ፡ ሶራ ።
ቀይ ጣላ፡ ቀይ ያለበት (የጣለበት) ።
ቀይ ፈረስ፡ ሐመር ዳማ ("(ራእ. ፮፥ ፬)") ።
ቀዮች፡ የቀሉ ቀያይ የኾኑ ስዎች፡ ሌሎችም ሥነ ፍጥረቶች ።
ቀደል፡ ጥላት (የጭላት ዐይነት ") ።
ቀደመ (ቀዲም ቀደመ)፡ በሩጫ በለጠ፡ ዐለፈ ዐልፎ ኼደ፡ ወደ ኋላ ተወ ። "አሳሄል በሩጫ ከፈረስ ቀደመ" ። "የቀደመን ሞት ይወስደዋል" ።
ቀደመ፡ በቀዳማ ላይ ሰቀለ አንጠለ ጠለ ። (ግጥም)፡ "እንግዴህ አላምንም ፈረሰኛውን፡ ቀደሙት ይሉኛል መርቆሬዎስን" ።
ቀደመ፡ ዠመረ ፈለመ፡ ጨፈለቀ -
ቀደማ፡ መቅደም ቅድሚያ ።
ቀደማ፡ ጭፍለቃ ዕዳሪ ማውጣት ።
ቀደም (ቀዳሚ)፡ በኵር ፊተኛ ። "ግን ባር ቀደም" እንዲሉ።
ቀደም፡ ቀደመ ። (የባለጌ ተረት)፡ "ሳትጋደም ፈሷ ቀደም" ። "ነበረን" እይ ።
ቀደም አለ፡ ቀደሙ ።
ቀደም፡ ያለፈ ጊዜ ("(ኤፌ. ፬፥ ፳፪)") ። "ከዚህ ቀደም" እንዲሉ።
ቀደሰ (ቀድሶ ቀደሰ)፡ ለየ ባረከ እነጻ አከበረ አመሰገነ፡ ቅዱስ አደረገ ከርኵሰት አራቀ ። "እራት የሌለው ቄስ እንደ ልቡ አይቀድስ" ። (ግጥም)፡ "አብ እሳት ወልድ እሳት መንፈስ ቅዱስ እሳት፡ ቄስ እንዴት ይሞታል ጐሥዐን ሲቀድሳት" ።
ቀደሰ፡ ቈረበ ።
ቀደደ፡ ሸረከተ ሠጠጠ ሠነጠቀ ተለተለ (በሸረከ በጨቀ ") ("(፪ነገ. ፭፥ ፯ - ፰)") ።
ቀደደ፡ በሳሸነቈረ ነደለ ። "ውሻ በቀ ደደው ዥብ ይገባል" እንዲሉ።
ቀደዳ፡ ሽርከታ ሥንጠቃ ሽንቈራ ።
ቀደጀ - ቀደወ)፡ አቀዳጀ (አስተቀጸለ)፡ ዘውድን አክሊልን ራስ ቍርን ራስ ወርቅን ጐፈርን አቍዳማን በራስ ላይ ጫነ አጠለቀ፡ ሸለመ አስጌጠ ።
ቀደጀ - ኦሮ ከደነ)፡ "ሲል ቀዳዴ" ከሚለው ጋራ በምስጢር ይገጥማል ።
ቀዳ (ቀድሐ)፡ ውሃን ጠላን ጠጅን ማንኛውንም ፈሳሽ ነገር ካለበት ስፍራ ዕቃ ጠለቀ ወደ ሌላ አወረደ ጨመረ፡ አንቈረቈረ ሞላ፡ ባንኮላ በጭልፋ ደነበቀ ወለፈ ገለበጠ ።
ቀዳ፡ አለልክ አለቀሰ (እንባውን አፈሰሰ ") ።
ቀዳ፡ አስቀመጠ አስቀዘነ ነዳ ።
ቀዳ፡ ጪር ጻፈ ።
ቀዳሚ (ዎች)፡ የቀደመ/የሚቀድም
ቀዳማ (ቀዳማይ)፡ በስተደረት ያለ የኮርቻ ከፍተኛ ድጋፍ የደኃራ አንጸር ።
ቀዳማዊ፡ የቀዳሚ ወገን ወይም ዐይነት (አንደኛ መዠመሪያ ሰው ማንኛውም ፍጥረት ") ።
ቀዳማይ፡ ከትንቢት አንቀጽ በፊት የሚነገር ተቀዳሚ አንቀጽ ኀላፊ ።
ቀዳሽ (ሾች)፡ የቀደሰ/የሚቀድስ (ባራኪ አመስጋኝ ቈራቢ ሰሞነኛ ዲያቆን ቄስ ቆሞስ ጳጳስ ") ።
ቀዳው፡ ዝናቡን አለመጠን አዘነበው ።
ቀዳደደ፡ ሸረካከተ ሠነጣጠቀ ።
ቀዳዳ፡ ብስሽንቍር ሥንጥቅ ("(ኢሳ. ፰፥ ፲፰)") ። (ተረት)፡ "ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ" ።
ቀዳዳ፡ ነገር የማይችል የማይቋጥር ሰው ።
ቀዳጅ (ጆች)፡ የቀደደ/የሚቀድ (ሸር ካች ሠንጣቂ ሸንቋሪ ") ።
ቀድሞ - ቅድም፡ የጊዜ ንኡስ አገባብ ።
ቀድሞ (ቀዲሙ)፡ ጥንት ዱሮ ፊት ።
ቀድሞ፡ ቦዝ እፊት ኹኖ ።
ቀድሞ ዘመን፡ ያለፈ የጥንት ጊዜ (ቀድሞ የዘመን ዘርፍ ነው ") ።
ቀድሞውን - ቀድሞውኑ፡ ዱሮውን/ዱሮውኑ ።
ቀጂ (ጆች)፡ የቀዳ/የሚቀዳ (ጨምማሪ ኣንቈርቋሪ ") ።
ቀጂነት፡ ቀጂ መኾን ።
ቀጋ (ጎች)፡ ከሥር እስከ ጫፍ ኹለንተናው እሾኸ ያለው ዕንጨት ። አበባው ነጭ፡ ሽታው ጣፋጭ ። (ተረት)፡ "የውጭ ዐልጋ የቤት ቀጋ" ።
ቀጠለ (ቀጸለ)፡ በቁመት ላይ ቁመት በሥራ ላይ ሥራ ኣከለ ጨመረ፡ ቋጠረ ገጠመ ሰፋ አረዘመ ። "ቀጸለን" እይ፡ "ቀጠለ" ዐማርኛ፡ "ቀጸለ" ግእዝኛ ነው ።
ቀጠለ (ቈጸለ)፡ ሣሣ ረቀቀ ።
ቀጠለ፡ ለመለመ ጨበጨበ ።
ቀጠለ፡ ተራ መታ ተከተለ ለጠቀ ።
ቀጠላ፡ ሻሽቀጸለ ።
ቀጠላ፡ ዐሰላ ።
ቀጠላ፡ ጥሩ የማር እንጀራ (ከወለላ በቀር ከዳና ቀለሕ የሌለበት ") ።
ቀጠረ (ቀጸረ)፡ ገነባ ካበ ከ በበ ከተማን አገርን፡ የውጭ ዐጥር ዐጠረ ጀጐለ ። "ከተማ እንደ ሐረር፡ አገር እንደ ሺን" ነው ።
ቀጠረ (ዐደመ ዐሠረ)፡ ቀን ወሰነ፡ በዚያ ለት መጥተሽ እንድትቀርብ አለ ። "ኹሉም የቅጥርን ምስጢር አይለቅም" ። (ተረት)፡ "ቀን ቢቀጥሩ ውሻ ቢጠሩ ይደርሳል በግሩ" ።
ቀጠረ፡ አሽከር ሎሌ ገረድ ኣሳደረ (ቀለብ ደመ ወዝ ምንዳ ሊሰጥ ") ።
ቀጠሮ፡ ታፌ ያለ በ፰ ከጠበቃዬ ያለ ባ፲፭ ቀን የሚቀርብበት ።
ቀጠሮ አፍራሽ፡ ቀጠሮ የማያከብር ተቃጥሮ የሚቀር ።
ቀጠሮ፡ የሰዓት ልክ/የጊዜ ውሳኔ (ሰው ተገናኝቶ ጕዳዩን የሚፈጽምበት እዳኛ ፊት ቀርቦ የሚነጋገርበት ") ።
ቀጠቀጠ ("ጨፈ ጨፈ ባጪር ባጪሩ ቈረጠ ገተገተን እይ ከትካች የከተከተ የሚከተክት ቀጥ ቃጭ ጨፍጫፊ ክትከታ ቅጥቀጣ ጭፍጨፋ ቈረጣ መከትከት መቀጥቀጥ መጨፍጨፍ መቍረጥ መከትከቻ መጨፍጨፊያ መቍረጫ ካራ ጩቤ አስከተከተ አስቀጠቀጠ አስጨፈጨፈ ተከተከተ ተቀጠቀጠ ተጨፈጨፈ ተ ቈረጠ ካቲ ስንድድ ከተረከዝ በላይ በስተኋላ ያለ ሥር እከሌ ከእከሌ ጋራ ተጣላና ካቲ ካቲውን አለው ካቲካላ ያረቄ ስም ሲጠጡት እንደ እሳት የሚያቃጥል መጠጥ የካቲን ርምጃ የሚከላ ካቲካላ የሚጠጡ አባትና እናት ድዳ ደንቈሮ ዕውር ልጅ ይወልዳሉ አንከተከተ ቀጥሎ ቀጥሎ እንባ እ ስኪወጣ ድረስ አሣቀ ማንከትከት ፈጽሞ ማሣቅ ተንከተከተ ባለማቋረጥ ሣቀ መንከትከት መሣቅ መንከትከቻ መሣቂያ ካታ የሚሥቅ የሚንከተከት ሣቂ - ፮፻፺፩ ካታ ወልደ ሚካኤል ባጤ ምኒልክ ዘመን በላይኛው ወግዳ የነበረ ተጫዋች ሥቆ የሚያሥቅ ሰው ከት አለ በጣም ሣቀ ") ።
ቀጠቀጠ (ቀጥቀጠ ቀጽቀጸ)፡ መታ ደበደበ ሰበረ አደቀቀ ።
ቀጠቀጠ፡ ብረት ሠራ አሾለ አጠፈ
ቀጠቀጠ፡ ወቀጠ ገብስን የወይፈንንና የወጠጤን ቍላ ።
ቀጠቀጥ - ቀጥቃጣ፡ የተንቀጠቀጠ/የ ሚንቀጠቀጥ (ሥጋ ፈሪ ንፉግ ") ። "ፈንዛን" እይ ።
ቀጠባ ማሪያም፡ የቀጠባ ማሪያም ።
ቀጠባ፡ የቀበሌ ስም (በደብረ ሊባኖስ ውስጥ ያለ የማሪያም አጥቢያ ") ። "አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከይፋት አገር በትምህርት በ ታምራት ማርከው ከነልጆቿ ደብረ ሊባኖስ አምጥተው ስን (ክርስቶስ ቀጸባ) ያሏት አንዲት ቅድስት ሴት ነበረች፡ የመቤታችንን ታቦት በዚህ ስፍራ ስለ ተከለች ከውሻ ገደል በታች ያለው ቀበሌ በስ ቀጠባ ተባለ ይላሉ ። የቀጠባት ርጓሜ ጠቀሳት ጠራት አቀረባት ማለት ነው" ።
ቀጠነ (ቀጢን ቀጠነ)፡ ነነ ከሳ ከውፍረት ከድንዳኔ ራቀ ሣሣ ረቀቀ ።
ቀጠና፡ ትንሽ ረኃብ፡ ሼጥ ያለ ዘመን ("(ዘዳ. ፳፰፥ ፳፪፡ ሰቈ. ፬፥ ፲፱፡ ዓሞ. ፬፥ ፮)") ። (ተረት)፡ "ምንም ቢታረስ በዘጠና ቤቱን አይስ ትም ቀጠና" ።
ቀ ፡ ፲፱ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ። በፊደልነት ቆፍ፡ በአኃዝነት 100 ይባላል ።
ቀ ጠሮ አፈረሰ)፡ ተቃጥሮ ሳይመጣ ቀረ ።
ቀሃ፡ የወንዝ ስም ። ቀሓ ።
ቀሓ፡ ያገር የወንዝ ስም (በበጌምድር ውስጥ ያለ ዠማ ") ። "የውሃ የውሃ ምን አለኝ ቀሓ" እንዲሉ።
ቀህረማን (ዐረ)፡ ቈርበት ካሪም ።
ቀለ - ቃለ፡ ቀንዳ - ቀንድ፡ ቃለ ደረቅ ማለት ነው ።
ቀለ፡ ተለጠፈ/ታዘለ/አቀለ፡ ለጠፈ/ዐዘለ (በዠርባ ወይም በደረት በጐን ያዘ) ።
ቀለሔ፡ የቀለሕ ዐይነት ባዶ፡ ፍሬ የሌለው እኸል ። "ቀለኸን" እይ ።
ቀለሔ፡ የኔ ቀለሕ ።
ቀለሕ (ሖች)፡ በቂጡ ከምሱር በው ስጡ ባሩድ በፉ ዐረር የሌለበት ውስጠ ክፍት ንሓስ ።
ቀለሕ ምላሽ፡ የርሳስ መምታት የቀለሕ መመለስ (መቅረት) ።
ቀለለ (ቀሊል ቀለ)፡ ("(ዘፍ. ፰፥ ፫)") ከክብደት ከክብር ከብዛት ከብርታት ራቀ አነሰ ጐደለ ። (ግጥም)፡ "እንዴት አደርጋለኹ ብዬ ስጨነቅ፡ እያደር ይቀላል ዐባይና ሥንቅ" ።
ቀለል፡ መቅለል ።
ቀለል አለ፡ አነስ ጐደል አለ ።
ቀለልተኛ፡ ቀላልነት ያለው ከመክበድ
ቀለመ (ቀሊም ቀለመ)፡ ቀለም እዘጋጀ ኣቦካ ዐሸ ።
ቀለመ፡ ምድር ሳያስነካ ያዘ፡ ቀ
ቀለመ፡ ነካ ነበዘ አሳደፈ ።
ቀለመ፡ ዐረደ ቈረጠ ከረከመ፡ ዐንገትን ሥጋን ቀሠምን ።
ቀለመ፡ አጠቀሰ ጻፈ ጣፈ፡ ቀለምን (ቃልን) በብራና በወረቀት ላይ አሳረፈ ።
ቀለመ ወርቅ፡ የወርቅ ቀለም፡ የወንድና የሴት ስም።
ቀለመ ጠጥ፡ ዐይነ ባርማምጠ ።
ቀለመው፡ ቀለሙ ልብሱን ነበዘው አሳደፈው፡ ልብሱ ቀለሙን ሠረበው ጠጣው ተዋሐደው ።
ቀለመጠ - ቀመጠ ለመጠ)፡ አቀላመጠ፡ በምላስ ሙሬነት ወይም አማካይነት አፉን ጠረገ አጮኸ፡ ምራቁን ዋጠ አጣጣመ ።
ቀለማት፡ ቀለሞች ሕብሮች ። "፯ቱ ቀለማት" እንዲሉ።
ቀለም (ሞች)፡ ከስንዴ ዐራራና ከአሜራ ሥር ከአውጥ ፍሬ የተበጀ ጥቍርና ቀይ ልጥልጥ ወይም ፈሳሽ ("(ኤር. ፴፮፥ ፲፰)") ።በጥቍሩ ሙጫ በቀዩ ከርቤ ይገባበታል ። ነጭ ብጫ ሰማያዊ አረንጓዴ ወይን ጠጅቀለም የመሰለው ኹሉ ።"እፍራንን ዶልንና ነድን" እይ፡ "ዶለ ነደደ" ።
ቀለም (ዐረ)፡ ከጐሽ መቃ የተቀረጸ ብር መጻፊያ ። ይኸንንም ፵፬ኛው የግእዝ መዝ ሙር (ቀለመ ጸሓፊ) በማለቱ ያስረዳል።
ቀለም፡ ቀሠም ቀጪን መቃ ።
ቀለም ቀባ፡ ላከከ በቀለም ሸፈነ አለበሰ ።
ቀለም ቀንድ፡ ቀለም ያለበት የቀለም ቀንድ ። (ግጥም፡ ተማሪ በሞተ ጊዜ)፡ "ዐፈር መልሱ እንጂ ደንጊያ ለምናችኹ፡ የቀለም ቀ ንድ ነው፡ ትሰብሩታላችኹ" ።
ቀለም፡ ትምርት ቃለ እግዚአብሔር ። (ግጥም)፡ "ይማርልኝ ብዬ በጌምድር ሰድጄ ቀለም ገባው አሉ፡ እሳት ኾነ ልጄ" ። "ዐጤ ቴዎድሮስ ልጇን ያቃጠሉባት ሴት" ።
ቀለም አገባ፡ ነከረ ዐለለ ።
ቀለም አግቢ፡ ዐላይ ("(ኢሳ. ፴፮፥ ፪)") ።
ቀለም፡ ደም ግባት ውበት ላሕይ ። (ግጥም)፡ "ሥራ ፈቶ ዋለ ትላንት ሸማኔው ! ያ ቀለምሽ ነወይ የተበላሸው" ።
ቀለም ገባው፡ ምሁር ኾነ፡ ትምርት ዐወቀ ።
ቀለም፡ ጐሽ መቃ ከቅጥነቱና ከውስጠ ድፍንነቱ በቀር መቃ የሚመስል ።
ቀለምሽሽ (ምሸሽ)፡ ርቦ ከቀለም (ጐሽ መቃ) የተሠራ ።
ቀለምጺጽ፡ የሠማ የጋለ፡ ምጣድ ድስት ማሰሮ ጀበና ቂጥ ብልጭልጭታ ።
ቀለምጺጽ፡ የእሳት ፍንጣሪ ብራሪ (ግእዝ) ።
ቀለሰ (ቀሊስ ቀለሰ)፡ መለሰ አጐበጠ አደገነ ቈለፈ ።
ቀለሰ፡ አለቍንጮ ቅስትኛ ሠራ ። "ጐዦ ቀለሰ" እንዲሉ።
ቀለሰ፡ አቀረቀረ ። "ዐንገቱን ቀለሰ" እንዲሉ።
ቀለሰ፡ ኣረ ከቀኝ ወደ ግራ አዞረ ።
ቀለሳ - ቅለሳ፡ የመቀለስ/የማጕበጥ ሥራ ።
ቀለስ፡ መለስ ።
ቀለስ አለ፡ መለስ አለ ።
ቀለሸ - ቀለበሸ)፡ አቅለሸለሸ፡ አጥ ወለወለ ልውጣ ልውጣ አለ ።
ቀለሸ)—ቀማ ።
ቀለቀለ - ቀልቀለ)፡ አንቀለቀለ (አ ንቀልቀለ)፡ ባለማቋረጥ አነደደ አንበለበለ ።
ቀለቀል - ቀልቃላ (ሎች)፡ የተንቀለ ቀለ/የሚንቀለቀል (ዘዋሪ ቀዥቃዣ ቀውቃዋ ") ።
ቀለቀንዳ፡ አፈኛ ተናጋሪ ለፍላፊ ወንድ ወይም ሴት ።
ቀለበ (ቀሊብ ቀለበ ቀለጰ)፡ ረዳ መገበ ኣበላ አጠጣ ("(፪ሳሙ. ፲፱፥ ፴፪፡ ፴፫)") ።
ቀለበ (ገለወ)፡ ሸፈነ በውስጥ አደረገ ።
ቀለበ፡ ቀለጠፈ ሰበቀለ ።
ቀለበ፡ የተወረወረ ነገርን ምድር ሳያስነካ ያዘ ተቀበለ ጨበጠ እጅ አደረገ ። "ቀለመን" እይ ።
ቀለበሰ፡ ከጫፍ ወደ ውስጥ ወይም ወደ ውጭ ዐጠፈ ሸነቀረ ቀነፈ ።
ቀለበሸ፡ መለሰ ገለበጠ፡ የውስጡን በላይ አደረገ፡ አቅለሸለሸ ።
ቀለበተ፡ ቀለበት ሠራ፡ አከበበ ።
ቀለበታም፡ ቀለበት ያለው ባለቀለበት ሰው ዕቃ ።
ቀለበት (ቀለበ)፡ ከብርና ከወርቅ ከንሓስ ከመዳብ የተሠራ የጣትና ያንገት ክብ ጌጥ ("(ዘፍ. ፴፰፥ ፲፰)") ። (ተረት)፡ "በዋስ ያለ ከብት፡ በጣት ያለ ቀለበት" ። ሲበዛ ቀለበቶች ያሰኛል ። ቀለበት በጣት የሚያዝ ጣት ቀለቡ ማለትን ያሳያል ።
ቀለባ - ቅልቢያ - ቅልቦሽ (ቍላቤ)፡ መቅለብ ።
ቀለብ፡ ሠራተኛ በየወሩ የሚቀበለው ጥሬ እኸል ጥሩ ታደፍ ("(፩ነገ. ፩፥ ፯)") ። ባመት ሲኾን ምንዳ ይባላል ።
ቀለብላባ - ቅልብልብ (ቦች)፡ የተቅለበለበ (ክልብልብ ስግብግብ ችኩል ") ። (ተረት)፡ "ለቅልብልብ ዐማት ሢሶ በትር አላት" ።
ቀለብተኛ (ኞች)፡ ቀለብ ተቀባይ ባለቀለብ ቀለብ ተሰፋሪ በቀለብ ዐዳሪ ሎሌ ገረድ አሽከር ወታደር ።
ቀለተ (ትግ)፡ ረጠበ ዐገዘ ረዳ፡ በጠፋ ተካ ሰጠ ።
ቀለተኛ፡ የቀለት ወገን ባለቀለት ።
ቀለተኞች፡ ቀለት ፈላጎች ተቀባዮች ።
ቀለታ፡ ዕገዛ ርዳታ ስጦታ ።
ቀለት፡ ርጥባን ።
ቀለኸ (ቀለሕ)፡ ዝነበበ ፍሬ አልባ ቀረ፡ የብር ያበባ ያገዳ እኸል ።
ቀለወ፡ ከለበ ።
ቀለዋ፡ የዛፍ ስም፡ ፍሬው ለዕከክና ለኮሶ መድኀኒት የሚኾን አነስተኛ የወይናደጋ ዕንጨት ።
ቀለው ቀለው አለ፡ ክልብ ክልብ አለ ። (ግጥም)፡ "ካንዱ ቤት አንዱ ቤት ስትይ ቀለው ቀለው አንዱ የነደደው ማዥራትሽን ባለው" ።
ቀለዘ፡ ኣለልክ ደረቀ ከቸለ ጨለኸ ።
ቀለደ (ቀሊድ ቀለደ)፡ አሾፈ ተረበ አቧለተ ዋዛ ፈዛዛ ተናገረ፡ አላገጠ አፌዘ አፌጠ አሌጠ ።
ቀለጠ፡ ተመታ ። "በጥፊ ቀለጠ" ።
ቀለጠ ነጠረ (ደከመ ጠፋ ") ("(ሚክ. ፭፥ ፲፭)") ። "እኸሉ ፈሰሰ"፡ "እንባው ፈሰሰ"፡ "ቅቤው ፈሰሰ"፡ "ልቡ ፈሰሰ"፡ "ዐይኑ ፈሰሰ" እንዲሉ ። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም "ይፈስ ይፈሳል" እያለ ጠብቆ ይነገራል እንጂ፡ "ይፈስስ ይፈስሳል" አይልም ። (ተረት)፡ "ውሃ ከፈሰሰ አልታፈሠ" ።
ቀለጠ፡ ወፈረ ደነደነ በጣም ሠባ ።
ቀለጠ፡ ደመቀ አማረ ። "ዘፈኑ ቀለጠ፡ እልልታው ቀለጠ" ።
ቀለጠ፡ ጝ ፈሰሰ፡ ተናደ ወደቀ ፈረስ ("(መዝ. ፳፪፥ ፲፬፡ ኢሳ. ፲፫፥ ፯)") ። (ተረት)፡ "እንደ ፈንታሌ ትቀልጣለኸ" ።
ቀለጠ፡ ጠፋ ። "ገንዘቤን ለማንም አበደርኹና የትም ቀልጦ ቀረ" ።
ቀለጠመ (ትግ ቀልጸመ)፡ ቅልጥም አወጣ፡ ቅልጥማም ኾነ ።
ቀለጠመ (አንጕዐ)፡ ቅልጥም መታ ሰበረ፡ ቅልጥም አሳክሎ ቈረጠ ። "ገለፀመን" እይ፡ የዚህ ሞክሼ ነው ።
ቀለጠመ፡ ቅልጥም በሚያኸል ሽክና ጠጣ፡ ዥው አደረገ ጨለጠ ። "ገበሬው ቀን ከዱር እቤት በገባ ጊዜ ጠላውን ባንኮላ ቀለጠመው" ።
ቀለጠጠ - ገለጠጠ)፡ አንቀለጠጠ፡ ከፈተ፡ ፈጽሞ ገለጠ፡ አንገለጠጠ ። በተገብሮነትም ይፈታል ።
ቀለጠጥ - ቀልጣጣ - ቅልጥጥ፡ የሚንቀለጠጥ፡ እንቅልጥ ከለላ አልባ ።
ቀለጣጠመ፡ ሰባበረ ኰረታተመ ("(፪ነገ. ፲፰፥ ፬፡ ሆሴ. ፲፥ ፪)") ።
ቀለጤ፡ በዋል ፈሰስ፡ ወፍራም ሰው ።
ቀለጦ፡ እንኵሮ በተነኰረ ጊዜ ከገበር ምጣድ ላይ ተለጥጦ የሚወጣ ሥሥና ደረቅ የንኵሮ ቅሬታ ።
ቀለፈፈ፡ ገለፈፈ ቀፈፈ ቈረጠ ።
ቀለፋ - ቈለፈ - ቀፈለ)፡ አንቀላፋ፡ ተኛ ተጋደመ ዐይኖቹን ጨፈነ ከንፈሩን ገጠመ ሰውየው ("(ዘፍ. ፪፥ ፳፩፡ ኢሳ. ፵፫፥ ፲፯፡ ሉቃ. ፰፥ ፳፫)") ።
ቀሊል፡ የቀለለ (ላባ ገለባ ላንፋ የመሰለው ኹሉ ") ። "ረከበን" እይ ።
ቀሊል የግእዝ፡ ቀላል ያማርኛ ነው ።
ቀሊል፡ ድበላ አደፍ ያበባ እኸል ። "ብስል ተቀሊል" እንዲሉ።
ቀላ (ቀልዐ ዕብ. ቃላዕ)፡ መታ
ቀላ (ቀዪሕ)፡ መቅላት ።
ቀላ (ቄሐ)፡ ደም መሰለ ("(ምሳ. ፳፫፥ ፴፩)") ።
ቀላ፡ ቈረጠ ። ፩ኛው ቀላና ይህ ፪ኛው ቀላ ባማርኛ ሲተባበሩ (ግጥም)፡ "የታጠቅ ጐራዴ፡ ብረት የነበረ፡ እየቀላ ኼደ ደም እየመሰለ" ።
ቀላ አለ፡ ቀላ ።
ቀላል (ሎች)፡ የቀለለ/የቀለለች (የተ ሙን ተቤሳ ዶሮ ") ። "አገረ ብለኸ እግርን ወገብን" ተመልከት ።
ቀላል መሬት፡ አሸዋማ ስፍራ ።
ቀላል ሴት፡ ቁም ነገር የሌላት ።
ቀላመደ (ቃለ ዐመፀ)፡ ዋሸ ዘላበደ ቀሣፈተ፡ በቃል በደለ ቃሉን ከዳ ።
ቀላሚ፡ የሚቀልም (ነባዥ አሳዳፊ ") ።
ቀላማ ።
ቀላማ (ሞች)፡ ወላድ ፈረስ እንስት ።
ቀላማጅ (ጆች)፡ የቀላመደ/የሚቀላምድ (ዘላባጅ ቀሣፋች ") ።
ቀላሳ፡ ጐባጣ መላሳ ።
ቀላሽ፡ አሪ በሬ (ጐዣምና ጐንደር) ።
ቀላሽ፡ የቀለሰ/የሚቀልስ (መላሽ አጕ
ቀላቀለ፡ ደባለቀ ቀየጠ ዘነቀ ።
ቀላቃይ፡ የቀላቀለ/የሚቀላቅል (ደባላቂ ቀያጭ ") ።
ቀላቢ (ላል)፡ የሚቀልብ፡ ከላይ ከሰማይ ተቀባይ ያዥ ጨባጭ ። "ኳስ ቀላቢ" እን ዲሉ።
ቀላቢ (ዎች)፡ የቀለበ/የሚቀልብ (አብሊ አጠጪ ረድ መጋቢ ገረድ ") ።
ቀላች (ቾች)፡ የቀለተ/የሚቀልት (ረ
ቀላወጠ፡ ከጀለ አፈጠጠ ። (ተረት)፡ "የወደዱትን ሲያጡ የጠሉትን ይቀላውጡ" ።
ቀላዋ (ከላዋ)፡ ከላባ ።
ቀላዋጭ (ጮች)፡ የቀላወጠ/የሚቀላውጥ (አፍጣጭ ") ። (ተረት)፡ "ወጥን ማን ያው ቃል ቢሉ፡ ቀላዋጭ" ።
ቀላዋጭነት፡ ቀላዋጭ መኾን፡ አፍጣጭነት ።
ቀላያት፡ ጥልቆች ውቅያኖሶች ።
ቀላይ (ቀለየ ጠለቀ)፡ ጥልቅና ሰፊ ባሕር ውቅያኖስ ("(ዘፍ. ፩፥ ፪)") ።
ቀላይ፡ የሚቀል የማይከብድ ።
ቀላይ—ቈለለ ።
ቀላድ (ዶች)፡ ከቃጫ/ከንሰት/ጭ ረት የተገመደ ገመድ ።
ቀላድ፡ በቀላድ የተለካ አንድ ጋሻ መሬት ። በግእዝ "ሐብለ ርስት" ይባላል ("(መዝ. ፻፭፥ ፲፩)") ።
ቀላድ ጣለ፡ መሬትን ለመለካት ቀላድን በምድር ላይ ዘረጋ፡ የረዘመውን በገመድ ያጠረውን በክንድ ለካ መጠነ ።
ቀላድ ጣይ (ዮች)፡ ቀላድ የሚጥል (የሚዘረጋ) ምድርን የሚለካ ።
ቀላጅ (ጆች)፡ የቀለደ/የሚቀልድ (አላጋጭ ") ።
ቀላጤ (ቃለ ሐፄ)፡ የንጉሥ ቃል።
ቀላጤ (ዎች)፡ የንጉሥ/የዳኛ ቃል ነጋሪ መልክተኛ ። "ዐጤን ይበልጡ ቀላጤ፡ ሙክትን ይሻል ወጠጤ" እንዲሉ።
ቀላጤ ዋሻ፡ ቀላጤ ካዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሲኼድ የሚያድርበት ዋሻ ስፍራ ።
ቀላጤ—ቀለጠጠ ።
ቀላጥም (ሞች)፡ በቅልጥም ልክ የተሰበረ (የተቈረጠ) የቃሬዛና የመሰላል አግዳሚ ዕንጨት ።
ቀላጥቤ፡ ተናጋሪ ለፍላፊ፡ ወሬ አማቂ ።
ቀላጭ፡ የሚቀልጥ/የሚማ (ፈሳሽ ፈራሽ ሠም ሞራ ተራራ ") ።
ቀላጭ፡ ጌታ ባለጠጋ ሀብታም ሰውነቱ የሚያምር ጭፍጭፍ የሚል ።
ቀላጭቱ፡ እመቤቲቱ ወይዘሮዪቱ ("(ኢሳ. ፵፯፥ ፩)") ።
ቀላጮች፡ ጌቶች መኳንንት ባለጠ ጎች ("(፩ቆሮ. ፮፥ ፱)") ።
ቀሌን - ቀርን፡ ዥ፥ዝኆን ።
ቀሌንጅ (ዥ)፡ ታናሽ የዝኆን ጥርስ ።
ቀልማዳ፡ ዝኒ ከማሁ፡ ዋሾ ።
ቀልቀል (ትግ)፡ ኵስ ዐይነ ምድር በዐዘቅተ ኵስሕ አፋፍ ኹኖ የሚጣል።
ቀልቀል፡ አፋፍ ገደል (ግእዝ) ።
ቀልቀልቱ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀልቀሎ (ዎች)፡ የወጠጤ ስልቻ ። ኦሮ ግን ትንሿን ኰረጆ ትልቁን ቀልቀሎ ይለዋል።
ቀልበ ቢስ (ሶች)፡ ልበ ቢስ፡ ቀልበ መጥፎ ።
ቀልበ ደረቅ፡ የጋኔን ስም፡ ለዛ ሙጥጤ ።
ቀልበ ጮሬ፡ ሾላካ የማይጠመድ ። "ጮሬን" እይ ።
ቀልባ - ቅልብጭ፡ የቀለበጪ፡ ቀል ጣፋ ቅልጥፍ ስብቅል ።
ቀልባሳ፡ የታጠፈ ቀናፋ ።
ቀልባሽ፡ የቀለበሰ/የሚቀለብስ (ቀናፊ ") ።
ቀልባጣ (ቀልብ ዐጣ)፡ ቀባጣሪ፬ አፉ እንዳመጣ የሚናገር ።
ቀልባጣ፡ ቀባጣሪ፡ ቀልብ ።
ቀልቤ፡ ጫፉ ደረቅ አከቻማ ።
ቀልብ (ኦሮ)፡ ልብ፡ የልብ ዕውቀት ።
ቀልብ—ቀለበሰ ።
ቀልዝ፡ ፍልማ መሬት (ጐዣም) ።
ቀልደኛ (ኞች)፡ ቀልድ ወዳድ ቧልተኛ ፌዘኛ ዋዘኛ ።
ቀልድ፡ ከውነት የራቀ ጨዋታ ተረብ ቧልት ፌዝ ወዘበሬታ ።
ቀልጠፍ አለ፡ ፈጠን አለ፡ ቀለጠፈ ።
ቀልጠፍ፡ ፈጠን ።
ቀልጣሚ፡ የቀለጠመ/የሚቀልጥም (ቅልጥም መቺ ሰባሪ ") ።
ቀልጣማ፡ ሰባራ ቶሎ የሚሰበር ።
ቀልጣፊ - ቀልጣፋ (ፎች)፡ የሚቀለ ጥፍ፡ ከዝብዝብ የራቀ ፈጣን ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፲፯)") ።
ቀልጣፋነት፡ ቀልጣፋ መኾን ።
ቀልጥፍ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ፡ ፍጠን፡ መር በል ("(ማሕ. ፯፥ ፲፬)") ።
ቀመ፡ አመለጠ ጠፋ ታጣ (ተገ) ብሮ ።
ቀመለ (ቀሚል ቀመለ)፡ ቅማል አበጀ ያዘ፡ ኣፈራ ወለደ ።
ቀመለ፡ ለቀሙ በጥፍር ዳጠ ገደለ ።
ቀመመ፡ ቅመምን መድኀኒትን ሰበሰበ ፈጨ አላመ አዘጋጀ፡ ደባለቀ ቀላቀለ አንድነት አደረገ መጠነ ።
ቀመሰ (ቀሠመ)፡ ጣመ ለከፈ በጥቂቱ በላ ጠጣ ዋጠ፡ ("(ኢዮ. ፲፪፥ ፲፩)") ። "አቶ እከሌ መድኀኒት ስለ ቀመሰ እቤት ዋለ" ። "አብነትን" እይ ።
ቀመሰ፡ ተመታ ተደበደበ ።
ቀመሰ፡ ተቀበረ ። "ዐፈርን" ተመልከት ።
ቀመሳ - ቅምሻ፡ የመቅመስ ድርጊት ።
ቀመስ፡ መቅመስ ።
ቀመስ አደረገ፡ ቀመሰ ።
ቀመስ፡ የበላ ። "ፈረንጅን" እይ ።
ቀመረ (ቀምሮ ቀመረ)፡ ቈጠረ፡ መደበ ለየ ከፈለ ።
ቀመር (ዐረ)፡ ጨረቃ ።
ቀመር (ገመር)፡ የዥብ ንጉሥ ወቸገል መልኩና ጨፈረር ጠጕሩ ከዥብ ኹሉ የተለየ፡ ዥቦች ፈርተው ይሸሹታል፡ ትራፊውንም ይበላሉ ።
ቀመር፡ ቍጥር፡ የቍጥር መደብ ወይም ክፍል፡ ዐውድ ሰንጠረዥ ።"
ቀመር፡ ፍሬው ትንንሽ የኾነ አደንጓሬ ።
ቀመቀመ (ከመከመ)፡ ጫፍ ጫፉን ሰፋ ዘመዘመ ።
ቀመቀመ፡ ብዙ ጊዜ ጠጣ ።
ቀመቀመ፡ ወጣ በቀለ ቀነቀነ ።
ቀመት፡ የሚዛን ልክ ፪ ተረን ፩ ቀመት ነው ።
ቀመኛ (ቀበኛ)፡ ልብስ የሚበላ ከ ብት የልብስ ቀማኛ ።"
ቀመድማዳ - ቅምድምድ - ቅምድማጅ፡ የተቅመደመደ (ጕትት ሽምድምድ ") ።
ቀመጠ)፡ "ተቀመጠ" ብለኸ "ተቀማጭን" አስተውል ። በ የ ከ ለ መነሻ እየኾኑት ሲነገር፡ "በቅርብ የቅርብ ከቅርብ ለቅርብ" ይላል ።
ቀመጠ)፡ (ቀምጦ ቀመጠ)፡ አስ ቀመጠ)፡ ቍጭ አደረገ አሳረፈ ጐለተ፡ እነበረ ኣኖረ አቈየ አሰነበተ ("(ዘፍ. ፪፥ ፲፭፡ ፩ነገ. ፭፥ ፭፡ ሉቃ. ፱፥ ፲፬፡ ፲፭)") ። "ረፈቀን" አስተውል ። አስቀመጠ አስደራጊ ሲኾን ባድራጊነት መተ ርጐሙ (ቀመጠ) በዘመን ብዛት ስለ ተረሳ ነው ። (ዐወሰ) ብለሽ አስታወሰን ተመልከት ።
ቀመጠ) ብለኽ ተቀመጠን እይ ።
ቀመጠለ (ገመደለ)፡ ፈጽሞ አጐደለ አሳነሰ ።
ቀመጠለ፡ ዐረደ ጐመደ ቀነጠሰ ።
ቀሚ (ቀማሒ ቀማዒ)፡ የቀማ/የሚቀማ ።ሲበዛ "ቀሚዎች" ይላል ።
ቀሚሳዊ፡ አንደ ቀሚስ፡ የሰውን ገላ የሚያጠልቅ ።
ቀሚሴ (ቀሚስየ)፡ የኔ ቀሚስ ።
ቀሚሴ፡ የቂጥኝ ስም ።
ቀሚስ (ሶች)፡ በ፫ ወገን የተሰፋ የሴት ልብስ፡ ልኩ ፮ ዘንግ ፳፬ ክንድ ነው ።
ቀሚስ ለበሰ፡ ረዥም የግምጃ እጀ ጠባብ ዐብደላ ካኒ ተሸለመ አጠለቀ ።
ቀሚስ፡ ቀና
ቀሚስ፡ እጀ ሰፊ የቄስ የመነኵሴ ልብስ፡ ረዥም ጥብቆ የሸማ የሐር የዳባ ("(ዘፍ. ፴፯፥ ፳፫፡ ፴፪)") ።
ቀሚስ፡ ዋና ዲያቆን የሱቲ ቀሚስ ለብሶ "ተንሥኡ ጸልዩ" የሚል ።
ቀሚስ፡ የመሶብ ልብስ ።
ቀሚስ፡ የበቅሎ የፈረስ ኮርቻ ልብስ ።
ቀማ (ቀምሐ ትግ ቀምዐ)፡ ነጠቀ ወሰደ ("(ሚክ. ፪፥ ፪)")፡ ሸክሙን ካናቱ ሱሪውን ከባቱ ። (ተረት)፡ "ዥብ የኔ ስለው ወናፌን ቀማኝ" ። "ዘረፈን" እይ ።
ቀማ፡ መጥፋት መታጣት ።
ቀማመሰ፡ ለካከፈ ።
ቀማሚ (ዎች)፡ የቀመመ/የሚቀምም (ሰብሳቢ አዘጋጂ ") ። "መድኀኒት ቀማሚ" እንዲሉ።
ቀማማ፡ ነጣጠቀ ።
ቀማሪ፡ የቀመረ/የሚቀምር (ቈጣሪ መዳቢ ") ።
ቀማሽ (ሾች)፡ የቀመሰ/የሚቀምስ (ቀን ከሕዝብ አስቀድሞ በቤተ መንግሥት የሚበላ የሚጋበዝ መኰንን ባለማዕርግ ") ። "እንወራረድ አህያ እንረድ እኔ ጠ ባሽ፡ አንተ ቀማሽ" እንዲሉ እረኞች ።
ቀማሽነት፡ ቀማሽ መኾን ።
ቀማኛ (ኞች)፡ ዝኒ ከማሁ፡ ነጣቂ ዳንዴ ወንበዴ ሽፍታ ነጥቆ በረር ።
ቀማኛነት፡ ቀማኛ መኾን፡ ነጣቂነት ።
ቀማይ (ዮች)፡ የቀመለ/የሚቀምል ( ቅማል ገዳይ ") ።
ቀምሶ፡ ጥሞ ። "ቀምሶ ሰጠ" እንዲሉ።
ቀምቀሞ፡ እጅግ በጣም ዐጪር ጠጕር በራስና ባገጭ ላይ በቅሎ የሚታይ ።
ቀምቃሚ (ዎች)፡ የቀመቀመ/የሚቀመቅም (ሰፊ ዘምዛሚ ") ።
ቀምበር፡ የበሬ ዕቃ ። —ቀነበረ ።
ቀምቶ በላ፡ እየነጠቀ የሚበላ ።
ቀምቶ፡ ነጥቆ ።
ቀምጣላ - ቅምጥል፡ የተቀመጠለ (ጐ
ቀምጣይ፡ የቀመጠለ/የሚቀመጥል (አ ጐዳይ ") ።
ቀሰመ ። አቀሣሠም፡ አለቃቀም/መቅሠም ።
ቀሠመ (ቀሢም - ቀሠመ)፡ አበባን ደምን ርጥበት ያለውን ነገር ኹሉ ለቀመ ሰበሰበ መጠጠ ።
ቀሰመ፡ ለቀመ/ቀሠመ ።
ቀሰመ፡ ቀመመ እጣፈጠ ("(ግእዝ)") ።
ቀሰመ፡ ቀሰቀሰ ።
ቀሠማ፡ ለቀማ ስብሰባ መጠጣ ።
ቀሠም (ሞች - ቀሠብ)፡ የቀጪን መቃ ቍራጭ የማግ መደወሪያ ። "ቀለምን" እይ፡ "ቀለመ" ።
ቀሰም፡ ቀጪን መቃ ።—ቀሠመ ።
ቀሠም፡ የወርቅ የብር ጥብጣብ ።
ቀሰሰ (ቀሲስ - ቀሰ)፡ ቅስና ተቀበለ ። (ተረት)፡ "ያልተሾመ እያዝ፡ ያልቀሰሰ አይናዘዝ" ።
ቀሰሰ፡ ቀዘዘ ፈዘዘ ።
ቀሰስ (የፈዘዘ ") ።
ቀሰስተኛ (ኞች)፡ ፈዛዛ ።
ቀሰረ ። ቅሣር፡ ጭረት ።
ቀሰረ (ቀተረ)፡ ገተረ/አቆመ ።"ቀና'ገ'ሰና ተ ተወራራሽ መኾናቸውን" አትዘንጋ ።
ቀሰረ ።ቀሠተ፡ ደገነ ። ቀሰተ ።
ቀሠረ፡ ገተረ ።
ቀሰቀሰ (ትግ ቀስቀሰ - አወከ)፡ ነቀ ነቀ አነቃ አስነሣ ።
ቀሰቀሰ፡ ቀሰረ ።
ቀሰቀሰ፡ በረበረ ፈተሸ ። "ሌባ በተያዘጊዜ ዘበኞች ኪሱን ይቀሰቅሱታል" ።
ቀሠብ (ዐረ ቀጸብ)፡ መቃ ውስጠ ክፍት ዕንጨት ወይም ብረት ("(ማሕ. ፬፥ ፲፬)") ።
ቀሰብ፡ ባሕረ ጃን ።—ቀሠብ ።
ቀሠብ፡ ባሕረ ጃን የበቅሎ ዕቃ ጌጥ ዐልፎ ዐልፎ ብስ ነዳላ የሚታይበት፡ በያይነቱ ቀለም ያለው ወረቀት ።
ቀሠብ፡ ውድ የሬት ሽቱ ። በግእዝ "ዐልው" ይባላል ።
ቀሰተ (ቀስተወ)፡ ደገነ አጐበጠ ።
ቀሰተ፡ (ቋተ)፡
ቀሰተ፡ (ቋተ)፡
ቀሠጠ (ቀሢጥ - ቀሠጠ)፡ በስውር ከፍሎ ሰረቀ ወሰደ፡ ዐበለ ።
ቀሰጠ፡ ሰረቀ/ቀሠጠ ።
ቀሠፈ (ቀሢፍ - ቀሠፈ)፡ መዓት አመጣ፡ ዕድሜ አሳጠረ፡ ቀጪ ቀጠፈ፡ በድንገት ገደለ አጠፋ ባጪር አስቀረ ዐፍለኛን ("(ዘዳ. ፭፥ ፲፩ ። ፪ሳሙ. ፮፥ ፯)") ።
ቀሠፈ፡ ሰቀዘ ወጠረ አስጨነቀ፡ ጐን በስ ቀና አላሠኝ አለ ።
ቀሠፈ፡ ደገነ አጐበጠ ።
ቀሲስ፡ ቄስ ።"አቡነ ቀሲስ" እንዲሉ ።
ቀሳ (ዕብ ቃጻህ - ለየ)፡ ብቻ ብቻነት (ልዩነት ") ። ፈረንጆች "ካራንቴን" ከሚሉት ጋራ ይሰማማል ።
ቀሳ ወጣ፡ ከቤት ወደ ዱር ኼደ፡ በደን ተቀመጠ ተኛ ታመመ፡ ከቤተ ሰቡ ተለየ (የሚጋባ በሽታ ተስቦ ስለ ያዘው ") ።
ቀሣሚ፡ የቀሠመ/የሚቀሥም (ለቃሚ ሰብሳቢ ንብ ጥንዝዛ ጣዝማ ዝንብ ብራብሮ ወፍ ") ።
ቀሳሪ፡ የቀሰረ/የሚቀስር (ገታሪ ") ።
ቀሳራ - ቅስር፡ የተቀሰረ (ገታራ ግትር ") ።
ቀሳሽ (ሾች)፡ የሚቀስ (ቄስ የሚኾን ") ።
ቀሳቀሰ፡ በራበረ ።
ቀሳቀሰ፡ አነቃቃ ።
ቀሳች፡ የቀሰተ/የሚቀስት (ደጋኝ አጕ ባጭ ") ።
ቀሣጢ፡ የቀሠጠ/የሚቀሥጥ (ዐባይ ሌባ ") ። "ቀሣጢ ሌባ" እንዲሉ ።
ቀሣጢነት፡ ቀሣጢ መኾን (ሌብነት ዐባይነት ") ።
ቀሣፈተ፡ ቀላመደ ዐበለ ዋሸ ወላ ወለ ዘላበደ ቀባጠረ ቀባዠረ፡ ቅሥፈት የሚያመጣ ነገር ተናገረ ።
ቀሣፊ፡ የቀሠፈ/የሚቀሥፍ (ገዳይ አጥፊ መልአከ ሞት ") ።
ቀሣፋች፡ የቀሣፈተ/የሚቀሣፍት (ዐ ባይ ወላዋይ ቀባዣሪ ") ።
ቀሣፋችነት፡ ወላዋይነት ቀባዣሪነት ።
ቀስ አለ፡ ዝግ አለ ።
ቀስ አለ፡ ዝግ አለ ።—ቀሰሰ ።
ቀስ፡ ዝግ ። "ቀስ በል !" "ቀስ ብሎ እን ዲሉ" ። (ተረት)፡ "ሴትና ቄስ ቀስ" ።
ቀስ፡ ዝግ ።—ቀሰሰ ።
ቀስመን፡ የልብ ቃታ፡ ዘሩ ቀሰመ ነው ።
ቀስመን፡ ግድ ግዴታ ።
ቀሥም፡ አዝመራ ("(ግእዝ)") ።
ቀስር፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀስቃሽ (ሾች)፡ የቀሰቀስ/የሚቀሰቅስ (ነቅናቂ አስነሽ፡ በርባሪ ፈታሽ ") ።
ቀስቅስ፡ የልዑል ራስ ካሳና የልዑል ራስ እምሩ ፈረስ ስም (ነቅንቅ አንቃ አስነሣ ማለት ነው ") ።
ቀስተ ደመና፡ የደመና ደጋን (ባላ፬ ሕብር የማሪያም መቀነት ") ። "በበልግ ዝናም ጊዜ ጫፍና ፉ በሰሜንና በደቡብመካከሉ ወደ ላይ ወደ ሰማይ ኹኖ ይታያል ። ከላይ ወደ ታች አረንጓዴ ቀይ ብጫ ሰማያዊ ቀለም አለው" ።
ቀስተ ደመና፡ የደመና ደጋን (ባላ፬ ሕብር የማሪያም መቀነት ") ። "በበልግ ዝናም ጊዜ ጫፍና ፉ በሰሜንና በደቡብመካከሉ ወደ ላይ ወደ ሰማይ ኹኖ ይታያል ። ከላይ ወደ ታች አረንጓዴ ቀይ ብጫ ሰማያዊ ቀለም አለው" ።
ቀስተኒቻ፡ የንጨት ስም (ለቀስት ለወስፈንጠር የሚኾን ጕብጠት የሚስማማው ዕን ጨት ") ። ኹለተኛ ስሙ "ሰሪቴ" ይባላል ። "መቃን" ተመልከት ።
ቀስተኛ (ኞች)፡ በቀስት የሚዋጋ ባለ ቀስት (አውሬ የሚያድን ነዳፊ ") ("(ዘፍ. ፳፩፥ ፳)") ።
ቀስተኛ (ኞች)፡ በቀስት የሚዋጋ ባለ ቀስት (አውሬ የሚያድን ነዳፊ ") ("(ዘፍ. ፳፩፥ ፳)") ።
ቀስቱን ለጠጠ፡ ሳበ ወጠረ ገተረ አ ዘገበ ።
ቀስቱን ለጠጠ፡ ሳበ ወጠረ ገተረ አ ዘገበ ።
ቀስታ፡ ዝግታ ። በግእዝ "ድቡት ጽሚት" ይባላል፡ ንኡስ አገባብ ነው ። "ታቦት የተሸከመ ቄስ በቀስታ ይኼዳል" ።
ቀስት (ቶች)፡ የወስፈንጠር/የፍላጻ መወርወሪያ ደጋን (የጦር መሣሪያ ") ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፬)") ።
ቀስት (ቶች)፡ የወስፈንጠር/የፍላጻ መወርወሪያ ደጋን (የጦር መሣሪያ ") ("(፩ሳሙ. ፲፰፥ ፬)") ።
ቀሥፋታ፡ ዝኒ ከማሁ ለቀሣፋች ።
ቀረ (ቀረየ)፡ ተረፈ ዳነ ተተወ ("ሳይያዝ ሳይገደል ቀረ ") ።
ቀረ፡ ቈየ ዘገየ፡ ተቀመጠ ። "ሳይኼድ ሳይመጣ ቀረ፡ እቤት ቀረ" ።
ቀረ፡ ቆመ ተከለከለ ። "በኤልያስ ዘመን ዝናም ቀረ" ። ለእስራኤል የሚወርድ መና በፊንቆን ቀረ ።
ቀረ፡ ተለወጠ ዐለፈ ።
ቀረ፡ አነሰ ጐደለ ። "ሳይመላ ቀረ" ።
ቀረ፡ ዐጣ ነጣ ባዶ እጅ ኾነ ። መና ቀረ ።
ቀረመተ (ቀሪም - ቀረመ)፡ ከፈለ ተነተነ ("ሥጋን ዐጥንትን ") ።
ቀረመት - ቅርምት - ቅርጫን፡ የሙዳ ክፍል ።
ቀረሰሰ - ቀሰሰ)፡ አንቀረሰሰ፡ (ጥ፱) አዘገመ በቀስታ አስኬደ ወሰደ ። ትግሬ ሐባብም "ቀርሰሰ" ብሎ ከሳ ይላል ።
ቀረሰስ - ቀርሳሳ፡ የተንቀረሰሰ (ዝግተኛ ዘገምተኛ ") ።
ቀረረ (ቈሪር - ቈረ)፡ ጠለለ ጠራ ጥራት አገኘ (ቅራሪው አተላው በታች ጥሩው በላይ ኾነ ") ።
ቀረረ፡ የጦር ግጥም ገጠመ (አጕራራ ") ።
ቀረራ፡ የርሾ ጥላይ ።
ቀረርቱ፡ ሽለላ የጦር ዘፈን ።
ቀረሮ፡ የዛፍ ስም ።
ቀረሸ፡ ምግብን ከሆዱ ጥቂት ፍልቅ አደረገ አወጣ፡ አስታወከ አፈሰሰ ሕፃኑ ።
ቀረሸመ፡ ገጨ ሰበረ ።
ቀረሻሸመ፡ ሰባበረ ።
ቀረሻሽምቦ፡ ቅጠል ።—ቀረሸመ፡
ቀረሻሽምቦ፡ በቀላል የሚሰበር ዕንጨት (አገዳው ውስጠ ክፍት የኾነ ") ። "የጨቆ የረግረግ ቅጠል፡ መሽረብ ውሃ መምጠጫ መጠጫ ዕፅ" ።
ቀረሽ፡ የቀረው/የጐደለው ። "ዱላ ቀረሽ ላባ ቀረሽ" እንዲሉ ።
ቀረቀረ (ቀቀረ)፡ አገባ ሸጐረ ለገደ ወረወረ ።
ቀረቀረ (ትግ ቀርቀረ)፡ ከረከረ፡ አ ሳጥሮ ቈረጠ ።
ቀረቀረ፡ ጐረሠ በላ ። (ተረት)፡ "ጦም ከማደር ዳቦ ቀርቅር" ።
ቀረቀረ፡ ጥይትን ለጠመንዣ አጐረሠ ።
ቀረቀበ (ቀረበ)፡ ኹለት ሸክምን ጭ ንትን ባንድነት አሰረ ወደነ ጠመረ ቈረኘ አረተ ።
ቀረቀፈ፡ ከረከረ ።
ቀረበ (ቀርበ)፡ ቅርብ ኾነ (ለጠቀ ተጠጋ ") ("(ዘፍ. ፳፱፥ ፲)") ።
ቀረበ፡ ነዳ ወሰደ ከብትን ።
ቀረበ፡ እሰው ፊት ተቀመጠ ገበታው ።
ቀረበበ - ገረበበ)፡ አንቀረበበ፡ እንገረበበ፡ አንቀረደደ አንከረፈፈ ።በተገብሮነትም ይፈታል ።
ቀረበጠ)፡ አንቀራበጠ፡ ካንዱ ስፍራ ወደ ሌላው አዛውሮ አስቀመጠ ።
ቀረባ (ኦሮ)፡ ወረንጦ (ጫፍና ጫፉ በመቃረብ እሾኸን ሥንጥርን ቈንጥጦ ከእግር ከገላ የሚነቅል መሣሪያ መቈንጠግና መዘ ንጠያ ") ።
ቀረባ፡ የመንዳት ሥራ/መቅረብ ።
ቀረብ (ቀሪብ)፡ ጠጋ ለጠበቅ ።
ቀረብ አለ፡ ጠጋ አለ፡ ቀረበ ።
ቀረት አለ፡ ቅዝዝ አለ፡ ጥቂት ጐ ደለ ስፍሩ ።
ቀረት፡ አነስ ጐደለ ።
ቀረነ (ቀሪን - ቀረነ)፡ ቀንድ አወጣ፡ ጠላ ወጋ ።
ቀረነተ፡ በቅራና አጥብቆ አሰረ ቀረ ቀበ ።
ቀረና (ትግ - ቀርንዐ)፡ ቀንድ ቀንድ አለ፡ ሸተተ ገማ ። "ጐረናን" እይ ።
ቀረንደላ፡ የተቃጠለ እኸል ።
ቀረንጠሎ፡ ባሪያ (የባሪያ ወገን ወይም ልብሱ ") ።
ቀረዋ፡ ከወደ ጫፉ ቀና ያለ ጐራዴ ።
ቀረዋ፡ የብረት ቍና (በሐረርጌ የሚገኝ ") ። አንዳንድ ሰዎች "ቀረዋ" የሚባል ፈረንጅ ስላመጣው በርሱ ስም "ቀረዋ" ተባለ ይላሉ፡ እውነት መኾኑን እንጂ ።
ቀረዘ (ቀረጸ)፡ ያዘ እነሣ ተሸከመ ።
ቀረደደ (ቀረፀ)፡ ቈረጠ ቈረሰ ገመሰ (ጐመንን እንጀራን ምድርን ") ።
ቀረጠ (ቀረፀ - ጸ)፡ ቈረጠ አሾለ ።
ቀረጠ፡ ዕዳሪ አወጣ ።
ቀረጠ፡ ወደ ገበያ መጥቶ ከሚሼጥ ነገር ላይ አነሣ ወሰደ ("(ማር. ፪፥ ፲፬)") ። ወይም በዚህ ፈንታ አሞሌ ብር አላድ ሩብ መሐለቅ ተቀበለ ።፫ኛውን ዐጠረ ባ፭ኛ ተራ ተመልከት፡ "ቀረጸን" እይ ።
ቀረጠፈ (ቀረጠ - ቀጠፈ)፡ የጌሾን ቀንበጥና ቅጠል በቅርብ በቅርብ እየመታ ቈረጠ አጠቀነ አደቀቀ ። "የጐመንና የሥጋሲኾን ቀረደደ ከተፈ o ያሠኛል" ።
ቀረጠፈ፡ ሰውነትን ዐመመ ።
ቀረጣ፡ መቅረጥ ።
ቀረጣጠፈ፡ ቈራረጠ አጠቃቀነ አደ ቃቀቀ ።
ቀረጣጠፈ፡ ዐማመመ ።
ቀረጥ (ቀረፅ)፡ ካሥር አንድ ዐሹራ ።
ቀረጥ (ጦች)፡ ያነስተኛ ዛፍ ስም (ሰዎች እየቀረጹ የጭራ የጅራፍ የማማሰያ የማንካ የወስፌ ዕንወት ያደርጉታል።")
ቀረጪ)፡ አንቀራጩ፡ ቈረጠመ አንቀጫቀጨ (ቈሎን አፋጩ ጥርስን ") ።
ቀረጪጪ፡ አጥብቆና አጥልቆ ነከሰ ጐዳ አሳመመ (እስካጥንት ድረስ ") ።
ቀረጸ (ቀሪጽ - ቀረጸ)፡ ቀረጠ ዐነ ጠጠ ፈለፈለ ጐበጐበ አሰመጠ አሰነበረ ነቀሰ ።
ቀረፈ (ቀሪፍ - ቀረፈ)፡ ላጠ መለጠ ለጠጠ (ቅርፊትን አስወገደ ") ። ሰበረ ፈለጠ ነጠለ አነሣ ።
ቀረፈ፡ ተወ አጠፋ ።"ቂሙን ቀረፈ" እንዲሉ ።
ቀረፈፈ - ከረፈፈ)፡ አንቀረፈፈ፡ አረዘመ አንከረፈፈ አንቀረበበ ። በተገብሮነትም ይፈታል ። "ቀረደደ" ብለኸ "ኣንቀረደደን" እይ ።
ቀረፈፍ - ቀርፋፋ - ከረፈፍ - ከርፋፋ፡ ቂል ።
ቀረፋ፡ መቅረፍ ።
ቀረፋ፡ ሽቱነትና ቅመምነት ያለው ቅርፊት (ከባሕር የመጣ ") ("(ዘፀ. ፴፥ ፳፫ ። ኢሳ. ፵፥ ፳፬ ። ራእ. ፲፰፥ ፲፫)") ። በግእዝ "ቀንሞን" ይባላል ።
ቀሪ (ዎች)፡ የቀረ/የሚቀር (ተለዋጭ ዐላፊ የማይፈለግ ነገር ") ።
ቀሪ፡ አባት እናቱን ቀብሮ ሳይሞት የሚቈይ (ቋሚ ") ።
ቀሪቦ፡ ሞኝ ሰው ብርታት የሌለው ።
ቀሪቦ፡ ወዲያው ተበጥብጦ የሚጠጣ የዳር አገር ጕሽ ።
ቀሪነት፡ ቀሪ መኾን (ዐላፊነት ") ።
ቀራ፡ ሌሊት ከብትን ጠበቀ ("(ጐዣም)") ። ዘሩ በግእዝ "ቀርዐ" ነው ።
ቀራረመ፡ ለቃቀመ፡ ሰባሰበ።
ቀራረፈ፡ መቀራረፍ፡ መመላለጥ መላላጥ መፈ ላለጥ ።
ቀራቅር፡ በጠገዴ ወረዳ የሚገኝ ተማ ።
ቀራቢ (ዎች)፡ የሚቀርብ/የሚነዳ/የሚጠጋ (ነጂ ") ።
ቀራንዮ፡ በኢየሩሳሌም ውስጥ ያለ ቦታ ("የራስ ስፍራ" ማለት ነው ") ።
ቀራውሎ፡ ሞኝ ቂል።
ቀራጭ (ጮች)፡ የቀረጠ/የሚቀርጥ (እሿይ ዐጣሪ የገበያ ግብር ተቀባይ ") ("(ማቴ. ፱፥ ፲ - ፲፩ ። ሉቃ. ፫፥ ፲፪)") ።
ቀራጭነት፡ ቀራጭ መኾን ።
ቀራፊ (ዎች)፡ የቀረፈ/የሚቀርፍ/የሚ ልጥ/የሚመልጥ (ሰባሪ ፈላጭ ") ። "የሙጋድ ዕንጨት አቅራቢ" ።
ቀራፎ (ዎች)፡ የቅል ስባሪ ፋጋ፡ ቂል ሰው ።
ቀርም፡ የፍሬ፡ ለቀም፡ (ግእዝ) ።ሰው፡ እንዳቅሙ፡ እኸል፡ እንደ፡ ቀርሙ፡ እንዲሉ።
ቀርቀም፡ ቈረቈረ ።
ቀርቀም፡ በውሃ ዳር የሚበቅል ታናሽ ቅጠል ።
ቀርቀሬ (ቀልቀላዊ)፡ የቀርቀር (ቈላ ጐድጓዳ የታች ታች ") ።
ቀርቀር (ቀልቀል)፡ ገደል ተራራ ።
ቀርቀቦ፡ ማንቀርቀቢያ ሰፌድ ።
ቀርቃሪ፡ የቀረቀረ/የሚቀረቅር (አግቢ ሸጓሪ ") ።
ቀርቃሬ፡ ቀባ መሪ ወፍ ("(ጐንደር)") ።
ቀርቃቢ፡ የቀረቀበ/የሚቀረቅብ (ኣሳሪ ወዳኝ ") ።
ቀርቃባ (ቦች)፡ በኹለት ወገን የታ ሰረ መንታ ጭነት ።
ቀርቃባ፡ ጠፍር፡ ካንዳንድ በኩል ጫፉ እየታጠፈ የተሰፋ ቅራና ("የቀርቃባ ጠፍር ") ።
ቀርበብ - ቀርባባ፡ የተንቀረበበ/የሚንቀረበብ (ቀርደድ ቀርዳዳ ከረፈፍ ከርፋፋ ዦሮ ትልቅ ሰው ") ።
ቀርበቦ (ዎች)፡ በጋን ቂጥ የተበጀ የበሬ ግንባር ቈዳ ሚዛን ቍና ። "እስላም በመንደሯ በቀርበቦ ትማታለች" እንዲሉ ።
ቀርበታ፡ ሆድ (ሆደ ትልቅ ") ።
ቀርበታ፡ የውሃ አቍማዳ ።
ቀርበታ፡ የውሃ ኣቍማዳ ።
ቀርቦታል፡ ተጠግቶታል ። "ደጉን ሰው መንፈስ ቅዱስ ቀርቦታል፡ ክፉውን ሰው ሰይጣን ቀርቦታል" እንዲሉ ።
ቀርነ በግዕ፡ የበግ ቀንድ ("እሱን የሚመስል የድጕስ መሣሪያ ") ።
ቀርን (ግእዝ)፡ ቀንድ ።
ቀርካሓ፡ ቀርክሓ፡ (ከርካዕ)፡ የዛፍ፡ ስም፡ ውስጠ ክፍት፡ ዕንጨት ።እንዝርት፡ ተራዳ፡ ሣጠራ፡ ይኾናል፡ ለቤት፡ ሥራም፡ ያገለግላል ።
ቀርዱ፡ የአራራት ተራራ ።
ቀርዳጅ፡ የቀረደደ/የሚቀረድድ (ቈራጭ ገማሽ ") ።
ቀርጠሙሽ፡ የቀድሞ ዘመን የጋሻ ጌጥ ። "የሙሽ ቅርጥ" ማለት ይመስላል ። "ቅርጫንቀረመት ቀረጠ" ።
ቀርጣ፡ ዕዳሪ በማረሻ መስቀልኛ የሚ
ቀርጣፊ፡ የቀረጠፈ/የሚቀረጥፍ ።
ቀርጥ፡ የርሻ ክፍል መዛሮ ።
ቀሸ፡ አኰራ ለጠጠ ባነጋገር ።
ቀሸመደ፡ በፍጥነት ሰበረ አነከተ ።
ቀሸመድ - ቀሽማዳ - ቅሽምድ፡ የተቀ ሸመደ (ሰባራ ስብር ደካማ ") ።
ቀሸማመደ፡ ሰባበረ አነካከተ ።
ቀሸረ (ቀተረ)፡ ከሸነ/አሳመረ ።
ቀሸረ፡ ነፋ ቀበተተ ሆድን ።"ገሸረን" እይ ።
ቀሸረረ፡ ከሳ ደረቀ ።"ከሸለለን" ተመልከት ።
ቀሸረር - ቀሽራራ፡ የከሳ የደረቀ/ደረቅ ።
ቀሸቀሸ - ከተከተ)፡ ተንቀሻቀሸ፡ ተሰባበረ ተንከታከተ ።
ቀሻሪ፡ የቀሸረ/የሚቀሽር (ከሻኝ አሳማሪ ") ።
ቀሽመሪ፡ ሠቅጌጠኛ መታጠቂያ ።"መሪ ቄስ" ማለት ይመስላል ።
ቀቀለ፡ አሞቀ አፈላ አበሰለ አነፈረ (እኸልን ሥጋን ")፡ ወጥ ሠራ ("(ዘፀ. ፴፬፥ ፳፮ ። ፪ነገ. ፮፥ ፳፱ ። ሰቈ. ፬፥ ፲ ። ዘካ. ፲፬፥ ፳፩)") ።
ቀቀረ (ጸለወ)፡ ዦሮውን መለሰ ጣለ (ለመስማት ለማድመጥ ") ።
ቀቀበ፡ ነፈገ ሠሠተ ሰገበ ።
ቀቀበታም፡ ሥሥታም ንፉግ ስግብግብ ("ስገባ በል (ዮሴፍ)") ።
ቀቀበት (ቀቀባ - ሰገባ)፡ ንፍገት ሥሥት ።
ቀቀተ (ቄቀየ)፡ ነፈገ ጮቀ ቤሰ ሠሠተ ።
ቀቀት - ቅቅት፡ ንፍገት ሥሥት ።
ቀቃ - ቍቁ (ከካ)፡ መታ አቈሰለ ነደለ ፈነቀለ ። "ቃቃንን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው ።
ቀቃሪ፡ የቀቀረ/የሚቀቅር ።
ቀቃይ (ዮች)፡ የቀቀለ/የሚቀቅል (አፍሊ አንፋሪ ወጠ ሠሪ ") ። "ንፍሮ ቀቃይ ዶዮ ቀቃይ" እንዲሉ ።
ቀቅ፡ ትንሽ ካሳ ለቈሰለ የሚሰጥ ።
ቀቅ፡ ዋግ ብትን ድልኸ የሚመስል የእኸል በሽታ ስንዴን የሚመታ ቀጭ ብርድ ።
ቀበለ) አቀበለ፡ እጅ በጅ ሰጠ አስረከበ እሲያዘ ("(ነሐ. ፲፫፥ ፴፩)") ።
ቀበሌ (ዎች)፡ ገደማ/ዘንድ(ዳ)/ጋ ።
ቀበሎ፡ ድር ሲቋጠር በስተጥርስ በኩል ተቀምጦ መቀበል ።
ቀበረ (ቀቢር ቀበረ)፡ ራስን ወደ ምዕራብ እግርን ወደ ምሥራቅ አድርጎ ሬሳን አንጋለለ በዠርባ አስተኛ፡ በድንን ማን ኛውንም ነገር ዐፈር አለበሰ ሸፈነ፡ በጕድጓድ ውስጥ ደፈነ ደበቀ ሸሸገ ።
ቀበረ፡ ሰውን ጐዳ ጨቈነ (እንዳይታወቅ እንዳይከብር እንዳይጠቀም አደረገ ") ። (አዝማሪ)፡ "የወዲያ ሰዎች ክፋታቸው ሬሳ አስቀምጠው መብላታቸው" ። "የ.........ሰው መልካም ወንድሙን ሳይቀብር አይበላም" ("(ጦቢ. ፩፥ ፲፯፡ ፪፥ ፯)") ።
ቀበረረ) አንቀባረረ፡ አቀማጠለ አንደላቀቀ አሞላቀቀ (የልጅን ጠባይ አበላሸ ") ። በተገብሮነትም ይፈታል።
ቀበረር - ቀብራራ፡ የተንቀባረረ (እንቅ ብር ቅምጥል፡ አያት ያሳደገው ልጅ ") ።
ቀበራ፡ ደፈና (የመቅበር ሥራ ዐፈር ") ።
ቀበራርት፡ ዝኒ ከማሁ (የካህናት ዐማርኛ ") ።
ቀበር፡ የቀበረ ። (ተረት)፡ "ማን ይንገር የነበር፡ ማን ያርዳ የቀበር" ።
ቀበርቾ፡ መድኀኒትነት ያለው ዕንጨት፡ ሥሩ ወፍራምና ሞላላ ነው ። ሰው ትኵሳት በያዘው ጊዜ ይታጠነዋል፡ ትኵሳትንም በላብ የሚያጠፋና የሚቀብር ስለ ኾነ ቀበርቾ ተባለ ።
ቀበርቾ፡ የዕፅ ስም ። ቀበረ ።
ቀበሮ (ዎች)፡ ያውሬ ስም (የተኵላ ወገን የዱር ውሻ የበግ ጠላት ") ። (ተረት)፡ "ቀበሮ የበሬ ቍላ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ት ውላለች" ። "ቀበሮ" ማለት በቈፈረው ጕድጓድ ውስጥ ተቀብሮ ገላውን መደበቁን ያሳያል ። ተባቱም እንስቱም ቀበሮ ይባላል ። ኹለቱን ለመለየት ነው ።
ቀበሮች፡ ቀበሮዎች ("(ሕዝ. ፲፫፥ ፬)") ።
ቀበሮዋ - ቀበሮዪቱ፡ ያች ቀበሮ ።
ቀበሮው፡ ያ ቀበሮ ።
ቀበቀበ (ገበገበ)፡ ኹለተኛ በርጥብ ዐረሰ ዐየመ ኣለሰለሰ ።
ቀበቀበ፡ ተከለ ቸከለ ።
ቀበቀበ፡ እንደ ገና ብረትን ቀጠቀጠ ዐደሰ አሾለ አሰላ ።
ቀበቀበ፡ ደጅ መታ ቍር ቍር አደ
ቀበቀብ - ቀብቃባ፡ ገበገብ/ገብጋባ (ንፉግ ሥሥታም ") ።
ቀበተተ፡ አሳበጠ ነፋ ወጠረ ነረተ ። "የነፋሽ ፥ የቀበተተሽ" እንዲል ኵስኵስት ተጫዋች ። "ቀበጠጠን" እይ፡ የዚህ ለውጥ ነው ።
ቀበታ፡ የባጥ ገበታ ዋልታ ። "ቀና ገ" መወራረሳቸውን አስተውል ።
ቀበቶ (ዎች)፡ ባንድ ወገን በጫፉ ላይ ዘለበት ያለበት ሰፊ ወይም ጠባብ ከነት ከተንቤን የተበጀ መታጠቂያ (የሱሪ የቀሚስ የጐራዴ የሽጕጥ መያዣ ") ።
ቀበነነ (ትግ. ሐባ ቀበነ በሰና)፡ ነፋ/ወጠረ ቀበተተ ።
ቀበና (ኦሮ)፡ ቀዝቃዛ ውሃ፡ ወይም ሌላ ነገር ።
ቀበና፡ በአዲስ አበባ ውስጥ በስተምሥራቅ ያለ ወንዝ፡ ቀበሌውም በወንዙ ስም ቀበና ይባላል ።
ቀበኛ (ቀማ)፡ ልብስ የሚበላ ከብት (በሬ ላም አህያ በቅሎ ") ። "የልብስ ቀማኛ" ማለት ነው ። ሲበዛ "ቀበኞች" ያሠኛል ።
ቀበዘ - ቃበዘ፡ ወዲያና ወዲህ ዐይኑን ወረወረ፡ ዦሮውን ጣለ (የጠፋውን ለመሻት ወሬ ለመስማት ዞረ ዛበረ ባዘነ ") ።
ቀበዝባዛ - ቅብዝብዝ፡ የተቅበዘበዘ (ቅንዝንዝ ባካና ") ።
ቀበዞ፡ የቀበዘ (ፊትና ኋላ የሚሮጥ የሚያይ የሚመለከት እግረ ቀላል ") ።
ቀበያውበጠ፡ ቀላወጠ ።"የቅኔ ' ቤት ' ዐማርኛ ' ነው" ።
ቀበደደ (ቀበተተ)፡ መታ ደበደበ ሰረረ ። "ቀበጠጠን" አስተውል ።
ቀበደድ - ቀብዳዳ - እንቅብድ -
ቀበጠ (ቀብጸ)፡ ጨዋነትን ጭምት ነትን ዐጣ (ተወዘወዘ ተነቃነቀ ዘለለ ፈነደቀ ተጫወተ ") ። (ተረት)፡ "የቀበጡ ለት ሞት አይገኝም" ። "ወበራን" እይ ።
ቀበጠጠ (ቀበለ)፡
ቀበጠጠ፡ ቀበተተ ።
ቀበጢና፡ የቀበጠች (ዕረፍት አልባ ") ። ፫ኛውን "ቅብጢ" ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀበጣጠረ፡ ለፋለፈ መላልሶ ተናገረ ።
ቀበጥ (ጦች)፡ እብድ ዐይነት (ልጅ አይሉት ዐዋቂ ከፈሱ የተጣላ ሰው አፍ ቂጡ የሣቀ ") ።
ቀበጥባጣ - ቅብጥብጥ፡ የተቅበጠበጠ (ቍንጥንጥ ብስጩ ") ።
ቀቢ (ዎች - ቀባዒ)፡ የቀባ/የሚ ቀባ (ለቅላቂ ደላሽ ") ። "ቀለም ቀቢ" እንዲሉ ። "ቅቤ"፡ ከተናጠ ወተት የሚገኝ ውጤት ። የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል። "ለጋ ቅቤ" "ለስታ ቅቤ" እንዲሉ ።
ቀባ (ስም)፡ ማጓ (በዋሻ በፍርኵታ በገደል ንቃቃት በውስጠ ክፍት ዛፍ መካከል ያለ ንብ ከነማሩ ") ።
ቀባ (ቀብዐ)፡ ላከከ ለቀለቀ ደለሰ ቅቤን ። የሕፃንን ሕዋሳት ሜሮን አስነካ፡ በራስ ላይ ዘይት አፈሰሰ፡ አከበረ ሾመ ሥልጣን ሀብት መብት ችሎት አሳደረ ዐደለ ሰጠ፡ ካህን ነቢይ ንጉሥ አደረገ ። (ተረት)፡ "አልቀባም ብትል ትመስክር" ።
ቀባ፡ ኀጢአተኛ በደለኛ አስመሰለ፡ ስም አሳደፈ ።
ቀባ መሪ፡ ሰውን ወደ ቀባ የምትመራ ወፍ ። በቡልጋ "ቡሊ"፡ በመራቤቴ "ባቲ"፡ በጐንደር "ቀርቃሬ" ትባላለች ።
ቀባ ቈራጭ፡ እዱር ኼዶ ቀባ የሚቈርጥ ሰው ።
ቀባ፡ ኰላ ዐደሰ (ጌጥን በወርቅ ቤትን በቀለም በበረቅ ") ።
ቀባሪ (ዎች)፡ የቀበረ/የሚቀብር (ዐፈር መላሽ ደፋኝ ") ። (ተረት)፡ "ቀባሪ በፈጣሪ" ። "ደኸየ" ብለኸ "ድኻን" እይ ።
ቀባሪ፡ የጐዳ/የሚጨቍን ። "ድኻ ቀባሪ" እንዲሉ ።
ቀባሪነት፡ ቀባሪ መኾን ።
ቀባርዋ፡ በወልቃይት የሚደረግ የዱላ ምክት ። በመርሐ ቤቴና በዜጋመል ቈላ አ ባት ልጁን አጋም ሥር አቁሞ የዱላ ምክት ያስተምረዋል ። በመቺና በመካች መካ ከል ወደ ላይ አሳይቶ እግርን፡ ወደ ታች አመልክቶ ትከሻን በማለት ታላቅ ቅልጥፍና ይታያል ። ይኸንንም ትምርት ያወቀ አንድ ሰው ዐሥር ሰው ሊመታ ይችላል ። የቀባርዋ ምስጢር ሸማን በግራ እጅ ላይ ጠቅሎ ራስን መከለል መጋረድ ነው ። በመቺና በተ መቺ (በመካች) መካከል ያለውንም ያመታት ስም አንቷን ዳባዲ እስካሥር ይቈጥረዋል ።
ቀባሮች፡ የቀበሩ/ቀባሪዎች ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፬ - ፲፭)") ።
ቀባበረ፡ መላልሶ ቀበረ ደፋፈነ ።
ቀባባ፡ መላልሶ ቀባ ደላለሰ አባበሰ ።
ቀባዠረ፡ ቃዠ ወዣበረ ዘባረቀ (የኾነ ያልኾነውን ተናገረ ") ። "ቀባዠረን" ተመልከት ።
ቀባዣሪ (ዎች)፡ የቀባዠረ/የሚቀባ ዥር (ወዣባሪ ዘባራቂ ") ።
ቀባጠረ፡ አገኝ ዐጣውን የባጥ የቈ ውን ተናገረ (ለፈለፈ ዘበዘበ ") ። "ቀባዠረን" ተመልከት ።
ቀባጣሪ (ሮች)፡ የቀባጠረ/የሚቀባ ጥር (ተናጋሪ ለፍላፊ ") ።
ቀባጣሪ፡ አማጭ (የጋብቻ መካከለኛ ") ። "ገለገለ" ብለኸ "ግልገልን" እይ ።
ቀባጣሪነት፡ ቀባጣሪ መኾን (ለፍላ ") ።
ቀባጭ (ጮች)፡ የቀበጠ/የሚቀብጥ ።
ቀብር፡ መቃብር (የሬሳ ማጋደሚያ ") ። (ግጥም)፡ "ቀብር ቀብር አሉ፡ ቀብር ምናለበት፡ ደግ ሥራ ሠርቶ ገብቶ ቢተኙበት" ። ቀበሮ (ቀበረው - ግእዝ) ።
ቀብር፡ ሥርዐተ መቃብር (ለቅሶ ") ። "እቀብር ውዬ መጣኹ" እንዲሉ።
ቀብቀብ አለ፡ ተንቀበቀበ ።
ቀብቃቢ፡ የቀበቀበ/የሚቀበቅብ (ዐራሽ ቀጥቃጭ ቸካይ ") ።
ቀብቃባነት፡ ቀብቃባ መኾን (ገብጋ ") ።
ቀብታች፡ የቀበተተ/የሚቀበትት (ነፊ አሳባቹ ") ።
ቀብዣራ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀብዥር፡ የነጋሪት ድምጥ ። "አብጅርን" አስተውል ።
ቀብድ - ቃብዱ (ኦሮ)፡ መያዣ (ዕቃን ከመግዛት በፊት ለሸያጩ የሚሰጥ ገንዘብ ") ። በግእዝ "ዐረቦን" ይባላል ።
ቀተለ (ቀቲል - ቀተለ)፡ ገደለ (ነፍስ አሳለፈ ") ። "ጕራጌ እግዜር ይማርኸ ቢሉት፡ ይቀትለኝ ማን ኹኖ እንዳለ" ።
ቀተረ (ቀቲር - ቀተረ)፡ ፮፻ሰዓት ኾነ፡ ፀሓይ ወይም ጮራው በሰማይ መካከል በራስ አንጻር ታየ፡ ከዚህ የተነሣ ጥላ ታጣ ።
ቀተረ፡ ቀረቀረ/ሸጐረ ።"ገተረንና ቀሰ ረን" ተመልከት ። "ገና ቀ'ሰና ተ ይወራረሳሉና፡ ፫ቱ ኹሉ በምስጢር አንድ ናቸው" ።
ቀተረ፡ ነፋ አሳበጠ ወጠረ ቀበተተ ።"የቂል በትር ሆድ ይቀትር" እንዲሉ ።"ቀሸ ረን" አስተውል ።
ቀተራ፡ ርኤም፡
ቀተራ፡ በኀይል ጮኸ አገሣ ጐደራ ።
ቀታሪ፡ የቀተረ/የሚቀትር (ቀርቃሪ
ቀታሪ፡ የቀተረ/የሚቀትር (ቀርቃሪ ሸጓሪ ነፊ ወጣሪ ") ።
ቀትረ ቀላል፡ ቅርጠ ቀላል ("ወፍ ራም ያይዶለ ሰው ") ።
ቀትር፡ ቁመና ("የሰውነት ቅርጥ ቀጥ ያለ ") ።
ቀትር፡ እኩለ ቀን ("አውራ ተሲያት ሙቀት የሚጸናበት ጊዜ ") ። "ጌታችን በቀትር ተሰቀለ" ።
ቀነ ጐደሎ
ቀነሰ (ነቀሰ)፡ ነሣ አጐደለ አሳነስ ። "ሴትዮ የተመላው ጠላ እንዳይፈስ ቀንሺው"
ቀነረ፡ ነፋ አሳበጠ ።
ቀነቀነ (ቈንቈነ)፡ ነቀዘ ጠነጠነ ("(ኢዮ. ፵፩፥ ፲፱)") ።
ቀነቀነ፡ መረመረ ፈተሸ ። (ተረት)፡ "ለንጉሥ የቀነቀነ ወርቅ ለግዜር የቀነቀነ ጽድቅ" ።
ቀነቀነ፡ ሠሠተ ነፈገ ።
ቀነቀነ፡ ቃኘ ዜማ ዠመረ ዘፈን አወረደ ።
ቀነቀነ፡ ቅንቅን አፈራ በርቀት በላ አሳከከ ።
ቀነቀነ፡ በቀለ ቀመቀመ ።
ቀነበረ፡ ደረቀ ጠና በእሳት በፀሓይ ተንቃቅቶ ።
ቀነበበ፡ ከበበ ክብ አደረገ ። "ጨደደን" ተመልከት ።
ቀነባ፡ ሰበረ ቀለጠመ ("(ሕዝ. ፲፯፥ ፬)") ።
ቀነተ (ቀኒት - ቀነተ)፡ በወገቡ ላይ ጠፍርን መቀነትን ጠመጠመ ታጠቀ አሰረ ሸብ አደረገ ።
ቀነኛ፡ የቀን ምሳ ዱማች በቀትር የሚበላ ።
ቀነወረ፡ ደረቀ ጠነከረ ከረረ ጨመረ፡ ዐጪር ኾነ ቈረቈዘ ።
ቀነዘ (ፈነዘ)፡ ከለፈ ከነፈ ። "ከነዘን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀነዘረ፡ አመነዘረ ሴሰነ ባንዲት ሴት የማይረጋ የማይወሰን ኾነ ሰውየው ።
ቀነዘረ፡ ፈጥኖ አደገ ረዘመ ከሌላው በለጠ እኸሉ ።
ቀነዘፈ (ቀዘፈ)፡ ዐረደ ቀነጠሰ፡ ባንድ ጊዜ ከወገብ ቈረጠ፡ መለመለ ።
ቀነዘፈ፡ እንባ አወረደ ዱብ ዱብ አ ደረገ አንጠባጠበ ።
ቀነዝናዛ - ቅንዝንዝ፡ የተቅነዘነዘ/የሚ ቅነዘነዝ (ፍንዝንዝ ክልፍልፍ ") ።
ቀነደለ፡ ቀነደበ በጣ ቈረጠ ቅንድብን፡ መጥፎ ጠጕርን ከሥሩ ለመንቀል ለማጥፋት ።
ቀነደረ (ቀነጠረ)፡ ቄደረ ኰራ ።
ቀነደሸ፡ ሰበረ አነከተ ቀንድን ሌላው ንም ። "ገነደሰን" እይ ።
ቀነደሸ፡ አረጀ ጐበጠ ። "የቀነደሸ ሽማ ግሌ" እንዲሉ።
ቀነደበ፡ ቀንድን ዐናትን መታ በቀንድ ወይም በሌላ ።
ቀነደበ፡ ቅንድብን ቀነደለ ።
ቀነደበ፡ በዋንጫ ጠጣ አጐደለ ።
ቀነዳ፡ እንደ ቀንድ ደረቀ ከረረ ። እ ከሌ ወገቡ ቀንድቶ ጐንበስ ቀና ማለት አቅቶታል ።
ቀነጀ፡ ተነጠለ (ነጠላ አንድ ብቻ ኾነ ") ።
ቀነጠሰ፡ ቀነጠበ ቈረጠ በጠሰ ጐመ ንን ሳማን ዐንገትን ።
ቀነጠረ - ቀጠረ - ነጠረ)፡ አሽቀነ ጠረ፡ አርቆ በኀይል ወረወረ ጣለ ።
ቀነጠበ (ቀንጠበ)፡ ከፍ ቈረጠ በ ጠሰ ቀነጠሰ ።
ቀነጣ ። ቀኖና፡ ሕግ ሥርዐት ደንብ ።
ቀነጣ ። ቅንጦት፡ ጥጋብ ።
ቀነጣ (ቀንጠወ - ቀነጸ ። ትግ ቀን ጥአ)፡ ታበየ ራሱን ከፍ አደረገ፡ ርስዎ ያ ለውን አንተ አለ፡ ነቀፈ አዋረደ፡ አላገጠ መስቃ ተናገረ ።
ቀነጣ፡ አንደዬ ወደ ላይ አንደዬ ወደ ታች - አለ ።
ቀነጣጠሰ፡ ቀነጣጠበ ቈራረጠ በጣጠሰ ።
ቀነጣጠበ፡ ቈራረጠ በጣጠሰ ቀነጣጠሰ ።
ቀነጨበ (ትግ ቀንጨበ - አነቀረ)፡ በጥቂቱ ተማረ ቈነጠረ ቈንጥሮ ወሰደ ።
ቀነጨበ፡ የገበጣ ጨዋታ ዠመረ ።
ቀነፈ፡ ዐጠፈ መለሰ ቀለበሰ ሸበለለ የልብስን ጫፍ ።
ቀነፌ (ቀነፋዊ)፡ የሰው ስም (ጠ ላትን ዕጠፍ መልስ ማለት ነው ") ።
ቀነፌ፡ የኔ ቀነፍ ።
ቀነፍ፡ ዝኒ ከማሁ (ሸብላይ ") ።
ቀና (ቀኒእ)፡ መቅናት ።
ቀና (ቀንአ ሐመመ)፡ ተመቀኘ፡ ምቀኛ ኾነ ። "መቀኘን" እይ፡ ከዚህ ወጥቷል ። መዠመሪያው የደግ፡ ይህ የክፉ ነው ። (ግጥም)፡ "አጐንብሼ መኼድ አላውቅ ብዬ እንደ ሰው፡ እቀና ብዬ ነው ቤቴ የፈረሰው" ።
ቀና (ቀንአ ረትዐ)፡ ቀጥ ኣለ፡ ቀጥታ ኾነ ።
ቀና (ተቀንየ)፡ ተገዛ ዕርሻ ተማረ ለመደ ሰላ ወይፈኑ ።
ቀና፡ ለማ ሰመረ በጀ ደኑ በረሓው ።
ቀና፡ ቀጥታ እውነት ። "ቀናውን ተና
ቀና፡ ታዘዘ ዕሺ በጎ አለ፡ ቅን ኾነ አሽከሩ ።
ቀና፡ ታጠቀ ገበረ አገሩ ።
ቀና አለ፡ ወደ ላይ አየ ።
ቀና፡ አላቀረቀረም ("(ዮሐ. ፰፥ ፯፡ ፲)") ።
ቀና አደረገ:ራስን ደገፈ አንተራሰ ።
ቀናሽ (ሾች):የቀነሰ/የሚቀንስ (አ ጕዳይ ") ።
ቀናተኛ (ኞች) (ቀናኢ)፡ ("(ናሆ. ፩፥ ፪)")፡ በገንዘቡ በሰው የቀና/የሚቀና (ምቀኛ ") ። (ተረት)፡ "የሙት ቀናተኛ ሚስቴን ዐደራ" ይላል ።
ቀናት - ቀኖች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች ።
ቀናት (ቀናእት)፡ የቀኑ/የሚቀኑ (ምቀኞች ") ።
ቀናነሰ፡ ነሣሣ አጐዳደለ ።
ቀናው ቀንቶታል፡ ኾነለት ኾኖለታል፡ ገባው ታወቀው፡ ጕዳዩ ተፈጸመለት ። "ግዳይ ቀናው" እንዲሉ።
ቀናፊ፡ የቀነፈ/የሚቀንፍ (ዐጣፊ ቀል ባሽ ") ።
ቀናፋ - ቅንፍ፡ የተቀነፈ የተመለሰ (የተቀለበሰ ምልስ ቅልብስ ክፈፍ ") ።
ቀኔ፡ ዘገር አበታ ጦር ("(ዘኍ. ፳፭፥ ፯ - ፰)") ።
ቀን (መዓልት)፡ የብርሃን ስም፡ ከጧት እስከ ማታ ያለው ጊዜ፡ ፲፪ የብርሃን ሰዓት ("(ዘፍ. ፩፥ ፭)") ። "ቀን ለሰራዊት፡ ሌሊት ለአራዊት፡ ቀንና ሌሊት" እንዲሉ። (ግጥም)፡ "መሸ መሰለኝ ሲጨልም፡ እንደ ቀን ጣይ የለም" ። ደቂቅ አገባቦች በ "የ" "ከ" "ለ" "ወደ" በመነሻ እየተጨመሩበት ሲነገር፡ "በቀን" "የቀን" "ከቀን" "ወደ ቀን" "ለቀን" ይላል ።
ቀን (ቀነየ)፡ ፳፬ ሰዓት (ሌሊትና መዓልት ") ።በግእዝ "ዕለት" ይባላል ። "አንድ ቀን ኹለት ቀን" ። "ቀንና ጨርቅ እንደ ምንም ያልቅ" እንዲሉ። ዕለትን ቀን ማለት በፀሓይ ነው፡ በጨረቃ ግን ሌሊት ይባላል ። ዳዊት ("(ይውዕል ወይትቀነይ እስከ ይመሲ)") ይላልና ("(መዝ. ፻፫፥ ፳፫)") ።የቀን ምስጢር ሥራ መሥሪያነትን ያሳያል ።
ቀን (ቀን)፡
ቀን ባላ ።
ቀን አያውቁ፡ ዓለማውያን ሰዎች የሚሞቱበትን ቀን አያውቅም ።
ቀን ኾነ፡ በጣም ረፈደ ። ቀን መቍጠሪያ፡ ያ፲፪ቱን ወር ዝር ዝር ከአ፩ እስከ ፴ የሚቈጥር ሰሌዳ ወይም ሰንጠረዥ ። በግእዝ "ዐውደ ዕለት" ይባላል ።
ቀን ወጣ፡ ክረምት ዐለቀ ። "ቀን ወጣ ብር ነጣ" እንዲሉ።
ቀን ወጣ፡ ክፉ ጊዜ ዐልፎ ደግ ዘመን መጣ ።
ቀን ወጣለት፡ ሀብታም ኾነ ከበረ ። ቀን ጣለው፡ ተዋረደ ተቸገረ ዐጣ ነጣ ።
ቀን ጐደለበት፡ አደጋ ወደቀበት ሙ ከራ አገኘው ።
ቀን) ብለኽ ቅኔን አስተውል።
ቀንሪ፡ የሚቀነጭር ።
ቀንቃኝ (ኞች)፡ የቀነቀነ/የሚቀነ ቅን (መርማሪ ፈታሽ፡ ዘፈን ዠማሪ ") ("(ዕዝ. ፪፥ ፷፭)") ።
ቀንቃኝነት፡ ቀንቃኝ መኾን (መርማ ሪነት ዠማሪነት ") ።
ቀንበር ።
ቀንበር - መንቈር ። ቀንበር ("(ግብ. ሐዋ. ፲፭፥ ፲)") ።
ቀንበር - ቀምበር (በረ ቀን - በረ ቀምሕ)፡ የቀን የፍሬ በር እየተባለ ይተረ ጐማል ።
ቀንበር (ሮች)፡ ሳይቈረጥ በቁሙ ተልጦ ላይ ላዩ የደረቀ በርሻ ጊዜ በበሬ ትከሻ የሚውል ጥኑ ጠንካራ ዕንጨት፡
ቀንበር ሰበር፡ ዳንዴ ወንበዴ ሕግ አፍራሽ ።
ቀንበጥ (ቀነጠበ)፡ ለጋ እንቦቀቅላ ለምለም ጫፍ ያልጠና ቅጠል ከነዕንጨቱ ።
ቀንበጦች፡ ለጎች ለምለሞች ።
ቀንባራ - ቅንብር፡ የቀነበረ (ደረቅ እን ጀራ ") ።
ቀንቧ አለ፡ እንደ ቅንቦ በፍጥ ነት ተሰበረ ተቀለጠመ ።
ቀንዛሪ (ዐረ ኸንዚር)፡ በልቶ የማ ይጠግብ ዐሣማ ።
ቀንዛሪ፡ የቀነዘረ/የሚቀነዝር (እንዳሣማ በቃኝ የማይል ") ።
ቀንዛፊ፡ የቀነዘፈ/የሚቀነዝፍ (ዐራጅ መልማይ አፍሳሽ ") ።
ቀንዛፋ - ቅንዛፊ፡ የተቀነዘፈ ምልማይ ።
ቀንደ መለከት፡ ከቀንድ የተበጀ የቀንድ መለከት፡ "ቀንዳ መለከትም" ይባላል ።
ቀንደ ገላላ፡ ቀንዱ ወደ ጐን የኼደ ።
ቀንደ ጐዳ፡ ቀንዱ ወደ ዦሮው የወረደ የተጠመዘዘ በሬ ።
ቀንደኛ (ኞች)፡ የሕዝብ መሪ ዋና አል ጉባኤ ተጠሪ ተናጋሪ ።
ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ምድር አበስ፡ ዐይቦ የሚባል በሬ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክና ሰው ።
ቀንዲል ።
ቀንዲል፡ የማብሪያ ስም፡ የፈትል የዘይት የቅባኑግ የሻማ (የሞራ) መደብ ከሸክላ ወይም ከብረት የተሠራ፡ ጌጠኛ መቅረዙ ከጠ ንካራ ዕንጨት የተቀረጸ ("(ኤር. ፶፪፥ ፲፱)") ። ይህ
ቀንዲሎች፡ ማብሪያዎች ("(ዘፀ. ፴፥ ፬፡ ፳፭)") ።
ቀንዲት፡ የእንስት በግ ስም ።
ቀንዳ ቀንዳ አለ፡ እፊት እፊት እ በልጥ እበልጥ አለ ባነጋገር ባካኼድ ።
ቀንዳ፡ ቀንድ ። "ቀንዳ መለከት" እንዲሉ።
ቀንዳላ - ቅንድል፡ የተቀነደለ ተቈርጦ የወደቀ ።
ቀንዳማ፡ ዝኒ ከማሁ (ባለቀንድ ") ።
ቀንዳም (ሞች)፡ ቀንደ ረዥም በሬ ዶባ አጋዘን ሳላ ።
ቀንዳሻ፡ የተቀነደሸ (ሰባራ ") ።
ቀንዳሽ፡ የቀነደሸ/የሚቀነድሽ (ቀንደ ሰባሪ ") ።
ቀንዳቢ፡ የቀነደበ/የሚቀነድብ (መቺ ") ።
ቀንዳውጣ (ቀንድ አውጣ)፡ የተ ንቀሳቃሽ ስም፡ በበጋ ደርቆ ይሞትና በክረምት ታድሶ ቀንድ የሚያወጣ ዛጐል ልብሱ
ቀንዳይ፡ የቀነደለ/የሚቀነድል (በጪ ቈራጭ ") ።
ቀንድ (ቈንደየ ቀርን)፡ በአንስሳትና በአራዊት ራስ ላይ የበቀለ፡ ሥጋዊ ጦር ጸብት ዋንጫና ዋጋምት መለኪያ የንዝርት ራስ የሚኾን ። አራዊት የተባሉ የዱር እንስሳት ናቸው ። "አውሬን" አስተውል ።
ቀንድ ከብት፡ ቀንድ ያለው የቀንድ ከብት (በሬ ላም የቤት እንስሳ ") ።
ቀንዶ፡ ያጋዘን ዐይነት የዱር እንስሳ ። በ፪ቱ ቀንዶቹ ላይ ብዙ የቀንድ ዐጽም አ ለው፡ ዕድሜው በቀንዱ ብዛት ይቈጠራል ። ዐይነቱ ብዙ ስለ ኾነ በግእዝ ድስክን ርኤም ሀየል ይባላል ። ልጆችም በተረታቸው ሰባት ቀንዶ ይሉታል ። ይኸውም ምሳሌ ከራእየ ዮሐንስ የመጣ ነው ። እንደዚሁም ብዙ ቀንድ ያለው ዋሊያ የፌቆ ዐይነት በስሜን ተ ራራ ይገኛል ።
ቀንዶች፡ የንስሳና የአውሬ ጦሮች የበዳ ጸብቶች ።
ቀንጃ፡ አጣማጅ የሌለው በራ ። "ጥንድ ከቀንጃ" እንዲሉ።
ቀንጠልባ (የቀን ተልባ)፡ ጥልቅ ብዬ ለፍላፊ ።
ቀንጠፋ፡ ስምና አንቀጽ ይኾናል ። ጌታ ችን የተሰቀለ ለት ቀን ጠፋ ("(ማቴ. ፳፯፥ ፵፭)") ።
ቀንጠፋ፡ በቈላ የሚበቅል እሾኻም ዕን ጨት ።
ቀንጣ ቀንጣ አለ፡ ፈጠን ፈጠን አለ ።
ቀንጣሽ (ሾች)፡ የቀነጠሰ/የሚቀነጥስ (ቀንጣቢ በጣሽ ") ።
ቀንጣቢ፡ የቀነጠበ/የሚቀነጥብ (ቈራጭ በጣሽ ቀንጣሽ ") ።
ቀንጣባ - ቅንጣቢ - ቅንጥብ፡ የተቀነጠበ (ብጥስ ቅንጥስ ") ።
ቀንጫራ - ቅንጭር፡ የቀነጨረ (ጠን ካራ ጥንክር ዐጪር ") ።
ቀኖት፡ ችንካር ምስማር (ግእዝ) ።
ቀኖና፡ ንስሓ የኀጢአት ቅጣት ።
ቀኖና ያዘ፡ ንስሓ ገባ በሱባዔ ተቀ መጠ ።
ቀኘ - ቀነየ)፡ አስቀኘ፡ ቅኔ እሳ ወቀ አሰጠ ። "ገኘ"ን እይ፡ አካኼዱ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቀኛዝማች (ቾች) (ቀኝ አዝማች)፡ የቀኝ አዝማች (ከሻለቃው በስተቀኝ ስፍራ ጭፍራውን የሚያዘምት የጦር መሪ ") ። "ግራዝማችን" ተመልከት ።
ቀኛዝማች አሻግሬ)፡ የደጃች ባልቻ በዥሮንድ ። በአዲስ አበባ ወይም በሲዳሞ ወንድና ሴት ልጅ በወለዱ ጊዜ ሕፃናቱን ወደ ወግዳ ይልካሉ፡ ወንዱንም ኾነ ሴት ልጃቸውን ለባላገር ይድራሉ።
ቀኛዝማችነት ተሾመ፡ ቀኛዝማች ተባለ፡ ማዕርግ አገኘ ።
ቀኝ (ኞች) (ቀናዪ - መቅንዪ - የማን)፡ በግራ አንጻር ያለ ስፍራ ወይም እጅ ። "ጌታ በፍርድ ቀን ጻድቃንን በቀኝ ኃጥኣንን በግራ ያቆማቸዋል" ። ቀኝ ከስም አስቀድሞ እየገባ በዘርፍነት ይነገራል፡ ቅጽልም ይኾናል ።
ቀኝ እጅ፡ የቀኝ እጅ (በቀኝ በኩል ያለ፡ ኀይለኛ ፈጣን ") ።
ቀኝ፡ ድር ዝሓ፡ ጥንካሬውን ያሳያል ። እውነተኛው የቀኝ ትርጓሜ ቅን ማለት ነው ።
ቀኝ ጌታ፡ የቀኝ ጌታ (በደብር አለቃ ቀኝ የሚቆም ባለማዕርግ ካህን ") ።
ቀወለለ - ገወለለ) ተንቀዋለለ (ተንገዋለለ)፡ ዞረ ተንከዋረረ ተንሰዋለለ (አደገ ረዘመ ") ። "ዱር ለዱር ስንቀዋለል ውዬ የጠፋብኝን በግ አገኘኹት" ። "ወስፋቴ ስለ ሞተ የጐረ ሥኩት እንጀራ ባፌ ተንቀዋለለ" ። "ይህች ልጃገረድ ባል ሳታገባ፡ ቁመቷ ተንቀዋለለ" ።
ቀወለል - ቀውላላ (ሎች)፡ የተንቀ ዋለለ (ዘዋሪ ") ።
ቀወመ)፡ ቆመ ተነሣ ቀጥ አለ ተገተረ ታገደ ተገታ ቀረ ታጐለ ተግ አለ ።
ቀወሰ፡ አጐበጠ ደገነ ቀውስ አበጀ ።
ቀወቀወ - ከወከወ - ጎገወ) አንቀወቀወ (አንጎገወ) አንከወከወ አንቀዠቀዠ ።
ቀወቀወ)፡ ቃዠ ።
ቀወቀው - ቀውቃዋ፡ የተንቀወቀወ/የሚንቀወቀው ።
ቀዊ፡ የቀዋ/የሚቀዋ ቍራ ።
ቀዋ (ቀዊዕ ቆዐ)፡ ፍሬ ለቀመ ቀሠመ አወለበ ጠረጠረ ።
ቀዋሚ (ዎች)፡ የቆመ/የሚቆም (ጸ ንቶ የሚኖር ዐምድ ሐውልት ") ።
ቀዋሚ ነገር፡ ደንበኛ ውለኛ ሥራ ።
ቀውሰኛ (ኞች)፡ በነገር ተቃራኒ (ከሕዝብ ከማኅበር የማይስማማ ") ።
ቀውስ (ዐረ)፡ ቀስት ።
ቀውስ እሳት፡ የእሳት ቀስት፡ ጠንቋይ የናትና የልጅን ስም ገጥሞ ባ፲፪ እየገደፈ ይቈጥርና ለአንዳንድ ሰው "ኮከብኸ ፥ ቀውስ እሳት ነው" ይለዋል።
ቀውስ፡ የነገር መሳሳት አለመግጠም ።
ቀውስ፡ የኮከብ ስም (ቀስት ይዞ የሚታይ የኅዳር ኮከብ ቀስተኛ ") ።
ቀውቀውቱ፡ ዝኒ ከማሁ (ከውከውቱ ") ።
ቀውጢ (ዐረ. ቀውሲ)፡ ቀስተኛ የ
ቀውጢ ቀን፡ ሽብረኛ ሁከተኛ ጦረኛ ብላ ተባላ ቀን ። "ቀውጢ ቀን በመጣ ጊዜ ጌቶቹ አንድ ጋን ጠጅና ዐምስት እብድ አያጡም" ("(ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ)") ።
ቀዎት፡ በይፋት ውስጥ ያለ አገር ።
ቀዎቶች፡ የቀዎት ሰዎች (የቀዎት ተ ወላጆች ") ።
ቀዘመ - ገዘመ) አቅዘመዘመ፡ ወረወረ እምዘገዘገ አውዘገዘገ ።
ቀዘቀዘ (ቀዘዘ)፡ በረደ ከሙቀት ራቀ (ሰንሰለት ኾነ ") ።
ቀዘባ፡ ርጥብ ለጋ ለምለም ስንዴና ገብስ ። (የዘፈን አዝማች)፡ "የማነሽ ቀዘባ፡ አንች ዐይነ ሌባ" ። "ቀዘባ ማለት በጥር መታጨድ ይገባው የነበረ የካቲት ላይ ሲያልፍ ነው" ።
ቀዘነ፡ ቶሎ ቶሎ ዕዳሪ ወጣ ተቀመጠ፡ ብጥብጥ ዐይነ ምድር በፍጥነት ለቀቀ ሿ አደረገ ። (ግጥም)፡ "ፍየል ከቀዘነ ዲያቆን ከዘፈነ አይድንም ይሞታል እየመነመነ" ።
ቀዘነ፡ ፈራ ተንበደበደ ።
ቀዘዘ (ገዘዘ)፡ ፈዘዘ (አልመላም ") ።
ቀዘዝ አለ፡ ቀረት አለ (የስፍር ") ።
ቀዘዝተኛ፡ ቀሰስተኛ ደካማ ።
ቀዘፈ (ቀዲፍ ቀደፈ)፡ ግራናቀኝ ባሕርን ገፋ ገለጠ ከፈለ፡ የመርከብ መንገድ አበጀ መራ ።
ቀዘፋ፡ ገለጣ ከፈላ (የመቅዘፍ ሥራ ") ።
ቀዛኝ፡ የቀዘነ/የሚቀዝን (ኮሶኛ ሆደ በሽተኛ ") ።
ቀዛዛ፡ የቀዘዘ (ፈዛዛ ") ።
ቀዛፊ፡ የቀዘፈ/የሚቀዝፍ (መርከብ መሪ ቋትለኛ ") ። በግእዝ "ኖትያ ኀዳፍ" ይባላል ።
ቀዛፎች፡ የቀዘፉ/የሚቀዝፉ ("(ሕዝ. ፳፯፥ ፳፮)") ።
ቀዝቃዛ፡ ዝኒ ከማሁ (የቀዘቀዘ በራድ ") ። ወንድና ሴትን ለመለየት፡
ቀዝቃዛነት፡ ቀዝቃዛ መኾን ።
ቀዝቃዛዋ - ቀዝቃዛዪቱ፡ ያች ቀዝቃዛ ("(ኤር. ፲፰፥ ፲፬)") ።
ቀዝቃዛው፡ ያ ቀዝቃዛ ።
ቀዝቃዥ፡ የሚቀዘቅዝ (በራጅ ውርጭ ውሃ አየር ") ።
ቀዠቀዠ)፡ አንቀዠቀዠ (አክለፈለፈ አክለበለበ ") ።
ቀዠቀዥ - ቀዥቃዣ (ዦች)፡ የተንቀዠቀዠ/የሚንቀዠቀዥ (ክልፍልፍ ") ።
ቀዣበረ፡ ዘባረቀ ቀባዠረ ።
ቀየመ ቄመ)፡ አጠቈረ አቀጨመ ኣከፋ ።
ቀየሰ (ዐረ)፡ ለካ መጠነ ነደፈ በገረ ።
ቀየረ (ዐረ)፡ ለወጠ ሌላ አደረገ፡
ቀየረና ቀየሰ፡ በከተማ እንጂ፡ በባላገር አይነገርም ።
ቀየደ፡ መናገር ከለከለ (ለንባዳ አደረገ ") ።
ቀየደ፡ ሰከለ አሰረ ጋዳ ። (ተረት)፡ "እንዳትበላ ለጐት፡ እንዳትኼድ ቀየዷት" ።
ቀየደ፡ ከፈለ መከተ ጋረደ ከለለ ።
ቀየጠ (ትግ. ቀየጸ ፎከረ)፡ ዘነቀ ቀላቀለ ደባለቀ ።
ቀዩት፡ ቀይ ብራብሮ እንስት ።
ቀያ፡ በመንዝ ክፍል ያለ አገር ።
ቀያሪ፡ የቀየረ/የሚቀይር (ለዋጭ አዛ
ቀያሽ (ሾች)፡ የቀየሰ/የሚቀይስ (ነዳፊ በጋሪ ") ።
ቀያቀይ፡ የቀይ ቀይ ።
ቀያቴ፡ ቀይ ጠመኔና ቀይነት ያለው አበባ ።
ቀያቴቀይ አበባ
ቀያየረ፡ ለዋወጠ ።
ቀያየጠ፡ መላልሶ ቀየጠ ።
ቀያይ፡ የውስጠ ብዙ ቀይ ቅጽል ።
ቀያዮች፡ ቀዮች ። ዐረቦች ቀያዮች ና
ቀያጅ (ጆች)፡ የቀየደ/የሚቀይድ (መካች ጋራጅ አሳሪ ") ።
ቀያጭ (ጮች)፡ የቀየጠ/የሚቀይጥ (ዘናቂ ቀላቃይ ደባላቂ ") ።
ቀያፋ፡ የሰው ስም፡ ጌታችንን ያስ ቀለ ሊቀ ካህናት ።
ቀዬ (ኦሮ)፡ ደጅ ካጥር ውጭ የሚገኝ ስፍራ ።
ቀይ (ቀይሕ)፡ የቀላ (ደም ጁኅ ጃዊ እንድኪ ፍሕሶ ነት ዐረብ አንቀልባ የሱፍ አበባ ") ።
ቀይ መልክ አይገፋም፡ እጅግ አያ ምርም፡ ደመ ግቡ አይኾንም ።
ቀይ መስቀል፡ በዓለም ኹሉ የተወደደ የበጎ አድራጎት ማኅበር፡ ሥራውም በጦርነት ጊዜ ጠላትና ወዳጅ ሳይለዩ ቍስለኛን ማንሣትና ማከም ማስታመም ነው፡ እንደ አውሮጳ አቈጣጠር ነሐሴ ፳፪ ቀን ፲፰፻፷፱ ዓ. ም. በዠኔብ ተዠመረ ።
ቀይ ሥር፡ የተክል ስም ።
ቀይ በሬ፡ ሶረን ።
ቀይ፡ በቁሙ ቀላ ።
ቀይ በግ፡ ዳንግሌ ።
ቀይ፡ አርእስቱ በቀይ ቀለም የሚጻፍ ከዳዊት መዝሙሮች አንዱ ። "ቀይ" ከስም አስቀድሞ እየገባ በቅጽልነት ይነገራል ።
ቀይ ዐፈር፡ ቦረቦር ሸክላ ።
ቀይ ዳማ፡ በጠይምነትና በቀይነት መካከል ያለ ሰው፡ ጠይምነቱ ወደ ቅላት የሚያደላ ። "ዳማ" በጋልኛ ቀይ ፈረስ ማለት ነው ።
ቀይ ዶሮ፡ ሶረኔ መልክ ።
ቀይ ግምጃ፡ ሶራ ።
ቀይ ጣላ፡ ቀይ ያለበት (የጣለበት) ።
ቀይ ፈረስ፡ ሐመር ዳማ ("(ራእ. ፮፥ ፬)") ።
ቀዮች፡ የቀሉ ቀያይ የኾኑ ስዎች፡ ሌሎችም ሥነ ፍጥረቶች ።
ቀደል፡ ጥላት (የጭላት ዐይነት ") ።
ቀደመ (ቀዲም ቀደመ)፡ በሩጫ በለጠ፡ ዐለፈ ዐልፎ ኼደ፡ ወደ ኋላ ተወ ። "አሳሄል በሩጫ ከፈረስ ቀደመ" ። "የቀደመን ሞት ይወስደዋል" ።
ቀደመ፡ በቀዳማ ላይ ሰቀለ አንጠለ ጠለ ። (ግጥም)፡ "እንግዴህ አላምንም ፈረሰኛውን፡ ቀደሙት ይሉኛል መርቆሬዎስን" ።
ቀደመ፡ ዠመረ ፈለመ፡ ጨፈለቀ -
ቀደማ፡ ጭፍለቃ ዕዳሪ ማውጣት ።
ቀደም (ቀዳሚ)፡ በኵር ፊተኛ ። "ግን ባር ቀደም" እንዲሉ።
ቀደም፡ ቀደመ ። (የባለጌ ተረት)፡ "ሳትጋደም ፈሷ ቀደም" ። "ነበረን" እይ ።
ቀደም አለ፡ ቀደሙ ።
ቀደም፡ ያለፈ ጊዜ ("(ኤፌ. ፬፥ ፳፪)") ። "ከዚህ ቀደም" እንዲሉ።
ቀደሰ (ቀድሶ ቀደሰ)፡ ለየ ባረከ እነጻ አከበረ አመሰገነ፡ ቅዱስ አደረገ ከርኵሰት አራቀ ። "እራት የሌለው ቄስ እንደ ልቡ አይቀድስ" ። (ግጥም)፡ "አብ እሳት ወልድ እሳት መንፈስ ቅዱስ እሳት፡ ቄስ እንዴት ይሞታል ጐሥዐን ሲቀድሳት" ።
ቀደሰ፡ ቈረበ ።
ቀደደ፡ ሸረከተ ሠጠጠ ሠነጠቀ ተለተለ (በሸረከ በጨቀ ") ("(፪ነገ. ፭፥ ፯ - ፰)") ።
ቀደደ፡ በሳሸነቈረ ነደለ ። "ውሻ በቀ ደደው ዥብ ይገባል" እንዲሉ።
ቀደዳ፡ ሽርከታ ሥንጠቃ ሽንቈራ ።
ቀደጀ - ቀደወ)፡ አቀዳጀ (አስተቀጸለ)፡ ዘውድን አክሊልን ራስ ቍርን ራስ ወርቅን ጐፈርን አቍዳማን በራስ ላይ ጫነ አጠለቀ፡ ሸለመ አስጌጠ ።
ቀደጀ - ኦሮ ከደነ)፡ "ሲል ቀዳዴ" ከሚለው ጋራ በምስጢር ይገጥማል ።
ቀዳ (ቀድሐ)፡ ውሃን ጠላን ጠጅን ማንኛውንም ፈሳሽ ነገር ካለበት ስፍራ ዕቃ ጠለቀ ወደ ሌላ አወረደ ጨመረ፡ አንቈረቈረ ሞላ፡ ባንኮላ በጭልፋ ደነበቀ ወለፈ ገለበጠ ።
ቀዳ፡ አለልክ አለቀሰ (እንባውን አፈሰሰ ") ።
ቀዳ፡ አስቀመጠ አስቀዘነ ነዳ ።
ቀዳ፡ ጪር ጻፈ ።
ቀዳሚ (ዎች)፡ የቀደመ/የሚቀድም
ቀዳማ (ቀዳማይ)፡ በስተደረት ያለ የኮርቻ ከፍተኛ ድጋፍ የደኃራ አንጸር ።
ቀዳማዊ፡ የቀዳሚ ወገን ወይም ዐይነት (አንደኛ መዠመሪያ ሰው ማንኛውም ፍጥረት ") ።
ቀዳማይ፡ ከትንቢት አንቀጽ በፊት የሚነገር ተቀዳሚ አንቀጽ ኀላፊ ።
ቀዳሽ (ሾች)፡ የቀደሰ/የሚቀድስ (ባራኪ አመስጋኝ ቈራቢ ሰሞነኛ ዲያቆን ቄስ ቆሞስ ጳጳስ ") ።
ቀዳው፡ ዝናቡን አለመጠን አዘነበው ።
ቀዳደደ፡ ሸረካከተ ሠነጣጠቀ ።
ቀዳዳ፡ ብስሽንቍር ሥንጥቅ ("(ኢሳ. ፰፥ ፲፰)") ። (ተረት)፡ "ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ" ።
ቀዳዳ፡ ነገር የማይችል የማይቋጥር ሰው ።
ቀዳጅ (ጆች)፡ የቀደደ/የሚቀድ (ሸር ካች ሠንጣቂ ሸንቋሪ ") ።
ቀድሞ - ቅድም፡ የጊዜ ንኡስ አገባብ ።
ቀድሞ (ቀዲሙ)፡ ጥንት ዱሮ ፊት ።
ቀድሞ፡ ቦዝ እፊት ኹኖ ።
ቀድሞ ዘመን፡ ያለፈ የጥንት ጊዜ (ቀድሞ የዘመን ዘርፍ ነው ") ።
ቀድሞውን - ቀድሞውኑ፡ ዱሮውን/ዱሮውኑ ።
ቀጂ (ጆች)፡ የቀዳ/የሚቀዳ (ጨምማሪ ኣንቈርቋሪ ") ።
ቀጂነት፡ ቀጂ መኾን ።
ቀጋ (ጎች)፡ ከሥር እስከ ጫፍ ኹለንተናው እሾኸ ያለው ዕንጨት ። አበባው ነጭ፡ ሽታው ጣፋጭ ። (ተረት)፡ "የውጭ ዐልጋ የቤት ቀጋ" ።
ቀጠለ (ቀጸለ)፡ በቁመት ላይ ቁመት በሥራ ላይ ሥራ ኣከለ ጨመረ፡ ቋጠረ ገጠመ ሰፋ አረዘመ ። "ቀጸለን" እይ፡ "ቀጠለ" ዐማርኛ፡ "ቀጸለ" ግእዝኛ ነው ።
ቀጠለ (ቈጸለ)፡ ሣሣ ረቀቀ ።
ቀጠለ፡ ለመለመ ጨበጨበ ።
ቀጠለ፡ ተራ መታ ተከተለ ለጠቀ ።
ቀጠላ፡ ሻሽቀጸለ ።
ቀጠላ፡ ዐሰላ ።
ቀጠላ፡ ጥሩ የማር እንጀራ (ከወለላ በቀር ከዳና ቀለሕ የሌለበት ") ።
ቀጠረ (ቀጸረ)፡ ገነባ ካበ ከ በበ ከተማን አገርን፡ የውጭ ዐጥር ዐጠረ ጀጐለ ። "ከተማ እንደ ሐረር፡ አገር እንደ ሺን" ነው ።
ቀጠረ (ዐደመ ዐሠረ)፡ ቀን ወሰነ፡ በዚያ ለት መጥተሽ እንድትቀርብ አለ ። "ኹሉም የቅጥርን ምስጢር አይለቅም" ። (ተረት)፡ "ቀን ቢቀጥሩ ውሻ ቢጠሩ ይደርሳል በግሩ" ።
ቀጠረ፡ አሽከር ሎሌ ገረድ ኣሳደረ (ቀለብ ደመ ወዝ ምንዳ ሊሰጥ ") ።
ቀጠሮ፡ ታፌ ያለ በ፰ ከጠበቃዬ ያለ ባ፲፭ ቀን የሚቀርብበት ።
ቀጠሮ አፍራሽ፡ ቀጠሮ የማያከብር ተቃጥሮ የሚቀር ።
ቀጠሮ፡ የሰዓት ልክ/የጊዜ ውሳኔ (ሰው ተገናኝቶ ጕዳዩን የሚፈጽምበት እዳኛ ፊት ቀርቦ የሚነጋገርበት ") ።
ቀጠቀጠ ("ጨፈ ጨፈ ባጪር ባጪሩ ቈረጠ ገተገተን እይ ከትካች የከተከተ የሚከተክት ቀጥ ቃጭ ጨፍጫፊ ክትከታ ቅጥቀጣ ጭፍጨፋ ቈረጣ መከትከት መቀጥቀጥ መጨፍጨፍ መቍረጥ መከትከቻ መጨፍጨፊያ መቍረጫ ካራ ጩቤ አስከተከተ አስቀጠቀጠ አስጨፈጨፈ ተከተከተ ተቀጠቀጠ ተጨፈጨፈ ተ ቈረጠ ካቲ ስንድድ ከተረከዝ በላይ በስተኋላ ያለ ሥር እከሌ ከእከሌ ጋራ ተጣላና ካቲ ካቲውን አለው ካቲካላ ያረቄ ስም ሲጠጡት እንደ እሳት የሚያቃጥል መጠጥ የካቲን ርምጃ የሚከላ ካቲካላ የሚጠጡ አባትና እናት ድዳ ደንቈሮ ዕውር ልጅ ይወልዳሉ አንከተከተ ቀጥሎ ቀጥሎ እንባ እ ስኪወጣ ድረስ አሣቀ ማንከትከት ፈጽሞ ማሣቅ ተንከተከተ ባለማቋረጥ ሣቀ መንከትከት መሣቅ መንከትከቻ መሣቂያ ካታ የሚሥቅ የሚንከተከት ሣቂ - ፮፻፺፩ ካታ ወልደ ሚካኤል ባጤ ምኒልክ ዘመን በላይኛው ወግዳ የነበረ ተጫዋች ሥቆ የሚያሥቅ ሰው ከት አለ በጣም ሣቀ ") ።
ቀጠቀጠ (ቀጥቀጠ ቀጽቀጸ)፡ መታ ደበደበ ሰበረ አደቀቀ ።
ቀጠቀጠ፡ ብረት ሠራ አሾለ አጠፈ
ቀጠቀጠ፡ ወቀጠ ገብስን የወይፈንንና የወጠጤን ቍላ ።
ቀጠቀጥ - ቀጥቃጣ፡ የተንቀጠቀጠ/የ ሚንቀጠቀጥ (ሥጋ ፈሪ ንፉግ ") ። "ፈንዛን" እይ ።
ቀጠባ ማሪያም፡ የቀጠባ ማሪያም ።
ቀጠባ፡ የቀበሌ ስም (በደብረ ሊባኖስ ውስጥ ያለ የማሪያም አጥቢያ ") ። "አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከይፋት አገር በትምህርት በ ታምራት ማርከው ከነልጆቿ ደብረ ሊባኖስ አምጥተው ስን (ክርስቶስ ቀጸባ) ያሏት አንዲት ቅድስት ሴት ነበረች፡ የመቤታችንን ታቦት በዚህ ስፍራ ስለ ተከለች ከውሻ ገደል በታች ያለው ቀበሌ በስ ቀጠባ ተባለ ይላሉ ። የቀጠባት ርጓሜ ጠቀሳት ጠራት አቀረባት ማለት ነው" ።
ቀጠነ (ቀጢን ቀጠነ)፡ ነነ ከሳ ከውፍረት ከድንዳኔ ራቀ ሣሣ ረቀቀ ።
ቀጠና፡ ትንሽ ረኃብ፡ ሼጥ ያለ ዘመን ("(ዘዳ. ፳፰፥ ፳፪፡ ሰቈ. ፬፥ ፲፱፡ ዓሞ. ፬፥ ፮)") ። (ተረት)፡ "ምንም ቢታረስ በዘጠና ቤቱን አይስ ትም ቀጠና" ።
ቀጠናማ፡ ቀጠናም (ባለቀጠና
") ።
ቀጠን (ቀጢን)፡ መቅጠን ።
ቀጠን አለ፡ ቀጠነ ።
ቀጠን ያለ፡ የቀጠነ ።
ቀጠጠ (ረትዐ - ትግ. ቀጸጸ - መላ. ዕብ. ቃጻጽ)፡ ቈረጠ ዐወደ ሸ ለተ ።
ቀጠጠ፡ ነፋ አሳበጠ ቀሰጠጠ ።
ቀጠጠ፡ ገብጠትንጠማማነትን አራቀ ።
ቀጠጣ፡ ቈረጣ ሽለታ ።
ቀጠጥና፡ ቀጥታነት ያለው ቀጪን ዕንጨት መጠነ ታናሽ፡ የቅጠሉ ስም ያህያ ዦሮ ነው ። "ደባክድን" ተመልከት ።
ቀጠጥና፡ ዕንጨት ። ቀጠጠ ።
ቀጠጦ፡ ፍሬው ቀጫጫ የኾነ ማሽላ ።
ቀጠፈ (ቀጢፍ ቀጠፈ)፡ ቈረጠ ሰበረ ቀነጠበ (ርጥብ ቅጠልን ") ።
ቀጠፈ፡ በልጅነት ገደለ ። "ቀሠፈን" እይ ።
ቀጠፈ፡ ዐበለ ዋሸ ።
ቀጠፋ፡ ቈረጣ ቅንጠባ ።
ቀጠፋ፡ የቅኔ ጫፍ፡ መነሻ የሌለው ኹለት ቤት ቅኔ ።
ቀጣ (ቀጽዐ)፡ አሰረ መታ ገረፈ ።
ቀጣ፡ ከላይ ዐንገትን ከታች ባትን ጐመደ ቈረጠ ።
ቀጣ፡ ገንዘብ አስከፈለ ።
ቀጣሪ (ሮች)፡ ዐጥር ያጠረ/የሚያ ጥር፡ አሽከር የቀጠረ/የሚቀጥር ።
ቀጣቀጠ፡ ደባደበ/ወቃቀጠ ።
ቀጣቢ፡ የቀጠበ/የሚቀጥብ (ከንጂ አመልካች ሸማኔ ") ።
ቀጣኒት፡ የቀጠነች ምድር ሴት
ቀጣኒት፡ የተንቀሳቃሽ ስም፡ መልኳ ላይ ላዩ አረንጓዴ ታች ታቹ ብጫ የኾነ የአንበጣ ወገን፡ ዳግመኛም ያቦ ፈረስ ትባላለች ።
ቀጣና (ኖች)፡ በገደልና በገደል መካከል ያለ ዕርከን የቃጥላ አረፍት ሰው የሚያልፍበት ከብት የሚሰማራበት ።
ቀጣይ (ዮች)፡ የቀጠለ/የሚቀጥል (አካይ ተከታይ ቋጣሪ ") ።
ቀጣጠለ፡ ጨማመረ ቈጣጠረ ገጣጠመ ። "፬ኛውን ና" እይ ።
ቀጣጠፈ፡ ቈራረጠ ቀነጣጠበ ።
ቀጣጣይ (ዮች)፡ የቀጣጠለ/የሚቀ ጣጥል (ነገረሠሪ ") ።
ቀጣጣፊ፡ የቀጣጠፈ/የሚቀጣጥፍ ።
ቀጣፊ (ፎች)፡ የቀጠፈ/የሚቀጥፍ (ቈራጭ ") ።
ቀጣፊ ሌባ፡ ዐባይ ዋሾ ቈርጦ ቀ ጥል ("(ሚክ. ፮፥ ፲)")
ቀጣፊነት፡ ቀጣፊ መኾን ።
ቀጤማ - ቄጠማ፡ በረግረግ ላይ የሚበቅል ለምለም ሣር ("(ኢዮ. ፰፥ ፲፩)") ። "የፀሓይ ጥላ ለእረኛ፡ የዝናም ልብስ ገሣ ምንጣፍ ኬሻ ይኾናል" ። በግእዝ "ሰት" ይባላል ። "ለመለመ" ብለኸ "አለመለመን" እይ ።
ቀጥ፡ መቅናት ።
ቀጥ አለ፡ ቀና ።
ቀጥ አደረገ፡ አቀና ።
ቀጥሎ፡ ቦዝ አንቀጽና ንኡስ አገባብ፡ አክሎ ቋጥሮ ጨምሮ ተከትሎ ። በደጊመ ቃል ሲነገር "ቀጥሎ ቀጥሎ" ይላል ።
ቀጥቃጭ (ጮች)፡ የቀጠቀጠ/የሚቀጠቅጥ (ብረተ ሠሪ ጠይብ ባለጅ ") ።
ቀጥቃጭነት፡ ቀጥቃጭ መኾን፡ ባለጅነት/ሠራተኛነት ።
ቀጥታ፡ ቀጥ ማለት፡ ወይም ቀጥ ያለ ዙሪያ ጥምጥም ያይዶለ ። "ቀጥታ መንገድ" እንዲሉ። "በቀጥታ መጣ፡ በቀጥታ ኼደ" ቢል፡ ግራ ቀኝ ሳይል ያሠኛል።
ቀጨ (ትግ. ቀጸየ)፡ ስንደዶን አ ክርማን እሸትን ከላይ ከመካከል ቈረጠ ነጨ ገነጠለ፡ አጠፋ አበላሸ (ሰብልን ") ።
ቀጨ (ትግ. ቈጸየ - ወለም አለ)፡ ትከሻን አሳመመ (ሥርን አዞረ ") ። "ገን" እይ፡ በግእዝ መሠረቱ "ቀጽዐ" ነው ።
ቀጨ፡ ቀሠፈ/አለዕድሜ በልጅነት ገደለ ።
ቀጨለ፡ ቃጨለ፡ ጮኸ ከለለ ተሰማ ። "በቀለ አቅጨለጨለን፡ በቃጨለ አቃወለን" ይመለከቷል ።
ቀጨመ፡ ቅም ያዘ አፈራ (ገቢር) ።
ቀጨሞ (ዎች)፡ የንጨት ስም፡ ፍሬው ሲቀምሱት የሚጐመዝዝ የሚያስቀምጥ ቀጪን ዕንጨት ።
ቀጨቀጨ፡ በጥርሱ ስበረ ቀጠቀጠ ዐኝ ዐኝ አለ አደቀቀ ።
ቀጨቀጭ፡ በጤፍ ውስጥ የሚበቅል ዐረግማ ቅጠል፡ ጤፍ እንጀራ ሲበሉ ቀጥ ቀጭ የሚል ።
ቀጨኔ ።
ቀጨኔ፡ ባዲስ አበባ ውስጥ ያለ ቀ በሌ ። "ቀጨኔ መድኀኔ ዓለም" እንዲሉ።
ቀጨጨ (ቈጢጥ ቈጠጠ)፡ ቀጠነ ኰሰመነ ሰለተ ።
ቀጪ (ቀጻዒ)፡ የቀጣ/የሚቀጣ (መቺ ገራፊ ") ። "አንጥያኮስ በእስራኤል ላይ ግፍ ስለ ሠራ ቀጪ አዘዘበት" ።
ቀጪነት፡ ቀጪ መኾን ።
ቀጪኔ (ዎች)፡ የግመል ዐይነት የዱር እንስሳ፡ ነብርማ ዐንገቱና የፊት እግ
ቀጪኔ፡ ነጭ አደንጓሬ ።
ቀጪኔ፡ የስንዴ ስም፡ በጣም ቀጪን
ቀጪኔ፡ ጐራዴ ። "ሾተልን" ተመልከት ።
ቀጪን (ኖች - ቀጢን)፡ የቀጠነ (የማነነ ሞናና ሰው ፈትል ሸማ ፉጨት ") ። "ቍጥኔን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው ።
ቀጪን ሊጥ፡ ውሃ የበዛበት ቡሖ ።
ቀጪን ሠጥር፡ ከጐድን ኹሉ የም ትቀጥን ታናሽ የጐን ዐጥንት ።
ቀጪን እመቤት፡ ከድኸነት የወጣች ራሷን የቻለች ።
ቀጪን ፈታይ፡ ኩታው በቀለበት የሚሾልክ ድርና ማግ የምትፈትል ሴት ።
ቀጪንነት፡ ቀጪን መኾን ።
ቀጪኖ፡ ዝኒ ከማሁ ለቀጪኔ ።
ቀጪዎች - ቀጮች፡ ጕዲት ግራኝ ዐጤ ቴዎድሮስ ሐበሻን እንደ እስራኤል ፫ ዘመን የቀጡ፡ በዚህ ላይ የፋሺስት ሲ መር ፸፭ ይኾናል።
ቀጫጫ (ጮች)፡ የቀጨጨ (ቀጪን ኰስማና ") ።
ቀጫጯን (ኖች)፡ ብዛቱና ቅጥነቱ ባንድነት የሚታይ ውዥኝን ዐደይ አበባን ፍየለ ፈጅን ቀጨሞን የመሰለ ።
ቀጭ ። ተጭ ።
ቀጭ አደረገ፡ ጨ መታ ።
ቀጭ፡ ከንፈርን የሚያቈስል አግርን የሚሠነጥቅ ብርድ ውርጭ ።
ቀጭ፡ የቀጨ/የሚቀጭ (ቈራጭ ገን ጣይ ") ። "ዝርዝረ ቀጭ" እንዲሉ።
ቀጭቀጨ፡ በውጋዴ በረሓ የሚገኝ ቅጠል የግርሽጥ ዐይነት፡ ሰው ኹሉ እያኘከ ውሃውን ይመጠዋል ።
ቀጭታ፡ የቀጨች/የምትቀጭ ።
ቀጸለ፡ ትምርትን አጠና ጨመረ ።
ቀጸለ፡ ዐማ ነቀፈ ስም አጠፋ ።
ቀጸለ፡ ደረበ በላይ አደረገ ("(ግእዝ)") ። "ከተለን" "ቀጠለን" ተመልከት ።
ቀጸላ፡ ኅባኔ (ሻሽ የራስ የፊት መሸፈኛ፡ ዐይነ ርግብ ወገሮ ሠርመዲ በዙሪያው የወርቅ መርገፍ ያለበትና የሌለበት የሐር የፈትል የግምጃ አጣፊኝ፡ ሥሥ ቀጪን መደረቢያ ") ("(፩ነገ. ፳፥ ፴፰)") ።
ቀጸላ፡ ዐሰላ ። ቀጠለ ።
ቀጸላ፡ የማር እንጀራ ። ቀጠለ ።
ቀጸላ፡ የወንድና የሴት የክርስትና ከፊለ ስም (በሕዝብ አነጋገር ቀጠላ ይባላል ") ።
ቀጸበ (ቀጺብ - ቀጸበ)፡ ጠቀሰ ባ ይን በጣት ጠራ አመለከተ አዘዘ፡ አፈጠነ ።
ቀጻ (ቀጽዐ)፡ ባንድ ልክ ብራናን ወረቀትን ቈረጠ አፈፈ ቀፈፈ ።
ቀፈረ፡ አቆመ ዘረጋ ዦሮን፡ ፊት ለፊት ቀቀረ፡ የከብት ።
ቀፈረረ - ከፈረረ)፡ አንቀፈረረ፡ አረዘመ ("(ረዘመ)") ።
ቀፈረር - ቀፍራራ፡ የተንቀፈረረ (እንቅፍር ርዝማኔው የሚያስቀይም ") ።
ቀፈቀፈ፡ በሳ ሰበረ ዕንቍላልን፡ ፈለ ፈለ ብዙ ወለደ ጫጩትን ዶሮው ሰው ።
ቀፈቀፈ፡ ግራና ቀኝ እየመታ ከመካ ከል ከረከረ ። የቀፈፈንና የቀፈቀፈን ልዩነት አስተውል፡ "ቀረቀፈን" እይ ።
ቀፈታም፡ ሆደ ዘርጣጣ ቦርጫም ።
ቀፈት (ቀፈፈ)፡ ቀፈድ የቈርበት ቀለበት ። በግእዝ ግን ፵ንቃ ደንደስ ማለት ነው ።
ቀፈት መራ፡ ቈርበትን ጠለፈ አያያዘ ወይም ቈዳን ወጠረ ገደገደ ።"ቀፈደን" እይ ።
ቀፈት፡ ትልቅ ሆድ ቦርጭ ደንደስ መሳይ ("(ጐንደር)") ። "ቈለፈ" ብለኸ "ቈለፈትን" ተመልከት ።
ቀፈት፡ የጠፋ ከብት ጭገሬታ ምል ክት ።
ቀፈደ፡ ቅፍንድን በሳ፡ ቀፈድ አበጀ፡ እሱንም እየጠለፈ አሰረ፡ ሸክምን ሣርን ነዶን ገለባን ዕቃን ።
ቀፈደደ፡ ማሰሪያን በመጠምጠም አጥ ብቆ አሰረ ሰውን ("(ገቢር)") ።
ቀፈደደ፡ ደነዘዘ ፍጥነት ቅልጥፍና አልባ ኾነ ("(ተገብሮ)") ።
ቀፈደድ - ቀፍዳዳ፡ ደነዝ ደንዛዛ ።
ቀፈዲያም፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀፈዳም - ቀፈታም፡ ሰውነተ ሻካራ ቈ ርፋዳ ።
ቀፈድ - ቀፈት፡ በቈርበት ዙሪያ በቅፍንድ ግፍ ያለ ቀዳዳ ጠፍርና ገመድ የሚያ ስገባ ። ቀፈድና ቀፈት አንድ ስም ነው ።
ቀፈፈ፡ ለመነ፡ መንደር ለመንደር እየዞረ "በአንተ ስማ ለማርያም ስለ ቸሩ እግዚአብሔር" አለ ።
ቀፈፈ፡ ሰቀጠጠ ጨመደደ ጨፈገገ ከበደ አሳመመ ። "ዛሬ ሰውነቴን ይቀፈኛል" ።
ቀፈፈ፡ ቈረጠ ከረከመ አስተካከለ የቈዳን የብራናን የቅልን ጫፍ ። "አፈፈን" አስተውል ።
ቀፈፋ፡ ክርከማ ልመና ።
ቀፋሪ፡ የቀፈረ/የሚቀፍር (ቀቃሪ ") ።
ቀፋራ - ቅፍር፡ የተቀፈረ/ቅቅር ።
ቀፋፊ (ዎች)፡ የቀፈፈ/የሚቀፍ (ከር ካሚ ለማኝ ") ።
ቀፋፋ፡ ከርፋፋ ።
ቀፋፎ፡ ቀራፎ ሞኝ ።
ቀፍቃፊ፡ የቀፈቀፈ/የሚቀፈቅፍ (ፈልፋይ ከርካሪ ") ።
ቀፍዳጅ፡ የቀፈደደ/የሚቀፈድድ (አሳሪ ") ።
ቀፎ (ዎች)፡ ከሐ ረግ ከመቃ ከቀጯን ዕንጨት የተታታ የተሠባጠረ የንብ ቤት በኹለት ወገን አፍ በመካከል ፍንጭ ያለው ።
ቀፎ፡ ሆድ ውስጠ ክፍት ነገር ።
ቀፎ ለቀፎ፡ ውስጥለውስጥ ።"አቶ እከሌን የመታው ጥይት ቀፎ ለቀፎ ኼዶ ስለ ወጣ ሳይገድለው ቀረ" ።
ቀፎ ቈራጭ፡ ከቀፎ ውስጥ ማርን የሚቈርጥ ። መኪና ሰፊ እንደ ማለት ያለ ነው ።
ቀፎ፡ ያሣ መያዣ ።
ቍ ብሎ ዞላ ዋለ (ኤር. ፲፡ ፬፡ ሕዝ. ፵፭፡ ፳) ። (ተረት)፡ "በሰጡኸ አትስነፍ፡ ከሰጡኸ አትለፍ"።
ቍለላ፡ ክመራ ።
ቍለፋ፡ ቅርቀራ ሽጐራ ።
ቍላ (ቍልሕ)፡ በሰውና በንስሳበአራዊት ብልት ሥር ተንጠልጥሎ የሚታይ ሥጋዊ ጓሚያ፡ ፍሬ ቈለጥ ኹለትነት ያለው ።
ቍላ፡ ሙርጥ ዘንጉ ወንዳወንዴ ። "የመ ዝጊያ ቍላ" "የመርዋ ቍላ"፡ "ማሞ ቍላው ታሞ" እንዲሉ።
ቍላ ቀረሽ፡ ወንዲላ ኀይለኛዪቱ ሴት ("(መሳ. ፬፥ ፳፩)") ።
ቍላ በንቅብ፡ በላይ ወግዳና በቡልጋ ክፍል የሚገኝ ቀበሌ መዋጊያ ስፍራ ።
ቍላዎች፡ ቈለጦች ።
ቍሌት፡ ጥብስ (የሥጋ ወጥ ") ጥቂት እንጂ ብዙ ያይዶለ ውሃ ያነሰው ።
ቍልላት (ጕልላት)፡ የክምር የጕቾ ሥራ ኹኔታ ።
ቍልል (ጕልል)፡ የተቈለለ፡ ክምር (የ ሣር የገለባ ጕቾ ") ።
ቍልልታ፡ የደንጊያ የመሬት ክምር በዕለተ ፍጥረት የተቈለለ ከጕባ የቀጠነ ።
ቍልመማ፡ ቅለሳ ጥምዘዛ ።
ቍልምማት፡ ቅልሳት ጕብጠት ።
ቍልምም፡ የተቈለመመ (ዝልስ ዝቅዝቅ ቅልስ ጥምዝ ") ።
ቍልምጫ፡ የማይረባ ምስጋና ልምምጥ ("(ኢዮ. ፴፪፥ ፳፪)") ።
ቍልቍለት፡ ከደጋ ወደ ቈላ ከተራራ ወደ ጥግ መውረጃ መንገድ፡ በግእዝ "ቍልቍሊት" ይባላል ።
ቍልቍለቶች፡ ዘቅዛቆች ተዳፋቶች ("(ሕዝ. ፴፰፥ ፳)") ።
ቍልቍል፡ የተቈለቈለ፡ ዝቅዝቅ ታች
ቍልቍሎሽ፡ ዝኒከማሁ ለቍልቍለት፡ ዝቅዝቆሽ ።
ቍልቋል (ሎች)፡ በቈላና በወይናደጋ የሚበቅል ወተታም ዛፍ፡ ከሥር እስከ ጫፍ ትንንሽ እሾኸ አለው፡ ውስጠ ክፍት የኾነ ዕንጨቱ እየተፈለጠ ለጣራ ይኾናል ። (ተረት) ካጋም የተጠጋ ቍልቋል ሲያለቅስ ይኖራል።
ቁልቢ (ኦሮ)፡ ነጭ ሽንኵርት ።
ቁልቢ፡ በሐረርጌ አውራጃ ያለ አገር ። "ቁልቢ ገብሬል" እንዲሉ።
ቍልቢጥ (ጦች)፡ ቃጤ፡ ዕፍኝ የምትይዝ መስፈሪያ ።
ቍልዕ (ቀልዐ ከላ አስወገደ)፡ ቅምጥ ዐይናር መክላት ማስወገድ የሚገባው ።
ቍልዕ ለግእዝም ይኾናል።
ቍልጭ አለ፡ ቈለ ጥርት አለ ።
ቍልጭ፡ የቈለ/የጠራ/የበራ ።
ቍልጭልጭ አለ፡ ተቍለጨለጨ ።
ቍልጭልጭ፡ የተቊለጨለጨ/የሚቍለጨለጭ (የሰው የዥብሪ የተከበበ አውሬ ዐይን ") ።
ቍልጭልጭታ፡ የዐይን ጥራት ጥሩ ነት፡ ቍልጭልጭ ማለት ።
ቍልፋት፡ ቅልሳት ጕብጠት ።
ቍልፍ አለ፡ ቅልስ ዕጥፍ ዝግት አለ ። "እምግቡ ውስጥ ጕድፍ ቢገባበት አን ዠቴ ቍልፍ አለ" እንዲል ባላገር ።
ቍልፍ፡ የመዝጊያ የሣጥን የልብስ ማገናኛ በመክፈቻ በጣት የሚቈለፍና የሚከ ፈት (ጓጕንቸር አዝራር አግራፍ ባልና ሚስት ") (ጥሬ) ። (መርፌ ቍልፍ) መካከሉ ታጥፎ ዳርና ዳሩ የሚገናኝ የቀሚስ የጥብቆ መግጠሚያ ።
ቍልፍ፡ የተቈለፈ/የተዘጋ/የታጠፈ (ምላስ ዥራት ምልስ ቅልስ ዝግ ") (ቅጽል) ።
ቍልፍ፡ የድንኳን ጣራና ግድግዳ ማያያዣ የንሓስና የጥብጣብ ቀለበት ("(ዘፀ. ፳፮፥ ፮)") ።
ቍልፍልፍ አለ፡ ተቈላለፈ ።
ቍልፍልፍ፡ የተቈላለፈ ።
ቍልፍነት፡ ዝግነት ቅልስነት ።
ቍልፎች፡ ጓጕንቸሮች ቀለበቶች አዝራ ሮች ("(ዘፀ. ፴፭፥ ፲፯)") ።
ቁመተ ሥጋ፡ የሥጋ መቆም አቋቋም ። "አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለቁመተ ሥጋ በሑዳዴ ቅጠል ይበሉ ነበር" ።
ቁመተ ዶሮ፡ ዐጪር ሰው ።
ቁመታም፡ ቁመቱ የረዘመ (ሰማይ
ቁመት፡ በቁሙ ቆመ ።
ቁመት፡ የአካል ልክ መጠን (ከራስ እስከ እግር ከግራ እጅ ጣት እስከ ቀኝ ጣት የሰው፡ ከእግር እስከ ዠርባ፡ ከራስ እስከ ዥራት የእንስሳ፡ ከሥር እስከ ጫፍ ያለ የዛፍ ") ("(ሕዝ. ፲፱፥ ፲፩)") ። "ቁመተ ዐጪር ቁመተ ረዥም" እንዲሉ። በግእዝ "ቆም" ይባ ላል ።
ቁመና፡ የቁመት ኹኔታ ። "ይህ ሰው ቁመናው ያምራል።"
ቁመኛ (ኞች)፡ አስማተኛ ቡዳ ዐይነ
ቁመኛቡዳ—(ቀወመ) ። ቅማንጅር የቅማል ጓዝ፡ መለ ።
ቍመዳ፡ ድረታ ደፈና ።
ቁማር (ዐረ)፡ የንጉሥና የንግሥት ሥዕል ሌላም ምልክት ከቍጥርና ከፊደል ጋራ በላዩ ያለበት የጨዋታ ወረቀት ወይም ዕንጨት ። ሰውን ባንድ ጊዜ ያከብራል ያደኸያል ።ቁማርን መዠመሪያ ያወጡ የጢሮስና የሶርያ ሰዎች ናቸው ይባላል ።
ቁማርተኛ (ኞች)፡ ቁማር ወዳድ ተጫዋች ዐዋቂ ።
ቁማሽ (ዐረ)፡ ጣቃ ።
ቍማጭ፡ ቍራጭ ጕማጅ ።
ቁም (ቅዉም)፡ የቆመ/የተገተረ (ደማ ዊት ነፍስ ያለችው የቤት እንስሳ፡ ለዕቃም ይነገራል ") ። "ቁም ሣጥን" እንዲሉ።
ቁም ለቁም፡ ቀውላላ ሰውነቱን/ሰውነቷን የማይሰበስብ/የማትሰበስብ ።
ቁም ሥቃይ፡ የሥጋ መከራ ።
ቁም ስቅል፡ የተሰቀለ ሰውነት ጭንቅ ሥቃይ ። "ፋሺስቶች አንዱን ሐርበኛ ይዘው ቁም ስቅሉን አሳዩት" ።
ቁም፡ ቁመት ቁመና ። "ፍራት ከቁም ይጥላል" እንዲሉ።
ቁም፡ ትእዛዝ አንቀጽ ("አትኺድ ርጋ ቀጥ በል ") ።
ቁም ነገራም (ሞች)፡ ሐቀኛ እውነተኛ ልጨኛ የሰው ውለታ የማይቀርበት በቃሉ የጸና ።
ቁም ነገር፡ ሐቅ ርግጥ ጠቃሚ ጕዳይ ።
ቁም እስር፡ ሳይታሰር የተጋዘ ("ከዚህ ኣትለፍ" የተባለ ሰው ") ("(፩ነገ. ፪፥ ፴፮ - ፴፯)") ።
ቁም ከብት፡ ብርና ወርቅ ያልኾነ (በግ ፍየል ፈረስ በቅሎ አህያ ግመል በሬ ") ።
ቁም ዜማ፡ ዝማሜ ጽፋት መረግድ ጸናጽል ከበሮ የሌለበት ዋና ዜማ ።
ቁም ደንጊያ፡ የቆመ/የተገተረ (ያልተ ጋደመ ") ።
ቁም ጥፈት፡ ጕልሕና ማለፊያ ጥፈት፡ ረቂቅ ያይዶለ በሩቅ የሚታይ ሳይጋደም በቀጥታ የተጣፈ፡ ሰው ቆሞ በዘንግ መጠን የ ሚያነበው ።
ቁምስና - ቆሞስነት፡ ቆሞስ መኾን ።ቁምስና የግእዝ፡ ቆሞስነት ያማርኛ ነው ።
ቁምሶ፡ ከስንዴ ጋራ የተጋገረ እን ። ዘሩ ቀመሰ ነው ።
ቁምሩ፡ ታናሽ ርግብ ቡያ የወፍ ዐይነት ። ባረብኛ "ቁምሪ" ትባላለች ።
ቁምባ፡ ያገር ስም።
ቍምድ፡ የተቈመደ (ድርት ግብረ መርፌ ውስብስብ ") ።
ቍምጣ፡ ቁመቱ ከጕልበት በላይ የኾነ ዐጪር ሱሪ ወንበር የለሽ ። "ቍምጣ ሱሪ" እንዲሉ።
ቍምጤ፡ ብጣሽ ቍራጭ ነገር ።
ቍምጤ፡ የሣር ስም ።
ቍምጥ፡ ቍርጥ ጕምድ፡ መቈመጥ ። (ተረት)፡ "ቈማጣ ቢለው፡ ያው ቍምጥ ነው፡ ሌላ ምን ይመጣል" አለ ።
ቍምጥ አለ፡ ጕምድ ብጥስ አለ ።
ቍምጥ፡ የተቈመጠ፡ ቍርጥ ጕምድ ።
ቍምጥምጥ አለ፡ ቍርጥርጥ አለ ።
ቍምጥና፡ ቈማጣነት፡ ቢስ ገላ ደዌ ሥጋ ። (ተረት)፡ "ከሹመት ክፉ ግብዝና፡ ከበሽታ ክፉ ቍምጥና" ።
ቁሞች፡ ከብቶች እንስሶች ።
ቍስለ ሥጋ፡ የሥጋ ቍስል (ቍምጥና ወይም ሌላ ") ።
ቍስለ ነፍስ፡ የነፍስ ቍስል (ኀጢአት ነፍስን የሚጐዳ ") ።
ቍስለት፡ ንዝንዝ ጭቅጭቅ ።
ቍስለኛ (ኞች)፡ ተመቶ ተወግቶ ተገ ርፎ፡ ተቈርጦ፡ ተፈንክቶ፡ ተቃጥሎ፡ የቈሰለ ሰው (ባለቍስ ") ።
ቍስሉ ሰፋ፡ አፋገ በዙሪያ ጨመረ ።
ቍስላም፡ ቍስል ያለበት የበዛበት ።
ቍስል (ሎች)፡ ደምና መግል እዥ የሚፈሰው ዕከክዐይነት (ብጕንጅ ችፌቂጥኝ ") ።
ቍስል (ቍሱል)፡ የቈሰለ ("(ቅጽል)") ("(፪ነገ. ፰፥ ፳፱ ። ፱፥ ፲፭)") ።
ቍስቈሳ፡ ጠቀሳ/ጭመራ ።
ቍስቋም ማሪያም፡ የቍስቋም ማሪ ያም ።
ቍስቋም፡ እመቤታችን ተሰዳ የተቀመ ጠችበት የግብጽ ተራራ ።
ቍስቋም፡ የታቦት ስም (በኅዳር ፮ ቀን የሚነግሥ የመቤታችን ጽላት ") ።
ቍስቋሞች፡ የቍስቋም ካህናት እወዳ ሾች ።
ቍስጥንጥንያ፡ የቈስጠንጢኖስ መናገሻ ከተማ ።እንደ ፈረንጅ አቈጣጠር ካ፲፬፻፷፯ ዓ ም ወዲህ ግን የቱርክ መዲና ኾናለች ።
ቍረማ፡ ኵርኰማ።
ቍረንጮ፡ ያለቀ የደቀቀ አሮጌ ዝተት (ቍርጩ የሚለብሰው ") ።
ቍረንጯም፡ ቍረንጮ ለባሽ ።
ቍሪት፡ የግል ገንዘብ ቅርስ ።ባረብኛ "ሰና ተ ተወራራሽ" ስለ ኾኑ "ቍሪትና ቅርስ" አንድ ወገን ናቸው ። "ጥሪት ቍሪት" እንዲሉ ።
ቍራ (ሮች)፡ ጥቍር አሞራ (ሲጮኸ ቍር ዋዋ የሚል ") ("(ዘፍ. ፯፥ ፮ ። ፩ነገ. ፲፯፥ ፬ - ፯)") ። (ተረት)፡ "ጩኸት ለቍራ፡ መብል ላሞራ" ።ቍራ አራት ዐይነት ነው፡ ኹለቱ ፍጹም ጥቍሮች በደጋ በቈላ የሚኖሩ፡ ሦስተኛው በራሱ ላይ ነጭ አለበት፡ በምሳሌ እንደ ቄስ ይታሰባል፡ እንስሳ አውሬ በሞተ ጊዜ ኹለት ዐይን ያወጣል፡ ("(ለሌሎች ይባርካል)") ። "ቧሔ ቍራ" እንዲሉ ። አራተኛው ደረቱና ዐንገቱ ነጭ ነው መጠኑም ከሦስቱ ያንሳል ። ቍራ በዕብራይስጥ "ቆሬእ" በግእዝ "ቋዕ" ይባላል፡ ፈላስፎች ፪፻ ዓመት ይኖራል ይላሉ ።
ቍራ ይጮኸበታል፡ ከነዋሪዎቹ ክፋት የተነሣ አገሩ ከተማው ይፈታል፡ ጠፍ ይኾናል ("(ኢሳ. ፴፬፥ ፲፩)") ።
ቍራሽ (ሾች)፡ የዳቤ/የንጀራ ክፍል (ትልቁም ትንሹም ") ("(ዘፍ. ፲፰፥ ፭ ። ማቴ. ፲፬፥ ፳)") ። የዳቦ ሲኾን ጕርማጅ ይባላል ።
ቍራን (ዐረ ቀረአ - አነበበ)፡ የመ ጽሐፍ ስም (እስላሞች ለነቢያችን መሐመድ ከሰማይ ወረደ የሚሉት መጽሐፍ ") ። ብሉይንና ሐዲስን የሚያስተባብል ። ትርጓሜው ንባብ ("ምንባብ") ማለት ነው ። ባረብኛ "ቁርኣን" ይባላል ።
ቍራኛ (ኞች)፡ ከጠላት ጋራ የታ ሰረ እስረኛ (በሰው ያደረ መንፈስ ርኩስ ") ።
ቍራጭ (ጮች)፡ ጕራጅ ጕማጅ ሙዳ ዕራፊ ("(፪ሳሙ. ፭፥ ፩ ። ማቴ. ፱፥ ፲፮ ። ማር. ፪፥ ፳፩)") ።
ቍሬማ፡ እኸል፡ የማያበቅል፡ መሬት ።
ቍሬማ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ራሱ፡ በትር፡ ኵርኵም፡ ያረፈበት "
ቍር (ቍርዕ)፡ የብረት ቆብ ቦርቦርቲ ራሰ ከል ። በግእዝ "ጌራ ኀጺን" ይባላል ። "ራስን" ተመልከት ።
ቍር (ቅሩሕ - ቅሩዕ - ኵሩዕ)፡ የተቈራ/የተበጣ (ብጥ ቍርም ቡቅር ልጩ ") ። የራሱን ጠጕርና ጥፍሩን በገዳም ቀብሮ የኼደ ጠበለተኛ ።
ቍር፡ ቅዝቃዜ ።
ቍር፡ ቅዝቃዜ ።
ቍር፡ ብርድ/ቅዝቃዜ ። ባላገር ግን ቍር በማለት ፈንታ ቈራ ይላል ።"ቍርዬን" እይ ።
ቍር አደረገ፡ ሰበረ ቀፈቀፈ ፈለፈለ አወጣ መለሰ ።
ቍር፡ ዝኒ ከማሁ፡ ክርከማ ።"ጥፍር ቍርጫ" እንዲሉ ።
ቍር፡ የብረት ቆብ፡ ቈራ ።
ቍርማሚ፡ የዳቤ/የዳቦ ሾለቅ ("ኵርማን ቀንድ መስሎ የሚታይ ") ።
ቍርም፡ የተቈረመ።
ቍርምቢ፡ ወጠጤ፤ቍርንቢ ።
ቍርስ አለ፡ ተቈረሰ ።
ቍርስ አደረገ፡ ቍርስ በላ ተመገበ (አፉን አጝሸ ") ።
ቍርስ አደረገ፡ ቈረሰ ።
ቍርስ፡ የተቈረሰ/የተፈተተ ("(ቅጽል)") ።
ቍርስ፡ ጥቂት ምግብ (ጧት የሚበላ ሙሽት ") ("(ስም)") ።
ቍርስርስ - ቍርስራሽ፡ የተቈራረሰ (ክፍልፍል ክፍልፋይ ") ።
ቍርር፡ የተቈረረ (ድርብርብ ንብብር ድንጋይ ") ።"በቍርር ላይ ቍርር" እንዲሉ ።
ቍርሾ፡ ትንሽ ቂም የቈየ ።
ቍርቍምባ፡ ዓሣ መያዣ የሻታ ዐይነት (ባለገመድ ጠርሙስ መሳይ ") ።
ቍርቍሩ፡ ኵኵሉ ።
ቍርቍሩ፡ ያ ቍርቍር (የርሱ ቍርቍር ") ።
ቍርቍራ፡ የዛፍ ስም (ፍሬው የሚበላ የበረሓ ዕንጨት እሾኸ ቈላፋ ") ። በዜጋመል "ገባ" ይባላል ።
ቍርቍር፡ በተጕለት ውስጥ ያለ ቀ በሌ ።
ቍርቍር አደረገ፡ መዝጊያ መታ ።
ቍርቍር፡ የተቈረቈረ የተበሳ ግንድ (የተደፈነ ድፍን ጥቅጥቅ ምሥርት ") ።
ቍርቍዝ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቍርቊስት፡ የዓሣ ስም (መናኛ ዓሣ ") ።
ቍርቊሻ፡ የጨዋታ የውጊት ፈተና ።
ቍርቈራ፡ ምሰት ቍፈራ ሽንቈራ ም ሥረታ ጕርበጣ ደፈና ።
ቍርቈራ፡ የጥሪ ምልክት ።
ቍርባ፡ ድንገተኛ በሽታ (የሚያስታው ክና የሚያስቀምጥ ሰውነትን የሚያደርቅ ") ።
ቁርባብቻ፡ ከቈዳና ከጨርቅ የተሰፋ ከረጢት ።
ቍርባን፡ ለግዜር ለጣዖት የሚቀርብ መሥዋዕት ዕርድ (ስንዴን ወይንን ዕጣንን የመሰለ የተቀደሰና ማለፊያ ስጦታ ኹሉ ") ።
ቍርባን ውጭ ክርስትና፡ (አይገባም የቀረው ነው)፡ አስቀድሞ ሊደረግ የሚገባው በኋላ እንዳይደረግ ለማስጠንቀቅ፡ "ቍርባን ውጭ ክርስትና" እየተባለ ይተረታል ።፫ኛውን ጠባ እይ ።
ቍርባን፡ የክርስቶስ ሥጋና ደም (በስንዴ ኅብስትና በወይን ጠጅ መልክ የሚሰጥ ") ።በሚገባ የተቀበለውን ወደ ፈጣሪ የሚያቀርብ ስለ ኾነ ፥ዳግመኛም ቄሱ ከጸሎትና ከቅዳሴ ጋራ በቅዱስ መንበር ላይ ላምላክ የሚያቀርበው በመኾኑ ቍርባን ተባለ ። (ግጥም)፡ "የግብጽ ሰዎች በስላም የተዋጡ ከቍርባን ይልቅ ትምርትን መረጡ፡ ጊዜ ሲመቻቸው ቍርባንን ሊገልጡ" ።
ቍርብ ጭታ፡ ዕትራት ።
ቍርብጭ አለ፡ ዕትር አለ ።
ቍርብጭ፡ የቈረበ (ጕርብ ") ።
ቍርታት (ቍርሐት)፡ ብጥታት ፍቅ ታት ቡቅራት ልጭታት ።"ቍርሐት" ባጤ ዘርዐ ያዕቆብ ታሪክ ይገኛል ።
ቍርንቢ፡ ተባት ፍየል (ታናሽ ወጠጤ ") ። ላውራ በግም ይነገራል ("(ሕዝ. ፴፬፥ ፪)") ።"ቍርን" "ቀርን" "ቢ" "ቢጽ" (ቀንዳም ቢጤ ማለት ይመ ስላል ") ። "ኵርንቢን" እይ ።
ቍርንባጥ፡ ዐጪር ።—ኵርንባጥ ።
ቍርንቦች፡ ተባቶች (ወጠጦች ") ("(ዘፍ. ፴፥ ፴፭)") ።
ቍርንድይ፡ የትንባኾ ልጥልጥ ።
ቍርንድድ፡ ደረቅ ሻካራ ከርዳዳ ቍጥርጥር የኾነ ጠጕር፡ ዘሩ ከረደደ ነው ።
ቍርንጭ፡ መጥፎ ጠባይ ያለው ሰው (ቈጭባራ ") ።"በመለ ቍርንጭ" እንዲሉ ።
ቍርንጭ፡ ዐጨርና ቍጥርጥር የሻንቅላ ጠጕር ።
ቍርኙ፡ የተቈረኘ የተጠመደ የታሰረ ።
ቍርኝት፡ የተቈረኘተ (ንፍ ሆደ ጒስር ") ።
ቍርዛም (ሞች)፡ ያልተገዘረ (ባለቍ ርዝ ") ።
ቍርዝ (ዞች)፡ የወይፈን የበሬ ብ ልት ።
ቍርዝ፡ ልንቡጥ ሽፍን ወሸላ ።
ቍርዝ፡ የተቈረዘ (ዛብ የሚመስል ጅ ራፍ ሽርብ ") ። ቍርዝ ያሠኘው ጥብቅነቱ ነው ።
ቍርዬ፡
ቍርጠማ፡ የመቈርጠም ሥራ (ጕርደማ ") ።
ቍርጠት፡ የሆድ በሽታ (አንዠትን እየቈረጠ የሚያም ") ። ትርጓሜው መቍረጥ መቈ ረጥ ። "ለሆድ ቍርጠት ብላበት ለራስ ምታት ጩኸበት" እንዲሉ ።
ቍርጠኛ (ኞች)፡ ርግጠኛ የማይወላውል የማያመነታ ።
ቍርጡ ታወቀ፡ ርግጡ እውነቱ ድ ርሱ መጨረሻው ተገኘ ተረዳ ።
ቍርጣ፡ ጭፍልቅ (የገላ ተኵስ በቁመት ") ።
ቍርጣሚ፡ ዕኛኪ ።
ቍርጣና ብርባሮ፡ መስቀልኛ የዠርባ ተኵስ (አግድምና ሽቅብ የተተኰሰ ") ። ከዚህ የተነሣ ቍስሉ ጠባሳው የሰንጠረዥ መደብ ይመስላል ።
ቍርጣና ብርባሮ፡ የዕዳሪ ዕርሻ ።
ቍርጥ፡ ርግጥ ያለቀ የተፈጸመ ("(ኢሳ. ፲፥ ፪)") ።
ቍርጥ ነገር፡ ያለቀ የደቀቀ ጕዳይ ።
ቍርጥ አለ፡ ብጥስ አለ ።
ቍርጥ ኾነ፡ ተረገጠ ተፈጸመ ።
ቍርጥ፡ የሰራዊት ክፍል (ልዩ ልዩ ጭፍራ ") ("(፩ሳሙ. ፲፫፥ ፲፯)") ።
ቍርጥ፡ የተቈረጠ (ጕምድ ሙዳ ሥጋ ") ። "እጀ ቍርጥ" እንዲሉ ። "ቈረፀን" እይ ።
ቍርጥ ፍርድ)፡ "ስቀለው ግደለው" የሚል ። "ገበዘ" ብለኸ "ግብዝን" እይ ።
ቍርጥማታም፡ ቍርጥማት የሚያጠቃው ሰው (ባለቍርጥማት ") ።
ቍርጥማት - የጡንቻ ህመም.
ቍርጥማት (ቍርጥ - ማት)፡ ቍርጠኛ ቍጣ ሥቃይ ።
ቍርጥማት፡ ያጥንት/የጥርስ/የዥማት በሽታ ("(፩ነገ. ፲፭፥ ፳፫)") ።
ቍርጥም አደረገ፡ ቈረጠመ ።
ቍርጥም፡ የተቈረጠመ/የታኘከ (ዕኝክ ") ።
ቍርጥርጥ አለ፡ ብጥስጥስ አለ ። "እከሌና እከሌ ቍርጥርጥ ያለ ጥል ተጣሉ" ።
ቍርጥርጥ፡ የተቈራረጠ (ብጥስጥስ ") ። ቍርጥራጭ፡ ዝኒ ከማሁ (የበገና ጠፈር ጠፍር ") ።
ቍርጩ፡ አንዳች ኣልባ ።
ቍርጩ ድኻ፡ አገኛለኹ ከማለት ተስፋው የተቈረጠ (ወርቀ ለባሽ ይልሰው ይቀምሰው የሌለው למנו ዐዳሪ መናጢ ችግረኛ ") ።
ቍርጭምጭሚት (ቶች)፡ በኹለት ወገን ያለ የእግር ጕጥ (የጫማና የቅልጥም መገናኛ ") ("(፪ሳሙ. ፳፪፥ ፴፯ ። ሕዝ. ፵፯፥ ፫)") ።
ቍርጭኝ፡ ዐጪር ድጓ ሰንበት አ ምኜ ። "ቍርንጭን" "ቍረንጮን" "ቍርንጫጭን" እይ፡ የቈረጪ ዘሮች ናቸው ።
ቍርጭኝ፡ ዐጪር ድጓ ቈ ረጨ ።
ቍርፅ፡ የተቈረፀ፡ ቍርጥ ዐጪር የዜማ ምልክት ።
ቍርፌ፡ አሮጌ ጋሻ ።
ቍርፍድ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቍሻሻ፡ ጥራጊ እድፍ ጕድፍ ግባስ ። ቍሽሽ፡ መቈሸሽ ። ቍሽሽ አለ፡ ቈሸሸ ። መቈሸሽ፡ ማደፍ/መኵለፍለፍ ። መቈሸሻ፡ ቈሻሻ መኾኛ ።
ቍሽቢያም፡ የቍሽብ ወገን፡ ወስፋቱ እኸል የማይቀበል ።
ቍቁ (ቈቀወ)፡ ኡኡ ።
ቍቁ አለ፡ ጮኸ ("ኑልኝ ድረሱልኝ የሰው ያለኸ አለ ") ።
ቍቁታ፡ ቍቁ ማለት (የተገፋ የተበ ዶለ ሰው የሚያደርገው ጩኸት ") ።
ቍቁታውን ለቀቀ፡ ጩኸቱን አበዛ (አደጋ ስለ ደረሰበት ") ።
ቍቂያም፡ ፈሱን ቍቅ ያደረገ ሰው (ባለቍቅ ") ።
ቍቅ፡ ታናሽ የፈስ ድምዕ ።
ቍቅ አለ፡ ተፈሳ ።
ቍቅም፡ ከፈስ ተቈጠረችና ። (ተረት) ።
ቍቅታ፡ ቀጪን ፈስ፡ ቍቅ ማለት ።
ቍባ፡ ጕባ (ዕንቍላል ቤት ") ። ቍባ ግእ ዝኛ ነው ።
ቁባት (ዕቅብት)፡ የተጠበቀች (ካ ስቀመጣት መኰንን በቀር ሌላ ወንድ እ ንዳይደርስባት በጃን ደረባ ተጠብቃ የምት ኖር ሴት - ምልምል ሥራ ቤት ገረድ ") ።
ቁባት፡ የተጠበቀች ዐቀበ ።
ቁባቶች (ዕቁባት)፡ ጥብቆች ሴ ቶች (ነገሥታት መኳንንት በተራ የሚደር ሱባቸው የሚገናኟቸው የንግሥታት ተወራ ጆች ") ።
ቍቤላ፡ የዝኆን ጊደር (ዘር ለመቀበል የምትችል ") ።
ቁብ (ዐቀበ - ዕቁብ)፡ ዐሳብ ግድ ። በጋልኛ ግን ጣት ማለት ነው ።
ቍብ፡ መቀመጥ ቈበበ ።
ቍብ ቍብ አለ፡ ጕብ ጕብ አለ ።
ቍብ አለ፡ ጕብ አለ ቍጭ አለ ።
ቁብ የለሽ፡ ዐሳብ የለሽ ግድ የለሽ ።
ቍብ፡ ጕብ ቍጭ (መቀመጥ ") ።
ቍብላ፡ ትልቅ ወይፈን (በትከሻው ቀንበር ለመቀበል ዘሩን ለማቀበል የሚች ") ።
ቍብታ፡ ጕብታ (ጕብ ማለት ") ።
ቍተማ፡ ስለፋ ።
ቍቲት (ቶች)፡ የነጠላ/የኩታ/የ ጋቢ ዘርፍ ("የሚቋጭ የሚከረር የሚሸረብ ") ።
ቍቲት በጣሽ፡ ሸማኔ ቍቲትን እየበጠሰ ድርን የሚቋጥር ።
ቍትቻ (ቀቶት)፡ አስከፋዩ የኅዋት ዳኛ ("ተከፋዩ ጋሬዳ የኾነ ገንዘብ ") ።
ቍቻ፡ እየተጠበሰ የሚበላ እንጕዳይ ("እሆድ ቋት የሚገባ ") ።
ቍነና፡ ጕንጐና ሽረባ ።
ቍና (ዎች)፡ መስፈሪያ የስፌት ዕቃ (ትንሽና ትልቅ መሸመቻ አጋማሽ መገበ ሪያ ቍና እንዲሉ ") ። (ተረት)፡ "ለስማ መጥሪያ ቍና ሰፋች" ። (አዝማሪ)፡ "እንዳይቀደድ ይህ ቍና፡ ብድር አለበትና" ("(ማቴ. ፯፥ ፪ ። ማር. ፬፥ ፳፬ ። ሉቃ. ፮፥ ፴፰)") ።
ቍና፡ መስፈሪያ ። ቈነነ ።
ቍና ቍና ተነፈሰ፡ ከሩጫ ብዛት የተነሣ እጅግ በጣም ተነፈሰ ።
ቍና ተኩል፡ የስፍር ስም (አንድ ተግማሽ ") ።
ቍና ፈጅ፡ አንድ ቍና እኸል የሚ ይዝ ሸክላ ።
ቍናሳም፡ ግማታም ጥንባታም ።
ቍናስ፡ ግማት ጥንባት (የማይሽር ቍ ስል መጥፎ ሽታ ") ።
ቍን (ቍንጽ - ቀነጸ)፡ የተባይ ስም፡ ቀን ተደብቆ ይውልና ሌሊት የሰውን ገላ የሚመጠምጥ የሚልስ የሚበላ ጥቍር ተባይ ተፈናጣሪ ዘላይ ። ሲበዛ "ቍንጮች" ያ ሠኛል ። "ሞያሌን" ተመልከት ።
ቍንም፡ ቤት ውሻ ።
ቍንቍኔ፡ ጥንጣን ነቀዝ ብል ትል ("(ግእዝ)") ። "ቅንቅንን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቍንቍን - ቍንቍኔ ።
ቍንቍን አለ፡ ቈጥቋጣ ኾነ ።
ቍንቍን፡ የተቈነቈነ (ትንትን ") ።
ቍንን (ኖች)፡ የተቈነነ (ትት ጕን ጕን ሽርብ፡ ጕኒና ቆብ ጭራ፡ ጅንን ኵሩ ") ።
ቍንን በላይ ነኸ፡ የመንዝ ባላ ባት የኰሩ የተጀነኑ የተቋፉ (ካጤ ምኒልክ እስከ ዐጤ ኀይለ ሥላሴ የነበሩ ደጃዝማች ") ።
ቍንዥና፡ ቈንዦ መኾን (ውበት ") ።
ቍንድድ፡ የተቈነደደ የተገረፈ (ግርፍ ") ።
ቍንድዶ፡ ከሐረር ከተማ ወደ ጅጅጋ ሲኼዱ በስተግራ የሚታይ ተራራ ነፋሳም ብርዳም ።
ቍንዶ (ጕንዶ)፡ ባለያ ሴት ሥራ ዐዋቂ ።
ቍንዶ በርበሬ (ጕንደ በርበሬ)፡ የቅመም ስም፡ ወጥ ተሠርቶ ሊወጣ አቅራቢያ የሚጨመር የሚነሰነስ (መከለሻ ከባሕር የመጣ የንጨት ፍሬ ") ።
ቍንጠራ፡ የመቈንጠር ሥራ ኹኔታ ።
ቍንጠጣ፡ ቍንጥ ረገጣ ።
ቍንጢብራ፡ ኀፍረተ ብእሲት ።
ቍንጢጥ፡ የጣት አጣብቂኝ (የሕፃን ቅጣት ") ።
ቍንጣሪ፡ የተቈነጠረ ትንሽ ነገር ።
ቍንጣሪት፡ የተቈነጠረች ።
ቍንጣራ፡ ፌንጣ ኵብኵባ ።
ቍንጣር (ሮች)፡ ጠይብ፡ የጠይብ ወ ገን ሸክላ ቈንጥሮ የሚሠራ ።
ቍንጣናም፡ ቍንጣን የያዘው ያስጨነ ቀው ሰው ።
ቍንጣን (ቅንጣዌ)፡ ከማርና ከማንኛ ውም ምግብ ብዛት የሚመጣ መጥፎ ጥጋብ በላይ ማስታወክን በታች መተንፈስን የሚከለ ክል። ውሻው ብዙ ደም ስለ ጠጣ ቍንጣን ይዞት በምድር ላይ ይንከባለላል ። "ፈለጠን" እይ ።
ቍንጣይ - ቍንጻይ ።
ቍንጥ ቍንጥ አለ፡ ተቍነጠነጠ ።
ቍንጥል - ቍንጽል ።
ቍንጥር ቍንጥር አለ፡ ፊናጥ ፊናጥ ብድግ ብድግ አለ፡ ተቅበጠበጠ ።
ቍንጥር አደረገ፡ ንክስ አደረገ ።
ቍንጥር፡ ዝኒ ከማሁ ለቍንጣሪ፡ ባለም ድር ካጋዛው ርስት ላይ ያነሣው ጥቂት መሬት ።
ቍንጥርጥር፡ የተቈነጣጠረ፡ ዐልፎ ዐ ልፎ ቍጭ ቍጭ ያለ ጠጕር ።
ቍንጥንጥ አለ፡ ቅብጥብጥ አለ ።
ቍንጥንጥ፡ የተቍነጠነጠ (ቅብጥብጥ ") ።
ቍንጥጥ አደረገ፡ ልምዝግ ንክስ አ ደረገ፡ ቈነጠጠ ።
ቍንጥጥ፡ የተቈነጠጠ የተለመዘገ የተ ቀጣ ልጅ ።
ቍንጪት፡ ከቍጫጭ የምታንስ ተ ንቀሳቃሽ፡ ዳግመኛም ባላገሮች ነፍሳት ይሏታል።
ቍንጫቶ፡ ጕልጓሎ ።
ቍንጭ፡ ተቈናጣጭ ፍጥረት ።
ቍንጮ (ዎች - ቍንጾ)፡ የሕፃን ዐናት ጠጕር ። ዳግመኛም በግእዝ "ቍንዝዕ" ይባላል ።
ቍንጮ፡ የጣራ የክዳን ጫፍ ጕል ላት የሚቀመጥበት ። "የቤት ቍንጮ" እንዲሉ።
ቍንጮ ያ፡ መኻል ራስ ።
ቍንጮ፡ ያጤ ምኒልክ እናት የወይዘሮ እጅጋየኹ አጫዋች ባናቱ አንድ ቀጪን ቍ ንጮ የነበረው፡ ታቦት ዘፋኝ ገና ተሳዳቢ ። ኣ ሽከሩም የልብ ዐውቃ ይባላል ። "ጀጀበን" እይ ። አቈናጨ፡ አላቀመ አጐላጐለ ።
ቍንጯም፡ ቍንጮው ያደገ የረዘመ ልጅ ።
ቍንጯም አሞራ፡ ጕትዬ ።
ቍንጸላ፡ ኵስተራ ሰበራ ግንጠላ ።
ቍንጻይ፡ የቍንጽል ዐይነት ።
ቍንጽል (ሎች - ሡዕ)፡ የተቈነጻለ (ኵስታሪ ቍራጭ ግንጣይ፡ የጧፍ የጥራዝ ") ። በ ግእዝ ግን ቀበሮ ተኵላ ማለት ነው ።
ቍዘማ፡ ዐዘን ለቅሶ ሙሾ የሐዘን እንጕርጕሮ ("(ሮሜ. ፰፥ ፳፮)") ።
ቍዝራት፡ የሆድ መነፋት ።
ቍዝር (ሮች)፡ የተቈዘረ (ጕኝር ጕስር ") ።
ቍዝር አለ፡ ጕስር አለ (ተቈዘረ ") ።
ቍዳማ - አቍዳማ፡ የብር ጌጥ (በባሕር ዐረብ ተሰፍቶ በግንባር ላይ የሚታ ሰር ያዳል ገዳይ ምልክት ") ።
ቍድ፡ መብራት የሚኾን ቋድ ።
ቍድስ፡ የተቈረሰ ቍርስ የምግብ ክፍል ። ባረብኛ ግን የቤተ መቅደስ ክልል ገረገራ ማለት ነው፡ ባማርኛም የኅብስተ ቍርባ ንን ፍታቴ ያሳያል።
ቍግ (ጎች)፡ የገመድ ጅራፍ ጫፍ ውልብልቢት ጕተና መሳይ ። ቍግ የሚኾኑ ና ስንደዶ ጥፍር አንዶ እንሰት ቃጫ ጭራ ዶቢ የበሬ ኋላ እግር ዥማት ናቸው ።
ቍጠባ፡ ቅነሳ (የመቈጠብ ሥራ፡ ፈረንጆች "ኤኮኖሚ" ይሉታል ") ።
ቍጠኛ፡ ቍጡ (ቍጣ ወዳድ ባለቍጣ ተቈጪ ") ።
ቍጠጣ፡ የመቈጠጥ ኹኔታ ።
ቍጠጥ)፡ ቅጥነት ቀጪንነት ይላል ።
ቍጡ (ቍጡዕ)፡ የተቈጣ/የሚቈጣ (ብስጩ ገሣጭ ገላማጭ ") ።
ቍጡነት፡ ቍጡ መኾን ።
ቍጢሶ፡ ባላንጣ ምንዝር ባለጢንጦ ።
ቍጢሶ አለ፡ ተለየ ተገለለ ዕልፍ ብሎ ተቀመጠ ።
ቍጢጥ፡ በቋፍ መቀመጥ ።
ቍጢጥ አለ፡ በእግሮቹ ጣቶች ተቀመጠ (ቍጣጥ የሚጥል መስሎ ") ።
ቍጣ (ቍጥዓ)፡ ተግሣጽ ዘለፋ ግልምጫ መዓት ።
ቍጣሮ - አቍጣሮ፡ የመቍጠሪያ ጸሎት ።
ቍጣጣም፡ ቍጣጠ ብዙ ባለቍጣጥ ።
ቍጣጥ (ጦች)፡ የንቦሳ የግልገል የሕፃን ወፈር ያለ ቅዘን ። ግእዝም (ቍጥ)፡ የጦር ውልብልቢት፡
ቍጥራት (ቶች)፡ የቊጥር ኹናቴ (እስ ራት ("(፩ሳሙ. ፴፥ ፲፪)")) ።
ቍጥር (ሮች)፡ የተቈጠረ ("(ሕዝ. ፭፥ ፫)") ። "የባቄላ ቍጥር" እንዲሉ። ሒሳብ ስሌት ልክ መጠን፡ መደመር መቀነስ ማብዛት ማካፈል። ቍጥር፡ አኃዝና ፊደል፡ ጥቅልና ዝርዝር ። "መደበኛ ቍጥር ተራ ቍጥር" እንዲሉ። ቍጥር የተቋጠረ፡ ቋጠረ ።
ቍጥር (ሮች)፡ የተቋጠረ/የታሰረ (እ ስር ") ። "የገመድ ቍጥር" እንዲሉ።
ቍጥር (ጥቋ)፡ መቋጠር ።
ቍጥር አለ፡ ተቋጠረ ።
ቍጥር የተቈጠረ፡ ቈጠረ ።
ቍጥርጥራም፡ ባለብዙ ቍጥር ።
ቍጥርጥር አለ፡ ተቈጣጠረ ።
ቍጥርጥር፡ የተቈጣጠረ (እስርስር ሣር ") ።
ቍጥቍጥ፡ መቈንጠር/ቍጠባ/ቍንጠራ ።
ቍጥቍጥ አደረገ፡ በጥቂት በጥቂት አወጣ ሰጠ ።
ቍጥቍጥ፡ የተቈጠቈጠ (ምልምል ቍርጥ ") ።
ቍጥቈጣ፡ ቈረጣ ልብለባ ።
ቍጥቋጦ (ዎች)፡ ከምድር ከፍ ያለ በጣም ያላደገ ወጣት ግራር ሌላውም እሾኽ ያለው ዕንወት ኹሉ። "ቴዎድሮስ መጣ ዐይኑን አፍጦ ወይ መሸሸጊያ ታናሽ ቍጥቋጦ" (እረኛ) ።
ቍጥቋጭ፡ የቍጥቋጦ ጭፍጫፊ ።
ቍጥባት፡ ቍጠባ ።
ቍጥብ፡ የተቈጠሰ (በሣጥን በከረጢት ያለ የተቀመጠ፡ ለወጪውም ይነገራል ") ።
ቍጥን (ቁጥን)፡ ጥጥ ።
ቁጥን፡ ዐረብኛ፡ ቍጥን፡ ግእዝኛ ነው፡ ከቀጠነ ጋራ ይሰማማል ። ፈረንጆች "ኩቶን" ይሉታል ።
ቍጥጥ አደረገ፡ ቈጠጠ ።
ቍጥጥ፡ የተቈጠጠ (በልብስ በምድር ላይ ያለ ") ።
ቍጥጥር፡ ምርምር ።
ቍጩት፡ የማክረር ሥራ ።
ቍጫ፡ በቈ ቡልኮ አምሳል ከፈረንጅ አገር ተሠርቶ የመጣ ልብስ ቍቲቱ የሚቋጭ ።
ቍጫም፡ ቍጭ ያለበት የበዛበት ስፍራ (የድንጋይ ሥር ") ።
ቍጫጭ (ጮች)፡ ታናሽ ፍጥረት (ከጕንዳን ከዘመሚት ከምሥጥ እጅግ የምታንስ ተንቀሳቃሽ የጤፍ ቅንጣት የምታኸል ከነፍሳት የምትበልጥ ") ።
ቍጫጮ - ጕጫጮ፡ ዐጪር ሣር ።
ቍጭ፡ መቀመጥ ።
ቍጭ ብዬ፡ የማሽላ ስም (ዐጪር
ቍጭ አለ፡ ተቀመጠ ።
ቍጭ ወረረው፡ ከበበው ወረሰው አለበሰው ።
ቍጭመቀመጥ፡ ቈ ቀጠበ (ቀጸበ - ዕብ. ቃጻብ)፡ ጨረሰ ቈረጠ፡ ጠቀሰ፡ ከነዳ ለካ መጠነ፡ አመለከተ ምልክት አደረገ ከሰለ ድርን ። ለዕ ድሜም ይነገራል።
ቍጭር፡ ሸሐኝ (የለገመ ቍስል ባለመጅ ") ። "ቍጭር ይቀመጥብኸ" እንዲሉ። "ጭንቍርና ጭንኰር" ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቍጭቋጮ፡ የጣት ትግል፡ ወይም ት
ቍጭብርብር፡ ጠባዩ ዐይጥ የበጣጠ ሰው ፈትል የኾነ ።
ቍጭት አለው፡ ጸጸተው ።
ቍጭት፡ ጸጸት ያልተገለጠ ቂም ቍርሾ ። "በጠላ ቤት ጠብ ቢነሣ እከሌ እከሌን በቍጭት መታው" ።
ቍፂያም - ቍጋም፡ የከሳ ሰው (ከሲታ ሴት ዥማታም ") ።
ቍፈራ - ቍፋሮ፡ ምንቀራ ጕድፈራ ምሰት ።
ቁፋ (ዐረ)፡ ታናሽ ቅርጫት ።
ቁፋሂ፡ ሂ ዋዌ ነው፡ ቅርጫትም ያሠኛል ።ባለቅኔዎች ግን ቅኔ ማሕሌት ይሉታል ።
ቁፋዳ - አቁፋዳ (አኩፋዳ)፡ የተማሪ ኰረጆ፡ በዙሪያው የቈዳ የገመድ ቀፈድ ያለው የምግብ መያዣ ከሰሌን ከሌጦ የተበጀ ።
ቍፍር፡ የተቈፈረ/የተማሰ ። (ተረት)፡ "ካባ ቍፍር እሸት ተበልቶለት" ።
ቂላቂል፡ የቂል ቂል ሞኛሞኝ ።
ቂላዋት (ቂል ኀዋት)፡ የቂል ወንድም (ወንድሞች ") ጅላዋት ።
ቂላዋት፡ የቂል ወንድም፡ ቄለ ።
ቂል ።
ቂል (ሎች)፡ ጅል ግጅል ሞኝ ከርፋፋ መነፍ ተላላ ነኹላላ እንከፍ ነጕላ ነፈዝ ። (ተረት)፡ "ቂል አይሙት እንዳያጫውት"
ቂል አስተኔ፡ የቂል ዐይነት ።
ቂል—ጅል—ቄለ ። ቃለ (ዐረ)፡ አለ ተናገረ ።
ቂሎ፡ የዘንጋዳ ስም፡ ቀጪን ረዥም
ቂመኛ (ኞች)፡ ባለቂም፡ ቂምን በልቡ የሚያኖር/የሚይዝ ("(መዝ. ፵፬፥ ፲፮)") ።
ቂሙን ቀረፈ፡ ብድሩን መለሰ፡ እንደ መቱት መታ፡ እንዳዋረዱት አዋረደ፡ ቂሙን ተወ ።
ቂም - ቍርሾ (ቀየመ - ቄመ) ።
ቂም፡ ቍርሾ ብሶት ቍጭት ክፉ ዐሳብ ("(ሮሜ. ፲፪፥ ፲፬)") ። (ተረት)፡ "ቂም ይዞ ጸሎት፡ ሳል ይዞ ስርቆት" ።
ቂም በቀል፡ የበቀል ቂም ።
ቂም ያዘ፡ ቂምን በልቡ አሳደረ ።
ቂም—(ቀመደ)፡
ቂስ፡ የሰው ስም (የሳኦል አባት ") ።
ቂራጥ፡ ግብዝ ወርቅ ። በግእዝ "ተምያን" ይባላል ። ፈረንጆች "ካራት" ይሉታል ።
ቂርቆስ፡ የሰው ስም ("ጨርቆስ") ።
ቂሮስ፡ ቈሰለ ።
ቂሮስ፡ የሰው ስም (መዠመሪያው የፋርስ ንጉሥ ") ።
ቂሮስ ዳርዮስ፡ ከቂሮስ ልጅ ከካምቢስ ቀጥሎ የነገሠ ዳርዮስ ሦስተኛ የፋርስ ንጉሥ፡ ቂሮስ የዳርዮስ ቅጽል ነው ።
ቂብ፡ ሴትኛ መቀመጥ መምላት ። ዘሩ ቈበበ ነው።
ቂብ አለ፡ መላ የሆድ ።
ቂብ አለች፡ ተቀመጠች ።
ቂንር - ቅንር፡ የተነፋ ንፍ ።
ቂንር አለ፡ ዕብጥ አለ ። "ሆዱ ቂንር ብሏል" እንዲል ባላገር ።"ጐኘረን" እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቂንቂን፡ መውጣት መታየት ።
ቂንቂን አለች፡ እታይ እታይ አ ለኹ ኣለኹ እለች፡ ተሽኰነተረች ።
ቂንዳም፡ ቂንድ ያለበት ባለቂንድ (ያ ገዳ እኸል ") ።
ቂንድ (ዶች)፡ ያገዳ ገለባ ፍሬ ዐቃፊ ።
ቂንጥ (ቂጥ)፡ ቂብ መቀመጥ ። "በረረን" እይ ።
ቂንጥራም፡ ብእሲት ።
ቂንጥር፡ ልሳነ ኀምስ፡ እንደ እንጥል በመካከል ይታያል ።
ቂው አለች፡ ጭው አለች (ተባት ፈለገች እንስት ዶሮ ") ።
ቂድር አለ፡ ህርት አለ ።
ቂድር፡ የቄደረ/የሚቄድር ኵሩ/ትቢተኛ ።
ቂጡ ቀጤማ ቈረጠ፡ ፈጽሞ ደስ ተሠኘ (ተደሰተ ") ።
ቂጡን ጣለ፡ ያለቀ ሱሪ ታጠቀ ።
ቂጣ (ቀጣ)፡ የምግብ ስም (ዱቄቱ በውሃ ተለውሶ ታሽቶ ሳይቦካ ወዲያውኑ በፍጥነት የሚጋገር የመንገደኛ የችግረኛ መብል ") ("(ዘፀ. ፳፱፥ ፪)") ። "የገብስ የስንዴ ያጃ የጤፍ የሽን ብራ የምስር ቂጣ የጠላ ቂጣ" እንዲሉ። ሲበዛ "ቂጣዎች" ይላል ።
ቂጣ ቈሎ፡ ከግንቦት ልደታ ዠምሮ ባ፲፪ቱ ወር መባቻ የሚ ደረግ፡ ልማዳዊ አምልኮ ባዕድ የበዓለ ናእት ምሳሌ ("(ዘሌ. ፳፫፥ ፮)") ። "ቂጣና ቈሎ" ወይም "ቂጣ ከቈሎ ጋራ" ማለት ነው ። ቈሎው የስንዴ ቂጣው የጤፍ ኹኖ በተልባ ብጥብጥ ይበላል ። ልደታ ከወር እወርሽ አድርሽኝ እየተባለ አስቀድሞ ተልባው በቂጣው ይረጫል፡ ቈሎውም ይበተናል ። የመቤታችን ልደት ርግጠኛው በመስከረም ፲ ቀን ሲኾን ከሣቴ ብርሃን ሰላማ በግንቦት ፩ ቀን ያደረገው ይህን አምልኮ ለማጥፋት ነው ይባላል ።
ቂጣ ቈረጥ፡ ዘወትር ቂጣ የሚበላ (ቂጣ ወዳድ ቂጣ የሚቈርጥ የሚገምጥ ") ።
ቂጣ በል፡ የጭፍራ ስም (ማደሪያ ያልተሰጠው ወታደር ቂጣ በል ይባላል፡ እሱ የሚያርሰውንም መሬት የቂጣ በል ምድር ይሉታል ") ።
ቂጣ፡ ያልሠለጠነ (ባላገር አእምሮው ያልተገራ ") ።
ቂጣ፡ ጥረሾ ከገብስ የተጋገረ ።
ቂጣለኝ (ቂጣ አለኝ)፡ የቀበሌ ስም (በላይኛው ወግዳ ካጤ ዋሻ በስተቀኝ ያለ ቀበሌ ") ።
ቂጣም - ቂጠ፡ ትልቅ ሰው ። ቂጥ፡ መቀመጥ ።
ቂጥ (ቀጣ)፡ መቀመጫ የዙስ የ እበት መውጫ መፍሻ መተንፈሻ ። የቂጥ ምስጢር ግራና ቀኙ እንደ ብራና ቅጽ ትክክል መኾኑንና የመካከሉን ክፍልነት ያሳያል ።
ቂጥ ለቂጥ ገጠመ፡ ዐበረ ዐደመ አሤረ ።
ቂጥ ቀጠበ
ቂጥ አለ፡ ከፍ ባለ ስፍራ በጫፍ ተቀመጠ (ቂብ አለ ") ።
ቂጥኛም (ሞች)፡ ቂጥኝ የያዘው ባለ ቂጥኝ ። "መነኵሴና ቂጥኛም ሰው ኹሉ እንደሱ እንዲኾን ይፈልጋል" ። "ወረደ" ብለኸ "ው ርዴን" አስተውል ።
ቂጥኝ (ቀጣ ቂጥ)፡ የቍስል በሽታ፡ ብዙ ስምና ዐይነት ያለው (ያመንዝሮች ቅጣት ") ። (ግጥም)፡ "ምን ይይዛት ብዬ ዝንጀሮን ቂጥኝ፡ አለመጠርጠሬ ጕድ አረገችኝ" ።
ቂፉንቂ፡ ጨፋና አሞራ (የቅኔ ቤት ዐማርኛ ነው ") ።
ቃ
ቃ፡ መድረቅ ።
ቃ፡ መድረቅ ቃቃ ።
ቃ አለ (ትግ ቀዐነ - ደረቀ)፡ (ጥቅጥ) ደረቅ መጠጥ ቀንበር አለ ።
ቃ አለ፡ ደረቀ ቃቃ ።
ቃ አደረገ፡ ቀንበር አደረገ ።
ቃለ ሕይወት፡ የሕይወት ቃል፡ ጌታችን ያስተማረው ወንጌል ። "ቃሌን የጠበቀ ሞትን አይቀምሰውም" የሚል ("(ዮሐ. ፮፥ ፷፰፡ ፰፥ ፶፩)") ። "ቃለ ሕይወት ያሰማዎ" እንዲሉ ተማሮች ከትምርት በኋላ ።
ቃለ ሰላላ)፡ ቃለ ቀን ሴት ድምጥ።
ቃለ አኅስሮ፡ የማዋረድ ቃል ።
ቃለ አራኅርኆ፡ የማራራት ቃል ። "ሆይን" ተመልከት ። ይህ ኹሉ በግእዝ ሰዋሰው ንኡስ አገባብ ይባላል፡ መሠረቱም "ኦ" ነው ።
ቃለ አክብሮ፡ የማክበር ቃል ።
ቃለ አጋኖ (ሆይ)፡ የማጋነን ቃል፡ ከዚህ ዠምሮ "ቃለ አራኅርኆ" አለው ድረስ የ"ሆይ" ትርጓሜ ነው ።
ቃለ አፍርሆ፡ የማስፈራት ቃል ።
ቃለ እግዚአብሔር፡ የግዜር ቃል (የሃይማኖት ትምርት ወይም ርሱ ራሱ ጌታ ችን ") ።
ቃሉ፡ ያ ቃል፡ የርሱ ቃል።
ቃሉን አከበረ፡ በቃሉ ጠና፡ የተናገረውን አደረገ ።
ቃሊም (ሞች ዐረ ቃሊብ ኵየት)፡ የመጠጫ ትንባኾና እሳት ማስቀመጫ የት የሚመስል የሚያኸል ።
ቃሊም፡ የወንዝ ዳር ደገፍ ዐቃባ ። በግእዝ "ናህብ" ይባላል ።
ቃሊቱ፡ ያች ቃል።
ቃላተኛ (ኞች)፡ ቃልቻ/ትንቢት ተናጋሪ ባለቆሌ ካህነ ጣዖት ("(ዘሌ. ፲፱፥ ፳፮፡ ፳፥ ፮)") ። "ቆሌንና ቃልቻን" እይ ።
ቃላት (ቃሎች)፡ ድምፆች ነገሮች ።
ቃል ።
ቃል (ሎች)፡ ብትን (ዝርው) ቃል፡ ድምፅ ነገር አፍ ።
ቃል ለቃል፡ አፍ ላፍ ።
ቃል ማሰሪያ፡ የጋብቻ ውል ፈጠም ። "ቃሌ ነው"፡ "ብያለኹ፡ ተናግሪያለኹ" ።
ቃል ሰጠ፡ ዕሺ "እሰጣለኹ/አደርጋ ለኹ" አለ ማለ ።
ቃል ሰጠ)፡ "ዕሺ አደርጋለኹ" አለ። "ሰጠ" የ፪ ፊደል ግስ ኹኖ መጥበቁ "ሰጠወ"ን ተከትሎ ነው። ላይችል አይሰጠውም)፡ እግዜር ለሰው ከዐቅሙ በላይ ጭንቅ አያመጣበትም።
ቃል ትምርት)፡ በቃል የሚማሩት (የንባብ/የዜማ/ጸሎት) ።
ቃል ዐባይ፡ የዋሾ የቀጣፊ የሐሰተኛ ቃል ።
ቃል ኪዳን ተጋባ፡ ተዋዋለ ተማማለ ("(፬ነገ. ፭፥ ፲፪፡ ኢሳ. ፶፯፥ ፰፡ ሕዝ. ፴፬፥ ፳፭)") ። "ቃል ለምድር ለሰማይ አለ"፡ ፈጽሞ ማለ፡ ማላውን አጸና ።
ቃል ኪዳን፡ የማይቀር የማይታበል እንደ መሐላ ያለ የውል ውለኛ ቃል። በግእዝ "ኪዳነ ቃል" ይባላል ።
ቃል፡ ወልድ ከቅድስት ሥላሴ ኹለተኛው አካላዊ ቃል ("(ማሕ. ፪፥ ፰፡ ዮሐ. ፩፥ ፩፡ ፩ዮሐ. ፭፥ ፯)") ።
ቃል ገቢ፡ ዋና ሚዜ ።
ቃል ገባ፡ የማይፈርስ ውል አደረገ ።
ቃልቻ (ቾች)፡ ቃላተኛ ባለዛር ሌሊት ድቤ ሲመታ የሚያድር፡ ቡሓ በግ ወሰራ ዶሮ ነጭ ኰርማ ጥቍር ፍየል ዕረዱ ሠዉ የሚል ።
ቃልቻ) ። ተሸካሚነት፡ ተሸካሚ መኾን ።
ቃሏ፡ የርሷ ቃል።
ቃመ (ቀሐመ)፡ እሸትን ንፍሮን ቈ ሎን ከውስጥ እጁ ወዳፉ ወረወረ ቻመ ገተመ ቸቸረ፡ ባፉ ምርትን ስጥን ገለባን ዐመድን ገፈረ ተረፈሰ ቸፈረ ሰመሰመ ዐፈሠ ።
ቃሚ (ቀሓሚ)፡ የቃመ/የሚቅም ( ቻሚ ሰምሳሚ ") ።
ቃሚያ (ቃሕም)፡ አንድ ጊዜ ተቅሞ የሚታኘክ የሚዋጥ፡ በውስጥ እጅ የተለካ የተ መጠነ፡ የዳቦ የንጀራ ፍርፋሪ ድቃቂ ። በግእዝ "ፍተ ቃሕም" ይባላል ።
ቃም (ቅሒም)፡ መቃም ።
ቃም አደረገ፡ ቃመ ።
ቃም፡ ዝኒ ከማሁ ። "ዐፈር ቃም" እንዲሉ።
ቃም፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ።
ቃሞ - ቅሞ፡ የመምህራን ዐማርኛ ነው ።
ቃሰተ፡ ኣኣ ኣለ፡ ቃተተ ቃዘነ ጣረ ተጨነቀ (ከውጋት የተነሣ በቀስት እንደ ተነደፈ ሰው ") ።
ቃሰተ፡ ኣኣ ኣለ፡ ቃተተ ቃዘነ ጣረ ተጨነቀ (ከውጋት የተነሣ በቀስት እንደ ተነደፈ ሰው ") ።
ቃሰነ (ቃዘነ)፡ ጐመዠ ቃቃ ።
ቃሰነኛ፡ ባለቃሰን (ቃሳኝ ጕምዡ ") ።
ቃሰን፡ ጕምዠታ ።
ቃሳኝ፡ የቃሰነ/የሚቃስን (ጐምዢ ") ።
ቃረ ። ቍርዬ፡ (ቍራዊ)፡ ያሞራ፡ ስም፡ በመከር፡ ጊዜ፡ ከውጭ፡ አገር፡ እየመጣ፡ እኽል፡ የሚበላ፡ በውሃ፡ ዳር፡ የሚያድር፡ ሲኼድ ቍር፡ (ኵር)፡ የሚል፡ የባሕር፡ አሞራ፡ ሲመጣም፡ ኾነ፡ ሲመለስ፡ በኣየር፡ መጥቆ፡ ተራ፡ ይመታና፡ እየተከታተለ፡ በመሪ፡ ይኼዳል፡ አገሩም፡ ኣውስትራልያ፡ ነው፡
ቃረ፡ ሳለ አፋጩ ፈገፈገ ።
ቃረመ፡ (ቀሪም፡ ቀረመ)፡ ካጨዳ፡ በኋላ፡ የወደቀውን፡ የእኸል፡ ዛላ፡ ለቀመ፡ ሰበሰበ።
ቃሩራ፡ ጠርሙስ ።
ቃሪያ በርበሬ፡ ያልቀላ/ያልበሰለ (እሳት ያልመሰለ ") ። ጨርቋ በርበሬ ሲበሉት አፍን የሚያቃጥል ።
ቃሪያ፡ እንጭጭ ጓሚያ ፍሬ ።
ቃሪያ ያልበሰለ፡ ፍሬ
ቃሪያ፡ ያልተማረ ያልሠለጠነ ሰው ።
ቃሪያ ጥፊ፡ አይበሉብሽ የውስጥ እጅ ዠርባ ። ቃሪያ ለጥፊ ቅጽል መኾኑን አስተውል፡ "በላን" እይ ።
ቃራሚ፡ የቃረመ፡ የሚቃርም፡ ለቃሚ፡ ሰብሳቢ ።
ቃራም፡ ቃር የማይለየው ።
ቃሬዛ፡ የሬሳ የቍስለኛ የበሽተኛ የወደቀ ከብት ማንሻ መሸከሚያ (ኹለት ኣጣና ባለቀላጥም ") ("(ግብ ሐዋ. ፭፥ ፲፭)") ።"ወሰካን" አስተውል ።
ቃሬዛ፡ የድግስ ስም (ስለ ሙታን ፍታትና ቍርባን ምክንያት ካህናት በደጀ ሰላም የሚመገቡት ምግብ የሚጠጡት መ ጠጥ ") ።
ቃር (ቀሐር)፡ የልብ ትኵሳት (በም ግብ ምክንያት የሚመጣ ") ።
ቃር አያውቅሽ፡ ታሞ የማያውቅ ሰው ጤናማ ።
ቃርሚያ፡ ቃርሞሽ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ (1 ሌዋ. ፲፱፡ ፲)
ቃሮዳ፡ በበጌምድር ከደንቀዝ በታች ከይፋግ በላይ ያለ አገር ።
ቃቂ፡ የቃቃ/የሚቃቃ (ጐምዢ ") ።
ቃቂል፡ ቃጭል ("(ግእዝ)") ።
ቃቃ (ትግ ቃዕቅዐ ።ግእዝ ቃሕቅሐ - ቈቍዐ - ሰቈቈ)፡ ጐመዠ ሠየ ተ ቃረ ፈለገ ። "ከብቶቹ ቃቅተዋል" እንዲል ባላገር ።
ቃቃታ፡ ሥየታ ቃቃ ።
ቃቃታ፡ ጕምዠታ ሥየታ ።
ቃቃታ፡ ፈጥኖ ኣለመናገር አፈ ጸያፍነት ።
ቃቃን፡ የአለት መንደያ ንጥር ብረት ካክራ ። "በትረ ቃቃን" እንዲሉ ። "ቀቃን" ተመልከት ።
ቃቄር (ሮች)፡ ቍራ ("(ግእዝ)") ።
ቃቄዳ፡ ግትቻ ዕላቂ ሰፌድ ።
ቃበበ (ትግ. ቀበበ)፡ እፌዘ አላ ።
ቃበበ (ዕብ. ቃባብ)፡ ናቀ ሰደበ ረገመ ።
ቃብትያ፡ እንደ ባልያ ያለ ተራራ ።
ቃተ - ቀአተ)፡ አቃተ፡ ተሳነ/ቸገረ ("አልቻልም አለ ") ።
ቃተ - ቀአተ)፡ አቃተ፡ ተሳነ/ቸገረ ("አልቻልም አለ ") ።
ቃተተ፡ ዞረ ለፋ ደከመ ("የጭንቅ ትንፋሽ ተነፈሰ ") ።
ቃተኛ፡ በያይነቱ ወጥ ያለበት ያነባ በሮ ዐይነት ዐምዛ ።
ቃታ (ቃቃ)፡ የጠመንዣ/የሽጕጥ/የመድፍ ጥይት ማስነሻ መተኰሻ ብረት ።
ቃታ (ቃቃ)፡ የጠመንዣ/የሽጕጥ/የመድፍ ጥይት ማስነሻ መተኰሻ ብረት ።
ቃታ (ቃተተ)፡ የማያቋርጥ ትንፋሽ ።"ሕፃኑ እጅግ ስለ ሮጠ ቃታ ይዞታል" ።
ቃታ (ቃተተ)፡ የማያቋርጥ ትንፋሽ ።"ሕፃኑ እጅግ ስለ ሮጠ ቃታ ይዞታል" ።
ቃታች፡ የቃተተ/የሚቃትት (ደካሚ ") ።
ቃት (ቃቃ)፡ ቃ ያለ የስንዴ እ ንጀራ ።
ቃት (ቃቃ)፡ ቃ ያለ የስንዴ እ ንጀራ ።
ቃነጠ)፡ አሽቃነጠ፡ ዘፈነ አረገደ እ ስክስታ ወረደ ።
ቃና (ቃነየ)፡ የዜማ የመጠጥ ጣ ዕም ። በግእዝ ግን ዜማ ማለት ነው ። "ንስርንና ምስርን" እይ ።
ቃና ምስር)፡ ከምስር የመጣ ዜማ። ዋሽንትም ምስር ቃና ሊባል ይቻላል (ዘሌ. ፳፭፥፱፡ ኢሳ. ፴፰፥፳፡ ሆሴ. ፭፥፰፡ ማቴ. ፳፬፥፴፩) ። ቃናን ተመልከት።
ቃና፡ የቀበሌ ስም፡ በቡልጋ ውስጥ ያለ ስፍራ ጉባኤ ቃና የተዠመረበት ።
ቃና፡ ጌታችን ውሃን ወይን ጠጅ ያደረገበት አገር በገሊላ አውራጃ ያለ ።
ቃናው ተለወጠ፡ ጣዕሙ ሌላ ኾነ ።
ቃንዛ፡ መንዘር (የደም ሥር በሽታ ") ።
ቃንዲላ፡ ጅራፍ ።
ቃንጤ፡ ፈሊጥ ዐመል ። "እከሌ ቃንጤው አይታወቅም" እንዲሉ።
ቃኘ (ቃነየ)፡ ቀነቀነ ዜማ ዠመረ አስቀድሞ አዜመ ።
ቃኘ (ትግ ቀነየ)፡ ሰነበተ ቈየ ።
ቃኘ፡ ዐሠሠ ጐበኘ ሰለለ ።
ቃኘ፡ የበገናን የክራርን ዥማት (ኦውታር) አጠበቀ አላላ አቃና አሰማማ ።
ቃኘ፡ ፈቀደ ማተረ ከብትን ።
ቃኘው፡ የልዑል ራስ መኰንን ፈ ረስ ስም ።
ቃኚ (ዎች)፡ የቃኘ/የሚቃኝ (ቀንቃኝ ጐብኚ ሰንባች ዐሣሽ ") ።
ቃውት፡ የዛፍ ስም (ርዝማኔና ቀጥታ ያለው ዕንጨት፡ ለደመራ ይፈለጋል ") ።
ቃዘነ፡ ተንከራተተ ባዘነ ። "ቃበዘን" አይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቃዛኝ፡ የቃዘነ/የሚቃዝን (ተንከራታች
ቃዠ (ጋዠ)፡ መጥፎ ሕልም አይቶ በንቅልፍ ልቡ ጮኸ አንቋረረ አላዘነ ።
ቃየል፡ የሰው ስም (የአዳም መዠመሪያ ልጅ ") ።
ቃዳ፡ ዝም እመም ተለላ ወረራ ።
ቃጠሎ፡ የእሳት አደጋ ።
ቃጠረ፡ ቀጠረ ቀጠሮ ሰጠ ።
ቃጠነ)፡ አቃጠነ፡ ወዲያና ወዲህ አለ፡ ነገር አሳካ አዋሸከ ።
ቃጣ (ቀጣ)፡ እጁን አነሣ ዘረጋ ደከረ ደቀነ አቀረበ (ለመምታት ለመያዝ ለማግኘት ") ። (ተረት)፡ "በሰው ቂጣ እጇን ትቃጣ (ትዘረጋ)") ።
ቃጣሪ፡ የቃጠረ/የሚቃጥር (ዳኛ ") ።
ቃጤ፡ ታናሽ መስፈሪያ ቍልቢጥ ።፡ ጭረቱ ቀላድ ወይም ገመድ
ቃጥላ፡ በመካከሉ ዝንጀሮና ጦጣ የሚኼዱበት ከአረኸ በላይ የቆመ ገደል፡ ምስጢሩ እንደ ተቀጠለ መኾንና ሣር አለማብቀል ነው ።
ቃጥላ ያኽላል፡ እጅግ ረዥም ነው ።
ቃጫ ቦራ፡ የፈረስ መልክ ብጫነት ያለው ።
ቃጭ፡ ሰይፍ የመታው የቈረጠው
ቃጭል (ሎች - ቃቂል)፡ በሕፃን በጥጃ በበቅሎ በተዋጊ በግና በተናካሽ ውሻ ዐንገት የሚንጠለጠል ድምፅ ሰዉ ጌጥ፡ ለቅዳሴ ለሰው መጥሪያ የሚኾን ታናሽ መርዋ ("(ዘፀ. ፳፰፥ ፴፫ - ፴፬)") ። (ተረት)፡ "በደንባሪ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ" ። "ብልብላን" እይ ።
ቃጭማ፡ የዛፍ ስም ።
ቃፍር፡ ከጥቦት የሚበልጥ በግ ።
ቄለ፡ ጀለ ተሞኘ፡ የማይረባ ቃል ተናገረ ።
ቄሎ፡ ከቅል የተበጀ መስፈሪያ ።
ቄሎ—ቀለበ ።
ቄሰ ገበዝ፡ ቅስናን ከግብዝና ያስተባበረ (የቤተ ክሲያን ንዋየ ቅድሳትና ገንዘብ ጠባቂ ሹም ") ። "ገበዝ ጐበዝ" ማለት ነው ። "አ መመ" ብለኸ "እምን"፡ "ነፈቀ" ብለኸ "ንፍቅን" አስተውል ።
ቄሳር፡ የሮማውያን ንጉሥ ስም (ሆድ ቀዳጅ ማለት ነው ") ("(ሉቃ. ፪፥ ፩ ። ፳፥ ፳፭)") ።
ቄስ (ቀሲስ)፡ ካህን ጳጳስ እጁን በራሱ ላይ ጭኖ መንፈሳዊ ሥልጣን የሰጠው የቤተ መቅደስ አገልጋይ (ባራኪ ቀዳሽ ናዛዥ የነፍስ አባት ") ። ሲበዛ "ቄሶች" ያሠኛል ። "ቄስ ያማርኛ፡ ቀሲስ የግእዝ" ነው ።
ቄስ፡ በቁሙ ።—ቀሰሰ ።
ቄስ በደጅ፡ ከቤት በስተውጭ የሚገኝ ቅጠል (መድኀኒትነት ያለው ") ።
ቄስ አሞራ፡ ቍራ ጥንብ ባራኪ (ራሰ መላጣ ጥንበ በላ ") ።
ቄስ ዐጤ (ቄሰ ሐፄ)፡ የንጉሥ ነፍስ አባት (ዘውድ ዐጣኝ ማእድ ባራኪ ") ።
ቄስ ዐጤ ዘወልድ፡ በዘፋኝ ዳዊት ባጤ በካፋ ዘመን የነበሩ ቄስ (ፍጹም ሊቅ ቅባቶችን ከሞት ያዳኑ ") ።
ቄራ (ቀረየ)፡ በግና ፍየል በሬ የርድ ከብት ኹሉ እየገባ የሚታረድበት ስፍራ (ሉካንዳ ሥጉያ ") ።
ቄራ፡ ማማ (የሰብል መጠበቂያ ረዥም ቈጥ ያዝመራ ዐልጋ ") ።ምስጢሩ ሰብሉ ከተ ነሣ በኋላ መንደድ መቃጠልን ያሳያል ።
ቄርሎስ፡ የሰው፡ ስም፡ የእስክንድርያ፣ ሊቀ፡ ጳጳሳት። በጽርእ፡ ፈለገ፡ እግዚእ፡ ማለት፡ ነው፡ ይላሉ።
ቄብ (ዕብ - ንቄባ - ቀዳዳ)፡ ያልተ ጠቃች እንስት (በግ ፍየል - አህያ ዶሮ ") ።
ቄብ ሻለቃ፡ ዝቅተኛ ጦር አዛዥ ።
ቄቦች፡ ያልተጠቁ እንስቶች/እንስሶች ።
ቄንጠኛ (ኞች)፡ ነቃፊ አላጋጭ (ባለ ቄንጠኛ ") ።
ቄንጠኛ፡ ጌጠኛ ተሽኰንታሪ ተሽሞን ኝ አለባበስ አሳማሪ ።
ቄንጥ፡ ልዩ ኹኔታ (ጌጥ ") ።
ቄንጥ፡ ጡር ነቀፋ ነውር መስቃ ።
ቄንጦ፡ የንጨት ስም (ትንንሽ ቈላፋ እሾኸ ያለው ዛፍ ") ።
ቄደረ (ዐረ. ቀደረ - ቻለ)፡ ኰራ (ተ በውቀት በችሎታ ") ።
ቄደር (ቄድር)፡ የመጽሐፍ ስም፡ ክ ርስቲያን ሃይማኖቱን ክዶ ማተቡን በጥሶ ቂጥኝ አውጥቶ ቢረክስ ንስሓ ከገባ በኋላ ቄሶች ይህን መጽሐፍ እየደገሙ ያጠ ምቁታል።
ቄጆ (ቀዳ)፡ ማለቢያ ቋ ጮጮ አኮሌ ።
ቄጥ፡ የበሬ ዕከክ ።
ቈ (ትግ. ቈጸየ)፡ ጸጸተ አተ ከዘ ። "ያለፈው አይቍጭኸ፡ ለሚመጣው ተጠንቀቅ" ። (አዝማሪ)፡ "ተይ መጭ በቅሎ ተይ መጭ፡ ነገር ካልሰሙት አይቈጭ" ።
ቈ፡ የቀ ዲቃላ በመኾኑ ስለ ቀለበቱ ቍ100 ይባላል ።
ቈለ፡ ተገለጠ ጠራ በራ ጐላ ።
ቈለለ (ጐለለ)፡ ደረደረ ደረበ አነባበረ ከመረ ጐቸ፡ አበዛ ። "ዋጋ ቈለለ" እንዲሉ።
ቈለል ቈለል አደረገ፡ ከብለል ከብለል አደረገ፡ አንገዋለለ ዐይኑን ።
ቈለመመ ።
ቈለመመ ። ቋሊማ፡ አንዠት ውስጥ የተከተተ ደቃቅ የሥጋ ክትፎ ።
ቈለመመ፡ ቀለሰ ዘለስ ዘቀዘቀ፡ አጐበጠ ጠመዘዘ ። "ቸለሰን" እይ ።
ቈለመም - ቈልማማ፡ የተቀለሰ/የተዘ ለሰ (ቀላሳ ጐባጣ ጠምዛዛ ቀንድ ") ።
ቈለመጠ)፡ አቈላመጠ፡ ውዳሴ ከንቱ ሰጠ፡ ፊት ለፊት አመሰገነ፡ ተለማመጠ ("(ኢዮ. ፲፱፥ ፲፯፡ ፴፪፥ ፳፩፡ ምሳ. ፲፱፥ ፮)") ።
ቈለቈለ - ቈልቈለ)፡ አቈለቈለ (አ ቈልቈለ)፡ ዘቀዘቀ፡ ቍልቍለት አደረገ፡ ቍልቍል ነዳ ወሰደ አወረደ፡ አጐነበሰ ("(ዘዳ. ፳፮፥ ፲፭)") ።
ቈለቈል (ሎች)፡ ባረኸ በቈላ በበ ረሓ ስፍራ የሚበቅል የቍልቋል ወገን ዕንጨት ። ደሙ መርዝነት ስላለው ዐይጥ ከሰሶ ጋራ በበላው ጊዜ ያብዳል፡ ርስ በርሱ እየተናከሰ ያልቃል ።
ቈለቈልዳ፡ ዝኒ ከማሁ፡ ዳ ከዕዳ መጥቶ ተጨምሯል።
ቈለበጠ፡ አነሰ ። "ቈለጠበን" እይ ።
ቈለኛ (ኞች)፡ በቈላ የተወለደ በቈላ የሚኖር ሰው/እንስሳ ።
ቈለዘ፡ ቈጠቈጠ እሾኸ ቈረጠ (ግእዝ) ።
ቈለዘመ)፡ ተቈላዘመ ተጐናዘለ ተዘናፈለ ተጠላለፈ፡ የሣር/የጠጕር ።
ቈለጠ (ፈተወ)፡ ቋመጠ ተወነገ ተወሰጠ ተወዘወዘ ።
ቈለጠበ፡ ብልጥ ኾነ፡ በሰው ነገር ገባ ።
ቈለጠብኸ፡ ብልጠት አበዛኸ ።
ቈለጣም፡ ቈለጠ ትልቅ ሰው ።
ቈለጥ (ጦች)፡ ቍላ የወንድ (ተባት) ብልት ፍሬ ።
ቈለጭ (ጕራጌ)፡ እንቍራሪት ጕርጥ ።
ቈለጭ፡ ዐይናማ ዐይነ ጥሩ ዐይነ ትልልቅ ።
ቈለጭ፡ የሰው ስም።
ቈለጭ፡ የዓሣ ስም።
ቈለጰለጠሰ - ቀለጰለጠሰ)፡ አን ቈላጰላጠሰ)፡ የቧልት የጨዋታ ግስ ። "ራሴን በራሴ ካላንቈላጰላጠስኹት ማን ያንቈላጰላጥስ ልኛል" እንዲል የቅኔ ተማሪ ። ትርጓሜውም ኰፈሰ አከበረ ማለት ነው ። ዳግመኛም በግእዛዊው "ቀለጰ"ና "ለጠሰ" ዘይቤ ሲፈቱት መብላ ትንና መተኛትን ያሳያል ። "ቀለበን" ተመልከት ።
ቈለፈ (ቈሊፍ ቈለፈ)፡ ውስጥ ለ ውስጥ ዘጋ ቀረቀረ ሸጐረ ።
ቈለፈ፡ ሸፈነ ወሸለ ።
ቈለፈ፡ አጐበጠ ቀለሰ ዐጠፈ ።
ቈለፈ፡ ያዘ ዐነቀ፡ አለቅ አለ ።
ቈለፈ—ቀላቀለ ።
ቈለፈታም፡ ልንቡጣም ቦርጫም ዘር ጣጣ ። "ቀፈትን" እይ ።
ቈለፈት፡ ሸለፈት ልንቡጥ ሸንኰፍ ሽፍን ሽፍናት ወሸላ ። በግእዝ "ቍልፈት" ይባላል ።
ቈለፈት፡ ቦርጭ ትልቅ ሆድ ።
ቈላ (ቀለወ)፡ በሠማ ምጣድ ጥሬ እኸልን አንጣጣ አበሰለ፡ በጐባጣ ዕንጨት ዐመሰ አማሰለ፡ ወጥን፡ ዐመፀኛን ጠበሰ ("(ኤር. ፳፱፥ ፳፪)") ።
ቈላ (አንሳሕስሐ)፡ አንቀሳቀሰ ወዘወዘ ነሰነሰ ። "ውሻ ጌታውን ባየ ጊዜ ዥራ ቱን ይቈላል" ።
ቈላ፡ ሰውን በጅራፍ ገረፈ፡ በጥይት
ቈላ ቍስል)፡ የቈላ ቍስል (ጐርምጥ ጫዌ ") ።
ቈላ፡ አቃረ አቃጠለ ልብን ።
ቈላ፡ ከደጋ በታች ያለ አገር፡ ወይም በረሓ ምድረ በዳ፡ ፀሓይ እንደ እሳት የሚፋ ጅበት የሚያቃጥልበት እንጭርጭር ስፍራ፡ የገሃነመ እሳት ምሳሌ ። (ተረት)፡ "እግዜር በትር ሊቈርጥ ቈላ አይወርድም" ።
ቈላ ደጋ ረገጠ፡ አንደዬ ወደ ታች አንደዬ ወደ ላይ አለ፡ አመነ ካደ ።
ቈላይ (ዮች)፡ የቈለለ/የሚቈልል (ከማሪ ") ።
ቈላፊ (ዎች)፡ የቈለፈ/የሚቈልፍ (ዘጊ ") ።
ቈላፋ፡ ጫፈ ቀላሳ ዕንጨት ከዘራ ብ ረት ። "ወንቃፍን" እይ ።
ቈላፍ፡ ወሸላ ሽፍን ያልተገረዘ አረመኔ (ግእዝ) ።በሱማልኛም "ቈለፍ" ይባላል ።
ቈላፍነት፡ ወሸላነት ("(ኤር. ፬፥ ፬፡ ሮሜ. ፬፥ ፲፡ ፲፪)") ።
ቈልማ፡ ቀንደ ዘላሳ ።
ቈልማ፡ ቀንዱ ዘላሳ ዘቅዛቃ ቀላሳ የኾነ በሬ ። "ጐዳንና ጕመላን" አስተውል ።
ቈልማሚ፡ የቈለመመ/የሚቈለምም (ቀላሽ አጕባጭ ጠምዛዥ ") ።
ቈልማሜ፡ ዳቦ ቈሎ የቈልማማ ዐይነት ወገን ።
ቈልጣባ፡ ጮሌ ጥልቅ ብዬ ።
ቈሎ (ቅልው)፡ የተቈላ በሠማ ምጣድ ላይ የበሰለ (ቅጽል) ። "ዳቦን" እይ ።
ቈመለለ፡ ዘለሰ—ቈለመመ ።
ቈመቂመ)—ቀመሰ፡
ቈመቈመ - ኰመኰመ)፡
ቈመደ (ቀመጠ)፡
ቈመደ (ጐመደ)፡ ክርን አዋሰበ፡ ድ ርና ማግን መጣፊያ አደረገ፡ የልብስን ቀዳዳ ደረተ ደበደበ ደፈነ ።
ቈመደ፡ በባላገር አይ ነገርም።
ቈመጠ (ቀመጠ)፡ የእጅንና የእግርን ጣት አቈሰለ ቈረጠ ጐመደ በጠሰ አሳ ጠረ ።
ቈመጠ፡ መታ ጠዘለ ደበደበ ነረተ ።
ቈመጥ፡ ባ፩ ወይም ባ፬ ወገን ስለት ያላት በሎታ በትከሻ የምትንጠለጠል ዐጪር ዱላ ራስ መጠበቂያ ።
ቈመጥማጣ - ቍምጥምጥ፡ የተቈማመጠ (ጕምድምድ ") ።
ቈሚጥ፡ ድንክ ዐጪር ሰው ።
ቈማመጠ፡ ቈራረጠ ጐማመደ ።
ቈማጅ፡ የቈመደ/የሚቈምድ (አዋሳቢ ደራች ") ።
ቈማጣ - ቈመጥማጣ፡ የቈመጥማጣ/ቈማጣ (ድርብ ስድብ ") ።
ቈማጣ (ጦች)፡ የተቈመጠ (ጣት አልባ ዱሽ ሽንድፍድፍ ገላውን ቍስል ድል ያደረገው አባ ጐንዳ ") ።
ቈማጣነት፡ ቈማጣ መኾን ።
ቈማጤ ።
ቈማጤ፡ የተክል ስም፡ ቈማጣ የሚመስል ጣፋጭ ፍሬ ሻካራ ፍርክርክ ።
ቈማጭ፡ የቈመጠ/የሚቈምጥ (ቈራጭ ጐማጅ ") ።
ቈሰለ (ቈሲል - ቈስለ)፡ ተነካ ተላጠ ተገጠበ ደማ ።
ቈሰለ፡ በጦር ተወጋ (በቀስት ተነደፈ በሰይፍ በጥይት ተመታ ") ።
ቈሰለ)፡ ዐዘነ ተናደደ ።
ቈሰሰ - ቈረሰሰ - ጐሰሰ)፡ ተንቋሰሰ፡ ተንቈረሰሰ ተጐተተ ።
ቈሰቈሰ (ኰሰኰሰ)፡ ጠቀሰ ገፋ አገባ ጨመረ (ማገዶን ወደ እሳት ቈሰቈሰ ") ። ነካ አወከ ። "ጐተጐተን" እይ ።
ቈሳሰለ፡ በብዙ ወገን ቈሰለ ።
ቈሳቍስ፡ የቤት ዕቃ ሰባራ ሥንጥር ። "ቈሳቊስ በግእዝ ዕቆች ማለት ነው፡ አንዱ ቈሰቈስ ይባላል" ።
ቈሳቈሰ፡ ፋፋ ጨማመረ ።
ቈስቋሽ (ሾች)፡ የቈሰቈሰ/የሚቈሰቍስ (ጠቃሽ ገፊ ጨማሪ ") ።
ቈስቋሽነት፡ ቈስቋሽ መኾን ።
ቈስጠንጢኖስ፡ በ፪፻፺፱ ዓ ም በግሪክ አገር የነገሠ መዠመሪያ የክርስቲያን ንጉሥ ።
ቈሥፌ፡ መልካም ሽታ ያለው ዛፍ ።
ቈረ፡ ፈጽሞ ደኸየ (የለት ጕርሥ ያመት ልብስ ዐጣ ነጣ መነጠ ") ።
ቈረመ፡ በቀላል፡ መታ፡ ኰረኰመ፡ ራስን።
ቈረመመ፡ አሾለቀ/አሾጠጠ ።
ቈረመደ)፡ ተቈራመደ፡ ተጨበጠ/ተኰራመተ (ከችግር ከብርድ የተነሣ ") ።
ቈረመድ - ቈርማዳ፡ የተቈራመደ (ጨባጣ ኰርማታ ") ።
ቈረሰ፡ ፈተተ ገመሰ ገመደለ ቀረደደ ከፈለ ጐረመደ ("(ማቴ. ፲፬፥ ፲፱ ። ሉቃ. ፱፥ ፲፮)") ።
ቈረሰሰ - ቈሰሰ)፡ አንቈረሰሰ፡ ዝኒ ከማሁ፡ እንቀረደደ ።
ቈረሳ፡ ፍተታ ።
ቈረረ (ቈለለ)፡ ጫነ ደረበ አነባበረ ።
ቈረረ (ቈሪር - ቈረ)፡ በረደ ቀዘቀዘ ።
ቈረረ፡ ቈረሰ ።
ቈረር፡ ድርብ የደንጊያ ምልክት ።"አንድ ቊራ በታየ ጊዜ መንገደኞች ኹለት ደንጊያ ያነባብራሉ" ።
ቈረቈሰ፡ አጫረ ጠብን ጦርነትን ዠመረ ፈተነ ።
ቈረቈሰ፡ የገና ጨዋታን ባረከ፡ ዕሩርን መታ (በትርን ገዉ ") ።
ቈረቈረ (ዕብ ቃር)፡ ማሰ ቈፈረ ሰ ረሰረ በሳ ነደለ ሸነቈረ (ከተማን መሠረተ ዠመረ ") ። "ዘሩ ቈረረ" ነው ።
ቈረቈረ፡ መታ ጠረጴዛን ገበታን ።
ቈረቈረ፡ አቈሰለ ራስን ።
ቈረቈረ፡ ወጋ ጐረበጠ ነካ አሳመመ (ገላን ሆድን ዐይንን ") ።
ቈረቈረ፡ ደፈነ መረገ ጠቀጠቀ (የሸክ ላን ቀዳዳ በዶሮ ማርና በብረት ዐር በጨርቅ በሾኸ ") ። "ደበደበን" እይ ።
ቈረቈራም፡ ቈረቈር ያለበት የበዛበት ልጅ ።
ቈረቈር፡ የራስ ቍስል (ከመጥፎምላE ከፀሓይ ሙቀት የተነሣ የሚመጣ ") ።
ቈረቈንዳ፡ ፍሬው የወጣ ያገዳ ራስ ።
ቈረቈዘ (ቀርቀም)፡
ቈረቈዘ፡ ጐኑ ጠበበ፡ ቁመቱ ዐጠረ ።
ቈረበ (ቀረበበ)፡ ተቀራረበ ተጠጋጋ ተገነኛኘ ።
ቈረበ (ቀርበ)፡ ቀደሰ ሠለሰ፡ ቍርባን ሥጋ አምላክ ተቀበለ ።"ከቈረበች ባሰች ከመነኮሰች አፈረሰች" እንዲሉ ።
ቈረበ፡ ጐረበ ተቋጠረ ውሃ ያዘ ዐዘለ ዐተረ ።
ቈረበበ)፡ አንቈረበበ፡ አቈረበጨ ። አጐረበ ። በተገብሮነትም ይፈታል።
ቈረበብ - ቈርባባ፡ የተንቈረበበ/የሚንቈረበብ (ቍርብጭ ") ።
ቈረበተ፡ ቈርበት ኣለበሰ ጐለበ ለጐመ ።
ቈረባ (ትግ ቈርብዐ)፡ ደረቀ ።
ቈረነ፡ ዐወደ ቦጨቀ ።
ቈረነ፡ ዶንጊያ ተከለ (ምልክት አደረገ ") ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፭)") ። ትርጓሜ ። "ቈረረን" እይ፡ ነና ረ ይወራረሳሉ ።
ቈረነ፡ ዶንጊያ ተከለ ምልክት አደረገ ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፭)") ። ትርጓሜ ። "ቈረረን" እይ፡ ነና ረ ይወራረሳሉ ።
ቈረን፡ የጤፍ አገዳ ቅሬታ (እንደ ቀርን (ቀንድ) ሽቅብ የቆመ ያሾተለ ") ። "የጤፍ ቈረን" እንዲሉ ።
ቈረኘ (ትግ ቁረነ)፡ አሰረ ጠመደ ። ገረኘን አስተውል ።
ቈረኘተ (ቈረኘ)፡ ነፋ ጐሰረ ።
ቈረዘ፡ ሸረበ፡ ቍርዝ አወጣ፡ ሸፈነ ።
ቈረዘዘ)፡ ኣንቈረዘዘ፡ አንጠለጠለ ("(ተንጠለጠለ)") ።
ቈረጠ (ቀረፀ)፡ ጐረደ ጐመደ መደ መደ ሸለተ በጠሰ (እንዳገዳ ከፍ እንደ ባቄላ ከሥር ") ። አጠፋ ("(ኤር. ፪፥ ፳)") ። "አፈፈን" "ዋጋን" "ካሳን" "መቅንን" "ሤራን" "ቀጻን" "ተስፋን" እይ ።
ቈረጠ፡ ሐሳቡን አንድ ወገን አደረገ፡ ጨረሰ ፈጸመ ።
ቈረጠ፡ ሆድን ዐመመ ።
ቈረጠ፡ ለየ ወሰነ ቀንን ።
ቈረጠ፡ ቀነሰ አጐደለ ።
ቈረጠ፡ ፍርድን ሻረ ደመሰሰ ለወጠ፡ ወይም ኣጸና አጸደቀ (ጥፋተኛን በመቅጣት በመግደል ") ።
ቈረጠመ፡ ገላን ዐጥንትን ዐመመ ።
ቈረጠመ፡ ጐረደመ በጥርስ ሰበረ ከረተሰ ዐኘከ በላ (ዕንጨትን ጥሬን ቈሎን ምላስን ") ("(ራእ. ፲፮፥ ፲)") ። ቈረጠመ እንደ መከርተፍ ዐንከ እንደ መሰለቅ ነው ።
ቈረጠጠ)፡ አንቈራጠጠ፡ አላሳርፍ አለ፡ አንጐራደደ ።
ቈረጠጥ - ቈርጣጣ፡ የተንቈራጠጠ (ጐረደድ ጐርዳዳ ") ።
ቈረጣ፡ የመቍረጥ ሥራ (አገዳ ቈረጣ ዕንጨት ቈረጣ ጠጕር ቈረጣ ወይን ቈረጣ እንዲሉ ") ("(ሚክ. ፯፥ ፩)") ።
ቈረጣጠመ፡ ዐኛኘከ በላላ፡ ዐማመመ ።
ቈረጪ፡ ዐጠረ ዐጢር ኾነ ።
ቈረፀ (ቈሪፅ - ቈረፀ)፡ ቈረጠ ሸለተ አሳጠረ ።
ቈረፈ፡ ቈፈረ ማሰ ከፈለ ተነተነ ።
ቈረፈ፡ ጨረፈ ለኰፈ፡ መለሰ ቀለበሰ ።
ቈረፈደ፡ ደረቀ ሻከረ ልስላሴ ዐጣ (ዳባው ቍርበቱ ") ።
ቈረፈድ - ቈርፋዳ፡ የቈረፈደ/የሚቈረፍድ (ደረቅ ሻካራ ቈዳ ") ።
ቈረፈፈ)፡ ቈረቈዘ ።
ቈረፈፈ)፡ አንቈረፈፈ፡ ቈፈነነ (የ እጅን ጣት ቈለፈ ወበጠ ") ።
ቈሪ (ቈራሒ - ቀራዒ)፡ የቈራ/የሚ ቈራ (በጪ ተኳሽ ቀቢ ነቃሽ ቈራሚ ") ።
ቈሪት፡ የእንስት በግ ስም ።
ቈሪፍ፡ ዝኒ ከማሁ (ዦሮ ትልቅ ") ።
ቈራ - ቍር ።
ቈራ (ቀርሐ)፡ ቦቀረ ላጩ ነጩ ።
ቈራ (ቈርሐ - ቀርዐ - ኰርዐ)፡ በጣ ፈቃ ጋረጠ፡ ተኰሰ ነቀሰ፡ ቀባ ምልክት አደረገ፡ መታ ቈረመ ።"ስም ጠርቶ ራስ ቈርቶ" እንዲሉ ።"ቈርሐ" ትግሪኛ ነው ።
ቈራሚ፡ የቈረመ፡ የሚቈርም፡ መቺ፡ ኰርኳሚ ።
ቈራሳ፡ ገማሳ ።
ቈራረሰ፡ ፈታተተ ገማመሰ ከፋፈለ ።
ቈራረጠ፡ ጐራረደ ጐማመደ ("(፪ዜና. ፴፬፥ ፯)") ።
ቈራሪ፡ የቈረረ/የሚቈርር (ደራቢ አነባባሪ ") ።
ቈራሽ (ሾች)፡ የቈረሰ/የሚቈርስ (ፈ ታች ") ።
ቈራቢ (ዎች)፡ የቈረበ/የሚቈርብ (ቀዳሽ ሠላሽ ") ። በቍርባን የተወሰነ ምእመን ።
ቈራብት፡ ቈርበቶች ማሶች ።
ቈራን፡ ለኰፈን፡ አስተውል።
ቈራጣ (ጦች)፡ አካለ ጐደሎ ። "እግረ ቈራጣ ዥራተ ቈራጣ" እንዲሉ ።
ቈራጣ፡ የደሴት ስም (በጣና ውስጥ ያለ ደሴታዊ አገር ") ። ባጠገቡ ካለው የብስ ባሕር የቈረጠው የለየው ማለት ነው ።
ቈራጤ፡ የቈራጣ (ቈራጣዊ ") ። "የኔ ቈራጣ"፡ ሥሥ ልብስ በቀላል የሚቀደድ ።
ቈራጥ (ጦች)፡ ሐሳቡን ባንድ ነገር ላይ ያደረገ የማያወላውል (በሞቱ የቈረጠ ጐበዝ ") ("(ምሳ. ፭፥ ፱)") ።"ድኻ ቈራጥ ነው" እንዲሉ ።
ቈራጥ ወለቴ፡ በቈራጣ ውስጥ የነበረች ቅድስት ("የቈራጣ ወለቴ ") ።
ቈራጥ፡ የተቈረጠ ።
ቈራጥነት፡ ቈራጥ መኾን ።
ቈራጭ፡ "እጅና እግርን ወይም ዐንገትን" ።
ቈራጭ (ጮች)፡ የቈረጠ/የሚቈርጥ (ጐራጅ ጐማጅ ጨራሽ ") ። "እንጥል ምንጭር ነገር ዕንጨት ቀፎ ቀባ ቈራጭ" እንዲሉ ።
ቈራጭ፡ ባለወግ ሰያፊ ገራፊ ሰቃይ ገዳይ ። በግእዝ "መስተራትዕ" ይባላል ።
ቈራጭ፡ ዋና የበላይ ጠቅላይ ሹም ራስ ደጃዝማች (ከበታቹ ያሉ ብዙዎች አገረ ገዢዎች የፈረዱትን ፍርድ የሚልጥ የሚሽር የሚለውጥ የሚገለብጥ የሚያጸድቅ ") ።
ቈራጭ ፈላጭ፡ የወንጀለኛን እጅ እግር የሚቈርጥ ንጉሥ (ከራስ እስከ ፈጋራ መኻል ለመኻል ሰውን የሚፈልጥ አረመኔ ") ።
ቈራጭነት፡ ቈራጭ መኾን (የበላይነት ") ።
ቈራፋ፡ ዦሮው የረዘመና የተቀለበሰ ሰው ።
ቈሬ፡ የሰው ስም ።
ቈሬ፡ የቤት ዕቃ ስም (በጣባ በወጭት በሳሕን አምሳል የታነጸ ዕቃ ") ። ዘሩ ቈረ ቈረ ይመስላል ። "ገበቴን" እይ ።
ቈርሪቋ፡ የቈረቈረ/የሚቈረቍር (መሥ ራች ጐርባጭ ወገ ደፋኝ ") ።
ቈርቍር፡ በሺ ሸንቋሪ ።"ግንደ ቈርቍር" እንዲሉ ።"ቈርቍር የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ ሲኾን በቅጽልነትመፈታቱን" አስተውል ።
ቈርቈሮ፡ ፈረንጆች ብረትነት ያለውን ደንጊያ አቅልጠው የሠሩት ብረትማ (የቤት ክዳን ቦይና ሸንተረር ያለው ") ።"በምስማር እየተ ቈረቈረ ስለሚከደን ቈርቈሮ ተባለ" ("(ዘኍ. ፴፩፥ ፳፪ ። ኢሳ. ፩፥ ፳፭)") ። በግእዝ "ናእክ" ይባላል ።
ቈርቋዛ፡ የቈረቈዘ/የማያድግ (ዐጪር ልጅ ጥጃ ") ።
ቈርበተ ሐሊብ፡ የወተት ስልባቦት (ለጋ ቅቤ የንቍላል አስኳል የሚመስል ብጫ የሰደፍ ዶቃ ወይም መቍጠሪያ ባለመዐዛ ") ። በግእዝ "አርማስቆስ" ይባላል ። "ቀሀረማንን" እይ ። ቈርበት ካሪም፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቈርበተ ሞኝ፡ ሲያዩት አላዋቂ የሚ መስል ሰው ።
ቈርበተ ዐሊም - ቈርበት (ርበት)፡ የጸሎት ዕቃ መቍጠሪያ ። ዐሊም የተማረ ማለት ነው ።
ቈርበት (ኵርበት)፡ የተ ለፋ ቈዳ (ለሰው መኝታ ምንጣፍ የሚኾን ") ። ነት ተንቤን ማስ ። ሲበዛ "ቈርበቶች" "ቍርበቶች" ያሠኛል ።
ቈርበት ነክ፡ ሥር የሌለው ነገር ።
ቈርበት፡ የሰው ገላ ቈዳ ("(ዘሌ. ፲፫፥ ፪ - ፫ - ፬)") ።
ቈርባ ቈርባ አለ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቈርነናታም፡ እንቍራሪትኛ የሚጮኸ ።
ቈርነናት (ቈርነናዓት)፡ ጓጕንቸር እንቍራሪት ጯኺ ነወሬ ።
ቈርኬ፡ (ኦሮ)፡ ቀጪኔ።
ቈርኬ፡ የቢራ፡ መክደኛ።
ቈርዛዛ፡ የተንቈረዘዘ (እንቍርዝ ") ።
ቈርጠጥ ቈርጠጥ አለ፡ ጐርደድ ጐርደድ አለ ።
ቈርጣሚ፡ የቈረጠመ/የሚቈረጥም (ጐርዳሚ ") ።
ቈርጦ ቀጥል፡ ዐባይ ጐመድ ቀጣፊ ኹለት ምላስ ።
ቈርጦ፡ በጥሶ ጐምዶ ።
ቈርጦ ኼደ፡ ሐሳቡን ከዓለም ለይቶ ወደ መንፈሳዊ ሥራ ዐለፈ ነጐደ ። "ደበረ" ብለኸ "ተድበረበረን" አስተውል ።
ቈሸሸ፡ አደፈ ተበከለ ተኵለፈለፈ (ትቢያ ለበሰ ") ።"በየቀኑ የማይጠረግ ቤት ይቈሽ ሻል" ።
ቈሸበ (ትግ ሐባ ቈሽበ - ዝግተኛ ኾነ)፡ ጀጀበ ጀጀረ፡ መብል ከለከለ ።
ቈሸበለ)፡ አንቈሻበለ፡ ለመነ ተለማ መጠ አባበለ አቀማጠለ ።
ቈሸንዳ፡ የከሳ ሰው ("ወይም ከብት") ።
ቈሸዳም፡ ቈሸድ ያለው (ባለቈሸድ ") ።
ቈሸድ፡ የደረቀ እንጀራ ("ዘኬ") ።
ቈሻ፡ ርጥብ፡ የማሽላ እንቀት፡ የሐረርጌ ሴቶች አስቀድሞ በሙቀጫ ይወቅጡታል፡ ዳግመኛም ያልሙታል ይለነቅጡታል ።
ቈሻሻ፡ የቈሸሸ (እድፋም ጽዳት የሌለው ዐሣማ ") ።
ቈሻባ - ቍሽብ፡ የተቈሸበ (መብል የማ ይገፋ ") ።
ቈሽት (ቶች)፡ ሆድ ዕቃ (ከጨጓራ ጋራ ያለ ሥጋዊ ከረጢት የብጥብጥ ምግብ መታቈሪያ ") ። በግእዝ "ቈሥጢ" ይባላል ።
ቈሽት አንድድ፡ ሀኬተኛ ልግመኛ እከየኛ ሰው ።
ቈቀረ፡ አነሰ ጠቀነ ዐጪር ኾነ ።
ቈቀር (ሮች)፡ ታናሽ የዕጣን ቅንጣት ልዝብ ጣፋጭ ። "አንኳርን" እይ ።
ቈበራም፡ ቈበር ያለው/ባለቈበር ። ቈበረ፡ ቈበሩን ደፈቀ (ካፉ አወጣ አፈሰሰ ") ።
ቈበር፡ ቆበር (ካፍ የሚወጣ ብዙም ራቅ ዐረፋ ") ።
ቈበቈበ (ጐበጐበ - ኰበኰበ)፡ ዐተረ ጐረበ ቈረበ ቍብ ቍብ አለ ።
ቈበበ (ጐበበ)፡ ገላውን ሰብስቦ እንደ ቈቦ እንደ ጕብ በቀላል ተቀመጠ ። "ሸረቈጠን" ተመልከት ።
ቈባ፡ ቀበደደ ።
ቈባ፡ ተናጋሪ ሴት ተናጣቢ (አፈኛ ምላሰኛ ") ።
ቈባባ፡ የቈበበ ጐባባ ።
ቈብቋባ፡ የቈበቈሰ/የሚቈበቍብ (ጕርብ ቍርብጭ ") ።
ቈቦ፡ ባንኮበር በኩል ያለ አገር ። "ሐር ዐምባና ቈቦ" እንዲሉ ። የቈባና የቈቦ ዘር ቈ በበ ነው።
ቈቦ፡ የዛፍ ስም (አነስተኛ ወተታም ዕንጨት ") ። ቅል በሚያካክል የፍሬው መሸፈኛ ውስጥ ነጭ ሐር የሚመስል ባዘቶ አለው፡ ወተቱም ለመጋኛ መድኀኒት ይኾናል። ዳግመኛም "ጦቢያ"፡ ሦስተኛም "ቅንቦ" ይባላል ። ጋሳም ጕሎን ቈቦ ይለዋል ።
ቈተመ፡ ነቃ ተጋ ።
ቈተመ፡ ጓጓ ሰለፈ (አንድ ነገር ለማ ግኘትና ለማድረግ ") ።
ቈተቸ (ቀተወ)፡ ውርርድ አደረገ ።
ቈታሚ፡ የቈተመ/የሚቈትም (ሰላፍ ") ።
ቈቻ፡ ብርታት ጥንካሬ ። ዘሩ "ቈተቸ" ነው ።
ቈቻ ዋለ፡ ከቀትር በፊት ካንድ በሬ ከቀትር በኋላ ከሌላ በሬ ጋራ ተጠመደ ዐረሰ ("ከኹለት ተወዳደረ ") ።
ቈነ፡ ለቀመ አጥመዘመዘ ገደለ ሰው የው ።
ቈነሰ፡ በሰበሰ ገማ ጠነባ ።
ቈነሠ፡ ገማ ። ቈነሰ ።
ቈነቈነ (ቈንቈነ)፡ ነቀዘ ጠነጠነ ተላ ። "ቀነቀነን" እይ ።
ቈነቈነ፡ ሠሠተ ቈጠበ ።
ቈነቈነ፡ ከተፈ ሸከፈ ተነተነ ። "ቈነነን" እይ፡ የዚህ ሥር ነው፡ "ቀነቀነን" አስተውል ።
ቈነነ፡ ለካ መጠነ ሰፈረ ድርጎን ።
ቈነነ፡ ቀስ አደረገ በቀስታ አስኬደ ጀነነ አኰራ አጓደደ አቋፈ ።
ቈነነ፡ ታታ ጐነጐነ ሸረበ ሠራ ጭ ራን የራስ ጠጕርን፡ ቋድ አስመሰለ ። "ጐነነን" ተመልከት ።
ቈነን ቈነን፡ ቶሎ ቶሎ አለመኼድ ።
ቈነዠ (ቍንዝዕ - ቈንዳላ)፡ ኦሞላ አማረ ተዋበ፡ የሴት ልጅ ገላ ። በቈነዠ ፈንታ "ቈነጀ" እየተባለ ይጻፋልና ስሕተት ነው ።
ቈነዠች፡ ዐቅመ ሔዋን አደረሰች፡ ጠ ጕሯ እትከሻዋ ላይ ወረደ ።
ቈነዣዥት፡ ዝኒ ከማሁ (የሚያማምሩ ልጃገረዶች ") ("(ዓሞ. ፰፥ ፲፫ ። ፩ጢሞ. ፭፥ ፪)") ። በግ እዝ "ደናግል" ይባላሉ ።
ቈነደለ፡ ሽሩባ ሠራ ጐነጐነ ቈነነ ዐ ተቈነደለ፡ ተጐነጐነ ተቈነነ ።
ቈነደደ (ነደደ)፡ በቋንዶ ገረፈ ለቈ ጠጠ ።
ቈነደደ፡ አደረቀ አሻከረ አሳጠረ ቁመ ትን ።
ቈነዳ (ቈንደየ)፡ ዘለለ ረገደ ።
ቈነጠ (ቀንጠወ)፡ ሆዱ ተነፋ ቍን ጣናም ኾነ ።
ቈነጠ፡ ጐነጠ ነካ በንክሻ ።
ቈነጠለ፡ ቈነጸለ ።
ቈነጠረ፡ ነካ በሦስት ጣት ያዘ፡ ጥ ቂት አነሣ ወሰደ ። "ቈጠበን" ተመልከት ።
ቈነጠረ፡ ወጋ ነከሰ ጫረ ዶሮ ሰውን ።
ቈነጠነ (ቀንጠወ)፡ ነፋ ከረበ ሆድን ።
ቈነጠጠ፡ ለመዘገ ቀጣ ልጅን ።
ቈነጠጠ፡ ረገጠ ርካብን በእግር አውራ ጣት ።
ቈነጠጠ፡ ሸፈነ ጠቀለለ ማገረ ጣራን በግምጃ በሐር ።
ቈነጠጠ፡ ነከሰ በላ ትንኝ ጕንዳን ገላን ።
ቈነጠጠ፡ አጣበቀ አጣብቆ ያዘ እሾ ኸን ምስማርን በወረንጦ፡ በጕጠት ትንባኾን በጣት ።
ቈነጣጠለ - ቈነጻጸለ ። አስቈነጠለ - አስቈነጸለ ።
ቈነጣጠረ፡ ከዚያም ከዚያም ላመል ላመል ወሳሰዶ ።
ቈነጥ፡ ትንኝ ዝንብ ባፉ የሚጐንጥ ። ቈነጤ፡ የቈነጥ ዐይነት (የሐሜት ስም ") ።
ቈነጩ፡ ቍንጫ ኾነ፡ ቍንጫ አፈራ
ቈነጩ፡ ነቀሰ አሳደገ ቍንጮን ።
ቈነጯ፡ ዐረምን ውራን ጐለጐለ ነቀለ ።
ቈነጸለ፡ ቈረጠ ገነጠለ ጥራዝን ።
ቈነጸለ፡ ኰሰተረ ሰበረ አለማ መብራ ትን ። "ተረከሰን" እይ ።
ቈነጻጸለ፡ ሰባበረ ከሰልን ።
ቈነጻጸለ፡ ቈራረጠ ገነጣጠለ ።
ቈናኝ (ኞች)፡ የቈነነ/የሚቈንን (ጐን ጓኝ ሸራቢ ጠጕር ሠሪ ") ።
ቈንቋና (ትግ ቈንቋን)፡ ዝኒ ከ ማሁ (ቈጣቢ ሥሥታም ") ።
ቈንቋኔ፡ የቈንቋና ወገን (እንደ ነቀዝ በቀስታ ሰውነትን የሚጐዳ "ቅኔ ቈንቋኔ" እንዲሉ ") ።
ቈንቋኝ፡ የቈነቈነ/የሚቈነቍን (ተን ታኝ ") ።
ቈንዢት፡ የሴት ስም ።
ቈንዦ፡ የቈነዠች ያማረች የተዋበች ውብ ደማም መልከ መልካም ያ፲፭ ዓመት ልጃገረድ፡ ደረተ ሳንቃ ዐንገተ መቃ አፍ ንጫ ስንደዶ ጥርሰ በረዶ ። (ተረት)፡ "የስንዴ ዐራራ የቈንዦ መራራ" ። በልማድም ወንድ፡ ቈንዦ ይባላል ። ቈንዦ የሚነገረው ለ ልጃገረድና ለምታምር ሴት ሲኾን፡ ጣሊያን ገዝቶ ከኼደ፡ "ቈንዦ ቤት ቈንዦ መብል ቈንዦ ልብስ" እየተባለ በአዲስ አበባ ይነገራል። ሴትን ከወንድ ለመለየት ።
ቈንዦነት፡ ዝኒ ከማሁ ("(ኤር. ፫፥ ፬)") ።
ቈንዦዋ - ቈንዦዪቱ፡ ያች ቈንዦ ("(ኤር. ፲፬፥ ፲፯)") ።
ቈንዦዎች፡ የሚያምሩ ሴቶች ።
ቈንደል፡ የማሽላ ስም፡ መልኩ ብጫ ዋሜራው ረዥም የኾነ ማሽላ ኮልኝ ። (ግጥም)፡ "ከማሽላው ቈንደል ከጤፉ ጐራዴ ረ ለማን ኛው ታደላለኸ ሆዴ" ።
ቈንዳ ቈንዳ አለ፡ መር መር አለ ።
ቈንዳላ፡ ጕተና ጐፈሬ ረፍረፎ ጠጕር ("(ማሕ. ፭፥ ፪፡ ፲፩ ። ኢሳ. ፵፯፥ ፪)") ። በጋልኛ ግን ወጣት ልጅ ማለት ነው ።
ቈንዳዳ፡ ደረቅ ሻካራ ያጠረ ጠጕር ።
ቈንዳጅ፡ የቈነደደ/የሚቈነድድ (ገራፊ ") ።
ቈንጣሪ (ዎች)፡ የቈነጠረ/የሚቈነ ጥር (አሳንሶ የሚወስድ የሚሰጥ ") ።
ቈንጣይ - ቈንጻይ ።
ቈንጣጭ፡ የቈነጠጠ/የሚቈነጥጥ (የሚ ነክስ ነካሽ ረጋጭ ") ("(ዘዳ. ፯፥ ፳)") ።
ቈንጥር (ስም)፡ እሾኸ ቈላፋ የበረሓ ዕንጨት ። ሲበዛ "ቈንጥሮች" ይላል ።
ቈንጥር (ትእዛዝ አንቀጽ)፡ ውጋ ንከስ ።
ቈንጪ፡ የቈነጨ/የሚቈነጭ (ለቃሚ ጐልጓይ ") ።
ቈንጻይ፡ የቈነጸለ/የሚቈነጽል (ኰስታሪ ") ።
ቈኘተ፡ ታታ አሠባጠረ አዋሰበ ።
ቈወጪ፡ ቍጫጭ አፈራ ።
ቈዘመ፡ ዐዘነ ተከዘ አለቀሰ (አሞሸ ዋይ አለ ") ("(ሕዝ. ፳፩፥ ፮ - ፯፡ ማር. ፯፥ ፴፬፡ ፪ቆሮ. ፭፥ ፪ - ፬)") ።
ቈዘረ፡ ጐኘረ ነፋ ጐሰረ ። "ቈረዘን"
ቈዛሚ (ሞች)፡ የቈዘመ/የሚቈዝም (ዐዛኝ አልቃሽ ") ።
ቈዝሞ፡ ዐዝኖ ተክዞ ("(ማር. ፰፥ ፲፪)") ።
ቈየ (ዕብ. ቃዌህ)፡ ባንድ ስፍራ ጥቂት ወይም ብዙ ጊዜ ተቀመጠ ኖረ ነበረ ዘገየ ("(ዘፍ. ፯፥ ፲፪)") ። "የቈየ ሰው የዘገየ መጨረሻውን ያየ" (አዝማሪ) ።
ቈየ፡ ቆመ ጠበቀ ሰውን ።
ቈየት አለ፡ ዘግየት አለ ።
ቈየት፡ ዘግየት ።
ቈዪ (ቀላዊ)፡ የቈላ/የሚቈላ ። ያለ ፈው አንቀጽ፡ የሚመጣው ስም መኾኑን አስተውል ።
ቈይ፡ አትኺድ፡ እዚሁ ተቀመጥ፡ ሥራን ነገርን ተው ። (ተረት)፡ "ኣላቻ ጋብቻ ቈይ ብቻ ቈይ ብቻ" ።
ቈይታ፡ የባለሥልጣኖች ብቻ ምክር፡ የምስጢር ንግግር ። በፈረንጅኛ "ሲያንስ" ይባ ላል ።
ቈይታ ያዘ፡ ንጉሡከባለሎቹ ጋራ
ቈደሰ (ቀወመ)፡ ቈደሰ (ቀደሰ)፡ ቈረሰ ከፈለ (ጥቂት ጥቂት በላ ዛቲን መክፈልትን ከቅዳሴ በኋላ ") ።
ቈዳ፡ የሥጋ ኹሉ ልብስ መሸፈኛ (ርጥቡም ደረቁም ቈዳ ይባላል ") ። "የበሬ የበግ የፍየል ያጋዘን የሡሥ የምዳቋ ቈዳ" እንዲሉ። (ግጥም)፡ "ባህያ ቈዳ የተሠራ ቤት ብትንትን ይላል ዥብ የጮኸ ለት" ። "አንጋሬንና ሌጦን" እይ ።
ቈዳ፡ ፍሬ የማይሰጥ መሬት ።
ቈጊ፡ የቈጋ/የሚቈጋ (ገራፊ ") ።
ቈጋ፡ ገረፈ (በጅራፍ መታ ቈነደደ ") ። "ጋ ጋን" ተመልከት ።
ቈጠሰ፡ ከፈለ ለየ ርስትን ።
ቈጠረ (ቈጸረ)፡ አንድ ኹለት ሦስት አለ፡ ዐሰበ አሰላ፡ ፊደል ተማረ ።
ቈጠረ፡ ርስቱን ከብቱን በወንድ ዐማቱና በጨዋ ፊት ዘረዘረ ነገረ አስረዳ አስታወቀ ።
ቈጠረ፡ ቅኔ አዘጋጀ፡ ቤት መታ ። (ግጥም)፡ "ሰዋስው ጨዋታ ዐማርኛ ቅኔ፡ ቈጥረኸ ስደድልኝ እፈታለኹ እኔ" ።
ቈጠራ (ቈጸራ)፡ የመቍጠር ሥራ ።
ቈጠቈጠ (ቈጠጠ ቀጠጠ)፡ እሾኽ ቍጥቋጦ ቈረጠ መለመለ ("(ዳን. ፬፥ ፲፬፡ ፳፫)") ። "ኰተኰተን" ተመልከት ።
ቈጠቈጠ፡ ለበለበ ፈጀ አቃጠለ አን
ቈጠቈጠ፡ ቈጠበ ቈነቈነ ቈነጠረ ።
ቈጠቈጥ - ቈጥቋጣ፡ የተንቈጣቈጠ/የሚንቈጣቈጥ (ቈንቋና ቈጣቢ ") ።
ቈጠቈጭ - ቈጭቋ፡ የተንቈጨ ቈ ስብርብር እንክትክት ።
ቈጠበ፡ በልክ በመጠን በስሌት በሒሳብ በቍጥቍጥ ገንዘብ አወጣ፡ ወጪን ቀ ነሰ አሳነሰ፡ ተቀማጭን አበዛ አበረከተ፡ በየጊዜው ገንዘብ አስቀመጠ ያዘ ጨበጠ አ ተረፈ አካበተ ።
ቈጠጠ (ቈጢጥ ቈጠጠ)፡ የወተት ኵስ ኰሳ ዐራ ። "ቈጠቈጠን" እይ ።
ቈጠጯ፡ ቍጭ አለ ። "ጐቸን" እይ ።
ቈጣ - ቈጥዐ)፡ አስቈጣ አስገሠጸ አዘለፈ አስገላመጠ ።
ቈጣ አለ፡ ጥቂት ሖምጠጥ አለ ።
ቈጣስር (ቈጥ አስር አሰር)፡ የጋ ብቻ ስም (ውሉ በቈጥ የታሰረ የተፈጸመ ጋብቻ ") ። "እሚስቱ አባት እናት ቤት ኼዶ የሚኖር ወንድ በታዛይ ከሚስቱ ጋራ በቈጥ ስለሚተኛ ጋብቻቸው ቈጣስር ተባለ፡ ይኸውም ማተብንና ቀለበትን ቃልን ያስተርጕ ማል" ።
ቈጣሪ (ሮች)፡ የቈጠረ/የሚቈጥር (ተማሪ ዘኬ ቈጣሪ ") እንዲሉ። "ኮከብን" እይ ።
ቈጣሪ፡ የተበራውን ኤሌትሪክ ልክ የተቀዳውን ውሃ መጠን የሚነግር መኪና በውስጡ የሚዞር ቍጥር ያለበት ።
ቈጣቈጠ፡ ቈራረጠ/መላመለ ።
ቈጣቢ (ዎች)፡ የቈጠበ/የሚቈጥብ (አስቀማጭ ጨባጭ አካባች ") ።
ቈጣጠረ፡ መላልሶ ቈጠረ ።
ቈጣጭ፡ የቈጠጠ/የሚቈጥጥ (ጥጃ ግልገል ሕፃን ") ።
ቈጥ (ቀጣ)፡ አራት እግሩ እመሬት የተተከለ የንጨት ዐልጋ (ሲበዛ ቈጦች ይላል ") ።
ቈጥ፡ የንጨቱን ትክክል ኹኖ መቈ ረጥ ያሳያል ። (ተረት)፡ "የቈጡን ኣወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" ።
ቈጥቋጭ፡ የቈጠቈጠ/የሚቈጠቈጥ (ለብ ላቢ ቈራጭ መልማይ ") ።
ቈጨቈጪ፡ ጣትን ከጣት ኣዋሰበ (አ ስታገለ አስተናነቀ ") ።
ቈጨበረ፡ ብስጩ ኾነ ።
ቈጨበር - ቈጭባራ (ሮች)፡ ቍጡ ብስጩ ዐመለ ቢስ ።
ቈጨጨ፡ አነሰ ቍርንጫጭ ኾነ ። "ጐጨጨን" አስተውል ።
ቈጫ (ኦሮ)፡ ዔሌ ድንጋይ ልብሱ ።
ቈጫ፡ ያገር ስም (በወላሞ ክፍል ያለ ወረዳ ማለፊያ - ቡልኮ የሚሠራበት ") ።
ቈጮ (ወላሞ)፡ እንሰት ።
ቈፈረ (ቀፈረ)፡ ማስ ጫረ መነ ቀረ ኳተ ኰተኰተ ጐደፈረ አጐደጐደ ("(ዘፍ. ፳፯፥ ፲፱ ። መዝ. ፯፥ ፲፭)") ። (ተረት)፡ "ሲቀላውጡ ዐይን አፍጦ፡ ሲቈፍሩ አንፈራጦ" ።
ቈፈር፡ ማስ ማር ።
ቈፈር ቈፈር አደረገ፡ ማስ ማስ ሣር ጫር አደረገ ።
ቈፈቈፈ)፡ አንቈፈቈፈ፡ አስጮኸ አስጠራ ።
ቈፈቈፍ - ቈፍቋፋ፡ የተንቈፈቈፈ/የሚንቈፈቈፍ (ጯኺ ጠሪ ዶሮ፡ ንፉግ ሥሥታም ቈጥቋጣ ሰው ") ።
ቈፈነ፡ በረደ ቀዘቀዘ ።
ቈፈነነ፡ ዐጠፈ ጨበጠ አደረቀ ጣትን ። "ጐፈነነን" ተመልከት ።
ቈፈነን - ቈፍናና፡ የተቈፈነነ/የታጠፈ የተጨበጠ ።
ቈፈናም፡ ቈፈን የያዘው (ባለቈፈን ጣቱ ሊይዝና ሊጨብጥ የማይችል ") ።
ቈፈን፡ ብርድ ቅዝቃዜ ።
ቈፈጠነ፡ ጕድለት አልባ ኾነ ።
ቈፋሪ (ሮች)፡ የቈፈረ/የሚቈፍር (ማሽ ዶመኛ ") ።
ቈፋፈረ፡ ጫጫረ መነቃቀረ ።
ቈፍና፡ በመርሐ ቤቴ ክፍል ያለ አገር ብርድ ያለበት ።
ቈፍና፡ የሩቅ ሴት ቦዝ አንቀጽ ነው ።
ቈፍጣና (ኖች)፡ ዝግጁ ድርጁ ስንዱ (በሞያ በሀብት በኑሮ በጌጥ ") ።
ቅለዳ፡ ትረባ ።
ቅሉ፡ ንኡስ አገባብ፡ ስንኳ ("(ማቴ. ፳፭፥ ፳፱)") ።
ቅሉ፡ ያ ቅል፡ የርሱ ቅል።
ቅሉ፡ ግን ። "እሱ እሷ አንተ እኔ ቅሉ" ("(፪ሳሙ. ፲፰፥ ፲፫)") ።
ቅላት (ቂሐት)፡ ቀይነት/ደም መም ሰል ("(ምሳ. ፳፫፥ ፳፱)") ።
ቅላጤ፡ ተጨማሪ ዜማ ከዋናው የተለየ ።
ቅሌ (ኦሮ)፡ ጥንግ ዕሩር ።
ቅሌታም (ሞች)፡ ቀላል ሰው ባለቅ ሌት መንፈሰ ቀላል ።
ቅሌት፡ ያመል የጠባይ መቅለል ("(፪ቆሮ. ፩፥ ፲፯)") ። በግእዝ "ቅለት" ይባላል ። "ነደደ" ብለኸ ንዴትን አስተውል።
ቅሌት—መቅለል—ቀለለ ።
ቅል (ሎች)፡ ሐረግማ ቅጠል በቅጥር ውስጥና በዱር የሚበቅል ("(ዮና. ፬፥ ፮፡ ፱)") ። በትግሪኛ "ቅልዕ" ይባላል ።
ቅል፡ ሞላላ የውሃ መቅጃ አንኮላ ሸክና ዐቦሬ ።
ቅል ባገኝ፡ ቅልን ተስፋ አድርጎ የሚዘምት ሰው ።
ቅል ብቻ፡ ራስ ።
ቅል ዐንገት፡ ቀጪን የቅል ዐንገት የደጋን መንዘሪያ የምትኾን ።
ቅል፡ ክብ እንክብል ቋንጅል መንቀል ። (ተረት)፡ "አሞራውም በረረ፡ ቅሉም ተሰበረ" ።
ቅልምጫ፡ ያፍ ድምፅ በምግብ ጊዜ ።
ቅልሞሽ—ቅልቦሽ—ቀለበ ።
ቅልሳት፡ ጕብጠት ።
ቅልስ፡ የተቀለሰ (ምልስ ቍልፍ ዐንገት ጐዦ ከዘራ ገና ጥንቅሽ ሙጭ ") ።
ቅልስልስ አለ፡ ተቅለሰለሰ ።
ቅልስልስ፡ የተቅለሰለሰ (ደካማ ") ።
ቅልሽልሽ አለው፡ ሽቅብ ሽቅብ አለው፡ በሽ አለው ።
ቅልሽልሽ፡ የተቅለሸለሸ (ጥውልው ") ።
ቅልሽልሽታ፡ የሆድ እውክታ ።
ቅልቅል አለ፡ ቅዥቅዥ አለ፡ ተንቀለ ቀለ ።
ቅልበሳ፡ ዐጠፋ ሽንቀራ ቅነፋ ።
ቅልብ (ቦች)፡ የተቀለበ/የተመገበ/ የበላ ሙክት ገች ድልብ ።
ቅልብ፡ የተያዘ የተጨበጠ ።
ቅልብልብነት፡ ስግብግብነት ።
ቅልብሳት፡ ዕጥፋት ቅንፋት፡ የሱሪ የጥብቆ የበርኖስ የለምድ የዳባ ፍና ጫፍ፡ የዝናር ዳርና ዳር እየተቀለበሰ የተሰፋ ።
ቅልብስ፡ የተቀለበሰ (ቅንፍ ሽንቅር ከንፈር ልብስ ") ።
ቅልብሽ አለው፡ ቅልሽልሽ አለው ።
ቅልብሽ፡ የተመለሰ/የተገለበጠ (ወደ ላይ የወጣ የሆድ ውስጥ ምግብ ") ።
ቅልብጭ አለ፡ ቅልጥፍ አለ ።
ቅልውጥ፡ የማድ ክጀላ ።
ቅልዝ አለ፡ ክችል አለ ።
ቅልዝ፡ የቀለዘ ዕንጨት በጋ ተክረ ምት ያለፈበት
ቅልጠፋ፡ ፍጥነት ክር ባጪር ።
ቅልጣቅልጥ (ቅልጥ አቅልጥ)፡ የቅልጥ ቅልጥ የምት ምት በሰንበር ላይ ሰንበር ያረፈበት ። "የዝንጀሮ ቅልጣቅልጥ" እንዲሉ።
ቅልጣን፡ ምቾት ድሎት ከልክ ያለፈ ሀብት ። መሬት ውሃ ሲያይልበት፡ ሠም ቅባት ሙቀት ሲበዛበት እንዲቀልጥ፡ ቅልጣንም ከባለቤቱ ዐልፎ ለሌላ መትረፉን ያሳያል ("(ዘዳ. ፳፰፥ ፶፬፡ ፶፮፡ ኤር. ፲፫፥ ፳፯)") ።
ቅልጣን—ምቾት ። ቀለጠ (ቀለጠፈ)፡ (ቀለጠ ለጠፈ)፡ ፈጠነ ተከወነ ቶሎ ኾነ ተደረገ ሥራው ነገሩ ።
ቅልጥ አለ፡ ፍስስ አለ፡ ፈጽሞ ሠባ ደመቀ ።
ቅልጥ፡ የቀለጠ የ የፈሰሰ የፈ ረሰ፡ የተመታ ።
ቅልጥልጥ አለ፡ ተቅለጠለጠ ።
ቅልጥልጥ፡ የተቅለጠለጠ ወዛም ።
ቅልጥማም (ሞች)፡ ቅልጥመረዥም ቋቲሮ ሰው አሞራ ።
ቅልጥም (ሞች)፡ ከቋንዣ እስከ ቍርጭምጭሚት ያለ የእግር ክፍል፡ መለልታ አገዳ ።
ቅልጥም ሰባሪ፡ ቅልጥምን ወደ ሰ ማይ አውጥቶ እየለቀቀ አለት ላይ የሚሰብርና ቅባቱን የሚጠጣ አሞራ ።ዠርባው ጥ ቍር ኾኖ ቅላትና ንጣት ያለው ባና መሳይ ነው ።በስተጕያውና በስተጭኑ ነጭ ሱሪ የታ ጠቀ ይመስላል ።
ቅልጥም አለ፡ ስብር አለ፡ ተቀለጠመ ።
ቅልጥም አደረገ፡ ስብር አደረገ፡ ቀለ
ቅልጥም፡ ከብብት እስከ ኵርማ ከክርን እስከ አንባር ያ ያለው ጡንቻ ክንድ ። ለከብትም የፊት እግር እንደዚሁ ይነገራል ።
ቅልጥም፡ የቅልጥም ቅባት
ቅልጥም፡ የተቀለጠመ/የተሰበረ (ስብር ") ።
ቅልጥምጥም አለ፡ ስብርብር አለ፡ ተ ቀለጣጠመ ።
ቅልጥምጥም፡ የተቀለጣጠመ ስብርብር ።
ቅልጥጥ ቅልጥጥ አለ፡ ሽቅብ ሽቅብ ግራና ቀኝ ዝንጀርኛ አየ ።
ቅልጥጥ አለ፡ ግልጥ አለ፡ ተንቀ ለጠጠ ።
ቅልጥፍ፡ የቀለጠፈ/ፈጥኖ የኾነ/የተደ ረገ ።
ቅልጥፍና፡ ቀልጣፋነት ።
ቅልጥፍጥፍ አለ፡ ክውንውን አለ፡ ተ ቀለጣጠፈ ።
ቅልጥፍጥፍ፡ የተቀለጣጠፈ ክውንውን ።
ቅልጥፍጥፍታ፡ ቅልጥፍጥፍ ማለት ።
ቅሏ - ቅሊቱ፡ ያች ቅል ("(ዮና. ፬፥ ፮፡ ፯፡ ፲)") ።
ቅሏ፡ የርሷ ቅል።
ቅመመን፡ የቅመም ዱቄት፡ ን ምእላድ ነው ።
ቅመመን፡ ድብልቅ ውጥንቅጥ ። ፈረንጆች "ኮክቴል" ከሚሉት ጋራ ይሰማማል ።
ቅመማ፡ ስብሰባ ቅልቀላ ድብለቃ ምጠና ።
ቅመማም፡ ቅመም ያለው ባለቅመም ።
ቅመማቅመም፡ የቅመም ቅመም (ብዙ ዐይነት ቅመም ") ።
ቅመም (ሞች)፡ አብሽ ድንብላል ኰረሪማ ዝንጅብል ነጭ አዝሙድ ጥቍር አዝሙድ ሰናፍጭ ፌጦ ነጭ ሽንኵርት ቀይ ሽንኵርት በሶብላ ጐመን ዘር ።
ቅመራ፡ ቈጠራ ምደባ ከፈላ ።
ቅሚያ፡ ንጥቂያ ("(ኤር. ፶፩፥ ፲፫፡ ናሆ. ፪፥ ፲፪፡ ማቴ. ፳፫፥ ፳፭)") ።
ቅማላም (ሞች)፡ ቅማል ያለበት የበዛበት የሚንፋሰስበት ሰው ።
ቅማላም ኾነ፡ ቀመለ ።
ቅማል (ሎች)፡ ከሰው እንፋሎትና ላብ በልብስና በራስ ጠጕር ውስጥ የሚፈጠር ተባይ ነጭና ጥቍር ።
ቅማል ጅራም (ቅማንጅራም)፡ ቅማንጅር የሚታይበት ሰው ባለቅማንጅር ።
ቅማል ጅር (ቅማንጅር)፡ የቅማል ጓዝ፡ የቅንድብና የሽፋል፡ የጢም ቅጫም ።
ቅማሽ፡ ቢጀ ጕርሻ ("(ዮሐ. ፲፫፥ ፳፮)") ።
ቅማት - ቅማያት፡ የቅድም አያት አባትና እናት የሽማት ልጆች ።
ቅማት፡ ፬ኛ አያት—ቀደመ ።
ቅማንት (ከመ አንተ)፡ የነገድ ስም፡ በበጌምድር አውራጃ በከርከር በጭልጋ ያለ ሕዝብ ። "አንድ ቅማንት ዐደን ዐድኖ ከደን ሲወጣ አንድ . . . . አገኘውና መኑ አንተ አለና ቢጠይቀው፡ ከመ አንተ ብሎ ስለመለሰለት በዘመን ብዛት ከመ አንተ በማለት ፈንታ ነገዱ ቅማንት ተባለ" ይላሉ ። "ዐዋጅ የተሻለውን መንገድ ለመያዝ" የሚል መጽሐፍ ተመልከት፡ ዳግመኛም አለቃ ታየ የጻፉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ እይ ።
ቅማንቶች፡ የቅማንት ነገዶች ወገ
ቅማጫም፡ ተቅማጣም ።
ቅማጭ፡ ተቅማጥ ።
ቅምሖ (ቀምሕ ፍሬ)፡ ዕጢ የ ሥጋ ቅንጣት ።
ቅምሖ፡ ለግዳ ለቅዳ በስተውስጥ በጕረሮ ጫፍ ግራና ቀኝ የሚወጣ ዕብጠት ። ዐዋቂ በጊዜው ካልቧጠጠው ምግብና ምራቅ መዋጥ ይከለክላል፡ ዦሮ ግንድን እንደ ጦር ይወጋል፡ እጅግ ባበጠ ጊዜ የገባና የንኰይ ፍሬ ስለሚያክል ቅምሖ ተባለ ።ፈረንጆች "ቶንሲል" ይሉታል ።
ቅምም፡ የተቀመመ (ቅልቅል ድብልቅ ምጥን፡ ቅመም የገባበት ድልኸ ") ።
ቅምምጦሽ፡ የትከሻ ሸክም ፈረቃ ።
ቅምስ አደረገ፡ ልክፍ አደረገ ።
ቅምስ፡ የተቀመሰ ።
ቅምር፡ የተቀመረ የተቈጠረ (ክፍል ምድብ ") ። "ርባ ቅምር" እንዲሉ።
ቅምቀማ፡ ስፌት ዝምዘማ ።
ቅምቅማት (ቶች)፡ ዝምዝማት ("(ዘፀ. ፳፰፥ ፴፪)") ።
ቅምቅም አለ፡ ጥቂት ጥቂት ጣ
ቅምቅም፡ የተቀመቀመ (ዝምዝም ") ።
ቅምቡርስ—ትል፡ ቅንቡርስ ።
ቅምና—ቅል—(ቀመጠ) ። ቅማያት—፬ኛ አያት—ቀደመ ።
ቅምድምድ አለ፡ ተቅመደመደ ።
ቅምጠላ፡ የማጕደል ሥራ፡ ቅንጠሳ ።
ቅምጥ፡ ቂጥ መቀመጫ ። "ራድ ከቅምጥ ይፈነቅላል" አንዲሉ ።
ቅምጥ፡ ዐይናር፡ ሌሊት በንቅልፍ ጊዜ ካይን የሚወጣ እድፍ ።
ቅምጥ፡ ዕጦት ችግር ሥራን ትቶ ከመቀመጥ የሚመጣ ።
ቅምጥ፡ የተቀመጠ ። "ያተር ቅምጥ" እንዲሉ ።ጕልት ሽባ ።
ቅምጥሉ፡ ያ ቅምጥል ።
ቅምጥላ፡ የዕውቀት ቅሬታ (ተረፈ አእምሮ) ።
ቅምጥላው ጠፋ፡ አእምሮው ታጣ በስካር ምክንያት (ኅሊናውን ሳተ) ።
ቅምጥል (ሎች)፡ የተቀማጠለ (ች)፡
ቅምጥል አለ፡ ጕድል እንስ አለ ።
ቅምጥልነት፡ ቅምጥል መኾን፡ ድልድ
ቅምጥልጥል አለ፡ ተዘናፍሎ ተኛ ።
ቅምጥልጥል፡ የተቀመጣጠለ ።
ቅምጥሏ - ቅምጥሊቱ፡ ያች ቅምጥል ("(፩ጢሞ. ፭፥ ፮)") ።
ቅምጦሽ፡ የጨዋታ ስም፡ ልጆች አንዱ ባንዱ ትከሻ ላይ እየተቀመጡ የሚያደርጉት የኳስ ጨዋታ ።
ቅምጫና (ኖች)፡ ቅል ቋንጅል ። መ ንቀልን እይ ።
ቅሞ፡ ሖምጣጣ የቅሞ ፍሬ ተረር ።
ቅሞ፡ የዛፍ ስም፡ ፍሬው የሚቃም አነስተኛ ዕንጨት ።
ቅሰራ፡ ግተራ ።
ቅሳር፡ ሠረዝ ጭረት ።"ኹለቱን ነጥብ ዐቢይ ሠረዝ ንኡስ ሠረዝ የሚያሠኘው ቅሳር ነው" ።
ቅሳር፡ ቈሸሸ !
ቅስሙ ተሰበረ፡ ስውነቱ ተጐዳ ።
ቅሥም፡ ሰውነት ።
ቅስም፡ ካ፬ቱ ባሕርያት የተቀመመ ሰው ነት ኹናቴ ። በግእዝ "ቅሳሜ" ይባላል ።
ቅሥም፡ የተቀሠመ (ልቅም ስብስብ አ ውላ ") ።
ቅስስ፡ ቅዝዝ/ፍዝዝ ።
ቅስስ አለ፡ ፍዝዝ አለ ።
ቅስር ቅስር አለ፡ ግትር ግትር አለ ።
ቅስር አለ፡ ግትር አለ ።
ቅስቀሳ፡ ንቅነቃ ብርበራ ፍተሻ ።
ቅስቃሴ (ነሰሕሳሕ)፡ መቀስቀስ ።
ቅስቅስ አለ፡ ንቅንቅ አለ ።
ቅስቅስ፡ የተቀሰቀሰ/የተበረበረ (ንቅንቅ ብርብር ፍትሽ ") ።
ቅስት፡ የተቀሰተ (በበር በድልድይ ውስጥ የተበጀ የግንብ የሳንቃ ደጋን ቅሥፍ ") ።
ቅስና፡ ቄስነት ።
ቅሥፈታም፡ ባለቅሥፈት ።
ቅሥፈት፡ መቅሠፍት/መቀሠፍ (ባፍላ በልጅነት መሞት ") ። በግእዝ ግን ግርፋት ማለት ነው ።
ቅሥፍ፡ የተቀሠፈ (የጐበጠ ቅስት ") ።
ቅረብ፡ ለጥቅ ተጠጋ ።
ቅረብ፡ ንዳ ውሰድ ።
ቅሪላ፡ (ሎች)፡ ከርጥብ፡ የበሬ፡ ቈዳ፡ ጐኑ፡ በስንዝር፡ ልክ፡ ተቀዶ፡ የለፋ፡ ጠፍር፡ በያይነቱ፡ ቅራና፡ መጫኛ፡ ይኾናል ።
ቅሪት፡ የፀነሰች ሴት ደ ፀኗ የቀረ (እርጉዝ ") ።
ቅራሚ፡ የተቃረመ፡ ያጫጅ፡ ቅሬታ።
ቅራሞ፡ ዝኒ፡ ከማሁ ።
ቅራሪ፡ የመጠጥ ስም (ጠላ ባለቀ ጊዜ የሚጠጣ መናኛ መጠጥ ") ።"አንደኛ ኹለተኛ ቅራሪ" እንዲሉ ።
ቅራቅንቦ፡ እንቶ ፈንቶ ምናምን ዕቃ፡ ኵሳንኵስ ሰባራ ሥንጥር ። "ቅላቅንቦ ቢል የቅንቦ ቅል" ማለት ይመስላል ።
ቅራተኛ፡ ባለቅራት ጠባቂ ።
ቅራት፡ ሌሊታዊ ጥበቃ ።
ቅራት፡ ያሞራ ቤት ።
ቅራት፡ ያሞራ ቤት ።—ቀራ ።
ቅራና (ኖች)፡ የቀርቃባ ጠፍር ። በትግሪኛ ግን አንድ ፈርጅ ሸማ ማለት ነው ። "የቅራና ምስጢር እንደ ቀርን (ቀንድ) ኹለት መኾኑን ያሳያል ። ከቈረኘና ከገረኘም ይሰማማል ። ቅሪላን ቀረነተን ተመልከት" ።
ቅራፊ፡ የተቀረፈ (ንጣይ ልጣጭ ") ።
ቅሬ - ቈራ ።
ቅሬ (ቃረ)፡ ዐጣሪ ዘፋኝ አረኾ (የሴት ወሮ በላ ባለጌ ማን ዘራሽ መሸተኛ አቅራሪ ጋለሞታ ሴትኛ ዐዳሪ ሸርሙጣ ነውር ጌጧ ") ።የቅሬ ምስጢር የተቃረች ማለት ነው ።"ወለደ" ብለኽ "ልጅን" እይ ።ቅሬ ለወን ድም ይነገራል።
ቅሬታ፡ ተረፍ ትራፊ ("(ዐብድ. ፩፥ ፲፰ ። ሶፎ. ፪፥ ፲፱)") ።
ቅሬነት፡ ቅሬ መኾን (ዐጣሪነት ጋለሞታነት ") ።
ቅሬዎች፡ ዐጣሮች አረኾዎች ጋለሞ ቶች ።
ቅር (ቍር)፡ የሽንብራ በሽታ የሚ ያደርቀው ዐልፎ ዐልፎ ጭብርር የሚያደርገው አለፍሬ የሚያስቀረው ።
ቅር (የቀረረ ") ።
ቅር ቅር አለው፡ ውል ውል አለው ።
ቅር አለ፡ ትዝ አለ፡ ታሰበ በልብ ተጕላላ ።
ቅር አለው፡ ግር አለው፡ ቸገረው ።
ቅርሚያ፡ ለቀማ፡ ስብሰባ።
ቅርምቻ፡ ትንተና/ክፍያ ።
ቅርምዝ - ቈረኘ፡
ቅርምዝ (ዐረ)፡ ቀይ ግምጃ ("እን ድኪ ጃዊ ") ("(ኢሳ. ፩፥ ፲፰)") ።
ቅርሥ፡ ተቀማጭ ገንዘብ ።—ቅ ርስ ።
ቅርስ፡ ተቀማጭ ገንዘብ፡ ወይም ካባት የወረደ ተካባች ብር ። ባረብኛ "ቅርሽ" ይባላል፡ የብር ክፍልፋይ ታናሽ ገንዘብ መሐልቅ እንደ ማለት ነው ። "ቍሪትን" ተመልከት ። "ግርሽና ቅርሽ" አንድ ስም ነው ። ዳግመኛም ብር በትግሪኛ "ቀርሽ" በጋልኛ "ቀርሺ" ይባላል ።
ቅርር አለ፡ ቀረረ ።
ቅርርት፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅርሻታም፡ ቅርሻት ያለበት የሚታይበት የሚበዛበት (ኹል ጊዜ የሚቀረሽ ልጅ ትፋታም ") ።
ቅርሻት፡ እውከት ትፋት ።
ቅርሽምሽም፡ ስብርብር ።
ቅርሽምሽም አለ፡ ስብርብር አለ፡ ተ ቀረሻሸመ ።
ቅርቀራ፡ ሽጐራ ውርወራ ።
ቅርቃር (ሮች)፡ መዝጊያ እንዳይከፈት በስተውስጥ ኹኖ የሚከለክል ዕንጨት ።
ቅርቃር፡ ሳንቃን ከሳንቃ የሚያገናኝ መስቀልኛ ውሻል (ርስ በርሱ የተሳካ ") ።
ቅርቅምቢጥ፡ ሰቡልጋ ውስጥ ያለ ቀበሌ ።
ቅርቅምቢጥ፡ ቅምምጦሽ፡ ቅልጥፍናን ያሳያል ።
ቅርቅር፡ የተቀረቀረ (ሽጕር ") ።
ቅርቅብ፡ የተቀረቀበ (ውድን እርት ") ።
ቅርቅፍ፡ የተቀረቀፈ (የግንድ ድቃቂ ") ።
ቅርቅፍት፡ ደንጊያ የበዛበት ሻካራ መንገድ ።
ቅርቢያ፡ ቀረቤታ (ቅርብነት ጎረቤትነት ልነት ") ።
ቅርብ (ቦች - ቅሩብ)፡ የቀረበ (ሩቅ ያይዶለ ")፡ የተጠጋ (በጐን ባጠገብ ያለ ") ። (ተረት)፡ "ሳይርቅ በቅርቡ ሳይደርቅ በርጥቡ" ። "ከሩቅ ዘመድ የቅርብ ጎረቤት" ።
ቅርብ ለቅርብ፡ ጐን ለጐን አጠ ገብ ላጠገብ ።
ቅርብ ዘመድ፡ ኹለት ቤት፡ ሦስት ቤት ።
ቅርታ፡ ትዝታ ችግር ዐሳብ አለመደሰት፡ ዐዘን ።"አቶ እከሌ በኔ ነገር ቅርታ ገብቶታል" ።
ቅርት፡ ሙትት ዝርግት ዟ ሰተት ።
ቅርት አለ፡ ድንገት ትንፋሹ ተቈረጠ፡ ድብን አለ ።
ቅርናታም፡ ባለቅርናት ("ግማታም አ ውራ ፍየል ") ።
ቅርናት፡ የብብት የተቃጠለ ቈዳና ቍ ረንጮ ክፉ ሽታ ግማት ።
ቅርን፡ ቀረመት (የሥጋ ክፍያ፡ በብዙ ወገን ቈርጠው መድበው የሚካፈሉት ") ።
ቅርንት፡ መቀርናት ።
ቅርንት አለ፡ ግምት አለ ።
ቅርንጥሳም፡ ቅርንጥስ ያለው (ባለቅር ንጥስ ") ።
ቅርንጥስ፡ ጨርቅ ጭርንቍስ የተጠቃቀመ (ዛተሎ ዘባተሎ ንጥስ ") ።
ቅርንጫፍ (ቀርነ - ጫፍ - ጫፈ - ቀርን)፡ እሾኸ (የዛፍ ፵ፍ ውልብልቢት ") ።"ቅርን" ከ "ቀርን" "ጫፍ" ከ "ጨፈጨፈ" መጥቶ አንድ ስም ኹኗል ።
ቅርንፉድ (ዶች)፡ የቅመም ስም (ከባሕር የሚመጣ ቅመም ") ። ባረብኛ "ቅርንፉል" ይባላል ።
ቅርንፉድ፡ ታናሽ የጠመንዣ መዘ ውር ።
ቅርደት፡ ያገር ስም ።
ቅርደዳ፡ ቈረጣ ገመሳ ።
ቅርድ (ዐረ ቀርድ)፡ ዝንጀሮ እን ዳሞድ ።
ቅርድ፡ የማዥራት ግድ አግዳሚ ሸ ለቆ ሠርጓዳው ጐድጓዳው ።
ቅርድድ፡ የተቀረደደ/የተቈረጠ ።
ቅርጠ ቀላል፡ ቀጪን ሰው (ቀትረ ቀላል ") ።
ቅርጠ ቢስ፡ ቁመናው የማያምር ሰው (ቅጠ መጥፎ ") ።
ቅርጠ የለሽ፡ ቅጥ የለሽ መልከ ቢስ ።
ቅርጠፋ፡ ቈረጣ ።
ቅርጣሽ (ቈረመደ)፡
ቅርጣሽ፡ የመብራት ቍራጭ (ኵስታሪ ") ።
ቅርጣሽ፣ኵስታሪ ቀረጠ።
ቅርጣፊ፡ የጌሾ/የሰንበሌጥ ድቃቂ ።
ቅርጥ፡ ቅጥ አካላዊ ሥራ መልክ ቁመና ኹኔታ ።
ቅርጥ፡ የተቀረጠ/የሾለ ። ካህናት ግን "ቅርጽ" ይላሉ ።
ቅርጥፋት፡ ቅርጠፋ/መቀርጠፍ/ክርክ ማት ።
ቅርጥፍ አለ፡ ተቀረጠፈ ።
ቅርጥፍ፡ የተቀረጠፈ ።
ቅርጫት (ቶች)፡ ከመቃ ከቀርክሓ ከክትክታ ከቀጨሞ ከሐረግ የተበጀ ዕቃ (ማንኛውንም ነገር መያዣና ማስቀመጫ ሰብል መሰብሰቢያ እኸል መስፈሪያ ") ። የንጨቱን መቀረጽና ሹለት ያሳያል ።
ቅርጫትከንጨት፡ የተበጀ፡ ዕቃ፡ ቀረጠ ።
ቅርጭም፡ የተቀራጨመ (ጥርቅም ") ።ቅርጫሚ፡ ጥርቃሚ ዞ መ ።
ቅርጭም፡ የተቀራጨመ (ጥርቅም ") ።ቅርጫሚ፡ ጥርቃሚ ዞ መ ።
ቅርጭጭ አደረገ፡ ንክስ ውግት አደረገ፡ ቀረጪዉ ።
ቅርጭጭ፡ የተቀረጪ ንክስ ።
ቅርጭፍት፡ ዕሩር የቋር ቍራጭ ።
ቅርጽ (ጾች)፡ የተቀረጸ (ቅርጥ ንጥ ፍ ልፍል ንቅስ ") ። "ደንጊያ ዕንጨት ብረት መዳብ ንሓስ ወርቅ ብር ማንኛውም ማዕድን" ።
ቅርጽ፡ የሰው መልክ ምስል፡ ጣዖት ።
ቅርፊት (ቅርፍት)፡ ልጥ ያለበትና የሌለበት የንጨት ልብስ፡ ተቀርፎ የወደቀ አለት ምርጊት ። "የዳቦ የሮማን ቅርፊት፡ የቍስል ቅርፊት" እንዲሉ ።
ቅርፋ (ቀረፈፈ)፡
ቅርፋ፡ ድንብላል ።
ቅርፍርፍ አለ፡ ተቅረፈረፈ ።
ቅርፍርፍ፡ የተቅረፈረፈ (ሥንጥቅጥቅ ፍርክርክ ") ።
ቅርፍርፍታ፡ ቅርፍርፍ ማለት ።
ቅርፍርፍነት፡ ፍርክርክነት ።
ቅርፎ፡ ያንኮላ የቅምጫና ጫፍ ቍራጭ ።
ቅሽምድ አለ፡ ስብር አለ ።
ቅሽር፡ የተቀሸረ (አለባበስ አሳማሪ ክሽን ንፍ ") ።
ቅቀላ፡ የመቀቀል ሥራ ።
ቅቀራ፡ የመቀቀር ሥራ ።
ቅቅላት፡ የቅቅል ኹኔታ ።
ቅቅል ዋጭ፡ ቅቅልን የሚወድ የሚውጥ ።
ቅቅል፡ የተቀቀለ/የበሰለ ሥጋ ዞ ።
ቅቅታም (ሞች)፡ ሥሥታም ንፉግ ጩቅ ቢስ እጁን ቢሉት የማይወድቀው ።
ቅበ ቢስ፡ ክቾ ነገረ ደረቅ ለዛ ቢስ ዕድለ ቢስ ።
ቅበላ (ቀበላ)፡ ያርባ ሑዳዴ ዋዜማ እሑድ ቀን የጦም መቀበያ ። የሐምሌ ሠላሳኛ ቀንም የፍልሰታ ጦም ቅበላ ይባላል ።
ቅቡጭ (ቅቡጽ)፡ ያነሰ የጐደለ ።
ቅቡጭ አለ፡ እንስ ጕድል አለ ። "ይበቃል ሲሉት በድንገት ዐለቀ ጠፋ ታጣ" ።
ቅባቅዱስ (ቅብዕ ቅዱስ)፡ ሜሮን (የተቀደሰ ሽቱ ") ። ሕፃን የክርስትናው ለት ታቦት በመባረኪያው ቀን የሚቀባው፡ ባገራችን የወይራ ፍልጥ ዘይት ነው ።
ቅባታም፡ ቅባት የሚወጣው (ባለቅባት ተልባ ኑግ ሰሊጥ ሱፍ ጕሎ ባር ቅል፡ የመሰለው ኹሉ ") ።
ቅባት፡
ቅባት (ቅብዐት)፡ ቅቤ ' ዘይት ሞራ ቅልጥም ላት የዶሮ ሥብ ጋዝ (የመሰለው ኹሉ ") ።
ቅባት፡ ዕድል ተሰጦ ሀብት ጸጋ ።
ቅባት፡ የሃይማኖት ስም ። "ባጤ ሲፋል ዘመን ዕውር ዘኢየሱስ የሚባል ሰው ያወጣው ሃይማኖት" ። "ቤተ ኤዎስጣቴዎስ" "የቤተ ተክለ ሃይማኖት ተቃራኒ" ። "የቅባት ባህል" ባጭር ቃል ይህ ነው ። "ቃል ሥጋ ለብሶ ሰው በኾነ ጊዜ (ዜገ) የባሕርይ ክብ ሩን ዐጣ ለቀቀ፡ ሲቀባ (መንፈስ ቅዱስን ሲቀበል) ግን ተገብሮ ተፈጥሮ ጠፍቶለት በሰውነቱም ባምላክነቱም አንድ ወገን የባሕርይ አምላክ ኾነ" ይላሉ ("(ኪ. ወ. ክ.)") ።
ቅባቶች፡ በቅባት ሃይማኖት የሚያምኑ ። "ለዘሐመ ልብ ቃለ ሃይማኖት መድኀኒቱ አኮኑ ቅባት" የሚሉ ።
ቅባኑግ፡ ከኑግ የሚወጣ ቅባት ዘይት (የጦም ወጥ የሚሠራበት ") ። አወጣጡም ለጥልጦ በማፍላትና በማሸት በፀሓይ ሙቀት ነው ። በግእዝ "ቅብዐ ንሒጕ" ይባላል ።
ቅባጥርሴ፡ ትርክም ምናምን ነገር ።
ቅቤ መዛኝ፡ ቅቤ እየመዘነ የሚሼጥ ። "ቅቤ መዛኝ ድርቅ ያወራል" እንዲሉ ።
ቅቤ ዐንጓች፡ ዝኒ ከማሁ ። "ለቅቤ ቅቤው ወጣ" ("(ትግ. ጸዐየ)") ። ሽፍታ ጠባሽ ኾነ ሰፈፈ ።
ቅቤ አድርቅ፡ ውርጭ ብርድ ።
ቅቤ ጠባሽ፡ እወደድ ባይ አከንፋሽ ።
ቅቤያም፡ ባለቅቤ (ብዙ ቅቤ የሚወጣት ላም ") ።
ቅብ (ቅቡዕ)፡ የተቀባ የተለቀለቀ የታደለ የተኰላ ። "ወርቅ ቅብ" እንዲሉ ። ተመልሰኸ "ቅብን" ተመልከት ።
ቅብ (ቅብዕ)፡ ቅቤ (የዘይት ዐይነት ") ።
ቅብ፡ የተቀባ ተቀባ ።
ቅብል፡ የተቀበሉት ።
ቅብር (ቅቡር)፡ የተቀበረ/የተደፈነ ።
ቅብር አለ፡ ድፍን አለ (ተቀበረ ") ።
ቅብር አደረገ፡ ድፍን አደረገ (ቀበረ ") ።
ቅብርር - ቀብራራ ።
ቅብርር አለ፡ ተንቀባረረ ።
ቅብቀባ፡ ዕየማ ቅጥቀጣ ችከላ ።
ቅብቃብ (ቦች)፡ ደረቅ ዕንጨት ችካል ካስማ (የከብት የመሠረት ገመድ ጠፍር ማሰሪያ የድንኳን አውታር መሳቢያ መወጠሪያ ") ("(ዘኍ. ፮፥ ፴፪)") ።
ቅብቅብ (ቦች)፡ የተቀበቀበ (የታረሰ ለስላሳ ዕርሻ ") ። (ተረት)፡ "አፍና ቅብቅብ ኹል ጊዜ እያበላም" ።
ቅብቅብ፡ የተተከለ/የተቸከለ (እመሬት የገባ ቅብቃብ ችክ ") ።
ቅብቅቦ፡ በጨው የታጀለ የማሽላ እሸት በድብዳብ የተሸፈነ ።
ቅብትት አለ፡ ንፍት ውጥር አለ ።
ቅብትት አደረገ፡ እጅግ በጣም ቀበ
ቅብትት፡ የተቀበተተ/የተነፋ/የተወጠረ (ንፍ ውጥር ንርት ") ።
ቅብንን አለ፡ ንፍት ውጥር አለ (ተቀ በነነ ") ።
ቅብንን፡ የተቀበነነ (ንፍ ውጥር ሆድ ") ።
ቅብዐ መንግሥት፡ የመንግሥት ቅ ባት (ንጉሥና ንግሥት ተቀብተው የሚነግሡበት ") ።
ቅብዐ ክህነት፡ የክህነት ቅባት (ካህ ንና ጳጳስ ተቀብተው የሚሾሙበት ዘይት ") ።
ቅብዝብዝ አለ፡ ተቅበዘበዘ ("(ኢዮ. ፲፭፥ ") ።
ቅብዝብዝታ፡ ቅብዝብዝ ማለት ብክ ነት ።
ቅብዥርዥር፡ ውዥብርብር ።
ቅብጠት (ቅብጸት)፡ ዝላይ ጨዋታ ልፊያ ድሪያ (ከጨዋ ደንብ የተለየ ሥራ ") ።
ቅብጢ - ቅብጣዊ፡ የቅብጥ (ግብጻዊ የግብጽ ሰው ") ።
ቅብጢ (ቅብጣዊ)፡ የቅብጥ ቋንቋ (ጥንታዊ የምስር ልሳን ") ። ፊደሉ ከጽርእ ፊደል አንድነት ያለው ። "ቅብጥ" ከጽርእ የሚ ለየው ፯ ፊደል ሲጨምር ነው ። ሌላም "ሄሮግሊፍ" የሚባል የተቀደሰ ሥዕላዊ ፊደል በግብጽ ነበረ ።
ቅብጢ፡ ቀበጥ ቀበጢና (ሴት ") ። ዘሩ ቀበጠ ነው።
ቅብጥ (ቀቢጽ)፡ መቅበጥ ።
ቅብጥ አለ፡ ፍንድቅ አለ (ፈጽሞ ") ።
ቅብጥ፡ ግብጽ ምስር ። "ግ ለቅ ጽ ለጥ መለወጡን አስተውል" ። ኹለቱም በግእዝ መጽሐፍ ይገኛሉ። "ግብጥን" እይ ።
ቅብጥርጥሬ፡ የቅብጥርጥር ዐይነት ።
ቅብጥርጥር፡ ልፍለፋ ዝብዝብ ሰበብ ።
ቅብጥና፡ ቀበጥነት/ፍንደቃ ።
ቅብጥጥ አለ፡ ቅብትት አለ ።
ቅብጥጥ፡ የተቀበጠጠ ።
ቅትር (ቅቱር)፡ የተቀተረ/የተቀረቀረ ("ንፍ ውጥር ") ።
ቅትር አለ፡ ውጥር አለ ።
ቅትርት (ቶች)፡ በሞፈርና በድግር ውስጥ የተቀረቀረች ቅርቃር ("የመንኰራኵር ብረት ወይም ዕንጨት መወጠሪያ መሳይ ") ("(፩ነገ. ፯፥ ፴፫)") ።
ቅትት፡ መቃተት ።
ቅትት ቅትት አለ፡ ትንፍስ ትንፍስ አለ ።"ቃታን" እይ ።
ቅነሳ፡ የመቀነስ ሥራ ።
ቅነፋ፡ ዐጠፋ ምለሳ ሽብለላ ።
ቅናሽ፡ ከጠላ የተቀነሰ ዐሠር ውሃ ሰለልታ ።
ቅናተ ኤልያስ፡ የኤልያስ መታጠ ቀያ ።
ቅናተ ዮሐንስ፡ የዮሐንስ መጥምቅ መታጠቂያ ።
ቅናተኛ፡ ቀናተኛ (ቅናት ያደረበት ") ።
ቅናት (ቅንአት)፡ ክፉ ምኞት ም ቀኝነት፡ ሌላው ሠርቶ እንዳይጠቀምና እንዳይመሰገን የመቃወም ሐሳብ ("(ሮሜ. ፲፫፥ ፲፫)") ።
ቅናት፡ መታጠቂያ ።
ቅናት፡ መነኵሴ ባሕታዊ ወገቡን የሚጠልፍበት ዐንገቱን የሚያገባበት በደረት በኩል መስቀልኛነት ያለው ሰንሰለት ጠፍር ጌታችን የታሰረበት ገመድ ምሳሌ ።
ቅናት፡ ምቀኝነት ። ቀና ።
ቅናት፡ በኮርቻ መካከል በቀኝ በኩል የተሰፋ ጠፍር ነት ወይም ባሕር ዐረብ ።
ቅናት፡ ትጥቅ ("(ኢዮ. ፳፪፥ ፲፰፡ ፳፩)") ።
ቅናት አደረገ፡ አበከረ ።
ቅናት፡ የመነኵሴ መታጠቂያ ከተንቤን ከባሕር ዐረብ የተበጀ ። (ቅናትና ቅንአት በግእዝ ልዩዎች ሲኾኑ ባማርኛ ይተባበራሉ።) (ግጥም)፡ "ባፋ በጐራዴ ትደነቃላችኹ፡ ወገብ ቈርጦ እሚጥል ቅናት ሳለላችኹ" ።
ቅናት፡ የዜማ ምልክት ።
ቅናዋት፡ ችንካሮች ምስማሮች ።
ቅናዋት፡ የዜማ መዝሙር መስቀል ነክ ሰው ሲሞትና ቅዳሜ ቀን የሚባል ።
ቅናጅ፡ የባሪያ ስም፡ የፍናጅ ልጅ ፫ኛ ።
ቅናጥ፡ ጐሣ ደሳ የዘላን ጐዦ ልብስ ።
ቅኔ (ዎች)፡ የድርሰት ስም፡ ክፍሉና ስሙ ፲፫ የኾነ የግእዝ ግጥም ሲሰ ሙት ደስ የሚያሠኝ እጅግ የሚጥም፡ ኹል ጊዜ ዐዲስ ("(መዝ. ፺፭፥ ፪)") ። "መጽሐፈ ቅኔ" ተመልከት ።ዘርፍና ተሳቢ ኾኖ ሲነገር ።
ቅኔ ማሕሌት (ማሕሌተ ቅኔ)፡ በቤተ ክሲያን ውስጥ ያለ ምዕራባዊ ክፍል፡ ደብተሮች ማሕሌት የሚቆሙበት ቅኔ የሚቀኙበት የቅኔ ወረብ ግጥም ዘፈን (ምስ ጋና) የሚያሰሙበት ስፍራ ። ቅኔ የማሕሌት ዘርፍ መኾኑን አስተውል ። ቅኔ እንደ ግእዙ መገዛት ተብሎ ቢተረጐም፡ ካህናት ለፈጣሪ በማሕሌት የሚገዙበት ያሠኛል ።
ቅኔ ሰጠ፡ ተቀኘ አበረከተ ።
ቅኔ ቈንቋኔ፡ የተማሪን ሰውነት እንደ ቅንቅን እንደ ነቀዝ የሚጐዳ ማለት ነው ። "ቅኔ ቈንቋኔን ድጓ ዶግዷጌን አያምጣብን" እያሉ ይጸልዩና ያሳርጉ ነበር ይባላል የጥንት የጕራጌ ወይም የአገው ቄሶች ። (ያማርኛ ቅኔ)፡ ኅብርነት ያለው ያማርኛ ስንኝ ወይም ግጥም ። "ኹለተኛውን ቈጠረ" እይ ።
ቅኔ ቈጠረ፡ ዐሰበ አዘጋጀ ።
ቅኔ ቤት (ቤተ ቅኔ)፡ የቅኔ ት ምርት ቤት ።
ቅኔ ነጋሪ፡ ቅኔ አስተማሪ ።
ቅኔ ዐዋቂ፡ ሲቀኝ ይበል ወሰው መልካም የሚያሠኝ ሊቅ ቅኔ የሚያውቅ ።
ቅኔ ዘረፈ፡ ሳይቈጥር ተቀኘ ።
ቅን (ኖች) (ቅኑእ - ቅኑይ - ርቱዕ)፡ የቀና/የተገዛ (ታዛዥ ፈቃደኛ ገር ትሑት ደግ ሰው ") ("(ዘዳ. ፳፭፥ ፩፡ ምሳ. ፪፥ ፰፡ ፯)") ።
ቅንሳት፡ ጕድለት ሕጸጽ ።
ቅንስ፡ ዝኒ ከማሁ (ከላዩ ተነሥቶለት የጐደለ ጐደሎ ") ።
ቅንቀና፡ ምርመራ ፍተሻ ቅኚት ሙሾ ።
ቅንቅናም (ሞች)፡ ሥሥታም ንፉግ ።
ቅንቅን (ኖች - ቍንቍኔ)፡ የተን ቀሳቃሽ ስም (ከጤፍ የሚያንስ የዶሮና ያልጋ ተባይ ") ።
ቅንቅን፡ ሥሥት ንፍገት ።
ቅንቅን፡ በገላ ላይ የሚፈስ ረቂቅ ዕ ከክ ። "ክሽክሽትን" እይ ።
ቅንቅን፡ ነቀዝ ("(ምሳ. ፲፪፥ ፬)") ።
ቅንቡርስ (ሶች)፡ የትል ስም፡ ርጥበት ባለው ጕድፍ ውስጥ የሚገኝ ነጭ ትል ። ንን ጣልቃ ስን ምእላድ አድርጎ (ቅቡር) የተቀበረ ተብሎ ይተረጐማል ።
ቅንብር አለ፡ ቀነበረ ።
ቅንብርብር አለ፡ ተቀነባበረ ።
ቅንብርብር፡ የተቀነባበረ (ክውንውን ") ።
ቅንብቢት፡ ክብ ተራራ ያለበት አገር ስም፡ በቡልጋ አጠገብ ይገኛል ። "ቅንብ ቢት የተቀነበበች" ማለት ነው ።
ቅንብብ፡ የተቀነበበ የተከበበ የሕፃን ርግብግቢት ጠጕር ።
ቅንብቻ (ቾች)፡ የተረሳና ትርፍ ዕቃ ማስቀመጫ ማኖሪያ፡ ከቈዳ የተሰፋ መናኛ ኰ ረጆ፡ አፈ ክፍት ስፌት ።
ቅንብቻ ሆድ፡ ሆደ ጕስር ሰው ።
ቅንቦ (ዎች)፡ ወተታም የቈላ የ በረሓ ዕንጨት ። የፍሬው እንቡጥ ቅል ያካክላል፡ በውስጡም ነጭ ሐር የሚመስል ባዘቶ ይገኝበታል ።ኹለተኛ ስሙ ጦቢያ ይባላል ። ወተቱም እውሃ ውስጥ ጠብ አድርጎ ሲቀምሱት ለመጋኛ መድኀኒት ይኾናል፡ ቅንቦ ማለት ቀልጣማነቱን ያሳያል ።
ቅንት፡ "እንደ ገበሬ ጥምድ እንደ በሬ" እንዲሉ ።
ቅንት (ቅኑት)፡ የቀነተ የታጠቀ ።
ቅንነት (ርትዐት)፡ ቅን መኾን፡ ፈቃደኛነት ታዛዥነት ትሕትና ("(፩ዜና. ፳፱፥ ፲፯)") ።
ቅንዘፋ፡ ምልመላ ።
ቅንዝር - ምንዝር፡ ሴሰን ከልክ ያለፈ ዝ ሙት ።
ቅንዝርና - ሽርሙጥና - ምንዝርና ። ቅንዝረኛ (ኞች)፡ ሴሰኛ አመንዝራ ወንድ ወይም ሴት ።
ቅንዝፍ ቅንዝፍ አለ፡ ፍስስ ፍስስ አለ እንባው ።
ቅንዝፍ አለ፡ ፍስስ አለ ።
ቅንዝፍ፡ ዝኒ ከማሁ (የታረደ የፈሰሰ ") ።
ቅንደላ፡ ብጥታት ቈረጣ ።
ቅንደባ፡ ምት ።
ቅንድብ (ቦች)፡ ነፋስና ውሃ ጪስ የማያስገባ ያይን መክደኛ መሸፈኛ ቈርበቱ ቈዳው በላይ በታች ያለው ። በግእዝ "ቅርንብ" ይባላል ("(መዝ. ፲፩፥ ፬፡ ፻፴፩፥ ፬)") ። "ቅንድቤ ርግብ ርግብ ይላል" እንዲል ባላገር ።
ቅንድብ፡ የተቀነደበ የተመታ ።
ቅንጁ፡ የተቀናጀ (ሌላ ኹለተኛ በሬ ") ። "ቀንጃ ከቀንጃ ጋራ" ።
ቅንጠሳ - ቅንጠባ - ብጠሳ ።
ቅንጠባ፡ ቈረጣ ብጠሳ ቅንጠሳ ።
ቅንጡ (ዎች)፡ የተቀናጣ የጠገበ (ቅም ጥል ") ።
ቅንጣር (ዐረ)፡ የሚዛን ስም፡ ግንጣር መቶ ነጥር አንድ ቅንጣር ይኾናል ("(ዘፀ. ፳፭፥ ፴፱ ። ፩ነገ. ፲፥ ፲)") ። በግእዝ "መክሊት" ይባላል ። ፈረንጆች ነጥርን ኪሎ፡ ቅንጣርን ኲንታል ይሉታል ።
ቅንጣሽ - ቅንጣቢ - ቍራጭ - ብጣሽ ።
ቅንጣት (ቶች)፡ አንድ ፍሬ ("(ማቴ. ፲፫፥ ፴፩)") ።
ቅንጣት፡ አንድ ፍሬ ።
ቅንጥ፡ ድሪያ ልፊያ ።
ቅንጦተኛ፡ ጥጋበኛ እብሪተኛ ።
ቅንጦት፡ ጥጋብ እብሪት ቅምጥልነት ።
ቅንጭር አለ፡ ቀነጨረ ።
ቅንፋት፡ ዕጥፋት ቅልብሳት ።
ቅንፍ፡ የፊደል የቃል ማጠሪያ መክ በቢያ ("()") ።
ቅኝት፡ የበገና ዥማት መጥበቅ መ ላላት መቃናት መሰማማት ።"
ቅዘናም (ሞች)፡ ኹል ጊዜ የሚቀዝን (ፈሪ ጡርቂ ") ።
ቅዘን፡ ተቅማጥ ሻታ ።
ቅዘን፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ።
ቅዛዛ - ቅዛዝ፡ መስተዋት ።
ቅዝምዝም፡ የተቅዘመዘመ (ምዝግዝግ እንዝግዝግ ውዝግዝግ ") ። ባላገር ግን "ቅዝምዝም" በማለት ፈንታ "ቅምዝምዝ" ይላል ።
ቅዝቃዜ፡ ብርድ ።
ቅዝታ፡ ቅርታ ታናሽ ሕጸጽ ።
ቅዝዝ አለው፡ ቅፍፍ አለው ።
ቅዝፊያ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅዠታም (ሞች)፡ የቃዠ/የሚቃዥ (ባለቅዠት ራሰ ቢስ ") ።
ቅዠት፡ የሕልም ጩኸት ከንቱ እ
ቅየማ - ቅያሜ፡ ኵርፊያ ።
ቅየሳ - ቅይሳት፡ የመቀየስ ሥራ፲ ብ ገራ ምጠና ።
ቅየራ - ቅያሬ - ቅይራት፡ ልወጣ ውላጤ ።
ቅየዳ፡ ምከታ እሰራ ስከላ ቀይድ፡ (ትግ. ቀይዲ)፡ ስካላ ጋዲ ።
ቅየጣ፡ ቅልቀላ ድብለቃ ዝነቃ ።
ቅያስ፡ ልክ መጠን ንድፍ ቢጋር
ቅይም አለ፡ ተቀየመ ።
ቅይም፡ የተቀየመ ።
ቅይስ፡ የተቀየሰ ቦታ መንገድ መሬት ።
ቅይር፡ የተቀየረ/የተዛወረ (ልውጥ ") ።
ቅይዳት፡ መከታ ግርዶ፡ ሰካላ እስራት ።
ቅይድ፡ የተቀየደ የተከፈለ የተመከተ፡ ስክል አፈ እስር ድዳ ።
ቅይጥ (ጦች)፡ የተቀየጠ (ዝንቅ ቅል ቅል ድብልቅ ውጥንቅጥ የወፍጮ የልመና እኸል፡ ዲቃላ ") ።
ቅደም ተከተል፡ ፊትና ኋላ ኹን ።
ቅደም፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (ኺድ ዕለፍ ") ።
ቅደሳ፡ የመባረክ የማመስገን ሥራ ።
ቅደቅ፡
ቅዱሰ ቅዱሳን፡ የቅዱሳን ቅዱስ፡ የካህናት አበል ("(ዘሌ. ፪፥ ፲)") ። ከዚህም በቀር ቅዱስ ከስም አስቀድሞ እየገባ በቅጽልነት ሲነገር፡ ቅዱስ ገብርኤል፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ፡ ቅዱስ ዮሐንስ፡ ቅዱስ ሚካኤል፡ ቅዱስ ጳውሎስ፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ይላል ።
ቅዱሳት፡ ንጹሓት ቡሩካት ሴቶች ።
ቅዱሳት አንስት፡ ጌታችን በዚህ ዓ ለም ሳለ እሱን የተከተሉና በገንዘባቸው ያገለገሉት ፴ ሴቶች ።
ቅዱሳን አማልክት፡ ሥላሴ ("(ዳን. ፫፥
ቅዱሳን፡ የተቀደሱ ንጹሓን ቡሩካን መላእክት ጻድቃን ።
ቅዱስ መጽሐፍ፡ ብሉይና ሐዲስ ኪዳን ። "መጽሐፍ ቅዱስ" ቢል ስሕተት ነው ።
ቅዱስ፡ በቁሙ ልዩ፡ የተቀደሰ የተባ ረከ የነጻ የበቃ፡ ቡሩክ ንጹሕ ምስጉን ።
ቅዱስ ባለጌ፡ የተለየ ልዩ ባለጌ ።
ቅዱስ፡ ከላይ ጥርስ የሌለው የሚያመሰኳ ጥፍረ ሥንጥቅ የቤትና የዱር እንስሳ ሥጋው የሚበላ ።
ቅዱስ፡ የርኩስ ተቃራኒ ።
ቅዱስ፡ የኪዳን መዠመሪያ ሳይደወል ቅዱስ እንዲሉ።
ቅዱስጌ (ጌቅዱስ)፡ በቡልጋ አውራጃ ያለ አገር፡ የተቀደሰ ምድር፡ ወይም አንድ ቅዱስ የኖረበት የጸለየበት የሰበከበት የቅዱስ አገር ምድር ማለት ነው፡ ነገር ግን ምድር የምትነገረው በሴት አንቀጽ መኾኑን አስተውል ።
ቅዳሜ (ቀዳም)፡ የሰባተኛ ቀን ስም፡ ሰባተኛው ቀን በዕረፍትነት ከእሑድ ስለ ቀደመ ቅዳሜ ተባለ እንጂ፡ ቅዳሜ መባል የሚገባው ለእሑድ ነበር ።
ቅዳሜ ሹር፡ የስቅለት ማግስት የሚውለው ቅዳሜ ወፍጮ ስለሚፈጭበትና ሌ ላም ለፋሲካ የሚኾን ሥራ ስለሚሠራበት ቅዳሜ ሹር ("የተሻረ ቅዳሜ") ተባለ ። ውስጠ ምስጢሩ ግን ክርስቲያኖች በዘመነ ሐዲስ በቅዳሜ ፈንታ እሑድን ማክበራቸውን ያሳያል ። ይኸውም የተዠመረው በታላቁ ቈስጠን ጢኖስ ዘመን ነው ።
ቅዳሴ (ጥደ)መቀደስመቀደስ፡ ቅ ደሳ ምስጋና ።
ቅዳሴ ሰማ፡ አደመጠ ("(አስቀደሰ)") ።
ቅዳሴ ቤት፡ የቤት ቅደሳ ምረቃ፡ ኅዳር ፯ ቀን የጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው ። መስከረም ፲፯ ቀን የመስቀል ቅዳሴ ቤቱ ይከበራል ።
ቅዳሴ ታጐለ፡ ሳይቀደስ ቀረ ተዳፈነ ።
ቅዳሴ፡ የመጽሐፍ ስም፡ በንባብና በዜማ የሚጸለይ የቍርባን ጸሎት፡ የቂሳርያው ባስልዮስና ሌሎችም ጳጳሳት ያዘጋጁት ድርሰት ።
ቅዳሴ፡ ገባ፡ ዠመረ ወጠነ ቅዳሴን ።
ቅዳሴ፡ ጠበል (ማየ መቍረርት ቅዳሴ ውጭ የሚጠጣ የቅዳሴ፡ ጠበል ") ።
ቅዳዴ፡ የብጫ ጣቃ ቅዳጅ ወታደሮች በራሳቸው ላይ የሚያስሩት የሚቀዳጁት ። "አቡቅዳዴ" እንዲሉ።
ቅዳዶቴ፡ የኔ ሸማ ቅዳጅ ።
ቅዳዶት፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅዳጅ (ጆች)፡ የሸማ የበርኖስ የደበሎ ሥንጣቂ ትልታይ ። "ዐዋጅ ዐዋጅ የደበሎ ቅዳጅ" እንዲሉ።
ቅዴታ፡ ያዢር ዕዳ (ባላገር እያዋጣ ለሹም የሚከፍለው ፈሰሴ ") ።
ቅድ፡ ሸፋሽፍት ። "ያይን ቅድ" እንዲሉ።
ቅድ፡ በከፊል የተጻፈ ። "ቅድ ድጓ ቅድ - ወንጌል" እንዲሉ።
ቅድ አፍ፡ ወሬኛ (እንዳገኘ የሚናገር ") ።
ቅድ፡ የተቀደደ ። ቀደደ ።
ቅድ፡ የተቀደደ/የተሸረከተ (ሽርክት ") ።
ቅድሙን - ቅድሙኑ፡ ፊቱን/ፊቱኑ ።
ቅድሚያ (ቅድመት - ቅድምና)፡ ዥመራ ፍለማ ።
ቅድም አያት፡ የወንድና የሴት አያት አባትና እናት ("እሚታ") ።
ቅድም፡ ከጥቂት ሰዓት ካኹን በፊት "አቶ እከሌ ቅድም መጥቶ ኼደ" ።
ቅድሳት፡ ዝኒ ከማሁ (ጸጋ ክብር ቍርባን ") ። "ንዋይን" ተመልከት ።
ቅድስተ ቅዱሳን፡ ከቅዱሳን ይልቅ የተቀደሰች (ከከበሩ የከበረች መቅደሰ ኦሪት ") ።
ቅድስት ፳ው ክንድ፡ ቅዱሳን የተባሉት እንደ ቅድስት ያሉት ፵ው ክንድና እንደ ቅኔ ማሕሌት ናቸው ። በግእዛዊት ቤተ ክርስ ቲያን ግንቡ (ግድግዳው) የ፫ነት፡ ጣራው የአ፩ነት ምሳሌ ነው ።
ቅድስት ሥላሴ፡ የተቀደሰች ሦስትነት ።
ቅድስት፡ የቤተ ክሲያን ኹለተኛ ክፍል ።
ቅድስት፡ የተቀደሰች የተባረከች (ንጽሕት ") ። "ቅድስት ሐና፡ ቅድስት ማርያም፡ ቅድስት አርሲማ" እንዲሉ።
ቅድስት፡ ያርባ ሑዳዴ ኹለተኛ እሑድ ወይም ሳምንት ።
ቅድስና፡ ቅዱስነት ንጽሕና ።
ቅድድ አለ፡ ሽርክት አለ ።
ቅድጁ (ቅድው)፡ የተቀዳጀ (ካህን ንጉሥ፡ የተቀዳጀች ንግሥት ልጃገረድ ") ።
ቅድጅት፡ ያክሊል ያበባ አደራረግ ።
ቅጅ (ቅዱሕ)፡ የተቀዳ የተገለበጠ የተጨመረ ። "አንድ ጋን ቅጅ" እንዲሉ።
ቅጅ (ቅድሕ)፡ የጠላ የጠጅ የማን ኛውም መጠጥና ዘይት ቅቤ ውጤት ። የፊተኛው ቅጽል፡ የኋለኛው ስም ጥሬ መኾኑን አስተውል ።
ቅጅ፡ ጽፈት ግልባጭ ("(ዕዝ. ፯፥ ፲፩፡ አስቴ. ፬፥ ፰)") ።
ቅጠ መልካም፡ ቅጡ (ኹኔታው)፡ ያማረ የሰመረ ።
ቅጠ ቢስ፡ ቅጠ መጥፎ የማያምር
ቅጠለ ወርቅ (ቈጽለ ወርቅ)፡ ከወርቅ የተሠራ የወርቅ ቅጠል ።
ቅጠለ ወርቅ፡ በወረቀት ተጠቅሎ የሚጠጣ ትንባኾ፡ ወርቅ የሚያወጣ ቅጠል ማለት ነው ።
ቅጠላ፡ ጭመራ እከላ ።
ቅጠላም፡ ቅጠለ ብዙ ባለቅጠል ። የቅጠል ከፍታት በፊት አለቀኑ የተበላ ተዝካር ። የቅጠል ማለት ጕዝጓዙን ያ ሳያል ።
ቅጠላቅጠል፡ የቅጠል ቅጠል፡ ብዙ ዐ ይነት ቅጠል ።
ቅጠላዊ፡ የቅጠል መልክ (ቀለመ ቅ
ቅጠል (ሎች - ቈጽል)፡ በእኸ ልና በተክል በዛፍ ዐጽቅ ላይ የሚወጣ
ቅጠል፡ ዦሮ፡ በቅጠል አምሳል የተሠራ ዕቃና ጌጥ፡ የጦር ብረት ።
ቅጠል የለሽ፡ ለዛ ቢስ (ንግግሩ ጣም የሌለው ሰው ") ።
ቅጠል፡ የታጠፈ ብራና ወረቀት ።
ቅጠልማ፡ ዝኒ ዓዲ ከማሁ ።
ቅጠልያ፡ ዝኒ ከማሁ (ቅጠል የሚመ
ቅጠባ፡ ክንዳታ ምጠና ምልከታክ ሰላ ።
ቅጡ (ጠባዩ ሥራው)፡ የማይታወቅ ምሳሌ አልባ ።
ቅጣተኛ፡ ቅጣት የተቀበለ ።
ቅጣት (ቅጽዐት)፡ መቅጣት መቀጣት (ግርፋት እስራት ") ።
ቅጣት (ቅጽዓ)፡ ትእዛዝ እንቀጽ ።
ቅጣጥይ፡ በመጨረሻ የሚወጣ መን
ቅጣፊ፡ የቅጠል ቍራጭ ቅንጣቢ ።
ቅጤ፡ የቅጥ (የሰይጣን) ዐይነት ወገን (የተቀጣ እባብ ") ። "አንድስ ቅጤ" እንዲሉ። እባብ ቅጤ መባሉ በርግማን እግሩን ዐጥቶ በደረቱ ስለ መኼዱ ነው ("(ዘፍ. ፫፥ ፲፬)") ።
ቅጥ (ቅጹዕ)፡ የተቀጣ የተቈረጠ ።
ቅጥ፡ ሥርዐት ደንብ አገባብ (ትክክል ልክ ") ("(ምሳ. ፲፩፥ ፳፬)") ። "በቅጥ አለቅጥ ሠራ" እንዲሉ።
ቅጥ፡ ሽልት ። ቀጠጠ ።
ቅጥ፡ ዐይነት ኹኔታ ምሳሌ ። "ሀዘንሽ ቅጥ ዐጣ፡ ከቤትሽም አልወጣ፡ የገደለው ባልሽ፡ የሞተው ወንድምሽ" ። "ቅጡም የምንኵስና ነው" እንዲሉ።
ቅጥ የለሽ፡ ያልተቀጣ ።
ቅጥ፡ የተቀጠጠ (ቍርጥ ዕጭድ ሽልት ") ።
ቅጥለት፡ ዝኒ ከማሁ (ንዴት ብግነት ") ።
ቅጥላት፡ የቅጥል አሠራር ኹኔታ ። (ቃጠለ)፡ ተቃጠለ፡ ነደደ ዐረረ ገመነ ተኰማተረ ተጋጠመ ።
ቅጥል (ሎች)፡ በቅርቃር በምስማር በስፌት በቍጥር የተቀጠለ (የሞፈር የልብስ የገመድ ተጨማሪ ነገር የጐደለ መሙሊያ ") ። "ቅጽልን" እይ ።
ቅጥልጣል፡ ቅጠላዊ ቅጠልያ (የወርቅ የብጫ የወይባ ዐይነት ") ። በግእዝ "ሐመልሚል" ይባላል ።
ቅጥልጣይ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅጥልጥላም፡ ቅጥልጥል ለባሽ (ባለቅ ጥልጥል ") ።
ቅጥልጥል፡ የተቀጣጠለ (ደበሎ ዝተት
ቅጥራት፡ ያጥር የቅጥር ሥራ ።
ቅጥራን፡ የሙጫ ቅመም መጣብቅ የሚኾን፡ ሙጫ ያለበት የስንዴ ዐራራ ቀለም ። "የወይን የበለስ ቅጥራን" ቢል፡ "ዐዞ ከል ሖም ጣጣ" ማለት ነው ። ማንኛውም ነገር ሲቦካ መጣብቅ ይኾናል ። ፈረንጆች ቅጥራንን "ካትራም" ይሉታል ። "ዝፍትን" አስተውል ።
ቅጥር (ሮች)፡ አሽከር ሎሌ ምንደኛ፡ "ጌታችን አንድ አገልጋይ ለኹለት ጌታ መገዛት አይችልም እንዳለ፡ ገረድን ቅጥር ማለት ባንድ ሰው ፈቃድ መታጠሯን በቅጥር (ዐጥር) ውስጥ ማደሯን ያስረዳል" ።
ቅጥር (ቅጹር)፡ የተቀጠረ የታጠረ (ቤት ከተማ ") (ቅጽል) ።
ቅጥር (ቅጽር)፡ መካበቢያ የግንብ የካብ ዐጥር (ስም) ።
ቅጥቀጣ፡ ድብደባ (ብረት ሥራ ወ
ቅጥቃጤ፡ ቅጥቀጣ/ቅጥቅጣት (ግእዝ) ።
ቅጥቅጣት፡ መቀጥቀጥ ።
ቅጥቅጥ (ጦች)፡ የተቀጠቀጠ (ብረት ወርቅ ("(፪ዜና. ፱፥ ፲፭)")) ። "የክትክታና የፍየለ ፈጅ ግጥግጥ" ።
ቅጥቅጥ፡ ውቅጥ (ተባት ፍየል ወይም በግ ") ።
ቅጥበት፡ ጥቅሻ ። በግእዝ "ቅጽበት" ይባላል ። "ቀጸበን" ተመልከት ።
ቅጥቡ ሞላ፡ ዕድሜው ዐለቀ ተፈ
ቅጥባት፡ ቅጠባ (የድር ልክ ምልክት ክስል ") ።
ቅጥብ (ቦች)፡ የተቀጠበ (የተከነዳ/የተለካ ምልክት መቍረ ") ።
ቅጥብ፡ የዕድሜ መጨረሻ ዕለተ
ቅጥነት፡ መክሳት ቀጪንነት ።
ቅጥን አለ፡ ክስት አለ ።
ቅጥን፡ የቀጠነ ቀጪን ። በግእዝም ታናሽ ጣት "ቅጠን" ይባላል ።
ቅጥንብር (ቅጥና ሕብር)፡ ቁመ ትና ቀለም (መልክ ") ።
ቅጥይ (ዮች)፡ ዐጽቅ ክንፍ ቅርንጫፍ፡ ፮ኛ ጣት ።
ቅጥጥ አለ፡ ዐበጠ ተነፋ ተቀበጠጠ ።
ቅጥጥ አደረገ፡ ንፍት ቅብትት አ
ቅጥጥብ፡ ያይን ጥቅሻ (ለግጥ ዘበት ፌዝ ") ። በግእዝ "ትዕይርት" ይባላል ።
ቅጥፊያ - ቅጥፈት፡ ዕብለት ውሸት
ቅጥፋት፡ የኻያጅና የቀሪ ቀንበጥ መለያ ።
ቅጥፍ አለ፡ ቍርጥ አለ ። ተቀጠፈ ።
ቅጥፍ፡ የተቀጠፈ/የተቈረጠ ።
ቅጥፍና፡ ቀጣፊነት ።
ቅጫማም፡ ቅጫም ያለበት የበዛበት ባለቅጫም ።
ቅጫም (ሞች)፡ የቅማል ቅንጣት ከጤፍ የሚያንስ፡ ረቂቅ የዕከክ ትል ። "ቅማንጅርን" እይ ።
ቅጭል፡ መቃጨል ።
ቅጭል አለ፡ ቃጨለ ።
ቅጭልጭል አለ፡ ቃጨለ ።
ቅጭልጭል፡ የተቅጨለጨለ (የቤተ ንጉሥ የቤተ ክሲያን አጫዋች ") ።
ቅጭቅጭ አደረገ፡ አንቀጫቀጨ ።
ቅጭት - ቅጭታት፡ የትከሻ መው ረድ ።
ቅጭት አደረገ፡ ቍርጥ ግንጥል አ ደረገ ።
ቅጭጭላት፡ ለገድ ነፈስ ።
ቅጭጭላት፡ የፈረስ ጕንጭ ትርፍ ሥጋ ተበጥቶ የሚወጣ ።
ቅጸላ፡ ጭመራ ትምርት ሐሜት ።
ቅጽ (ቅጹዕ)፡ የተቀጸ (ያልታጠፈ ብራና ወይም ወረቀት ") ።
ቅጽ፡ የጥራዝ የመጣፍ ልክ መጠን ቁመትናጐን ።ቀጻ ቅጽ የካህናት፡ ቀጣ ቅጥ የሕዝብ ነው ።
ቅጽል (ሎች)፡ ግብርን ዐይነትን መጠንን ለመግለጥ ከስም አስቀድሞ የሚነገር ቃል ።"ደግ ክፉ ቀይ ጥቍር ረዥም ዐጪር" የመሰለው ኹሉ ።ሌላውም ካ፭ቱ አዕማድ የሚወጣ ቅጽል የሠራተኛ ስም፡ "ገዳይ አስገ ዳይ ተገዳይ ተጋዳይ ተገዳዳይ ኣጋዳይ አገዳዳይ" ይላል ።ዳግመኛም "አበድ አሰስ ነበር ቀበር ሰበር ነደድ ሰደድ" የሚል ቅጽል አለ ።"ወንዛወንዝ ጨርቃጨርቅ ቅጠላቅጠል ርጥባ ርጥብ" ይህ ደጊመ ቃል ወይም ተናባቢ ቅጽል ይባላል ።
ቅጽል ተምሳሌ፡ ቅጽል ከምሳሌ ጋራ ባንድነት ሲነገር፡ እሱም የቅኔ ትምርት ነው ።
ቅጽበተ ዐይን፡ ያይን ጥቅሻ ወይም ፍጥነት (ዐይን ተጨፍኖ እስኪገለጥ ያለ እጅግ በጣም ዐጪር ጊዜ ") ("(ኤር. ፲፰፥ ፯)") ።"ቀጠ በን" አስተውል ።
ቅጽበት፡ ከስሳ ካልኢት ("(ሰጎንድ)") አንዲቱ ጭረት ።
ቅጽበት፡ ጥቅሻ ፍጥነት ።
ቅፈፍ - ቀፈፋ ።
ቅፈፍ፡ ቍራጭ ብራና ።
ቅፈፍ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ ፲ ከርክም ለምን ።
ቅፋፊ፡ የተቀፈፈ (ተቀፎ የወደቀ ") ።
ቅፍ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅፍለት (ዐረ ቃፍላ)፡ ተከታትሎ አተርትሮ ባንድነት የሚኼድ የሚጓዝ ባለጭነት የነጋዴ ግመል ("(ዘፍ. ፴፯፥ ፳፭)") ።
ቅፍለቶች፡ ሲራራ የጫኑ ግመሎች ("(ኢዮ. ፮፥ ፲፰ - ፲፱)") ።
ቅፍርናሖም፡ በምድረ እስራኤል ክ ፍል ያለ ቀበሌ ።
ቅፍቀፋ፡ ሰበራ ፍልፈላ ክርከራ ።
ቅፍቅፋት፡ የንቍላል የግንድ ስብር ባሪ ድቃቂ ።
ቅፍቅፍ፡ የተቀፈቀፈ የተፈለፈለ (ፍልፍል የተከረከረ ") ።
ቅፍቅፍ፡ የተነቃቀፈ።
ቅፍንድ፡ የቈርበት ዘርፍ ። "ቀፈደን" እይ ።
ቅፍድ፡ የተቀፈደ በቀፈድ የታሰረ ።
ቅፍድድ አደረገ፡ ቀፈደደ ።
ቅፍድድ፡ የተቀፈደደ ።
ቅፍጣን፡ የላይ ልብስ ዐጽፍ፡ ጌጠኛ መደረቢያ ከነጭ ሐር የተሰፋ ።
ቅፍፍ አለው፡ ጨፈገገው ከበደው ጨደደው ።
ቆለ ቢስ፡ ውቃበ ቢስ ።
ቆሊያም፡ ባለቆሌ ዛራም ።
ቆሌ (ቃላዊ)፡ ዛር ለፍላፊ የቃልቻ መንፈስ፡ ውቃቢ ለዛ ።
ቆል (ዕብ)፡ ቃል።
ቆመ፡ ረጋ ጸና፡ ነገሩ ።
ቆመ ብእሲ፡ ዐምደ ወርቅ ። መኻል ለመኻል አንድ ሊቅ ተደግፎት ስለሚቆም ዐምደ ወርቅ በካህናት ቋንቋ ቆመ ብእሲ ተባለ ። ትርጓሜው ሰው ቆመ ወይም የሰው ቁመት ማለት ነው ። ይህ አነጋገር ስምዖን ዘዐምድን ያሳያል ።
ቆመ፡ ተገተረ—(ቀወመ) ።
ቆመልኝ፡ ባለጋራዬን ሞገተልኝ ።
ቆመብኝ፡ ጠበቃ ኾነብኝ ።
ቆማ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ። "ቆማ ፋሲለደስ" እንዲሉ።
ቆማ፡ የሩቅ ሴት ቦዝ አንቀጽ/ንኡስ አገባብ (ተገትራ ") ። "ልጃገረዲቱ ባል ሳታገባ እንዲሁ ቆማ ቀረች" ።
ቆሜ፡ የዜማ ስም (ረዥም ዜማ የቆማ ቆማዊ ማለት ነው ") ።
ቆም (ቀዊም)፡ መቆም ።
ቆም፡ ቁመት ።
ቆም አለ፡ ፈጥኖ ቆመ ።
ቆሞስ (ሶች)፡ ማዕርጉ በኤጲስቆጶስና በቄስ መካከል የኾነ መነኵሴ ምንኵስና ሰጪ ታቦት ባራኪ ።
ቆሬ ። ቃረ (ትግ ቀሐረ)፡ ተኰሰ ፈጀ አቃጠለ ። ሥሩ በግእዝ "ቀርሐ" ነው ።
ቆሬ (ዕብ ቆራህ)፡ የሰው ስም፡ ከሌዊ የተወለደ የሌዊ ዘር ።
ቆሮ (ዎች)፡ የኦሮ የሻንቅላ ዋና ባላባት አምሳለ ንጉሥ ።"አባ ቆሮ" ቢል የቆሮ ኣባት ማለት ነው ።
ቆቁ፡ ያ ቆቅ ።
ቆቅ (ቆቃሕ)፡ በዱር የሚኖር የዶሮ ዐይነት ፍጥረት ። ተባቱም እንስቱም ቆቅ ይባላል ። (ተረት)፡ "እኔ ዐውቃለኹ የቆቅ መላ፡ ወይ በራለች ወይ ደፍጣለች" ። ሲበዛ "ቆቆች" ያሠኛል ።
ቆቅ ማሪ አቦዬ፡ የንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ አባት አቶ አቦዬ አንድ ሰው ቆቅ ቢያመጣላቸው በርኅራኄ ስለ ለቀቋት "ቆቅ ማሪ" የስማቸው ቅጽል ኹኖ ሲነገር ይኖራል ።
ቆቅ፡ ንቁህ ጠን ቃቃ ሰው ።
ቆቅማ፡ ቆቅ የሚመስል ዶሮ ።
ቆቋ፡ ያች ቆቅ ።
ቆበ ጣል፡ ቆቡን ከራሱ አውልቆ የጣለ የወረወረ ያሽቀነጠረ ።
ቆበ ጥላ፡ ቆብ ጥላው፡ ቆቡን እንደ ጥላ የሚቈጥር ዓለማዊ መነኵሴ ።
ቆበተ፡ ቁባት አደረገ (ጠበቀ ") ።
ቆበተ፡ ጠበቀ ዐቀበ ።
ቆባስጥል (ቆብ አስጥል)፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ (ታቹ ገደል ላዩ ቆብየሚ ያስጥል ኀይለኛ ነፋስ የሚነፍስበት ሜዳ ") ።
ቆብ (ቦች - ቆብዕ)፡ ከሰሌን ከሸማ ከክር ከጠጕር ከሣር ገመድ ከበርኖስ የተበጀ (የራስ ማግቢያ መክደኛ ") ። የተባረከ መንፈሳዊ ምሳሌ፡ ምሳሌነቱም የንጽሐ መላእክት ነው ። ሌላም የአይሁድ የስላም የባኒያን የፈረንጅ ቆብ አለ ። "ባርሜጣን" እይ ።
ቆብ ፵ነ፡ መነኰሰ ።
ቆቱ ቀተረ፡
ቆቱ፡ የሐረርጌ ኦሮ ስም (ወራሽ ቈፋሪ ማለት ነው ") ።
ቆን በቀር ሌላ ሰው አይገባበትም ።
ቆንስል (ሎች)፡ የፈረንጅ ንጉሥ መልክተኛ በኼደበት አገር ለወገኖቹ ዳኛ ጠባቂ ለላከው መንግሥት ወኪል ኹኖ በባዕድ አገር የሚቀመጥ ።"የንግሊዝ የፈረንሳይ የጀርመን የመስኮብ የጣሊያን ቆንስል" እን ዲሉ። በፈረንጅኛ "ኮንሱል" ይባላል ።
ቆግላ (ኦሮ - ጎግላ - ክንፍ)፡ ርግብግብ ለማጣ ሰው ።
ቆፍ (ዕብ)፡ ዝንጀሮ (በብዙ ወገን ሰውን የሚመስል አውሬ ") ።
ቆፍ፡ የፊደል ስም (ቀ ") ።
ቋ
ቋ (ኳ)፡ መሰበር መጮኸ ።
ቋ፡ መጮኸ ቋቋ ።
ቋ ሣር፡ አንጓ ያለው ወፍራም ሣር፡ ሲሰብሩት የሚቀለጠም ቋያ ።
ቋ እቋ አለ፡ ተሰበረ ተሰማ ። "የሙክቱ እግር እቀጭ እቋ ይላል" ።
ቋሊማ ማለት አንዠቱ እ ንደ ቀለም (ቀሠም) ውስጠ ክፍት መኾኑን ያሳያል ። ፈረንጆች "ሶሲሶ" ይሉታል ።
ቋመጠ፡ ጐመዠ ሠየ፡ አኹን አኹን አለ ።
ቋሚ (ዎች - ሞች)፡ ቀን ዕንጨት ። እየሰበረ ማታ በጌታው ፊት የሚቆም አሽከር ሎሌ ። "ቋሚ ለጓሚ" እንዲሉ።
ቋሚ፡ ለቤት ሥራ በምድር የሚተከል አራት ማእዘን ዕንጨት ወይም ብረት ።
ቋሚ፡ በሕይወት ያለ ።
ቋሚ፡ ድግስ ሲበላ ሲጠጣ ዐዳይ አሳላፊ አስተናባሪ ።
ቋሚነት፡ ቋሚ መኾን (ፈላጭነት ") ።
ቋማጭ፡ የቋመጠ/የሚቋምጥ (ጕምዡ ") ።
ቋም፡ የውሃ መጠን ዘንግ አቁሞ ወይም በቁመት የሚለካ መልካ ሜዴ ቆመው የሚሻገሩት ። "ወደ ፊት አቋምን" እይ ።
ቋም—ሜዴ—ቆመ ።
ቋሳ (ቈስያ)፡ የተክል ስም (ዱባ ") ።
ቋረኛ (ኞች)፡ የቋራ ሰው የቋራ ተወላጅ ። "ቋረኛ ኢያሱ" እንዲሉ ።
ቋሪት፡ በጐዣም ውስጥ ያለች ቀበሌ ።
ቋሪት፡ የቀበሌ ስም ።—ቋር ።
ቋራ፡ በበጌ ምድር አውራጃ ያለ አገር ስም ።
ቋራም (ሞች)፡ ቋር ያለው (ባለቋር ራሳም ጕጣም ") ።
ቋራም፡ ዱላ እንዲሉ ።
ቋሬ - ቋራዊ፡ የቋራ አገር ልብስ ሸማ (በቋራ ተፈትሎ የተሠራ ዝቅዝቅ ገበርባሬ ") ። በትግሪኛ ግን "ጃኖ" ማለት ነው ።
ቋር፡ የንጨት የፈትል ቋጣራ ("(ዐይን) ጕጥ ") ።
ቋር፡ የዱላ ራስ ።
ቋርፍ፡ የዱር ፍሬና ሥራሥር (እንቅ ርብጭን የወፍ ቈሎን የመሰለ ") ። "የመናኝ የዝንጀሮ ምግብ" ።
ቋሮ፡ ራሳም ዓሣ ።
ቋሸ)፡ አቋሸ፡ ሥጋን በንጀራ አጣበቀ ያዘ፡ ዐንከ በላ፡ በጥርሱ እንደ ቈሻ አደቀቀ/አለነቀጠ ።
ቋቍቻ (ቈቍዐ)፡ የገላ በሽታ (የዕ ከክ ዐይነት፡ ዐንገትን ጕንጭና ጕንጭን ደረትን የሚያሳክክ የሚያፍረከርክ ሴቴ ") ።ዳግመ ኛም አጓጐት ይባላል ("(ዘሌ. ፲፬፥ ፶፮)") ።
ቋቅ (ቀዪእ)፡ ማስታወክ ማውጣት ።
ቋቅ አለ (ቄአ)፡ አስታወከ አስመ ለሰ ።
ቋቅ አለው፡ ጐጓው አስታወከው ።
ቋቋ (ቆቅሐ - ቃሕቅሐ)፡ ቍር ።
ቋቋ አደረገ፡ ኳኳ መታ መታ አደረገ ።
ቋቋቴ - ኳኳቴ፡ ቋቋ ።
ቋቋቴ - ኳኳቴ፡ የንጨት (የጦጣ ቍላ ") እንቡጥ እረኞች እያፈነዱ የሚያንቋቁት የሚ ያስጮኹት ።
ቋቋቴ፡ የጣት አንጓ ።
ቋቋቴ፡ ያሮጌና ያሮጊት ወገብ ሲጫ ኑት፡ የሚንቋቋ ።
ቋተ - ኰዐተ)፡ አቋተ፡ ቋት እ በጀ፡ እቋት ጨመረ ደቀነ ጥሬ እኸልን ።
ቋተ - ኰዐተ)፡ አቋተ፡ ቋት እ በጀ፡ እቋት ጨመረ ደቀነ ጥሬ እኸልን ።
ቋቱ ጠብ አለ፡ ጥቂት ጥቅም ተ ገኘ ።
ቋቱ ጠብ አላለለትም፡ አላገኘም ("እንጀራ አልጠገበም ሆዱ ") ።
ቋቲሮ፡ ቅልጥማም አሞራ (ሽመላ ")፡ ቀጪንና ረዥም ሰው/ከብት ("እንደ ሰጐን ያለ ") ።
ቋታ - ቋቅታ፡ ቋቅ ማለት ! ጓታ፡ እውከት ምላሽ ።
ቋት (ምእላደ ሐሪጽ)፡ የዱቄት መፍሰሻ/መግቢያ/ማረፊያ/መጠራቀሚያ/መከ ማቻ፡ በማቋቻ አንጻር በስተታች ያለ ጕድጓድ (ከጭቃ ከሸክላ የተሠራ ") ።
ቋት፡ ሆድ ።
ቋትለኛ (ኞች)፡ የቋትል ወገን (ዋነተኛ መርከብ መሪ ") ። በግእዝ "ኖትያዊ ኅ ዳፍ" ይባላል ።
ቋትል፡ ከባሕር ከማዕበል ከጐርፍ ከውሃ ምላት ጋራ የሚታገል/የሚጋደል (ዋና ዐዋቂ ") ።
ቋና፡ በበጌ ምድር ክፍል ያለ አገር ።
ቋን ጣዊ፡ የቋንጣ ማለት ነው፡ የጠፍሩን ድርቀት ያሳያል ።
ቋንቍራ፡ ቅራቅንቦ ዕቃ ግሴት ሰባራ ሥንጥር፡ መንገደኛ የሚይዘው ቅል ወረ ንጦ ።
ቋንቍሬ ባቡ ። ቋንቍሬ፡ የኔ ቋንቍራ ።
ቋንቍሬ፡ የስም ቅጽል (የቋንቍራ ቋንቍራዊ ") ።
ቋንቋ ለወጠ፡ ሌላ ልሳን ተናገረ ።
ቋንቋ፡ ልዩ ልዩ ሕዝብ ("(ራእ. ፲፬፥ ፮፡ ፲፯፥ ፲፭)") ።
ቋንቋ፡ አፍ ልሳን ነገር የምላስ ፍሬ ባንደበት ሲነገር የሚሰማ ("(ግብ. ሐዋ. ፪፥ ፮፡ ፮፥ ፲፩ ። ፩ቆሮ. ፲፪፥ ፲)") ። "እከሌና እከሌ ቋንቋ ለቋንቋ ይተዋወቃሉ" ። ሲበዛ "ቋንቆች" ያሠኛል ። በጋልኛ ጕረሮ ቆንቆ ይባላል፡ በምስጢር ከዚህ ጋራ ይሰማማል ። ሰው በየጊዜው እንዲ ወለድ ቋንቋም በየዘመኑ ይፈጠራል ። "ዘነጠንና ጦለበን" ተመልከት ። መደበኛው የኢትዮጵያ ቋንቋ ግእዝ ዐማርኛ፡ ሌሎችም ትግሬ ትግሪኛ አገውኛ አዳልኛ ወላምኛ ጋልኛ ሱማልኛ የከፋ የሲዳሞ የሻንቅላ፡ ከነዚህም በቀር ብዙዎች ዘርፎች አሉ ።
ቋንዣ ቈረጠ፡ እግርን ሰነከለ ።
ቋንዣ ቈራጭ፡ ዐመፀኛ ወንጀለኛ ሽፍታ ምሕረት የማይገባው ።
ቋንዣ፡ ከጕልበት በስተኋላ ከባት በ ላይ ያለ፡ የእግር ማጠፊያ፡ ዋና የደም ሥር ። ሲበዛ "ቋንዦች" ይላል ።
ቋንዶ (ዎች)፡ ያረግ ስም (ጥኑ ጠንካራ ዐረግ ") ።
ቋንዶ ዐረግ (ቀንደ ሐረግ)፡ ያረግ ቀንድ (ዋና ዐረግ ") ።
ቋንጃ፡ የእግር ማጠፊያ (ቋንዣ ") ።
ቋንጅል (ሎች)፡ ቅል ቅምጫና ።
ቋንጢት፡ ከሲታ ሴት ። "ንሺ ቋንጢት" እንዲሉ።
ቋንጣ (ነቅጸ)፡ ተዘልዝሎ የደረቀ ሥጋ ።
ቋንጣ፡ ቀጪን ሰው ኰስማና አካለ ደረቅ ።
ቋንጣ፡ በንዝርት ራስ ላይ ያለች ቈ ላፋ የሽቦ ብረት ።
ቋንጣ፡ ደረቅ የበለስና የወርካ ፍሬ ።
ቋንጤ፡ በቈዳ የተታታ ወንበር ።
ቋንጦች፡ የደረቁ ዝልዝሎች በለሶች፡ ሽቦዎች፡ ኰስማኞች ሰዎች ።
ቋኛት (ቶች)፡ ካረግ ከመቃ የተበጀ ሞላላ ቅርጫት ዓሣ መያዣ ።
ቋኛት ሆድ፡ ሆዱ እንደ ቋኛት የ ኾነ ሰው ።
ቋዝመን፡ እንደ ጩቤ ያለ ታናሽ ካራ ጋፋቶች የሚታጠቁት ።
ቋያ፡ ቋ የበረሓ ሣር ሳይታጨድ ቈይቶ የደረቀ ። "የቋያ እሳት" እንዲሉ። "ሰደደ" ብለኸ "ሰደደን" ተመልከት ።
ቋድ (ዶች)፡ የጠፍር የክር የገመድ የሐር የጥለት የሽቦ አራት ማእዘን ጕንጕን ። ፈረንጆች ቋድን "ኮርዶን" ይሉታል ።
ቋድ አበጀ (ትግ. ቀወደ ቆደ)፡ ወዘበ ዕዛብ ሠራ ጐነጐነ አጠላለፈ ከቈዳ ።
ቋድ፡ ዛብ ሥራ ማተብ ።
ቋድ፡ የዱሮ ጠመንዣ ስቦ መተኰሻ ።
ቋጠረ (ቈጸረ)፡ በሆድ በልብስ ያዘ (አረገዘ ዐቈረ (ምሳ. ፴፥ ፬፡ ኢዮ. ፴፩፥ ፰፡ ፴፯) ።
ቋጠረ፡ ነገር ፀነሰ ዠመረ ወጠነ፡ ሤራ ዐድማ አደረገ ። "አቶ እከሌ የቋጠረው አይፈታም" እንዲሉ።
ቋጠረ፡ አሰረ ቀጠለ ።
ቋጠረ፡ እሰጥ አለ፡ ውርርድ ተከለ (ጐንደር) ።
ቋጠረ፡ ጣቱን ከጣቱ ጋራ አዋሰበ፡ ጋንን ከነአተላውና ከነጠላው ለማንሣት ።
ቋጠረ፡ ፊቱን ኰፈተረ ሰገጠ ጨመ
ቋጠራ፡ አሰራ እርግዝና ።
ቋጣሪ (ዎች)፡ የቋጠረ/የሚቋጥር (አ ሳሪ ቀጣይ ሸማኔ ሢረኛ ") ። "ነገር ቋጣሪ" እንዲሉ።
ቋጣራ፡ ዕጢ የንጨት ዐይን ቋር ጕጥ ።
ቋጣራነት፡ ቋጣራ መኾን፡ ጕጕለት ።
ቋጣሮ፡ ቈቀር ቡጢ፡ የተሳሰረ ሣር፡ የቅጠል ችቦ ("(ማሕ. ፩፥ ፲፫)") ።
ቋጥኝ (ኞች - ቀጣ)፡ ገለብ ገዎቻ ከገደል ተቀርፎ ወይም ተቈርጦ የወረደ ደንጊያ ቤት የሚያኸል ።
ቋጨ (ትግ. ቈጸየ)፡ ጠመዘዘ ኣ ከረረ ጠመረ ገመደ (፪ቱን ወይም ፫ቱን ፈትል ደበለ አንድ አደረገ ") ።
ቋጨራ፡ የታሰረ ጓሳ ነዶ (አንድ ጭብጥ ") ።
ቋጪ፡ የቋጨ/የሚቋጭ (አክራሪ ጠ
ቋፈ) አቋፈ፡ ቈነነ ቀስ አደረገ በመንገድና በምግብ ላይ ።
ቋፍ፡ በገደል ላይ የዝንጀሮ አቀማ መጥ ።
ቋፍ፡ ጫፍ አፋፍ፡ ዐጕል ኑሮ ። "በቋፍ አትቀመጥ ትወድቃለኸ" ።
ቀጠን (ቀጢን)፡ መቅጠን ።
ቀጠን አለ፡ ቀጠነ ።
ቀጠን ያለ፡ የቀጠነ ።
ቀጠጠ (ረትዐ - ትግ. ቀጸጸ - መላ. ዕብ. ቃጻጽ)፡ ቈረጠ ዐወደ ሸ ለተ ።
ቀጠጠ፡ ነፋ አሳበጠ ቀሰጠጠ ።
ቀጠጠ፡ ገብጠትንጠማማነትን አራቀ ።
ቀጠጣ፡ ቈረጣ ሽለታ ።
ቀጠጥና፡ ቀጥታነት ያለው ቀጪን ዕንጨት መጠነ ታናሽ፡ የቅጠሉ ስም ያህያ ዦሮ ነው ። "ደባክድን" ተመልከት ።
ቀጠጥና፡ ዕንጨት ። ቀጠጠ ።
ቀጠጦ፡ ፍሬው ቀጫጫ የኾነ ማሽላ ።
ቀጠፈ (ቀጢፍ ቀጠፈ)፡ ቈረጠ ሰበረ ቀነጠበ (ርጥብ ቅጠልን ") ።
ቀጠፈ፡ በልጅነት ገደለ ። "ቀሠፈን" እይ ።
ቀጠፈ፡ ዐበለ ዋሸ ።
ቀጠፋ፡ ቈረጣ ቅንጠባ ።
ቀጠፋ፡ የቅኔ ጫፍ፡ መነሻ የሌለው ኹለት ቤት ቅኔ ።
ቀጣ (ቀጽዐ)፡ አሰረ መታ ገረፈ ።
ቀጣ፡ ከላይ ዐንገትን ከታች ባትን ጐመደ ቈረጠ ።
ቀጣ፡ ገንዘብ አስከፈለ ።
ቀጣሪ (ሮች)፡ ዐጥር ያጠረ/የሚያ ጥር፡ አሽከር የቀጠረ/የሚቀጥር ።
ቀጣቀጠ፡ ደባደበ/ወቃቀጠ ።
ቀጣቢ፡ የቀጠበ/የሚቀጥብ (ከንጂ አመልካች ሸማኔ ") ።
ቀጣኒት፡ የቀጠነች ምድር ሴት
ቀጣኒት፡ የተንቀሳቃሽ ስም፡ መልኳ ላይ ላዩ አረንጓዴ ታች ታቹ ብጫ የኾነ የአንበጣ ወገን፡ ዳግመኛም ያቦ ፈረስ ትባላለች ።
ቀጣና (ኖች)፡ በገደልና በገደል መካከል ያለ ዕርከን የቃጥላ አረፍት ሰው የሚያልፍበት ከብት የሚሰማራበት ።
ቀጣይ (ዮች)፡ የቀጠለ/የሚቀጥል (አካይ ተከታይ ቋጣሪ ") ።
ቀጣጠለ፡ ጨማመረ ቈጣጠረ ገጣጠመ ። "፬ኛውን ና" እይ ።
ቀጣጠፈ፡ ቈራረጠ ቀነጣጠበ ።
ቀጣጣይ (ዮች)፡ የቀጣጠለ/የሚቀ ጣጥል (ነገረሠሪ ") ።
ቀጣጣፊ፡ የቀጣጠፈ/የሚቀጣጥፍ ።
ቀጣፊ (ፎች)፡ የቀጠፈ/የሚቀጥፍ (ቈራጭ ") ።
ቀጣፊ ሌባ፡ ዐባይ ዋሾ ቈርጦ ቀ ጥል ("(ሚክ. ፮፥ ፲)")
ቀጤማ - ቄጠማ፡ በረግረግ ላይ የሚበቅል ለምለም ሣር ("(ኢዮ. ፰፥ ፲፩)") ። "የፀሓይ ጥላ ለእረኛ፡ የዝናም ልብስ ገሣ ምንጣፍ ኬሻ ይኾናል" ። በግእዝ "ሰት" ይባላል ። "ለመለመ" ብለኸ "አለመለመን" እይ ።
ቀጥ፡ መቅናት ።
ቀጥ አለ፡ ቀና ።
ቀጥ አደረገ፡ አቀና ።
ቀጥሎ፡ ቦዝ አንቀጽና ንኡስ አገባብ፡ አክሎ ቋጥሮ ጨምሮ ተከትሎ ። በደጊመ ቃል ሲነገር "ቀጥሎ ቀጥሎ" ይላል ።
ቀጥቃጭ (ጮች)፡ የቀጠቀጠ/የሚቀጠቅጥ (ብረተ ሠሪ ጠይብ ባለጅ ") ።
ቀጥቃጭነት፡ ቀጥቃጭ መኾን፡ ባለጅነት/ሠራተኛነት ።
ቀጥታ፡ ቀጥ ማለት፡ ወይም ቀጥ ያለ ዙሪያ ጥምጥም ያይዶለ ። "ቀጥታ መንገድ" እንዲሉ። "በቀጥታ መጣ፡ በቀጥታ ኼደ" ቢል፡ ግራ ቀኝ ሳይል ያሠኛል።
ቀጨ (ትግ. ቀጸየ)፡ ስንደዶን አ ክርማን እሸትን ከላይ ከመካከል ቈረጠ ነጨ ገነጠለ፡ አጠፋ አበላሸ (ሰብልን ") ።
ቀጨ (ትግ. ቈጸየ - ወለም አለ)፡ ትከሻን አሳመመ (ሥርን አዞረ ") ። "ገን" እይ፡ በግእዝ መሠረቱ "ቀጽዐ" ነው ።
ቀጨ፡ ቀሠፈ/አለዕድሜ በልጅነት ገደለ ።
ቀጨለ፡ ቃጨለ፡ ጮኸ ከለለ ተሰማ ። "በቀለ አቅጨለጨለን፡ በቃጨለ አቃወለን" ይመለከቷል ።
ቀጨመ፡ ቅም ያዘ አፈራ (ገቢር) ።
ቀጨሞ (ዎች)፡ የንጨት ስም፡ ፍሬው ሲቀምሱት የሚጐመዝዝ የሚያስቀምጥ ቀጪን ዕንጨት ።
ቀጨቀጨ፡ በጥርሱ ስበረ ቀጠቀጠ ዐኝ ዐኝ አለ አደቀቀ ።
ቀጨቀጭ፡ በጤፍ ውስጥ የሚበቅል ዐረግማ ቅጠል፡ ጤፍ እንጀራ ሲበሉ ቀጥ ቀጭ የሚል ።
ቀጨኔ ።
ቀጨኔ፡ ባዲስ አበባ ውስጥ ያለ ቀ በሌ ። "ቀጨኔ መድኀኔ ዓለም" እንዲሉ።
ቀጨጨ (ቈጢጥ ቈጠጠ)፡ ቀጠነ ኰሰመነ ሰለተ ።
ቀጪ (ቀጻዒ)፡ የቀጣ/የሚቀጣ (መቺ ገራፊ ") ። "አንጥያኮስ በእስራኤል ላይ ግፍ ስለ ሠራ ቀጪ አዘዘበት" ።
ቀጪነት፡ ቀጪ መኾን ።
ቀጪኔ (ዎች)፡ የግመል ዐይነት የዱር እንስሳ፡ ነብርማ ዐንገቱና የፊት እግ
ቀጪኔ፡ ነጭ አደንጓሬ ።
ቀጪኔ፡ የስንዴ ስም፡ በጣም ቀጪን
ቀጪኔ፡ ጐራዴ ። "ሾተልን" ተመልከት ።
ቀጪን (ኖች - ቀጢን)፡ የቀጠነ (የማነነ ሞናና ሰው ፈትል ሸማ ፉጨት ") ። "ቍጥኔን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው ።
ቀጪን ሊጥ፡ ውሃ የበዛበት ቡሖ ።
ቀጪን ሠጥር፡ ከጐድን ኹሉ የም ትቀጥን ታናሽ የጐን ዐጥንት ።
ቀጪን እመቤት፡ ከድኸነት የወጣች ራሷን የቻለች ።
ቀጪን ፈታይ፡ ኩታው በቀለበት የሚሾልክ ድርና ማግ የምትፈትል ሴት ።
ቀጪንነት፡ ቀጪን መኾን ።
ቀጪኖ፡ ዝኒ ከማሁ ለቀጪኔ ።
ቀጪዎች - ቀጮች፡ ጕዲት ግራኝ ዐጤ ቴዎድሮስ ሐበሻን እንደ እስራኤል ፫ ዘመን የቀጡ፡ በዚህ ላይ የፋሺስት ሲ መር ፸፭ ይኾናል።
ቀጫጫ (ጮች)፡ የቀጨጨ (ቀጪን ኰስማና ") ።
ቀጫጯን (ኖች)፡ ብዛቱና ቅጥነቱ ባንድነት የሚታይ ውዥኝን ዐደይ አበባን ፍየለ ፈጅን ቀጨሞን የመሰለ ።
ቀጭ ። ተጭ ።
ቀጭ አደረገ፡ ጨ መታ ።
ቀጭ፡ ከንፈርን የሚያቈስል አግርን የሚሠነጥቅ ብርድ ውርጭ ።
ቀጭ፡ የቀጨ/የሚቀጭ (ቈራጭ ገን ጣይ ") ። "ዝርዝረ ቀጭ" እንዲሉ።
ቀጭቀጨ፡ በውጋዴ በረሓ የሚገኝ ቅጠል የግርሽጥ ዐይነት፡ ሰው ኹሉ እያኘከ ውሃውን ይመጠዋል ።
ቀጭታ፡ የቀጨች/የምትቀጭ ።
ቀጸለ፡ ትምርትን አጠና ጨመረ ።
ቀጸለ፡ ዐማ ነቀፈ ስም አጠፋ ።
ቀጸለ፡ ደረበ በላይ አደረገ ("(ግእዝ)") ። "ከተለን" "ቀጠለን" ተመልከት ።
ቀጸላ፡ ኅባኔ (ሻሽ የራስ የፊት መሸፈኛ፡ ዐይነ ርግብ ወገሮ ሠርመዲ በዙሪያው የወርቅ መርገፍ ያለበትና የሌለበት የሐር የፈትል የግምጃ አጣፊኝ፡ ሥሥ ቀጪን መደረቢያ ") ("(፩ነገ. ፳፥ ፴፰)") ።
ቀጸላ፡ ዐሰላ ። ቀጠለ ።
ቀጸላ፡ የማር እንጀራ ። ቀጠለ ።
ቀጸላ፡ የወንድና የሴት የክርስትና ከፊለ ስም (በሕዝብ አነጋገር ቀጠላ ይባላል ") ።
ቀጸበ (ቀጺብ - ቀጸበ)፡ ጠቀሰ ባ ይን በጣት ጠራ አመለከተ አዘዘ፡ አፈጠነ ።
ቀጻ (ቀጽዐ)፡ ባንድ ልክ ብራናን ወረቀትን ቈረጠ አፈፈ ቀፈፈ ።
ቀፈረ፡ አቆመ ዘረጋ ዦሮን፡ ፊት ለፊት ቀቀረ፡ የከብት ።
ቀፈረረ - ከፈረረ)፡ አንቀፈረረ፡ አረዘመ ("(ረዘመ)") ።
ቀፈረር - ቀፍራራ፡ የተንቀፈረረ (እንቅፍር ርዝማኔው የሚያስቀይም ") ።
ቀፈቀፈ፡ በሳ ሰበረ ዕንቍላልን፡ ፈለ ፈለ ብዙ ወለደ ጫጩትን ዶሮው ሰው ።
ቀፈቀፈ፡ ግራና ቀኝ እየመታ ከመካ ከል ከረከረ ። የቀፈፈንና የቀፈቀፈን ልዩነት አስተውል፡ "ቀረቀፈን" እይ ።
ቀፈታም፡ ሆደ ዘርጣጣ ቦርጫም ።
ቀፈት (ቀፈፈ)፡ ቀፈድ የቈርበት ቀለበት ። በግእዝ ግን ፵ንቃ ደንደስ ማለት ነው ።
ቀፈት መራ፡ ቈርበትን ጠለፈ አያያዘ ወይም ቈዳን ወጠረ ገደገደ ።"ቀፈደን" እይ ።
ቀፈት፡ ትልቅ ሆድ ቦርጭ ደንደስ መሳይ ("(ጐንደር)") ። "ቈለፈ" ብለኸ "ቈለፈትን" ተመልከት ።
ቀፈት፡ የጠፋ ከብት ጭገሬታ ምል ክት ።
ቀፈደ፡ ቅፍንድን በሳ፡ ቀፈድ አበጀ፡ እሱንም እየጠለፈ አሰረ፡ ሸክምን ሣርን ነዶን ገለባን ዕቃን ።
ቀፈደደ፡ ማሰሪያን በመጠምጠም አጥ ብቆ አሰረ ሰውን ("(ገቢር)") ።
ቀፈደደ፡ ደነዘዘ ፍጥነት ቅልጥፍና አልባ ኾነ ("(ተገብሮ)") ።
ቀፈደድ - ቀፍዳዳ፡ ደነዝ ደንዛዛ ።
ቀፈዲያም፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቀፈዳም - ቀፈታም፡ ሰውነተ ሻካራ ቈ ርፋዳ ።
ቀፈድ - ቀፈት፡ በቈርበት ዙሪያ በቅፍንድ ግፍ ያለ ቀዳዳ ጠፍርና ገመድ የሚያ ስገባ ። ቀፈድና ቀፈት አንድ ስም ነው ።
ቀፈፈ፡ ለመነ፡ መንደር ለመንደር እየዞረ "በአንተ ስማ ለማርያም ስለ ቸሩ እግዚአብሔር" አለ ።
ቀፈፈ፡ ሰቀጠጠ ጨመደደ ጨፈገገ ከበደ አሳመመ ። "ዛሬ ሰውነቴን ይቀፈኛል" ።
ቀፈፈ፡ ቈረጠ ከረከመ አስተካከለ የቈዳን የብራናን የቅልን ጫፍ ። "አፈፈን" አስተውል ።
ቀፈፋ፡ ክርከማ ልመና ።
ቀፋሪ፡ የቀፈረ/የሚቀፍር (ቀቃሪ ") ።
ቀፋራ - ቅፍር፡ የተቀፈረ/ቅቅር ።
ቀፋፊ (ዎች)፡ የቀፈፈ/የሚቀፍ (ከር ካሚ ለማኝ ") ።
ቀፋፋ፡ ከርፋፋ ።
ቀፋፎ፡ ቀራፎ ሞኝ ።
ቀፍቃፊ፡ የቀፈቀፈ/የሚቀፈቅፍ (ፈልፋይ ከርካሪ ") ።
ቀፍዳጅ፡ የቀፈደደ/የሚቀፈድድ (አሳሪ ") ።
ቀፎ (ዎች)፡ ከሐ ረግ ከመቃ ከቀጯን ዕንጨት የተታታ የተሠባጠረ የንብ ቤት በኹለት ወገን አፍ በመካከል ፍንጭ ያለው ።
ቀፎ፡ ሆድ ውስጠ ክፍት ነገር ።
ቀፎ ለቀፎ፡ ውስጥለውስጥ ።"አቶ እከሌን የመታው ጥይት ቀፎ ለቀፎ ኼዶ ስለ ወጣ ሳይገድለው ቀረ" ።
ቀፎ ቈራጭ፡ ከቀፎ ውስጥ ማርን የሚቈርጥ ። መኪና ሰፊ እንደ ማለት ያለ ነው ።
ቀፎ፡ ያሣ መያዣ ።
ቍ ብሎ ዞላ ዋለ (ኤር. ፲፡ ፬፡ ሕዝ. ፵፭፡ ፳) ። (ተረት)፡ "በሰጡኸ አትስነፍ፡ ከሰጡኸ አትለፍ"።
ቍለላ፡ ክመራ ።
ቍለፋ፡ ቅርቀራ ሽጐራ ።
ቍላ (ቍልሕ)፡ በሰውና በንስሳበአራዊት ብልት ሥር ተንጠልጥሎ የሚታይ ሥጋዊ ጓሚያ፡ ፍሬ ቈለጥ ኹለትነት ያለው ።
ቍላ፡ ሙርጥ ዘንጉ ወንዳወንዴ ። "የመ ዝጊያ ቍላ" "የመርዋ ቍላ"፡ "ማሞ ቍላው ታሞ" እንዲሉ።
ቍላ ቀረሽ፡ ወንዲላ ኀይለኛዪቱ ሴት ("(መሳ. ፬፥ ፳፩)") ።
ቍላ በንቅብ፡ በላይ ወግዳና በቡልጋ ክፍል የሚገኝ ቀበሌ መዋጊያ ስፍራ ።
ቍላዎች፡ ቈለጦች ።
ቍሌት፡ ጥብስ (የሥጋ ወጥ ") ጥቂት እንጂ ብዙ ያይዶለ ውሃ ያነሰው ።
ቍልላት (ጕልላት)፡ የክምር የጕቾ ሥራ ኹኔታ ።
ቍልል (ጕልል)፡ የተቈለለ፡ ክምር (የ ሣር የገለባ ጕቾ ") ።
ቍልልታ፡ የደንጊያ የመሬት ክምር በዕለተ ፍጥረት የተቈለለ ከጕባ የቀጠነ ።
ቍልመማ፡ ቅለሳ ጥምዘዛ ።
ቍልምማት፡ ቅልሳት ጕብጠት ።
ቍልምም፡ የተቈለመመ (ዝልስ ዝቅዝቅ ቅልስ ጥምዝ ") ።
ቍልምጫ፡ የማይረባ ምስጋና ልምምጥ ("(ኢዮ. ፴፪፥ ፳፪)") ።
ቍልቍለት፡ ከደጋ ወደ ቈላ ከተራራ ወደ ጥግ መውረጃ መንገድ፡ በግእዝ "ቍልቍሊት" ይባላል ።
ቍልቍለቶች፡ ዘቅዛቆች ተዳፋቶች ("(ሕዝ. ፴፰፥ ፳)") ።
ቍልቍል፡ የተቈለቈለ፡ ዝቅዝቅ ታች
ቍልቍሎሽ፡ ዝኒከማሁ ለቍልቍለት፡ ዝቅዝቆሽ ።
ቍልቋል (ሎች)፡ በቈላና በወይናደጋ የሚበቅል ወተታም ዛፍ፡ ከሥር እስከ ጫፍ ትንንሽ እሾኸ አለው፡ ውስጠ ክፍት የኾነ ዕንጨቱ እየተፈለጠ ለጣራ ይኾናል ። (ተረት) ካጋም የተጠጋ ቍልቋል ሲያለቅስ ይኖራል።
ቁልቢ (ኦሮ)፡ ነጭ ሽንኵርት ።
ቁልቢ፡ በሐረርጌ አውራጃ ያለ አገር ። "ቁልቢ ገብሬል" እንዲሉ።
ቍልቢጥ (ጦች)፡ ቃጤ፡ ዕፍኝ የምትይዝ መስፈሪያ ።
ቍልዕ (ቀልዐ ከላ አስወገደ)፡ ቅምጥ ዐይናር መክላት ማስወገድ የሚገባው ።
ቍልዕ ለግእዝም ይኾናል።
ቍልጭ አለ፡ ቈለ ጥርት አለ ።
ቍልጭ፡ የቈለ/የጠራ/የበራ ።
ቍልጭልጭ አለ፡ ተቍለጨለጨ ።
ቍልጭልጭ፡ የተቊለጨለጨ/የሚቍለጨለጭ (የሰው የዥብሪ የተከበበ አውሬ ዐይን ") ።
ቍልጭልጭታ፡ የዐይን ጥራት ጥሩ ነት፡ ቍልጭልጭ ማለት ።
ቍልፋት፡ ቅልሳት ጕብጠት ።
ቍልፍ አለ፡ ቅልስ ዕጥፍ ዝግት አለ ። "እምግቡ ውስጥ ጕድፍ ቢገባበት አን ዠቴ ቍልፍ አለ" እንዲል ባላገር ።
ቍልፍ፡ የመዝጊያ የሣጥን የልብስ ማገናኛ በመክፈቻ በጣት የሚቈለፍና የሚከ ፈት (ጓጕንቸር አዝራር አግራፍ ባልና ሚስት ") (ጥሬ) ። (መርፌ ቍልፍ) መካከሉ ታጥፎ ዳርና ዳሩ የሚገናኝ የቀሚስ የጥብቆ መግጠሚያ ።
ቍልፍ፡ የተቈለፈ/የተዘጋ/የታጠፈ (ምላስ ዥራት ምልስ ቅልስ ዝግ ") (ቅጽል) ።
ቍልፍ፡ የድንኳን ጣራና ግድግዳ ማያያዣ የንሓስና የጥብጣብ ቀለበት ("(ዘፀ. ፳፮፥ ፮)") ።
ቍልፍልፍ አለ፡ ተቈላለፈ ።
ቍልፍልፍ፡ የተቈላለፈ ።
ቍልፍነት፡ ዝግነት ቅልስነት ።
ቍልፎች፡ ጓጕንቸሮች ቀለበቶች አዝራ ሮች ("(ዘፀ. ፴፭፥ ፲፯)") ።
ቁመተ ሥጋ፡ የሥጋ መቆም አቋቋም ። "አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለቁመተ ሥጋ በሑዳዴ ቅጠል ይበሉ ነበር" ።
ቁመተ ዶሮ፡ ዐጪር ሰው ።
ቁመታም፡ ቁመቱ የረዘመ (ሰማይ
ቁመት፡ በቁሙ ቆመ ።
ቁመት፡ የአካል ልክ መጠን (ከራስ እስከ እግር ከግራ እጅ ጣት እስከ ቀኝ ጣት የሰው፡ ከእግር እስከ ዠርባ፡ ከራስ እስከ ዥራት የእንስሳ፡ ከሥር እስከ ጫፍ ያለ የዛፍ ") ("(ሕዝ. ፲፱፥ ፲፩)") ። "ቁመተ ዐጪር ቁመተ ረዥም" እንዲሉ። በግእዝ "ቆም" ይባ ላል ።
ቁመና፡ የቁመት ኹኔታ ። "ይህ ሰው ቁመናው ያምራል።"
ቁመኛቡዳ—(ቀወመ) ። ቅማንጅር የቅማል ጓዝ፡ መለ ።
ቍመዳ፡ ድረታ ደፈና ።
ቁማር (ዐረ)፡ የንጉሥና የንግሥት ሥዕል ሌላም ምልክት ከቍጥርና ከፊደል ጋራ በላዩ ያለበት የጨዋታ ወረቀት ወይም ዕንጨት ። ሰውን ባንድ ጊዜ ያከብራል ያደኸያል ።ቁማርን መዠመሪያ ያወጡ የጢሮስና የሶርያ ሰዎች ናቸው ይባላል ።
ቁማርተኛ (ኞች)፡ ቁማር ወዳድ ተጫዋች ዐዋቂ ።
ቁማሽ (ዐረ)፡ ጣቃ ።
ቍማጭ፡ ቍራጭ ጕማጅ ።
ቁም (ቅዉም)፡ የቆመ/የተገተረ (ደማ ዊት ነፍስ ያለችው የቤት እንስሳ፡ ለዕቃም ይነገራል ") ። "ቁም ሣጥን" እንዲሉ።
ቁም ለቁም፡ ቀውላላ ሰውነቱን/ሰውነቷን የማይሰበስብ/የማትሰበስብ ።
ቁም ሥቃይ፡ የሥጋ መከራ ።
ቁም ስቅል፡ የተሰቀለ ሰውነት ጭንቅ ሥቃይ ። "ፋሺስቶች አንዱን ሐርበኛ ይዘው ቁም ስቅሉን አሳዩት" ።
ቁም፡ ቁመት ቁመና ። "ፍራት ከቁም ይጥላል" እንዲሉ።
ቁም፡ ትእዛዝ አንቀጽ ("አትኺድ ርጋ ቀጥ በል ") ።
ቁም ነገራም (ሞች)፡ ሐቀኛ እውነተኛ ልጨኛ የሰው ውለታ የማይቀርበት በቃሉ የጸና ።
ቁም ነገር፡ ሐቅ ርግጥ ጠቃሚ ጕዳይ ።
ቁም እስር፡ ሳይታሰር የተጋዘ ("ከዚህ ኣትለፍ" የተባለ ሰው ") ("(፩ነገ. ፪፥ ፴፮ - ፴፯)") ።
ቁም ከብት፡ ብርና ወርቅ ያልኾነ (በግ ፍየል ፈረስ በቅሎ አህያ ግመል በሬ ") ።
ቁም ዜማ፡ ዝማሜ ጽፋት መረግድ ጸናጽል ከበሮ የሌለበት ዋና ዜማ ።
ቁም ደንጊያ፡ የቆመ/የተገተረ (ያልተ ጋደመ ") ።
ቁም ጥፈት፡ ጕልሕና ማለፊያ ጥፈት፡ ረቂቅ ያይዶለ በሩቅ የሚታይ ሳይጋደም በቀጥታ የተጣፈ፡ ሰው ቆሞ በዘንግ መጠን የ ሚያነበው ።
ቁምስና - ቆሞስነት፡ ቆሞስ መኾን ።ቁምስና የግእዝ፡ ቆሞስነት ያማርኛ ነው ።
ቁምሶ፡ ከስንዴ ጋራ የተጋገረ እን ። ዘሩ ቀመሰ ነው ።
ቁምሩ፡ ታናሽ ርግብ ቡያ የወፍ ዐይነት ። ባረብኛ "ቁምሪ" ትባላለች ።
ቁምባ፡ ያገር ስም።
ቍምድ፡ የተቈመደ (ድርት ግብረ መርፌ ውስብስብ ") ።
ቍምጣ፡ ቁመቱ ከጕልበት በላይ የኾነ ዐጪር ሱሪ ወንበር የለሽ ። "ቍምጣ ሱሪ" እንዲሉ።
ቍምጤ፡ ብጣሽ ቍራጭ ነገር ።
ቍምጤ፡ የሣር ስም ።
ቍምጥ፡ ቍርጥ ጕምድ፡ መቈመጥ ። (ተረት)፡ "ቈማጣ ቢለው፡ ያው ቍምጥ ነው፡ ሌላ ምን ይመጣል" አለ ።
ቍምጥ አለ፡ ጕምድ ብጥስ አለ ።
ቍምጥ፡ የተቈመጠ፡ ቍርጥ ጕምድ ።
ቍምጥምጥ አለ፡ ቍርጥርጥ አለ ።
ቍምጥና፡ ቈማጣነት፡ ቢስ ገላ ደዌ ሥጋ ። (ተረት)፡ "ከሹመት ክፉ ግብዝና፡ ከበሽታ ክፉ ቍምጥና" ።
ቁሞች፡ ከብቶች እንስሶች ።
ቍስለ ሥጋ፡ የሥጋ ቍስል (ቍምጥና ወይም ሌላ ") ።
ቍስለ ነፍስ፡ የነፍስ ቍስል (ኀጢአት ነፍስን የሚጐዳ ") ።
ቍስለት፡ ንዝንዝ ጭቅጭቅ ።
ቍስለኛ (ኞች)፡ ተመቶ ተወግቶ ተገ ርፎ፡ ተቈርጦ፡ ተፈንክቶ፡ ተቃጥሎ፡ የቈሰለ ሰው (ባለቍስ ") ።
ቍስሉ ሰፋ፡ አፋገ በዙሪያ ጨመረ ።
ቍስላም፡ ቍስል ያለበት የበዛበት ።
ቍስል (ሎች)፡ ደምና መግል እዥ የሚፈሰው ዕከክዐይነት (ብጕንጅ ችፌቂጥኝ ") ።
ቍስል (ቍሱል)፡ የቈሰለ ("(ቅጽል)") ("(፪ነገ. ፰፥ ፳፱ ። ፱፥ ፲፭)") ።
ቍስቈሳ፡ ጠቀሳ/ጭመራ ።
ቍስቋም ማሪያም፡ የቍስቋም ማሪ ያም ።
ቍስቋም፡ እመቤታችን ተሰዳ የተቀመ ጠችበት የግብጽ ተራራ ።
ቍስቋም፡ የታቦት ስም (በኅዳር ፮ ቀን የሚነግሥ የመቤታችን ጽላት ") ።
ቍስቋሞች፡ የቍስቋም ካህናት እወዳ ሾች ።
ቍስጥንጥንያ፡ የቈስጠንጢኖስ መናገሻ ከተማ ።እንደ ፈረንጅ አቈጣጠር ካ፲፬፻፷፯ ዓ ም ወዲህ ግን የቱርክ መዲና ኾናለች ።
ቍረማ፡ ኵርኰማ።
ቍረንጮ፡ ያለቀ የደቀቀ አሮጌ ዝተት (ቍርጩ የሚለብሰው ") ።
ቍረንጯም፡ ቍረንጮ ለባሽ ።
ቍሪት፡ የግል ገንዘብ ቅርስ ።ባረብኛ "ሰና ተ ተወራራሽ" ስለ ኾኑ "ቍሪትና ቅርስ" አንድ ወገን ናቸው ። "ጥሪት ቍሪት" እንዲሉ ።
ቍራ (ሮች)፡ ጥቍር አሞራ (ሲጮኸ ቍር ዋዋ የሚል ") ("(ዘፍ. ፯፥ ፮ ። ፩ነገ. ፲፯፥ ፬ - ፯)") ። (ተረት)፡ "ጩኸት ለቍራ፡ መብል ላሞራ" ።ቍራ አራት ዐይነት ነው፡ ኹለቱ ፍጹም ጥቍሮች በደጋ በቈላ የሚኖሩ፡ ሦስተኛው በራሱ ላይ ነጭ አለበት፡ በምሳሌ እንደ ቄስ ይታሰባል፡ እንስሳ አውሬ በሞተ ጊዜ ኹለት ዐይን ያወጣል፡ ("(ለሌሎች ይባርካል)") ። "ቧሔ ቍራ" እንዲሉ ። አራተኛው ደረቱና ዐንገቱ ነጭ ነው መጠኑም ከሦስቱ ያንሳል ። ቍራ በዕብራይስጥ "ቆሬእ" በግእዝ "ቋዕ" ይባላል፡ ፈላስፎች ፪፻ ዓመት ይኖራል ይላሉ ።
ቍራ ይጮኸበታል፡ ከነዋሪዎቹ ክፋት የተነሣ አገሩ ከተማው ይፈታል፡ ጠፍ ይኾናል ("(ኢሳ. ፴፬፥ ፲፩)") ።
ቍራሽ (ሾች)፡ የዳቤ/የንጀራ ክፍል (ትልቁም ትንሹም ") ("(ዘፍ. ፲፰፥ ፭ ። ማቴ. ፲፬፥ ፳)") ። የዳቦ ሲኾን ጕርማጅ ይባላል ።
ቍራን (ዐረ ቀረአ - አነበበ)፡ የመ ጽሐፍ ስም (እስላሞች ለነቢያችን መሐመድ ከሰማይ ወረደ የሚሉት መጽሐፍ ") ። ብሉይንና ሐዲስን የሚያስተባብል ። ትርጓሜው ንባብ ("ምንባብ") ማለት ነው ። ባረብኛ "ቁርኣን" ይባላል ።
ቍራኛ (ኞች)፡ ከጠላት ጋራ የታ ሰረ እስረኛ (በሰው ያደረ መንፈስ ርኩስ ") ።
ቍራጭ (ጮች)፡ ጕራጅ ጕማጅ ሙዳ ዕራፊ ("(፪ሳሙ. ፭፥ ፩ ። ማቴ. ፱፥ ፲፮ ። ማር. ፪፥ ፳፩)") ።
ቍሬማ፡ እኸል፡ የማያበቅል፡ መሬት ።
ቍሬማ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ራሱ፡ በትር፡ ኵርኵም፡ ያረፈበት "
ቍር (ቅሩሕ - ቅሩዕ - ኵሩዕ)፡ የተቈራ/የተበጣ (ብጥ ቍርም ቡቅር ልጩ ") ። የራሱን ጠጕርና ጥፍሩን በገዳም ቀብሮ የኼደ ጠበለተኛ ።
ቍር፡ ቅዝቃዜ ።
ቍር፡ ቅዝቃዜ ።
ቍር፡ ብርድ/ቅዝቃዜ ። ባላገር ግን ቍር በማለት ፈንታ ቈራ ይላል ።"ቍርዬን" እይ ።
ቍር አደረገ፡ ሰበረ ቀፈቀፈ ፈለፈለ አወጣ መለሰ ።
ቍር፡ ዝኒ ከማሁ፡ ክርከማ ።"ጥፍር ቍርጫ" እንዲሉ ።
ቍር፡ የብረት ቆብ፡ ቈራ ።
ቍርማሚ፡ የዳቤ/የዳቦ ሾለቅ ("ኵርማን ቀንድ መስሎ የሚታይ ") ።
ቍርም፡ የተቈረመ።
ቍርምቢ፡ ወጠጤ፤ቍርንቢ ።
ቍርስ አለ፡ ተቈረሰ ።
ቍርስ አደረገ፡ ቍርስ በላ ተመገበ (አፉን አጝሸ ") ።
ቍርስ አደረገ፡ ቈረሰ ።
ቍርስ፡ የተቈረሰ/የተፈተተ ("(ቅጽል)") ።
ቍርስ፡ ጥቂት ምግብ (ጧት የሚበላ ሙሽት ") ("(ስም)") ።
ቍርስርስ - ቍርስራሽ፡ የተቈራረሰ (ክፍልፍል ክፍልፋይ ") ።
ቍርር፡ የተቈረረ (ድርብርብ ንብብር ድንጋይ ") ።"በቍርር ላይ ቍርር" እንዲሉ ።
ቍርሾ፡ ትንሽ ቂም የቈየ ።
ቍርቍምባ፡ ዓሣ መያዣ የሻታ ዐይነት (ባለገመድ ጠርሙስ መሳይ ") ።
ቍርቍሩ፡ ኵኵሉ ።
ቍርቍሩ፡ ያ ቍርቍር (የርሱ ቍርቍር ") ።
ቍርቍራ፡ የዛፍ ስም (ፍሬው የሚበላ የበረሓ ዕንጨት እሾኸ ቈላፋ ") ። በዜጋመል "ገባ" ይባላል ።
ቍርቍር፡ በተጕለት ውስጥ ያለ ቀ በሌ ።
ቍርቍር አደረገ፡ መዝጊያ መታ ።
ቍርቍር፡ የተቈረቈረ የተበሳ ግንድ (የተደፈነ ድፍን ጥቅጥቅ ምሥርት ") ።
ቍርቍዝ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቍርቊስት፡ የዓሣ ስም (መናኛ ዓሣ ") ።
ቍርቊሻ፡ የጨዋታ የውጊት ፈተና ።
ቍርቈራ፡ ምሰት ቍፈራ ሽንቈራ ም ሥረታ ጕርበጣ ደፈና ።
ቍርቈራ፡ የጥሪ ምልክት ።
ቍርባ፡ ድንገተኛ በሽታ (የሚያስታው ክና የሚያስቀምጥ ሰውነትን የሚያደርቅ ") ።
ቁርባብቻ፡ ከቈዳና ከጨርቅ የተሰፋ ከረጢት ።
ቍርባን፡ ለግዜር ለጣዖት የሚቀርብ መሥዋዕት ዕርድ (ስንዴን ወይንን ዕጣንን የመሰለ የተቀደሰና ማለፊያ ስጦታ ኹሉ ") ።
ቍርባን ውጭ ክርስትና፡ (አይገባም የቀረው ነው)፡ አስቀድሞ ሊደረግ የሚገባው በኋላ እንዳይደረግ ለማስጠንቀቅ፡ "ቍርባን ውጭ ክርስትና" እየተባለ ይተረታል ።፫ኛውን ጠባ እይ ።
ቍርባን፡ የክርስቶስ ሥጋና ደም (በስንዴ ኅብስትና በወይን ጠጅ መልክ የሚሰጥ ") ።በሚገባ የተቀበለውን ወደ ፈጣሪ የሚያቀርብ ስለ ኾነ ፥ዳግመኛም ቄሱ ከጸሎትና ከቅዳሴ ጋራ በቅዱስ መንበር ላይ ላምላክ የሚያቀርበው በመኾኑ ቍርባን ተባለ ። (ግጥም)፡ "የግብጽ ሰዎች በስላም የተዋጡ ከቍርባን ይልቅ ትምርትን መረጡ፡ ጊዜ ሲመቻቸው ቍርባንን ሊገልጡ" ።
ቍርብ ጭታ፡ ዕትራት ።
ቍርብጭ አለ፡ ዕትር አለ ።
ቍርብጭ፡ የቈረበ (ጕርብ ") ።
ቍርታት (ቍርሐት)፡ ብጥታት ፍቅ ታት ቡቅራት ልጭታት ።"ቍርሐት" ባጤ ዘርዐ ያዕቆብ ታሪክ ይገኛል ።
ቍርንቢ፡ ተባት ፍየል (ታናሽ ወጠጤ ") ። ላውራ በግም ይነገራል ("(ሕዝ. ፴፬፥ ፪)") ።"ቍርን" "ቀርን" "ቢ" "ቢጽ" (ቀንዳም ቢጤ ማለት ይመ ስላል ") ። "ኵርንቢን" እይ ።
ቍርንባጥ፡ ዐጪር ።—ኵርንባጥ ።
ቍርንቦች፡ ተባቶች (ወጠጦች ") ("(ዘፍ. ፴፥ ፴፭)") ።
ቍርንድይ፡ የትንባኾ ልጥልጥ ።
ቍርንድድ፡ ደረቅ ሻካራ ከርዳዳ ቍጥርጥር የኾነ ጠጕር፡ ዘሩ ከረደደ ነው ።
ቍርንጭ፡ መጥፎ ጠባይ ያለው ሰው (ቈጭባራ ") ።"በመለ ቍርንጭ" እንዲሉ ።
ቍርንጭ፡ ዐጨርና ቍጥርጥር የሻንቅላ ጠጕር ።
ቍርኙ፡ የተቈረኘ የተጠመደ የታሰረ ።
ቍርኝት፡ የተቈረኘተ (ንፍ ሆደ ጒስር ") ።
ቍርዛም (ሞች)፡ ያልተገዘረ (ባለቍ ርዝ ") ።
ቍርዝ (ዞች)፡ የወይፈን የበሬ ብ ልት ።
ቍርዝ፡ ልንቡጥ ሽፍን ወሸላ ።
ቍርዝ፡ የተቈረዘ (ዛብ የሚመስል ጅ ራፍ ሽርብ ") ። ቍርዝ ያሠኘው ጥብቅነቱ ነው ።
ቍርዬ፡
ቍርጠማ፡ የመቈርጠም ሥራ (ጕርደማ ") ።
ቍርጠት፡ የሆድ በሽታ (አንዠትን እየቈረጠ የሚያም ") ። ትርጓሜው መቍረጥ መቈ ረጥ ። "ለሆድ ቍርጠት ብላበት ለራስ ምታት ጩኸበት" እንዲሉ ።
ቍርጠኛ (ኞች)፡ ርግጠኛ የማይወላውል የማያመነታ ።
ቍርጡ ታወቀ፡ ርግጡ እውነቱ ድ ርሱ መጨረሻው ተገኘ ተረዳ ።
ቍርጣ፡ ጭፍልቅ (የገላ ተኵስ በቁመት ") ።
ቍርጣሚ፡ ዕኛኪ ።
ቍርጣና ብርባሮ፡ መስቀልኛ የዠርባ ተኵስ (አግድምና ሽቅብ የተተኰሰ ") ። ከዚህ የተነሣ ቍስሉ ጠባሳው የሰንጠረዥ መደብ ይመስላል ።
ቍርጣና ብርባሮ፡ የዕዳሪ ዕርሻ ።
ቍርጥ፡ ርግጥ ያለቀ የተፈጸመ ("(ኢሳ. ፲፥ ፪)") ።
ቍርጥ ነገር፡ ያለቀ የደቀቀ ጕዳይ ።
ቍርጥ አለ፡ ብጥስ አለ ።
ቍርጥ ኾነ፡ ተረገጠ ተፈጸመ ።
ቍርጥ፡ የሰራዊት ክፍል (ልዩ ልዩ ጭፍራ ") ("(፩ሳሙ. ፲፫፥ ፲፯)") ።
ቍርጥ፡ የተቈረጠ (ጕምድ ሙዳ ሥጋ ") ። "እጀ ቍርጥ" እንዲሉ ። "ቈረፀን" እይ ።
ቍርጥ ፍርድ)፡ "ስቀለው ግደለው" የሚል ። "ገበዘ" ብለኸ "ግብዝን" እይ ።
ቍርጥማታም፡ ቍርጥማት የሚያጠቃው ሰው (ባለቍርጥማት ") ።
ቍርጥማት - የጡንቻ ህመም.
ቍርጥማት፡ ያጥንት/የጥርስ/የዥማት በሽታ ("(፩ነገ. ፲፭፥ ፳፫)") ።
ቍርጥም አደረገ፡ ቈረጠመ ።
ቍርጥም፡ የተቈረጠመ/የታኘከ (ዕኝክ ") ።
ቍርጥርጥ አለ፡ ብጥስጥስ አለ ። "እከሌና እከሌ ቍርጥርጥ ያለ ጥል ተጣሉ" ።
ቍርጥርጥ፡ የተቈራረጠ (ብጥስጥስ ") ። ቍርጥራጭ፡ ዝኒ ከማሁ (የበገና ጠፈር ጠፍር ") ።
ቍርጩ፡ አንዳች ኣልባ ።
ቍርጩ ድኻ፡ አገኛለኹ ከማለት ተስፋው የተቈረጠ (ወርቀ ለባሽ ይልሰው ይቀምሰው የሌለው למנו ዐዳሪ መናጢ ችግረኛ ") ።
ቍርጭምጭሚት (ቶች)፡ በኹለት ወገን ያለ የእግር ጕጥ (የጫማና የቅልጥም መገናኛ ") ("(፪ሳሙ. ፳፪፥ ፴፯ ። ሕዝ. ፵፯፥ ፫)") ።
ቍርጭኝ፡ ዐጪር ድጓ ሰንበት አ ምኜ ። "ቍርንጭን" "ቍረንጮን" "ቍርንጫጭን" እይ፡ የቈረጪ ዘሮች ናቸው ።
ቍርጭኝ፡ ዐጪር ድጓ ቈ ረጨ ።
ቍርፅ፡ የተቈረፀ፡ ቍርጥ ዐጪር የዜማ ምልክት ።
ቍርፌ፡ አሮጌ ጋሻ ።
ቍርፍድ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቍሻሻ፡ ጥራጊ እድፍ ጕድፍ ግባስ ። ቍሽሽ፡ መቈሸሽ ። ቍሽሽ አለ፡ ቈሸሸ ። መቈሸሽ፡ ማደፍ/መኵለፍለፍ ። መቈሸሻ፡ ቈሻሻ መኾኛ ።
ቍሽቢያም፡ የቍሽብ ወገን፡ ወስፋቱ እኸል የማይቀበል ።
ቍቁ (ቈቀወ)፡ ኡኡ ።
ቍቁ አለ፡ ጮኸ ("ኑልኝ ድረሱልኝ የሰው ያለኸ አለ ") ።
ቍቁታ፡ ቍቁ ማለት (የተገፋ የተበ ዶለ ሰው የሚያደርገው ጩኸት ") ።
ቍቁታውን ለቀቀ፡ ጩኸቱን አበዛ (አደጋ ስለ ደረሰበት ") ።
ቍቂያም፡ ፈሱን ቍቅ ያደረገ ሰው (ባለቍቅ ") ።
ቍቅ፡ ታናሽ የፈስ ድምዕ ።
ቍቅ አለ፡ ተፈሳ ።
ቍቅም፡ ከፈስ ተቈጠረችና ። (ተረት) ።
ቍቅታ፡ ቀጪን ፈስ፡ ቍቅ ማለት ።
ቍባ፡ ጕባ (ዕንቍላል ቤት ") ። ቍባ ግእ ዝኛ ነው ።
ቁባት (ዕቅብት)፡ የተጠበቀች (ካ ስቀመጣት መኰንን በቀር ሌላ ወንድ እ ንዳይደርስባት በጃን ደረባ ተጠብቃ የምት ኖር ሴት - ምልምል ሥራ ቤት ገረድ ") ።
ቁባት፡ የተጠበቀች ዐቀበ ።
ቁባቶች (ዕቁባት)፡ ጥብቆች ሴ ቶች (ነገሥታት መኳንንት በተራ የሚደር ሱባቸው የሚገናኟቸው የንግሥታት ተወራ ጆች ") ።
ቍቤላ፡ የዝኆን ጊደር (ዘር ለመቀበል የምትችል ") ።
ቁብ (ዐቀበ - ዕቁብ)፡ ዐሳብ ግድ ። በጋልኛ ግን ጣት ማለት ነው ።
ቍብ፡ መቀመጥ ቈበበ ።
ቍብ ቍብ አለ፡ ጕብ ጕብ አለ ።
ቍብ አለ፡ ጕብ አለ ቍጭ አለ ።
ቁብ የለሽ፡ ዐሳብ የለሽ ግድ የለሽ ።
ቍብ፡ ጕብ ቍጭ (መቀመጥ ") ።
ቍብላ፡ ትልቅ ወይፈን (በትከሻው ቀንበር ለመቀበል ዘሩን ለማቀበል የሚች ") ።
ቍብታ፡ ጕብታ (ጕብ ማለት ") ።
ቍተማ፡ ስለፋ ።
ቍቲት (ቶች)፡ የነጠላ/የኩታ/የ ጋቢ ዘርፍ ("የሚቋጭ የሚከረር የሚሸረብ ") ።
ቍቲት በጣሽ፡ ሸማኔ ቍቲትን እየበጠሰ ድርን የሚቋጥር ።
ቍትቻ (ቀቶት)፡ አስከፋዩ የኅዋት ዳኛ ("ተከፋዩ ጋሬዳ የኾነ ገንዘብ ") ።
ቍቻ፡ እየተጠበሰ የሚበላ እንጕዳይ ("እሆድ ቋት የሚገባ ") ።
ቍነና፡ ጕንጐና ሽረባ ።
ቍና (ዎች)፡ መስፈሪያ የስፌት ዕቃ (ትንሽና ትልቅ መሸመቻ አጋማሽ መገበ ሪያ ቍና እንዲሉ ") ። (ተረት)፡ "ለስማ መጥሪያ ቍና ሰፋች" ። (አዝማሪ)፡ "እንዳይቀደድ ይህ ቍና፡ ብድር አለበትና" ("(ማቴ. ፯፥ ፪ ። ማር. ፬፥ ፳፬ ። ሉቃ. ፮፥ ፴፰)") ።
ቍና፡ መስፈሪያ ። ቈነነ ።
ቍና ቍና ተነፈሰ፡ ከሩጫ ብዛት የተነሣ እጅግ በጣም ተነፈሰ ።
ቍና ተኩል፡ የስፍር ስም (አንድ ተግማሽ ") ።
ቍና ፈጅ፡ አንድ ቍና እኸል የሚ ይዝ ሸክላ ።
ቍናሳም፡ ግማታም ጥንባታም ።
ቍናስ፡ ግማት ጥንባት (የማይሽር ቍ ስል መጥፎ ሽታ ") ።
ቍን (ቍንጽ - ቀነጸ)፡ የተባይ ስም፡ ቀን ተደብቆ ይውልና ሌሊት የሰውን ገላ የሚመጠምጥ የሚልስ የሚበላ ጥቍር ተባይ ተፈናጣሪ ዘላይ ። ሲበዛ "ቍንጮች" ያ ሠኛል ። "ሞያሌን" ተመልከት ።
ቍንም፡ ቤት ውሻ ።
ቍንቍኔ፡ ጥንጣን ነቀዝ ብል ትል ("(ግእዝ)") ። "ቅንቅንን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቍንቍን - ቍንቍኔ ።
ቍንቍን አለ፡ ቈጥቋጣ ኾነ ።
ቍንቍን፡ የተቈነቈነ (ትንትን ") ።
ቍንን (ኖች)፡ የተቈነነ (ትት ጕን ጕን ሽርብ፡ ጕኒና ቆብ ጭራ፡ ጅንን ኵሩ ") ።
ቍንን በላይ ነኸ፡ የመንዝ ባላ ባት የኰሩ የተጀነኑ የተቋፉ (ካጤ ምኒልክ እስከ ዐጤ ኀይለ ሥላሴ የነበሩ ደጃዝማች ") ።
ቍንዥና፡ ቈንዦ መኾን (ውበት ") ።
ቍንድድ፡ የተቈነደደ የተገረፈ (ግርፍ ") ።
ቍንድዶ፡ ከሐረር ከተማ ወደ ጅጅጋ ሲኼዱ በስተግራ የሚታይ ተራራ ነፋሳም ብርዳም ።
ቍንዶ (ጕንዶ)፡ ባለያ ሴት ሥራ ዐዋቂ ።
ቍንዶ በርበሬ (ጕንደ በርበሬ)፡ የቅመም ስም፡ ወጥ ተሠርቶ ሊወጣ አቅራቢያ የሚጨመር የሚነሰነስ (መከለሻ ከባሕር የመጣ የንጨት ፍሬ ") ።
ቍንጠራ፡ የመቈንጠር ሥራ ኹኔታ ።
ቍንጠጣ፡ ቍንጥ ረገጣ ።
ቍንጢብራ፡ ኀፍረተ ብእሲት ።
ቍንጢጥ፡ የጣት አጣብቂኝ (የሕፃን ቅጣት ") ።
ቍንጣሪ፡ የተቈነጠረ ትንሽ ነገር ።
ቍንጣሪት፡ የተቈነጠረች ።
ቍንጣራ፡ ፌንጣ ኵብኵባ ።
ቍንጣር (ሮች)፡ ጠይብ፡ የጠይብ ወ ገን ሸክላ ቈንጥሮ የሚሠራ ።
ቍንጣናም፡ ቍንጣን የያዘው ያስጨነ ቀው ሰው ።
ቍንጣን (ቅንጣዌ)፡ ከማርና ከማንኛ ውም ምግብ ብዛት የሚመጣ መጥፎ ጥጋብ በላይ ማስታወክን በታች መተንፈስን የሚከለ ክል። ውሻው ብዙ ደም ስለ ጠጣ ቍንጣን ይዞት በምድር ላይ ይንከባለላል ። "ፈለጠን" እይ ።
ቍንጣይ - ቍንጻይ ።
ቍንጥ ቍንጥ አለ፡ ተቍነጠነጠ ።
ቍንጥል - ቍንጽል ።
ቍንጥር ቍንጥር አለ፡ ፊናጥ ፊናጥ ብድግ ብድግ አለ፡ ተቅበጠበጠ ።
ቍንጥር አደረገ፡ ንክስ አደረገ ።
ቍንጥር፡ ዝኒ ከማሁ ለቍንጣሪ፡ ባለም ድር ካጋዛው ርስት ላይ ያነሣው ጥቂት መሬት ።
ቍንጥርጥር፡ የተቈነጣጠረ፡ ዐልፎ ዐ ልፎ ቍጭ ቍጭ ያለ ጠጕር ።
ቍንጥንጥ አለ፡ ቅብጥብጥ አለ ።
ቍንጥንጥ፡ የተቍነጠነጠ (ቅብጥብጥ ") ።
ቍንጥጥ አደረገ፡ ልምዝግ ንክስ አ ደረገ፡ ቈነጠጠ ።
ቍንጥጥ፡ የተቈነጠጠ የተለመዘገ የተ ቀጣ ልጅ ።
ቍንጪት፡ ከቍጫጭ የምታንስ ተ ንቀሳቃሽ፡ ዳግመኛም ባላገሮች ነፍሳት ይሏታል።
ቍንጫቶ፡ ጕልጓሎ ።
ቍንጭ፡ ተቈናጣጭ ፍጥረት ።
ቍንጮ (ዎች - ቍንጾ)፡ የሕፃን ዐናት ጠጕር ። ዳግመኛም በግእዝ "ቍንዝዕ" ይባላል ።
ቍንጮ፡ የጣራ የክዳን ጫፍ ጕል ላት የሚቀመጥበት ። "የቤት ቍንጮ" እንዲሉ።
ቍንጮ ያ፡ መኻል ራስ ።
ቍንጮ፡ ያጤ ምኒልክ እናት የወይዘሮ እጅጋየኹ አጫዋች ባናቱ አንድ ቀጪን ቍ ንጮ የነበረው፡ ታቦት ዘፋኝ ገና ተሳዳቢ ። ኣ ሽከሩም የልብ ዐውቃ ይባላል ። "ጀጀበን" እይ ። አቈናጨ፡ አላቀመ አጐላጐለ ።
ቍንጯም፡ ቍንጮው ያደገ የረዘመ ልጅ ።
ቍንጯም አሞራ፡ ጕትዬ ።
ቍንጸላ፡ ኵስተራ ሰበራ ግንጠላ ።
ቍንጻይ፡ የቍንጽል ዐይነት ።
ቍንጽል (ሎች - ሡዕ)፡ የተቈነጻለ (ኵስታሪ ቍራጭ ግንጣይ፡ የጧፍ የጥራዝ ") ። በ ግእዝ ግን ቀበሮ ተኵላ ማለት ነው ።
ቍዘማ፡ ዐዘን ለቅሶ ሙሾ የሐዘን እንጕርጕሮ ("(ሮሜ. ፰፥ ፳፮)") ።
ቍዝራት፡ የሆድ መነፋት ።
ቍዝር (ሮች)፡ የተቈዘረ (ጕኝር ጕስር ") ።
ቍዝር አለ፡ ጕስር አለ (ተቈዘረ ") ።
ቍዳማ - አቍዳማ፡ የብር ጌጥ (በባሕር ዐረብ ተሰፍቶ በግንባር ላይ የሚታ ሰር ያዳል ገዳይ ምልክት ") ።
ቍድ፡ መብራት የሚኾን ቋድ ።
ቍድስ፡ የተቈረሰ ቍርስ የምግብ ክፍል ። ባረብኛ ግን የቤተ መቅደስ ክልል ገረገራ ማለት ነው፡ ባማርኛም የኅብስተ ቍርባ ንን ፍታቴ ያሳያል።
ቍግ (ጎች)፡ የገመድ ጅራፍ ጫፍ ውልብልቢት ጕተና መሳይ ። ቍግ የሚኾኑ ና ስንደዶ ጥፍር አንዶ እንሰት ቃጫ ጭራ ዶቢ የበሬ ኋላ እግር ዥማት ናቸው ።
ቍጠባ፡ ቅነሳ (የመቈጠብ ሥራ፡ ፈረንጆች "ኤኮኖሚ" ይሉታል ") ።
ቍጠኛ፡ ቍጡ (ቍጣ ወዳድ ባለቍጣ ተቈጪ ") ።
ቍጠጣ፡ የመቈጠጥ ኹኔታ ።
ቍጠጥ)፡ ቅጥነት ቀጪንነት ይላል ።
ቍጡ (ቍጡዕ)፡ የተቈጣ/የሚቈጣ (ብስጩ ገሣጭ ገላማጭ ") ።
ቍጡነት፡ ቍጡ መኾን ።
ቍጢሶ፡ ባላንጣ ምንዝር ባለጢንጦ ።
ቍጢሶ አለ፡ ተለየ ተገለለ ዕልፍ ብሎ ተቀመጠ ።
ቍጢጥ፡ በቋፍ መቀመጥ ።
ቍጢጥ አለ፡ በእግሮቹ ጣቶች ተቀመጠ (ቍጣጥ የሚጥል መስሎ ") ።
ቍጣ (ቍጥዓ)፡ ተግሣጽ ዘለፋ ግልምጫ መዓት ።
ቍጣሮ - አቍጣሮ፡ የመቍጠሪያ ጸሎት ።
ቍጣጣም፡ ቍጣጠ ብዙ ባለቍጣጥ ።
ቍጣጥ (ጦች)፡ የንቦሳ የግልገል የሕፃን ወፈር ያለ ቅዘን ። ግእዝም (ቍጥ)፡ የጦር ውልብልቢት፡
ቍጥራት (ቶች)፡ የቊጥር ኹናቴ (እስ ራት ("(፩ሳሙ. ፴፥ ፲፪)")) ።
ቍጥር (ሮች)፡ የተቈጠረ ("(ሕዝ. ፭፥ ፫)") ። "የባቄላ ቍጥር" እንዲሉ። ሒሳብ ስሌት ልክ መጠን፡ መደመር መቀነስ ማብዛት ማካፈል። ቍጥር፡ አኃዝና ፊደል፡ ጥቅልና ዝርዝር ። "መደበኛ ቍጥር ተራ ቍጥር" እንዲሉ። ቍጥር የተቋጠረ፡ ቋጠረ ።
ቍጥር (ሮች)፡ የተቋጠረ/የታሰረ (እ ስር ") ። "የገመድ ቍጥር" እንዲሉ።
ቍጥር (ጥቋ)፡ መቋጠር ።
ቍጥር አለ፡ ተቋጠረ ።
ቍጥር የተቈጠረ፡ ቈጠረ ።
ቍጥርጥራም፡ ባለብዙ ቍጥር ።
ቍጥርጥር አለ፡ ተቈጣጠረ ።
ቍጥርጥር፡ የተቈጣጠረ (እስርስር ሣር ") ።
ቍጥቍጥ፡ መቈንጠር/ቍጠባ/ቍንጠራ ።
ቍጥቍጥ አደረገ፡ በጥቂት በጥቂት አወጣ ሰጠ ።
ቍጥቍጥ፡ የተቈጠቈጠ (ምልምል ቍርጥ ") ።
ቍጥቈጣ፡ ቈረጣ ልብለባ ።
ቍጥቋጦ (ዎች)፡ ከምድር ከፍ ያለ በጣም ያላደገ ወጣት ግራር ሌላውም እሾኽ ያለው ዕንወት ኹሉ። "ቴዎድሮስ መጣ ዐይኑን አፍጦ ወይ መሸሸጊያ ታናሽ ቍጥቋጦ" (እረኛ) ።
ቍጥቋጭ፡ የቍጥቋጦ ጭፍጫፊ ።
ቍጥባት፡ ቍጠባ ።
ቍጥብ፡ የተቈጠሰ (በሣጥን በከረጢት ያለ የተቀመጠ፡ ለወጪውም ይነገራል ") ።
ቍጥን (ቁጥን)፡ ጥጥ ።
ቁጥን፡ ዐረብኛ፡ ቍጥን፡ ግእዝኛ ነው፡ ከቀጠነ ጋራ ይሰማማል ። ፈረንጆች "ኩቶን" ይሉታል ።
ቍጥጥ አደረገ፡ ቈጠጠ ።
ቍጥጥ፡ የተቈጠጠ (በልብስ በምድር ላይ ያለ ") ።
ቍጥጥር፡ ምርምር ።
ቍጩት፡ የማክረር ሥራ ።
ቍጫ፡ በቈ ቡልኮ አምሳል ከፈረንጅ አገር ተሠርቶ የመጣ ልብስ ቍቲቱ የሚቋጭ ።
ቍጫም፡ ቍጭ ያለበት የበዛበት ስፍራ (የድንጋይ ሥር ") ።
ቍጫጭ (ጮች)፡ ታናሽ ፍጥረት (ከጕንዳን ከዘመሚት ከምሥጥ እጅግ የምታንስ ተንቀሳቃሽ የጤፍ ቅንጣት የምታኸል ከነፍሳት የምትበልጥ ") ።
ቍጫጮ - ጕጫጮ፡ ዐጪር ሣር ።
ቍጭ፡ መቀመጥ ።
ቍጭ ብዬ፡ የማሽላ ስም (ዐጪር
ቍጭ አለ፡ ተቀመጠ ።
ቍጭ ወረረው፡ ከበበው ወረሰው አለበሰው ።
ቍጭመቀመጥ፡ ቈ ቀጠበ (ቀጸበ - ዕብ. ቃጻብ)፡ ጨረሰ ቈረጠ፡ ጠቀሰ፡ ከነዳ ለካ መጠነ፡ አመለከተ ምልክት አደረገ ከሰለ ድርን ። ለዕ ድሜም ይነገራል።
ቍጭር፡ ሸሐኝ (የለገመ ቍስል ባለመጅ ") ። "ቍጭር ይቀመጥብኸ" እንዲሉ። "ጭንቍርና ጭንኰር" ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቍጭቋጮ፡ የጣት ትግል፡ ወይም ት
ቍጭብርብር፡ ጠባዩ ዐይጥ የበጣጠ ሰው ፈትል የኾነ ።
ቍጭት አለው፡ ጸጸተው ።
ቍጭት፡ ጸጸት ያልተገለጠ ቂም ቍርሾ ። "በጠላ ቤት ጠብ ቢነሣ እከሌ እከሌን በቍጭት መታው" ።
ቍፂያም - ቍጋም፡ የከሳ ሰው (ከሲታ ሴት ዥማታም ") ።
ቍፈራ - ቍፋሮ፡ ምንቀራ ጕድፈራ ምሰት ።
ቁፋ (ዐረ)፡ ታናሽ ቅርጫት ።
ቁፋሂ፡ ሂ ዋዌ ነው፡ ቅርጫትም ያሠኛል ።ባለቅኔዎች ግን ቅኔ ማሕሌት ይሉታል ።
ቁፋዳ - አቁፋዳ (አኩፋዳ)፡ የተማሪ ኰረጆ፡ በዙሪያው የቈዳ የገመድ ቀፈድ ያለው የምግብ መያዣ ከሰሌን ከሌጦ የተበጀ ።
ቍፍር፡ የተቈፈረ/የተማሰ ። (ተረት)፡ "ካባ ቍፍር እሸት ተበልቶለት" ።
ቂላቂል፡ የቂል ቂል ሞኛሞኝ ።
ቂላዋት (ቂል ኀዋት)፡ የቂል ወንድም (ወንድሞች ") ጅላዋት ።
ቂላዋት፡ የቂል ወንድም፡ ቄለ ።
ቂል ።
ቂል (ሎች)፡ ጅል ግጅል ሞኝ ከርፋፋ መነፍ ተላላ ነኹላላ እንከፍ ነጕላ ነፈዝ ። (ተረት)፡ "ቂል አይሙት እንዳያጫውት"
ቂል—ጅል—ቄለ ። ቃለ (ዐረ)፡ አለ ተናገረ ።
ቂሎ፡ የዘንጋዳ ስም፡ ቀጪን ረዥም
ቂመኛ (ኞች)፡ ባለቂም፡ ቂምን በልቡ የሚያኖር/የሚይዝ ("(መዝ. ፵፬፥ ፲፮)") ።
ቂሙን ቀረፈ፡ ብድሩን መለሰ፡ እንደ መቱት መታ፡ እንዳዋረዱት አዋረደ፡ ቂሙን ተወ ።
ቂም - ቍርሾ (ቀየመ - ቄመ) ።
ቂም፡ ቍርሾ ብሶት ቍጭት ክፉ ዐሳብ ("(ሮሜ. ፲፪፥ ፲፬)") ። (ተረት)፡ "ቂም ይዞ ጸሎት፡ ሳል ይዞ ስርቆት" ።
ቂም በቀል፡ የበቀል ቂም ።
ቂም ያዘ፡ ቂምን በልቡ አሳደረ ።
ቂም—(ቀመደ)፡
ቂስ፡ የሰው ስም (የሳኦል አባት ") ።
ቂራጥ፡ ግብዝ ወርቅ ። በግእዝ "ተምያን" ይባላል ። ፈረንጆች "ካራት" ይሉታል ።
ቂርቆስ፡ የሰው ስም ("ጨርቆስ") ።
ቂሮስ፡ ቈሰለ ።
ቂሮስ፡ የሰው ስም (መዠመሪያው የፋርስ ንጉሥ ") ።
ቂሮስ ዳርዮስ፡ ከቂሮስ ልጅ ከካምቢስ ቀጥሎ የነገሠ ዳርዮስ ሦስተኛ የፋርስ ንጉሥ፡ ቂሮስ የዳርዮስ ቅጽል ነው ።
ቂብ፡ ሴትኛ መቀመጥ መምላት ። ዘሩ ቈበበ ነው።
ቂብ አለ፡ መላ የሆድ ።
ቂብ አለች፡ ተቀመጠች ።
ቂንር - ቅንር፡ የተነፋ ንፍ ።
ቂንር አለ፡ ዕብጥ አለ ። "ሆዱ ቂንር ብሏል" እንዲል ባላገር ።"ጐኘረን" እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቂንቂን፡ መውጣት መታየት ።
ቂንቂን አለች፡ እታይ እታይ አ ለኹ ኣለኹ እለች፡ ተሽኰነተረች ።
ቂንዳም፡ ቂንድ ያለበት ባለቂንድ (ያ ገዳ እኸል ") ።
ቂንድ (ዶች)፡ ያገዳ ገለባ ፍሬ ዐቃፊ ።
ቂንጥ (ቂጥ)፡ ቂብ መቀመጥ ። "በረረን" እይ ።
ቂንጥራም፡ ብእሲት ።
ቂንጥር፡ ልሳነ ኀምስ፡ እንደ እንጥል በመካከል ይታያል ።
ቂው አለች፡ ጭው አለች (ተባት ፈለገች እንስት ዶሮ ") ።
ቂድር አለ፡ ህርት አለ ።
ቂድር፡ የቄደረ/የሚቄድር ኵሩ/ትቢተኛ ።
ቂጡ ቀጤማ ቈረጠ፡ ፈጽሞ ደስ ተሠኘ (ተደሰተ ") ።
ቂጡን ጣለ፡ ያለቀ ሱሪ ታጠቀ ።
ቂጣ (ቀጣ)፡ የምግብ ስም (ዱቄቱ በውሃ ተለውሶ ታሽቶ ሳይቦካ ወዲያውኑ በፍጥነት የሚጋገር የመንገደኛ የችግረኛ መብል ") ("(ዘፀ. ፳፱፥ ፪)") ። "የገብስ የስንዴ ያጃ የጤፍ የሽን ብራ የምስር ቂጣ የጠላ ቂጣ" እንዲሉ። ሲበዛ "ቂጣዎች" ይላል ።
ቂጣ ቈሎ፡ ከግንቦት ልደታ ዠምሮ ባ፲፪ቱ ወር መባቻ የሚ ደረግ፡ ልማዳዊ አምልኮ ባዕድ የበዓለ ናእት ምሳሌ ("(ዘሌ. ፳፫፥ ፮)") ። "ቂጣና ቈሎ" ወይም "ቂጣ ከቈሎ ጋራ" ማለት ነው ። ቈሎው የስንዴ ቂጣው የጤፍ ኹኖ በተልባ ብጥብጥ ይበላል ። ልደታ ከወር እወርሽ አድርሽኝ እየተባለ አስቀድሞ ተልባው በቂጣው ይረጫል፡ ቈሎውም ይበተናል ። የመቤታችን ልደት ርግጠኛው በመስከረም ፲ ቀን ሲኾን ከሣቴ ብርሃን ሰላማ በግንቦት ፩ ቀን ያደረገው ይህን አምልኮ ለማጥፋት ነው ይባላል ።
ቂጣ ቈረጥ፡ ዘወትር ቂጣ የሚበላ (ቂጣ ወዳድ ቂጣ የሚቈርጥ የሚገምጥ ") ።
ቂጣ በል፡ የጭፍራ ስም (ማደሪያ ያልተሰጠው ወታደር ቂጣ በል ይባላል፡ እሱ የሚያርሰውንም መሬት የቂጣ በል ምድር ይሉታል ") ።
ቂጣ፡ ያልሠለጠነ (ባላገር አእምሮው ያልተገራ ") ።
ቂጣ፡ ጥረሾ ከገብስ የተጋገረ ።
ቂጣለኝ (ቂጣ አለኝ)፡ የቀበሌ ስም (በላይኛው ወግዳ ካጤ ዋሻ በስተቀኝ ያለ ቀበሌ ") ።
ቂጣም - ቂጠ፡ ትልቅ ሰው ። ቂጥ፡ መቀመጥ ።
ቂጥ (ቀጣ)፡ መቀመጫ የዙስ የ እበት መውጫ መፍሻ መተንፈሻ ። የቂጥ ምስጢር ግራና ቀኙ እንደ ብራና ቅጽ ትክክል መኾኑንና የመካከሉን ክፍልነት ያሳያል ።
ቂጥ ለቂጥ ገጠመ፡ ዐበረ ዐደመ አሤረ ።
ቂጥ ቀጠበ
ቂጥ አለ፡ ከፍ ባለ ስፍራ በጫፍ ተቀመጠ (ቂብ አለ ") ።
ቂጥኛም (ሞች)፡ ቂጥኝ የያዘው ባለ ቂጥኝ ። "መነኵሴና ቂጥኛም ሰው ኹሉ እንደሱ እንዲኾን ይፈልጋል" ። "ወረደ" ብለኸ "ው ርዴን" አስተውል ።
ቂጥኝ (ቀጣ ቂጥ)፡ የቍስል በሽታ፡ ብዙ ስምና ዐይነት ያለው (ያመንዝሮች ቅጣት ") ። (ግጥም)፡ "ምን ይይዛት ብዬ ዝንጀሮን ቂጥኝ፡ አለመጠርጠሬ ጕድ አረገችኝ" ።
ቂፉንቂ፡ ጨፋና አሞራ (የቅኔ ቤት ዐማርኛ ነው ") ።
ቃ
ቃ፡ መድረቅ ።
ቃ፡ መድረቅ ቃቃ ።
ቃ አለ (ትግ ቀዐነ - ደረቀ)፡ (ጥቅጥ) ደረቅ መጠጥ ቀንበር አለ ።
ቃ አለ፡ ደረቀ ቃቃ ።
ቃ አደረገ፡ ቀንበር አደረገ ።
ቃለ ሕይወት፡ የሕይወት ቃል፡ ጌታችን ያስተማረው ወንጌል ። "ቃሌን የጠበቀ ሞትን አይቀምሰውም" የሚል ("(ዮሐ. ፮፥ ፷፰፡ ፰፥ ፶፩)") ። "ቃለ ሕይወት ያሰማዎ" እንዲሉ ተማሮች ከትምርት በኋላ ።
ቃለ ሰላላ)፡ ቃለ ቀን ሴት ድምጥ።
ቃለ አኅስሮ፡ የማዋረድ ቃል ።
ቃለ አራኅርኆ፡ የማራራት ቃል ። "ሆይን" ተመልከት ። ይህ ኹሉ በግእዝ ሰዋሰው ንኡስ አገባብ ይባላል፡ መሠረቱም "ኦ" ነው ።
ቃለ አክብሮ፡ የማክበር ቃል ።
ቃለ አጋኖ (ሆይ)፡ የማጋነን ቃል፡ ከዚህ ዠምሮ "ቃለ አራኅርኆ" አለው ድረስ የ"ሆይ" ትርጓሜ ነው ።
ቃለ አፍርሆ፡ የማስፈራት ቃል ።
ቃለ እግዚአብሔር፡ የግዜር ቃል (የሃይማኖት ትምርት ወይም ርሱ ራሱ ጌታ ችን ") ።
ቃሉ፡ ያ ቃል፡ የርሱ ቃል።
ቃሉን አከበረ፡ በቃሉ ጠና፡ የተናገረውን አደረገ ።
ቃሊም (ሞች ዐረ ቃሊብ ኵየት)፡ የመጠጫ ትንባኾና እሳት ማስቀመጫ የት የሚመስል የሚያኸል ።
ቃሊም፡ የወንዝ ዳር ደገፍ ዐቃባ ። በግእዝ "ናህብ" ይባላል ።
ቃሊቱ፡ ያች ቃል።
ቃላተኛ (ኞች)፡ ቃልቻ/ትንቢት ተናጋሪ ባለቆሌ ካህነ ጣዖት ("(ዘሌ. ፲፱፥ ፳፮፡ ፳፥ ፮)") ። "ቆሌንና ቃልቻን" እይ ።
ቃላት (ቃሎች)፡ ድምፆች ነገሮች ።
ቃል ።
ቃል (ሎች)፡ ብትን (ዝርው) ቃል፡ ድምፅ ነገር አፍ ።
ቃል ለቃል፡ አፍ ላፍ ።
ቃል ማሰሪያ፡ የጋብቻ ውል ፈጠም ። "ቃሌ ነው"፡ "ብያለኹ፡ ተናግሪያለኹ" ።
ቃል ሰጠ፡ ዕሺ "እሰጣለኹ/አደርጋ ለኹ" አለ ማለ ።
ቃል ሰጠ)፡ "ዕሺ አደርጋለኹ" አለ። "ሰጠ" የ፪ ፊደል ግስ ኹኖ መጥበቁ "ሰጠወ"ን ተከትሎ ነው። ላይችል አይሰጠውም)፡ እግዜር ለሰው ከዐቅሙ በላይ ጭንቅ አያመጣበትም።
ቃል ትምርት)፡ በቃል የሚማሩት (የንባብ/የዜማ/ጸሎት) ።
ቃል ዐባይ፡ የዋሾ የቀጣፊ የሐሰተኛ ቃል ።
ቃል ኪዳን ተጋባ፡ ተዋዋለ ተማማለ ("(፬ነገ. ፭፥ ፲፪፡ ኢሳ. ፶፯፥ ፰፡ ሕዝ. ፴፬፥ ፳፭)") ። "ቃል ለምድር ለሰማይ አለ"፡ ፈጽሞ ማለ፡ ማላውን አጸና ።
ቃል ኪዳን፡ የማይቀር የማይታበል እንደ መሐላ ያለ የውል ውለኛ ቃል። በግእዝ "ኪዳነ ቃል" ይባላል ።
ቃል፡ ወልድ ከቅድስት ሥላሴ ኹለተኛው አካላዊ ቃል ("(ማሕ. ፪፥ ፰፡ ዮሐ. ፩፥ ፩፡ ፩ዮሐ. ፭፥ ፯)") ።
ቃል ገቢ፡ ዋና ሚዜ ።
ቃል ገባ፡ የማይፈርስ ውል አደረገ ።
ቃልቻ (ቾች)፡ ቃላተኛ ባለዛር ሌሊት ድቤ ሲመታ የሚያድር፡ ቡሓ በግ ወሰራ ዶሮ ነጭ ኰርማ ጥቍር ፍየል ዕረዱ ሠዉ የሚል ።
ቃልቻ) ። ተሸካሚነት፡ ተሸካሚ መኾን ።
ቃሏ፡ የርሷ ቃል።
ቃመ (ቀሐመ)፡ እሸትን ንፍሮን ቈ ሎን ከውስጥ እጁ ወዳፉ ወረወረ ቻመ ገተመ ቸቸረ፡ ባፉ ምርትን ስጥን ገለባን ዐመድን ገፈረ ተረፈሰ ቸፈረ ሰመሰመ ዐፈሠ ።
ቃሚ (ቀሓሚ)፡ የቃመ/የሚቅም ( ቻሚ ሰምሳሚ ") ።
ቃሚያ (ቃሕም)፡ አንድ ጊዜ ተቅሞ የሚታኘክ የሚዋጥ፡ በውስጥ እጅ የተለካ የተ መጠነ፡ የዳቦ የንጀራ ፍርፋሪ ድቃቂ ። በግእዝ "ፍተ ቃሕም" ይባላል ።
ቃም (ቅሒም)፡ መቃም ።
ቃም አደረገ፡ ቃመ ።
ቃም፡ ዝኒ ከማሁ ። "ዐፈር ቃም" እንዲሉ።
ቃም፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ።
ቃሞ - ቅሞ፡ የመምህራን ዐማርኛ ነው ።
ቃሰተ፡ ኣኣ ኣለ፡ ቃተተ ቃዘነ ጣረ ተጨነቀ (ከውጋት የተነሣ በቀስት እንደ ተነደፈ ሰው ") ።
ቃሰተ፡ ኣኣ ኣለ፡ ቃተተ ቃዘነ ጣረ ተጨነቀ (ከውጋት የተነሣ በቀስት እንደ ተነደፈ ሰው ") ።
ቃሰነ (ቃዘነ)፡ ጐመዠ ቃቃ ።
ቃሰነኛ፡ ባለቃሰን (ቃሳኝ ጕምዡ ") ።
ቃሰን፡ ጕምዠታ ።
ቃሳኝ፡ የቃሰነ/የሚቃስን (ጐምዢ ") ።
ቃረ ። ቍርዬ፡ (ቍራዊ)፡ ያሞራ፡ ስም፡ በመከር፡ ጊዜ፡ ከውጭ፡ አገር፡ እየመጣ፡ እኽል፡ የሚበላ፡ በውሃ፡ ዳር፡ የሚያድር፡ ሲኼድ ቍር፡ (ኵር)፡ የሚል፡ የባሕር፡ አሞራ፡ ሲመጣም፡ ኾነ፡ ሲመለስ፡ በኣየር፡ መጥቆ፡ ተራ፡ ይመታና፡ እየተከታተለ፡ በመሪ፡ ይኼዳል፡ አገሩም፡ ኣውስትራልያ፡ ነው፡
ቃረ፡ ሳለ አፋጩ ፈገፈገ ።
ቃረመ፡ (ቀሪም፡ ቀረመ)፡ ካጨዳ፡ በኋላ፡ የወደቀውን፡ የእኸል፡ ዛላ፡ ለቀመ፡ ሰበሰበ።
ቃሩራ፡ ጠርሙስ ።
ቃሪያ በርበሬ፡ ያልቀላ/ያልበሰለ (እሳት ያልመሰለ ") ። ጨርቋ በርበሬ ሲበሉት አፍን የሚያቃጥል ።
ቃሪያ፡ እንጭጭ ጓሚያ ፍሬ ።
ቃሪያ ያልበሰለ፡ ፍሬ
ቃሪያ፡ ያልተማረ ያልሠለጠነ ሰው ።
ቃሪያ ጥፊ፡ አይበሉብሽ የውስጥ እጅ ዠርባ ። ቃሪያ ለጥፊ ቅጽል መኾኑን አስተውል፡ "በላን" እይ ።
ቃራሚ፡ የቃረመ፡ የሚቃርም፡ ለቃሚ፡ ሰብሳቢ ።
ቃራም፡ ቃር የማይለየው ።
ቃሬዛ፡ የሬሳ የቍስለኛ የበሽተኛ የወደቀ ከብት ማንሻ መሸከሚያ (ኹለት ኣጣና ባለቀላጥም ") ("(ግብ ሐዋ. ፭፥ ፲፭)") ።"ወሰካን" አስተውል ።
ቃሬዛ፡ የድግስ ስም (ስለ ሙታን ፍታትና ቍርባን ምክንያት ካህናት በደጀ ሰላም የሚመገቡት ምግብ የሚጠጡት መ ጠጥ ") ።
ቃር (ቀሐር)፡ የልብ ትኵሳት (በም ግብ ምክንያት የሚመጣ ") ።
ቃር አያውቅሽ፡ ታሞ የማያውቅ ሰው ጤናማ ።
ቃርሚያ፡ ቃርሞሽ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ (1 ሌዋ. ፲፱፡ ፲)
ቃቂ፡ የቃቃ/የሚቃቃ (ጐምዢ ") ።
ቃቂል፡ ቃጭል ("(ግእዝ)") ።
ቃቃ (ትግ ቃዕቅዐ ።ግእዝ ቃሕቅሐ - ቈቍዐ - ሰቈቈ)፡ ጐመዠ ሠየ ተ ቃረ ፈለገ ። "ከብቶቹ ቃቅተዋል" እንዲል ባላገር ።
ቃቃታ፡ ሥየታ ቃቃ ።
ቃቃታ፡ ጕምዠታ ሥየታ ።
ቃቃታ፡ ፈጥኖ ኣለመናገር አፈ ጸያፍነት ።
ቃቃን፡ የአለት መንደያ ንጥር ብረት ካክራ ። "በትረ ቃቃን" እንዲሉ ። "ቀቃን" ተመልከት ።
ቃቄር (ሮች)፡ ቍራ ("(ግእዝ)") ።
ቃቄዳ፡ ግትቻ ዕላቂ ሰፌድ ።
ቃበበ (ትግ. ቀበበ)፡ እፌዘ አላ ።
ቃበበ (ዕብ. ቃባብ)፡ ናቀ ሰደበ ረገመ ።
ቃብትያ፡ እንደ ባልያ ያለ ተራራ ።
ቃተ - ቀአተ)፡ አቃተ፡ ተሳነ/ቸገረ ("አልቻልም አለ ") ።
ቃተ - ቀአተ)፡ አቃተ፡ ተሳነ/ቸገረ ("አልቻልም አለ ") ።
ቃተተ፡ ዞረ ለፋ ደከመ ("የጭንቅ ትንፋሽ ተነፈሰ ") ።
ቃተኛ፡ በያይነቱ ወጥ ያለበት ያነባ በሮ ዐይነት ዐምዛ ።
ቃታ (ቃቃ)፡ የጠመንዣ/የሽጕጥ/የመድፍ ጥይት ማስነሻ መተኰሻ ብረት ።
ቃታ (ቃቃ)፡ የጠመንዣ/የሽጕጥ/የመድፍ ጥይት ማስነሻ መተኰሻ ብረት ።
ቃታ (ቃተተ)፡ የማያቋርጥ ትንፋሽ ።"ሕፃኑ እጅግ ስለ ሮጠ ቃታ ይዞታል" ።
ቃታ (ቃተተ)፡ የማያቋርጥ ትንፋሽ ።"ሕፃኑ እጅግ ስለ ሮጠ ቃታ ይዞታል" ።
ቃታች፡ የቃተተ/የሚቃትት (ደካሚ ") ።
ቃት (ቃቃ)፡ ቃ ያለ የስንዴ እ ንጀራ ።
ቃት (ቃቃ)፡ ቃ ያለ የስንዴ እ ንጀራ ።
ቃነጠ)፡ አሽቃነጠ፡ ዘፈነ አረገደ እ ስክስታ ወረደ ።
ቃና (ቃነየ)፡ የዜማ የመጠጥ ጣ ዕም ። በግእዝ ግን ዜማ ማለት ነው ። "ንስርንና ምስርን" እይ ።
ቃና ምስር)፡ ከምስር የመጣ ዜማ። ዋሽንትም ምስር ቃና ሊባል ይቻላል (ዘሌ. ፳፭፥፱፡ ኢሳ. ፴፰፥፳፡ ሆሴ. ፭፥፰፡ ማቴ. ፳፬፥፴፩) ። ቃናን ተመልከት።
ቃና፡ የቀበሌ ስም፡ በቡልጋ ውስጥ ያለ ስፍራ ጉባኤ ቃና የተዠመረበት ።
ቃና፡ ጌታችን ውሃን ወይን ጠጅ ያደረገበት አገር በገሊላ አውራጃ ያለ ።
ቃናው ተለወጠ፡ ጣዕሙ ሌላ ኾነ ።
ቃንዛ፡ መንዘር (የደም ሥር በሽታ ") ።
ቃንዲላ፡ ጅራፍ ።
ቃንጤ፡ ፈሊጥ ዐመል ። "እከሌ ቃንጤው አይታወቅም" እንዲሉ።
ቃኘ (ቃነየ)፡ ቀነቀነ ዜማ ዠመረ አስቀድሞ አዜመ ።
ቃኘ (ትግ ቀነየ)፡ ሰነበተ ቈየ ።
ቃኘ፡ ዐሠሠ ጐበኘ ሰለለ ።
ቃኘ፡ የበገናን የክራርን ዥማት (ኦውታር) አጠበቀ አላላ አቃና አሰማማ ።
ቃኘ፡ ፈቀደ ማተረ ከብትን ።
ቃኘው፡ የልዑል ራስ መኰንን ፈ ረስ ስም ።
ቃኚ (ዎች)፡ የቃኘ/የሚቃኝ (ቀንቃኝ ጐብኚ ሰንባች ዐሣሽ ") ።
ቃውት፡ የዛፍ ስም (ርዝማኔና ቀጥታ ያለው ዕንጨት፡ ለደመራ ይፈለጋል ") ።
ቃዘነ፡ ተንከራተተ ባዘነ ። "ቃበዘን" አይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ።
ቃዛኝ፡ የቃዘነ/የሚቃዝን (ተንከራታች
ቃዠ (ጋዠ)፡ መጥፎ ሕልም አይቶ በንቅልፍ ልቡ ጮኸ አንቋረረ አላዘነ ።
ቃየል፡ የሰው ስም (የአዳም መዠመሪያ ልጅ ") ።
ቃዳ፡ ዝም እመም ተለላ ወረራ ።
ቃጠሎ፡ የእሳት አደጋ ።
ቃጠረ፡ ቀጠረ ቀጠሮ ሰጠ ።
ቃጠነ)፡ አቃጠነ፡ ወዲያና ወዲህ አለ፡ ነገር አሳካ አዋሸከ ።
ቃጣ (ቀጣ)፡ እጁን አነሣ ዘረጋ ደከረ ደቀነ አቀረበ (ለመምታት ለመያዝ ለማግኘት ") ። (ተረት)፡ "በሰው ቂጣ እጇን ትቃጣ (ትዘረጋ)") ።
ቃጣሪ፡ የቃጠረ/የሚቃጥር (ዳኛ ") ።
ቃጤ፡ ታናሽ መስፈሪያ ቍልቢጥ ።፡ ጭረቱ ቀላድ ወይም ገመድ
ቃጥላ፡ በመካከሉ ዝንጀሮና ጦጣ የሚኼዱበት ከአረኸ በላይ የቆመ ገደል፡ ምስጢሩ እንደ ተቀጠለ መኾንና ሣር አለማብቀል ነው ።
ቃጥላ ያኽላል፡ እጅግ ረዥም ነው ።
ቃጫ ቦራ፡ የፈረስ መልክ ብጫነት ያለው ።
ቃጭ፡ ሰይፍ የመታው የቈረጠው
ቃጭል (ሎች - ቃቂል)፡ በሕፃን በጥጃ በበቅሎ በተዋጊ በግና በተናካሽ ውሻ ዐንገት የሚንጠለጠል ድምፅ ሰዉ ጌጥ፡ ለቅዳሴ ለሰው መጥሪያ የሚኾን ታናሽ መርዋ ("(ዘፀ. ፳፰፥ ፴፫ - ፴፬)") ። (ተረት)፡ "በደንባሪ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ" ። "ብልብላን" እይ ።
ቃጭማ፡ የዛፍ ስም ።
ቃፍር፡ ከጥቦት የሚበልጥ በግ ።
ቄለ፡ ጀለ ተሞኘ፡ የማይረባ ቃል ተናገረ ።
ቄሎ፡ ከቅል የተበጀ መስፈሪያ ።
ቄሎ—ቀለበ ።
ቄሰ ገበዝ፡ ቅስናን ከግብዝና ያስተባበረ (የቤተ ክሲያን ንዋየ ቅድሳትና ገንዘብ ጠባቂ ሹም ") ። "ገበዝ ጐበዝ" ማለት ነው ። "አ መመ" ብለኸ "እምን"፡ "ነፈቀ" ብለኸ "ንፍቅን" አስተውል ።
ቄሳር፡ የሮማውያን ንጉሥ ስም (ሆድ ቀዳጅ ማለት ነው ") ("(ሉቃ. ፪፥ ፩ ። ፳፥ ፳፭)") ።
ቄስ (ቀሲስ)፡ ካህን ጳጳስ እጁን በራሱ ላይ ጭኖ መንፈሳዊ ሥልጣን የሰጠው የቤተ መቅደስ አገልጋይ (ባራኪ ቀዳሽ ናዛዥ የነፍስ አባት ") ። ሲበዛ "ቄሶች" ያሠኛል ። "ቄስ ያማርኛ፡ ቀሲስ የግእዝ" ነው ።
ቄስ፡ በቁሙ ።—ቀሰሰ ።
ቄስ በደጅ፡ ከቤት በስተውጭ የሚገኝ ቅጠል (መድኀኒትነት ያለው ") ።
ቄስ አሞራ፡ ቍራ ጥንብ ባራኪ (ራሰ መላጣ ጥንበ በላ ") ።
ቄስ ዐጤ (ቄሰ ሐፄ)፡ የንጉሥ ነፍስ አባት (ዘውድ ዐጣኝ ማእድ ባራኪ ") ።
ቄስ ዐጤ ዘወልድ፡ በዘፋኝ ዳዊት ባጤ በካፋ ዘመን የነበሩ ቄስ (ፍጹም ሊቅ ቅባቶችን ከሞት ያዳኑ ") ።
ቄራ (ቀረየ)፡ በግና ፍየል በሬ የርድ ከብት ኹሉ እየገባ የሚታረድበት ስፍራ (ሉካንዳ ሥጉያ ") ።
ቄራ፡ ማማ (የሰብል መጠበቂያ ረዥም ቈጥ ያዝመራ ዐልጋ ") ።ምስጢሩ ሰብሉ ከተ ነሣ በኋላ መንደድ መቃጠልን ያሳያል ።
ቄርሎስ፡ የሰው፡ ስም፡ የእስክንድርያ፣ ሊቀ፡ ጳጳሳት። በጽርእ፡ ፈለገ፡ እግዚእ፡ ማለት፡ ነው፡ ይላሉ።
ቄብ (ዕብ - ንቄባ - ቀዳዳ)፡ ያልተ ጠቃች እንስት (በግ ፍየል - አህያ ዶሮ ") ።
ቄብ ሻለቃ፡ ዝቅተኛ ጦር አዛዥ ።
ቄቦች፡ ያልተጠቁ እንስቶች/እንስሶች ።
ቄንጠኛ (ኞች)፡ ነቃፊ አላጋጭ (ባለ ቄንጠኛ ") ።
ቄንጠኛ፡ ጌጠኛ ተሽኰንታሪ ተሽሞን ኝ አለባበስ አሳማሪ ።
ቄንጥ፡ ልዩ ኹኔታ (ጌጥ ") ።
ቄንጥ፡ ጡር ነቀፋ ነውር መስቃ ።
ቄንጦ፡ የንጨት ስም (ትንንሽ ቈላፋ እሾኸ ያለው ዛፍ ") ።
ቄደረ (ዐረ. ቀደረ - ቻለ)፡ ኰራ (ተ በውቀት በችሎታ ") ።
ቄደር (ቄድር)፡ የመጽሐፍ ስም፡ ክ ርስቲያን ሃይማኖቱን ክዶ ማተቡን በጥሶ ቂጥኝ አውጥቶ ቢረክስ ንስሓ ከገባ በኋላ ቄሶች ይህን መጽሐፍ እየደገሙ ያጠ ምቁታል።
ቄጆ (ቀዳ)፡ ማለቢያ ቋ ጮጮ አኮሌ ።
ቄጥ፡ የበሬ ዕከክ ።
ቈ (ትግ. ቈጸየ)፡ ጸጸተ አተ ከዘ ። "ያለፈው አይቍጭኸ፡ ለሚመጣው ተጠንቀቅ" ። (አዝማሪ)፡ "ተይ መጭ በቅሎ ተይ መጭ፡ ነገር ካልሰሙት አይቈጭ" ።
ቈ፡ የቀ ዲቃላ በመኾኑ ስለ ቀለበቱ ቍ100 ይባላል ።
ቈለ፡ ተገለጠ ጠራ በራ ጐላ ።
ቈለለ (ጐለለ)፡ ደረደረ ደረበ አነባበረ ከመረ ጐቸ፡ አበዛ ። "ዋጋ ቈለለ" እንዲሉ።
ቈለል ቈለል አደረገ፡ ከብለል ከብለል አደረገ፡ አንገዋለለ ዐይኑን ።
ቈለመመ ።
ቈለመመ ። ቋሊማ፡ አንዠት ውስጥ የተከተተ ደቃቅ የሥጋ ክትፎ ።
ቈለመመ፡ ቀለሰ ዘለስ ዘቀዘቀ፡ አጐበጠ ጠመዘዘ ። "ቸለሰን" እይ ።
ቈለመም - ቈልማማ፡ የተቀለሰ/የተዘ ለሰ (ቀላሳ ጐባጣ ጠምዛዛ ቀንድ ") ።
ቈለመጠ)፡ አቈላመጠ፡ ውዳሴ ከንቱ ሰጠ፡ ፊት ለፊት አመሰገነ፡ ተለማመጠ ("(ኢዮ. ፲፱፥ ፲፯፡ ፴፪፥ ፳፩፡ ምሳ. ፲፱፥ ፮)") ።
ቈለቈለ - ቈልቈለ)፡ አቈለቈለ (አ ቈልቈለ)፡ ዘቀዘቀ፡ ቍልቍለት አደረገ፡ ቍልቍል ነዳ ወሰደ አወረደ፡ አጐነበሰ ("(ዘዳ. ፳፮፥ ፲፭)") ።
ቈለቈል (ሎች)፡ ባረኸ በቈላ በበ ረሓ ስፍራ የሚበቅል የቍልቋል ወገን ዕንጨት ። ደሙ መርዝነት ስላለው ዐይጥ ከሰሶ ጋራ በበላው ጊዜ ያብዳል፡ ርስ በርሱ እየተናከሰ ያልቃል ።
ቈለቈልዳ፡ ዝኒ ከማሁ፡ ዳ ከዕዳ መጥቶ ተጨምሯል።
ቈለበጠ፡ አነሰ ። "ቈለጠበን" እይ ።
ቈለኛ (ኞች)፡ በቈላ የተወለደ በቈላ የሚኖር ሰው/እንስሳ ።
ቈለዘ፡ ቈጠቈጠ እሾኸ ቈረጠ (ግእዝ) ።
ቈለዘመ)፡ ተቈላዘመ ተጐናዘለ ተዘናፈለ ተጠላለፈ፡ የሣር/የጠጕር ።
ቈለጠ (ፈተወ)፡ ቋመጠ ተወነገ ተወሰጠ ተወዘወዘ ።
ቈለጠበ፡ ብልጥ ኾነ፡ በሰው ነገር ገባ ።
ቈለጠብኸ፡ ብልጠት አበዛኸ ።
ቈለጣም፡ ቈለጠ ትልቅ ሰው ።
ቈለጥ (ጦች)፡ ቍላ የወንድ (ተባት) ብልት ፍሬ ።
ቈለጭ (ጕራጌ)፡ እንቍራሪት ጕርጥ ።
ቈለጭ፡ ዐይናማ ዐይነ ጥሩ ዐይነ ትልልቅ ።
ቈለጭ፡ የሰው ስም።
ቈለጭ፡ የዓሣ ስም።
ቈለጰለጠሰ - ቀለጰለጠሰ)፡ አን ቈላጰላጠሰ)፡ የቧልት የጨዋታ ግስ ። "ራሴን በራሴ ካላንቈላጰላጠስኹት ማን ያንቈላጰላጥስ ልኛል" እንዲል የቅኔ ተማሪ ። ትርጓሜውም ኰፈሰ አከበረ ማለት ነው ። ዳግመኛም በግእዛዊው "ቀለጰ"ና "ለጠሰ" ዘይቤ ሲፈቱት መብላ ትንና መተኛትን ያሳያል ። "ቀለበን" ተመልከት ።
ቈለፈ (ቈሊፍ ቈለፈ)፡ ውስጥ ለ ውስጥ ዘጋ ቀረቀረ ሸጐረ ።
ቈለፈ፡ ሸፈነ ወሸለ ።
ቈለፈ፡ አጐበጠ ቀለሰ ዐጠፈ ።
ቈለፈ፡ ያዘ ዐነቀ፡ አለቅ አለ ።
ቈለፈ—ቀላቀለ ።
ቈለፈታም፡ ልንቡጣም ቦርጫም ዘር ጣጣ ። "ቀፈትን" እይ ።
ቈለፈት፡ ሸለፈት ልንቡጥ ሸንኰፍ ሽፍን ሽፍናት ወሸላ ። በግእዝ "ቍልፈት" ይባላል ።
ቈለፈት፡ ቦርጭ ትልቅ ሆድ ።
ቈላ (ቀለወ)፡ በሠማ ምጣድ ጥሬ እኸልን አንጣጣ አበሰለ፡ በጐባጣ ዕንጨት ዐመሰ አማሰለ፡ ወጥን፡ ዐመፀኛን ጠበሰ ("(ኤር. ፳፱፥ ፳፪)") ።
ቈላ (አንሳሕስሐ)፡ አንቀሳቀሰ ወዘወዘ ነሰነሰ ። "ውሻ ጌታውን ባየ ጊዜ ዥራ ቱን ይቈላል" ።
ቈላ፡ ሰውን በጅራፍ ገረፈ፡ በጥይት
ቈላ ቍስል)፡ የቈላ ቍስል (ጐርምጥ ጫዌ ") ።
ቈላ፡ አቃረ አቃጠለ ልብን ።
ቈላ፡ ከደጋ በታች ያለ አገር፡ ወይም በረሓ ምድረ በዳ፡ ፀሓይ እንደ እሳት የሚፋ ጅበት የሚያቃጥልበት እንጭርጭር ስፍራ፡ የገሃነመ እሳት ምሳሌ ። (ተረት)፡ "እግዜር በትር ሊቈርጥ ቈላ አይወርድም" ።
ቈላ ደጋ ረገጠ፡ አንደዬ ወደ ታች አንደዬ ወደ ላይ አለ፡ አመነ ካደ ።
ቈላይ (ዮች)፡ የቈለለ/የሚቈልል (ከማሪ ") ።
ቈላፊ (ዎች)፡ የቈለፈ/የሚቈልፍ (ዘጊ ") ።
ቈላፋ፡ ጫፈ ቀላሳ ዕንጨት ከዘራ ብ ረት ። "ወንቃፍን" እይ ።
ቈላፍ፡ ወሸላ ሽፍን ያልተገረዘ አረመኔ (ግእዝ) ።በሱማልኛም "ቈለፍ" ይባላል ።
ቈላፍነት፡ ወሸላነት ("(ኤር. ፬፥ ፬፡ ሮሜ. ፬፥ ፲፡ ፲፪)") ።
ቈልማ፡ ቀንደ ዘላሳ ።
ቈልማ፡ ቀንዱ ዘላሳ ዘቅዛቃ ቀላሳ የኾነ በሬ ። "ጐዳንና ጕመላን" አስተውል ።
ቈልማሚ፡ የቈለመመ/የሚቈለምም (ቀላሽ አጕባጭ ጠምዛዥ ") ።
ቈልማሜ፡ ዳቦ ቈሎ የቈልማማ ዐይነት ወገን ።
ቈልጣባ፡ ጮሌ ጥልቅ ብዬ ።
ቈሎ (ቅልው)፡ የተቈላ በሠማ ምጣድ ላይ የበሰለ (ቅጽል) ። "ዳቦን" እይ ።
ቈመለለ፡ ዘለሰ—ቈለመመ ።
ቈመቂመ)—ቀመሰ፡
ቈመቈመ - ኰመኰመ)፡
ቈመደ (ቀመጠ)፡
ቈመደ (ጐመደ)፡ ክርን አዋሰበ፡ ድ ርና ማግን መጣፊያ አደረገ፡ የልብስን ቀዳዳ ደረተ ደበደበ ደፈነ ።
ቈመደ፡ በባላገር አይ ነገርም።
ቈመጠ (ቀመጠ)፡ የእጅንና የእግርን ጣት አቈሰለ ቈረጠ ጐመደ በጠሰ አሳ ጠረ ።
ቈመጠ፡ መታ ጠዘለ ደበደበ ነረተ ።
ቈመጥ፡ ባ፩ ወይም ባ፬ ወገን ስለት ያላት በሎታ በትከሻ የምትንጠለጠል ዐጪር ዱላ ራስ መጠበቂያ ።
ቈመጥማጣ - ቍምጥምጥ፡ የተቈማመጠ (ጕምድምድ ") ።
ቈሚጥ፡ ድንክ ዐጪር ሰው ።
ቈማመጠ፡ ቈራረጠ ጐማመደ ።
ቈማጅ፡ የቈመደ/የሚቈምድ (አዋሳቢ ደራች ") ።
ቈማጣ - ቈመጥማጣ፡ የቈመጥማጣ/ቈማጣ (ድርብ ስድብ ") ።
ቈማጣ (ጦች)፡ የተቈመጠ (ጣት አልባ ዱሽ ሽንድፍድፍ ገላውን ቍስል ድል ያደረገው አባ ጐንዳ ") ።
ቈማጣነት፡ ቈማጣ መኾን ።
ቈማጤ ።
ቈማጤ፡ የተክል ስም፡ ቈማጣ የሚመስል ጣፋጭ ፍሬ ሻካራ ፍርክርክ ።
ቈማጭ፡ የቈመጠ/የሚቈምጥ (ቈራጭ ጐማጅ ") ።
ቈሰለ (ቈሲል - ቈስለ)፡ ተነካ ተላጠ ተገጠበ ደማ ።
ቈሰለ፡ በጦር ተወጋ (በቀስት ተነደፈ በሰይፍ በጥይት ተመታ ") ።
ቈሰለ)፡ ዐዘነ ተናደደ ።
ቈሰሰ - ቈረሰሰ - ጐሰሰ)፡ ተንቋሰሰ፡ ተንቈረሰሰ ተጐተተ ።
ቈሰቈሰ (ኰሰኰሰ)፡ ጠቀሰ ገፋ አገባ ጨመረ (ማገዶን ወደ እሳት ቈሰቈሰ ") ። ነካ አወከ ። "ጐተጐተን" እይ ።
ቈሳሰለ፡ በብዙ ወገን ቈሰለ ።
ቈሳቍስ፡ የቤት ዕቃ ሰባራ ሥንጥር ። "ቈሳቊስ በግእዝ ዕቆች ማለት ነው፡ አንዱ ቈሰቈስ ይባላል" ።
ቈሳቈሰ፡ ፋፋ ጨማመረ ።
ቈስቋሽ (ሾች)፡ የቈሰቈሰ/የሚቈሰቍስ (ጠቃሽ ገፊ ጨማሪ ") ።
ቈስቋሽነት፡ ቈስቋሽ መኾን ።
ቈስጠንጢኖስ፡ በ፪፻፺፱ ዓ ም በግሪክ አገር የነገሠ መዠመሪያ የክርስቲያን ንጉሥ ።
ቈሥፌ፡ መልካም ሽታ ያለው ዛፍ ።
ቈረ፡ ፈጽሞ ደኸየ (የለት ጕርሥ ያመት ልብስ ዐጣ ነጣ መነጠ ") ።
ቈረመ፡ በቀላል፡ መታ፡ ኰረኰመ፡ ራስን።
ቈረመመ፡ አሾለቀ/አሾጠጠ ።
ቈረመደ)፡ ተቈራመደ፡ ተጨበጠ/ተኰራመተ (ከችግር ከብርድ የተነሣ ") ።
ቈረመድ - ቈርማዳ፡ የተቈራመደ (ጨባጣ ኰርማታ ") ።
ቈረሰ፡ ፈተተ ገመሰ ገመደለ ቀረደደ ከፈለ ጐረመደ ("(ማቴ. ፲፬፥ ፲፱ ። ሉቃ. ፱፥ ፲፮)") ።
ቈረሰሰ - ቈሰሰ)፡ አንቈረሰሰ፡ ዝኒ ከማሁ፡ እንቀረደደ ።
ቈረሳ፡ ፍተታ ።
ቈረረ (ቈለለ)፡ ጫነ ደረበ አነባበረ ።
ቈረረ (ቈሪር - ቈረ)፡ በረደ ቀዘቀዘ ።
ቈረረ፡ ቈረሰ ።
ቈረር፡ ድርብ የደንጊያ ምልክት ።"አንድ ቊራ በታየ ጊዜ መንገደኞች ኹለት ደንጊያ ያነባብራሉ" ።
ቈረቈሰ፡ አጫረ ጠብን ጦርነትን ዠመረ ፈተነ ።
ቈረቈሰ፡ የገና ጨዋታን ባረከ፡ ዕሩርን መታ (በትርን ገዉ ") ።
ቈረቈረ (ዕብ ቃር)፡ ማሰ ቈፈረ ሰ ረሰረ በሳ ነደለ ሸነቈረ (ከተማን መሠረተ ዠመረ ") ። "ዘሩ ቈረረ" ነው ።
ቈረቈረ፡ መታ ጠረጴዛን ገበታን ።
ቈረቈረ፡ አቈሰለ ራስን ።
ቈረቈረ፡ ወጋ ጐረበጠ ነካ አሳመመ (ገላን ሆድን ዐይንን ") ።
ቈረቈረ፡ ደፈነ መረገ ጠቀጠቀ (የሸክ ላን ቀዳዳ በዶሮ ማርና በብረት ዐር በጨርቅ በሾኸ ") ። "ደበደበን" እይ ።
ቈረቈራም፡ ቈረቈር ያለበት የበዛበት ልጅ ።
ቈረቈር፡ የራስ ቍስል (ከመጥፎምላE ከፀሓይ ሙቀት የተነሣ የሚመጣ ") ።
ቈረቈንዳ፡ ፍሬው የወጣ ያገዳ ራስ ።
ቈረቈዘ (ቀርቀም)፡
ቈረቈዘ፡ ጐኑ ጠበበ፡ ቁመቱ ዐጠረ ።
ቈረበ (ቀረበበ)፡ ተቀራረበ ተጠጋጋ ተገነኛኘ ።
ቈረበ (ቀርበ)፡ ቀደሰ ሠለሰ፡ ቍርባን ሥጋ አምላክ ተቀበለ ።"ከቈረበች ባሰች ከመነኮሰች አፈረሰች" እንዲሉ ።
ቈረበ፡ ጐረበ ተቋጠረ ውሃ ያዘ ዐዘለ ዐተረ ።
ቈረበበ)፡ አንቈረበበ፡ አቈረበጨ ። አጐረበ ። በተገብሮነትም ይፈታል።
ቈረበብ - ቈርባባ፡ የተንቈረበበ/የሚንቈረበብ (ቍርብጭ ") ።
ቈረበተ፡ ቈርበት ኣለበሰ ጐለበ ለጐመ ።
ቈረባ (ትግ ቈርብዐ)፡ ደረቀ ።
ቈረነ፡ ዐወደ ቦጨቀ ።
ቈረነ፡ ዶንጊያ ተከለ (ምልክት አደረገ ") ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፭)") ። ትርጓሜ ። "ቈረረን" እይ፡ ነና ረ ይወራረሳሉ ።
ቈረነ፡ ዶንጊያ ተከለ ምልክት አደረገ ("(ሕዝ. ፴፱፥ ፲፭)") ። ትርጓሜ ። "ቈረረን" እይ፡ ነና ረ ይወራረሳሉ ።
ቈረን፡ የጤፍ አገዳ ቅሬታ (እንደ ቀርን (ቀንድ) ሽቅብ የቆመ ያሾተለ ") ። "የጤፍ ቈረን" እንዲሉ ።
ቈረኘ (ትግ ቁረነ)፡ አሰረ ጠመደ ። ገረኘን አስተውል ።
ቈረኘተ (ቈረኘ)፡ ነፋ ጐሰረ ።
ቈረዘ፡ ሸረበ፡ ቍርዝ አወጣ፡ ሸፈነ ።
ቈረዘዘ)፡ ኣንቈረዘዘ፡ አንጠለጠለ ("(ተንጠለጠለ)") ።
ቈረጠ (ቀረፀ)፡ ጐረደ ጐመደ መደ መደ ሸለተ በጠሰ (እንዳገዳ ከፍ እንደ ባቄላ ከሥር ") ። አጠፋ ("(ኤር. ፪፥ ፳)") ። "አፈፈን" "ዋጋን" "ካሳን" "መቅንን" "ሤራን" "ቀጻን" "ተስፋን" እይ ።
ቈረጠ፡ ሐሳቡን አንድ ወገን አደረገ፡ ጨረሰ ፈጸመ ።
ቈረጠ፡ ሆድን ዐመመ ።
ቈረጠ፡ ለየ ወሰነ ቀንን ።
ቈረጠ፡ ቀነሰ አጐደለ ።
ቈረጠ፡ ፍርድን ሻረ ደመሰሰ ለወጠ፡ ወይም ኣጸና አጸደቀ (ጥፋተኛን በመቅጣት በመግደል ") ።
ቈረጠመ፡ ገላን ዐጥንትን ዐመመ ።
ቈረጠመ፡ ጐረደመ በጥርስ ሰበረ ከረተሰ ዐኘከ በላ (ዕንጨትን ጥሬን ቈሎን ምላስን ") ("(ራእ. ፲፮፥ ፲)") ። ቈረጠመ እንደ መከርተፍ ዐንከ እንደ መሰለቅ ነው ።
ቈረጠጠ)፡ አንቈራጠጠ፡ አላሳርፍ አለ፡ አንጐራደደ ።
ቈረጠጥ - ቈርጣጣ፡ የተንቈራጠጠ (ጐረደድ ጐርዳዳ ") ።
ቈረጣ፡ የመቍረጥ ሥራ (አገዳ ቈረጣ ዕንጨት ቈረጣ ጠጕር ቈረጣ ወይን ቈረጣ እንዲሉ ") ("(ሚክ. ፯፥ ፩)") ።
ቈረጣጠመ፡ ዐኛኘከ በላላ፡ ዐማመመ ።
ቈረጪ፡ ዐጠረ ዐጢር ኾነ ።
ቈረፀ (ቈሪፅ - ቈረፀ)፡ ቈረጠ ሸለተ አሳጠረ ።
ቈረፈ፡ ቈፈረ ማሰ ከፈለ ተነተነ ።
ቈረፈ፡ ጨረፈ ለኰፈ፡ መለሰ ቀለበሰ ።
ቈረፈደ፡ ደረቀ ሻከረ ልስላሴ ዐጣ (ዳባው ቍርበቱ ") ።
ቈረፈድ - ቈርፋዳ፡ የቈረፈደ/የሚቈረፍድ (ደረቅ ሻካራ ቈዳ ") ።
ቈረፈፈ)፡ ቈረቈዘ ።
ቈረፈፈ)፡ አንቈረፈፈ፡ ቈፈነነ (የ እጅን ጣት ቈለፈ ወበጠ ") ።
ቈሪ (ቈራሒ - ቀራዒ)፡ የቈራ/የሚ ቈራ (በጪ ተኳሽ ቀቢ ነቃሽ ቈራሚ ") ።
ቈሪት፡ የእንስት በግ ስም ።
ቈሪፍ፡ ዝኒ ከማሁ (ዦሮ ትልቅ ") ።
ቈራ - ቍር ።
ቈራ (ቀርሐ)፡ ቦቀረ ላጩ ነጩ ።
ቈራ (ቈርሐ - ቀርዐ - ኰርዐ)፡ በጣ ፈቃ ጋረጠ፡ ተኰሰ ነቀሰ፡ ቀባ ምልክት አደረገ፡ መታ ቈረመ ።"ስም ጠርቶ ራስ ቈርቶ" እንዲሉ ።"ቈርሐ" ትግሪኛ ነው ።
ቈራሚ፡ የቈረመ፡ የሚቈርም፡ መቺ፡ ኰርኳሚ ።
ቈራሳ፡ ገማሳ ።
ቈራረሰ፡ ፈታተተ ገማመሰ ከፋፈለ ።
ቈራረጠ፡ ጐራረደ ጐማመደ ("(፪ዜና. ፴፬፥ ፯)") ።
ቈራሪ፡ የቈረረ/የሚቈርር (ደራቢ አነባባሪ ") ።
ቈራሽ (ሾች)፡ የቈረሰ/የሚቈርስ (ፈ ታች ") ።
ቈራቢ (ዎች)፡ የቈረበ/የሚቈርብ (ቀዳሽ ሠላሽ ") ። በቍርባን የተወሰነ ምእመን ።
ቈራብት፡ ቈርበቶች ማሶች ።
ቈራን፡ ለኰፈን፡ አስተውል።
ቈራጣ (ጦች)፡ አካለ ጐደሎ ። "እግረ ቈራጣ ዥራተ ቈራጣ" እንዲሉ ።
ቈራጣ፡ የደሴት ስም (በጣና ውስጥ ያለ ደሴታዊ አገር ") ። ባጠገቡ ካለው የብስ ባሕር የቈረጠው የለየው ማለት ነው ።
ቈራጤ፡ የቈራጣ (ቈራጣዊ ") ። "የኔ ቈራጣ"፡ ሥሥ ልብስ በቀላል የሚቀደድ ።
ቈራጥ (ጦች)፡ ሐሳቡን ባንድ ነገር ላይ ያደረገ የማያወላውል (በሞቱ የቈረጠ ጐበዝ ") ("(ምሳ. ፭፥ ፱)") ።"ድኻ ቈራጥ ነው" እንዲሉ ።
ቈራጥ ወለቴ፡ በቈራጣ ውስጥ የነበረች ቅድስት ("የቈራጣ ወለቴ ") ።
ቈራጥ፡ የተቈረጠ ።
ቈራጥነት፡ ቈራጥ መኾን ።
ቈራጭ፡ "እጅና እግርን ወይም ዐንገትን" ።
ቈራጭ (ጮች)፡ የቈረጠ/የሚቈርጥ (ጐራጅ ጐማጅ ጨራሽ ") ። "እንጥል ምንጭር ነገር ዕንጨት ቀፎ ቀባ ቈራጭ" እንዲሉ ።
ቈራጭ፡ ባለወግ ሰያፊ ገራፊ ሰቃይ ገዳይ ። በግእዝ "መስተራትዕ" ይባላል ።
ቈራጭ፡ ዋና የበላይ ጠቅላይ ሹም ራስ ደጃዝማች (ከበታቹ ያሉ ብዙዎች አገረ ገዢዎች የፈረዱትን ፍርድ የሚልጥ የሚሽር የሚለውጥ የሚገለብጥ የሚያጸድቅ ") ።
ቈራጭ ፈላጭ፡ የወንጀለኛን እጅ እግር የሚቈርጥ ንጉሥ (ከራስ እስከ ፈጋራ መኻል ለመኻል ሰውን የሚፈልጥ አረመኔ ") ።
ቈራጭነት፡ ቈራጭ መኾን (የበላይነት ") ።
ቈራፋ፡ ዦሮው የረዘመና የተቀለበሰ ሰው ።
ቈሬ፡ የሰው ስም ።
ቈሬ፡ የቤት ዕቃ ስም (በጣባ በወጭት በሳሕን አምሳል የታነጸ ዕቃ ") ። ዘሩ ቈረ ቈረ ይመስላል ። "ገበቴን" እይ ።
ቈርሪቋ፡ የቈረቈረ/የሚቈረቍር (መሥ ራች ጐርባጭ ወገ ደፋኝ ") ።
ቈርቍር፡ በሺ ሸንቋሪ ።"ግንደ ቈርቍር" እንዲሉ ።"ቈርቍር የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ ሲኾን በቅጽልነትመፈታቱን" አስተውል ።
ቈርቈሮ፡ ፈረንጆች ብረትነት ያለውን ደንጊያ አቅልጠው የሠሩት ብረትማ (የቤት ክዳን ቦይና ሸንተረር ያለው ") ።"በምስማር እየተ ቈረቈረ ስለሚከደን ቈርቈሮ ተባለ" ("(ዘኍ. ፴፩፥ ፳፪ ። ኢሳ. ፩፥ ፳፭)") ። በግእዝ "ናእክ" ይባላል ።
ቈርቋዛ፡ የቈረቈዘ/የማያድግ (ዐጪር ልጅ ጥጃ ") ።
ቈርበተ ሐሊብ፡ የወተት ስልባቦት (ለጋ ቅቤ የንቍላል አስኳል የሚመስል ብጫ የሰደፍ ዶቃ ወይም መቍጠሪያ ባለመዐዛ ") ። በግእዝ "አርማስቆስ" ይባላል ። "ቀሀረማንን" እይ ። ቈርበት ካሪም፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቈርበተ ሞኝ፡ ሲያዩት አላዋቂ የሚ መስል ሰው ።
ቈርበተ ዐሊም - ቈርበት (ርበት)፡ የጸሎት ዕቃ መቍጠሪያ ። ዐሊም የተማረ ማለት ነው ።
ቈርበት (ኵርበት)፡ የተ ለፋ ቈዳ (ለሰው መኝታ ምንጣፍ የሚኾን ") ። ነት ተንቤን ማስ ። ሲበዛ "ቈርበቶች" "ቍርበቶች" ያሠኛል ።
ቈርበት ነክ፡ ሥር የሌለው ነገር ።
ቈርበት፡ የሰው ገላ ቈዳ ("(ዘሌ. ፲፫፥ ፪ - ፫ - ፬)") ።
ቈርባ ቈርባ አለ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቈርነናታም፡ እንቍራሪትኛ የሚጮኸ ።
ቈርነናት (ቈርነናዓት)፡ ጓጕንቸር እንቍራሪት ጯኺ ነወሬ ።
ቈርኬ፡ (ኦሮ)፡ ቀጪኔ።
ቈርኬ፡ የቢራ፡ መክደኛ።
ቈርዛዛ፡ የተንቈረዘዘ (እንቍርዝ ") ።
ቈርጠጥ ቈርጠጥ አለ፡ ጐርደድ ጐርደድ አለ ።
ቈርጣሚ፡ የቈረጠመ/የሚቈረጥም (ጐርዳሚ ") ።
ቈርጦ ቀጥል፡ ዐባይ ጐመድ ቀጣፊ ኹለት ምላስ ።
ቈርጦ፡ በጥሶ ጐምዶ ።
ቈርጦ ኼደ፡ ሐሳቡን ከዓለም ለይቶ ወደ መንፈሳዊ ሥራ ዐለፈ ነጐደ ። "ደበረ" ብለኸ "ተድበረበረን" አስተውል ።
ቈሸሸ፡ አደፈ ተበከለ ተኵለፈለፈ (ትቢያ ለበሰ ") ።"በየቀኑ የማይጠረግ ቤት ይቈሽ ሻል" ።
ቈሸበ (ትግ ሐባ ቈሽበ - ዝግተኛ ኾነ)፡ ጀጀበ ጀጀረ፡ መብል ከለከለ ።
ቈሸበለ)፡ አንቈሻበለ፡ ለመነ ተለማ መጠ አባበለ አቀማጠለ ።
ቈሸንዳ፡ የከሳ ሰው ("ወይም ከብት") ።
ቈሸዳም፡ ቈሸድ ያለው (ባለቈሸድ ") ።
ቈሸድ፡ የደረቀ እንጀራ ("ዘኬ") ።
ቈሻ፡ ርጥብ፡ የማሽላ እንቀት፡ የሐረርጌ ሴቶች አስቀድሞ በሙቀጫ ይወቅጡታል፡ ዳግመኛም ያልሙታል ይለነቅጡታል ።
ቈሻሻ፡ የቈሸሸ (እድፋም ጽዳት የሌለው ዐሣማ ") ።
ቈሻባ - ቍሽብ፡ የተቈሸበ (መብል የማ ይገፋ ") ።
ቈሽት (ቶች)፡ ሆድ ዕቃ (ከጨጓራ ጋራ ያለ ሥጋዊ ከረጢት የብጥብጥ ምግብ መታቈሪያ ") ። በግእዝ "ቈሥጢ" ይባላል ።
ቈሽት አንድድ፡ ሀኬተኛ ልግመኛ እከየኛ ሰው ።
ቈቀረ፡ አነሰ ጠቀነ ዐጪር ኾነ ።
ቈቀር (ሮች)፡ ታናሽ የዕጣን ቅንጣት ልዝብ ጣፋጭ ። "አንኳርን" እይ ።
ቈበራም፡ ቈበር ያለው/ባለቈበር ። ቈበረ፡ ቈበሩን ደፈቀ (ካፉ አወጣ አፈሰሰ ") ።
ቈበር፡ ቆበር (ካፍ የሚወጣ ብዙም ራቅ ዐረፋ ") ።
ቈበቈበ (ጐበጐበ - ኰበኰበ)፡ ዐተረ ጐረበ ቈረበ ቍብ ቍብ አለ ።
ቈበበ (ጐበበ)፡ ገላውን ሰብስቦ እንደ ቈቦ እንደ ጕብ በቀላል ተቀመጠ ። "ሸረቈጠን" ተመልከት ።
ቈባ፡ ቀበደደ ።
ቈባ፡ ተናጋሪ ሴት ተናጣቢ (አፈኛ ምላሰኛ ") ።
ቈባባ፡ የቈበበ ጐባባ ።
ቈብቋባ፡ የቈበቈሰ/የሚቈበቍብ (ጕርብ ቍርብጭ ") ።
ቈቦ፡ ባንኮበር በኩል ያለ አገር ። "ሐር ዐምባና ቈቦ" እንዲሉ ። የቈባና የቈቦ ዘር ቈ በበ ነው።
ቈቦ፡ የዛፍ ስም (አነስተኛ ወተታም ዕንጨት ") ። ቅል በሚያካክል የፍሬው መሸፈኛ ውስጥ ነጭ ሐር የሚመስል ባዘቶ አለው፡ ወተቱም ለመጋኛ መድኀኒት ይኾናል። ዳግመኛም "ጦቢያ"፡ ሦስተኛም "ቅንቦ" ይባላል ። ጋሳም ጕሎን ቈቦ ይለዋል ።
ቈተመ፡ ነቃ ተጋ ።
ቈተመ፡ ጓጓ ሰለፈ (አንድ ነገር ለማ ግኘትና ለማድረግ ") ።
ቈተቸ (ቀተወ)፡ ውርርድ አደረገ ።
ቈታሚ፡ የቈተመ/የሚቈትም (ሰላፍ ") ።
ቈቻ፡ ብርታት ጥንካሬ ። ዘሩ "ቈተቸ" ነው ።
ቈቻ ዋለ፡ ከቀትር በፊት ካንድ በሬ ከቀትር በኋላ ከሌላ በሬ ጋራ ተጠመደ ዐረሰ ("ከኹለት ተወዳደረ ") ።
ቈነ፡ ለቀመ አጥመዘመዘ ገደለ ሰው የው ።
ቈነሰ፡ በሰበሰ ገማ ጠነባ ።
ቈነሠ፡ ገማ ። ቈነሰ ።
ቈነቈነ (ቈንቈነ)፡ ነቀዘ ጠነጠነ ተላ ። "ቀነቀነን" እይ ።
ቈነቈነ፡ ሠሠተ ቈጠበ ።
ቈነቈነ፡ ከተፈ ሸከፈ ተነተነ ። "ቈነነን" እይ፡ የዚህ ሥር ነው፡ "ቀነቀነን" አስተውል ።
ቈነነ፡ ለካ መጠነ ሰፈረ ድርጎን ።
ቈነነ፡ ቀስ አደረገ በቀስታ አስኬደ ጀነነ አኰራ አጓደደ አቋፈ ።
ቈነነ፡ ታታ ጐነጐነ ሸረበ ሠራ ጭ ራን የራስ ጠጕርን፡ ቋድ አስመሰለ ። "ጐነነን" ተመልከት ።
ቈነን ቈነን፡ ቶሎ ቶሎ አለመኼድ ።
ቈነዠ (ቍንዝዕ - ቈንዳላ)፡ ኦሞላ አማረ ተዋበ፡ የሴት ልጅ ገላ ። በቈነዠ ፈንታ "ቈነጀ" እየተባለ ይጻፋልና ስሕተት ነው ።
ቈነዠች፡ ዐቅመ ሔዋን አደረሰች፡ ጠ ጕሯ እትከሻዋ ላይ ወረደ ።
ቈነዣዥት፡ ዝኒ ከማሁ (የሚያማምሩ ልጃገረዶች ") ("(ዓሞ. ፰፥ ፲፫ ። ፩ጢሞ. ፭፥ ፪)") ። በግ እዝ "ደናግል" ይባላሉ ።
ቈነደለ፡ ሽሩባ ሠራ ጐነጐነ ቈነነ ዐ ተቈነደለ፡ ተጐነጐነ ተቈነነ ።
ቈነደደ (ነደደ)፡ በቋንዶ ገረፈ ለቈ ጠጠ ።
ቈነደደ፡ አደረቀ አሻከረ አሳጠረ ቁመ ትን ።
ቈነዳ (ቈንደየ)፡ ዘለለ ረገደ ።
ቈነጠ (ቀንጠወ)፡ ሆዱ ተነፋ ቍን ጣናም ኾነ ።
ቈነጠ፡ ጐነጠ ነካ በንክሻ ።
ቈነጠለ፡ ቈነጸለ ።
ቈነጠረ፡ ነካ በሦስት ጣት ያዘ፡ ጥ ቂት አነሣ ወሰደ ። "ቈጠበን" ተመልከት ።
ቈነጠረ፡ ወጋ ነከሰ ጫረ ዶሮ ሰውን ።
ቈነጠነ (ቀንጠወ)፡ ነፋ ከረበ ሆድን ።
ቈነጠጠ፡ ለመዘገ ቀጣ ልጅን ።
ቈነጠጠ፡ ረገጠ ርካብን በእግር አውራ ጣት ።
ቈነጠጠ፡ ሸፈነ ጠቀለለ ማገረ ጣራን በግምጃ በሐር ።
ቈነጠጠ፡ ነከሰ በላ ትንኝ ጕንዳን ገላን ።
ቈነጠጠ፡ አጣበቀ አጣብቆ ያዘ እሾ ኸን ምስማርን በወረንጦ፡ በጕጠት ትንባኾን በጣት ።
ቈነጣጠለ - ቈነጻጸለ ። አስቈነጠለ - አስቈነጸለ ።
ቈነጣጠረ፡ ከዚያም ከዚያም ላመል ላመል ወሳሰዶ ።
ቈነጥ፡ ትንኝ ዝንብ ባፉ የሚጐንጥ ። ቈነጤ፡ የቈነጥ ዐይነት (የሐሜት ስም ") ።
ቈነጩ፡ ቍንጫ ኾነ፡ ቍንጫ አፈራ
ቈነጩ፡ ነቀሰ አሳደገ ቍንጮን ።
ቈነጯ፡ ዐረምን ውራን ጐለጐለ ነቀለ ።
ቈነጸለ፡ ቈረጠ ገነጠለ ጥራዝን ።
ቈነጸለ፡ ኰሰተረ ሰበረ አለማ መብራ ትን ። "ተረከሰን" እይ ።
ቈነጻጸለ፡ ሰባበረ ከሰልን ።
ቈነጻጸለ፡ ቈራረጠ ገነጣጠለ ።
ቈናኝ (ኞች)፡ የቈነነ/የሚቈንን (ጐን ጓኝ ሸራቢ ጠጕር ሠሪ ") ።
ቈንቋና (ትግ ቈንቋን)፡ ዝኒ ከ ማሁ (ቈጣቢ ሥሥታም ") ።
ቈንቋኔ፡ የቈንቋና ወገን (እንደ ነቀዝ በቀስታ ሰውነትን የሚጐዳ "ቅኔ ቈንቋኔ" እንዲሉ ") ።
ቈንቋኝ፡ የቈነቈነ/የሚቈነቍን (ተን ታኝ ") ።
ቈንዢት፡ የሴት ስም ።
ቈንዦ፡ የቈነዠች ያማረች የተዋበች ውብ ደማም መልከ መልካም ያ፲፭ ዓመት ልጃገረድ፡ ደረተ ሳንቃ ዐንገተ መቃ አፍ ንጫ ስንደዶ ጥርሰ በረዶ ። (ተረት)፡ "የስንዴ ዐራራ የቈንዦ መራራ" ። በልማድም ወንድ፡ ቈንዦ ይባላል ። ቈንዦ የሚነገረው ለ ልጃገረድና ለምታምር ሴት ሲኾን፡ ጣሊያን ገዝቶ ከኼደ፡ "ቈንዦ ቤት ቈንዦ መብል ቈንዦ ልብስ" እየተባለ በአዲስ አበባ ይነገራል። ሴትን ከወንድ ለመለየት ።
ቈንዦነት፡ ዝኒ ከማሁ ("(ኤር. ፫፥ ፬)") ።
ቈንዦዋ - ቈንዦዪቱ፡ ያች ቈንዦ ("(ኤር. ፲፬፥ ፲፯)") ።
ቈንዦዎች፡ የሚያምሩ ሴቶች ።
ቈንደል፡ የማሽላ ስም፡ መልኩ ብጫ ዋሜራው ረዥም የኾነ ማሽላ ኮልኝ ። (ግጥም)፡ "ከማሽላው ቈንደል ከጤፉ ጐራዴ ረ ለማን ኛው ታደላለኸ ሆዴ" ።
ቈንዳ ቈንዳ አለ፡ መር መር አለ ።
ቈንዳላ፡ ጕተና ጐፈሬ ረፍረፎ ጠጕር ("(ማሕ. ፭፥ ፪፡ ፲፩ ። ኢሳ. ፵፯፥ ፪)") ። በጋልኛ ግን ወጣት ልጅ ማለት ነው ።
ቈንዳዳ፡ ደረቅ ሻካራ ያጠረ ጠጕር ።
ቈንዳጅ፡ የቈነደደ/የሚቈነድድ (ገራፊ ") ።
ቈንጣሪ (ዎች)፡ የቈነጠረ/የሚቈነ ጥር (አሳንሶ የሚወስድ የሚሰጥ ") ።
ቈንጣይ - ቈንጻይ ።
ቈንጣጭ፡ የቈነጠጠ/የሚቈነጥጥ (የሚ ነክስ ነካሽ ረጋጭ ") ("(ዘዳ. ፯፥ ፳)") ።
ቈንጥር (ስም)፡ እሾኸ ቈላፋ የበረሓ ዕንጨት ። ሲበዛ "ቈንጥሮች" ይላል ።
ቈንጥር (ትእዛዝ አንቀጽ)፡ ውጋ ንከስ ።
ቈንጪ፡ የቈነጨ/የሚቈነጭ (ለቃሚ ጐልጓይ ") ።
ቈንጻይ፡ የቈነጸለ/የሚቈነጽል (ኰስታሪ ") ።
ቈኘተ፡ ታታ አሠባጠረ አዋሰበ ።
ቈወጪ፡ ቍጫጭ አፈራ ።
ቈዘመ፡ ዐዘነ ተከዘ አለቀሰ (አሞሸ ዋይ አለ ") ("(ሕዝ. ፳፩፥ ፮ - ፯፡ ማር. ፯፥ ፴፬፡ ፪ቆሮ. ፭፥ ፪ - ፬)") ።
ቈዘረ፡ ጐኘረ ነፋ ጐሰረ ። "ቈረዘን"
ቈዝሞ፡ ዐዝኖ ተክዞ ("(ማር. ፰፥ ፲፪)") ።
ቈየ (ዕብ. ቃዌህ)፡ ባንድ ስፍራ ጥቂት ወይም ብዙ ጊዜ ተቀመጠ ኖረ ነበረ ዘገየ ("(ዘፍ. ፯፥ ፲፪)") ። "የቈየ ሰው የዘገየ መጨረሻውን ያየ" (አዝማሪ) ።
ቈየ፡ ቆመ ጠበቀ ሰውን ።
ቈየት አለ፡ ዘግየት አለ ።
ቈየት፡ ዘግየት ።
ቈዪ (ቀላዊ)፡ የቈላ/የሚቈላ ። ያለ ፈው አንቀጽ፡ የሚመጣው ስም መኾኑን አስተውል ።
ቈይ፡ አትኺድ፡ እዚሁ ተቀመጥ፡ ሥራን ነገርን ተው ። (ተረት)፡ "ኣላቻ ጋብቻ ቈይ ብቻ ቈይ ብቻ" ።
ቈይታ፡ የባለሥልጣኖች ብቻ ምክር፡ የምስጢር ንግግር ። በፈረንጅኛ "ሲያንስ" ይባ ላል ።
ቈይታ ያዘ፡ ንጉሡከባለሎቹ ጋራ
ቈደሰ (ቀወመ)፡ ቈደሰ (ቀደሰ)፡ ቈረሰ ከፈለ (ጥቂት ጥቂት በላ ዛቲን መክፈልትን ከቅዳሴ በኋላ ") ።
ቈዳ፡ የሥጋ ኹሉ ልብስ መሸፈኛ (ርጥቡም ደረቁም ቈዳ ይባላል ") ። "የበሬ የበግ የፍየል ያጋዘን የሡሥ የምዳቋ ቈዳ" እንዲሉ። (ግጥም)፡ "ባህያ ቈዳ የተሠራ ቤት ብትንትን ይላል ዥብ የጮኸ ለት" ። "አንጋሬንና ሌጦን" እይ ።
ቈዳ፡ ፍሬ የማይሰጥ መሬት ።
ቈጊ፡ የቈጋ/የሚቈጋ (ገራፊ ") ።
ቈጋ፡ ገረፈ (በጅራፍ መታ ቈነደደ ") ። "ጋ ጋን" ተመልከት ።
ቈጠሰ፡ ከፈለ ለየ ርስትን ።
ቈጠረ (ቈጸረ)፡ አንድ ኹለት ሦስት አለ፡ ዐሰበ አሰላ፡ ፊደል ተማረ ።
ቈጠረ፡ ርስቱን ከብቱን በወንድ ዐማቱና በጨዋ ፊት ዘረዘረ ነገረ አስረዳ አስታወቀ ።
ቈጠረ፡ ቅኔ አዘጋጀ፡ ቤት መታ ። (ግጥም)፡ "ሰዋስው ጨዋታ ዐማርኛ ቅኔ፡ ቈጥረኸ ስደድልኝ እፈታለኹ እኔ" ።
ቈጠራ (ቈጸራ)፡ የመቍጠር ሥራ ።
ቈጠቈጠ (ቈጠጠ ቀጠጠ)፡ እሾኽ ቍጥቋጦ ቈረጠ መለመለ ("(ዳን. ፬፥ ፲፬፡ ፳፫)") ። "ኰተኰተን" ተመልከት ።
ቈጠቈጠ፡ ለበለበ ፈጀ አቃጠለ አን
ቈጠቈጠ፡ ቈጠበ ቈነቈነ ቈነጠረ ።
ቈጠቈጥ - ቈጥቋጣ፡ የተንቈጣቈጠ/የሚንቈጣቈጥ (ቈንቋና ቈጣቢ ") ።
ቈጠቈጭ - ቈጭቋ፡ የተንቈጨ ቈ ስብርብር እንክትክት ።
ቈጠበ፡ በልክ በመጠን በስሌት በሒሳብ በቍጥቍጥ ገንዘብ አወጣ፡ ወጪን ቀ ነሰ አሳነሰ፡ ተቀማጭን አበዛ አበረከተ፡ በየጊዜው ገንዘብ አስቀመጠ ያዘ ጨበጠ አ ተረፈ አካበተ ።
ቈጠጠ (ቈጢጥ ቈጠጠ)፡ የወተት ኵስ ኰሳ ዐራ ። "ቈጠቈጠን" እይ ።
ቈጠጯ፡ ቍጭ አለ ። "ጐቸን" እይ ።
ቈጣ - ቈጥዐ)፡ አስቈጣ አስገሠጸ አዘለፈ አስገላመጠ ።
ቈጣ አለ፡ ጥቂት ሖምጠጥ አለ ።
ቈጣስር (ቈጥ አስር አሰር)፡ የጋ ብቻ ስም (ውሉ በቈጥ የታሰረ የተፈጸመ ጋብቻ ") ። "እሚስቱ አባት እናት ቤት ኼዶ የሚኖር ወንድ በታዛይ ከሚስቱ ጋራ በቈጥ ስለሚተኛ ጋብቻቸው ቈጣስር ተባለ፡ ይኸውም ማተብንና ቀለበትን ቃልን ያስተርጕ ማል" ።
ቈጣሪ (ሮች)፡ የቈጠረ/የሚቈጥር (ተማሪ ዘኬ ቈጣሪ ") እንዲሉ። "ኮከብን" እይ ።
ቈጣሪ፡ የተበራውን ኤሌትሪክ ልክ የተቀዳውን ውሃ መጠን የሚነግር መኪና በውስጡ የሚዞር ቍጥር ያለበት ።
ቈጣቈጠ፡ ቈራረጠ/መላመለ ።
ቈጣቢ (ዎች)፡ የቈጠበ/የሚቈጥብ (አስቀማጭ ጨባጭ አካባች ") ።
ቈጣጠረ፡ መላልሶ ቈጠረ ።
ቈጣጭ፡ የቈጠጠ/የሚቈጥጥ (ጥጃ ግልገል ሕፃን ") ።
ቈጥ (ቀጣ)፡ አራት እግሩ እመሬት የተተከለ የንጨት ዐልጋ (ሲበዛ ቈጦች ይላል ") ።
ቈጥ፡ የንጨቱን ትክክል ኹኖ መቈ ረጥ ያሳያል ። (ተረት)፡ "የቈጡን ኣወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" ።
ቈጥቋጭ፡ የቈጠቈጠ/የሚቈጠቈጥ (ለብ ላቢ ቈራጭ መልማይ ") ።
ቈጨቈጪ፡ ጣትን ከጣት ኣዋሰበ (አ ስታገለ አስተናነቀ ") ።
ቈጨበረ፡ ብስጩ ኾነ ።
ቈጨበር - ቈጭባራ (ሮች)፡ ቍጡ ብስጩ ዐመለ ቢስ ።
ቈጨጨ፡ አነሰ ቍርንጫጭ ኾነ ። "ጐጨጨን" አስተውል ።
ቈጫ (ኦሮ)፡ ዔሌ ድንጋይ ልብሱ ።
ቈጫ፡ ያገር ስም (በወላሞ ክፍል ያለ ወረዳ ማለፊያ - ቡልኮ የሚሠራበት ") ።
ቈጮ (ወላሞ)፡ እንሰት ።
ቈፈረ (ቀፈረ)፡ ማስ ጫረ መነ ቀረ ኳተ ኰተኰተ ጐደፈረ አጐደጐደ ("(ዘፍ. ፳፯፥ ፲፱ ። መዝ. ፯፥ ፲፭)") ። (ተረት)፡ "ሲቀላውጡ ዐይን አፍጦ፡ ሲቈፍሩ አንፈራጦ" ።
ቈፈር፡ ማስ ማር ።
ቈፈር ቈፈር አደረገ፡ ማስ ማስ ሣር ጫር አደረገ ።
ቈፈቈፈ)፡ አንቈፈቈፈ፡ አስጮኸ አስጠራ ።
ቈፈቈፍ - ቈፍቋፋ፡ የተንቈፈቈፈ/የሚንቈፈቈፍ (ጯኺ ጠሪ ዶሮ፡ ንፉግ ሥሥታም ቈጥቋጣ ሰው ") ።
ቈፈነ፡ በረደ ቀዘቀዘ ።
ቈፈነነ፡ ዐጠፈ ጨበጠ አደረቀ ጣትን ። "ጐፈነነን" ተመልከት ።
ቈፈነን - ቈፍናና፡ የተቈፈነነ/የታጠፈ የተጨበጠ ።
ቈፈናም፡ ቈፈን የያዘው (ባለቈፈን ጣቱ ሊይዝና ሊጨብጥ የማይችል ") ።
ቈፈን፡ ብርድ ቅዝቃዜ ።
ቈፈጠነ፡ ጕድለት አልባ ኾነ ።
ቈፋሪ (ሮች)፡ የቈፈረ/የሚቈፍር (ማሽ ዶመኛ ") ።
ቈፋፈረ፡ ጫጫረ መነቃቀረ ።
ቈፍና፡ በመርሐ ቤቴ ክፍል ያለ አገር ብርድ ያለበት ።
ቈፍና፡ የሩቅ ሴት ቦዝ አንቀጽ ነው ።
ቈፍጣና (ኖች)፡ ዝግጁ ድርጁ ስንዱ (በሞያ በሀብት በኑሮ በጌጥ ") ።
ቅለዳ፡ ትረባ ።
ቅሉ፡ ንኡስ አገባብ፡ ስንኳ ("(ማቴ. ፳፭፥ ፳፱)") ።
ቅሉ፡ ያ ቅል፡ የርሱ ቅል።
ቅሉ፡ ግን ። "እሱ እሷ አንተ እኔ ቅሉ" ("(፪ሳሙ. ፲፰፥ ፲፫)") ።
ቅላት (ቂሐት)፡ ቀይነት/ደም መም ሰል ("(ምሳ. ፳፫፥ ፳፱)") ።
ቅላጤ፡ ተጨማሪ ዜማ ከዋናው የተለየ ።
ቅሌ (ኦሮ)፡ ጥንግ ዕሩር ።
ቅሌታም (ሞች)፡ ቀላል ሰው ባለቅ ሌት መንፈሰ ቀላል ።
ቅሌት፡ ያመል የጠባይ መቅለል ("(፪ቆሮ. ፩፥ ፲፯)") ። በግእዝ "ቅለት" ይባላል ። "ነደደ" ብለኸ ንዴትን አስተውል።
ቅሌት—መቅለል—ቀለለ ።
ቅል (ሎች)፡ ሐረግማ ቅጠል በቅጥር ውስጥና በዱር የሚበቅል ("(ዮና. ፬፥ ፮፡ ፱)") ። በትግሪኛ "ቅልዕ" ይባላል ።
ቅል፡ ሞላላ የውሃ መቅጃ አንኮላ ሸክና ዐቦሬ ።
ቅል ባገኝ፡ ቅልን ተስፋ አድርጎ የሚዘምት ሰው ።
ቅል ብቻ፡ ራስ ።
ቅል ዐንገት፡ ቀጪን የቅል ዐንገት የደጋን መንዘሪያ የምትኾን ።
ቅል፡ ክብ እንክብል ቋንጅል መንቀል ። (ተረት)፡ "አሞራውም በረረ፡ ቅሉም ተሰበረ" ።
ቅልምጫ፡ ያፍ ድምፅ በምግብ ጊዜ ።
ቅልሞሽ—ቅልቦሽ—ቀለበ ።
ቅልሳት፡ ጕብጠት ።
ቅልስ፡ የተቀለሰ (ምልስ ቍልፍ ዐንገት ጐዦ ከዘራ ገና ጥንቅሽ ሙጭ ") ።
ቅልስልስ አለ፡ ተቅለሰለሰ ።
ቅልስልስ፡ የተቅለሰለሰ (ደካማ ") ።
ቅልሽልሽ አለው፡ ሽቅብ ሽቅብ አለው፡ በሽ አለው ።
ቅልሽልሽ፡ የተቅለሸለሸ (ጥውልው ") ።
ቅልሽልሽታ፡ የሆድ እውክታ ።
ቅልቅል አለ፡ ቅዥቅዥ አለ፡ ተንቀለ ቀለ ።
ቅልበሳ፡ ዐጠፋ ሽንቀራ ቅነፋ ።
ቅልብ (ቦች)፡ የተቀለበ/የተመገበ/ የበላ ሙክት ገች ድልብ ።
ቅልብ፡ የተያዘ የተጨበጠ ።
ቅልብልብነት፡ ስግብግብነት ።
ቅልብሳት፡ ዕጥፋት ቅንፋት፡ የሱሪ የጥብቆ የበርኖስ የለምድ የዳባ ፍና ጫፍ፡ የዝናር ዳርና ዳር እየተቀለበሰ የተሰፋ ።
ቅልብስ፡ የተቀለበሰ (ቅንፍ ሽንቅር ከንፈር ልብስ ") ።
ቅልብሽ አለው፡ ቅልሽልሽ አለው ።
ቅልብሽ፡ የተመለሰ/የተገለበጠ (ወደ ላይ የወጣ የሆድ ውስጥ ምግብ ") ።
ቅልብጭ አለ፡ ቅልጥፍ አለ ።
ቅልውጥ፡ የማድ ክጀላ ።
ቅልዝ አለ፡ ክችል አለ ።
ቅልዝ፡ የቀለዘ ዕንጨት በጋ ተክረ ምት ያለፈበት
ቅልጠፋ፡ ፍጥነት ክር ባጪር ።
ቅልጣቅልጥ (ቅልጥ አቅልጥ)፡ የቅልጥ ቅልጥ የምት ምት በሰንበር ላይ ሰንበር ያረፈበት ። "የዝንጀሮ ቅልጣቅልጥ" እንዲሉ።
ቅልጣን፡ ምቾት ድሎት ከልክ ያለፈ ሀብት ። መሬት ውሃ ሲያይልበት፡ ሠም ቅባት ሙቀት ሲበዛበት እንዲቀልጥ፡ ቅልጣንም ከባለቤቱ ዐልፎ ለሌላ መትረፉን ያሳያል ("(ዘዳ. ፳፰፥ ፶፬፡ ፶፮፡ ኤር. ፲፫፥ ፳፯)") ።
ቅልጣን—ምቾት ። ቀለጠ (ቀለጠፈ)፡ (ቀለጠ ለጠፈ)፡ ፈጠነ ተከወነ ቶሎ ኾነ ተደረገ ሥራው ነገሩ ።
ቅልጥ አለ፡ ፍስስ አለ፡ ፈጽሞ ሠባ ደመቀ ።
ቅልጥ፡ የቀለጠ የ የፈሰሰ የፈ ረሰ፡ የተመታ ።
ቅልጥልጥ አለ፡ ተቅለጠለጠ ።
ቅልጥልጥ፡ የተቅለጠለጠ ወዛም ።
ቅልጥማም (ሞች)፡ ቅልጥመረዥም ቋቲሮ ሰው አሞራ ።
ቅልጥም (ሞች)፡ ከቋንዣ እስከ ቍርጭምጭሚት ያለ የእግር ክፍል፡ መለልታ አገዳ ።
ቅልጥም ሰባሪ፡ ቅልጥምን ወደ ሰ ማይ አውጥቶ እየለቀቀ አለት ላይ የሚሰብርና ቅባቱን የሚጠጣ አሞራ ።ዠርባው ጥ ቍር ኾኖ ቅላትና ንጣት ያለው ባና መሳይ ነው ።በስተጕያውና በስተጭኑ ነጭ ሱሪ የታ ጠቀ ይመስላል ።
ቅልጥም አለ፡ ስብር አለ፡ ተቀለጠመ ።
ቅልጥም አደረገ፡ ስብር አደረገ፡ ቀለ
ቅልጥም፡ ከብብት እስከ ኵርማ ከክርን እስከ አንባር ያ ያለው ጡንቻ ክንድ ። ለከብትም የፊት እግር እንደዚሁ ይነገራል ።
ቅልጥም፡ የቅልጥም ቅባት
ቅልጥም፡ የተቀለጠመ/የተሰበረ (ስብር ") ።
ቅልጥምጥም አለ፡ ስብርብር አለ፡ ተ ቀለጣጠመ ።
ቅልጥምጥም፡ የተቀለጣጠመ ስብርብር ።
ቅልጥጥ ቅልጥጥ አለ፡ ሽቅብ ሽቅብ ግራና ቀኝ ዝንጀርኛ አየ ።
ቅልጥጥ አለ፡ ግልጥ አለ፡ ተንቀ ለጠጠ ።
ቅልጥፍ፡ የቀለጠፈ/ፈጥኖ የኾነ/የተደ ረገ ።
ቅልጥፍና፡ ቀልጣፋነት ።
ቅልጥፍጥፍ አለ፡ ክውንውን አለ፡ ተ ቀለጣጠፈ ።
ቅልጥፍጥፍ፡ የተቀለጣጠፈ ክውንውን ።
ቅልጥፍጥፍታ፡ ቅልጥፍጥፍ ማለት ።
ቅሏ - ቅሊቱ፡ ያች ቅል ("(ዮና. ፬፥ ፮፡ ፯፡ ፲)") ።
ቅሏ፡ የርሷ ቅል።
ቅመመን፡ የቅመም ዱቄት፡ ን ምእላድ ነው ።
ቅመመን፡ ድብልቅ ውጥንቅጥ ። ፈረንጆች "ኮክቴል" ከሚሉት ጋራ ይሰማማል ።
ቅመማ፡ ስብሰባ ቅልቀላ ድብለቃ ምጠና ።
ቅመማም፡ ቅመም ያለው ባለቅመም ።
ቅመማቅመም፡ የቅመም ቅመም (ብዙ ዐይነት ቅመም ") ።
ቅመም (ሞች)፡ አብሽ ድንብላል ኰረሪማ ዝንጅብል ነጭ አዝሙድ ጥቍር አዝሙድ ሰናፍጭ ፌጦ ነጭ ሽንኵርት ቀይ ሽንኵርት በሶብላ ጐመን ዘር ።
ቅመራ፡ ቈጠራ ምደባ ከፈላ ።
ቅሚያ፡ ንጥቂያ ("(ኤር. ፶፩፥ ፲፫፡ ናሆ. ፪፥ ፲፪፡ ማቴ. ፳፫፥ ፳፭)") ።
ቅማላም (ሞች)፡ ቅማል ያለበት የበዛበት የሚንፋሰስበት ሰው ።
ቅማላም ኾነ፡ ቀመለ ።
ቅማል (ሎች)፡ ከሰው እንፋሎትና ላብ በልብስና በራስ ጠጕር ውስጥ የሚፈጠር ተባይ ነጭና ጥቍር ።
ቅማል ጅራም (ቅማንጅራም)፡ ቅማንጅር የሚታይበት ሰው ባለቅማንጅር ።
ቅማል ጅር (ቅማንጅር)፡ የቅማል ጓዝ፡ የቅንድብና የሽፋል፡ የጢም ቅጫም ።
ቅማሽ፡ ቢጀ ጕርሻ ("(ዮሐ. ፲፫፥ ፳፮)") ።
ቅማት - ቅማያት፡ የቅድም አያት አባትና እናት የሽማት ልጆች ።
ቅማት፡ ፬ኛ አያት—ቀደመ ።
ቅማንት (ከመ አንተ)፡ የነገድ ስም፡ በበጌምድር አውራጃ በከርከር በጭልጋ ያለ ሕዝብ ። "አንድ ቅማንት ዐደን ዐድኖ ከደን ሲወጣ አንድ . . . . አገኘውና መኑ አንተ አለና ቢጠይቀው፡ ከመ አንተ ብሎ ስለመለሰለት በዘመን ብዛት ከመ አንተ በማለት ፈንታ ነገዱ ቅማንት ተባለ" ይላሉ ። "ዐዋጅ የተሻለውን መንገድ ለመያዝ" የሚል መጽሐፍ ተመልከት፡ ዳግመኛም አለቃ ታየ የጻፉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ እይ ።
ቅማንቶች፡ የቅማንት ነገዶች ወገ
ቅማጫም፡ ተቅማጣም ።
ቅማጭ፡ ተቅማጥ ።
ቅምሖ (ቀምሕ ፍሬ)፡ ዕጢ የ ሥጋ ቅንጣት ።
ቅምሖ፡ ለግዳ ለቅዳ በስተውስጥ በጕረሮ ጫፍ ግራና ቀኝ የሚወጣ ዕብጠት ። ዐዋቂ በጊዜው ካልቧጠጠው ምግብና ምራቅ መዋጥ ይከለክላል፡ ዦሮ ግንድን እንደ ጦር ይወጋል፡ እጅግ ባበጠ ጊዜ የገባና የንኰይ ፍሬ ስለሚያክል ቅምሖ ተባለ ።ፈረንጆች "ቶንሲል" ይሉታል ።
ቅምም፡ የተቀመመ (ቅልቅል ድብልቅ ምጥን፡ ቅመም የገባበት ድልኸ ") ።
ቅምምጦሽ፡ የትከሻ ሸክም ፈረቃ ።
ቅምስ አደረገ፡ ልክፍ አደረገ ።
ቅምስ፡ የተቀመሰ ።
ቅምር፡ የተቀመረ የተቈጠረ (ክፍል ምድብ ") ። "ርባ ቅምር" እንዲሉ።
ቅምቀማ፡ ስፌት ዝምዘማ ።
ቅምቅማት (ቶች)፡ ዝምዝማት ("(ዘፀ. ፳፰፥ ፴፪)") ።
ቅምቅም አለ፡ ጥቂት ጥቂት ጣ
ቅምቅም፡ የተቀመቀመ (ዝምዝም ") ።
ቅምቡርስ—ትል፡ ቅንቡርስ ።
ቅምና—ቅል—(ቀመጠ) ። ቅማያት—፬ኛ አያት—ቀደመ ።
ቅምድምድ አለ፡ ተቅመደመደ ።
ቅምጠላ፡ የማጕደል ሥራ፡ ቅንጠሳ ።
ቅምጥ፡ ቂጥ መቀመጫ ። "ራድ ከቅምጥ ይፈነቅላል" አንዲሉ ።
ቅምጥ፡ ዐይናር፡ ሌሊት በንቅልፍ ጊዜ ካይን የሚወጣ እድፍ ።
ቅምጥ፡ ዕጦት ችግር ሥራን ትቶ ከመቀመጥ የሚመጣ ።
ቅምጥ፡ የተቀመጠ ። "ያተር ቅምጥ" እንዲሉ ።ጕልት ሽባ ።
ቅምጥሉ፡ ያ ቅምጥል ።
ቅምጥላ፡ የዕውቀት ቅሬታ (ተረፈ አእምሮ) ።
ቅምጥላው ጠፋ፡ አእምሮው ታጣ በስካር ምክንያት (ኅሊናውን ሳተ) ።
ቅምጥል (ሎች)፡ የተቀማጠለ (ች)፡
ቅምጥል አለ፡ ጕድል እንስ አለ ።
ቅምጥልነት፡ ቅምጥል መኾን፡ ድልድ
ቅምጥልጥል አለ፡ ተዘናፍሎ ተኛ ።
ቅምጥልጥል፡ የተቀመጣጠለ ።
ቅምጥሏ - ቅምጥሊቱ፡ ያች ቅምጥል ("(፩ጢሞ. ፭፥ ፮)") ።
ቅምጦሽ፡ የጨዋታ ስም፡ ልጆች አንዱ ባንዱ ትከሻ ላይ እየተቀመጡ የሚያደርጉት የኳስ ጨዋታ ።
ቅምጫና (ኖች)፡ ቅል ቋንጅል ። መ ንቀልን እይ ።
ቅሞ፡ ሖምጣጣ የቅሞ ፍሬ ተረር ።
ቅሞ፡ የዛፍ ስም፡ ፍሬው የሚቃም አነስተኛ ዕንጨት ።
ቅሰራ፡ ግተራ ።
ቅሳር፡ ሠረዝ ጭረት ።"ኹለቱን ነጥብ ዐቢይ ሠረዝ ንኡስ ሠረዝ የሚያሠኘው ቅሳር ነው" ።
ቅሳር፡ ቈሸሸ !
ቅሥም፡ ሰውነት ።
ቅስም፡ ካ፬ቱ ባሕርያት የተቀመመ ሰው ነት ኹናቴ ። በግእዝ "ቅሳሜ" ይባላል ።
ቅሥም፡ የተቀሠመ (ልቅም ስብስብ አ ውላ ") ።
ቅስስ፡ ቅዝዝ/ፍዝዝ ።
ቅስስ አለ፡ ፍዝዝ አለ ።
ቅስር ቅስር አለ፡ ግትር ግትር አለ ።
ቅስር አለ፡ ግትር አለ ።
ቅስቀሳ፡ ንቅነቃ ብርበራ ፍተሻ ።
ቅስቃሴ (ነሰሕሳሕ)፡ መቀስቀስ ።
ቅስቅስ አለ፡ ንቅንቅ አለ ።
ቅስቅስ፡ የተቀሰቀሰ/የተበረበረ (ንቅንቅ ብርብር ፍትሽ ") ።
ቅስት፡ የተቀሰተ (በበር በድልድይ ውስጥ የተበጀ የግንብ የሳንቃ ደጋን ቅሥፍ ") ።
ቅስና፡ ቄስነት ።
ቅሥፈታም፡ ባለቅሥፈት ።
ቅሥፈት፡ መቅሠፍት/መቀሠፍ (ባፍላ በልጅነት መሞት ") ። በግእዝ ግን ግርፋት ማለት ነው ።
ቅሥፍ፡ የተቀሠፈ (የጐበጠ ቅስት ") ።
ቅረብ፡ ለጥቅ ተጠጋ ።
ቅረብ፡ ንዳ ውሰድ ።
ቅሪላ፡ (ሎች)፡ ከርጥብ፡ የበሬ፡ ቈዳ፡ ጐኑ፡ በስንዝር፡ ልክ፡ ተቀዶ፡ የለፋ፡ ጠፍር፡ በያይነቱ፡ ቅራና፡ መጫኛ፡ ይኾናል ።
ቅሪት፡ የፀነሰች ሴት ደ ፀኗ የቀረ (እርጉዝ ") ።
ቅራሚ፡ የተቃረመ፡ ያጫጅ፡ ቅሬታ።
ቅራሞ፡ ዝኒ፡ ከማሁ ።
ቅራሪ፡ የመጠጥ ስም (ጠላ ባለቀ ጊዜ የሚጠጣ መናኛ መጠጥ ") ።"አንደኛ ኹለተኛ ቅራሪ" እንዲሉ ።
ቅራቅንቦ፡ እንቶ ፈንቶ ምናምን ዕቃ፡ ኵሳንኵስ ሰባራ ሥንጥር ። "ቅላቅንቦ ቢል የቅንቦ ቅል" ማለት ይመስላል ።
ቅራተኛ፡ ባለቅራት ጠባቂ ።
ቅራት፡ ሌሊታዊ ጥበቃ ።
ቅራት፡ ያሞራ ቤት ።
ቅራት፡ ያሞራ ቤት ።—ቀራ ።
ቅራና (ኖች)፡ የቀርቃባ ጠፍር ። በትግሪኛ ግን አንድ ፈርጅ ሸማ ማለት ነው ። "የቅራና ምስጢር እንደ ቀርን (ቀንድ) ኹለት መኾኑን ያሳያል ። ከቈረኘና ከገረኘም ይሰማማል ። ቅሪላን ቀረነተን ተመልከት" ።
ቅራፊ፡ የተቀረፈ (ንጣይ ልጣጭ ") ።
ቅሬ - ቈራ ።
ቅሬ (ቃረ)፡ ዐጣሪ ዘፋኝ አረኾ (የሴት ወሮ በላ ባለጌ ማን ዘራሽ መሸተኛ አቅራሪ ጋለሞታ ሴትኛ ዐዳሪ ሸርሙጣ ነውር ጌጧ ") ።የቅሬ ምስጢር የተቃረች ማለት ነው ።"ወለደ" ብለኽ "ልጅን" እይ ።ቅሬ ለወን ድም ይነገራል።
ቅሬታ፡ ተረፍ ትራፊ ("(ዐብድ. ፩፥ ፲፰ ። ሶፎ. ፪፥ ፲፱)") ።
ቅሬነት፡ ቅሬ መኾን (ዐጣሪነት ጋለሞታነት ") ።
ቅሬዎች፡ ዐጣሮች አረኾዎች ጋለሞ ቶች ።
ቅር (ቍር)፡ የሽንብራ በሽታ የሚ ያደርቀው ዐልፎ ዐልፎ ጭብርር የሚያደርገው አለፍሬ የሚያስቀረው ።
ቅር (የቀረረ ") ።
ቅር ቅር አለው፡ ውል ውል አለው ።
ቅር አለ፡ ትዝ አለ፡ ታሰበ በልብ ተጕላላ ።
ቅር አለው፡ ግር አለው፡ ቸገረው ።
ቅርሚያ፡ ለቀማ፡ ስብሰባ።
ቅርምቻ፡ ትንተና/ክፍያ ።
ቅርምዝ - ቈረኘ፡
ቅርምዝ (ዐረ)፡ ቀይ ግምጃ ("እን ድኪ ጃዊ ") ("(ኢሳ. ፩፥ ፲፰)") ።
ቅርሥ፡ ተቀማጭ ገንዘብ ።—ቅ ርስ ።
ቅርስ፡ ተቀማጭ ገንዘብ፡ ወይም ካባት የወረደ ተካባች ብር ። ባረብኛ "ቅርሽ" ይባላል፡ የብር ክፍልፋይ ታናሽ ገንዘብ መሐልቅ እንደ ማለት ነው ። "ቍሪትን" ተመልከት ። "ግርሽና ቅርሽ" አንድ ስም ነው ። ዳግመኛም ብር በትግሪኛ "ቀርሽ" በጋልኛ "ቀርሺ" ይባላል ።
ቅርር አለ፡ ቀረረ ።
ቅርርት፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅርሻታም፡ ቅርሻት ያለበት የሚታይበት የሚበዛበት (ኹል ጊዜ የሚቀረሽ ልጅ ትፋታም ") ።
ቅርሻት፡ እውከት ትፋት ።
ቅርሽምሽም፡ ስብርብር ።
ቅርሽምሽም አለ፡ ስብርብር አለ፡ ተ ቀረሻሸመ ።
ቅርቀራ፡ ሽጐራ ውርወራ ።
ቅርቃር (ሮች)፡ መዝጊያ እንዳይከፈት በስተውስጥ ኹኖ የሚከለክል ዕንጨት ።
ቅርቃር፡ ሳንቃን ከሳንቃ የሚያገናኝ መስቀልኛ ውሻል (ርስ በርሱ የተሳካ ") ።
ቅርቅምቢጥ፡ ሰቡልጋ ውስጥ ያለ ቀበሌ ።
ቅርቅምቢጥ፡ ቅምምጦሽ፡ ቅልጥፍናን ያሳያል ።
ቅርቅር፡ የተቀረቀረ (ሽጕር ") ።
ቅርቅብ፡ የተቀረቀበ (ውድን እርት ") ።
ቅርቅፍ፡ የተቀረቀፈ (የግንድ ድቃቂ ") ።
ቅርቅፍት፡ ደንጊያ የበዛበት ሻካራ መንገድ ።
ቅርቢያ፡ ቀረቤታ (ቅርብነት ጎረቤትነት ልነት ") ።
ቅርብ (ቦች - ቅሩብ)፡ የቀረበ (ሩቅ ያይዶለ ")፡ የተጠጋ (በጐን ባጠገብ ያለ ") ። (ተረት)፡ "ሳይርቅ በቅርቡ ሳይደርቅ በርጥቡ" ። "ከሩቅ ዘመድ የቅርብ ጎረቤት" ።
ቅርብ ለቅርብ፡ ጐን ለጐን አጠ ገብ ላጠገብ ።
ቅርብ ዘመድ፡ ኹለት ቤት፡ ሦስት ቤት ።
ቅርታ፡ ትዝታ ችግር ዐሳብ አለመደሰት፡ ዐዘን ።"አቶ እከሌ በኔ ነገር ቅርታ ገብቶታል" ።
ቅርት፡ ሙትት ዝርግት ዟ ሰተት ።
ቅርት አለ፡ ድንገት ትንፋሹ ተቈረጠ፡ ድብን አለ ።
ቅርናታም፡ ባለቅርናት ("ግማታም አ ውራ ፍየል ") ።
ቅርናት፡ የብብት የተቃጠለ ቈዳና ቍ ረንጮ ክፉ ሽታ ግማት ።
ቅርን፡ ቀረመት (የሥጋ ክፍያ፡ በብዙ ወገን ቈርጠው መድበው የሚካፈሉት ") ።
ቅርንት፡ መቀርናት ።
ቅርንት አለ፡ ግምት አለ ።
ቅርንጥሳም፡ ቅርንጥስ ያለው (ባለቅር ንጥስ ") ።
ቅርንጥስ፡ ጨርቅ ጭርንቍስ የተጠቃቀመ (ዛተሎ ዘባተሎ ንጥስ ") ።
ቅርንጫፍ (ቀርነ - ጫፍ - ጫፈ - ቀርን)፡ እሾኸ (የዛፍ ፵ፍ ውልብልቢት ") ።"ቅርን" ከ "ቀርን" "ጫፍ" ከ "ጨፈጨፈ" መጥቶ አንድ ስም ኹኗል ።
ቅርንፉድ (ዶች)፡ የቅመም ስም (ከባሕር የሚመጣ ቅመም ") ። ባረብኛ "ቅርንፉል" ይባላል ።
ቅርንፉድ፡ ታናሽ የጠመንዣ መዘ ውር ።
ቅርደት፡ ያገር ስም ።
ቅርደዳ፡ ቈረጣ ገመሳ ።
ቅርድ (ዐረ ቀርድ)፡ ዝንጀሮ እን ዳሞድ ።
ቅርድ፡ የማዥራት ግድ አግዳሚ ሸ ለቆ ሠርጓዳው ጐድጓዳው ።
ቅርድድ፡ የተቀረደደ/የተቈረጠ ።
ቅርጠ ቀላል፡ ቀጪን ሰው (ቀትረ ቀላል ") ።
ቅርጠ ቢስ፡ ቁመናው የማያምር ሰው (ቅጠ መጥፎ ") ።
ቅርጠ የለሽ፡ ቅጥ የለሽ መልከ ቢስ ።
ቅርጠፋ፡ ቈረጣ ።
ቅርጣሽ (ቈረመደ)፡
ቅርጣሽ፡ የመብራት ቍራጭ (ኵስታሪ ") ።
ቅርጣሽ፣ኵስታሪ ቀረጠ።
ቅርጣፊ፡ የጌሾ/የሰንበሌጥ ድቃቂ ።
ቅርጥ፡ ቅጥ አካላዊ ሥራ መልክ ቁመና ኹኔታ ።
ቅርጥ፡ የተቀረጠ/የሾለ ። ካህናት ግን "ቅርጽ" ይላሉ ።
ቅርጥፋት፡ ቅርጠፋ/መቀርጠፍ/ክርክ ማት ።
ቅርጥፍ አለ፡ ተቀረጠፈ ።
ቅርጥፍ፡ የተቀረጠፈ ።
ቅርጫት (ቶች)፡ ከመቃ ከቀርክሓ ከክትክታ ከቀጨሞ ከሐረግ የተበጀ ዕቃ (ማንኛውንም ነገር መያዣና ማስቀመጫ ሰብል መሰብሰቢያ እኸል መስፈሪያ ") ። የንጨቱን መቀረጽና ሹለት ያሳያል ።
ቅርጫትከንጨት፡ የተበጀ፡ ዕቃ፡ ቀረጠ ።
ቅርጭም፡ የተቀራጨመ (ጥርቅም ") ።ቅርጫሚ፡ ጥርቃሚ ዞ መ ።
ቅርጭም፡ የተቀራጨመ (ጥርቅም ") ።ቅርጫሚ፡ ጥርቃሚ ዞ መ ።
ቅርጭጭ አደረገ፡ ንክስ ውግት አደረገ፡ ቀረጪዉ ።
ቅርጭጭ፡ የተቀረጪ ንክስ ።
ቅርጭፍት፡ ዕሩር የቋር ቍራጭ ።
ቅርጽ (ጾች)፡ የተቀረጸ (ቅርጥ ንጥ ፍ ልፍል ንቅስ ") ። "ደንጊያ ዕንጨት ብረት መዳብ ንሓስ ወርቅ ብር ማንኛውም ማዕድን" ።
ቅርጽ፡ የሰው መልክ ምስል፡ ጣዖት ።
ቅርፊት (ቅርፍት)፡ ልጥ ያለበትና የሌለበት የንጨት ልብስ፡ ተቀርፎ የወደቀ አለት ምርጊት ። "የዳቦ የሮማን ቅርፊት፡ የቍስል ቅርፊት" እንዲሉ ።
ቅርፋ (ቀረፈፈ)፡
ቅርፋ፡ ድንብላል ።
ቅርፍርፍ አለ፡ ተቅረፈረፈ ።
ቅርፍርፍ፡ የተቅረፈረፈ (ሥንጥቅጥቅ ፍርክርክ ") ።
ቅርፍርፍታ፡ ቅርፍርፍ ማለት ።
ቅርፍርፍነት፡ ፍርክርክነት ።
ቅርፎ፡ ያንኮላ የቅምጫና ጫፍ ቍራጭ ።
ቅሽምድ አለ፡ ስብር አለ ።
ቅሽር፡ የተቀሸረ (አለባበስ አሳማሪ ክሽን ንፍ ") ።
ቅቀላ፡ የመቀቀል ሥራ ።
ቅቀራ፡ የመቀቀር ሥራ ።
ቅቅላት፡ የቅቅል ኹኔታ ።
ቅቅል ዋጭ፡ ቅቅልን የሚወድ የሚውጥ ።
ቅቅል፡ የተቀቀለ/የበሰለ ሥጋ ዞ ።
ቅቅታም (ሞች)፡ ሥሥታም ንፉግ ጩቅ ቢስ እጁን ቢሉት የማይወድቀው ።
ቅበ ቢስ፡ ክቾ ነገረ ደረቅ ለዛ ቢስ ዕድለ ቢስ ።
ቅበላ (ቀበላ)፡ ያርባ ሑዳዴ ዋዜማ እሑድ ቀን የጦም መቀበያ ። የሐምሌ ሠላሳኛ ቀንም የፍልሰታ ጦም ቅበላ ይባላል ።
ቅቡጭ (ቅቡጽ)፡ ያነሰ የጐደለ ።
ቅቡጭ አለ፡ እንስ ጕድል አለ ። "ይበቃል ሲሉት በድንገት ዐለቀ ጠፋ ታጣ" ።
ቅባቅዱስ (ቅብዕ ቅዱስ)፡ ሜሮን (የተቀደሰ ሽቱ ") ። ሕፃን የክርስትናው ለት ታቦት በመባረኪያው ቀን የሚቀባው፡ ባገራችን የወይራ ፍልጥ ዘይት ነው ።
ቅባታም፡ ቅባት የሚወጣው (ባለቅባት ተልባ ኑግ ሰሊጥ ሱፍ ጕሎ ባር ቅል፡ የመሰለው ኹሉ ") ።
ቅባት፡
ቅባት (ቅብዐት)፡ ቅቤ ' ዘይት ሞራ ቅልጥም ላት የዶሮ ሥብ ጋዝ (የመሰለው ኹሉ ") ።
ቅባት፡ ዕድል ተሰጦ ሀብት ጸጋ ።
ቅባት፡ የሃይማኖት ስም ። "ባጤ ሲፋል ዘመን ዕውር ዘኢየሱስ የሚባል ሰው ያወጣው ሃይማኖት" ። "ቤተ ኤዎስጣቴዎስ" "የቤተ ተክለ ሃይማኖት ተቃራኒ" ። "የቅባት ባህል" ባጭር ቃል ይህ ነው ። "ቃል ሥጋ ለብሶ ሰው በኾነ ጊዜ (ዜገ) የባሕርይ ክብ ሩን ዐጣ ለቀቀ፡ ሲቀባ (መንፈስ ቅዱስን ሲቀበል) ግን ተገብሮ ተፈጥሮ ጠፍቶለት በሰውነቱም ባምላክነቱም አንድ ወገን የባሕርይ አምላክ ኾነ" ይላሉ ("(ኪ. ወ. ክ.)") ።
ቅባቶች፡ በቅባት ሃይማኖት የሚያምኑ ። "ለዘሐመ ልብ ቃለ ሃይማኖት መድኀኒቱ አኮኑ ቅባት" የሚሉ ።
ቅባኑግ፡ ከኑግ የሚወጣ ቅባት ዘይት (የጦም ወጥ የሚሠራበት ") ። አወጣጡም ለጥልጦ በማፍላትና በማሸት በፀሓይ ሙቀት ነው ። በግእዝ "ቅብዐ ንሒጕ" ይባላል ።
ቅባጥርሴ፡ ትርክም ምናምን ነገር ።
ቅቤ መዛኝ፡ ቅቤ እየመዘነ የሚሼጥ ። "ቅቤ መዛኝ ድርቅ ያወራል" እንዲሉ ።
ቅቤ ዐንጓች፡ ዝኒ ከማሁ ። "ለቅቤ ቅቤው ወጣ" ("(ትግ. ጸዐየ)") ። ሽፍታ ጠባሽ ኾነ ሰፈፈ ።
ቅቤ አድርቅ፡ ውርጭ ብርድ ።
ቅቤ ጠባሽ፡ እወደድ ባይ አከንፋሽ ።
ቅቤያም፡ ባለቅቤ (ብዙ ቅቤ የሚወጣት ላም ") ።
ቅብ (ቅቡዕ)፡ የተቀባ የተለቀለቀ የታደለ የተኰላ ። "ወርቅ ቅብ" እንዲሉ ። ተመልሰኸ "ቅብን" ተመልከት ።
ቅብ (ቅብዕ)፡ ቅቤ (የዘይት ዐይነት ") ።
ቅብ፡ የተቀባ ተቀባ ።
ቅብል፡ የተቀበሉት ።
ቅብር (ቅቡር)፡ የተቀበረ/የተደፈነ ።
ቅብር አለ፡ ድፍን አለ (ተቀበረ ") ።
ቅብር አደረገ፡ ድፍን አደረገ (ቀበረ ") ።
ቅብርር - ቀብራራ ።
ቅብርር አለ፡ ተንቀባረረ ።
ቅብቀባ፡ ዕየማ ቅጥቀጣ ችከላ ።
ቅብቃብ (ቦች)፡ ደረቅ ዕንጨት ችካል ካስማ (የከብት የመሠረት ገመድ ጠፍር ማሰሪያ የድንኳን አውታር መሳቢያ መወጠሪያ ") ("(ዘኍ. ፮፥ ፴፪)") ።
ቅብቅብ (ቦች)፡ የተቀበቀበ (የታረሰ ለስላሳ ዕርሻ ") ። (ተረት)፡ "አፍና ቅብቅብ ኹል ጊዜ እያበላም" ።
ቅብቅብ፡ የተተከለ/የተቸከለ (እመሬት የገባ ቅብቃብ ችክ ") ።
ቅብቅቦ፡ በጨው የታጀለ የማሽላ እሸት በድብዳብ የተሸፈነ ።
ቅብትት አለ፡ ንፍት ውጥር አለ ።
ቅብትት አደረገ፡ እጅግ በጣም ቀበ
ቅብትት፡ የተቀበተተ/የተነፋ/የተወጠረ (ንፍ ውጥር ንርት ") ።
ቅብንን አለ፡ ንፍት ውጥር አለ (ተቀ በነነ ") ።
ቅብንን፡ የተቀበነነ (ንፍ ውጥር ሆድ ") ።
ቅብዐ መንግሥት፡ የመንግሥት ቅ ባት (ንጉሥና ንግሥት ተቀብተው የሚነግሡበት ") ።
ቅብዐ ክህነት፡ የክህነት ቅባት (ካህ ንና ጳጳስ ተቀብተው የሚሾሙበት ዘይት ") ።
ቅብዝብዝ አለ፡ ተቅበዘበዘ ("(ኢዮ. ፲፭፥ ") ።
ቅብዝብዝታ፡ ቅብዝብዝ ማለት ብክ ነት ።
ቅብዥርዥር፡ ውዥብርብር ።
ቅብጠት (ቅብጸት)፡ ዝላይ ጨዋታ ልፊያ ድሪያ (ከጨዋ ደንብ የተለየ ሥራ ") ።
ቅብጢ - ቅብጣዊ፡ የቅብጥ (ግብጻዊ የግብጽ ሰው ") ።
ቅብጢ (ቅብጣዊ)፡ የቅብጥ ቋንቋ (ጥንታዊ የምስር ልሳን ") ። ፊደሉ ከጽርእ ፊደል አንድነት ያለው ። "ቅብጥ" ከጽርእ የሚ ለየው ፯ ፊደል ሲጨምር ነው ። ሌላም "ሄሮግሊፍ" የሚባል የተቀደሰ ሥዕላዊ ፊደል በግብጽ ነበረ ።
ቅብጢ፡ ቀበጥ ቀበጢና (ሴት ") ። ዘሩ ቀበጠ ነው።
ቅብጥ (ቀቢጽ)፡ መቅበጥ ።
ቅብጥ አለ፡ ፍንድቅ አለ (ፈጽሞ ") ።
ቅብጥ፡ ግብጽ ምስር ። "ግ ለቅ ጽ ለጥ መለወጡን አስተውል" ። ኹለቱም በግእዝ መጽሐፍ ይገኛሉ። "ግብጥን" እይ ።
ቅብጥርጥሬ፡ የቅብጥርጥር ዐይነት ።
ቅብጥርጥር፡ ልፍለፋ ዝብዝብ ሰበብ ።
ቅብጥና፡ ቀበጥነት/ፍንደቃ ።
ቅብጥጥ አለ፡ ቅብትት አለ ።
ቅብጥጥ፡ የተቀበጠጠ ።
ቅትር (ቅቱር)፡ የተቀተረ/የተቀረቀረ ("ንፍ ውጥር ") ።
ቅትር አለ፡ ውጥር አለ ።
ቅትርት (ቶች)፡ በሞፈርና በድግር ውስጥ የተቀረቀረች ቅርቃር ("የመንኰራኵር ብረት ወይም ዕንጨት መወጠሪያ መሳይ ") ("(፩ነገ. ፯፥ ፴፫)") ።
ቅትት፡ መቃተት ።
ቅትት ቅትት አለ፡ ትንፍስ ትንፍስ አለ ።"ቃታን" እይ ።
ቅነሳ፡ የመቀነስ ሥራ ።
ቅነፋ፡ ዐጠፋ ምለሳ ሽብለላ ።
ቅናሽ፡ ከጠላ የተቀነሰ ዐሠር ውሃ ሰለልታ ።
ቅናተ ኤልያስ፡ የኤልያስ መታጠ ቀያ ።
ቅናተ ዮሐንስ፡ የዮሐንስ መጥምቅ መታጠቂያ ።
ቅናተኛ፡ ቀናተኛ (ቅናት ያደረበት ") ።
ቅናት (ቅንአት)፡ ክፉ ምኞት ም ቀኝነት፡ ሌላው ሠርቶ እንዳይጠቀምና እንዳይመሰገን የመቃወም ሐሳብ ("(ሮሜ. ፲፫፥ ፲፫)") ።
ቅናት፡ መታጠቂያ ።
ቅናት፡ መነኵሴ ባሕታዊ ወገቡን የሚጠልፍበት ዐንገቱን የሚያገባበት በደረት በኩል መስቀልኛነት ያለው ሰንሰለት ጠፍር ጌታችን የታሰረበት ገመድ ምሳሌ ።
ቅናት፡ ምቀኝነት ። ቀና ።
ቅናት፡ በኮርቻ መካከል በቀኝ በኩል የተሰፋ ጠፍር ነት ወይም ባሕር ዐረብ ።
ቅናት፡ ትጥቅ ("(ኢዮ. ፳፪፥ ፲፰፡ ፳፩)") ።
ቅናት አደረገ፡ አበከረ ።
ቅናት፡ የመነኵሴ መታጠቂያ ከተንቤን ከባሕር ዐረብ የተበጀ ። (ቅናትና ቅንአት በግእዝ ልዩዎች ሲኾኑ ባማርኛ ይተባበራሉ።) (ግጥም)፡ "ባፋ በጐራዴ ትደነቃላችኹ፡ ወገብ ቈርጦ እሚጥል ቅናት ሳለላችኹ" ።
ቅናት፡ የዜማ ምልክት ።
ቅናዋት፡ ችንካሮች ምስማሮች ።
ቅናዋት፡ የዜማ መዝሙር መስቀል ነክ ሰው ሲሞትና ቅዳሜ ቀን የሚባል ።
ቅናጅ፡ የባሪያ ስም፡ የፍናጅ ልጅ ፫ኛ ።
ቅናጥ፡ ጐሣ ደሳ የዘላን ጐዦ ልብስ ።
ቅኔ (ዎች)፡ የድርሰት ስም፡ ክፍሉና ስሙ ፲፫ የኾነ የግእዝ ግጥም ሲሰ ሙት ደስ የሚያሠኝ እጅግ የሚጥም፡ ኹል ጊዜ ዐዲስ ("(መዝ. ፺፭፥ ፪)") ። "መጽሐፈ ቅኔ" ተመልከት ።ዘርፍና ተሳቢ ኾኖ ሲነገር ።
ቅኔ ማሕሌት (ማሕሌተ ቅኔ)፡ በቤተ ክሲያን ውስጥ ያለ ምዕራባዊ ክፍል፡ ደብተሮች ማሕሌት የሚቆሙበት ቅኔ የሚቀኙበት የቅኔ ወረብ ግጥም ዘፈን (ምስ ጋና) የሚያሰሙበት ስፍራ ። ቅኔ የማሕሌት ዘርፍ መኾኑን አስተውል ። ቅኔ እንደ ግእዙ መገዛት ተብሎ ቢተረጐም፡ ካህናት ለፈጣሪ በማሕሌት የሚገዙበት ያሠኛል ።
ቅኔ ሰጠ፡ ተቀኘ አበረከተ ።
ቅኔ ቈንቋኔ፡ የተማሪን ሰውነት እንደ ቅንቅን እንደ ነቀዝ የሚጐዳ ማለት ነው ። "ቅኔ ቈንቋኔን ድጓ ዶግዷጌን አያምጣብን" እያሉ ይጸልዩና ያሳርጉ ነበር ይባላል የጥንት የጕራጌ ወይም የአገው ቄሶች ። (ያማርኛ ቅኔ)፡ ኅብርነት ያለው ያማርኛ ስንኝ ወይም ግጥም ። "ኹለተኛውን ቈጠረ" እይ ።
ቅኔ ቈጠረ፡ ዐሰበ አዘጋጀ ።
ቅኔ ቤት (ቤተ ቅኔ)፡ የቅኔ ት ምርት ቤት ።
ቅኔ ነጋሪ፡ ቅኔ አስተማሪ ።
ቅኔ ዐዋቂ፡ ሲቀኝ ይበል ወሰው መልካም የሚያሠኝ ሊቅ ቅኔ የሚያውቅ ።
ቅኔ ዘረፈ፡ ሳይቈጥር ተቀኘ ።
ቅን (ኖች) (ቅኑእ - ቅኑይ - ርቱዕ)፡ የቀና/የተገዛ (ታዛዥ ፈቃደኛ ገር ትሑት ደግ ሰው ") ("(ዘዳ. ፳፭፥ ፩፡ ምሳ. ፪፥ ፰፡ ፯)") ።
ቅንሳት፡ ጕድለት ሕጸጽ ።
ቅንስ፡ ዝኒ ከማሁ (ከላዩ ተነሥቶለት የጐደለ ጐደሎ ") ።
ቅንቀና፡ ምርመራ ፍተሻ ቅኚት ሙሾ ።
ቅንቅናም (ሞች)፡ ሥሥታም ንፉግ ።
ቅንቅን (ኖች - ቍንቍኔ)፡ የተን ቀሳቃሽ ስም (ከጤፍ የሚያንስ የዶሮና ያልጋ ተባይ ") ።
ቅንቅን፡ ሥሥት ንፍገት ።
ቅንቅን፡ በገላ ላይ የሚፈስ ረቂቅ ዕ ከክ ። "ክሽክሽትን" እይ ።
ቅንቅን፡ ነቀዝ ("(ምሳ. ፲፪፥ ፬)") ።
ቅንቡርስ (ሶች)፡ የትል ስም፡ ርጥበት ባለው ጕድፍ ውስጥ የሚገኝ ነጭ ትል ። ንን ጣልቃ ስን ምእላድ አድርጎ (ቅቡር) የተቀበረ ተብሎ ይተረጐማል ።
ቅንብር አለ፡ ቀነበረ ።
ቅንብርብር አለ፡ ተቀነባበረ ።
ቅንብርብር፡ የተቀነባበረ (ክውንውን ") ።
ቅንብቢት፡ ክብ ተራራ ያለበት አገር ስም፡ በቡልጋ አጠገብ ይገኛል ። "ቅንብ ቢት የተቀነበበች" ማለት ነው ።
ቅንብብ፡ የተቀነበበ የተከበበ የሕፃን ርግብግቢት ጠጕር ።
ቅንብቻ (ቾች)፡ የተረሳና ትርፍ ዕቃ ማስቀመጫ ማኖሪያ፡ ከቈዳ የተሰፋ መናኛ ኰ ረጆ፡ አፈ ክፍት ስፌት ።
ቅንብቻ ሆድ፡ ሆደ ጕስር ሰው ።
ቅንቦ (ዎች)፡ ወተታም የቈላ የ በረሓ ዕንጨት ። የፍሬው እንቡጥ ቅል ያካክላል፡ በውስጡም ነጭ ሐር የሚመስል ባዘቶ ይገኝበታል ።ኹለተኛ ስሙ ጦቢያ ይባላል ። ወተቱም እውሃ ውስጥ ጠብ አድርጎ ሲቀምሱት ለመጋኛ መድኀኒት ይኾናል፡ ቅንቦ ማለት ቀልጣማነቱን ያሳያል ።
ቅንት፡ "እንደ ገበሬ ጥምድ እንደ በሬ" እንዲሉ ።
ቅንት (ቅኑት)፡ የቀነተ የታጠቀ ።
ቅንነት (ርትዐት)፡ ቅን መኾን፡ ፈቃደኛነት ታዛዥነት ትሕትና ("(፩ዜና. ፳፱፥ ፲፯)") ።
ቅንዘፋ፡ ምልመላ ።
ቅንዝር - ምንዝር፡ ሴሰን ከልክ ያለፈ ዝ ሙት ።
ቅንዝርና - ሽርሙጥና - ምንዝርና ። ቅንዝረኛ (ኞች)፡ ሴሰኛ አመንዝራ ወንድ ወይም ሴት ።
ቅንዝፍ ቅንዝፍ አለ፡ ፍስስ ፍስስ አለ እንባው ።
ቅንዝፍ አለ፡ ፍስስ አለ ።
ቅንዝፍ፡ ዝኒ ከማሁ (የታረደ የፈሰሰ ") ።
ቅንደላ፡ ብጥታት ቈረጣ ።
ቅንደባ፡ ምት ።
ቅንድብ (ቦች)፡ ነፋስና ውሃ ጪስ የማያስገባ ያይን መክደኛ መሸፈኛ ቈርበቱ ቈዳው በላይ በታች ያለው ። በግእዝ "ቅርንብ" ይባላል ("(መዝ. ፲፩፥ ፬፡ ፻፴፩፥ ፬)") ። "ቅንድቤ ርግብ ርግብ ይላል" እንዲል ባላገር ።
ቅንድብ፡ የተቀነደበ የተመታ ።
ቅንጁ፡ የተቀናጀ (ሌላ ኹለተኛ በሬ ") ። "ቀንጃ ከቀንጃ ጋራ" ።
ቅንጠሳ - ቅንጠባ - ብጠሳ ።
ቅንጠባ፡ ቈረጣ ብጠሳ ቅንጠሳ ።
ቅንጡ (ዎች)፡ የተቀናጣ የጠገበ (ቅም ጥል ") ።
ቅንጣር (ዐረ)፡ የሚዛን ስም፡ ግንጣር መቶ ነጥር አንድ ቅንጣር ይኾናል ("(ዘፀ. ፳፭፥ ፴፱ ። ፩ነገ. ፲፥ ፲)") ። በግእዝ "መክሊት" ይባላል ። ፈረንጆች ነጥርን ኪሎ፡ ቅንጣርን ኲንታል ይሉታል ።
ቅንጣሽ - ቅንጣቢ - ቍራጭ - ብጣሽ ።
ቅንጣት (ቶች)፡ አንድ ፍሬ ("(ማቴ. ፲፫፥ ፴፩)") ።
ቅንጣት፡ አንድ ፍሬ ።
ቅንጥ፡ ድሪያ ልፊያ ።
ቅንጦተኛ፡ ጥጋበኛ እብሪተኛ ።
ቅንጦት፡ ጥጋብ እብሪት ቅምጥልነት ።
ቅንጭር አለ፡ ቀነጨረ ።
ቅንፋት፡ ዕጥፋት ቅልብሳት ።
ቅንፍ፡ የፊደል የቃል ማጠሪያ መክ በቢያ ("()") ።
ቅኝት፡ የበገና ዥማት መጥበቅ መ ላላት መቃናት መሰማማት ።"
ቅዘን፡ ተቅማጥ ሻታ ።
ቅዘን፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ።
ቅዛዛ - ቅዛዝ፡ መስተዋት ።
ቅዝምዝም፡ የተቅዘመዘመ (ምዝግዝግ እንዝግዝግ ውዝግዝግ ") ። ባላገር ግን "ቅዝምዝም" በማለት ፈንታ "ቅምዝምዝ" ይላል ።
ቅዝቃዜ፡ ብርድ ።
ቅዝታ፡ ቅርታ ታናሽ ሕጸጽ ።
ቅዝዝ አለው፡ ቅፍፍ አለው ።
ቅዝፊያ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅዠታም (ሞች)፡ የቃዠ/የሚቃዥ (ባለቅዠት ራሰ ቢስ ") ።
ቅዠት፡ የሕልም ጩኸት ከንቱ እ
ቅየማ - ቅያሜ፡ ኵርፊያ ።
ቅየሳ - ቅይሳት፡ የመቀየስ ሥራ፲ ብ ገራ ምጠና ።
ቅየራ - ቅያሬ - ቅይራት፡ ልወጣ ውላጤ ።
ቅየዳ፡ ምከታ እሰራ ስከላ ቀይድ፡ (ትግ. ቀይዲ)፡ ስካላ ጋዲ ።
ቅየጣ፡ ቅልቀላ ድብለቃ ዝነቃ ።
ቅያስ፡ ልክ መጠን ንድፍ ቢጋር
ቅይም አለ፡ ተቀየመ ።
ቅይም፡ የተቀየመ ።
ቅይስ፡ የተቀየሰ ቦታ መንገድ መሬት ።
ቅይር፡ የተቀየረ/የተዛወረ (ልውጥ ") ።
ቅይዳት፡ መከታ ግርዶ፡ ሰካላ እስራት ።
ቅይድ፡ የተቀየደ የተከፈለ የተመከተ፡ ስክል አፈ እስር ድዳ ።
ቅይጥ (ጦች)፡ የተቀየጠ (ዝንቅ ቅል ቅል ድብልቅ ውጥንቅጥ የወፍጮ የልመና እኸል፡ ዲቃላ ") ።
ቅደም ተከተል፡ ፊትና ኋላ ኹን ።
ቅደም፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (ኺድ ዕለፍ ") ።
ቅደሳ፡ የመባረክ የማመስገን ሥራ ።
ቅደቅ፡
ቅዱሰ ቅዱሳን፡ የቅዱሳን ቅዱስ፡ የካህናት አበል ("(ዘሌ. ፪፥ ፲)") ። ከዚህም በቀር ቅዱስ ከስም አስቀድሞ እየገባ በቅጽልነት ሲነገር፡ ቅዱስ ገብርኤል፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ፡ ቅዱስ ዮሐንስ፡ ቅዱስ ሚካኤል፡ ቅዱስ ጳውሎስ፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ይላል ።
ቅዱሳት፡ ንጹሓት ቡሩካት ሴቶች ።
ቅዱሳት አንስት፡ ጌታችን በዚህ ዓ ለም ሳለ እሱን የተከተሉና በገንዘባቸው ያገለገሉት ፴ ሴቶች ።
ቅዱሳን አማልክት፡ ሥላሴ ("(ዳን. ፫፥
ቅዱሳን፡ የተቀደሱ ንጹሓን ቡሩካን መላእክት ጻድቃን ።
ቅዱስ መጽሐፍ፡ ብሉይና ሐዲስ ኪዳን ። "መጽሐፍ ቅዱስ" ቢል ስሕተት ነው ።
ቅዱስ፡ በቁሙ ልዩ፡ የተቀደሰ የተባ ረከ የነጻ የበቃ፡ ቡሩክ ንጹሕ ምስጉን ።
ቅዱስ ባለጌ፡ የተለየ ልዩ ባለጌ ።
ቅዱስ፡ ከላይ ጥርስ የሌለው የሚያመሰኳ ጥፍረ ሥንጥቅ የቤትና የዱር እንስሳ ሥጋው የሚበላ ።
ቅዱስ፡ የርኩስ ተቃራኒ ።
ቅዱስ፡ የኪዳን መዠመሪያ ሳይደወል ቅዱስ እንዲሉ።
ቅዱስጌ (ጌቅዱስ)፡ በቡልጋ አውራጃ ያለ አገር፡ የተቀደሰ ምድር፡ ወይም አንድ ቅዱስ የኖረበት የጸለየበት የሰበከበት የቅዱስ አገር ምድር ማለት ነው፡ ነገር ግን ምድር የምትነገረው በሴት አንቀጽ መኾኑን አስተውል ።
ቅዳሜ (ቀዳም)፡ የሰባተኛ ቀን ስም፡ ሰባተኛው ቀን በዕረፍትነት ከእሑድ ስለ ቀደመ ቅዳሜ ተባለ እንጂ፡ ቅዳሜ መባል የሚገባው ለእሑድ ነበር ።
ቅዳሜ ሹር፡ የስቅለት ማግስት የሚውለው ቅዳሜ ወፍጮ ስለሚፈጭበትና ሌ ላም ለፋሲካ የሚኾን ሥራ ስለሚሠራበት ቅዳሜ ሹር ("የተሻረ ቅዳሜ") ተባለ ። ውስጠ ምስጢሩ ግን ክርስቲያኖች በዘመነ ሐዲስ በቅዳሜ ፈንታ እሑድን ማክበራቸውን ያሳያል ። ይኸውም የተዠመረው በታላቁ ቈስጠን ጢኖስ ዘመን ነው ።
ቅዳሴ (ጥደ)መቀደስመቀደስ፡ ቅ ደሳ ምስጋና ።
ቅዳሴ ሰማ፡ አደመጠ ("(አስቀደሰ)") ።
ቅዳሴ ቤት፡ የቤት ቅደሳ ምረቃ፡ ኅዳር ፯ ቀን የጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው ። መስከረም ፲፯ ቀን የመስቀል ቅዳሴ ቤቱ ይከበራል ።
ቅዳሴ ታጐለ፡ ሳይቀደስ ቀረ ተዳፈነ ።
ቅዳሴ፡ የመጽሐፍ ስም፡ በንባብና በዜማ የሚጸለይ የቍርባን ጸሎት፡ የቂሳርያው ባስልዮስና ሌሎችም ጳጳሳት ያዘጋጁት ድርሰት ።
ቅዳሴ፡ ገባ፡ ዠመረ ወጠነ ቅዳሴን ።
ቅዳሴ፡ ጠበል (ማየ መቍረርት ቅዳሴ ውጭ የሚጠጣ የቅዳሴ፡ ጠበል ") ።
ቅዳዴ፡ የብጫ ጣቃ ቅዳጅ ወታደሮች በራሳቸው ላይ የሚያስሩት የሚቀዳጁት ። "አቡቅዳዴ" እንዲሉ።
ቅዳዶቴ፡ የኔ ሸማ ቅዳጅ ።
ቅዳዶት፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅዳጅ (ጆች)፡ የሸማ የበርኖስ የደበሎ ሥንጣቂ ትልታይ ። "ዐዋጅ ዐዋጅ የደበሎ ቅዳጅ" እንዲሉ።
ቅዴታ፡ ያዢር ዕዳ (ባላገር እያዋጣ ለሹም የሚከፍለው ፈሰሴ ") ።
ቅድ፡ ሸፋሽፍት ። "ያይን ቅድ" እንዲሉ።
ቅድ፡ በከፊል የተጻፈ ። "ቅድ ድጓ ቅድ - ወንጌል" እንዲሉ።
ቅድ አፍ፡ ወሬኛ (እንዳገኘ የሚናገር ") ።
ቅድ፡ የተቀደደ ። ቀደደ ።
ቅድ፡ የተቀደደ/የተሸረከተ (ሽርክት ") ።
ቅድሙን - ቅድሙኑ፡ ፊቱን/ፊቱኑ ።
ቅድሚያ (ቅድመት - ቅድምና)፡ ዥመራ ፍለማ ።
ቅድም አያት፡ የወንድና የሴት አያት አባትና እናት ("እሚታ") ።
ቅድም፡ ከጥቂት ሰዓት ካኹን በፊት "አቶ እከሌ ቅድም መጥቶ ኼደ" ።
ቅድሳት፡ ዝኒ ከማሁ (ጸጋ ክብር ቍርባን ") ። "ንዋይን" ተመልከት ።
ቅድስተ ቅዱሳን፡ ከቅዱሳን ይልቅ የተቀደሰች (ከከበሩ የከበረች መቅደሰ ኦሪት ") ።
ቅድስት ፳ው ክንድ፡ ቅዱሳን የተባሉት እንደ ቅድስት ያሉት ፵ው ክንድና እንደ ቅኔ ማሕሌት ናቸው ። በግእዛዊት ቤተ ክርስ ቲያን ግንቡ (ግድግዳው) የ፫ነት፡ ጣራው የአ፩ነት ምሳሌ ነው ።
ቅድስት ሥላሴ፡ የተቀደሰች ሦስትነት ።
ቅድስት፡ የቤተ ክሲያን ኹለተኛ ክፍል ።
ቅድስት፡ የተቀደሰች የተባረከች (ንጽሕት ") ። "ቅድስት ሐና፡ ቅድስት ማርያም፡ ቅድስት አርሲማ" እንዲሉ።
ቅድስት፡ ያርባ ሑዳዴ ኹለተኛ እሑድ ወይም ሳምንት ።
ቅድስና፡ ቅዱስነት ንጽሕና ።
ቅድድ አለ፡ ሽርክት አለ ።
ቅድጁ (ቅድው)፡ የተቀዳጀ (ካህን ንጉሥ፡ የተቀዳጀች ንግሥት ልጃገረድ ") ።
ቅድጅት፡ ያክሊል ያበባ አደራረግ ።
ቅጅ (ቅዱሕ)፡ የተቀዳ የተገለበጠ የተጨመረ ። "አንድ ጋን ቅጅ" እንዲሉ።
ቅጅ (ቅድሕ)፡ የጠላ የጠጅ የማን ኛውም መጠጥና ዘይት ቅቤ ውጤት ። የፊተኛው ቅጽል፡ የኋለኛው ስም ጥሬ መኾኑን አስተውል ።
ቅጅ፡ ጽፈት ግልባጭ ("(ዕዝ. ፯፥ ፲፩፡ አስቴ. ፬፥ ፰)") ።
ቅጠ መልካም፡ ቅጡ (ኹኔታው)፡ ያማረ የሰመረ ።
ቅጠ ቢስ፡ ቅጠ መጥፎ የማያምር
ቅጠለ ወርቅ (ቈጽለ ወርቅ)፡ ከወርቅ የተሠራ የወርቅ ቅጠል ።
ቅጠለ ወርቅ፡ በወረቀት ተጠቅሎ የሚጠጣ ትንባኾ፡ ወርቅ የሚያወጣ ቅጠል ማለት ነው ።
ቅጠላ፡ ጭመራ እከላ ።
ቅጠላም፡ ቅጠለ ብዙ ባለቅጠል ። የቅጠል ከፍታት በፊት አለቀኑ የተበላ ተዝካር ። የቅጠል ማለት ጕዝጓዙን ያ ሳያል ።
ቅጠላቅጠል፡ የቅጠል ቅጠል፡ ብዙ ዐ ይነት ቅጠል ።
ቅጠላዊ፡ የቅጠል መልክ (ቀለመ ቅ
ቅጠል (ሎች - ቈጽል)፡ በእኸ ልና በተክል በዛፍ ዐጽቅ ላይ የሚወጣ
ቅጠል፡ ዦሮ፡ በቅጠል አምሳል የተሠራ ዕቃና ጌጥ፡ የጦር ብረት ።
ቅጠል የለሽ፡ ለዛ ቢስ (ንግግሩ ጣም የሌለው ሰው ") ።
ቅጠል፡ የታጠፈ ብራና ወረቀት ።
ቅጠልማ፡ ዝኒ ዓዲ ከማሁ ።
ቅጠልያ፡ ዝኒ ከማሁ (ቅጠል የሚመ
ቅጠባ፡ ክንዳታ ምጠና ምልከታክ ሰላ ።
ቅጡ (ጠባዩ ሥራው)፡ የማይታወቅ ምሳሌ አልባ ።
ቅጣተኛ፡ ቅጣት የተቀበለ ።
ቅጣት (ቅጽዐት)፡ መቅጣት መቀጣት (ግርፋት እስራት ") ።
ቅጣት (ቅጽዓ)፡ ትእዛዝ እንቀጽ ።
ቅጣጥይ፡ በመጨረሻ የሚወጣ መን
ቅጣፊ፡ የቅጠል ቍራጭ ቅንጣቢ ።
ቅጤ፡ የቅጥ (የሰይጣን) ዐይነት ወገን (የተቀጣ እባብ ") ። "አንድስ ቅጤ" እንዲሉ። እባብ ቅጤ መባሉ በርግማን እግሩን ዐጥቶ በደረቱ ስለ መኼዱ ነው ("(ዘፍ. ፫፥ ፲፬)") ።
ቅጥ (ቅጹዕ)፡ የተቀጣ የተቈረጠ ።
ቅጥ፡ ሥርዐት ደንብ አገባብ (ትክክል ልክ ") ("(ምሳ. ፲፩፥ ፳፬)") ። "በቅጥ አለቅጥ ሠራ" እንዲሉ።
ቅጥ፡ ሽልት ። ቀጠጠ ።
ቅጥ፡ ዐይነት ኹኔታ ምሳሌ ። "ሀዘንሽ ቅጥ ዐጣ፡ ከቤትሽም አልወጣ፡ የገደለው ባልሽ፡ የሞተው ወንድምሽ" ። "ቅጡም የምንኵስና ነው" እንዲሉ።
ቅጥ የለሽ፡ ያልተቀጣ ።
ቅጥ፡ የተቀጠጠ (ቍርጥ ዕጭድ ሽልት ") ።
ቅጥለት፡ ዝኒ ከማሁ (ንዴት ብግነት ") ።
ቅጥላት፡ የቅጥል አሠራር ኹኔታ ። (ቃጠለ)፡ ተቃጠለ፡ ነደደ ዐረረ ገመነ ተኰማተረ ተጋጠመ ።
ቅጥል (ሎች)፡ በቅርቃር በምስማር በስፌት በቍጥር የተቀጠለ (የሞፈር የልብስ የገመድ ተጨማሪ ነገር የጐደለ መሙሊያ ") ። "ቅጽልን" እይ ።
ቅጥልጣል፡ ቅጠላዊ ቅጠልያ (የወርቅ የብጫ የወይባ ዐይነት ") ። በግእዝ "ሐመልሚል" ይባላል ።
ቅጥልጣይ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅጥልጥላም፡ ቅጥልጥል ለባሽ (ባለቅ ጥልጥል ") ።
ቅጥልጥል፡ የተቀጣጠለ (ደበሎ ዝተት
ቅጥራት፡ ያጥር የቅጥር ሥራ ።
ቅጥራን፡ የሙጫ ቅመም መጣብቅ የሚኾን፡ ሙጫ ያለበት የስንዴ ዐራራ ቀለም ። "የወይን የበለስ ቅጥራን" ቢል፡ "ዐዞ ከል ሖም ጣጣ" ማለት ነው ። ማንኛውም ነገር ሲቦካ መጣብቅ ይኾናል ። ፈረንጆች ቅጥራንን "ካትራም" ይሉታል ። "ዝፍትን" አስተውል ።
ቅጥር (ሮች)፡ አሽከር ሎሌ ምንደኛ፡ "ጌታችን አንድ አገልጋይ ለኹለት ጌታ መገዛት አይችልም እንዳለ፡ ገረድን ቅጥር ማለት ባንድ ሰው ፈቃድ መታጠሯን በቅጥር (ዐጥር) ውስጥ ማደሯን ያስረዳል" ።
ቅጥር (ቅጹር)፡ የተቀጠረ የታጠረ (ቤት ከተማ ") (ቅጽል) ።
ቅጥር (ቅጽር)፡ መካበቢያ የግንብ የካብ ዐጥር (ስም) ።
ቅጥቀጣ፡ ድብደባ (ብረት ሥራ ወ
ቅጥቃጤ፡ ቅጥቀጣ/ቅጥቅጣት (ግእዝ) ።
ቅጥቅጣት፡ መቀጥቀጥ ።
ቅጥቅጥ (ጦች)፡ የተቀጠቀጠ (ብረት ወርቅ ("(፪ዜና. ፱፥ ፲፭)")) ። "የክትክታና የፍየለ ፈጅ ግጥግጥ" ።
ቅጥቅጥ፡ ውቅጥ (ተባት ፍየል ወይም በግ ") ።
ቅጥበት፡ ጥቅሻ ። በግእዝ "ቅጽበት" ይባላል ። "ቀጸበን" ተመልከት ።
ቅጥቡ ሞላ፡ ዕድሜው ዐለቀ ተፈ
ቅጥባት፡ ቅጠባ (የድር ልክ ምልክት ክስል ") ።
ቅጥብ (ቦች)፡ የተቀጠበ (የተከነዳ/የተለካ ምልክት መቍረ ") ።
ቅጥብ፡ የዕድሜ መጨረሻ ዕለተ
ቅጥነት፡ መክሳት ቀጪንነት ።
ቅጥን አለ፡ ክስት አለ ።
ቅጥን፡ የቀጠነ ቀጪን ። በግእዝም ታናሽ ጣት "ቅጠን" ይባላል ።
ቅጥንብር (ቅጥና ሕብር)፡ ቁመ ትና ቀለም (መልክ ") ።
ቅጥይ (ዮች)፡ ዐጽቅ ክንፍ ቅርንጫፍ፡ ፮ኛ ጣት ።
ቅጥጥ አለ፡ ዐበጠ ተነፋ ተቀበጠጠ ።
ቅጥጥ አደረገ፡ ንፍት ቅብትት አ
ቅጥጥብ፡ ያይን ጥቅሻ (ለግጥ ዘበት ፌዝ ") ። በግእዝ "ትዕይርት" ይባላል ።
ቅጥፊያ - ቅጥፈት፡ ዕብለት ውሸት
ቅጥፋት፡ የኻያጅና የቀሪ ቀንበጥ መለያ ።
ቅጥፍ አለ፡ ቍርጥ አለ ። ተቀጠፈ ።
ቅጥፍ፡ የተቀጠፈ/የተቈረጠ ።
ቅጥፍና፡ ቀጣፊነት ።
ቅጫማም፡ ቅጫም ያለበት የበዛበት ባለቅጫም ።
ቅጫም (ሞች)፡ የቅማል ቅንጣት ከጤፍ የሚያንስ፡ ረቂቅ የዕከክ ትል ። "ቅማንጅርን" እይ ።
ቅጭል፡ መቃጨል ።
ቅጭል አለ፡ ቃጨለ ።
ቅጭልጭል አለ፡ ቃጨለ ።
ቅጭልጭል፡ የተቅጨለጨለ (የቤተ ንጉሥ የቤተ ክሲያን አጫዋች ") ።
ቅጭቅጭ አደረገ፡ አንቀጫቀጨ ።
ቅጭት - ቅጭታት፡ የትከሻ መው ረድ ።
ቅጭት አደረገ፡ ቍርጥ ግንጥል አ ደረገ ።
ቅጭጭላት፡ ለገድ ነፈስ ።
ቅጭጭላት፡ የፈረስ ጕንጭ ትርፍ ሥጋ ተበጥቶ የሚወጣ ።
ቅጸላ፡ ጭመራ ትምርት ሐሜት ።
ቅጽ (ቅጹዕ)፡ የተቀጸ (ያልታጠፈ ብራና ወይም ወረቀት ") ።
ቅጽ፡ የጥራዝ የመጣፍ ልክ መጠን ቁመትናጐን ።ቀጻ ቅጽ የካህናት፡ ቀጣ ቅጥ የሕዝብ ነው ።
ቅጽል (ሎች)፡ ግብርን ዐይነትን መጠንን ለመግለጥ ከስም አስቀድሞ የሚነገር ቃል ።"ደግ ክፉ ቀይ ጥቍር ረዥም ዐጪር" የመሰለው ኹሉ ።ሌላውም ካ፭ቱ አዕማድ የሚወጣ ቅጽል የሠራተኛ ስም፡ "ገዳይ አስገ ዳይ ተገዳይ ተጋዳይ ተገዳዳይ ኣጋዳይ አገዳዳይ" ይላል ።ዳግመኛም "አበድ አሰስ ነበር ቀበር ሰበር ነደድ ሰደድ" የሚል ቅጽል አለ ።"ወንዛወንዝ ጨርቃጨርቅ ቅጠላቅጠል ርጥባ ርጥብ" ይህ ደጊመ ቃል ወይም ተናባቢ ቅጽል ይባላል ።
ቅጽል ተምሳሌ፡ ቅጽል ከምሳሌ ጋራ ባንድነት ሲነገር፡ እሱም የቅኔ ትምርት ነው ።
ቅጽበተ ዐይን፡ ያይን ጥቅሻ ወይም ፍጥነት (ዐይን ተጨፍኖ እስኪገለጥ ያለ እጅግ በጣም ዐጪር ጊዜ ") ("(ኤር. ፲፰፥ ፯)") ።"ቀጠ በን" አስተውል ።
ቅጽበት፡ ከስሳ ካልኢት ("(ሰጎንድ)") አንዲቱ ጭረት ።
ቅጽበት፡ ጥቅሻ ፍጥነት ።
ቅፈፍ - ቀፈፋ ።
ቅፈፍ፡ ቍራጭ ብራና ።
ቅፈፍ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ ፲ ከርክም ለምን ።
ቅፋፊ፡ የተቀፈፈ (ተቀፎ የወደቀ ") ።
ቅፍ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ቅፍለት (ዐረ ቃፍላ)፡ ተከታትሎ አተርትሮ ባንድነት የሚኼድ የሚጓዝ ባለጭነት የነጋዴ ግመል ("(ዘፍ. ፴፯፥ ፳፭)") ።
ቅፍለቶች፡ ሲራራ የጫኑ ግመሎች ("(ኢዮ. ፮፥ ፲፰ - ፲፱)") ።
ቅፍርናሖም፡ በምድረ እስራኤል ክ ፍል ያለ ቀበሌ ።
ቅፍቀፋ፡ ሰበራ ፍልፈላ ክርከራ ።
ቅፍቅፋት፡ የንቍላል የግንድ ስብር ባሪ ድቃቂ ።
ቅፍቅፍ፡ የተቀፈቀፈ የተፈለፈለ (ፍልፍል የተከረከረ ") ።
ቅፍቅፍ፡ የተነቃቀፈ።
ቅፍንድ፡ የቈርበት ዘርፍ ። "ቀፈደን" እይ ።
ቅፍድ፡ የተቀፈደ በቀፈድ የታሰረ ።
ቅፍድድ አደረገ፡ ቀፈደደ ።
ቅፍድድ፡ የተቀፈደደ ።
ቅፍጣን፡ የላይ ልብስ ዐጽፍ፡ ጌጠኛ መደረቢያ ከነጭ ሐር የተሰፋ ።
ቅፍፍ አለው፡ ጨፈገገው ከበደው ጨደደው ።
ቆለ ቢስ፡ ውቃበ ቢስ ።
ቆሊያም፡ ባለቆሌ ዛራም ።
ቆሌ (ቃላዊ)፡ ዛር ለፍላፊ የቃልቻ መንፈስ፡ ውቃቢ ለዛ ።
ቆል (ዕብ)፡ ቃል።
ቆመ፡ ረጋ ጸና፡ ነገሩ ።
ቆመ ብእሲ፡ ዐምደ ወርቅ ። መኻል ለመኻል አንድ ሊቅ ተደግፎት ስለሚቆም ዐምደ ወርቅ በካህናት ቋንቋ ቆመ ብእሲ ተባለ ። ትርጓሜው ሰው ቆመ ወይም የሰው ቁመት ማለት ነው ። ይህ አነጋገር ስምዖን ዘዐምድን ያሳያል ።
ቆመ፡ ተገተረ—(ቀወመ) ።
ቆመልኝ፡ ባለጋራዬን ሞገተልኝ ።
ቆመብኝ፡ ጠበቃ ኾነብኝ ።
ቆማ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ። "ቆማ ፋሲለደስ" እንዲሉ።
ቆማ፡ የሩቅ ሴት ቦዝ አንቀጽ/ንኡስ አገባብ (ተገትራ ") ። "ልጃገረዲቱ ባል ሳታገባ እንዲሁ ቆማ ቀረች" ።
ቆሜ፡ የዜማ ስም (ረዥም ዜማ የቆማ ቆማዊ ማለት ነው ") ።
ቆም (ቀዊም)፡ መቆም ።
ቆም፡ ቁመት ።
ቆም አለ፡ ፈጥኖ ቆመ ።
ቆሞስ (ሶች)፡ ማዕርጉ በኤጲስቆጶስና በቄስ መካከል የኾነ መነኵሴ ምንኵስና ሰጪ ታቦት ባራኪ ።
ቆሬ ። ቃረ (ትግ ቀሐረ)፡ ተኰሰ ፈጀ አቃጠለ ። ሥሩ በግእዝ "ቀርሐ" ነው ።
ቆሬ (ዕብ ቆራህ)፡ የሰው ስም፡ ከሌዊ የተወለደ የሌዊ ዘር ።
ቆሮ (ዎች)፡ የኦሮ የሻንቅላ ዋና ባላባት አምሳለ ንጉሥ ።"አባ ቆሮ" ቢል የቆሮ ኣባት ማለት ነው ።
ቆቁ፡ ያ ቆቅ ።
ቆቅ (ቆቃሕ)፡ በዱር የሚኖር የዶሮ ዐይነት ፍጥረት ። ተባቱም እንስቱም ቆቅ ይባላል ። (ተረት)፡ "እኔ ዐውቃለኹ የቆቅ መላ፡ ወይ በራለች ወይ ደፍጣለች" ። ሲበዛ "ቆቆች" ያሠኛል ።
ቆቅ ማሪ አቦዬ፡ የንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ አባት አቶ አቦዬ አንድ ሰው ቆቅ ቢያመጣላቸው በርኅራኄ ስለ ለቀቋት "ቆቅ ማሪ" የስማቸው ቅጽል ኹኖ ሲነገር ይኖራል ።
ቆቅ፡ ንቁህ ጠን ቃቃ ሰው ።
ቆቅማ፡ ቆቅ የሚመስል ዶሮ ።
ቆቋ፡ ያች ቆቅ ።
ቆበ ጣል፡ ቆቡን ከራሱ አውልቆ የጣለ የወረወረ ያሽቀነጠረ ።
ቆበ ጥላ፡ ቆብ ጥላው፡ ቆቡን እንደ ጥላ የሚቈጥር ዓለማዊ መነኵሴ ።
ቆበተ፡ ቁባት አደረገ (ጠበቀ ") ።
ቆበተ፡ ጠበቀ ዐቀበ ።
ቆባስጥል (ቆብ አስጥል)፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ (ታቹ ገደል ላዩ ቆብየሚ ያስጥል ኀይለኛ ነፋስ የሚነፍስበት ሜዳ ") ።
ቆብ (ቦች - ቆብዕ)፡ ከሰሌን ከሸማ ከክር ከጠጕር ከሣር ገመድ ከበርኖስ የተበጀ (የራስ ማግቢያ መክደኛ ") ። የተባረከ መንፈሳዊ ምሳሌ፡ ምሳሌነቱም የንጽሐ መላእክት ነው ። ሌላም የአይሁድ የስላም የባኒያን የፈረንጅ ቆብ አለ ። "ባርሜጣን" እይ ።
ቆብ ፵ነ፡ መነኰሰ ።
ቆቱ ቀተረ፡
ቆቱ፡ የሐረርጌ ኦሮ ስም (ወራሽ ቈፋሪ ማለት ነው ") ።
ቆን በቀር ሌላ ሰው አይገባበትም ።
ቆንስል (ሎች)፡ የፈረንጅ ንጉሥ መልክተኛ በኼደበት አገር ለወገኖቹ ዳኛ ጠባቂ ለላከው መንግሥት ወኪል ኹኖ በባዕድ አገር የሚቀመጥ ።"የንግሊዝ የፈረንሳይ የጀርመን የመስኮብ የጣሊያን ቆንስል" እን ዲሉ። በፈረንጅኛ "ኮንሱል" ይባላል ።
ቆግላ (ኦሮ - ጎግላ - ክንፍ)፡ ርግብግብ ለማጣ ሰው ።
ቆፍ (ዕብ)፡ ዝንጀሮ (በብዙ ወገን ሰውን የሚመስል አውሬ ") ።
ቆፍ፡ የፊደል ስም (ቀ ") ።
ቋ
ቋ (ኳ)፡ መሰበር መጮኸ ።
ቋ፡ መጮኸ ቋቋ ።
ቋ ሣር፡ አንጓ ያለው ወፍራም ሣር፡ ሲሰብሩት የሚቀለጠም ቋያ ።
ቋ እቋ አለ፡ ተሰበረ ተሰማ ። "የሙክቱ እግር እቀጭ እቋ ይላል" ።
ቋሊማ ማለት አንዠቱ እ ንደ ቀለም (ቀሠም) ውስጠ ክፍት መኾኑን ያሳያል ። ፈረንጆች "ሶሲሶ" ይሉታል ።
ቋመጠ፡ ጐመዠ ሠየ፡ አኹን አኹን አለ ።
ቋሚ (ዎች - ሞች)፡ ቀን ዕንጨት ። እየሰበረ ማታ በጌታው ፊት የሚቆም አሽከር ሎሌ ። "ቋሚ ለጓሚ" እንዲሉ።
ቋሚ፡ ለቤት ሥራ በምድር የሚተከል አራት ማእዘን ዕንጨት ወይም ብረት ።
ቋሚ፡ በሕይወት ያለ ።
ቋሚ፡ ድግስ ሲበላ ሲጠጣ ዐዳይ አሳላፊ አስተናባሪ ።
ቋሚነት፡ ቋሚ መኾን (ፈላጭነት ") ።
ቋማጭ፡ የቋመጠ/የሚቋምጥ (ጕምዡ ") ።
ቋም፡ የውሃ መጠን ዘንግ አቁሞ ወይም በቁመት የሚለካ መልካ ሜዴ ቆመው የሚሻገሩት ። "ወደ ፊት አቋምን" እይ ።
ቋም—ሜዴ—ቆመ ።
ቋሳ (ቈስያ)፡ የተክል ስም (ዱባ ") ።
ቋረኛ (ኞች)፡ የቋራ ሰው የቋራ ተወላጅ ። "ቋረኛ ኢያሱ" እንዲሉ ።
ቋሪት፡ በጐዣም ውስጥ ያለች ቀበሌ ።
ቋሪት፡ የቀበሌ ስም ።—ቋር ።
ቋራ፡ በበጌ ምድር አውራጃ ያለ አገር ስም ።
ቋራም (ሞች)፡ ቋር ያለው (ባለቋር ራሳም ጕጣም ") ።
ቋራም፡ ዱላ እንዲሉ ።
ቋሬ - ቋራዊ፡ የቋራ አገር ልብስ ሸማ (በቋራ ተፈትሎ የተሠራ ዝቅዝቅ ገበርባሬ ") ። በትግሪኛ ግን "ጃኖ" ማለት ነው ።
ቋር፡ የንጨት የፈትል ቋጣራ ("(ዐይን) ጕጥ ") ።
ቋር፡ የዱላ ራስ ።
ቋርፍ፡ የዱር ፍሬና ሥራሥር (እንቅ ርብጭን የወፍ ቈሎን የመሰለ ") ። "የመናኝ የዝንጀሮ ምግብ" ።
ቋሮ፡ ራሳም ዓሣ ።
ቋሸ)፡ አቋሸ፡ ሥጋን በንጀራ አጣበቀ ያዘ፡ ዐንከ በላ፡ በጥርሱ እንደ ቈሻ አደቀቀ/አለነቀጠ ።
ቋቍቻ (ቈቍዐ)፡ የገላ በሽታ (የዕ ከክ ዐይነት፡ ዐንገትን ጕንጭና ጕንጭን ደረትን የሚያሳክክ የሚያፍረከርክ ሴቴ ") ።ዳግመ ኛም አጓጐት ይባላል ("(ዘሌ. ፲፬፥ ፶፮)") ።
ቋቅ (ቀዪእ)፡ ማስታወክ ማውጣት ።
ቋቅ አለ (ቄአ)፡ አስታወከ አስመ ለሰ ።
ቋቅ አለው፡ ጐጓው አስታወከው ።
ቋቋ (ቆቅሐ - ቃሕቅሐ)፡ ቍር ።
ቋቋ አደረገ፡ ኳኳ መታ መታ አደረገ ።
ቋቋቴ - ኳኳቴ፡ ቋቋ ።
ቋቋቴ - ኳኳቴ፡ የንጨት (የጦጣ ቍላ ") እንቡጥ እረኞች እያፈነዱ የሚያንቋቁት የሚ ያስጮኹት ።
ቋቋቴ፡ የጣት አንጓ ።
ቋቋቴ፡ ያሮጌና ያሮጊት ወገብ ሲጫ ኑት፡ የሚንቋቋ ።
ቋተ - ኰዐተ)፡ አቋተ፡ ቋት እ በጀ፡ እቋት ጨመረ ደቀነ ጥሬ እኸልን ።
ቋተ - ኰዐተ)፡ አቋተ፡ ቋት እ በጀ፡ እቋት ጨመረ ደቀነ ጥሬ እኸልን ።
ቋቱ ጠብ አለ፡ ጥቂት ጥቅም ተ ገኘ ።
ቋቱ ጠብ አላለለትም፡ አላገኘም ("እንጀራ አልጠገበም ሆዱ ") ።
ቋቲሮ፡ ቅልጥማም አሞራ (ሽመላ ")፡ ቀጪንና ረዥም ሰው/ከብት ("እንደ ሰጐን ያለ ") ።
ቋታ - ቋቅታ፡ ቋቅ ማለት ! ጓታ፡ እውከት ምላሽ ።
ቋት (ምእላደ ሐሪጽ)፡ የዱቄት መፍሰሻ/መግቢያ/ማረፊያ/መጠራቀሚያ/መከ ማቻ፡ በማቋቻ አንጻር በስተታች ያለ ጕድጓድ (ከጭቃ ከሸክላ የተሠራ ") ።
ቋት፡ ሆድ ።
ቋትለኛ (ኞች)፡ የቋትል ወገን (ዋነተኛ መርከብ መሪ ") ። በግእዝ "ኖትያዊ ኅ ዳፍ" ይባላል ።
ቋትል፡ ከባሕር ከማዕበል ከጐርፍ ከውሃ ምላት ጋራ የሚታገል/የሚጋደል (ዋና ዐዋቂ ") ።
ቋና፡ በበጌ ምድር ክፍል ያለ አገር ።
ቋን ጣዊ፡ የቋንጣ ማለት ነው፡ የጠፍሩን ድርቀት ያሳያል ።
ቋንቍራ፡ ቅራቅንቦ ዕቃ ግሴት ሰባራ ሥንጥር፡ መንገደኛ የሚይዘው ቅል ወረ ንጦ ።
ቋንቍሬ ባቡ ። ቋንቍሬ፡ የኔ ቋንቍራ ።
ቋንቍሬ፡ የስም ቅጽል (የቋንቍራ ቋንቍራዊ ") ።
ቋንቋ ለወጠ፡ ሌላ ልሳን ተናገረ ።
ቋንቋ፡ ልዩ ልዩ ሕዝብ ("(ራእ. ፲፬፥ ፮፡ ፲፯፥ ፲፭)") ።
ቋንቋ፡ አፍ ልሳን ነገር የምላስ ፍሬ ባንደበት ሲነገር የሚሰማ ("(ግብ. ሐዋ. ፪፥ ፮፡ ፮፥ ፲፩ ። ፩ቆሮ. ፲፪፥ ፲)") ። "እከሌና እከሌ ቋንቋ ለቋንቋ ይተዋወቃሉ" ። ሲበዛ "ቋንቆች" ያሠኛል ። በጋልኛ ጕረሮ ቆንቆ ይባላል፡ በምስጢር ከዚህ ጋራ ይሰማማል ። ሰው በየጊዜው እንዲ ወለድ ቋንቋም በየዘመኑ ይፈጠራል ። "ዘነጠንና ጦለበን" ተመልከት ። መደበኛው የኢትዮጵያ ቋንቋ ግእዝ ዐማርኛ፡ ሌሎችም ትግሬ ትግሪኛ አገውኛ አዳልኛ ወላምኛ ጋልኛ ሱማልኛ የከፋ የሲዳሞ የሻንቅላ፡ ከነዚህም በቀር ብዙዎች ዘርፎች አሉ ።
ቋንዣ ቈረጠ፡ እግርን ሰነከለ ።
ቋንዣ ቈራጭ፡ ዐመፀኛ ወንጀለኛ ሽፍታ ምሕረት የማይገባው ።
ቋንዣ፡ ከጕልበት በስተኋላ ከባት በ ላይ ያለ፡ የእግር ማጠፊያ፡ ዋና የደም ሥር ። ሲበዛ "ቋንዦች" ይላል ።
ቋንዶ (ዎች)፡ ያረግ ስም (ጥኑ ጠንካራ ዐረግ ") ።
ቋንዶ ዐረግ (ቀንደ ሐረግ)፡ ያረግ ቀንድ (ዋና ዐረግ ") ።
ቋንጃ፡ የእግር ማጠፊያ (ቋንዣ ") ።
ቋንጅል (ሎች)፡ ቅል ቅምጫና ።
ቋንጢት፡ ከሲታ ሴት ። "ንሺ ቋንጢት" እንዲሉ።
ቋንጣ (ነቅጸ)፡ ተዘልዝሎ የደረቀ ሥጋ ።
ቋንጣ፡ ቀጪን ሰው ኰስማና አካለ ደረቅ ።
ቋንጣ፡ በንዝርት ራስ ላይ ያለች ቈ ላፋ የሽቦ ብረት ።
ቋንጣ፡ ደረቅ የበለስና የወርካ ፍሬ ።
ቋንጤ፡ በቈዳ የተታታ ወንበር ።
ቋንጦች፡ የደረቁ ዝልዝሎች በለሶች፡ ሽቦዎች፡ ኰስማኞች ሰዎች ።
ቋኛት (ቶች)፡ ካረግ ከመቃ የተበጀ ሞላላ ቅርጫት ዓሣ መያዣ ።
ቋኛት ሆድ፡ ሆዱ እንደ ቋኛት የ ኾነ ሰው ።
ቋዝመን፡ እንደ ጩቤ ያለ ታናሽ ካራ ጋፋቶች የሚታጠቁት ።
ቋያ፡ ቋ የበረሓ ሣር ሳይታጨድ ቈይቶ የደረቀ ። "የቋያ እሳት" እንዲሉ። "ሰደደ" ብለኸ "ሰደደን" ተመልከት ።
ቋድ (ዶች)፡ የጠፍር የክር የገመድ የሐር የጥለት የሽቦ አራት ማእዘን ጕንጕን ። ፈረንጆች ቋድን "ኮርዶን" ይሉታል ።
ቋድ አበጀ (ትግ. ቀወደ ቆደ)፡ ወዘበ ዕዛብ ሠራ ጐነጐነ አጠላለፈ ከቈዳ ።
ቋድ፡ ዛብ ሥራ ማተብ ።
ቋድ፡ የዱሮ ጠመንዣ ስቦ መተኰሻ ።
ቋጠረ (ቈጸረ)፡ በሆድ በልብስ ያዘ (አረገዘ ዐቈረ (ምሳ. ፴፥ ፬፡ ኢዮ. ፴፩፥ ፰፡ ፴፯) ።
ቋጠረ፡ ነገር ፀነሰ ዠመረ ወጠነ፡ ሤራ ዐድማ አደረገ ። "አቶ እከሌ የቋጠረው አይፈታም" እንዲሉ።
ቋጠረ፡ አሰረ ቀጠለ ።
ቋጠረ፡ እሰጥ አለ፡ ውርርድ ተከለ (ጐንደር) ።
ቋጠረ፡ ጣቱን ከጣቱ ጋራ አዋሰበ፡ ጋንን ከነአተላውና ከነጠላው ለማንሣት ።
ቋጠረ፡ ፊቱን ኰፈተረ ሰገጠ ጨመ
ቋጠራ፡ አሰራ እርግዝና ።
ቋጣሪ (ዎች)፡ የቋጠረ/የሚቋጥር (አ ሳሪ ቀጣይ ሸማኔ ሢረኛ ") ። "ነገር ቋጣሪ" እንዲሉ።
ቋጣራ፡ ዕጢ የንጨት ዐይን ቋር ጕጥ ።
ቋጣራነት፡ ቋጣራ መኾን፡ ጕጕለት ።
ቋጣሮ፡ ቈቀር ቡጢ፡ የተሳሰረ ሣር፡ የቅጠል ችቦ ("(ማሕ. ፩፥ ፲፫)") ።
ቋጥኝ (ኞች - ቀጣ)፡ ገለብ ገዎቻ ከገደል ተቀርፎ ወይም ተቈርጦ የወረደ ደንጊያ ቤት የሚያኸል ።
ቋጨ (ትግ. ቈጸየ)፡ ጠመዘዘ ኣ ከረረ ጠመረ ገመደ (፪ቱን ወይም ፫ቱን ፈትል ደበለ አንድ አደረገ ") ።
ቋጨራ፡ የታሰረ ጓሳ ነዶ (አንድ ጭብጥ ") ።
ቋጪ፡ የቋጨ/የሚቋጭ (አክራሪ ጠ
ቋፈ) አቋፈ፡ ቈነነ ቀስ አደረገ በመንገድና በምግብ ላይ ።
ቋፍ፡ በገደል ላይ የዝንጀሮ አቀማ መጥ ።
ቋፍ፡ ጫፍ አፋፍ፡ ዐጕል ኑሮ ። "በቋፍ አትቀመጥ ትወድቃለኸ" ።
No comments:
Post a Comment