ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ለ በን ፈንታ እየተነገረ ገቢር ተ ሳቢ ይኾናል ("ጨለማው ላይን ያዘ ለ ፮፻፺፱ ኸን ") ("ከነ") ።
ለሐም፡ ለሐጪ፡ ብዙ፡ ሰው፡ ባለለሐጭ፡ ላንቍሶ፡ አውሬ፡ እንስሳ ።
ለኈሳስ፡ ሹክታ።
ለኈሳስ፡ ላጪ፡
ለሐጭ፡ (ልሕጸ)፡ ቀጪን፡ ምራቅ፡ ካፍ፡ እየወጣ፡ የሚፈስ። ልጋግን፡ እይ።
ለሐፍ፡ (ዐረ)፡ ጥሩ፡ የላይ፡ ልብስ፡ መደረቢያ፡ ባለዘርፍ፡ ምንጣፍ፡ ("ምሳ. ፯፡ ፲፮") ።
ለላመት (ለዓመት)፡ ዝኒ ከማሁ ("ለ
ለመለመ፣ (ለምለመ)፡ ጠደቀ፡ አቀጠለ፡ ለጋ፡ ኾነ፡ ጀፈጀፈ፡ ("ዘኁ. ፲፡ ፯, ፰ ። ማር. ፲፫፡ ፳፰") ።መለመለን፡ እይ፡ ፈጠፈጠንና፡ ቈጠቈጠን፡ ተመልከት።
ለመመ፡ ደገደገ፡ እደፈ።
ለመነ፡ ማለደ፡ ስጦታ፡ ጠየቀ፡ ስጡኝአድርጉልኝ፡ ሥሩልኝ፡ አብሉኝ፡ አጠጡኝአብሱኝ፡ ችሩኝ፡ እለ፡ አባበለ፡ እሽበለበለ፡ ቀፈፈቧገተ ። (ተረት)፡ የለመነ፡ መነመነ ። (ሹም ፣መነ)፣አዘዘ ።ጸለየን፡ እይ ።
ለመከከ፡ መረገ፡ ቀባ፡ ላከከ።
ለመዘ፡ ጠመዘዘ፡ ፈተለ ።
ለመዘገ፡ አጥብቆ፡ ቈነጠጠ።
ለመደ፡ (ለሚድ፡ ለመደ)፡ ተማረ፡ ደገመ፡ አጠና፡ ያዘ፡ ተስማማ፡ ዐወቀ፡ (ጎባው)፡ ባንድ፡ ሥራ፡ ላይ፡ ሠለጠነ። ጽፈት፡ ለመደ፡ ኣገር፡ ለመደ፡ እንዲሉ።
ለመደ፡ ለምድ፡ አበጀ፡ ሰፋ።
ለመደች፡ ከባሏ፡ ተስማማች። (ግጥም)፡ እከሊት፡ ለምዳለች፡ እንዝርቴን፡ ደጋኔን፡ አምጡልኝ፡ ብላለች ።
ለመገገ፡ ሳበ፡ ጐተተ፡ ጠባ።
ለመጠ፡ እነጣ፡ ለምጥ፡ እወጣ፡ የተላ፡ ዕንጨት፡ አስመሰለ ።
ለመጠ፡ ፈገፈገ፡ ሳለ፡ አሰላ፡ ምላጭንበጠፍር - ኣለዘበ፡ ኣለሰለሰ።
ለመጠ ለመጠጠ፡
ለመጠ፡ (ለመጸ)፡ ለማጣ፡ አደረገ፡ ኦጐበጠ፡ አሀባ፡ ኦዘበጠ፡ አደራ፡ ጣራን፡ ወገብን ዕንጨትን፡ ብረትን፣ ማንኛውንም፡ ነገር።
ለመጠ፡ ለጠጠ፡ ቈነነ። ምን ፡ ይለምና ኻል፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ና።
ለመጠጠ፡ ፈጀ፡ አቃጠለ፡ ለቈጠጠ፡ ገረፈ፡ አሰፋ።
ለመጥ፡ ለመጥ፡ ቈነን፡ ቈነን።
ለመጥ፡ አለ፣ ተለመጠ።
ለመጥ፡ መለመጥ።
ለመጮ፣ ለጠሰ፡ አስተኛ
ለመጯ ጯ፡ አሞቀሞቀ።
ለሚ፡ የሚለማ፡ የሚለመልም።
ለማ፡ የሰው፡ ስም።
ለማ፡ (ለምዐ)፡ ለመለመ፡ በጀ፡ ሰመረ፡ በዛ፡ አዝመራው ("ኢሳ. ፲፫፡ ፳") ። (ተረት)፡ ከለማበት፡ የተጋባበት ።የጠፋ፡ ዐዳር፡ ከለማ፡ አንድ፡ ነው ።ለሰው፡ ብትል፡ ትጠፋለኸ፡ ለግዜር፡ ብትል፡ ትለማለኸ።
ለማ፡ በራ፡ ገነነ፡ መብራቱ።
ለማልሞ፡ ወጣት፡ ጐበዝ።
ለማልሞ፡ ከበጌምድር፡ ወደ፡ ስሜን፡ መው፡ ረዥም፡ ገደል፡
ለማመጠ፡ አጐባበጠ ፣ሳሳለ ።
ለማን፡ ዐዝና፡ ላንፋ፡
ለማን፡ ዐዝና፣ የኮከብ፡ ስም ሎሚ፡
ለማኝ፡ (ኞች)፡ የለመነ፡ የሚለምንድኻ፡ ቀፋፊ፡ ቧጋች፡ (ተረት)፡ የለማኝ፡ ለማ ቍረንጮዬን፡ ቀማኝ።
ለማኝ፡ ሳያራ፡ ማለዳ፡ ጧት። እከለማኝ፡ ሳያራ፡ መጣ ።
ለማኝነት፡ ለማኝ፡ መኾን ።
ለማዳ፡ (ዶች)፡ የለመደ፡ የሚለምድ፡ የቤት፡ አውሬ፡ ሰዎች፡ ከዱር፡ ይዘው፡ ወደ፡ ቤት፡ ያመጡት።
ለማጣልምጥ፡ የተለመጠ፣የደራ፡ ድር፡
ለማጭ ፣ የለመጠ፡ የሚለምጥ፡ አዝቢ፡ አ
ለም ።
ለም፡ መሬት፡ ለም፡ ከጠፍ፡ እንዲሉ ።ለምጨቅን፡ ተመልከት ።
ለም፡ (ለምዕ)፡ ለምለም፡ የቀና፡ የለማ፡ መሬት፡ እኸልና፡ ተክል፡ የሚኾን፡ ባለመስኖ፡ (የካህናትና የመኳንንትርስት አብዛኛው) ።
ለምለም፡ ምላስ፡ ደረቅ፡ ያይዶለ፡ ዐጥንት፡ ጕልጥምት፡ የለሽ። በለምለም፡ ምላሱ፡ በሠላሳ፡ ጥርሱ፡ እንዲሉ።
ለምለም፡ (ሞች)፡ የለመለመ፡ ለጋ፡ ቅጠል፡ ርጥብ፡ ሣር፡ እንግ፵፡ ቀጤማ፡ ቀንበጥ፡ እንቦቀቅላ፡ የመሰለው፡ ኹሉ።
ለምለም፡ ፍ∶፡ እንጀራ፡ ወዛም ፣ለስላሳ፣ ማለት፡ ነው።
ለምለምነት፡ ለምለም፡ መኾን።
ለምላሚ፡ የሚለመልም፡ ጠዳቂ።
ለምዛጊ፣ የለመዘዝ፡ የሚለመዝግ፡ ቈን
ለምደኛ፡ የለምድ፡ ዐይነት፡ ከወደ፡ መ ላበሻው፡ በክር፡ የተጋጠመ፡ ዐንገት፡ ልብስ።
ለምደኛ፡ ለምዳም፡ ባለለምድ፡ ለምደ፡ ለባሽ ።
ለምድ፡ (ዶች)፡ ከግምጃ፡ ከሐር፡ ከተለፋ፡ ያንበሳ፡ የነብር፡ የግስላ፡ ቈዳ፡ በደበሎ፡ ዐይነት፡ ተበጅቶ፡ የተሰፋ፡ የጦር፡ ሰራዊት፡ መደረቢያ፡ ልብስ፡ ከጥንት፡ ዠምሮ፡ የተለመደ።
ለምድ፡ አወጣ፡ ገፈፈ።
ለምድ፡ ያንቀልባ፡ ዐይነት፡ አንቀልባ። የታዘለ፡ በለምድ፡ የተረገዘ፡ በሆድ፡ እንዲሉ።
ለምድ፡ ደበሎ፡ ("ማቴ. ፯፡ ፲፭") ። (ተረት)፡ መናጆ፡ የሌለው፡ በሬ፡ ለምድ፡ የሌለው፡ ገበሬ።
ለምድ፡ የፍየል፡ ቈዳ፡ ("ዘፍ. ፳፯፡ ፲፮") ።
ለምዶ፡ ዝላይ፡ ከቅጠል፡ ላይ፡ ልጃገረዶች፡ ወደ፡ ፊትና፡ ወደ፡ ኋላ፡ እየዘለሉ፡ የፋሲካና፡ የገና፡ ለት፡ የሚጫወቱት፡ የባላገር፡ ጨዋታ፣ከጥንት፡ ካባት፡ የቈየ፡ የተለመደ ።ኣንደርዶን፡ ተመልከት ።
ለምዶ፡ ተምሮ፡ ዐውቆ።
ለምጣም፡ (ሞች)፡ ለምጥ፡ የወጣበት ያለበት፡ ባለለምጥ።
ለምጣጭ፡ የለመጠጠ፡ የሚለመጥጥ፣ አቃጣይ፡ ገራፊ ።
ለምጥ፡ (ለምጽ)፡ የበሽታ፡ ስም፣ ገላንነጭ፡ የሚያደርግ፡ ርኩስ፡ በሽታ ።
ለምጦ፡ ኣፉና፡ አፍንጫው፡ ለምጥ፡ የሚመስል፡ ፈረስ።
ለምጨቅ፡ (ለም፡ ጭቃ)፣ሣርና፡ ጭቃ - ጨቆ፣ ጨቀጨቅ ።
ለሞት ተሰጠ)፡ "ይሞት በቃ" ተባለ፡ ዐለፈ።
ለሰሰ፡ ላበ፡ ሞቀ፡ በጥቂቱ።
ለሰስ፡ አለ፣ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለሰቀ (ለጸቀ)፡ ለጠቀ፡ ለጥ፡ ቀጥ፡ አደረገ፡ ጨፈቀ፡ አጣበቀ፡ እያያዘ፡ ርጥብ፣ ጨፈቃን ።
ለሠቀ፡ ለጥ፡ አደረገ፡ ለሰቀ
ለሰነ፣ (ለስኖ፡ ለሰነ)፡ ነገረ፡ ተናገረ፡ (ግእዝ) ።
ለሰነ፡ ምርግን፡ ወይም፡ ልጥፍን፡ ትምትምን፡ ጕርዖን፡ በብዙ፡ ጭድና፡ በቀጪን፡ ጭቃ፡ ለቀለቀ፡ በንፊት፡ ሉሕ፡ ዐሸ፡ ዐሠሠ፡ አስተካ ከለ። ለሰነ፡ በግእዝ፡ ብሰሰ፡ ይባላል ።
ለሳቂ፡ የለሰቀ፡ የሚለስቅ፡ ፋቂ።
ለሳኝ፡ (ኞች)፡ የለሰነ፡ የሚለስን፡ ልስን፡ ዐዋቂ።
ለሳኝነት፡ ለሳኝ፣ መኾን።
ለሴ፡ ሙቀት፡ ያለው፡ ጢብኛ፡ ለከት፡ ሙልሙል። (ተረት)፡ ለመነኵሴ፡ መልካም፡ ለሴ።
ለስ፡ አለ፡ ለብ፡ አለ፡
ለስላሳ፡ ልስልስ፡ የለሰለሰ፡ የለዘበ፡ ልዝብ፡ ("ዘፍ. ፳፯፡ ፲፩, ፲፯") ።ባዘቶ፡ የድመት፡ ጕር ።ዐመልን፡ እይ ።
ለስላሳነት፡ ለስላሳ፡ መኾን ።
ለስላሽ፡ የሚለሰልስ ፣ለዛቢ ።
ለስታ፡ ቅቤ፡ ለጋና፡ ትኩስ፡ ቅቤ
ለስታ፡ ትኵስ፦ለሰሰ ።ላስታ ፣ያገር፡ ስም፡ በየጁ፡ ኣጠገብ ፣ያለ፡ አገር ።
ለስታ፡ (ለስድ)፣ ለብታ፡ ሙቀት።
ለሩቅ ሴት የአን ቀጽ ዝርዝር ("አንተ እሷን ገደልኻት ኻች ካች ") ("ከተተ") ።
ለሩቅ ወንድ የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ እሱን ባረክኹት መረቅኹት ኻት ") ("ካ/ሃ") ።
ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር ("አንተ እነሱን መረ ቅኻቸው ሊ እሱ እነሱ በተባሉት ሰራዊት እየገባ ከእንዲ በኋላ የዘንድ አንቀጽ ኹሉ መነሻ ይኾናል ሊማር ይወዳል ሲማሩ ይወዳሉ ሊበሉት ያሰቡትን አሞራ ስሙን ይሉታል ዥግራ ላ በስም መጨረሻ እየተጨመረ ቅጽልና አንቀጽ ይኾናል ") ።
ለሸለሸ፡ ለሰነ፡
ለሸለሸ፣ ጣለ፡ አወደቀ፡ አጋደመ፡ ፈጽሞ፡ ኣስተኛ፡ ረፈረፈ። የኅዳርበሽታ፡ ሰዉን፡ ኹሉ፡ ለሸለሸው ።
ለሽ፡ አለ፡ ትኝት፡ አለ፡ በደረቱ።
ለቀለቀ ፣ (ለቅለቀ)፡ በዘይት፡ በቅቤ፡ በቀለም፡ በበረቅ፡ በኖራ፡ በበት፡ ቀባ ።እከሊት፡ እበት፡ ይዛ፡ የሰው፡ ቤት፡ ትለቀልቃለች፡ እንዲሉ ።
ለቀለቀ ፣ ቀላልና፡ መጨረሻ፡ ዕጥበትዐጠበ፡ አጠራ፡ አጸዳ ። (ተረት)፡ ጋን፡ ቢለቀልቁት፡ ምንቸት፡ ይመላል።
ለቀለቀ ፣ አሳበጠ፡ ገጠመ፡ ጕረሮን፡ አበዛ፡ ድንኳንን።
ለቀለቀ፡ ወዘወዘ፡ አስጨፈረ።
ለቀመ ፡
ለቀምት፡ የከተማ፡ ስም፡ ነቀምት።
ለቀቀ ፣ ሰደደ፡ ፈታ፡ አወጣ፡ አወለቀኣፈሰሰ፡ ከፈተ፡ ተወ፡ ("ዘፀ. ፲፩፡ ፲ ።ኤር. ፵፰፡ ፳፰ ሕዝ. ፰፡ ፲፪") ። ሚስቱን፡ ለቀቀ፡ ከብቱን፡ ለቀቀልቃቂት፡ ለቀቀ፡ ሽንቱን፡ ለቀቀ፡ አፉን፡ ለቃ ስፍራውን፡ ለቀቀ፡ እንዲሉ። ለመ፡ ብለኽ ልጓምን፡ እይ ።
ለቀቀ፡ ነጻ፡ አደረ፡ ፡ አሰናበተ፡ ባሪያ፥ለቃቂ፡ የለቀቀ የሚለቅፈቺ ከፋች አሰናባች ።
ለቀቅ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ለቀቀ።
ለቀጠ፡ የለነቀጠ፡ ሥር። ቀለጠ፡ ተውሮ፡ ለቀጠ፡ ተብሏል ።
ለቃቃ፡ (ስፉሕ)،ከፋታ፡ አፈ፡ ስፊእንስራ፡ ማድጋ ። (ግጥም)፡ ተገፍቶ፡ ተገፍቶ በታላቅ፡ ለቃቃ፡ ካሳ፡ ሽፍታ፡ ኾነ፡ ለራስ፡ የሚበቃ ።
ለቄታ፡ ለሰለሰ፣
ለቈታ፡ (ሕግ)፡ ስልቻ፡ አቍማዳ። ለሴ፡ ጢብኛ፡- ለሰሰ። ለስ፡ አለ፡ ለብ፡ አለ፡- ለሰሰ። ላሰ፡ (ለሐሰ)፡ ምላስ፡ ጠረገ፡ አጠዳ፡ በላ፡ ተመገበ። እከሌ፡ በጣም፡ ጠግቧል- ማርም፡ ኣይልስ ። (እሳት፡ የላሰ፡ ተንጠልባ፡ የማያናግር። ላሰ፡ አቃጠለ፡
ለቈደ፡ (ለቀደ፡ ያዘ) ድዳ፡ ለንባዳ፡ አደረገ፡ ትክክል፡ መናገር፡ ከለከለ፡ ኣፍ፡ ያዘ ።
ለቈጠጠ፡ ባረፈ፡ ቈነደደ፡ ፈጀ፡ እቃ
ለቅ፡ ዝኒከማሁ፡ የሚያሾልክ ።ወፍን ለቀቃ ፡ ከፈታ፡ መልቀቅ ።ለቀቅ፡ ተወት ።
ለቅላቂ፡ (ዎች)፡ የለቀለቀ፡ የሚለቅልቅ ፣ ቀቢ፡ ዐጣቢ።
ለቅሶ ፣ ሐዘን፡ ትካዜ፡ ቍዘማ፡ ሙሾ፡ የንባ፡ መመንጨት፡ መፍሰስ መውረድ። (ተረት)፡ እንደ፡ ነደደች፡ ተነሥታ፡ የሰው፡ ለቅሶ፡ አጠፋች።
ለቅሶኛ (ኞች)፡ ባለለቅሶ፡ እለቅሶ፡ ቤት፡ ኻያጅ፡ የሬሳ፡ ዐጀብ።
ለቅርብ ሴት የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ አንቺን አሰርኹሽ ተበተብኹሽ ወደድኩሽ ጠላኹሽ ኹት ") ("ክዎ") ።
ለቆ፡ ዐዘል፡ ለቆ፡ ያዘለ፡ ደረቅ፡ የበልግ፡ ሣር ።
ለቆ፡ (ዎች)፡ ለቀወ፡ የሣር፡ ል
ለቆ፡ ላቀ ፣
ለቋዳ ፣ ልቍድ፡ የተለቈደአፈ፡ እስር።
ለበሰ፡ ለጋ፡
ለበሳ መልበስ ("ልብስ ") ("ሶች") ።
ለበስ አለ ("ወፈር አለ ሸማው ልቡስ የለበሰ ") ("ግእዝ") ።
ለበን፡ ለበሰ፡
ለበጠ፡ ሐሰትን እውነት አስመሰለ ("ሸለፈ ሸረደደ ለበጠ ሠነበጠ ለጠጠ ለባጭ ") ("ጮች") ።
ለበጣ/ለበጥ ሽለፋ ("ሽንገላ ሽርደዳ ምፀት ለበጣ ነገር ካንገት በላይ እንጂ ከልብ ያልኾነ ግብዝ የለበጣ ነገር ልበጣ ልጠፋ ሽፈና ሥንበጣ መለበጥ መለጠፍ ማልበስ ማስጌጥ መለበጥ መሸለፍ መሸርደድ መለበግ መለጠፊያ መሸፈኛ ማስጌጫ ብርና ወርቅ ንሓስ ") ("ዘኍ. ፲፮፡ ፴፰-፴፱") ።
ለብታ ለብ ማለት ("ለብታ ለስታ ቀላል ሙቀት ለብ አደረገ ጥቂት አሞቀ ቅዝቃ ዜን ኣራቀ ለብ አለ ለስ አለ ለብ ያለ ለስ ያለ ") ("ራእ. ፫፡ ፲፮") ።
ለተተ፡ (ለትቶ፡ ለተተ፡ ኰለተፈ)፡ ለፋ፡ ለሰለሰ፡ ደከመ፡ መኼድ፡ መሥራት፡ እቃተው፡ ሰነፈ ።ለተለተን፡ እይ፡ የዚህ፡ ደጊም፡ ነው ።
ለታ፡ የሰው፡ ስም፡ በመንዝ፡ የግድም፣ ባላባት።
ለታታ፡ (ለታት፡ ኰልታፋ)፡ የለተተ፡ የለፋ።
ለት፡ (ሎቱ)، በዘማች፡ አንቀጽ፡ መፊረሻ፡ በሩቅ፡ ወንድ፡ ዝርዝርነት፡ እየገባ ፣በቁም፡ ቀሪ፡ ኹኖ፡ ይነገራል ። (ማስረጃ)፡ መባ ለት፡ ወረደለት፡ ዐለፈለት። ይኸውም፡ የበጎ፡ ነው። በትንቢትና፡ በትእዛዝ፡ አንቀጽም፡ ሲገባ፡ ይመጣለት፡ ይምጣለት፡ ይላል ።
ለት ፣፡ ቀን ዕለት።
ለት/ለታ/ዕለት፡ ያን ለት (አኹን)።
ለነቀጠ፡ (ትግ ለንቀጠ)፡ በሙቀጫ፡ ተወቅጦ፡ በውሃ፡ የተዘፈዘፈውን፡ የማሽላ፡ እንቀት፡ ፈጫ፡ አላመ፡ ኣለዘበ ።ለቀጠን፡ እይ፡ ሥሩ፡ ርሱ፡ ነው ።
ለንቃጭ፡ የለነቀጠ፡ የሚለነቅጥ፡ አላሚ ።ልንቀጣ፡ የመለንቀጥ፡ የማላም፡ ሥራ።መለንቀጥ፡ መፍት፡ ማላም፡ ማለዘብ ።መለንቀጫ፡ ማላሚያ፡ ማለዘቢያ፡ የቅምጥ፡ ወፍጮ።
ለንቋጣ፡ (ጦች)፡ የንጨት፡ ስም፡ በወይናደጋ፡ ቈላ፡ የሚበቅል፡ አነስተኛ፡ ዛፍ፡ ልጠ፡ ማላጋ ።
ለከለከ በምላሱ፡ እየጨለፈ፡ ውሃ፡ ጠጣ፡ ሊጥን፡ ዋጠ፡ የውሻ።
ለከለከ፡ ለከፈ፡
ለከመ፡ (ለኰመ)፡ ወሬ፡ ለቀመ፡ አወራ፡ ተናገረ፡ ለፈለፈ፡ አሳበቀ። ትግሬ፡ ግን፡ ለከመን፡ ይዞ፡ ኼደ፡ ወሰደ፡ ይለዋል።
ለከሰ፡ (ልህሰ)፡ ደከመ፡ ዐቅም፡ ዐጣ፡ ሰነፈ፡ ታከተ።
ለከስካሳ፡ የተልከሰከሰ፡ የሚልከሰከስ።
ለከተ፡ (ለካ)፡ ገጠመ፡ ዝም፡ አሠኘ።
ለከት፡ (ቶች)፡ ታናሽና፡ ሞላላ፡ ጢብኛ፡ የሊጥ፡ መፈተኛ። አክሥቴ፡ ቤት፡ አለኝ፡ ለከት፡ እንዲል፡ እረኛ
ለከት፡ ልክ፡ መግጠሚያ፡ (ዝምታ) ። እከሌ፡ ላፉ፡ ለከት፡ የለውም፡ እንዲሉ። ለካን፡ ኣስተውል ።
ለከፈ፡ (ለኪፍ፡ ለከፈ)፡ ቀመስ፡ ነካ፡ ነከሰ ። ውሻ፡ ለከፈው። ለከፈ ዠመረ፡ ያዘ። በሽታ፡ ለከፈው፡ ጋኔን፡ ለከፈው።
ለከፈ፡ አቀረበ፡ ደቀነ። ከምድራኹ፡ ላይ፡ ዘወር፡ በል፡ እዚህ፡ ምን፡ ለክፎኻል።
ለከፋ፡ ልክፊያ፡ ቅምሻ።
ለኪ (ለካኢ)፡ የለካ፡ የሚለካ፡ ሸላጊ።
ለካ፡ (ለክአ)፡ መጠነ፡ ሰፈረ፡ ቀጠበ፡ ሸለገ፡ ረተመ፡ ከነዳ፡ መዘነ፡ ("ራእ. ፳፩፡ ፲፯") ። ውሃ፡ በዘንግ፡ ይለካል፡ እንዲሉ።
ለካ፡ ትእዘዝ፡ አንቀጽ፡ መጥን፡ ስፈር፡ ከንዳ፡ መትር።
ለካ፡ ንኡስ፡ አገባብ፡ እኔ፡ ነገሩ፡ አልገባኝም ነበር፡ ለካ፡ እንዲህ፡ ኑሯልን። እኮንና፡ ብ ያን፡ እይ። ተደጋግሞ፡ ሲነገር፡ እውነት፡ እውነት፡ ርግጥ፡ ርግጥ፡ እንደ፡ ማለት፡ ለካ፡ ለካ፡ ይላል፡ ምስጢሩ፡ ልክን፡ አይለቅም ።ያው፡ የነገር፡ አጐ ላማሽ፡ ነው።
ለካሚ፡ (ዎች)፡ የለከመ፡ የሚለክም፡ ወሬኛ፡ ወሬ፡ ማዱ፡ ለፍላፊ።
ለካከፈ፡ ቀማመሰ፡ ነካካ።
ለካፋ፣ የተለከፈ፡ የሚለከፍ፡ የተደቀነ፡ የሚደቀን ።
ለክ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ዋጠ። ለክ፡ ለክ፡ አደረገ፡ ዋጥ፡ ዋጥ፡ ጠጣ፡ ጠጣ፡ አደረገ።
ለክ፡ ዋጥ፡ ሰልቀጥ።
ለክላኪ፡ የለከለከ፡ የሚለከልክ፡ ዋጭ።
ለኮ፡ (ኦሮ)፡ የፈረስ፡ የበቅሎ፡ መሳሲያ፡ ጠፍር፡ ወይም፡ ገመድ፡ ከልባብ፡ ጋራ፡ የተ ቋጠረ፡ ፫፡ ክንድ፡ የሚኾን።
ለኮ፡ መሬት፡ በለኮ፡ የተለካ መሬት፡ በዘመቻ፡ ግልቢያ፡ የተገኘ፡ መኾኑንም፡ ያሳያል ።
ለኰሰ፡ (ለኈሰ)፡ ተኰሰ፡ አቃጠለ፡ አያያዘ፡ አነደደ።
ለኰሰ፡ ላላ፡
ለኰሰ፡ ሰነቀረ፡ አጋባ፡ ነገርን፡ በሽታን።
ለኰሠ፡ እሳት፡ አያያዘ፤ለኰሰ።
ለኮቴ፡ ለኾቴ፡ መሳል፡ የመሳል፣
ለኰፈ፡ (ኰለፈ)፡ ጥቂት፡ መታ፡ ተነኰሰ ።
ለኰፈ፡ ለከሰ፡
ለኰፍ ፣ መለከፍ።
ለኰፍ፡ አደረገ፡ ለኰፈ።
ለኳሳ፡ ዐቅለ፡ ቢስ፡ ለዋሳ ።
ለኳሽ፡ (ሾች)፡ የለኰሰ፡ የሚለኵስ፡ ተኳሽ፡ አቃጣይ።
ለኳኰፈ፡ በቀላል፡ መታታ፡ ተነኳኰሰ።
ለኳፊ፡ የለኰፈ፡ የሚለፍ፡ ተንኳሽ።
ለኳፋ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለኸ፡ (ሀሎከ)፡ አንተ፡ ለሚባል፡ ለቅርብ፡ ወንድ፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር፡ ሲኾን፡ (ትማር፡ አለኸ፡ ትጽፍ፡ አለኸ)፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ትማራለኸ፡ ትጽፋለኸ፡ ተብሎ፡ ይነገራል ።
ለኹ፡ (ሀሎኩ)፡ እኔ፡ ለሚል፡ በግስ፡ መጨረሻ፡ እየገባ፡ የሚነገር፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር። (በልቼ፡ አለኹ፡ ጠጥቼ፡ አለኹ)፡ በማለት፡ ፈንታ፡ በልቻለኹ፡ ጠጥቻለኹ፡ ይባላል። አ፡ ተቀዳሚውን፡ ፊደል፡ ራብዕ፡ አድርጎ፡ ስለ፡ ተጐረደ፡ ለኹ፡ ተባለ ።
ለወሰ፡ ("ሎሰ")፡ ቀላቀለ፡ አላቈጠ፡ ዐሸ፡ አዋዋደ፡ አቦካ፡ ("ዘፍ. ፲፰፡ ፮ ።፩ሳሙ. ፳፰፡ ፳፬") ።ለወሰ፡ በጭቃ፡ በከለ፡ ረገጠ።
ለወዘዘ፡ ወ፡ ስሯጽ፡ ነው፡ ለዘዘ፡ እንደ፡ ለውዝ፡ ኾነ።
ለወዘዝ፡ ለውዛዛ፡ የለወዘዘ፡ ለዛዝ፡ ለ ዛዛ፡ ደረቅነትና፡ ርጥብነት፡ ያለው።
ለወገ፡ የሎገ፡ ዘር፡ ነው፡ ሎማን፡ ተመ
ለወጉ/ለወጓ፡ የወንድና የሴት ስም ("ዝርዝሩ ኣባትንና እናትን ያያል") ።
ለወጠ፡ (ወለጠ)፡ ሌላ፡ አደረገ፡ ቀየረ፡ ("፪ዜና. ፴፮፡ ፬") ።የራሱን፡ ገንዘብ፡ ሰጥቶ፡ የሌ ላውን፡ ገንዘብ፡ ገዛ፡ ተቀበለ፡ እጅ፡ አደረገ፡ ወሰደ ።
ለወጠ፡ አሸተተ፡ አገማ፡ ጠረኑን፡ መዐዛውን፡ ቃናውን።
ለወጠ፡ ዐደሰ፡ አረቀቀ።
ለወጥ፡ አለ፡ ተለወጠ ።
ለወጥ፡ (ተወልጦ)፡ መለወጥ ።
ለዋ፡ (ለወየ)፡ አብዝቶ፡ ጠጣ፡ ሰበከተ፡ ለገሸ ።
ለዋሳ፡ (ሶች)፡ የተለወሰ፡ ደካማ።
ለዋሳነት፡ (ልውሰት)፡ ለዋሳ፡ መኾን፡ ደካማነት ።
ለዋሽ፡ (ሾች)፣ የለወሰ፡ የሚለውስ፡ አላቋጭ ።
ለዋወጠ፡ ቀያየረ፡ መላልሶ፡ ለወጠ።
ለዋጭ፡ (ጮች)፡ ወላጢ፡ መወልጥ)፡ የለወጠ፡ የሚለውጥ፡ ዐጣሪ፡ ቸርቻሪ፡ ("ዮሐ. ፪፡ ፲፬") ።
ለውለው፡ አለ፡ ዘው፡ ዘው፡ እለ፡ እዚያም፡ እዚያም፡ ኼደ፡ ተገኘ ።
ለውለው፡ ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለውላዋ፡ (ለውለወ)፡ ውልብልብ፡ ቀውቃዋ ።
ለውንድዝ፡ የሚያስፈራ፡ ደሴት "
ለውዜ፡ የኔ፡ ለውዝ፡ ዜማኸ፡ የለውዝ፡ ጣዕም፡ ያለው፡ ማለት፡ ነው ።
ለውዝ፡ (ዞች)፡ የተክል፡ ስም፡ ፍሬው፡ የሚጣፍጥ፡ ዕንጨት።ለውዝ፡ ገውዝ፡ እንዲሉ፡ ("ኤር. ፩፡ ፲፩") ።
ለውጤ፡ የሰው፡ ስም፡ ምትኬ፡ ማለት፡ ነው ።
ለውጥ፡ ልዋጭ፡ ልው፡ ምትክ ' ፈንታ፡ ("ዘሌ. ፳፯፡ ፲ ።መዝ. ፵፬፡ ፲፪ ።ኢሳ. ፫፡ ፳፬ " ኤር. ፳፪፡ ፲፩") ።
ለውጥነት፡ ለውጥ፡ መኾን።
ለውጦች፡ ምትኮች፡ ፈንቶች።
ለዘለቃ፡ ለፍጻሜ/ለመጨረሻ ።
ለዘለዘ፡ (ለዘዘ፡ ነዘነዘ)፡ ጠጠ፡ መጠመጠ፡ አረሰረሰ፡ መዘመዘ።
ለዘለዝ፡ ለዝላዛ ፣ የለዘለዘ፡ የሚለዘልዝ።
ለዘላለም፡ ለብዙ ዘመን ።
ለዘበ፡ ተባለ፡ ተወረበ፡ ዜማው።
ለዘበ፡ ደቀቀ፡ ላመ፡ ለሰለሰ፡ ምላሱ፡ ነገሩ፡ ጠባዩ፡ ዶቄቱ፡ እጀ፡ ሥራው፡("ምሳ. ፳፱፡ ፭") ።
ለዘብ ፣ ወረብ፡ በበዓል፡ ቀን፡ በቅኔ፡ ማሕሌትና፡ በዑደት፡ ጊዜ፡ ታቦት፡ ሲነግሥ፡ በጸናጽልና፡ በከበሮ፡ እየተመላለሰ፡ የሚባል፡ ረዥም፡ ዜማ ።
ለዘብታ፡ ቀስታ፡ ትሕትና "
ለዘዘ፡ ርጥብ፡ አስተኔ፡ ኾነ፡ ከመክረር፡ ከመጠጠር፡ ራቀ። ዐተሩንና፡ ባቄላውን፡ የንጀራ፡ ጕዝጓዝ፡ ብታደርገው፡ ይለዝዛል። ለወሀዘን፡ እይ።
ለዘገ ፣ (ለሐቀ)፡
ለዚያ (ሎቱ)፡ ለርሱ ።
ለዚያ፡ ለርሱ፡ ዚያ ።
ለዛ፡ ቢስ፡ ውበት፡ ማማር፡ የሌለው፡ ለዛው፡ መጥፎ።
ለዛ ሙጥጤ፡ ክቾ፡ ደመ፡ ቢስ ።
ለዛ፡ (ትግ፡ ለዘየ፡ አለገገ)፣ ወዝ ፡ ውበት፡ የነገር፡ ጣዕም።
ለዛቢ፡ የሚለዝብ።
ለዛባ፡ ለስላሳ፡ ሻካራ፡ ያይዶለ።
ለዛዛ፡ ለዛዝ፡ የለዘዘ፡ የሚለዝ።
ለዛዛነት፡ ለዛዝነት፡ ለዛዛ፡ ለዛዝ፡ መኾን ።
ለዝና፡ የወንድና የሴት ስም ።
ለየ፡ (ለእየ)፡ እያንዳንዱ፡ እየራሱ፡ እየፊናው፡ እየብቻው፡ የሚባለው፡ ቃል፡ ለ፡ ተቀባይና፡ በቁም፡ ቀሪ፡ ኹኖ፡ በመነሻው ፣ሲመር በት፡ ለያንዳንዱ፡ ለየራሱ፡ ለየፊናው፡ ለየብቻው፡ ተብሎ፡ ይነገራል። እየን፡ እይ።
ለየብቻ (ለእየብቻ)፡ ለያንዳንድ ለ የራስ ለየቅል ። ዳንኤል ረበናትን ለየብቻቸው ጠየቃቸው ።
ለይኩን፡ ፍቱን መድኀኒት አብነት ።
ለደለደ (ለጠለጠ)፡ ለሰለስ፡ ተሰማማ፡ ተዋዋደ፡ ወፈረ፡ የወጥ፡ የመረቅ፡ የምራቅ፡ የሳሙና፡ የንዶድ፡ ዐረፋ ።
ለደለድ፡ ለድላዳ፣ የለዶለደ፣የተዋዋዶ፡ ልድላዴ፡ ልስላሴ፡ ውፋሬ "
ለደመ፡ ለጠመ፡ ለተመ ።
ለደፈ፡ (ትግ፡ ሐባ፡ ለፅፈ)፡ ለጠፈ፡ ምራቅን ።ባላገር፡ ለጠፈ፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ለደፈ፡ ይላል፡ ይኸውም፡ ደና፡ ፀ፡ ተወራራሽ፡ መኾናቸውን፡ ያስረዳል ።
ለዳፊ፡ የለደፈ፡ የሚለድፍ፡ ለጣፊ።
ለገሰ፡ ብዙ፡ ዝናብ፡ ጣለ፡ ወለሰ።
ለገሰ፡ ባለመቈጠብ፡ ሰጠ፡ ናኘ፣ ቸረ።
ለገሠ፡ ቸረ ለገሰ።
ለገሸ፡ አለልክ፡ ጠጣ።
ለገበ፡ (ትግ)፡ ልብስን፡ ጣፈ " ሥሩ፡ ለጐመ፡ ነው።
ለገተ፡ (ለጐተ)፡ ለገደ።
ለገቸ፡ አስጠጋ፡ አሳዘነ፡ አማለ።
ለገቻ፡ ማስጠጋት፡ ዐዘን፡ ውል፡ ማሳ።
ለገን፡ (ልጕን)፡ የሸክላ፡ ዕቃ፡ የደቅ፡ ዐይነት፡ ደቅ፡ ዋዲያት። ሲበዛ፡ ለገኖች፡ ይላል፡
ለገደ፡ ኣገባ፡ ወተፈ፡ ቀረቀረ፡ ደነቀረ፡ መረገ።
ለገደ፡ (ትግ፡ ለገጸ)፡ ቀለደ፡ ተረበ። ባረብኛ፡ ፀና፡ ደ፡ ተወራራሽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ ትግሪ ኛው፡ ለገጸ፡ ባማርኛ፡ ለገደ፡ ተባለ። ("ለገጠ")ን እይ።
ለገዳ፡ ቅርቀራ፡ ውተፋ።
ለገድ፡ ነፈል፡ ቅጭጭላት።
ለገገ፡ (ሠወነ)፡ ተለቀቀ፡ ወጣ፡ ተ
ለጊ፡ የለጋ፡ የሚለጋ፡ የሚመታ፡ አጠንጊ።
ለጋ፡ ልጅ፡ ካ፲፭፡ ዓመት፡ በታች፡ ያለ፡
ለጋ፡ ቅቤ፡ ትኵስ፡ ለስታ፡ ቅቤ።
ለጋ፡ ጨረቃ፡ ብርሃኗ፡ ያልሞላ፡ ያልደ
ለጋ፡ ቀንበጥ፡ ሙሽራ፡ ያልጠና፡ ያልጠ ነከረ፡ ቅጠል፡ ልጅ፡ ለምለም፡ እንቦቀቅላ፡ ("፩ዜና. ፳፱፡ ፩") ።("ኢሳ. ፲፭፡ ፮") ።ለጋ፡ ጐመን፡ እንዲሉ ። (ግጥም)፡ እኔ፡ እንቢ፡ አሻፈረኝ፡ እወጣለኹ፡ ደጋ፡ ዐንገቷ፡ ይመስላል፡ የጠንበለል፡ ለጋ ።
ለጋ፡ ባለማቋረጥ፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ጠጣ። ሸመጠጠን፡ እይ ።
ለጋስ፡ (ሶች)፡ የለገሰ፡ የሚለግስ፡ ቸር፡ ሰጪ፡ አባ፡ መስጠት፡ ("ኢሳ. ፴፪፡ ፭") ።
ለጋስነት፡ ለጋስ፡ መኾን።
ለጋዎች፡ ለጎች፡ ቀንበጦች፡ ለምለሞች፡ ለጋ፡ ጐበዝ፡ ወጣት፡ ልጅ፡ እግር፡ ሦታ። ለጋ፡ ደመና፡ ጥቍረት፡ ጥቍርነት፡ የሌ ለው፡ ደመና።
ለጋጅ፡ የለገደ፡ የሚለግድ፡ ቀርቃሪ።
ለግ መስፈሪያ፡ ሎን ።
ለግዳ፡ ቅምሖ፡ የጕረሮ፡ ዕብጠት፡ በኹለት፡ ወገን፡ የሚበቅል፡ በማንቍርት፡ ጫፍ፡ የሚ ለገድ። ለቅዳ፡ ተብሎ፡ ሊጻፍም፡ ይቻላል።
ለግድ፡ ለግጥ።
ለጐመ ("ጐለበ በኮርቻ ዕንጨት ላይ ቈዳን ሰፋ መረገ ለበደ ") ("ትግ") ።
ለጐመ፡ (ለገበ)፡ አገልግልን፡ ማንኛውንም፡ ስፌት፡ በቈዳ፡ በተንቤን፡ ሰፋ፡ ለበደ፡ አለበሰ፡ መላውን፡ ወይም፡ ከንፈሩንና፡ እግሩን ።ከፈፈን፡ እይ ።
ለጐመ፡ (ለጒም፡ ለጐመ)፡ ልጓምን፡ ጥይትን፡ ኳስን፡ ለበቅሎ፡ ለፈረስ፡ ለጠመ ንዣ፡ ለባሪያ፡ አጐረሠ፡ ቀረቀረ።
ለጐመ፡ ልዳ፡
ለጐመ፡ ዝም፡ አሠኘ፡ አሰረ፡ ዘጋ፡ አፍን፡ ("ዘዳ. ፳፭፡ ፬") ።
ለጐደ፡ ለደፈ፡ ለጠፈ፡ የምራቅ፡ የንፍጥ፡ የጭቃ ።
ለጐጠን፡ አስተውል ።
ለጓሚ፡ (ሞች)፡ የለጐመ፡ የሚለጕም ፈረስ፡ በቅሎ፡ ጫኝ።
ለጓጅ፡ የለጐደ፡ የሚለጕድ፡ ለዳፊ።
ለጠ፡ የሊቃውንት፡ ሊቅ፡
ለጠ፡ ዳለጠ፡ ለዘበ፡ ከመሻከር ራቀ፡ ሥራ ፈታ፡ ማገጠ።
ለጠለጠ፡ (ለጽለጸ)፡ ሊጥ፡ እስኪኾን፡ ቅባት፡ እስኪወጣው፡ ወቀጠ።
ለጠለጠ፡ (ትግ፡ ለጥለጠ፡ ዘበጠ)፡ ጠፈጠፈ፡ አጠፈጠፈ፡ ዘረጋ፡ እንደ፡ ነጥር፡ ልክ፡ ትክክል፡ አደረገ።
ለጠለጠ፡ ለጠፈ ፡
ለጠቀ ("ቀጠለ ዐ ጀበ በነገር በሥራ በሥልጣን በንብረት ተተካ ") (ዘፀ. ፲፬፡ ፰) ።
ለጠበ፡ (ለጠመ)፡ ለጠብ፡ ሰፋ፡ አበጀ፡ ከደነ፡ ገጠመ።
ለጠብ፡ (ቦች)፡ የቅል'የናርጅ፡ የጮጮ፡ መክደኛ። ጠብና፡ ለጠብ፡ ባማርኛ፡ ይተባበራሉ ።ሴትዮዋ፡ የመጣችው፡ ለጠብ፡ ነው፡ ለጠብ ፣ት ሰፋለች።
ለጠጠ፡ ዘረጋ፡ አስተካከለ ።
ለጠጠ፡ (ለጺጽ፡ ለጸጸ። ትግ፡ ለጠጠ፡ አብዝቶ፡ ጫነ)፡ ሠነበጠ፡ ከፈለ፡ ነጠለ፡ ብቻ፡ አደረገ፡ የንጨት፡ የድር ።
ለጠጠ፡ ሳበ፡ ጐተተ፡ ገተረ፡ ቀስትን፡ ("ኤር. ፱፡ ፫ ። ፶፩፡ ፫ ። ዘካ. ፱፡ ፲፫") ።
ለጠጠ፡ አበዛ። ዛሬ፡ ሌሊት፡ አቶ፡ እከሌ፡ እንቅልፉን፡ ሲለጥጥ፡ ዐደረ ።
ለጠጠ፡ መታ፡ ደበደበ ።
ለጠጠ፡ ቈነነ፡ ሰውን ።
ለጠጦ፡ ረዥም፡ በትር፡ ወይም፡ ሽመል፡ (ጐንደር) ።
ለጠጦ፡ ካገዳ፡ እንኵሮ፡ ሥር፡ ከገበር፡ ምጣድ፡ ላይ፡ ተለጥጦ፡ የሚነሣ፡ ሥሥና፡ ደረቅ፡ አንኳሪ፡ የሚበላው፡ የንኵሮ፡ ሉሕ። ቀለጦን፡ እይ፡ ከዚህ፡ ጋራ፡ አንድ፡ ነው።
ለጠፈ ("ሸፈነ አለበሰ አስጌጠ በወርቅና በብር ") ("ዘኍ. ፲፮፡ ፴፰") ።
ለጣጭ፡ (ጮች)፡ የለጠጠ፡ የሚለጥጥ፡ ሠንባጭ፡ ከፋይ፡ ነጣይ፡ ሳቢ፡ ጐታች፡ ቈናኝ። ልጠጣ፡ ንጠላ፡ ጕተታ።
ለጥ፡ አለ ተዘረጋ፡ ተሰጣ፡ ተኛ፡ ተ ካከለ ። ለጥ፡ ያለ፡ ሜዳ፡ እንዲሉ። ለጥ፡ አለ፡ ግእዝ፡ ለጥሐ፡ ከሚለው፡ ሊወጣም፡ ይችላል ።
ለጥ፡ አለ፤ትክክል፡ ኾነ፡ ለ ጠጠ ።
ለጥ፡ ይበሉ፡ የሰው፡ ስም ።
ለጥላጭ፡ የለጠለጠ፡ የሚለጠልጥ፡ አጠፍጣፊ፡ ዘርጊ "
ለጨ፡ ድጥ ኾነ።
ለፈለፈ፡ (ለፈፈ)፡ ቀባጠረ ነገር፡ አበዛ ፣ባለማቋረጥ፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ተናገረ ። (ተረት) ፣ይጠፉ በለፈለፉ።
ለፈወቀ፡ በምግብ፡ ጊዜ፡ አፉን፡ አጮኸ፡ እንጯ፡ እንጯ፡ አደረገ ።
ለፈደ፡ ዘበዘበ፡ ነገርአልቈርጥ፡ ኣለ ።
ለፈደደን፡ ተመልከት ።
ለፈደድ፡ ለፍዳዳ፣ የተለፋደደ፣ የሚለፋደድ፡ ጨመለቅ፡ ጨምላቃ፡ ነገረ፡ በክ ።
ለፈዲያም፡ ዝብዝባም፡ ነገረ፡ ጐትት ።
ለፈድ፡ ዝብዝብ፡ ጣመ፡ ቢስ፡ ነገር ።
ለፈጠ፡ (ለፈጸ)፡ ዐሸ፡ ለወሰ፡ አበቀ፡ አበሰበሰ ።
ለፈጨቀ፡ ነዘነዘ፡ ጨቀጨቀ ።
ለፈጯ፡ ልፋጭ፡ አደረገ፡ ልፋጭ፡ አወጣ ።
ለፈፈ፡ ዐጠፈ፡ ጠቀለለ ።
ለፈፈ፡ (ለፊፍ፡ ለፈ)፡ እየዞረ ' ኾነገረ፡ ዐወጀ፡ አሰማ፡ ሰበከ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፴፮") ።
ለፊ (ለፋዒ)፡ የለፋ፡ የሚለፋ፡ የሚደክም፡ ውርደት፡ ተቀባይ። (ግጥም)፡ ሰዉ፡ ሰው፡ ላይ፡ ገቢ፡ ነው፡ የተያዘ፡ እንደኹ፡ ለፊነው ።
ለፋ፡ (ትግ፡ ለፍዐ)፡ ታሸ፡ ተፈተን፡ ተረገጠ፡ ተገለጠ፡ ለሰለሰ፡ ለተተ፡ ደቀቀ -
ለፋ፡ ጣረ፡ ጋረ፡ ደከመ ።
ለፋለፈ፡ ቀበጣጠረ፣ ነገር፡ መላለሰ።
ለፋፊ፡ (ዎች)፡ የለፈፈ፡ የሚለፍ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፴፯") ።
ለፋፊነት፡ ለፋፊ፡ መኾን። ለፈፋ፡ የመልፈፍ፡ ኹናቴ፡ ዕወጃ መልፈፍ፡ መንገር፡ ማሰማት
ለፍላፊ፡ (ፎች)፡ የለፈለፈ፡ የሚለፈልፍ፡ ቀባጣሪ፡ የዝምታ፡ ጠላት።
ለፍላፊነት፡ ለፍላፊ፡ መኾን፡ ቀባጣሪነት ።
ለፍላፋ፡ አፈኛ፡ ተናጋሪ።
ለፍቃ፡ ለፍዳዳየሚለፋጨቅ፡ ነዝናዛ፡ ጨቅጫቃ ።
ለፍቶ፡ መና፡ ዐርሶ፡ ነግዶ፡ የማያልፍለት፡ ትርፍ፡ የለሽ ።
ለፍቶ፡ ጥሮ፡ ደክሞ።
ለፍቶ፡ ዐደር፡ እንዲሉ።
ለፎ፡ (ለፈየ)፣ አገዳ፡ መቃ፡ የግዳይ፡ መቍጠሪያ ።
ለፎ፡ ለፈቀ፣
ለፎ፡ ጀሌ፡ መደዴ፡ ወያኔ።
ሉህ ሰሌዳ፡ ሉሕ።
ሉሕ፡ (ለውሕ)፡ ልዝብ፡ ሳንቃ፡ ጠርብ፡ ሰሌዳ፡ ብራና፡ ወረቀት።
ሉሖች፡ ሳንቆች፡ ወረቀቶች።
ሉሜ፡ ላሙ ፡
ሉሜ፡ በአዳ፡ ወረዳ፡ ያለ፡ ቀበሌ ።
ሉቃሳም፡ (ሞች)፡ የሉቃስ፡ ባለሉታስ፡ ችጋራም፡ ራብተኛ፡ በልቶ፡ የማይጠግብ፡ ሥሡ፡ ገብጋባ ።ባላገር፡ ግን፡ ልቋስ፡ ልቋሳም፡ ይላል ።
ሉቃስ ፣ ከብት፡ ያለቀበትና፡ ረኃብ፡ የጸናበት፡ ጊዜ፡ ክፉ፡ ቀን፡ ይኸውም፡ ባ፲፰፻፹፩፡ ዓ፡ ም፡ ዠምሮ፡ ነው ።
ሉቃስ ፣ የሰው፡ ስም፡ ካራቱ፡ ወንጌላውያን፡ አንዱ ።ግብረ፡ ሐዋርያትንም፡ የጻፈ፡ ርሱነው፡ ቍጥሩና፡ ማዕርጉ፡ ከ፸፪ቱ አርድእት።
ሉቃስ፡ የዘመን፡ ክፍል፡ አራተኛ፡ ዓመት፡ ጳጕሜ፡ ፮፡ የምትኾንበት፡ ፬ኛነቱ፡ ለዮሐንስ፡ ነው።
ሉካንዳ፡ (ዶች)፡ የምግብ፡ ቤት፡ የመብል፡ መደብር፡ ሥጉያ ።
ሉካንዳ፡ በጣሊያንኛ፣ ሎካንዳ፡ ይባላል።
ሉክ፡ ወረቀት ሉሕ። ሉክ፡ ኰፊር።
ሉድ፡ የሴት፡ ስም።
ሉግ፡ ፲፪፡ ዕንቍላል፡ የሚይዝ፡ መስፈሪያ፡ ("ዘሌ. ፲፬፡ ፲") ።
ሊሙ፡ በጅማ፡ አውራጃ፡ የሚገኝ፡ አገር፡ ሊሙ፡ ያቅኒው፡ ስም፡ ነው ።
ሊቀ፡ ሐመር፡ የመርከብ ፡ አዛዥ ። ፈረንጆች፡ አሚራል፡ ይሉታል።
ሊቀ፡ ሀገር፡ አገረ፡ ገዢ።
ሊቀ፡ መላእክት፡ የመላእክት፡ አለቃ፡ ቅዱስ፡ ሚካኤል፡ ቅዱስ፡ ገብርኤል፡ ቅዱስ፡ ሩፋኤል ።
ሊቀ፡ መንበር፡ የጉባኤ፡ አለቃ።
ሊቀ፡ መዘምራን፡ የመዘምራን፡ አለቃ፡
ሊቀ፡ ምርፋቅ፡ የዳስ፡ ሹም፡ አሳዳሪ።
ሊቀ፡ ሰማዕታት፡ የሰማዕታት፡ አለቃ፡ ቅዱስ፡ ጊዮርጊስ።
ሊቀ፡ ካህናት፡ የካህናትአለቃ ጳጳስኤጲስቆጶስ፡ ንቡረ፡ እድ፡ ዕጨጊ ።ዳግመኛም ፣በግእዝ፡ (ሊቀ፡ ኖሎት፡ የረኞች፡ አለቃ፡ ይባላል፡
ሊቀ፡ ደብተራ፡ የደብተራ፡ አለቃ፡ መሪ፡ ጌታ፡ ወይም፡ ሌላ።
ሊቀ፡ ዲያቆን፣ የዲያቆን፡ ኣለቃ፡ ኣስተዳዳሪ። ይህ፡ ማዕርግ፡ መዠመሪያ፡ ከሐዋርያት፡ ለቅዱስ፡ እስጢፋኖስ፡ ተሰጥቷል ።
ሊቀ፡ ጠበብት፡ ያዋቆች፡ የደብዳሮች፡ አለቃ፡ የቤተ፡ ክሲያን፡ ሸም፡ ከዋናው፡ ኦ ለቃ፡ በስተግራ፡ በወንበር፡ የሚቀመጥ።
ሊቀ፡ ጳጳሳት፡ የጳጳሳት፡ አለቃ፡ ጳጳሳትን፡ የሚሾም፡ የሚሽር፡ በሮም፡ በእስክንድርያ፡ በቍስጥንጥንያ፣ በአንጾኪያ፡ ወንበርየሚቀመጥ፡ ሌላውም፣ ከበታቹ፡ ጳጳሳት፡ የሚሾም፡ ዅሉ፡ ሊቀ፡ ጳጳሳት፡ ይባላል ።
ሊቀ፡ ሊቃውንት፡ ከሊቃውንት፡ የበ
ሊቀ፡ መኳስ፡ (ሊቀ ፣ሞገስ)፡ የመወደድ፡ አለቃ፡ ጭራና፡ መነሳንስ፡ ይዞ፡ በንጉሥ፡ አጠገብ፡ የሚቆም፡ ባለል፡ የንጉሥ፡ አሳሳች፡ የባለል፡ አለቃ።
ሊቀ፡ መጣኞች፡ የይግባኝ፡ ሰሚዎችአለቃ፡ ይኸውም፡ በጐንደር፡ መንግሥት፡ ነው ።
ሊቀ፡ ምርፋቅ፡ የምርፋቅ፡ አሳራጊ፡ መነኵሴ ።
ሊቀ፡ ረድ፡ የረድ፡ አለቃ፡ እንደ፡ ደብረ፡ ሊባኖስ፡ ባለው፡ ገዳም፡ የመጋቢ፡ ምክትል፡ አዛዥ፡
ሊቃውንት ፣ ሊቆች፡ ባላገር፡ ግን፡ ሊቃውንት፡ በማለት ፈንታ- ሊቃውንቶች፡ ይላል ።
ሊቃውንት፡ ፪፡ የበገና፡ ዥማት፡ (እውታር) ።
ሊቄ፡ (ሊቅየ)፡ በቤተክሲያን፡ የማዕርግ፡ ስም፡ ከሊቃውንት፡ በትምርት፡ ብል፡ ያለውን፡ ንጉሡ፡ ሊቄ፡ ይለዋል። ሊቄ፡ በጸሎቱ፡ እንዲሉ።
ሊቅ፡ (ልሂቅ)፡ ካምሳ፡ ዓመት፡ በላይ፡ ያለ፡ ሽማግሌ፡ ዐዋቂ፣ጨዋ፡ ዐዛውንት፡ አሮጌ፡ (አረጋዊ) ።ከሊቅ፡ እስከ፡ ደቂቅ፡ እንዲሉ ።
ሊቅ፡ ምሁር፡ የተማረ፡ ትምርት፡ የጠዝበ፡ በትምርትና፡ በዕድሜ፡ የበሰለ አለቃ፡ መምር፣ ጌታ፡ ብለይና፡ ሐዲስ፡ ዐዋቂ። ፈረንጆች፡ ዶክተር፡ ይሉታል ።አፍን፡ እይ ።
ሊቅ፡ የሊቃውንት፡ መጻፍ፡ ሃይማኖተ አበው፡ አፈ፡ ወርቅ፡ ቄርሎስ፡ ኤጲፋንዮስ፡ ቅዳሴ፡ አቡ፡ ሻህር ።
ሊቅ፡ አሊቃ፡ (ግእዝ) ።
ሊቅ የተማረ፡ ላቀ ።
ሊቅነት፡ ሊቅ፡ መኾን፡ ምሁርነት፡ ዐዋቂነት፡ ፍጹም፡ ትምርት ።
ሊቆች፡ (ሊቃውንት፡ ሊቃናት)፡ እጅግ፡ የተማሩ፡ ዐዋቆች፡ መምሮች።
ሊጋባ፡ የማዕርግ፡ ስም —ገባ።
ሊጋባ (ቦች)፡ ሰውን ወደ ቤተ መንግሥት ሊያገባ (ሊአገባ) ሊያስገባ የተሾመ ያጋፋሮችና የከልካዮች የበላይ ባለሥልጣን ። ቀድሞ ዘመን ራቅ ማሰሬ ይባል ነበር ።
ሊጡ/ጠላው ቀጠነ)፡ ውሃ ኾነ ።
ሊጥ፡ በቁሙ፡ ለጠለጠ። ላጠ፡ (ልሕጸ)፡ ዛፍን፡ ገፈፈ፡ አራቈተ፡ አደረገ፡ ልጥን፡ ከቅርፊት፡ ጋራ፡ ወሰደ፡ ("ዘፍ. ፴፡ ፴፯") ።
ሊፍ፡ የሳንቃ፡ ንጣጭ፡ የባሕር፡ ዕቃ፡ መጠቅለያ።
ሊፍ፡ ንጣጭላፈ ። (ለአፈ) ፣ቅርፊትን፡ ከልጥ፡ ለየ፡ ገፈፈ ።ላፈፈን፡ ተመልከት ።
ላሑ፡ ሥሥ፡ ጠጕር፡ ከመተኛት፡ በቀር፡ መቆም፡ የማይችል፡ በጋልኛ፡ ሉጫ፡ ይባላል ።
ላሕማ፡ (ዐረለሐመ፡ መረገ)፡ መጣብቅ፡ ሙ፵፡ የደብዳቤ፡ የቀዳዳ፡ ቈርቈሮ፡ ወይም፡ ታኒካ፡ መምረጊያ፡ መድፈኛ፡ ባረብኛ፡ ልሐማ፡ ይባላል ።ሸብን፡ ተመልከት ።
ላሊበላ፡ (ሎች)፡ የነገድ፡ ስም፡ ሌሊት፡ ወየው፡ ዓለም፡ እያለ፡ ለምኖ፡ የሚበላ፡ ስለ፡ ኾነ፡ ላሊበላ፡ ተባለ። ሐባብ፡ ሌሊት፡ ሲል፡ ላሊ፡ እንዲል ("መዝ. ፩፡ ፪") ።የላሊ በላ፡ ጋብቻ፡ በየተዝካሩ፡ ቤት፡ ነው ። (ተረት)፡
ላሊበላ፡ (ላሊ፡ በላ)፡ የንጉሥ፡ ስም፡ በላስታ፡ የነገሠ፡ የኢትዮጵያ፡ ንጉሥ፡ ፲፪፡ መ ቅዶስ፡ ባንድ፡ ዋሻ፡ ውስጥ፡ ያነጸ። ላስታ፡ ላሊበላ፡ እንዲሉ ።አንዳንድ፡ ሰዎች፡ ዐጤ፡ ላሊ በላ፡ የተወለደ፡ ለት፡ በንብ፡ ስለ፡ ተከበበ፡ ማር፡ ይበላ፡ እንደ፡ ማለት፡ በአገው፡ ቋንቋ፡ ላልይበላ፡ ተባለ፡ ይላሉ።
ላሊበላ፡ ዐደራውን፡ አይበላ። ደብራሆምንና፡ ሐሚናን፡ እይ። ዐጤ፡ ላሊበላም፡ ሲጦም፡ እየዋለ፡ ማታ፡ (ሌሊት)፡ በመብላቱ፡ ላሊበላ፡ (ሌሊተ፡ በላ)፡ የተባለ፡ ይመስላል፡ ብንል፡ የተመቸ፡ ነው። ሌሊት፡ በቁሙ፡ ፡ ለየ ።
ላላ፡ አደረገ፡ በጥቂቱ፡ አላላ።
ላላ፡ አለ፡ ራስ፡ ረገብ፡ አለ፡ ላላ።
ላላ፡ (ላሕልሖ)፡ መላላት።
ላላቴ፡ ታናሽ፡ ዕብስት፡ ለስላሳ፡ ተስፋ።
ላላገ፡ ፋፋቀ፡ አለዛዘበ።
ላላጠ፡ መላልሶ፡ ላጠ።
ላሎ፡ ምድር፡ የላሎ፡ ምድር፡ ወይም፡ ርስት።
ላሎ፡ ለማ፡
ላሎ፡ የሰው፡ ስም፡ የግማሽ፡ መንዝ፡ ባላባት ።
ላመ፡ ፈጅ፡ ታላቅ፡ የብረት፡ ድስት፡ መካከለኛ፡ ጐላ ።
ላመ፡ (ልሕመ)፡ ደቀቀ፡ ተሰለቀ፡ ለዘበ፡ ለሰለሰ፡ ደከመ፡ ለፋ፡ የዶቄት፡ የሰውነት።
ላመል (ለዐመል)፡ ለልማድ (ጥቂት ") ።
ላመት፡ የሚመጣው ዓመት ።
ላሙ፡ ሲገኝ፡ ዐላቢው፡ አይገኝ ።
ላሙ፡ የላም፡ መንጋ።
ላሙ፡ ያ፡ ላም።
ላሚ፡ የሚልም፡ ለዛቢ ።
ላሚቱ፡ ያች፡ ላም፡ ("ዘኁ. ፲፱፡ ፭, ፰, ፱, ፲") ።
ላሜዳ ላይዳ ፣ላይ ።
ላሜድ፣ የፊደል፡ ስም፡ ለ፡ ትምርት፡ ወይም፡ የተማረ፡ ማለት፡ ነው።
ላም፡ ላጊ፡ ላምን፡ የሚጠባ፡ ሸሌ፡ መጠማጥ ።
ላም፡ አለ፡ ልዝብ፡ አለ፡ ላመ።
ላም፡ ዐንገት፡ ፈሪ፡ ርግብግብ።
ላም፡ አለኝ፡ (አለችኝ)፡ በሰማይ፡ ወተትም፡ አልጠጣ፡ ዐሲቡንም፡ አላይ ።የሥጋ፡ መድኀኒት፡ ላም፡ የነፍስ፡ መድኀ ኒት፡ ማርያም፡ እንዲሉ። ሲበዛ፡ ላሞች፡ ይላል፡ ("ዘ፱፡ ፫") ። ላም፡ በግእዝ፡ የወል፡ ስም፡ ስለ፡ ኾነ፡ ለተባቱም፡ ይነገራል፡ ("ምሳ. ፲፬፡ ፬") ። ላም፡ ባልዋለበት፡ ኵበት፡ ለቀማ ።
ላም፡ (ላሕም)፡ የቤት፡ እንስሳ፡ እንስት፡ የቀንድ፡ ከብት፡ የበሬ፡ ጣምራ፡ የጥጃ፡ እናት፡ የዋህ፡ ዐመለ፡ ደንሴ። እከሌ፡ ላም፡ ነው፡ እንዲሉ ። (ተረት)፡ ላም፡ የዋለችበትን፡ ትመስላለች፡ ለላም፡ ቀንዷ፡ አይከብዳትም።
ላምባ፡ (ልንጳስ)፡ መብራት፡ የሚኾን፡ የምድር፡ ዘይት፡ ጋዝ። ላምባን፡ ጋዝ፡ ማለት፡ ባረብኛ፡ ነው ።
ላምባ፡ ላምፓ (ሮማይ፡ ላምፖስ)፡ ችቦ፡ ቲሃ።
ላምዛን፡ አነባበሮ፡ ሊጡ፡ ታሽቶ፡ የተቦካ።
ላምጌ ንብጌ ዐዲስጌ ዕጨጌ (ሐፄጌ) ዐምባላጌ ዐንገትጌ ፍንጥርጌ ቅዱስጌ ራስጌ ሰላምጌ፡ የኹሉንም ትርጓሜ በየስፍራው ይመለከቷል ። ትግሬ ሐባብም አገርን ድጌ ይለዋል ።
ላሰሰ፡ (ትግ፡ ላሕሰሰ)፡ ኣብዝቶ፡ ነቀለ፡ ሰሰ፡ እሸትን፡ ጤፍን።
ላሳሽ፡ የላሰሰ፡ የሚላስስ፡ ነይ፡
ላስ፡ (ልሒስ)፡ መላስ።
ላስ፡ አደረገ፡ ፈጀ፡ ጨረሰ፡ እሳት፡
ላስ፡ አደረገ፡ ጥርግ፡ አደረገ።
ላስቲክ፡ (ኮች)፡ ፈረንጆች፡ ከንጨትደም፡ የሚሠሩት፡ ሲስቡት፡ የሚረዝም፡ ሲለቁት፡ የሚያጥር፡ ነገር፡ ነትና፡ ተንቤን፡ መሳይ፡ ሥሥና፡ ወፍራም፡ እንደ፡ ርጥብ፣ ስልቻ፡ ይነፋናለተንቀሳቃሽ፡ መኪና፡ እግር፡ ይኾናል ፣ለሌላም - ጕዳይ፣ ይገባል፡ ጠንካራው፡ ጎማ፡ ይባላል።
ላስታ፡ ላሊበላ፡ ያጤ፡ ላሊበላ፡ እግር፡ ላስታ፡ ወይም፡ የላስታው፡ ላሊበላ ።ላሊበላን፡ እይ ።
ላስቶች፡ የላስታ፡ ሰዎች፡ የላስታ፡ ተወላጆች ።
ላሸ፡ (ትግ፡ ላሸወ. ለስሐ)፡ ላላ፡ ጥብቀት፡ ዐጣ፡ ለጠ፡ የምላስ፡ የጠመንዣ፣ የወፍጮ፡ ("መክ. ፲፪፡ ፬") ።
ላሸ፡ የላሸቀ፡ ከፊል፡ ነው ።
ላሸቀ ፣ በጣም፡ ለፋ፡ ቈዳው፡ ላላ፡ ለጠ፡ ቃታው። ላሸን፡ እይ።
ላሽ፡ (ለሓሲ)፡ የላሰ፡ የሚልስ፡ ላሺ፡ ተብሎ፡ ሊጻፍም፡ ይችላል ።
ላሽ፣ ላሺት፡ መርዝ፡ ያላት፡ ታናሽ፡ ዝበሎ፡ ሳትታይ፡ ሳትሰማ፡ የራስን፡ ጠጕር፡ እየላሰች፡ ትመልጣለች፡ ይላሉ። ሐኪሞች፡ ግን፡ በደም፡ መበላሸት፡ ምክንያት፡ መኾኑን፡ ያስረዳሉ ።
ላቀ፡ (ልህቀ)፡ አደገ፡ ጐለመሰ፡ አካለ፡ መጠን ፣ እደረሰ፡ ከፍ፡ አለ፡ በለ።
ላቀ፡ ከበረ፡ ተሾመ፡ አለቃ፡ ኾነ።
ላቀ፡ አረጀ፡ ሸመገለ።
ላቀም፡ ማሰባሰብ።
ላቀቀ፡ (ዕብ፡ ላቃቅ፣ ላሰ)፡ ፈቀደ፡ መብት፡ ሰጠ፡ አሰናበተ፡ ዋስን፡ ዐግት፡ አለ።
ላቀች፡ የሴት፡ ስም፡ በለጠች፡ ማለት፡
ላቀው፡ የሰው፡ ስም፡ በለጠው፡ ማለት፡
ላቂ፡ የዟይ፡ ደሴት፡ ፭ቱ፡ ኹሉ ፣በጋልኛ፡ ቀዛፊ፡ ማለት፡ ነው።
ላቂ (ለሃቂ)፣የላቀ፡ የሚልቅ፡ የበ
ላቂያ ፣ ብልጫማ፣ ማዕርግ፡ ከፍታ።
ላቃቂ፣ የላቀቀ፡ የሚላቅቅ፣ ዳኛ።
ላቈጠ ፣ ፈጽሞ፡ ራሰ፡ ተረገጠ፡ ታሸተለወሰ ።
ላቅ፡ (ልሂቅ)፡ መላቅ ።
ላቅ፡ አለ፡ በለጥአለ ።
ላቢ)ረቢ (ረባሒ)፡ የሚወልድ/የሚበዛ/የሚረባ/የሚጠቅም (ጠቃሚ ") ።
ላተ፡ (ለዐተ)፡ ላት፡ አወጣ፡ ሠራ።
ላት ፣ (ለዐት)፡ የበግ፡ ዥራት፡ ("ፀ. ፳፬፡ ፳፪") ።
ላት፡ (ላቲ)፡ ለሩቅ፡ ሴት፡ የአንቀጽዝርዝር ።እከሊት፡ ልጇ፡ ከዘመቻ፡ ደኅና፡ ገባላት ብዙ፡ ምርኮ፡ አመጣላት። አሽከሯ፡ ውሃ፡ ቀዳላትዕንጨት፡ ሰበረላት ።
ላት፡ ላት፡ የሚመስል፡ የጐራዴ፡ እጀታዳር፡ ማገጃ ፣ኹለተኛ፡ ስው፡ ደም፡ ዐፋሽ፡ ይባላል። መክድን፡ እይ።
ላት፡ የጠመንዣ፡ ሰደፍ። (የበግ፡ ላት)፡ የቅጠል፡ ስም፡ ዠርባው፡ ነጭ፡ የኾነ፡ ገላላ፣ቅጠል ።
ላቶ) ሽቶ፡ ፈልጎ ፈቅዶ ።
ላቸው፡ (ሎሙን)፡ ለሩቆች፡ ወንዶችና፡ ሴቶች፡ የኔንቀጽ፡ ዝርዝር። ኢየሱስ፡ ክርስቶስ፡ ለእስራኤል፡ ወንጌልን፡ ሰበክላቸው፡ ዕውሮቻቸውን፡ አበራላቸው፡ የሞቱትንም፡ አስነሳቸው ።
ላችኹ፡ (ለክሙ፡ ን)፡ ለቅርቦች፡ ወንዶችና፡ ሴቶች፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር ።ነቢያት፡ ሆይ፡ ደስ፡ ይበላችኹ ፣ክርስቶስ፡ ተወለደላችኹ፡ ብርሃን፡ ተገለጠላችኹ።
ላንቍሶ፡ (ዎች)፡ ያረግ፡ ስም፡ ወፍራም፡ ዐረግ። ባላገሮች፡ በመጥረቢያ፡ እየሸነሸኑ፡ ዐጥርና፡ ግድግዳ፡ ይማግሩበታል፡ ልጡ፡ ከተልባ፡ ይልቅ፡ ይማልጋል ።
ላንቍሶ፡ የሚያለቅስ፡ ልጅ። ላንሴታ፡ (ዎች)፡ የሚዛን፡ ምላስ፡ ፍ፡ ውልብልቢት፡ በግእዝ፡ ለጽሊጽ፡ ይባላል። ኮለሌን፡ እይ ።
ላንቃ፡ ባለመደረቢያ፡ ካባ ።ካባ፡ ላንቃ፡ እንዲሉ።
ላንቃ፡ ትናጋ፡ ያፍ፡ ዋሻ፡ ላይኛው " አ ፌን፡ ስለ፡ ተጋረፈኝ፡ ላንቃዬን፡ ዐሞኛል።
ላንቃ፡ ነዲድ፡ ነበልባል፡ ውልብልቢቱ፡ ("ኢሳ. ፶፡ ፲፩") ። የእሳት፡ ላንቃ፡ እንዲሉ።
ላንቴ፡ ከፊለ፡ ስም። አንተ፡ ግባ፡ አንተ፡ ውጣ፡ አለች፣ አመነዘረች፡ ሸረሞጠች፡ ሴሰነች።
ላንት፡ ይደሩ፡ የሰው፡ ስም፡ ላንተ፡ አሽከር፡ ይኹኑ፡ ማለት፡ ነው ።
ላንት፡ (ለአንት)፡ ላንተ።
ላከ፡ (ለአከ)፡ ሰደደ፡ አመጣ፡ አወረደ ።በትና፡ ለት ሲሰማሙት፡ ላከበት፡ ላከለት፡ ይላል።
ላከ፡ ላከከ፣
ላከ፡ ምግብን፡ ወደ፡ ሆድ፡ አገባ፡ ዋጠ፡ ሰለቀጠ።
ላከከ፡ (ለሕሐ፡ ረጠበ)፡ ቀሳ፡ ደለሰ፡ ለጠፈ፡ አጣበቀ፡ ገጠመ፡ አመካኘ ።(ግጥም)፡ አበ፡ ተቈጡልኝ፡ እመ፡ ቈንጥጡልኝ፡ እሷ፡ በፈሳ ችው፡ በኔ፡ ላከከችው። ለደፈንና፡ ደፈደፈን፡ ተመልከት ።
ላኪነት፡ ላኪ፡ መኾን።
ላካኪ፡ የላከከ፡ የሚላክክ፡ ቀቢ።
ላክ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ዋላ፡ ገን ፎን፡ ፍትፍትን።
ላክ፡ (ልኢክ) ዋጥ፡ መዋጥ።
ላወሰ፡ ዞረ፡ ኳተነ፡ ለፋ፡ ደከመ። ዛሬ፡ እንዲያው፡ በከንቱ፡ ስላውስ፡ ውዬ መጣኹ።
ላዊ፡ የፊደል፡ ስም፡ ለ፡ ጠማማ፡ ቈልማማ፡ ማለት፡ ነው ።መዝገበ፡ ፊደል፡ እይ ።
ላዘነ)፡ አላዘነ)፡ በንቅልፍ፡ ልቡ፡ ጮኸ፡ አንቋረረ፡ የሰው፡ የበሬ "
ላዘገ፡ (ዘለገ)፡ እንደ፡ ላስቲክ፡ ኾነ፡ ተሳበ፡ ተጐተተ።
ላዘገን፡ ተመልከት ።
ላዙና፡ የሐሞት፡ ወርቅ፡ ከበሬ፡ ሆድ፡ የሚገኝ፡ በውስጡ፡ ወርቅ፡ ውሃ፡ ያለበት፡ ብጫ፡ የሚመስል፡ የልፋጭ፡ ከረጢት፡ በደረቀ፡ ጊዜ፡ ፈረንጆች፡ ሱካር፡ ለሚሉት፡ በሽታ፡ ከሻይ፡ ጋራ፡ እየተጠጣ፡ መድኀኒት፡ ይኾናል፡ ይላሉ ።ላዙና፡ የሚነገረው፡ በሐረርጌ፡ የሚገኘውም፡ በኦሮ፡ ቤት፡ ነው ።
ላዛ፡ ልስላሴ፡ ለስላስነት፡ የጠጕር ።
ላይ፡ ቤት፡ (የላይ፡ ቤት)፡ ደርብ፡
ላይ፡ ቤት፡ ገነትመንግሥተ፡ ሰማይ።
ላይ፡ ወደ፡ ዛፍ፡ ላይ፡ ከላይ፡ ከተራራ፡ ላይ፡ ከላይ፡ ወረደ፡ ከላይ፡ መጣ፡ ይላል። (ተረት)፡ ከራስ፡ በላይ፡ ነፋስ። እንጃን፡ ተመልከት።
ላይ፡ ቤት፣ በጐንደር፡ የነበረ፡ የጉባኤ፡ የመጻፍ፡ ትርጓሜ፡ ትምርት፡ ቤት።
ላይ፡ ቤት፡ በመራቤቴ፡ ያለ፡ ቀበሌ ።ኼደ፡ አፋፍ፡ አፋፉን፡ ላይ፡ ላዩን፡ ደጋ፡ ደጋውን፡ ዐለፈ፡ ነጐደ።
ላይ፡ (ላዕል፡ ለዐለ)፡ ደቂቅ፡ አገባብ፡ ደጋ፡ ሰማይ፡ ሽቅብ፡ ዐቀበት፡ ከፍታ፡ በታች፡ በግርጌ፡ በሥር፡ አንጻር፡ ያለ፡ ከፍተኛ፡ ስፍራ፡ ራስ፡ ራስጌ፡ ጫፍ፡ ውልብልቢት፡ በ፡ ማድረጊያ፡ ወደ፡ መገሥገሻ፡ ከ፡ መነሻ፡ ኹነው፡ ያለስምና፡ ከስም፡ ጋራ፡ በመነሻው፡ እየገቡሲነገሩ፡ በላይ፡ በሰማይ፡ ላይ፡ በሰው፡ ላይ፡ ወደ፡
ላይና፡ ታች፡ ሰማይና፡ ምድር፡ ደጋና፡ ቈላ፡ ራስጌና፡ ግርጌ።
ላይኛ፡ (ላዕላይ)፡ የላይ፡ የሰማይ፡ በላይ፡ ያለ፡ የሚኖር፡ ሲዘረዝር፡ ላይኛው፡ ይላል፡ ላይኞች፡ ደገኞች፡ በላይ፡ የሚኖሩ፡ መላእክት፡ ጻድቃን ።
ላይዳ፡ አለ፡ በላይዳ፡ እኸልን፡ ወደ፡ ላይ፡ ወረወረ፡ በተነ፡ ለነፋስ፡ ሰጠ፡ ፍሬን፡ ከገለባ፡ ለየ፡ አመረተ ።
ላይዳ፡ ላሜዳ፡ (ላዩ፡ ሜዳ)፡ ከንወት፡ የታነጸ፡ ዝርግ፡ ሾጣጣ፡ ያውድማ፡ ማንካ ።ሲበዛ፡ ላይዶች፡ ላሜዶች፡ ይላል ።ላሜዳ፡ ከለመ ደም፡ ሊወጣ፡ ይችላል።
ላዳን፡ (ኖች)፡ የመስፈሪያ፡ ስም፡ የዳውላ፡ እኩሌታ፡ ፲፡ ቍና፡ የሚይዝ፡ ቅርጫት፡ ማ ድጋ፡ እንቅብ።
ላገ፡ (ልሕገ። ትግ፡ ለሐገ፡ ላከ፡ ዐነጠ፡ ዐነጠጠ፡ ፋቀ፡ አለዘበ፡ እለሰለሰ። ልሕገ፡ ጥንታዊ፡ ዐማርኛ፡ ነው ።
ላገ፡ ሳባ፡ አጠበቀ፡ መጫኛን። ላገ፡ አማሰለ፡ ገንፎን።
ላገ፡ ዐለበ። (የረኛ፡ ግጥም)፣ የክትክታ፡ ሞፈር፡ የሚያረገው፡ እመቤቴ፡ ማሪያም፣አን ዠትኸን፡ ትላገው።
ላገ፡ ጠባ፡ ለገለገ።
ላገር በቅ፡ ያንድ ብቁ እንዲሉ ።
ላጊ፡ (ለሓጊ)፡ የላጊ፡ የሚልግ፡ ዐናጢ፡ ፋቂ፡ ጠቢ። ላም፡ ላጊ፡ እንዲሉ።
ላጊ፡ ጕንዳን፡ የጤፍን፡ ፍሬ፡ ከነገለባው፡ የሚያጠፋ፡ ኣገዳውን፡ ባዶ፡ የሚያስቀረው፡ የተ ፋቀ፡ የሚያስመስለው።
ላጠ፡ ሻረ፡ ለወጠ።
ላጠ፡ ዐማ፡ ስም፡ አጠፋ።
ላጠ፡ እንዳህያ፡ ፈሳ፡ ፈሱን፡ ለቀቀ። ላጠ፤መዘዘ፡ ጐራዴውን ።
ላጣ (ጦች)፡ የለጠ/የሚልጥ፡ ዳላጣ ወፍጮ፡ ሥራ ፈት/ማጋጣ።
ላጤ፡ መላጤ፡ ልብስ፡ ያረረበት፡ ፍጹም፡ ድኻ፡ ትፈሳ፡ ዶሮ፡ የሌለችው፡ የተላጠ፡ የተመለጠ፡ ግንድ፡ የሚመስል ።
ላጤ፡ የተላጠ፡ የተገፈፈ።
ላጤ፡ ፈሳም፡ ዕፍረተ፡ ቢስ።
ላጥ፡ አደረገ፡ በኀይል፡ ፈሳ።
ላጥ፡ ላጥ፡ አለ፡ ልጥኛ፡ ጮኸ፡ ተፈሳ።
ላጥ፡ (ልሒጽ)፡ መላጥ ።
ላጥሻ)፡ መሻር መሻር (ዕብ. ፯፡ ፲፰) ።
ላጨ ለጠጠ፡
ላጩ፡ (ላጸየ)፡ ጠጕርን፡ በምላጭ፡ ከራስ፡ ከጕንጭ፡ ካገጭ፡ ከኀፍረት፡ ላይ፡ ፈገፈገ፡ ገፈፈ፡ ጠረገ፡ አስወገደ ። (በደረቅ፡ ላፊ)፡ አታ ሰለ ።
ላጩ፡ ረባ፡ ጠቀመ፡ ውለታ፡ መለሰ።
ላጪ፡ (ጮች)፡ የላጨ፡ የሚላጭ፡ ራስ፡
ላጪ፡ የላጪን፡ ልጅ፡ ቅማል፡ በላት፡ እንዲሉ። በግእዝ፡ ላጻዪ፡ (ላጸይት)፡ ይባላል።
ላጪታ፡ (ላጻዪት)፡ የላጨች፡ የምትላጭ፡ ለሴት፡ ብቻ፡ ይነገራል ።
ላጭ፡ (ለሓጺ)፡ የላጠ፡ የሚልጥ፡ ሐሜተኛ፡ ሰው፡
ላጲስ፡ ላፒስ፡ በደረቅ፡ ርሳስ፡ የተጻፈ ጽፈት፡ ማጥፊያ፡ እውነተኛ፡ ስሙ፡ ጎማ፡ ይባላል ።ጣሊያኖች፡ ግን፡ ላፒስን፡ ርሳስ፡ ይሉታል፣ ዐማሮችም፡ ጎማውና፡ ርሳሱ፡ ባንድነት፡ ስለተገኙ፡ የጎማውን፡ ስም፡ በስሕተት፡ ለርሳሱ፡ ሰጥተውታል ።
ላፈ ፣ አቃጠለ፡ ፈጀ፡ ላጠ፡ አካልን።
ላፈ፡ በፍጥነት፡ በላ፡ ጠጣ፡ ሙቅ፡ ም
ላፈን፡ ፈጀን፡ አቃጠለን፡ ላጠን።
ላፈደ ፣ ለፋ፡ ጋጠረ፡ ደከመ ።
ላፊ ፣ የላፈ፡ የሚልፍ፡ የሚጠጣ።
ሌለ፡ (የለ)፡ የአለ፡ አሉታ፡ የየለ፡ መንትያ ። አልነበረ፡ አልተገኘ ።የና፡ ለ፡ ተወራራሽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ የለ፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ሌለ፡ ይላል። የ፡ መነሻ፡ ሲኾነው፡ በቂና፡ ቅጽል፡ ይኾናል።
ሌሊት፡ (ቶች)፡ የጨለማ፡ ስም፡
ሌላ፡ (ሎች)፡ ኹለተኛ፡ ልዩ፡ ባዳ ።
ሌላ፡ ሌላ፡ አለ፡ ጣዕም፡ ለወጠ፡ ምግቡ፡ መጠጡ ።
ሌላ፡ ነገር፡ ሌላ፡ ሰው፡ እንዲሉ።
ሌላ፡ በቀር፡ ("ዘፀ. ፲፪፡ ፴፯ ። ኢሳ. ፷፬፡ ፬ ። ፷፭፡ ፳፪") ።
ሌላኹለተኛ፡ ለየ።
ሌሌ፡ አለ፡ አዘመረ፡ በማሲንቆ፡ ዘፈነ፡ ቀነቀነ።
ሌሌ፡ ዘፋኝ፡ አመስጋኝ፡ ማለት፡ ነው ።
ሌሌ፡ (ሌለየ። ዕብ፡ ሀሎል)፡ የማሲንቆ፡ ዘፈን፡ አዝማች ።አያ፡ ሌሌ፡ ሌሌ፡ እን ዲል፡ አዝማሪ።
ሌቃ፡ በኦሮ፡ ቤት፡ ያለ፡ አገር።
ሌቃያቅኒው፡ ስም፡ ነው፡
ሌባ ሻይ ("ፈላጊ የውሸት መድኀኒት ጠጥቶ ወገበንበመቀነት ይያዝና ሌባ ይሻል ወይም ተ 700 ") ።
ሌብነት፡ ሌባ፡ መኾን፡ ሰራቂነት።
ሌቦ ቃለ አኅስሮ ("የማዋረድ ቃል ሌቦ ሣህሉ የታወቀ ሌባ በሥደር መንግሥት የነበረ አንዲት አሮጊት ሌቦ ሣህሉ እንዳይወስድብኝ ስልቻዬን ብ ቅልኝ ብትለው ወይ አለመተዋወቅ ሌቦ ሣህሉ ይሉሻል እኔ ነኝ ዕንቺ ስልቻሽ አለ ይላሉ ሌባሻይ ") ("ዮች") ።
ሌታ፡ ሌት፡ ሌሊት ለየ።
ሌታቀን፡ (ሕብረ፡ ከብድ)፡ ጕበት፡ የሚመስል፡ ግምጃ፡ የቀንና፡ የሌት፡ ኹናቴ፡(ብርሃንና፡ ጨለማ)፡ የሚታይበት ።
ሌት፡ ቀኑ፡ ሌት፡ እንደ፡ ቀን፡ የሚያይ፡ የሌት፡ ወፍ፡ ጕጕት። ሊልንና፡ ሲሎን፡ እይ፡ የዚህ፡ ዘሮች፡ ናቸው።
ሌት፡ ቀኑ፡ ያሜሪካ፡ ኣዝርና፡ ሕዝብ።
ሌት፡ ተቀን፡ ሌት፡ ከቀን፡ ጋራ ' ወ ይም፡ ሌትና፡ ቀን። እከሌ፡ ሌት፡ ተቀን፡ ይሠራል ።
ሌት፡ ሌት፡ ያማርኛ፡ ሌሊት፡ የግእዝ፡
ሌንች፡ በአካንዱራ፡ ጨዋታ፡ ጊዜየሚነገር፡ ቃል፡ ይኸውም፡ አንዲቱን፡ የልት፡
ሌዊ፡ የሰው፡ ስም፡ ካ፲፪ቱ፡ ነገደ፡ እስራኤል፡ ፩ዱ፡ ሀብተ፡ ክህነት፡ የተሰጠው፡ ትር ጓሜው፡ (ልጹቅ)፡ የቀረበ፡ ማለት፡ ነው፡ (ኪ፡ ወ፡ ክ) ።
ሌዋታን፡ ለዘበ፣
ሌዋታን፡ ያውሬ፡ ስም፡ በዓለም፡ ዙሪያ፡ በባሕር፡ በኩል፡ ተጋድማ፡ ያለች፡ እንስት፡ ዓሣ፡ ነባሪ፡ ("ኢዮ. ፵፡ ፳፭ ።ሱቱ፡ ዕዝ. ፮፡ ፵፱-፶፪")፡ ዳግመኛም፡ ዘንዶ፡ ትባላለች፡ ክፉ፡ ቀንን፡ ዙሪ ያው፡ ዘንዶ፡ ማለት፡ ከዚህ፡ የመጣ፡ ነው። ብሂሞትን፡ እይ ።
ሌዋዊ፡ (ውያን)፡ የሌዊ፡ ወገን፡ ነገድ።
ሌዋውያን፡ ካ፭ቱ፡ ኦሪት፡ ፫ኛው፡ ክ
ሌጣ፡ (ትግ፡ ሐባ፡ ብቻ)፡ ልጅ፡ የማታጠባ፡ የማታዝል፡ ሴት፡ ልጂ፡ ከዠርባዋ፡ የወረደላት።
ሌጣ፡ ወረጋ፡ ላጠ።
ሌጣ፡ ጭነት፡ ኮርቻ፡ በዠርባው፡ የሌለ፡ ፈረስ፡ በቅሎ፡ አህያ። ወረጋን፡ አስተውል።
ሌጦ፡ ቈዳ፡ ላጠ።
ሌጦ፡ የተለፋ፡ የበግ፡ ቈዳ፡ ዕላቂ፡ ጠጕሩ፡ የበነነ ።በግእዝ፡ መሊጦ፡ ይባላል፡ ስለ ዚህ፡ ዘሩ፡ መለጠ፡ ሊኾን፡ ይችላል። (እከሌ፡ ከቍንጫ፡ ሌጦ፡ ያወጣል)፡ ይቀልዳል፡ ይነቅፋል ።
ልለሳለስ፡ የሴት፡ ባሪያ፡ ስም፡
ልላጭ፡ የሽንኩርት፡ የድንች፡ ልብስ፡ ገለባ።
ልል፡ (ልእል)፡ እኔ፡ ለሚል፡ ፫ኛ፡ ዘንድ፡ አንቀጽ ።ኣልኹ፡ እል፡ እል፡ ዘንድ፡ እን ድል፡ ልል፡ እፈቅዳለኹ። አለን፡ ተመልከት።
ልመት፡ (ልሕመት)፡ ልዘባ፡ ደቃቅነት፣ ልዝብነት፡ ልስላሴ።
ልመና፡ ምልጃ፡ ጸሎት፡ መለመንፈፋ፡ ቧገታ፡ ("፩ነገ. ፰፡ ፵፭ ። ዳን. ፮፡ ፲፫ ። ኤፈ. ፲፰") ። ዛርልመና፡ ሳይያዙ፣ገና።ያንበሳ፡ ልጋማ፡ ይዞ። የልመና፣ እኽል፡ እንዲሉ።
ልመደው፡ ያሞሌ፡ ስም፡ ፪፡ አሞሌ፡ የሚያነሣ - ፩፡ አሞሌ ።
ልሙጥ፡ (ልሙጽ)፡ ጌጥ፡ የሌለው፡ የበቅሎ፡ ዕቃ፡ ዝናር ።
ልሙጥ፡ ብርሌ፡ ሰንበር፡ አልባ።
ልሙጥ፡ አለጥለት፡ የተሠራ፡ ሸማ።
ልማም፡ ሰው፡ ብዙ፡ ጊዜ፡ ሲታመምከትኵሳት፡ ብዛት፡ የተነሣ፡ በጥርሱ፡ ላይ፡ የታይ፡ እድፍ፡ ብ። ቸክን፣ ተመልከት።
ልማም፡ ያዘ፡ ለመመ፡ ቈሸሸ።
ልማት፡ ልምላሜ፡ ብጀታ፡ ብዛት ።
ልማደኛ፡ (ኞች)፡ ልማዳም፡ ባለልማድ፡ ልማድ ያለው፡ ዐመለኛ፡ ይኸውም፡ ክፉና፡ በጎ፡ ነው።
ልማድ፡ (ዶች)፡ ዐመል፡ ደንብ፡ ሕግ፡
ልማድ፡ በኀላፊ፡ አንቀጽ፡ መነሻ፡ የሚጨመር፡ ፊደል፡ እ፡ አን፡ አስ፡ አስተ፡ አሽ፡ ተ፡ ተን ።
ልማድ፡ ትንባኾ፡ ጫት፡ ቡና፡ ጠጅ፡ ዐረቄ፡ ልዩ፡ ልዩ፡መብልና፡ መጠጥ ፣በያንዳንዱ፡ ሰው፡ ዘንድ፡ ዘወትር፡ ተፈላጊ፡ የኾነ፡ ነገር፡ ኹሉ፡ ልማድ፡ ይባላል ። (ተረት)፡ ክፉ፡ ልማድ፡ ያሰርቃል፡ ከማድ።
ልም፡ ዕቃ፡ ምራን፡ የመርገጥ፡ የማነቆ፡
ልም፡ (ልሑም)፡ የላመ፡ ልዝብ፡ ልስልስ፡ የድመት፡ ጠጕር፡ ደቃቅ።
ልም፡ (ልሙዕ)፡ የለማ፡ ዐዲስ፡ ግብር፡ ባባት፡ የሌለ፡ ከተዠመረ፡ እየለማ፡ የኼደ።
ልም፡ የለማ፡ ለማ።
ልም፡ የደከመ፡ ደካማ።
ልምለማ፡ መለምለም።
ልምላሜ፡ ዝኒከማሁ፡ ጠል፡ ርጥበት፡ ለምለምነት ።
ልምምጥ፡ መለማመጥ።
ልምሹ፣ ልምሾ፡ (ዎች)፡ የለመሸ፡ ጥምልምል፡ አምልማሎ፡ እግር፡ ሽባ፡ እጀ፡ ሰላላ።
ልምሾ፡ አደረገ፡ (አዕወሰ)፡ አጥመለመለ፡ ሽባ፡ አደረገ ።
ልምሾነት፣ ልምሾ፡ መኾን፡ ሽባነት።
ልምን፡ የተለመነየተቀፈፈ የልመና፡ እኸል፡ ወይም፡ ሌላ፡ ነገር።
ልምክክ፡ አለ፡ ልክክ፡ ምርግ፡ አለ። ላመል፡ ጥቂት፡ ዐመል።
ልምክክ፡ የተለመከከ፡ የተላከከ።
ልምዘጋ፡ ቍንጠጣ፡ ቍንጥ።
ልምዝግ፡ አደረገ፡ ቍንጥጥ፡ አደረገ -
ልምዝግ፡ የተለመዘገ፣ ቍንጥጥ።
ልምድ፡ ልማድ፣ የተለመደ፡ የተጠና፡ የታወቀ፡ ዕውቅ ።
ልምጥ፡ አለ፡ ጕብጥ፡ አለ።
ልምጥምጥ፡ አለ፣ ብዙ፡ ጊዜ፡ ተለ
ልምጥምጥ፣ የተለማመጠ።
ልምጥጥ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ልምጥጥ፡ አለ፡ (ውዕየ)፡ ቅጥል፡ አለ፡ ተለመጠጠ ።
ልምጭ፡ አይነካሽ፣ የሥጋ፡ ስም፡ ጡንቻ፡ ነብሮ
ልምጭ፡ (ልብኔ)፡ የንጨት፡ ስም፡ ልጠ፡ ጥቍር፡ ዛፍ፡ እየተቀረጸ፡ መስቀል፡ ይኾናል፡ አቋቋሙ፡ ድግጣ፡ ይመስላል ።የስሙ፡ ምስጢር፡ መለመጥንና፡ መለስለስን፡ ያሳያል ።
ልምጭ፡ (ጮች)፣ ከእሓያና፡ ከወይራ፡ ከቀጨሞ፡ ከሌላውም፡ ቀጥታ፡ ካለው፡ ዕንጨት፡ የተቈረጠ፡ ቀጫጪን፡ አርጩሜ፡ አሽንቋጦ፡ ጨንገር።
ልምጭጭ፡ አለ፡ ተለመጪ።
ልምጭጭ፡ አለ፡ እንደ፡ ሙጫና፡ እንደ፡ ቅቤ፡ ኾነ፡ ሞቀሞቀ፡ ዳቦው ።
ልምጭጭ፣ የተለመፊ፣ ለጣሳ።
ልሰቃ፣ የመለሰቅ፡ ሥራ፡ ጭፈቃ።
ልሰና፡ የመለሰን፡ ሥራ፡ ልቅለቃ።
ልሳሽ፡ ለውጥ፡ ድጋሚ ።የነገር፡ ልሳሽ እንዲሉ።
ልሳሽ፣ በመስከረም፡ የታጨደውን፡ የብስ፡ ብር፡ ወዲያው፡ እየላሰሱ፡ የሚዘሩት፡ የሽን ብራና፡ የጓያ፣ ዘር።
ልሳነ፡ ምድር፡ ወደ፡ ባሕር፡ የገባ፡ የምድር፡ ሠላጤ።
ልሳነ፡ ባሕር፡ ወደ፡ የብስ፡ ወይም፡ ወዳገር፡ የገባ፡ የባሕር፡ ሠላጢ። ፈረንጆች፡ ጎልፍ፡ ይሉታል።
ልሳነ፡ ዓለም፡ መንፈስ፡ ቅዱስ፡ ያንዱን፡ ቋንቋ፡ ለሌላው፡ ገልጦ፡ የሚያናግር ።
ልሳነ፡ ዓለም፡ ሰው፡ ኩሉ፡ በያገሩ፡ የሚናገርበት፡ ቋንቋ።
ልሳነ፡ ዓለም፡ የዓለም፡ መገናኛ፡ ቋንቋ ።ከ፲፱፻፴፫፡ ዓ፡ ም፡ በፊት፡ ፈረንሳይኛ ከዚያ፡ ወዲህ፡ እንግሊዝኛ።
ልሳኑ፡ ተዘጋ፡ መናገር፡ አቃተው ዝም፡ አለ ።
ልሳን፡ ቋንቋ፡ በልሳን፡ (ምላስ)፡ የሚነግር ።ለዝማሪና፡ ለሐሚና፡ ከግእዝና፡ ካማርኛ፡ የማይገጥም፡ ሌላ፡ የምስጢር፡ ልሳን፡ አላቸው።
ልሳን፡ የመጥረቢያ፡ ጕረሮ። ይህ፡ ምሣር፡ ልሳኑ፡ ጠቧል፡ ዛቢያ፡ አያስገባም።
ልሳን፡ የሰይፍ፡ ስለት፡ ("ራእ. ፪፡ ፲፪") ።
ልሳን፡ መባል፡ የሚገባው፡ ለስለቱ፡ ነበር።
ልሳን፡(ኖች)፡ ምላስ፡ አንደበት፡ የነገር፡ ሕዋስ። እከሌ፡ ልሳኔን፡ ይዝጋው፡ ብሎ፡ ማለ።
ልሳን፡ የሚዛን፡ መርፌ ።
ልሳኖ፡ (ትግ)፡ ትርፍ፡ ምላስ ።
ልስ፡ የተላሰሰ፡ ንቅል ።
ልስለሳ፡ ልዘባ።
ልስላሴ፡ ልዝብነት ።
ልስልስ፡ አለ፡ ልዝብ፡ አለ ።
ልስስ፡ አለ፡ ንቅል፡ አለ፡ ተላሰሰ።
ልስቅ፡ አለ፡ ተለሰቀ፡
ልስቅ፡ (ልጹቅ) ቀጥ፡ ያለ።
ልስን፡ (ስም)፡ የምርግ፡ ወይም፡ የልጥፍና፡ የትምትም፡ መጨረሻሥራ ።የዚህ፡ ቤት፡ ልስኑ፡ ያምራል ።
ልስን፡ (ቅጽል)፡ የተለሰነ፡ ቅብ፡ ልቅልቅ ።
ልሻ፡ ጠጕር፣ ጠጕሩ፡ እንደ፡ ልሻ፡ ቍልቍል፡ የሚያድግ፡ ሰው።
ልሻ፡ ለስላሳ፡ ያረኸ፡ የገደል፡ ሣር፡ እ ንደ፡ ጭድ፡ ከጭቃጋራ፣ የሚስማማ፡ እንስት፡ ገርሣ ።
ልሻን፡ ሽልማት ኒሻን ።
ልሽልሽ ፣ የተለሸለሸ፡ የተኛ።
ልቍጥ፡ በርበሬ ፣ውሃ፡ የገባበት፡ ድልኸ፡ የታሸ፡ የተለወሰ።
ልቍጥ፡ የላቈጠ፡ ልውስ፡ ጭቃ፡ ሊጥ፡ መድኀኒት።
ልቍጦሽ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለልቍጥ ።
ልቃቂት፡ (ቶች)፡ ክንዝርት፡ የወጣ፡ የወለቀ፡ የተለየ፡ የድርና፡ የማግ፡ ፈትል።
ልቅ፡ ልቃቂት፡ ልቅ፡ ያኽል፡ ጐረሠእንዲሉ ።
ልቅ፡ የተለቀቀ፣ስድ፣ አግድሞ፡ አደግ መረን ።
ልቅ፡ ወጣች፡ አንድም፡ ነገር፡ ሳትካፈል፡ ሳትይዝ፡ ባዶ፡ እጇን፡ ኼደች፡ ነውረኛዪቱ፡ ሴት ላቀቀ፡
ልቅ፡ (ለቃቂ)፡ የለቀቀ፡ የተወ፡ ባዶ፡ እንዳች፡ አልባ።
ልቅ፡ ስድ ለቅዳ- ለግዳ፡ ቅምሖ ።
ልቅለቃ፡ (ልቅላቄ) ፣ የመለቅለቅ ሥራ፡ ዐጠባ፣ እስክስታ፡ ውዝዋዜ። ዋንጫ፡
ልቅሶ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ("፪ዜና. ፴፭፡ ፳፭ ። ኤር. ፱፡ ፲፰") ።በግእዝ፡ ብካይ፡ ይባላል ።
ልቅና ፣(ልህቅና)፣ዝኒ፡ ከማሁ፡ አለቃ፡ መኾን።
ልቆ፡ (ልቃሕ)፡ ብድር ።
ልቆኛ፡ ኹል፡ ጊዜ፡ የሚበደር፡ ከልቆ፡ የማይወጣ።
ልበ ቢስ፡ (ሶች)፡ ቀልበ፡ ቢስ፡ ዝንጉ ።
ልበ ብርቱ፡ የማይፈራ፡ የማይፈታ ጨካኝ ።
ልበ ክፍት፡ ብልኅ፡ ማንኛውም፡ ሥ ራና፡ ነገር፡ ቶሎ፡ የሚገባው።
ልበ ውልቅ፡ ስልቹ።
ልበ ደረቅ፡ ዐዘኔታና፡ ርኅራኄ፡ የሌ
ልበ ደንዳና፡ ዐሳብ፡ የለሽ። ሲበዛ፡ ልበ፡ ደንዳኖች፡ ይላል፡ ("ኢሳ. ፵፯፡ ፲፪") ።
ልበ ደንጊያ፡ የነገሩትን፡ የማይሰማ።
ልበ ደፋር፡ ጐበዝ፡ ኀይለኛ "
ልበ ድፍን፡ ደደብ፡ ደንቈሮ።
ልበ ጡል፡ ልቡ፡ የዞረ፡ እብድ፡ ዐይነት።
ልበ ጥኑ፡ ጨካኝ፡ ወርጅ ።
ልበ ጨካኝ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለልበ፡ ደ
ልበል፡ ዕብለት ልናገር ("ባለን" አስተውል) ።
ልበኢ፡ ልብ፡ የለሽ፡
ልቡ ተሰቀለ)፡ ባንድ ሐሳብ ተያዘ።
ልቡ ተሰበረ)፡ ፈጽሞ ዐዘነ።
ልቡ ተሰወረ)፡ አበደ (አእምሮ ጠፋ) ።
ልቡ ገባ፡ አእምሮው፡ ተመለሰ ።
ልቡሰ ሥጋ ሥጋ የለበሰ ("ጋኔን ") ("በሰው ያደረ") ።
ልቡን ሰረቀው)፡ ከዳው ነሣው ።
ልባልባ፡ (ዐልባ፡ ልብ)፡ በሐርና፡ በወርቅ፡ የተጠለፈ፡ ባለማዕርግ፡ ሴት፡ የምታጠልቀው፡ ጌጠኛ፡ ሱሪ፡ ልብ ዐልባ፡ መባሉ፡ ገንዘብ፡ የልብ፡ ሥር፡ ስለ፡ ተባለ፡ ነው ።ልብ አልባ፡ ተብሎ፡ ቢጻፍ፡ ግን፡ እሱን፡ ያጠለቀች፡
ልባም፡ (ሞች)፡ ለባዊ)፡ ልብ፡ አ ድራጊ፡ አስተዋይ፡ የማይዘነጋ፡ ዠግና፡ ሐርበኛ ።ለበመን፡ ተመልከት፡ ከዚህ፡ የወጣ፡ ቅጽላዊ፡ ግስ፡ ነው ።
ልባም ዐዋቂ ("ልበኛነት ልባምነት ልቡና/ልቦና ልብ ልብነት የልብ ማስተዋል ትግሥት ልቦና ይስጥኸ እንዲሉ። ልቡና የግእዝ ልቦና ያማርኛ ነው ለበበ ") ("ለቢብ/ለበ/ሐሰለ") ።
ልባምነት (ልባዌ)፡ ልባም፡ መኾን፡ ("ሮሜ. ፲፪፡ ፰") ።
ልባጥ የጣራ የግንብ የግድግዳ መሸፈኛ ሉሕ ግምጃ ("የሣጥን የታቦት ተለጣፊ ማዕድን ሥሥ ብላጥን እይ ተለባበጠ ተሸላለፈ መለባበጥ መሸላለፍ መለባበጫ መሸላለፊያ አላበጠ አላጠፈ አሻፈነ አላበሰ አላበጠ አሠናበጠ አላጠጠ አለባበጥ ኣለጣጠፍ አሠነባበጥ መለበዋ ለበለበ ") ("ለበበ") ።
ልብ፡ (ቦች)፡ ለበበ፡ ለበወ)፡ ከው ስጥ፡ አካላት፡ አንዱ፡ የደም፡ መመላለሻ፡ ያሳብ፡ መፍለቂያ፡ ("መዝ. ፯፡ ፱") ። አልባብን፡ ተመልከት። (ግጥም)፡ ያውና፡ እዚያ፡ ማዶ፡ ፍሪዳ፡ ተጥሏል፡ ቢላዋው፡ ደንዞ፡ ልብ፡ አልቈርጥ፡ ብሏል።
ልብ ሰጠ ("ዐ ዋቂ አደረገ አልመተ 703 ") ።
ልብ አለ፡ ዐሰበ፡ ኣስታወሰ፡ አጤነ።
ልብ አሳጣ፡ ኣፈዘዘ፡ ኣሞኘ፡ አታ
ልብ አስደረገ፡ አሳሰበ ።
ልብ አቍስል፡ ጨቅጫቃ፡ አተካራም ።
ልብ አብርድ፡ ውሃ፡ ወተት ።
ልብ አብሽቅ፡ አሳዛኝ።
ልብ አብግን፡ አናዳጅ።
ልብ አንድድ፡ ዐረቄ፡ መጥፎ፡ መጠጥ ።
ልብ አውልቅ፡ (ቆች)፡ አሰልቺ ነዝናዛ ።
ልብ አደረገ ("ዐወቀ ዐዋቂ ኾነ መተ አስተዋለ ልብን እይ መላ ለበመ ሰፈረ አዘጋጀ አሰናዳ ሠየመ መላ ለባሚ ") ("መላኢ") ።
ልብ አደረገ፡ (ለበወ)፡ አጤነ፡ በልብ፡ አዋለ አሳደረ፡ አቈየ፡ ኣኖረ። ዋለ፡ ብለኸ፡ አስተዋለን፡ እይ።
ልብ አድራጊ፡ ያየውን፡ የሰማውን፡ የተማረውን፡ የማይረሳ፡ የማይዘነጋ።
ልብ አድርቅ፡ መንቻካ፡ ሰው፡
ልብ አድርግልኝ፡ እማኝ፡ ነኸ።
ልብ አጠፋ፡ ቀልበ፡ ቢስ፡ አደረገ።
ልብ ወለድ፡ ፈጠራ፣ መጽሐፈ፡ ጨ ዋታ፡ ወዳጄ፡ ልቤ፡ ጦቢያው፡ ረቅ ።
ልብ ወረደው፣ ደከመ፡ በሬው።
ልብ ውጋት፡ ዱሮ፡ ባገራችን፡ ይሠራ፡ የነበረ፡ ችንካር፡ ምስማር፡ እንደ፡ ካስማ፡ ያለ፲ ፪ቱን፡ ፬፡ ማእዘን፡ ያገናኛል።
ልብ፡ ዕውቀት፡ ማስተዋል፡("መዝ. ፴፪፡ ፰") ።ልብ፡ ሆድ፡ ደረት ።እከሌ፡ አሽከሩን፡ በ ልቡ፡ አስተኛና፡ ገረፈው።
ልብ፡ እውነት፡ ሐቅ፡ ልብ፡ ሳይዙ፡ ነገር፡ አያበዙ።
ልብ፡ ውስጥ፡ ቡጥ። (ተረት)፡ በገዛ፡ ዳቦዬ፡ ልብ፡ ልቡን፡ ዐጣኹት።
ልብሱን፡ ለወጠ)፡ የሠርክ፡ ልብሱን፡ አስቀምጦ፡ የክት፡ ልብስ፡ አሮጌውን፡ አኑሮ፡ ዐዲስ፡ ለበሰ።
ልብድ የብረት ቀሚስ ውስጤ ነት'ያርበኛን ገላ መለበጃ ("(፩ነገ. ፳፪፡ ፴፬) ጥሩርን ተመልከት ልብደ ሠሪ ልብድን የሚሠራ የሚያበጅ የሚሰፋ አለባበድ አለጓጐም መለበድ ለበጠ ") ("ለቢጥ/ለበጠ") ።
ልት፡ (ቶች)፡ የቅጠል፡ ስም፡ ዕንጨቱ፡ ጥንካሬ፡ የሌለው፡ የደረቀ፡ ቍስል፡ የሚያለሰልስ፡ ማላጋ፡ ቅጠል፡ የታወቀ፡ ዕውቅ፡ እንደ፡ ጐመን፡ እየቀቀሉ፡ ሲበሉት፡ ለሆድ፡ መድኀኒት፡ ይኾናል።
ልት፡ ቅጠል፣ ለተተ።
ልትት፡ አለ፡ እንደ፡ ልት፡ ኾነ፡ ድክም፡ አለ፡ ባዘተ።
ልትት፡ የለተተ ።መዠመሪያው፡ ት፡ ይጠብቃል ።
ልትጥፍ ("(አንተ) ልትጥፊ ልጥፍ እወዳለኹ ልጣፍ ልትጥፉ ልንጥፍ እንወዳ ለን የሣልሱና የሳድሱ ") ("ሊ/ል") ።
ልቼ፡ (ኦሮ፡ ልምጭ)، በደብረ፡ ብርሃን፡ አጠገብ፡ ያለ፡ ቀበሌ።
ልንቅጥ፣ የተለነቀጠ፡ የተላመ፡ ሊጥ።
ልዑላን ፣ ልዑላት፡ ከፍተኞች፡ ወንችና፡ ሴቶች።
ልዑል፡ (ለዐለ)፡ የነገሥታት፡ ብላጆች፡ የታላላቆች፣መሳፍንትና፡ ባላባቶች፡ የስነ ቅጽል፡ ትርጓሜውም፡ ከፍ፡ ያለ፡ በላይ፡ የኾ፣ላይኛ፡ ከፍተኛ፡ ማለት፡ ነው ።
ልዑል፡ እምልዑላን፡ ከከፍተኞች ልቅ፡ ከፍ፡ ያለ።
ልዑል፡ ወል ወራሽ፡
ልዑል፡ መኰንን፣ መስፍነ፡ ሐረር፡ ዲሉ።
ልዕልት፡ ከፍ፡ ያለች፡ ከፍተኛዋ፡ ኵና
ልዕልና፡ ከፍታ።
ልከኛ፡ (ምጡን)፡ የልክ፡ ዐይነት፡ ልክ፡ ያለው፡ ባለልክ፡ መጠነኛ፡ እኩያ፡
ልኵስ፡ አደረገ፡ ትኵስ፡ አደረገ።
ልኵስ፡ የተለኰሰ ።
ልኵስኵስ፡ የተልኰሰኰሰ፡ መስክ፡ ዝሪት።
ልኵፍ፡ የተለኰፈ፡ ትንኰስ።
ልኵፍኵፍ፡ አለ፣ ኵልፍልፍ፡ አለ። ኰለፈን፡ እይ።
ልኵፍኵፍ፡ የተልኰፈኰፈ፡ ኵልፍልፍ።
ልክ፡ ናቸው፡ መንቶች፡ ልጆች፡ ትክክል፡ ናቸው፡ አይበላለጡም ።
ልክ፡ የለሽ፡ የሴት፡ መጠሪያ፡ ስም።
ልክ፡ የለኸ፡ የወንድ፡ መጠሪያ፡ ስም፡ ለሰውነትኸ፡ አቻ፡ ለሀብትኸ፡ ወሰን፡ የለውም፡ ማለት፡ ነው ።
ልክ፡ ነው፡ ምሉ፡ ነው፡ አልጐደለም፡ አልተረፈም ።
ልክ፡ ዐቅም፡ ቅጥብ፡ ዕለተ፡ ሞት። ሰው፡ ከልኩ፡ አያልፍም።
ልክ፡ ኾነ፡ መላ፡ ደረሰ፡ ገጠመ።
ልክ፡ መጠን፡ ስፍር፡ ("ነሐ. ፫፡ ፲፱, ፳, ፳፩") ። ሲበዛ፡ ልኮች፡ ይላል። ውሃን፡ ተመልከት።
ልክስክስ፡ (ሶች)፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ አመንዝራ፡ ርኩስ፡ ዐሣማ፡ ውሻ፡ ዝንብ ።
ልክስክስ፡ ነገር፡ የማይረባ፡ ፈሎ፡ ቢስ ።
ልክስክስ፡ አለ፡ ተልከሰከሰ ።
ልክስክስ፡ (ሰልቢባ)፡ የሚዞር፡ የሚጥወለወል፡ ባንድ፡ ስፍራ፡ ቀጥ፡ ብሎ፡ የሚቆም፡ ዐውሎ፡ ነፋስ ።
ልክና፡ መልክ፡ የሕዋሳትን፡ ኹለትነትና፡ ትክክልነት፡ አንድ፡ ዐይነት፡ መኾንን፡ ያሳያል ።
ልክክ፡ አለ፡ ግጥም፡ አለ።
ልክክ አደረገ፡ ግጥም፡ አደረገ።
ልክክ፡ የተላከከ። ፩ኛውንክ፡ አጥብቅ ።
ልክፍ፡ አለ፡ ድቅን፡ አለ፡ ተለከፈ፡ ስ
ልክፍት፡ ጥንተ፡ ደዌ፡ የበሽታ፡ ዥምር'ውጥን ።በግእዝ፡ ግን፡ የተለከፈች፡ ማለት፡ ነው፡
ልክፍክፍ፡ የተልከፈከፈ፡ የተልከሰከሰ፡ ልክስክስ፡ የውሻ፡ ያሣማ፡ ዐይነት።
ልኰሳ፡ ትኰሳ።
ልኮሽ፡ መላክ፡ እሱ፡ አንቺን፡ ልኮሽ፡ ቢል፡ ቦዝ፡ ይኾናል።
ልኰፋ፡ ትንኰሳ ።
ልወሳ፡ የማላቈጥ፡ የማዋዋድ፡ ሥራ።
ልወጣ፡ ቅየራ፡ የመለወጥ፡ ሥራ
ልውስ፡ አለ፡ ቅስቅስ፡ ንቅንቅ፡ አለ።
ልውስ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለለዋሳ፡ ቅልቅል፡ ልቍጥ፡ ሊጥ፡ ቅቤና፡ አዶስ ።
ልውጡ፡ የራስ፡ ወሌ፡ ዘዬ፡ ፈሊጥ ።
ልውጥ፡ ግልብጥ፡ እንዲሉ።
ልውጥ፡ (ውሉጥ)፡ የተለወጠ፡ ቅይር።
ልውጥ፡ አለ፡ ተለወጠ ።
ልውጥ፡ አደረገ፡ ለወጠ ።
ልውጥነት፡ ልውጥ፡ መኾን ።
ልውጥውጥ፡ አለ፡ ተለዋወጠ።
ልውጥውጥ፡ የተለዋወጠ።
ልዘባ፡ ልስለሳ ።
ልዝብ፡ ጠርብ፡ በዕቃ፡ መጥረቢያ፡ የተጠረበ፡ በመላጊያ፡ የተላገ፡ ሰፊና፡ ጠባብ፡ የን ጨት፡ ሉሕ።
ልዝብ፡ (ቦች)፡ የለዘበ፡ ልስልስ፣ልም' ደቃቅ፡ ዐይንቢጨምሩት፡ የማይቈረቍር ዶቄት፡ የድመት፡ ጠጕር፡ ሰላማዊ፡ ሰው፡
ልዝብ፡ አለ፡ ላም፡ ልስልስ፡ ድቅቅ፡ አለ፡
ልዝብ፡ ደንጊያ፡ ልሙጥ፡ የለሰለሰ፡ አለት፡ ("ኢሳ. ፶፯፡ ፮") ።
ልዝብነት፡ ልዝብ፡ መኾን ።
ልዩ፡ ልዩ፡ (ዘዘ፡ ዚኣሁ)፡ የልዩ፡ ልዩ፡ እየብቻ፡ እየብቻው፡ እየራስ፡ እየራሱ፡ እየቅል፡ እየቅሉ፡ የኾነ፡ ነገር፡
ልዩ፡ ፍጥረት፡ የሌት፡ ወፍ።
ልዩ፡ (ሊሉይ)፡ የተለየ፡ እንግዳ፡ ባዕድ፡ ከሌላው፡ የዘር፡ የልማድ፡ አንድነት፡ ኅ ብረት፡ የሌለው፡ ("ዘሌ. ፳፡ ፳፬") ። ልዩ፡ ነገር፡ ልዩ፡ ሥራ፡ እንዲሉ። የሥላሴ፡ ባሕርያቸው፡ አንድ፡ ሲኾን፡ አካላቸው፡ ልዩ፡ ነው። ሲበዛ፡ ልዩዎች፡ ይላል።
ልዩ፡ ባሕታዊ፡ ግሑሥ።
ልዩነት፡ ልዩ፡ መኾን፡ ባዕድነት።
ልያ፡ የሴት፡ ስም፡ የላባ፡ ልጅ፡ የያዕቆብ፡ ሚስት ።
ልይት፡ አለ፡ ክፍል፡ አለ፡ ተለየ።
ልይት፡ ልዩ፡ የተለየ፡ የተከፈለ።
ልይትአደረገ፡ ክፍል፡ አደረገ፡ ለየ።
ልይትይት፡ አለ፡ ንጥልጥል፡ አለ።
ልይትይት፡ የተለያየ፡ የተፈራረቀ፡ የተነጣጠለ ።
ልደተ ወልድ፡ የወልድ መወለድ ("የክርስትና ስም") ።
ልደታ፡ የታቦት፡ ስም፣ወለደ።
ልደት፡ መወለድ፡ ወለደ ።
ልዳ፡ ያገር፡ ስም፡ በእስያ፡ ውስጥ፡ ያለ፡ የጊዮርጊስ፡ አገር።
ልድፋት፡ ልጥፋት ።
ልድፍ፡ አለ፡ ልጥፍ፡ አለ፡
ልድፍ፡ ልጥፍ።
ልጅ (ጆች) (ወልድ)፡ ያራስ የጨ ቅላ የሕፃን የትንሹም የትልቁም የወንዱም የሴቱም የባሕርይ ስም ("ሰው ተወልዶ እስ ኪያድግ ድረስ የሚጠራበት አንተ ልጅ አ ንቺ ልጅ ልጅ ደረሰ ቤት ፈረሰ” እንዲሉ) ።
ልጅ፡ በቁሙ፡ ወለደ ።
ልገሳ፡ ስጦታ፡ ችሮታ፡
ልገገ (ጠገገ/ጸጐጐ)፡ ቅፍፍ አለ ("ጭጋግ ኾነ") ።
ልጕማት፡ የመለጐም፡ ስፌት፡ አኳዃን።
ልጕም፣ የተለጐመ፡ በቅሎ፡ ፈረስ፡ አህያ፡ አገልግል፡ የስፌት፡ ዕቃ፡ ጕልብ፡ ነት፡ ተንቤን፡ የለበሰ ።
ልጕድ፡ የተለጐደ፡ ልድፍ።
ልጋጋም፡ (ሞች)፡ ለሐጫም።
ልጋግ፡ (ሠወን)፡ ለሐጭ፡ እንደ፡ ድር፡ ያለ፡ ካፍ፡ ካንጓ፡ የሚወጣ፡ ("፩ሳሙ. ፳፩፡ ፲፫") ።
ልግ፡ (ልጉዕ)፡ የተለጋ፡ የተቀላ፡ ጥ
ልግስና፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ቸርነት፡ ("፪ቆሮ. ፱፡ ፲፩ ።፩ጢሞ. ፮፡ ፲፯") ።
ልግዕ፡ (ትግ፡ ልግዒ)፡ እንገር፡ ዐዲስ፡ ወተት " ልግዕ፡ ለግእዝም፡ ሊኾን፡ ይችላል ።
ልግድ፡ የተለገደ፡ በፈፋ፡ መካከል፡ የተቀረቀረ፡ ቋጥኝ፡ ገለብ ።
ልጐማ፡ የመለጐም፡ ሥራ።
ልጎሽ፡ ንጣጭ፡ ሊፍ፡ የሳንቃ፡ የማእ ዘን፡ ፍቄት።
ልጓም፡ (ሞች) የከብት፡ አፍ፡ መዝጊያ፡ እንዳይኼድ፡ እንዳይበላ፡ መከልከያ፡ መግቻ፡ መመለሻ፡ ("ምሳ. ፳፮፡ ፫") ። (ተረት)፡ ጠፍር፡ በሊታ፡ ብትኼድ፡ ልጓም፡ በሊታ፡ መጣች ።
ልጓም፡ ለቀቀ፡ በቀላል፡ ያዘ፡ ጨበጠ።
ልጓም፡ አላላ፡ ወደ፡ ፊት፡ ያዘ፡ ሽምጥ፡ ለመጋለብ ።
ልጓም፡ አወለቀ፡ ከፈረስ፡ ከበቅሎ፡ አፍ፡ አወጣ።
ልጓም፡ አጥባቂ፡ ልጓምን፡ ዐኝ፡ እያለ፡ ሽምጥ፡ የሚጋልብ፡ ("፪ዜና. ፳፰፡ ፲፱") ።
ልጓም፡ ጣሰ፡ አልመለስ፡ አልገታ፡ አለ፡ ፈረሱ።
ልጡ፡ የተራሰ፡ መቃብሩ፡ የተማሰ፡ በጣም፡ ያረጀ - ያፈጀ - የደከመ፡ ሽማግሌ ።
ልጣም፣ ብዙ፡ ልጥ፡ የሚወጣው፡ ዛፍ። ለጠመን፡ ተመልከት።
ልጣጭ፡ ሥንባጭ፡ ንጣይ፡ የልጥ፡ ዐይነት፡ ዕንጨት፡ ትርፍ፡ ድር ።
ልጥ፡ (ጦች)፡ ልሕጽ)፡ በቂዳ፡ እም ሳል፡ ከንጨት፡ ኹሉ፡ ላይ፡ የሚገፈፍ፡ በቅርፊት፡ ውስጥ፡ ያለ፡ ማሰሪያ፡ የሚኾን ።የሺ - ፍልጥ፡ ማሰሪያው፡ ልጥ፡ እንዲሉ ።
ልጥለጣ፡ የመለጥለጥ፡ ሥራ፡ ወቀጣ፡ ጥ ፍጠፋ።
ልጥቅ፡ አለ፡ እጅጉ፡ ጥቂት፡ መሰለ።
ልጥጥ፡ የተለጠጠ፡ የተነጠለ፡ ንጥል፡ የተቈነነ፡ ቍንን።
ልጥፋት ሽፍ ናት ("") ("ኢሳ. ፴፡ ፳፪") ።
ልጦ፡ ጕርዶ፡ ጕርዶ፡ እንቅጥቃጭ፡ ልጦ፡ እንዳለፈው። ስንዴ፡ እንደ፡ ቀይ፣ ሽንርት፡ ተልጦ፡ የሚያልቅ፡ ስለ፡ ኾነ፡ ንፋሹ፡ ልጦ፡ ተባለ። ኅዕቦን፡ እይ።
ልጦ፡ ጕርዶ፡ አወጣ፡ ፈተግ አነፈሰ፡ አበጠረ ።
ልጦ፡ የፍትግ፡ ስንዴ፡ እብቅ፡ ገለባ፡
ልጨኛ፡ (ኞች)፡ ልጭ፡ አድራጊ፡ ባለ ልጭ፡ ውለታ፡ ከፋይ።
ልጨኛነት፡ ልጨኛ፡ መኾን።
ልጩ፡ (ልጹይ)፡ የተላጨ፡ ጠጕሩ፡ የተጠረገ፡ ጐፈሬ፡ የሌለው። ከጨርቅ፡ ነጩ፡ ከበራ፡ ልጩ፡ እንዲሉ ።
ልጩ፡ (ትግ)፡ አጫዋች፡ ድንክ፡ ሰው፡
ልጭ፡ ረብ፡ ጥቅም፡ ወረታ፡ ውለታ ።
ልጭታት፡ የመላጨት፡ ኹናቴ አኳዃን። (ጥላ)መላጨት፡ መጠረግ፡ መወገድ፡ መው ደቅ፡ የጠጕር።
ልፊያ፣ የጨዋታ፡ ምት፡ ቍልመማ ።
ልፋም፡ ልፋጭ፡ ያለው፡ ባለልፋጭ፡
ልፋት፡ (ልፍዐት)፡ ጥረት፡ ድካም። አማረን፡ አስተውል።
ልፋጭ፡ ንፍጥ፡ መሳይ፡ ሥጋ ።
ልፍ፡ (ልፉዕ)፡ የለፋ፣የተለፋ፡ ደበሎ፡ ስልቻ፡ ቈርበት።
ልፍለፋ፡ የነገር፡ ብዛት።
ልፍት፡ አለ፡ ድክም፡ አለ።
ልፍት፡ ድክም።
ልፍጥ፡ (ልፉጽ)፣ የተለፈጠ፡ ልውስ።
ሎላልት፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ("ኢሳ. ፲፬፡ ፪ ። ዮሐ. ፯፡ ፵፭, ፵፮") ።
ሎሌ፡ በትን፡ ታናሽ፡ ዋንጫ።
ሎሌ፡ (ወዓሊ)፡ ምንደኛ፡ ታዛዥ፡ አሽከር ። (ተረት)፡ ቅልና፡ ድንጋይ፡ ተማቶ፡ ሎሌና፡ ጌታ፡ ተግቶ።
ሎሌነት፡ ሎሌ፡ መኾን፡ ምንደኛነት፡ አሽከርነት ።
ሎሌዎች፡ (ወዐልት)፡ ምንደኞች፡ ታ
ሎል፡ (ልዑል)፡ የታላቅ፡ ዛፍ፡ ስም፡ ዕንጨትነቱ፡ ክብደት፡ ያለው፡ በጊዜው፡ ከተቈረጠ፡ ጽላት፡ ይኾናል ።ሲበዛ፡ ሎሎች፡ ይላል ።
ሎሚ፡ (ዎች)፡ ለመለመ)፡ የተክል፡ ስም፡ የታወቀ፡ ተክል፡ ሽታው፡ የሚጣፍጥ፡ ለሥራይና፡ ለመርዝ፡ መድኀኒት፡ የሚኾን፡ ዕንጨቱም፡ ፍሬውም፡ ሎሚ፡ ይባላል። (ተረት)፡ ፶፡ ሎሚ፡ ላ፩፡ ሰው፡ ሸክም፡ ነው፡ ላ፶፡ ሰው፡ ጌጥ፡ ነው። በከረን፡ እይ። በትግሪኛ፡ ግን፡ ሎሚ፡ ዛሬ፡ ማለት፡ ነው፡ ዮማዊ፡ እንደ፡ ማለት ።
ሎሚታ፡ (ዎች)፡ እንደ፡ ሎሚ፡ ክብ፡ ኹኖ፡ የሚታይ፡ ጕልበት።
ሎሚታ፡ በሙጣ፡ ጫፍ፡ ላይ፡ ያለ፡ ፩፡ ወይም፡ ፪፡ የብር፡ እንክብል።
ሎሚናት፡ መጠጥ፣፡(ጥሸ)ለመሸ፡ (ፀወሰ)፡ ተጥመለመለ፡ ሽባ ' ኾነ ፣ ሰለለ።
ሎሚናት፡ ከሎሚ፡ የሚወጣ፡ መጠጥ፡ ፈረንጆች፡ ሎሚናድ፡ ይሉታል፡ በግእዝም፡ ሎሚዎች፡ ማለት፡ ነው ።
ሎም፡ ሎም፡ አለ፡ ላላ፡ እንደ፡ ሎሚ፡ ኾነ።
ሎምቢ፡ ያሣ፡ ስም፡ ጌታችን፡ ከሰባት፡ እንጀራ፡ ጋራ፡ ፬፡ ሺሕ፡ ሰው፡ ያጠገበበት፡ ዓሣ፡ ("ማቴ. ፲፭፡ ፴፬, ፴፭") ።
ሎቲ፡ (ዎች)፡ ከወርቅና፡ ክብር፡ ከንሓስ፡ ከሌላም ፣ማዕድን፡ ከዝኆን፡ ጥርስና፡ ካውራሪሥ፡ ቀንድ፡ የተበጀ፡ ሰፊ፡ ቀለበት፡ አንበሳ፡ ዝኆን፡ ግስላ፡ አውራሪ፡ ጉዳይ፡ በዦሮው፡ የሚያንጠለጥለው።
ሎቲጋልኛ፡ ነው ።
ሎክሎክ፡ አለ፡ (ላሕልሐ)፡ ላላ፡ ከመጠጠር፡ ራቀ፡ ፍሬው፡ ዕባጩ ።
ሎክሏካ፡ ልል።
ሎዛ፡ ያገር፡ ስም፡ በፍልስጥኤም፡ ያለ፡ አገር፡ ያዕቆብ፡ በሕልሙ፡ ከምድር፡ እስኪ፡ ሰማይ፡ የተተከለ፡ መሰላል፡ ያየባት፡ ምድረ፡ ለውዝ፡
ሎዜ፡ ገብሩ፡ ባጤ፡ ቴዎድሮስ፡ ዘመን፡ በጐንደር፡ የነበሩ፡ ያሬዳዊ፡ ሊቅ።
ሎዜ፡ ለውዛዊ፡ ዘለውዝ፡ በዓለ፡ ለውዝ ፣የለውዝ፡ ባለለውዝ ።
ሎጋ፡ (ሊወጋ)፡ ረዥምና፡ ጠንካራ፡ ጦር፡ ከነሶማያው።
ሎጋ፡ ቁመተ፡ ረዥም፡ ሰው፡
ሎጋው፡ ሽቦ፣ የጦረኛና፡ የሐርበኛ፡ ዘፈን፡ ሽቦ፡ ያለበት፡ የተጠመጠመበት፡ ባለሽቦ፡ ሎጋ፡ ማለት፡ ነው ።ሎጋው፡ ሽቦ፡ አመጣው፡ ስቦ፡ እንዲሉ ።
ሎጋው ሽቦ)፡ በጦር ጕረሮ ላይ ያለ ሽቦ፡ "ሎጋ" የተባለ ጦሩ ነው ።
ሎጤቀላዋጭ፡ ሎጠሎጥ።
ሎጥ፡ የሰው፡ ስም፡ የአብርሃም፡ ወንድም ።
ሎፌ፡ (ለአፈ)፡ ሎጤ፡ ቀላዋጭ።
ሎፍ፡ አለ፡ ሰለፈ፡ ቀረበ፡ ተደቀነ። ሎፊሳን፡ ተመልከት ።
ሎፍ፣ ድቅን።
ሏ ("(ሎልዎ) መቃጠል ሏ ") ("ሎለወ") ።
ለ በን ፈንታ እየተነገረ ገቢር ተ ሳቢ ይኾናል ("ጨለማው ላይን ያዘ ለ ፮፻፺፱ ኸን ") ("ከነ") ።
ለሐም፡ ለሐጪ፡ ብዙ፡ ሰው፡ ባለለሐጭ፡ ላንቍሶ፡ አውሬ፡ እንስሳ ።
ለኈሳስ፡ ሹክታ።
ለኈሳስ፡ ላጪ፡
ለሐጭ፡ (ልሕጸ)፡ ቀጪን፡ ምራቅ፡ ካፍ፡ እየወጣ፡ የሚፈስ። ልጋግን፡ እይ።
ለሐፍ፡ (ዐረ)፡ ጥሩ፡ የላይ፡ ልብስ፡ መደረቢያ፡ ባለዘርፍ፡ ምንጣፍ፡ ("ምሳ. ፯፡ ፲፮") ።
ለላመት (ለዓመት)፡ ዝኒ ከማሁ ("ለ
ለመለመ፣ (ለምለመ)፡ ጠደቀ፡ አቀጠለ፡ ለጋ፡ ኾነ፡ ጀፈጀፈ፡ ("ዘኁ. ፲፡ ፯, ፰ ። ማር. ፲፫፡ ፳፰") ።መለመለን፡ እይ፡ ፈጠፈጠንና፡ ቈጠቈጠን፡ ተመልከት።
ለመመ፡ ደገደገ፡ እደፈ።
ለመነ፡ ማለደ፡ ስጦታ፡ ጠየቀ፡ ስጡኝአድርጉልኝ፡ ሥሩልኝ፡ አብሉኝ፡ አጠጡኝአብሱኝ፡ ችሩኝ፡ እለ፡ አባበለ፡ እሽበለበለ፡ ቀፈፈቧገተ ። (ተረት)፡ የለመነ፡ መነመነ ። (ሹም ፣መነ)፣አዘዘ ።ጸለየን፡ እይ ።
ለመከከ፡ መረገ፡ ቀባ፡ ላከከ።
ለመዘ፡ ጠመዘዘ፡ ፈተለ ።
ለመዘገ፡ አጥብቆ፡ ቈነጠጠ።
ለመደ፡ (ለሚድ፡ ለመደ)፡ ተማረ፡ ደገመ፡ አጠና፡ ያዘ፡ ተስማማ፡ ዐወቀ፡ (ጎባው)፡ ባንድ፡ ሥራ፡ ላይ፡ ሠለጠነ። ጽፈት፡ ለመደ፡ ኣገር፡ ለመደ፡ እንዲሉ።
ለመደ፡ ለምድ፡ አበጀ፡ ሰፋ።
ለመደች፡ ከባሏ፡ ተስማማች። (ግጥም)፡ እከሊት፡ ለምዳለች፡ እንዝርቴን፡ ደጋኔን፡ አምጡልኝ፡ ብላለች ።
ለመገገ፡ ሳበ፡ ጐተተ፡ ጠባ።
ለመጠ፡ እነጣ፡ ለምጥ፡ እወጣ፡ የተላ፡ ዕንጨት፡ አስመሰለ ።
ለመጠ፡ ፈገፈገ፡ ሳለ፡ አሰላ፡ ምላጭንበጠፍር - ኣለዘበ፡ ኣለሰለሰ።
ለመጠ ለመጠጠ፡
ለመጠ፡ (ለመጸ)፡ ለማጣ፡ አደረገ፡ ኦጐበጠ፡ አሀባ፡ ኦዘበጠ፡ አደራ፡ ጣራን፡ ወገብን ዕንጨትን፡ ብረትን፣ ማንኛውንም፡ ነገር።
ለመጠ፡ ለጠጠ፡ ቈነነ። ምን ፡ ይለምና ኻል፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ና።
ለመጠጠ፡ ፈጀ፡ አቃጠለ፡ ለቈጠጠ፡ ገረፈ፡ አሰፋ።
ለመጥ፡ ለመጥ፡ ቈነን፡ ቈነን።
ለመጥ፡ አለ፣ ተለመጠ።
ለመጥ፡ መለመጥ።
ለመጮ፣ ለጠሰ፡ አስተኛ
ለመጯ ጯ፡ አሞቀሞቀ።
ለሚ፡ የሚለማ፡ የሚለመልም።
ለማ፡ የሰው፡ ስም።
ለማ፡ (ለምዐ)፡ ለመለመ፡ በጀ፡ ሰመረ፡ በዛ፡ አዝመራው ("ኢሳ. ፲፫፡ ፳") ። (ተረት)፡ ከለማበት፡ የተጋባበት ።የጠፋ፡ ዐዳር፡ ከለማ፡ አንድ፡ ነው ።ለሰው፡ ብትል፡ ትጠፋለኸ፡ ለግዜር፡ ብትል፡ ትለማለኸ።
ለማ፡ በራ፡ ገነነ፡ መብራቱ።
ለማልሞ፡ ወጣት፡ ጐበዝ።
ለማልሞ፡ ከበጌምድር፡ ወደ፡ ስሜን፡ መው፡ ረዥም፡ ገደል፡
ለማመጠ፡ አጐባበጠ ፣ሳሳለ ።
ለማን፡ ዐዝና፡ ላንፋ፡
ለማን፡ ዐዝና፣ የኮከብ፡ ስም ሎሚ፡
ለማኝ፡ (ኞች)፡ የለመነ፡ የሚለምንድኻ፡ ቀፋፊ፡ ቧጋች፡ (ተረት)፡ የለማኝ፡ ለማ ቍረንጮዬን፡ ቀማኝ።
ለማኝ፡ ሳያራ፡ ማለዳ፡ ጧት። እከለማኝ፡ ሳያራ፡ መጣ ።
ለማኝነት፡ ለማኝ፡ መኾን ።
ለማዳ፡ (ዶች)፡ የለመደ፡ የሚለምድ፡ የቤት፡ አውሬ፡ ሰዎች፡ ከዱር፡ ይዘው፡ ወደ፡ ቤት፡ ያመጡት።
ለማጣልምጥ፡ የተለመጠ፣የደራ፡ ድር፡
ለማጭ ፣ የለመጠ፡ የሚለምጥ፡ አዝቢ፡ አ
ለም ።
ለም፡ መሬት፡ ለም፡ ከጠፍ፡ እንዲሉ ።ለምጨቅን፡ ተመልከት ።
ለም፡ (ለምዕ)፡ ለምለም፡ የቀና፡ የለማ፡ መሬት፡ እኸልና፡ ተክል፡ የሚኾን፡ ባለመስኖ፡ (የካህናትና የመኳንንትርስት አብዛኛው) ።
ለምለም፡ ምላስ፡ ደረቅ፡ ያይዶለ፡ ዐጥንት፡ ጕልጥምት፡ የለሽ። በለምለም፡ ምላሱ፡ በሠላሳ፡ ጥርሱ፡ እንዲሉ።
ለምለም፡ (ሞች)፡ የለመለመ፡ ለጋ፡ ቅጠል፡ ርጥብ፡ ሣር፡ እንግ፵፡ ቀጤማ፡ ቀንበጥ፡ እንቦቀቅላ፡ የመሰለው፡ ኹሉ።
ለምለም፡ ፍ∶፡ እንጀራ፡ ወዛም ፣ለስላሳ፣ ማለት፡ ነው።
ለምለምነት፡ ለምለም፡ መኾን።
ለምላሚ፡ የሚለመልም፡ ጠዳቂ።
ለምዛጊ፣ የለመዘዝ፡ የሚለመዝግ፡ ቈን
ለምደኛ፡ የለምድ፡ ዐይነት፡ ከወደ፡ መ ላበሻው፡ በክር፡ የተጋጠመ፡ ዐንገት፡ ልብስ።
ለምደኛ፡ ለምዳም፡ ባለለምድ፡ ለምደ፡ ለባሽ ።
ለምድ፡ (ዶች)፡ ከግምጃ፡ ከሐር፡ ከተለፋ፡ ያንበሳ፡ የነብር፡ የግስላ፡ ቈዳ፡ በደበሎ፡ ዐይነት፡ ተበጅቶ፡ የተሰፋ፡ የጦር፡ ሰራዊት፡ መደረቢያ፡ ልብስ፡ ከጥንት፡ ዠምሮ፡ የተለመደ።
ለምድ፡ አወጣ፡ ገፈፈ።
ለምድ፡ ያንቀልባ፡ ዐይነት፡ አንቀልባ። የታዘለ፡ በለምድ፡ የተረገዘ፡ በሆድ፡ እንዲሉ።
ለምድ፡ ደበሎ፡ ("ማቴ. ፯፡ ፲፭") ። (ተረት)፡ መናጆ፡ የሌለው፡ በሬ፡ ለምድ፡ የሌለው፡ ገበሬ።
ለምድ፡ የፍየል፡ ቈዳ፡ ("ዘፍ. ፳፯፡ ፲፮") ።
ለምዶ፡ ዝላይ፡ ከቅጠል፡ ላይ፡ ልጃገረዶች፡ ወደ፡ ፊትና፡ ወደ፡ ኋላ፡ እየዘለሉ፡ የፋሲካና፡ የገና፡ ለት፡ የሚጫወቱት፡ የባላገር፡ ጨዋታ፣ከጥንት፡ ካባት፡ የቈየ፡ የተለመደ ።ኣንደርዶን፡ ተመልከት ።
ለምዶ፡ ተምሮ፡ ዐውቆ።
ለምጣም፡ (ሞች)፡ ለምጥ፡ የወጣበት ያለበት፡ ባለለምጥ።
ለምጣጭ፡ የለመጠጠ፡ የሚለመጥጥ፣ አቃጣይ፡ ገራፊ ።
ለምጥ፡ (ለምጽ)፡ የበሽታ፡ ስም፣ ገላንነጭ፡ የሚያደርግ፡ ርኩስ፡ በሽታ ።
ለምጦ፡ ኣፉና፡ አፍንጫው፡ ለምጥ፡ የሚመስል፡ ፈረስ።
ለምጨቅ፡ (ለም፡ ጭቃ)፣ሣርና፡ ጭቃ - ጨቆ፣ ጨቀጨቅ ።
ለሞት ተሰጠ)፡ "ይሞት በቃ" ተባለ፡ ዐለፈ።
ለሰሰ፡ ላበ፡ ሞቀ፡ በጥቂቱ።
ለሰስ፡ አለ፣ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለሰቀ (ለጸቀ)፡ ለጠቀ፡ ለጥ፡ ቀጥ፡ አደረገ፡ ጨፈቀ፡ አጣበቀ፡ እያያዘ፡ ርጥብ፣ ጨፈቃን ።
ለሠቀ፡ ለጥ፡ አደረገ፡ ለሰቀ
ለሰነ፣ (ለስኖ፡ ለሰነ)፡ ነገረ፡ ተናገረ፡ (ግእዝ) ።
ለሰነ፡ ምርግን፡ ወይም፡ ልጥፍን፡ ትምትምን፡ ጕርዖን፡ በብዙ፡ ጭድና፡ በቀጪን፡ ጭቃ፡ ለቀለቀ፡ በንፊት፡ ሉሕ፡ ዐሸ፡ ዐሠሠ፡ አስተካ ከለ። ለሰነ፡ በግእዝ፡ ብሰሰ፡ ይባላል ።
ለሳቂ፡ የለሰቀ፡ የሚለስቅ፡ ፋቂ።
ለሳኝ፡ (ኞች)፡ የለሰነ፡ የሚለስን፡ ልስን፡ ዐዋቂ።
ለሳኝነት፡ ለሳኝ፣ መኾን።
ለሴ፡ ሙቀት፡ ያለው፡ ጢብኛ፡ ለከት፡ ሙልሙል። (ተረት)፡ ለመነኵሴ፡ መልካም፡ ለሴ።
ለስ፡ አለ፡ ለብ፡ አለ፡
ለስላሳ፡ ልስልስ፡ የለሰለሰ፡ የለዘበ፡ ልዝብ፡ ("ዘፍ. ፳፯፡ ፲፩, ፲፯") ።ባዘቶ፡ የድመት፡ ጕር ።ዐመልን፡ እይ ።
ለስላሳነት፡ ለስላሳ፡ መኾን ።
ለስላሽ፡ የሚለሰልስ ፣ለዛቢ ።
ለስታ፡ ቅቤ፡ ለጋና፡ ትኩስ፡ ቅቤ
ለስታ፡ ትኵስ፦ለሰሰ ።ላስታ ፣ያገር፡ ስም፡ በየጁ፡ ኣጠገብ ፣ያለ፡ አገር ።
ለስታ፡ (ለስድ)፣ ለብታ፡ ሙቀት።
ለሩቅ ሴት የአን ቀጽ ዝርዝር ("አንተ እሷን ገደልኻት ኻች ካች ") ("ከተተ") ።
ለሩቅ ወንድ የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ እሱን ባረክኹት መረቅኹት ኻት ") ("ካ/ሃ") ።
ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽ ዝርዝር ("አንተ እነሱን መረ ቅኻቸው ሊ እሱ እነሱ በተባሉት ሰራዊት እየገባ ከእንዲ በኋላ የዘንድ አንቀጽ ኹሉ መነሻ ይኾናል ሊማር ይወዳል ሲማሩ ይወዳሉ ሊበሉት ያሰቡትን አሞራ ስሙን ይሉታል ዥግራ ላ በስም መጨረሻ እየተጨመረ ቅጽልና አንቀጽ ይኾናል ") ።
ለሸለሸ፡ ለሰነ፡
ለሸለሸ፣ ጣለ፡ አወደቀ፡ አጋደመ፡ ፈጽሞ፡ ኣስተኛ፡ ረፈረፈ። የኅዳርበሽታ፡ ሰዉን፡ ኹሉ፡ ለሸለሸው ።
ለሽ፡ አለ፡ ትኝት፡ አለ፡ በደረቱ።
ለቀለቀ ፣ (ለቅለቀ)፡ በዘይት፡ በቅቤ፡ በቀለም፡ በበረቅ፡ በኖራ፡ በበት፡ ቀባ ።እከሊት፡ እበት፡ ይዛ፡ የሰው፡ ቤት፡ ትለቀልቃለች፡ እንዲሉ ።
ለቀለቀ ፣ ቀላልና፡ መጨረሻ፡ ዕጥበትዐጠበ፡ አጠራ፡ አጸዳ ። (ተረት)፡ ጋን፡ ቢለቀልቁት፡ ምንቸት፡ ይመላል።
ለቀለቀ ፣ አሳበጠ፡ ገጠመ፡ ጕረሮን፡ አበዛ፡ ድንኳንን።
ለቀለቀ፡ ወዘወዘ፡ አስጨፈረ።
ለቀመ ፡
ለቀምት፡ የከተማ፡ ስም፡ ነቀምት።
ለቀቀ ፣ ሰደደ፡ ፈታ፡ አወጣ፡ አወለቀኣፈሰሰ፡ ከፈተ፡ ተወ፡ ("ዘፀ. ፲፩፡ ፲ ።ኤር. ፵፰፡ ፳፰ ሕዝ. ፰፡ ፲፪") ። ሚስቱን፡ ለቀቀ፡ ከብቱን፡ ለቀቀልቃቂት፡ ለቀቀ፡ ሽንቱን፡ ለቀቀ፡ አፉን፡ ለቃ ስፍራውን፡ ለቀቀ፡ እንዲሉ። ለመ፡ ብለኽ ልጓምን፡ እይ ።
ለቀቀ፡ ነጻ፡ አደረ፡ ፡ አሰናበተ፡ ባሪያ፥ለቃቂ፡ የለቀቀ የሚለቅፈቺ ከፋች አሰናባች ።
ለቀቅ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ለቀቀ።
ለቀጠ፡ የለነቀጠ፡ ሥር። ቀለጠ፡ ተውሮ፡ ለቀጠ፡ ተብሏል ።
ለቃቃ፡ (ስፉሕ)،ከፋታ፡ አፈ፡ ስፊእንስራ፡ ማድጋ ። (ግጥም)፡ ተገፍቶ፡ ተገፍቶ በታላቅ፡ ለቃቃ፡ ካሳ፡ ሽፍታ፡ ኾነ፡ ለራስ፡ የሚበቃ ።
ለቄታ፡ ለሰለሰ፣
ለቈታ፡ (ሕግ)፡ ስልቻ፡ አቍማዳ። ለሴ፡ ጢብኛ፡- ለሰሰ። ለስ፡ አለ፡ ለብ፡ አለ፡- ለሰሰ። ላሰ፡ (ለሐሰ)፡ ምላስ፡ ጠረገ፡ አጠዳ፡ በላ፡ ተመገበ። እከሌ፡ በጣም፡ ጠግቧል- ማርም፡ ኣይልስ ። (እሳት፡ የላሰ፡ ተንጠልባ፡ የማያናግር። ላሰ፡ አቃጠለ፡
ለቈደ፡ (ለቀደ፡ ያዘ) ድዳ፡ ለንባዳ፡ አደረገ፡ ትክክል፡ መናገር፡ ከለከለ፡ ኣፍ፡ ያዘ ።
ለቈጠጠ፡ ባረፈ፡ ቈነደደ፡ ፈጀ፡ እቃ
ለቅ፡ ዝኒከማሁ፡ የሚያሾልክ ።ወፍን ለቀቃ ፡ ከፈታ፡ መልቀቅ ።ለቀቅ፡ ተወት ።
ለቅላቂ፡ (ዎች)፡ የለቀለቀ፡ የሚለቅልቅ ፣ ቀቢ፡ ዐጣቢ።
ለቅሶ ፣ ሐዘን፡ ትካዜ፡ ቍዘማ፡ ሙሾ፡ የንባ፡ መመንጨት፡ መፍሰስ መውረድ። (ተረት)፡ እንደ፡ ነደደች፡ ተነሥታ፡ የሰው፡ ለቅሶ፡ አጠፋች።
ለቅሶኛ (ኞች)፡ ባለለቅሶ፡ እለቅሶ፡ ቤት፡ ኻያጅ፡ የሬሳ፡ ዐጀብ።
ለቅርብ ሴት የአንቀጽ ዝርዝር ("እኔ አንቺን አሰርኹሽ ተበተብኹሽ ወደድኩሽ ጠላኹሽ ኹት ") ("ክዎ") ።
ለቆ፡ ዐዘል፡ ለቆ፡ ያዘለ፡ ደረቅ፡ የበልግ፡ ሣር ።
ለቆ፡ (ዎች)፡ ለቀወ፡ የሣር፡ ል
ለቆ፡ ላቀ ፣
ለቋዳ ፣ ልቍድ፡ የተለቈደአፈ፡ እስር።
ለበሰ፡ ለጋ፡
ለበሳ መልበስ ("ልብስ ") ("ሶች") ።
ለበስ አለ ("ወፈር አለ ሸማው ልቡስ የለበሰ ") ("ግእዝ") ።
ለበን፡ ለበሰ፡
ለበጠ፡ ሐሰትን እውነት አስመሰለ ("ሸለፈ ሸረደደ ለበጠ ሠነበጠ ለጠጠ ለባጭ ") ("ጮች") ።
ለበጣ/ለበጥ ሽለፋ ("ሽንገላ ሽርደዳ ምፀት ለበጣ ነገር ካንገት በላይ እንጂ ከልብ ያልኾነ ግብዝ የለበጣ ነገር ልበጣ ልጠፋ ሽፈና ሥንበጣ መለበጥ መለጠፍ ማልበስ ማስጌጥ መለበጥ መሸለፍ መሸርደድ መለበግ መለጠፊያ መሸፈኛ ማስጌጫ ብርና ወርቅ ንሓስ ") ("ዘኍ. ፲፮፡ ፴፰-፴፱") ።
ለብታ ለብ ማለት ("ለብታ ለስታ ቀላል ሙቀት ለብ አደረገ ጥቂት አሞቀ ቅዝቃ ዜን ኣራቀ ለብ አለ ለስ አለ ለብ ያለ ለስ ያለ ") ("ራእ. ፫፡ ፲፮") ።
ለተተ፡ (ለትቶ፡ ለተተ፡ ኰለተፈ)፡ ለፋ፡ ለሰለሰ፡ ደከመ፡ መኼድ፡ መሥራት፡ እቃተው፡ ሰነፈ ።ለተለተን፡ እይ፡ የዚህ፡ ደጊም፡ ነው ።
ለታ፡ የሰው፡ ስም፡ በመንዝ፡ የግድም፣ ባላባት።
ለታታ፡ (ለታት፡ ኰልታፋ)፡ የለተተ፡ የለፋ።
ለት፡ (ሎቱ)، በዘማች፡ አንቀጽ፡ መፊረሻ፡ በሩቅ፡ ወንድ፡ ዝርዝርነት፡ እየገባ ፣በቁም፡ ቀሪ፡ ኹኖ፡ ይነገራል ። (ማስረጃ)፡ መባ ለት፡ ወረደለት፡ ዐለፈለት። ይኸውም፡ የበጎ፡ ነው። በትንቢትና፡ በትእዛዝ፡ አንቀጽም፡ ሲገባ፡ ይመጣለት፡ ይምጣለት፡ ይላል ።
ለት ፣፡ ቀን ዕለት።
ለት/ለታ/ዕለት፡ ያን ለት (አኹን)።
ለነቀጠ፡ (ትግ ለንቀጠ)፡ በሙቀጫ፡ ተወቅጦ፡ በውሃ፡ የተዘፈዘፈውን፡ የማሽላ፡ እንቀት፡ ፈጫ፡ አላመ፡ ኣለዘበ ።ለቀጠን፡ እይ፡ ሥሩ፡ ርሱ፡ ነው ።
ለንቃጭ፡ የለነቀጠ፡ የሚለነቅጥ፡ አላሚ ።ልንቀጣ፡ የመለንቀጥ፡ የማላም፡ ሥራ።መለንቀጥ፡ መፍት፡ ማላም፡ ማለዘብ ።መለንቀጫ፡ ማላሚያ፡ ማለዘቢያ፡ የቅምጥ፡ ወፍጮ።
ለንቋጣ፡ (ጦች)፡ የንጨት፡ ስም፡ በወይናደጋ፡ ቈላ፡ የሚበቅል፡ አነስተኛ፡ ዛፍ፡ ልጠ፡ ማላጋ ።
ለከለከ በምላሱ፡ እየጨለፈ፡ ውሃ፡ ጠጣ፡ ሊጥን፡ ዋጠ፡ የውሻ።
ለከለከ፡ ለከፈ፡
ለከመ፡ (ለኰመ)፡ ወሬ፡ ለቀመ፡ አወራ፡ ተናገረ፡ ለፈለፈ፡ አሳበቀ። ትግሬ፡ ግን፡ ለከመን፡ ይዞ፡ ኼደ፡ ወሰደ፡ ይለዋል።
ለከሰ፡ (ልህሰ)፡ ደከመ፡ ዐቅም፡ ዐጣ፡ ሰነፈ፡ ታከተ።
ለከስካሳ፡ የተልከሰከሰ፡ የሚልከሰከስ።
ለከተ፡ (ለካ)፡ ገጠመ፡ ዝም፡ አሠኘ።
ለከት፡ (ቶች)፡ ታናሽና፡ ሞላላ፡ ጢብኛ፡ የሊጥ፡ መፈተኛ። አክሥቴ፡ ቤት፡ አለኝ፡ ለከት፡ እንዲል፡ እረኛ
ለከት፡ ልክ፡ መግጠሚያ፡ (ዝምታ) ። እከሌ፡ ላፉ፡ ለከት፡ የለውም፡ እንዲሉ። ለካን፡ ኣስተውል ።
ለከፈ፡ (ለኪፍ፡ ለከፈ)፡ ቀመስ፡ ነካ፡ ነከሰ ። ውሻ፡ ለከፈው። ለከፈ ዠመረ፡ ያዘ። በሽታ፡ ለከፈው፡ ጋኔን፡ ለከፈው።
ለከፈ፡ አቀረበ፡ ደቀነ። ከምድራኹ፡ ላይ፡ ዘወር፡ በል፡ እዚህ፡ ምን፡ ለክፎኻል።
ለከፋ፡ ልክፊያ፡ ቅምሻ።
ለኪ (ለካኢ)፡ የለካ፡ የሚለካ፡ ሸላጊ።
ለካ፡ (ለክአ)፡ መጠነ፡ ሰፈረ፡ ቀጠበ፡ ሸለገ፡ ረተመ፡ ከነዳ፡ መዘነ፡ ("ራእ. ፳፩፡ ፲፯") ። ውሃ፡ በዘንግ፡ ይለካል፡ እንዲሉ።
ለካ፡ ትእዘዝ፡ አንቀጽ፡ መጥን፡ ስፈር፡ ከንዳ፡ መትር።
ለካ፡ ንኡስ፡ አገባብ፡ እኔ፡ ነገሩ፡ አልገባኝም ነበር፡ ለካ፡ እንዲህ፡ ኑሯልን። እኮንና፡ ብ ያን፡ እይ። ተደጋግሞ፡ ሲነገር፡ እውነት፡ እውነት፡ ርግጥ፡ ርግጥ፡ እንደ፡ ማለት፡ ለካ፡ ለካ፡ ይላል፡ ምስጢሩ፡ ልክን፡ አይለቅም ።ያው፡ የነገር፡ አጐ ላማሽ፡ ነው።
ለካሚ፡ (ዎች)፡ የለከመ፡ የሚለክም፡ ወሬኛ፡ ወሬ፡ ማዱ፡ ለፍላፊ።
ለካከፈ፡ ቀማመሰ፡ ነካካ።
ለካፋ፣ የተለከፈ፡ የሚለከፍ፡ የተደቀነ፡ የሚደቀን ።
ለክ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ዋጠ። ለክ፡ ለክ፡ አደረገ፡ ዋጥ፡ ዋጥ፡ ጠጣ፡ ጠጣ፡ አደረገ።
ለክ፡ ዋጥ፡ ሰልቀጥ።
ለክላኪ፡ የለከለከ፡ የሚለከልክ፡ ዋጭ።
ለኮ፡ (ኦሮ)፡ የፈረስ፡ የበቅሎ፡ መሳሲያ፡ ጠፍር፡ ወይም፡ ገመድ፡ ከልባብ፡ ጋራ፡ የተ ቋጠረ፡ ፫፡ ክንድ፡ የሚኾን።
ለኮ፡ መሬት፡ በለኮ፡ የተለካ መሬት፡ በዘመቻ፡ ግልቢያ፡ የተገኘ፡ መኾኑንም፡ ያሳያል ።
ለኰሰ፡ (ለኈሰ)፡ ተኰሰ፡ አቃጠለ፡ አያያዘ፡ አነደደ።
ለኰሰ፡ ላላ፡
ለኰሰ፡ ሰነቀረ፡ አጋባ፡ ነገርን፡ በሽታን።
ለኰሠ፡ እሳት፡ አያያዘ፤ለኰሰ።
ለኮቴ፡ ለኾቴ፡ መሳል፡ የመሳል፣
ለኰፈ፡ (ኰለፈ)፡ ጥቂት፡ መታ፡ ተነኰሰ ።
ለኰፈ፡ ለከሰ፡
ለኰፍ፡ አደረገ፡ ለኰፈ።
ለኳሳ፡ ዐቅለ፡ ቢስ፡ ለዋሳ ።
ለኳሽ፡ (ሾች)፡ የለኰሰ፡ የሚለኵስ፡ ተኳሽ፡ አቃጣይ።
ለኳኰፈ፡ በቀላል፡ መታታ፡ ተነኳኰሰ።
ለኳፊ፡ የለኰፈ፡ የሚለፍ፡ ተንኳሽ።
ለኳፋ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለኸ፡ (ሀሎከ)፡ አንተ፡ ለሚባል፡ ለቅርብ፡ ወንድ፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር፡ ሲኾን፡ (ትማር፡ አለኸ፡ ትጽፍ፡ አለኸ)፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ትማራለኸ፡ ትጽፋለኸ፡ ተብሎ፡ ይነገራል ።
ለኹ፡ (ሀሎኩ)፡ እኔ፡ ለሚል፡ በግስ፡ መጨረሻ፡ እየገባ፡ የሚነገር፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር። (በልቼ፡ አለኹ፡ ጠጥቼ፡ አለኹ)፡ በማለት፡ ፈንታ፡ በልቻለኹ፡ ጠጥቻለኹ፡ ይባላል። አ፡ ተቀዳሚውን፡ ፊደል፡ ራብዕ፡ አድርጎ፡ ስለ፡ ተጐረደ፡ ለኹ፡ ተባለ ።
ለወሰ፡ ("ሎሰ")፡ ቀላቀለ፡ አላቈጠ፡ ዐሸ፡ አዋዋደ፡ አቦካ፡ ("ዘፍ. ፲፰፡ ፮ ።፩ሳሙ. ፳፰፡ ፳፬") ።ለወሰ፡ በጭቃ፡ በከለ፡ ረገጠ።
ለወዘዘ፡ ወ፡ ስሯጽ፡ ነው፡ ለዘዘ፡ እንደ፡ ለውዝ፡ ኾነ።
ለወዘዝ፡ ለውዛዛ፡ የለወዘዘ፡ ለዛዝ፡ ለ ዛዛ፡ ደረቅነትና፡ ርጥብነት፡ ያለው።
ለወገ፡ የሎገ፡ ዘር፡ ነው፡ ሎማን፡ ተመ
ለወጉ/ለወጓ፡ የወንድና የሴት ስም ("ዝርዝሩ ኣባትንና እናትን ያያል") ።
ለወጠ፡ (ወለጠ)፡ ሌላ፡ አደረገ፡ ቀየረ፡ ("፪ዜና. ፴፮፡ ፬") ።የራሱን፡ ገንዘብ፡ ሰጥቶ፡ የሌ ላውን፡ ገንዘብ፡ ገዛ፡ ተቀበለ፡ እጅ፡ አደረገ፡ ወሰደ ።
ለወጠ፡ አሸተተ፡ አገማ፡ ጠረኑን፡ መዐዛውን፡ ቃናውን።
ለወጠ፡ ዐደሰ፡ አረቀቀ።
ለወጥ፡ አለ፡ ተለወጠ ።
ለወጥ፡ (ተወልጦ)፡ መለወጥ ።
ለዋ፡ (ለወየ)፡ አብዝቶ፡ ጠጣ፡ ሰበከተ፡ ለገሸ ።
ለዋሳ፡ (ሶች)፡ የተለወሰ፡ ደካማ።
ለዋሳነት፡ (ልውሰት)፡ ለዋሳ፡ መኾን፡ ደካማነት ።
ለዋሽ፡ (ሾች)፣ የለወሰ፡ የሚለውስ፡ አላቋጭ ።
ለዋወጠ፡ ቀያየረ፡ መላልሶ፡ ለወጠ።
ለዋጭ፡ (ጮች)፡ ወላጢ፡ መወልጥ)፡ የለወጠ፡ የሚለውጥ፡ ዐጣሪ፡ ቸርቻሪ፡ ("ዮሐ. ፪፡ ፲፬") ።
ለውለው፡ አለ፡ ዘው፡ ዘው፡ እለ፡ እዚያም፡ እዚያም፡ ኼደ፡ ተገኘ ።
ለውለው፡ ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ለውላዋ፡ (ለውለወ)፡ ውልብልብ፡ ቀውቃዋ ።
ለውንድዝ፡ የሚያስፈራ፡ ደሴት "
ለውዝ፡ (ዞች)፡ የተክል፡ ስም፡ ፍሬው፡ የሚጣፍጥ፡ ዕንጨት።ለውዝ፡ ገውዝ፡ እንዲሉ፡ ("ኤር. ፩፡ ፲፩") ።
ለውጤ፡ የሰው፡ ስም፡ ምትኬ፡ ማለት፡ ነው ።
ለውጥ፡ ልዋጭ፡ ልው፡ ምትክ ' ፈንታ፡ ("ዘሌ. ፳፯፡ ፲ ።መዝ. ፵፬፡ ፲፪ ።ኢሳ. ፫፡ ፳፬ " ኤር. ፳፪፡ ፲፩") ።
ለውጥነት፡ ለውጥ፡ መኾን።
ለውጦች፡ ምትኮች፡ ፈንቶች።
ለዘለቃ፡ ለፍጻሜ/ለመጨረሻ ።
ለዘለዘ፡ (ለዘዘ፡ ነዘነዘ)፡ ጠጠ፡ መጠመጠ፡ አረሰረሰ፡ መዘመዘ።
ለዘለዝ፡ ለዝላዛ ፣ የለዘለዘ፡ የሚለዘልዝ።
ለዘላለም፡ ለብዙ ዘመን ።
ለዘበ፡ ተባለ፡ ተወረበ፡ ዜማው።
ለዘበ፡ ደቀቀ፡ ላመ፡ ለሰለሰ፡ ምላሱ፡ ነገሩ፡ ጠባዩ፡ ዶቄቱ፡ እጀ፡ ሥራው፡("ምሳ. ፳፱፡ ፭") ።
ለዘብ ፣ ወረብ፡ በበዓል፡ ቀን፡ በቅኔ፡ ማሕሌትና፡ በዑደት፡ ጊዜ፡ ታቦት፡ ሲነግሥ፡ በጸናጽልና፡ በከበሮ፡ እየተመላለሰ፡ የሚባል፡ ረዥም፡ ዜማ ።
ለዘብታ፡ ቀስታ፡ ትሕትና "
ለዘገ ፣ (ለሐቀ)፡
ለዚያ (ሎቱ)፡ ለርሱ ።
ለዚያ፡ ለርሱ፡ ዚያ ።
ለዛ፡ ቢስ፡ ውበት፡ ማማር፡ የሌለው፡ ለዛው፡ መጥፎ።
ለዛ ሙጥጤ፡ ክቾ፡ ደመ፡ ቢስ ።
ለዛ፡ (ትግ፡ ለዘየ፡ አለገገ)፣ ወዝ ፡ ውበት፡ የነገር፡ ጣዕም።
ለዛቢ፡ የሚለዝብ።
ለዛባ፡ ለስላሳ፡ ሻካራ፡ ያይዶለ።
ለዛዛ፡ ለዛዝ፡ የለዘዘ፡ የሚለዝ።
ለዛዛነት፡ ለዛዝነት፡ ለዛዛ፡ ለዛዝ፡ መኾን ።
ለዝና፡ የወንድና የሴት ስም ።
ለየ፡ (ለእየ)፡ እያንዳንዱ፡ እየራሱ፡ እየፊናው፡ እየብቻው፡ የሚባለው፡ ቃል፡ ለ፡ ተቀባይና፡ በቁም፡ ቀሪ፡ ኹኖ፡ በመነሻው ፣ሲመር በት፡ ለያንዳንዱ፡ ለየራሱ፡ ለየፊናው፡ ለየብቻው፡ ተብሎ፡ ይነገራል። እየን፡ እይ።
ለየብቻ (ለእየብቻ)፡ ለያንዳንድ ለ የራስ ለየቅል ። ዳንኤል ረበናትን ለየብቻቸው ጠየቃቸው ።
ለይኩን፡ ፍቱን መድኀኒት አብነት ።
ለደለደ (ለጠለጠ)፡ ለሰለስ፡ ተሰማማ፡ ተዋዋደ፡ ወፈረ፡ የወጥ፡ የመረቅ፡ የምራቅ፡ የሳሙና፡ የንዶድ፡ ዐረፋ ።
ለደለድ፡ ለድላዳ፣ የለዶለደ፣የተዋዋዶ፡ ልድላዴ፡ ልስላሴ፡ ውፋሬ "
ለደፈ፡ (ትግ፡ ሐባ፡ ለፅፈ)፡ ለጠፈ፡ ምራቅን ።ባላገር፡ ለጠፈ፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ለደፈ፡ ይላል፡ ይኸውም፡ ደና፡ ፀ፡ ተወራራሽ፡ መኾናቸውን፡ ያስረዳል ።
ለዳፊ፡ የለደፈ፡ የሚለድፍ፡ ለጣፊ።
ለገሰ፡ ብዙ፡ ዝናብ፡ ጣለ፡ ወለሰ።
ለገሰ፡ ባለመቈጠብ፡ ሰጠ፡ ናኘ፣ ቸረ።
ለገሠ፡ ቸረ ለገሰ።
ለገሸ፡ አለልክ፡ ጠጣ።
ለገበ፡ (ትግ)፡ ልብስን፡ ጣፈ " ሥሩ፡ ለጐመ፡ ነው።
ለገተ፡ (ለጐተ)፡ ለገደ።
ለገቸ፡ አስጠጋ፡ አሳዘነ፡ አማለ።
ለገቻ፡ ማስጠጋት፡ ዐዘን፡ ውል፡ ማሳ።
ለገን፡ (ልጕን)፡ የሸክላ፡ ዕቃ፡ የደቅ፡ ዐይነት፡ ደቅ፡ ዋዲያት። ሲበዛ፡ ለገኖች፡ ይላል፡
ለገደ፡ ኣገባ፡ ወተፈ፡ ቀረቀረ፡ ደነቀረ፡ መረገ።
ለገደ፡ (ትግ፡ ለገጸ)፡ ቀለደ፡ ተረበ። ባረብኛ፡ ፀና፡ ደ፡ ተወራራሽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ ትግሪ ኛው፡ ለገጸ፡ ባማርኛ፡ ለገደ፡ ተባለ። ("ለገጠ")ን እይ።
ለገዳ፡ ቅርቀራ፡ ውተፋ።
ለገድ፡ ነፈል፡ ቅጭጭላት።
ለገገ፡ (ሠወነ)፡ ተለቀቀ፡ ወጣ፡ ተ
ለጊ፡ የለጋ፡ የሚለጋ፡ የሚመታ፡ አጠንጊ።
ለጋ፡ ልጅ፡ ካ፲፭፡ ዓመት፡ በታች፡ ያለ፡
ለጋ፡ ቅቤ፡ ትኵስ፡ ለስታ፡ ቅቤ።
ለጋ፡ ጨረቃ፡ ብርሃኗ፡ ያልሞላ፡ ያልደ
ለጋ፡ ቀንበጥ፡ ሙሽራ፡ ያልጠና፡ ያልጠ ነከረ፡ ቅጠል፡ ልጅ፡ ለምለም፡ እንቦቀቅላ፡ ("፩ዜና. ፳፱፡ ፩") ።("ኢሳ. ፲፭፡ ፮") ።ለጋ፡ ጐመን፡ እንዲሉ ። (ግጥም)፡ እኔ፡ እንቢ፡ አሻፈረኝ፡ እወጣለኹ፡ ደጋ፡ ዐንገቷ፡ ይመስላል፡ የጠንበለል፡ ለጋ ።
ለጋ፡ ባለማቋረጥ፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ጠጣ። ሸመጠጠን፡ እይ ።
ለጋስ፡ (ሶች)፡ የለገሰ፡ የሚለግስ፡ ቸር፡ ሰጪ፡ አባ፡ መስጠት፡ ("ኢሳ. ፴፪፡ ፭") ።
ለጋስነት፡ ለጋስ፡ መኾን።
ለጋዎች፡ ለጎች፡ ቀንበጦች፡ ለምለሞች፡ ለጋ፡ ጐበዝ፡ ወጣት፡ ልጅ፡ እግር፡ ሦታ። ለጋ፡ ደመና፡ ጥቍረት፡ ጥቍርነት፡ የሌ ለው፡ ደመና።
ለጋጅ፡ የለገደ፡ የሚለግድ፡ ቀርቃሪ።
ለግ መስፈሪያ፡ ሎን ።
ለግዳ፡ ቅምሖ፡ የጕረሮ፡ ዕብጠት፡ በኹለት፡ ወገን፡ የሚበቅል፡ በማንቍርት፡ ጫፍ፡ የሚ ለገድ። ለቅዳ፡ ተብሎ፡ ሊጻፍም፡ ይቻላል።
ለግድ፡ ለግጥ።
ለጐመ ("ጐለበ በኮርቻ ዕንጨት ላይ ቈዳን ሰፋ መረገ ለበደ ") ("ትግ") ።
ለጐመ፡ (ለገበ)፡ አገልግልን፡ ማንኛውንም፡ ስፌት፡ በቈዳ፡ በተንቤን፡ ሰፋ፡ ለበደ፡ አለበሰ፡ መላውን፡ ወይም፡ ከንፈሩንና፡ እግሩን ።ከፈፈን፡ እይ ።
ለጐመ፡ (ለጒም፡ ለጐመ)፡ ልጓምን፡ ጥይትን፡ ኳስን፡ ለበቅሎ፡ ለፈረስ፡ ለጠመ ንዣ፡ ለባሪያ፡ አጐረሠ፡ ቀረቀረ።
ለጐመ፡ ልዳ፡
ለጐመ፡ ዝም፡ አሠኘ፡ አሰረ፡ ዘጋ፡ አፍን፡ ("ዘዳ. ፳፭፡ ፬") ።
ለጐደ፡ ለደፈ፡ ለጠፈ፡ የምራቅ፡ የንፍጥ፡ የጭቃ ።
ለጐጠን፡ አስተውል ።
ለጓሚ፡ (ሞች)፡ የለጐመ፡ የሚለጕም ፈረስ፡ በቅሎ፡ ጫኝ።
ለጓጅ፡ የለጐደ፡ የሚለጕድ፡ ለዳፊ።
ለጠ፡ የሊቃውንት፡ ሊቅ፡
ለጠ፡ ዳለጠ፡ ለዘበ፡ ከመሻከር ራቀ፡ ሥራ ፈታ፡ ማገጠ።
ለጠለጠ፡ (ለጽለጸ)፡ ሊጥ፡ እስኪኾን፡ ቅባት፡ እስኪወጣው፡ ወቀጠ።
ለጠለጠ፡ (ትግ፡ ለጥለጠ፡ ዘበጠ)፡ ጠፈጠፈ፡ አጠፈጠፈ፡ ዘረጋ፡ እንደ፡ ነጥር፡ ልክ፡ ትክክል፡ አደረገ።
ለጠለጠ፡ ለጠፈ ፡
ለጠቀ ("ቀጠለ ዐ ጀበ በነገር በሥራ በሥልጣን በንብረት ተተካ ") (ዘፀ. ፲፬፡ ፰) ።
ለጠበ፡ (ለጠመ)፡ ለጠብ፡ ሰፋ፡ አበጀ፡ ከደነ፡ ገጠመ።
ለጠብ፡ (ቦች)፡ የቅል'የናርጅ፡ የጮጮ፡ መክደኛ። ጠብና፡ ለጠብ፡ ባማርኛ፡ ይተባበራሉ ።ሴትዮዋ፡ የመጣችው፡ ለጠብ፡ ነው፡ ለጠብ ፣ት ሰፋለች።
ለጠጠ፡ ዘረጋ፡ አስተካከለ ።
ለጠጠ፡ (ለጺጽ፡ ለጸጸ። ትግ፡ ለጠጠ፡ አብዝቶ፡ ጫነ)፡ ሠነበጠ፡ ከፈለ፡ ነጠለ፡ ብቻ፡ አደረገ፡ የንጨት፡ የድር ።
ለጠጠ፡ ሳበ፡ ጐተተ፡ ገተረ፡ ቀስትን፡ ("ኤር. ፱፡ ፫ ። ፶፩፡ ፫ ። ዘካ. ፱፡ ፲፫") ።
ለጠጠ፡ አበዛ። ዛሬ፡ ሌሊት፡ አቶ፡ እከሌ፡ እንቅልፉን፡ ሲለጥጥ፡ ዐደረ ።
ለጠጠ፡ መታ፡ ደበደበ ።
ለጠጠ፡ ቈነነ፡ ሰውን ።
ለጠጦ፡ ረዥም፡ በትር፡ ወይም፡ ሽመል፡ (ጐንደር) ።
ለጠጦ፡ ካገዳ፡ እንኵሮ፡ ሥር፡ ከገበር፡ ምጣድ፡ ላይ፡ ተለጥጦ፡ የሚነሣ፡ ሥሥና፡ ደረቅ፡ አንኳሪ፡ የሚበላው፡ የንኵሮ፡ ሉሕ። ቀለጦን፡ እይ፡ ከዚህ፡ ጋራ፡ አንድ፡ ነው።
ለጠፈ ("ሸፈነ አለበሰ አስጌጠ በወርቅና በብር ") ("ዘኍ. ፲፮፡ ፴፰") ።
ለጣጭ፡ (ጮች)፡ የለጠጠ፡ የሚለጥጥ፡ ሠንባጭ፡ ከፋይ፡ ነጣይ፡ ሳቢ፡ ጐታች፡ ቈናኝ። ልጠጣ፡ ንጠላ፡ ጕተታ።
ለጥ፡ አለ ተዘረጋ፡ ተሰጣ፡ ተኛ፡ ተ ካከለ ። ለጥ፡ ያለ፡ ሜዳ፡ እንዲሉ። ለጥ፡ አለ፡ ግእዝ፡ ለጥሐ፡ ከሚለው፡ ሊወጣም፡ ይችላል ።
ለጥ፡ አለ፤ትክክል፡ ኾነ፡ ለ ጠጠ ።
ለጥ፡ ይበሉ፡ የሰው፡ ስም ።
ለጥላጭ፡ የለጠለጠ፡ የሚለጠልጥ፡ አጠፍጣፊ፡ ዘርጊ "
ለፈለፈ፡ (ለፈፈ)፡ ቀባጠረ ነገር፡ አበዛ ፣ባለማቋረጥ፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ ተናገረ ። (ተረት) ፣ይጠፉ በለፈለፉ።
ለፈወቀ፡ በምግብ፡ ጊዜ፡ አፉን፡ አጮኸ፡ እንጯ፡ እንጯ፡ አደረገ ።
ለፈደ፡ ዘበዘበ፡ ነገርአልቈርጥ፡ ኣለ ።
ለፈደደን፡ ተመልከት ።
ለፈደድ፡ ለፍዳዳ፣ የተለፋደደ፣ የሚለፋደድ፡ ጨመለቅ፡ ጨምላቃ፡ ነገረ፡ በክ ።
ለፈዲያም፡ ዝብዝባም፡ ነገረ፡ ጐትት ።
ለፈድ፡ ዝብዝብ፡ ጣመ፡ ቢስ፡ ነገር ።
ለፈጠ፡ (ለፈጸ)፡ ዐሸ፡ ለወሰ፡ አበቀ፡ አበሰበሰ ።
ለፈጨቀ፡ ነዘነዘ፡ ጨቀጨቀ ።
ለፈጯ፡ ልፋጭ፡ አደረገ፡ ልፋጭ፡ አወጣ ።
ለፈፈ፡ ዐጠፈ፡ ጠቀለለ ።
ለፈፈ፡ (ለፊፍ፡ ለፈ)፡ እየዞረ ' ኾነገረ፡ ዐወጀ፡ አሰማ፡ ሰበከ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፴፮") ።
ለፊ (ለፋዒ)፡ የለፋ፡ የሚለፋ፡ የሚደክም፡ ውርደት፡ ተቀባይ። (ግጥም)፡ ሰዉ፡ ሰው፡ ላይ፡ ገቢ፡ ነው፡ የተያዘ፡ እንደኹ፡ ለፊነው ።
ለፋ፡ (ትግ፡ ለፍዐ)፡ ታሸ፡ ተፈተን፡ ተረገጠ፡ ተገለጠ፡ ለሰለሰ፡ ለተተ፡ ደቀቀ -
ለፋለፈ፡ ቀበጣጠረ፣ ነገር፡ መላለሰ።
ለፋፊ፡ (ዎች)፡ የለፈፈ፡ የሚለፍ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፴፯") ።
ለፋፊነት፡ ለፋፊ፡ መኾን። ለፈፋ፡ የመልፈፍ፡ ኹናቴ፡ ዕወጃ መልፈፍ፡ መንገር፡ ማሰማት
ለፍላፊ፡ (ፎች)፡ የለፈለፈ፡ የሚለፈልፍ፡ ቀባጣሪ፡ የዝምታ፡ ጠላት።
ለፍላፊነት፡ ለፍላፊ፡ መኾን፡ ቀባጣሪነት ።
ለፍላፋ፡ አፈኛ፡ ተናጋሪ።
ለፍቃ፡ ለፍዳዳየሚለፋጨቅ፡ ነዝናዛ፡ ጨቅጫቃ ።
ለፍቶ፡ መና፡ ዐርሶ፡ ነግዶ፡ የማያልፍለት፡ ትርፍ፡ የለሽ ።
ለፍቶ፡ ጥሮ፡ ደክሞ።
ለፍቶ፡ ዐደር፡ እንዲሉ።
ለፎ፡ (ለፈየ)፣ አገዳ፡ መቃ፡ የግዳይ፡ መቍጠሪያ ።
ለፎ፡ ለፈቀ፣
ለፎ፡ ጀሌ፡ መደዴ፡ ወያኔ።
ሉህ ሰሌዳ፡ ሉሕ።
ሉሕ፡ (ለውሕ)፡ ልዝብ፡ ሳንቃ፡ ጠርብ፡ ሰሌዳ፡ ብራና፡ ወረቀት።
ሉሖች፡ ሳንቆች፡ ወረቀቶች።
ሉሜ፡ ላሙ ፡
ሉሜ፡ በአዳ፡ ወረዳ፡ ያለ፡ ቀበሌ ።
ሉቃሳም፡ (ሞች)፡ የሉቃስ፡ ባለሉታስ፡ ችጋራም፡ ራብተኛ፡ በልቶ፡ የማይጠግብ፡ ሥሡ፡ ገብጋባ ።ባላገር፡ ግን፡ ልቋስ፡ ልቋሳም፡ ይላል ።
ሉቃስ ፣ ከብት፡ ያለቀበትና፡ ረኃብ፡ የጸናበት፡ ጊዜ፡ ክፉ፡ ቀን፡ ይኸውም፡ ባ፲፰፻፹፩፡ ዓ፡ ም፡ ዠምሮ፡ ነው ።
ሉቃስ ፣ የሰው፡ ስም፡ ካራቱ፡ ወንጌላውያን፡ አንዱ ።ግብረ፡ ሐዋርያትንም፡ የጻፈ፡ ርሱነው፡ ቍጥሩና፡ ማዕርጉ፡ ከ፸፪ቱ አርድእት።
ሉቃስ፡ የዘመን፡ ክፍል፡ አራተኛ፡ ዓመት፡ ጳጕሜ፡ ፮፡ የምትኾንበት፡ ፬ኛነቱ፡ ለዮሐንስ፡ ነው።
ሉካንዳ፡ (ዶች)፡ የምግብ፡ ቤት፡ የመብል፡ መደብር፡ ሥጉያ ።
ሉካንዳ፡ በጣሊያንኛ፣ ሎካንዳ፡ ይባላል።
ሉክ፡ ወረቀት ሉሕ። ሉክ፡ ኰፊር።
ሉድ፡ የሴት፡ ስም።
ሉግ፡ ፲፪፡ ዕንቍላል፡ የሚይዝ፡ መስፈሪያ፡ ("ዘሌ. ፲፬፡ ፲") ።
ሊሙ፡ በጅማ፡ አውራጃ፡ የሚገኝ፡ አገር፡ ሊሙ፡ ያቅኒው፡ ስም፡ ነው ።
ሊቀ፡ ሐመር፡ የመርከብ ፡ አዛዥ ። ፈረንጆች፡ አሚራል፡ ይሉታል።
ሊቀ፡ ሀገር፡ አገረ፡ ገዢ።
ሊቀ፡ መላእክት፡ የመላእክት፡ አለቃ፡ ቅዱስ፡ ሚካኤል፡ ቅዱስ፡ ገብርኤል፡ ቅዱስ፡ ሩፋኤል ።
ሊቀ፡ መንበር፡ የጉባኤ፡ አለቃ።
ሊቀ፡ መዘምራን፡ የመዘምራን፡ አለቃ፡
ሊቀ፡ ምርፋቅ፡ የዳስ፡ ሹም፡ አሳዳሪ።
ሊቀ፡ ሰማዕታት፡ የሰማዕታት፡ አለቃ፡ ቅዱስ፡ ጊዮርጊስ።
ሊቀ፡ ካህናት፡ የካህናትአለቃ ጳጳስኤጲስቆጶስ፡ ንቡረ፡ እድ፡ ዕጨጊ ።ዳግመኛም ፣በግእዝ፡ (ሊቀ፡ ኖሎት፡ የረኞች፡ አለቃ፡ ይባላል፡
ሊቀ፡ ደብተራ፡ የደብተራ፡ አለቃ፡ መሪ፡ ጌታ፡ ወይም፡ ሌላ።
ሊቀ፡ ዲያቆን፣ የዲያቆን፡ ኣለቃ፡ ኣስተዳዳሪ። ይህ፡ ማዕርግ፡ መዠመሪያ፡ ከሐዋርያት፡ ለቅዱስ፡ እስጢፋኖስ፡ ተሰጥቷል ።
ሊቀ፡ ጠበብት፡ ያዋቆች፡ የደብዳሮች፡ አለቃ፡ የቤተ፡ ክሲያን፡ ሸም፡ ከዋናው፡ ኦ ለቃ፡ በስተግራ፡ በወንበር፡ የሚቀመጥ።
ሊቀ፡ ጳጳሳት፡ የጳጳሳት፡ አለቃ፡ ጳጳሳትን፡ የሚሾም፡ የሚሽር፡ በሮም፡ በእስክንድርያ፡ በቍስጥንጥንያ፣ በአንጾኪያ፡ ወንበርየሚቀመጥ፡ ሌላውም፣ ከበታቹ፡ ጳጳሳት፡ የሚሾም፡ ዅሉ፡ ሊቀ፡ ጳጳሳት፡ ይባላል ።
ሊቀ፡ ሊቃውንት፡ ከሊቃውንት፡ የበ
ሊቀ፡ መኳስ፡ (ሊቀ ፣ሞገስ)፡ የመወደድ፡ አለቃ፡ ጭራና፡ መነሳንስ፡ ይዞ፡ በንጉሥ፡ አጠገብ፡ የሚቆም፡ ባለል፡ የንጉሥ፡ አሳሳች፡ የባለል፡ አለቃ።
ሊቀ፡ መጣኞች፡ የይግባኝ፡ ሰሚዎችአለቃ፡ ይኸውም፡ በጐንደር፡ መንግሥት፡ ነው ።
ሊቀ፡ ምርፋቅ፡ የምርፋቅ፡ አሳራጊ፡ መነኵሴ ።
ሊቀ፡ ረድ፡ የረድ፡ አለቃ፡ እንደ፡ ደብረ፡ ሊባኖስ፡ ባለው፡ ገዳም፡ የመጋቢ፡ ምክትል፡ አዛዥ፡
ሊቃውንት ፣ ሊቆች፡ ባላገር፡ ግን፡ ሊቃውንት፡ በማለት ፈንታ- ሊቃውንቶች፡ ይላል ።
ሊቃውንት፡ ፪፡ የበገና፡ ዥማት፡ (እውታር) ።
ሊቄ፡ (ሊቅየ)፡ በቤተክሲያን፡ የማዕርግ፡ ስም፡ ከሊቃውንት፡ በትምርት፡ ብል፡ ያለውን፡ ንጉሡ፡ ሊቄ፡ ይለዋል። ሊቄ፡ በጸሎቱ፡ እንዲሉ።
ሊቅ፡ (ልሂቅ)፡ ካምሳ፡ ዓመት፡ በላይ፡ ያለ፡ ሽማግሌ፡ ዐዋቂ፣ጨዋ፡ ዐዛውንት፡ አሮጌ፡ (አረጋዊ) ።ከሊቅ፡ እስከ፡ ደቂቅ፡ እንዲሉ ።
ሊቅ፡ ምሁር፡ የተማረ፡ ትምርት፡ የጠዝበ፡ በትምርትና፡ በዕድሜ፡ የበሰለ አለቃ፡ መምር፣ ጌታ፡ ብለይና፡ ሐዲስ፡ ዐዋቂ። ፈረንጆች፡ ዶክተር፡ ይሉታል ።አፍን፡ እይ ።
ሊቅ፡ የሊቃውንት፡ መጻፍ፡ ሃይማኖተ አበው፡ አፈ፡ ወርቅ፡ ቄርሎስ፡ ኤጲፋንዮስ፡ ቅዳሴ፡ አቡ፡ ሻህር ።
ሊቅ፡ አሊቃ፡ (ግእዝ) ።
ሊቅ የተማረ፡ ላቀ ።
ሊቅነት፡ ሊቅ፡ መኾን፡ ምሁርነት፡ ዐዋቂነት፡ ፍጹም፡ ትምርት ።
ሊቆች፡ (ሊቃውንት፡ ሊቃናት)፡ እጅግ፡ የተማሩ፡ ዐዋቆች፡ መምሮች።
ሊጋባ፡ የማዕርግ፡ ስም —ገባ።
ሊጋባ (ቦች)፡ ሰውን ወደ ቤተ መንግሥት ሊያገባ (ሊአገባ) ሊያስገባ የተሾመ ያጋፋሮችና የከልካዮች የበላይ ባለሥልጣን ። ቀድሞ ዘመን ራቅ ማሰሬ ይባል ነበር ።
ሊጡ/ጠላው ቀጠነ)፡ ውሃ ኾነ ።
ሊጥ፡ በቁሙ፡ ለጠለጠ። ላጠ፡ (ልሕጸ)፡ ዛፍን፡ ገፈፈ፡ አራቈተ፡ አደረገ፡ ልጥን፡ ከቅርፊት፡ ጋራ፡ ወሰደ፡ ("ዘፍ. ፴፡ ፴፯") ።
ሊፍ፡ የሳንቃ፡ ንጣጭ፡ የባሕር፡ ዕቃ፡ መጠቅለያ።
ሊፍ፡ ንጣጭላፈ ። (ለአፈ) ፣ቅርፊትን፡ ከልጥ፡ ለየ፡ ገፈፈ ።ላፈፈን፡ ተመልከት ።
ላሑ፡ ሥሥ፡ ጠጕር፡ ከመተኛት፡ በቀር፡ መቆም፡ የማይችል፡ በጋልኛ፡ ሉጫ፡ ይባላል ።
ላሕማ፡ (ዐረለሐመ፡ መረገ)፡ መጣብቅ፡ ሙ፵፡ የደብዳቤ፡ የቀዳዳ፡ ቈርቈሮ፡ ወይም፡ ታኒካ፡ መምረጊያ፡ መድፈኛ፡ ባረብኛ፡ ልሐማ፡ ይባላል ።ሸብን፡ ተመልከት ።
ላሊበላ፡ (ሎች)፡ የነገድ፡ ስም፡ ሌሊት፡ ወየው፡ ዓለም፡ እያለ፡ ለምኖ፡ የሚበላ፡ ስለ፡ ኾነ፡ ላሊበላ፡ ተባለ። ሐባብ፡ ሌሊት፡ ሲል፡ ላሊ፡ እንዲል ("መዝ. ፩፡ ፪") ።የላሊ በላ፡ ጋብቻ፡ በየተዝካሩ፡ ቤት፡ ነው ። (ተረት)፡
ላሊበላ፡ (ላሊ፡ በላ)፡ የንጉሥ፡ ስም፡ በላስታ፡ የነገሠ፡ የኢትዮጵያ፡ ንጉሥ፡ ፲፪፡ መ ቅዶስ፡ ባንድ፡ ዋሻ፡ ውስጥ፡ ያነጸ። ላስታ፡ ላሊበላ፡ እንዲሉ ።አንዳንድ፡ ሰዎች፡ ዐጤ፡ ላሊ በላ፡ የተወለደ፡ ለት፡ በንብ፡ ስለ፡ ተከበበ፡ ማር፡ ይበላ፡ እንደ፡ ማለት፡ በአገው፡ ቋንቋ፡ ላልይበላ፡ ተባለ፡ ይላሉ።
ላሊበላ፡ ዐደራውን፡ አይበላ። ደብራሆምንና፡ ሐሚናን፡ እይ። ዐጤ፡ ላሊበላም፡ ሲጦም፡ እየዋለ፡ ማታ፡ (ሌሊት)፡ በመብላቱ፡ ላሊበላ፡ (ሌሊተ፡ በላ)፡ የተባለ፡ ይመስላል፡ ብንል፡ የተመቸ፡ ነው። ሌሊት፡ በቁሙ፡ ፡ ለየ ።
ላላ፡ አደረገ፡ በጥቂቱ፡ አላላ።
ላላ፡ አለ፡ ራስ፡ ረገብ፡ አለ፡ ላላ።
ላላ፡ (ላሕልሖ)፡ መላላት።
ላላቴ፡ ታናሽ፡ ዕብስት፡ ለስላሳ፡ ተስፋ።
ላላገ፡ ፋፋቀ፡ አለዛዘበ።
ላላጠ፡ መላልሶ፡ ላጠ።
ላሎ፡ ምድር፡ የላሎ፡ ምድር፡ ወይም፡ ርስት።
ላሎ፡ ለማ፡
ላሎ፡ የሰው፡ ስም፡ የግማሽ፡ መንዝ፡ ባላባት ።
ላመ፡ ፈጅ፡ ታላቅ፡ የብረት፡ ድስት፡ መካከለኛ፡ ጐላ ።
ላመ፡ (ልሕመ)፡ ደቀቀ፡ ተሰለቀ፡ ለዘበ፡ ለሰለሰ፡ ደከመ፡ ለፋ፡ የዶቄት፡ የሰውነት።
ላመል (ለዐመል)፡ ለልማድ (ጥቂት ") ።
ላመት፡ የሚመጣው ዓመት ።
ላሙ፡ ሲገኝ፡ ዐላቢው፡ አይገኝ ።
ላሙ፡ የላም፡ መንጋ።
ላሙ፡ ያ፡ ላም።
ላሚ፡ የሚልም፡ ለዛቢ ።
ላሚቱ፡ ያች፡ ላም፡ ("ዘኁ. ፲፱፡ ፭, ፰, ፱, ፲") ።
ላሜዳ ላይዳ ፣ላይ ።
ላሜድ፣ የፊደል፡ ስም፡ ለ፡ ትምርት፡ ወይም፡ የተማረ፡ ማለት፡ ነው።
ላም፡ ላጊ፡ ላምን፡ የሚጠባ፡ ሸሌ፡ መጠማጥ ።
ላም፡ አለ፡ ልዝብ፡ አለ፡ ላመ።
ላም፡ ዐንገት፡ ፈሪ፡ ርግብግብ።
ላም፡ አለኝ፡ (አለችኝ)፡ በሰማይ፡ ወተትም፡ አልጠጣ፡ ዐሲቡንም፡ አላይ ።የሥጋ፡ መድኀኒት፡ ላም፡ የነፍስ፡ መድኀ ኒት፡ ማርያም፡ እንዲሉ። ሲበዛ፡ ላሞች፡ ይላል፡ ("ዘ፱፡ ፫") ። ላም፡ በግእዝ፡ የወል፡ ስም፡ ስለ፡ ኾነ፡ ለተባቱም፡ ይነገራል፡ ("ምሳ. ፲፬፡ ፬") ። ላም፡ ባልዋለበት፡ ኵበት፡ ለቀማ ።
ላም፡ (ላሕም)፡ የቤት፡ እንስሳ፡ እንስት፡ የቀንድ፡ ከብት፡ የበሬ፡ ጣምራ፡ የጥጃ፡ እናት፡ የዋህ፡ ዐመለ፡ ደንሴ። እከሌ፡ ላም፡ ነው፡ እንዲሉ ። (ተረት)፡ ላም፡ የዋለችበትን፡ ትመስላለች፡ ለላም፡ ቀንዷ፡ አይከብዳትም።
ላምባ፡ (ልንጳስ)፡ መብራት፡ የሚኾን፡ የምድር፡ ዘይት፡ ጋዝ። ላምባን፡ ጋዝ፡ ማለት፡ ባረብኛ፡ ነው ።
ላምባ፡ ላምፓ (ሮማይ፡ ላምፖስ)፡ ችቦ፡ ቲሃ።
ላምዛን፡ አነባበሮ፡ ሊጡ፡ ታሽቶ፡ የተቦካ።
ላምጌ ንብጌ ዐዲስጌ ዕጨጌ (ሐፄጌ) ዐምባላጌ ዐንገትጌ ፍንጥርጌ ቅዱስጌ ራስጌ ሰላምጌ፡ የኹሉንም ትርጓሜ በየስፍራው ይመለከቷል ። ትግሬ ሐባብም አገርን ድጌ ይለዋል ።
ላሰሰ፡ (ትግ፡ ላሕሰሰ)፡ ኣብዝቶ፡ ነቀለ፡ ሰሰ፡ እሸትን፡ ጤፍን።
ላሳሽ፡ የላሰሰ፡ የሚላስስ፡ ነይ፡
ላስ፡ (ልሒስ)፡ መላስ።
ላስ፡ አደረገ፡ ፈጀ፡ ጨረሰ፡ እሳት፡
ላስ፡ አደረገ፡ ጥርግ፡ አደረገ።
ላስቲክ፡ (ኮች)፡ ፈረንጆች፡ ከንጨትደም፡ የሚሠሩት፡ ሲስቡት፡ የሚረዝም፡ ሲለቁት፡ የሚያጥር፡ ነገር፡ ነትና፡ ተንቤን፡ መሳይ፡ ሥሥና፡ ወፍራም፡ እንደ፡ ርጥብ፣ ስልቻ፡ ይነፋናለተንቀሳቃሽ፡ መኪና፡ እግር፡ ይኾናል ፣ለሌላም - ጕዳይ፣ ይገባል፡ ጠንካራው፡ ጎማ፡ ይባላል።
ላስታ፡ ላሊበላ፡ ያጤ፡ ላሊበላ፡ እግር፡ ላስታ፡ ወይም፡ የላስታው፡ ላሊበላ ።ላሊበላን፡ እይ ።
ላስቶች፡ የላስታ፡ ሰዎች፡ የላስታ፡ ተወላጆች ።
ላሸ፡ (ትግ፡ ላሸወ. ለስሐ)፡ ላላ፡ ጥብቀት፡ ዐጣ፡ ለጠ፡ የምላስ፡ የጠመንዣ፣ የወፍጮ፡ ("መክ. ፲፪፡ ፬") ።
ላሸ፡ የላሸቀ፡ ከፊል፡ ነው ።
ላሸቀ ፣ በጣም፡ ለፋ፡ ቈዳው፡ ላላ፡ ለጠ፡ ቃታው። ላሸን፡ እይ።
ላሽ፡ (ለሓሲ)፡ የላሰ፡ የሚልስ፡ ላሺ፡ ተብሎ፡ ሊጻፍም፡ ይችላል ።
ላሽ፣ ላሺት፡ መርዝ፡ ያላት፡ ታናሽ፡ ዝበሎ፡ ሳትታይ፡ ሳትሰማ፡ የራስን፡ ጠጕር፡ እየላሰች፡ ትመልጣለች፡ ይላሉ። ሐኪሞች፡ ግን፡ በደም፡ መበላሸት፡ ምክንያት፡ መኾኑን፡ ያስረዳሉ ።
ላቀ፡ (ልህቀ)፡ አደገ፡ ጐለመሰ፡ አካለ፡ መጠን ፣ እደረሰ፡ ከፍ፡ አለ፡ በለ።
ላቀ፡ ከበረ፡ ተሾመ፡ አለቃ፡ ኾነ።
ላቀ፡ አረጀ፡ ሸመገለ።
ላቀም፡ ማሰባሰብ።
ላቀቀ፡ (ዕብ፡ ላቃቅ፣ ላሰ)፡ ፈቀደ፡ መብት፡ ሰጠ፡ አሰናበተ፡ ዋስን፡ ዐግት፡ አለ።
ላቀች፡ የሴት፡ ስም፡ በለጠች፡ ማለት፡
ላቀው፡ የሰው፡ ስም፡ በለጠው፡ ማለት፡
ላቂ፡ የዟይ፡ ደሴት፡ ፭ቱ፡ ኹሉ ፣በጋልኛ፡ ቀዛፊ፡ ማለት፡ ነው።
ላቂ (ለሃቂ)፣የላቀ፡ የሚልቅ፡ የበ
ላቂያ ፣ ብልጫማ፣ ማዕርግ፡ ከፍታ።
ላቃቂ፣ የላቀቀ፡ የሚላቅቅ፣ ዳኛ።
ላቈጠ ፣ ፈጽሞ፡ ራሰ፡ ተረገጠ፡ ታሸተለወሰ ።
ላቅ፡ (ልሂቅ)፡ መላቅ ።
ላቅ፡ አለ፡ በለጥአለ ።
ላቢ)ረቢ (ረባሒ)፡ የሚወልድ/የሚበዛ/የሚረባ/የሚጠቅም (ጠቃሚ ") ።
ላተ፡ (ለዐተ)፡ ላት፡ አወጣ፡ ሠራ።
ላት ፣ (ለዐት)፡ የበግ፡ ዥራት፡ ("ፀ. ፳፬፡ ፳፪") ።
ላት፡ (ላቲ)፡ ለሩቅ፡ ሴት፡ የአንቀጽዝርዝር ።እከሊት፡ ልጇ፡ ከዘመቻ፡ ደኅና፡ ገባላት ብዙ፡ ምርኮ፡ አመጣላት። አሽከሯ፡ ውሃ፡ ቀዳላትዕንጨት፡ ሰበረላት ።
ላት፡ ላት፡ የሚመስል፡ የጐራዴ፡ እጀታዳር፡ ማገጃ ፣ኹለተኛ፡ ስው፡ ደም፡ ዐፋሽ፡ ይባላል። መክድን፡ እይ።
ላት፡ የጠመንዣ፡ ሰደፍ። (የበግ፡ ላት)፡ የቅጠል፡ ስም፡ ዠርባው፡ ነጭ፡ የኾነ፡ ገላላ፣ቅጠል ።
ላቶ) ሽቶ፡ ፈልጎ ፈቅዶ ።
ላቸው፡ (ሎሙን)፡ ለሩቆች፡ ወንዶችና፡ ሴቶች፡ የኔንቀጽ፡ ዝርዝር። ኢየሱስ፡ ክርስቶስ፡ ለእስራኤል፡ ወንጌልን፡ ሰበክላቸው፡ ዕውሮቻቸውን፡ አበራላቸው፡ የሞቱትንም፡ አስነሳቸው ።
ላችኹ፡ (ለክሙ፡ ን)፡ ለቅርቦች፡ ወንዶችና፡ ሴቶች፡ የአንቀጽ፡ ዝርዝር ።ነቢያት፡ ሆይ፡ ደስ፡ ይበላችኹ ፣ክርስቶስ፡ ተወለደላችኹ፡ ብርሃን፡ ተገለጠላችኹ።
ላንቍሶ፡ (ዎች)፡ ያረግ፡ ስም፡ ወፍራም፡ ዐረግ። ባላገሮች፡ በመጥረቢያ፡ እየሸነሸኑ፡ ዐጥርና፡ ግድግዳ፡ ይማግሩበታል፡ ልጡ፡ ከተልባ፡ ይልቅ፡ ይማልጋል ።
ላንቍሶ፡ የሚያለቅስ፡ ልጅ። ላንሴታ፡ (ዎች)፡ የሚዛን፡ ምላስ፡ ፍ፡ ውልብልቢት፡ በግእዝ፡ ለጽሊጽ፡ ይባላል። ኮለሌን፡ እይ ።
ላንቃ፡ ባለመደረቢያ፡ ካባ ።ካባ፡ ላንቃ፡ እንዲሉ።
ላንቃ፡ ትናጋ፡ ያፍ፡ ዋሻ፡ ላይኛው " አ ፌን፡ ስለ፡ ተጋረፈኝ፡ ላንቃዬን፡ ዐሞኛል።
ላንቃ፡ ነዲድ፡ ነበልባል፡ ውልብልቢቱ፡ ("ኢሳ. ፶፡ ፲፩") ። የእሳት፡ ላንቃ፡ እንዲሉ።
ላንቴ፡ ከፊለ፡ ስም። አንተ፡ ግባ፡ አንተ፡ ውጣ፡ አለች፣ አመነዘረች፡ ሸረሞጠች፡ ሴሰነች።
ላንት፡ ይደሩ፡ የሰው፡ ስም፡ ላንተ፡ አሽከር፡ ይኹኑ፡ ማለት፡ ነው ።
ላንት፡ (ለአንት)፡ ላንተ።
ላከ፡ (ለአከ)፡ ሰደደ፡ አመጣ፡ አወረደ ።በትና፡ ለት ሲሰማሙት፡ ላከበት፡ ላከለት፡ ይላል።
ላከ፡ ላከከ፣
ላከ፡ ምግብን፡ ወደ፡ ሆድ፡ አገባ፡ ዋጠ፡ ሰለቀጠ።
ላከከ፡ (ለሕሐ፡ ረጠበ)፡ ቀሳ፡ ደለሰ፡ ለጠፈ፡ አጣበቀ፡ ገጠመ፡ አመካኘ ።(ግጥም)፡ አበ፡ ተቈጡልኝ፡ እመ፡ ቈንጥጡልኝ፡ እሷ፡ በፈሳ ችው፡ በኔ፡ ላከከችው። ለደፈንና፡ ደፈደፈን፡ ተመልከት ።
ላኪነት፡ ላኪ፡ መኾን።
ላካኪ፡ የላከከ፡ የሚላክክ፡ ቀቢ።
ላክ፡ አደረገ፡ በፍጥነት፡ ዋላ፡ ገን ፎን፡ ፍትፍትን።
ላክ፡ (ልኢክ) ዋጥ፡ መዋጥ።
ላወሰ፡ ዞረ፡ ኳተነ፡ ለፋ፡ ደከመ። ዛሬ፡ እንዲያው፡ በከንቱ፡ ስላውስ፡ ውዬ መጣኹ።
ላዊ፡ የፊደል፡ ስም፡ ለ፡ ጠማማ፡ ቈልማማ፡ ማለት፡ ነው ።መዝገበ፡ ፊደል፡ እይ ።
ላዘነ)፡ አላዘነ)፡ በንቅልፍ፡ ልቡ፡ ጮኸ፡ አንቋረረ፡ የሰው፡ የበሬ "
ላዘገን፡ ተመልከት ።
ላዙና፡ የሐሞት፡ ወርቅ፡ ከበሬ፡ ሆድ፡ የሚገኝ፡ በውስጡ፡ ወርቅ፡ ውሃ፡ ያለበት፡ ብጫ፡ የሚመስል፡ የልፋጭ፡ ከረጢት፡ በደረቀ፡ ጊዜ፡ ፈረንጆች፡ ሱካር፡ ለሚሉት፡ በሽታ፡ ከሻይ፡ ጋራ፡ እየተጠጣ፡ መድኀኒት፡ ይኾናል፡ ይላሉ ።ላዙና፡ የሚነገረው፡ በሐረርጌ፡ የሚገኘውም፡ በኦሮ፡ ቤት፡ ነው ።
ላዛ፡ ልስላሴ፡ ለስላስነት፡ የጠጕር ።
ላይ፡ ቤት፡ (የላይ፡ ቤት)፡ ደርብ፡
ላይ፡ ቤት፡ ገነትመንግሥተ፡ ሰማይ።
ላይ፡ ወደ፡ ዛፍ፡ ላይ፡ ከላይ፡ ከተራራ፡ ላይ፡ ከላይ፡ ወረደ፡ ከላይ፡ መጣ፡ ይላል። (ተረት)፡ ከራስ፡ በላይ፡ ነፋስ። እንጃን፡ ተመልከት።
ላይ፡ ቤት፣ በጐንደር፡ የነበረ፡ የጉባኤ፡ የመጻፍ፡ ትርጓሜ፡ ትምርት፡ ቤት።
ላይ፡ ቤት፡ በመራቤቴ፡ ያለ፡ ቀበሌ ።ኼደ፡ አፋፍ፡ አፋፉን፡ ላይ፡ ላዩን፡ ደጋ፡ ደጋውን፡ ዐለፈ፡ ነጐደ።
ላይ፡ (ላዕል፡ ለዐለ)፡ ደቂቅ፡ አገባብ፡ ደጋ፡ ሰማይ፡ ሽቅብ፡ ዐቀበት፡ ከፍታ፡ በታች፡ በግርጌ፡ በሥር፡ አንጻር፡ ያለ፡ ከፍተኛ፡ ስፍራ፡ ራስ፡ ራስጌ፡ ጫፍ፡ ውልብልቢት፡ በ፡ ማድረጊያ፡ ወደ፡ መገሥገሻ፡ ከ፡ መነሻ፡ ኹነው፡ ያለስምና፡ ከስም፡ ጋራ፡ በመነሻው፡ እየገቡሲነገሩ፡ በላይ፡ በሰማይ፡ ላይ፡ በሰው፡ ላይ፡ ወደ፡
ላይና፡ ታች፡ ሰማይና፡ ምድር፡ ደጋና፡ ቈላ፡ ራስጌና፡ ግርጌ።
ላይኛ፡ (ላዕላይ)፡ የላይ፡ የሰማይ፡ በላይ፡ ያለ፡ የሚኖር፡ ሲዘረዝር፡ ላይኛው፡ ይላል፡ ላይኞች፡ ደገኞች፡ በላይ፡ የሚኖሩ፡ መላእክት፡ ጻድቃን ።
ላይዳ፡ አለ፡ በላይዳ፡ እኸልን፡ ወደ፡ ላይ፡ ወረወረ፡ በተነ፡ ለነፋስ፡ ሰጠ፡ ፍሬን፡ ከገለባ፡ ለየ፡ አመረተ ።
ላይዳ፡ ላሜዳ፡ (ላዩ፡ ሜዳ)፡ ከንወት፡ የታነጸ፡ ዝርግ፡ ሾጣጣ፡ ያውድማ፡ ማንካ ።ሲበዛ፡ ላይዶች፡ ላሜዶች፡ ይላል ።ላሜዳ፡ ከለመ ደም፡ ሊወጣ፡ ይችላል።
ላዳን፡ (ኖች)፡ የመስፈሪያ፡ ስም፡ የዳውላ፡ እኩሌታ፡ ፲፡ ቍና፡ የሚይዝ፡ ቅርጫት፡ ማ ድጋ፡ እንቅብ።
ላገ፡ (ልሕገ። ትግ፡ ለሐገ፡ ላከ፡ ዐነጠ፡ ዐነጠጠ፡ ፋቀ፡ አለዘበ፡ እለሰለሰ። ልሕገ፡ ጥንታዊ፡ ዐማርኛ፡ ነው ።
ላገ፡ ሳባ፡ አጠበቀ፡ መጫኛን። ላገ፡ አማሰለ፡ ገንፎን።
ላገ፡ ዐለበ። (የረኛ፡ ግጥም)፣ የክትክታ፡ ሞፈር፡ የሚያረገው፡ እመቤቴ፡ ማሪያም፣አን ዠትኸን፡ ትላገው።
ላገ፡ ጠባ፡ ለገለገ።
ላገር በቅ፡ ያንድ ብቁ እንዲሉ ።
ላጊ፡ (ለሓጊ)፡ የላጊ፡ የሚልግ፡ ዐናጢ፡ ፋቂ፡ ጠቢ። ላም፡ ላጊ፡ እንዲሉ።
ላጊ፡ ጕንዳን፡ የጤፍን፡ ፍሬ፡ ከነገለባው፡ የሚያጠፋ፡ ኣገዳውን፡ ባዶ፡ የሚያስቀረው፡ የተ ፋቀ፡ የሚያስመስለው።
ላጠ፡ ሻረ፡ ለወጠ።
ላጠ፡ ዐማ፡ ስም፡ አጠፋ።
ላጠ፡ እንዳህያ፡ ፈሳ፡ ፈሱን፡ ለቀቀ። ላጠ፤መዘዘ፡ ጐራዴውን ።
ላጣ (ጦች)፡ የለጠ/የሚልጥ፡ ዳላጣ ወፍጮ፡ ሥራ ፈት/ማጋጣ።
ላጤ፡ መላጤ፡ ልብስ፡ ያረረበት፡ ፍጹም፡ ድኻ፡ ትፈሳ፡ ዶሮ፡ የሌለችው፡ የተላጠ፡ የተመለጠ፡ ግንድ፡ የሚመስል ።
ላጤ፡ የተላጠ፡ የተገፈፈ።
ላጤ፡ ፈሳም፡ ዕፍረተ፡ ቢስ።
ላጥ፡ አደረገ፡ በኀይል፡ ፈሳ።
ላጥ፡ ላጥ፡ አለ፡ ልጥኛ፡ ጮኸ፡ ተፈሳ።
ላጥ፡ (ልሒጽ)፡ መላጥ ።
ላጥሻ)፡ መሻር መሻር (ዕብ. ፯፡ ፲፰) ።
ላጨ ለጠጠ፡
ላጩ፡ (ላጸየ)፡ ጠጕርን፡ በምላጭ፡ ከራስ፡ ከጕንጭ፡ ካገጭ፡ ከኀፍረት፡ ላይ፡ ፈገፈገ፡ ገፈፈ፡ ጠረገ፡ አስወገደ ። (በደረቅ፡ ላፊ)፡ አታ ሰለ ።
ላጩ፡ ረባ፡ ጠቀመ፡ ውለታ፡ መለሰ።
ላጪ፡ (ጮች)፡ የላጨ፡ የሚላጭ፡ ራስ፡
ላጪ፡ የላጪን፡ ልጅ፡ ቅማል፡ በላት፡ እንዲሉ። በግእዝ፡ ላጻዪ፡ (ላጸይት)፡ ይባላል።
ላጪታ፡ (ላጻዪት)፡ የላጨች፡ የምትላጭ፡ ለሴት፡ ብቻ፡ ይነገራል ።
ላጭ፡ (ለሓጺ)፡ የላጠ፡ የሚልጥ፡ ሐሜተኛ፡ ሰው፡
ላጲስ፡ ላፒስ፡ በደረቅ፡ ርሳስ፡ የተጻፈ ጽፈት፡ ማጥፊያ፡ እውነተኛ፡ ስሙ፡ ጎማ፡ ይባላል ።ጣሊያኖች፡ ግን፡ ላፒስን፡ ርሳስ፡ ይሉታል፣ ዐማሮችም፡ ጎማውና፡ ርሳሱ፡ ባንድነት፡ ስለተገኙ፡ የጎማውን፡ ስም፡ በስሕተት፡ ለርሳሱ፡ ሰጥተውታል ።
ላፈ ፣ አቃጠለ፡ ፈጀ፡ ላጠ፡ አካልን።
ላፈ፡ በፍጥነት፡ በላ፡ ጠጣ፡ ሙቅ፡ ም
ላፈን፡ ፈጀን፡ አቃጠለን፡ ላጠን።
ላፈደ ፣ ለፋ፡ ጋጠረ፡ ደከመ ።
ላፊ ፣ የላፈ፡ የሚልፍ፡ የሚጠጣ።
ሌለ፡ (የለ)፡ የአለ፡ አሉታ፡ የየለ፡ መንትያ ። አልነበረ፡ አልተገኘ ።የና፡ ለ፡ ተወራራሽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ የለ፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ሌለ፡ ይላል። የ፡ መነሻ፡ ሲኾነው፡ በቂና፡ ቅጽል፡ ይኾናል።
ሌሊት፡ (ቶች)፡ የጨለማ፡ ስም፡
ሌላ፡ (ሎች)፡ ኹለተኛ፡ ልዩ፡ ባዳ ።
ሌላ፡ ሌላ፡ አለ፡ ጣዕም፡ ለወጠ፡ ምግቡ፡ መጠጡ ።
ሌላ፡ ነገር፡ ሌላ፡ ሰው፡ እንዲሉ።
ሌላ፡ በቀር፡ ("ዘፀ. ፲፪፡ ፴፯ ። ኢሳ. ፷፬፡ ፬ ። ፷፭፡ ፳፪") ።
ሌላኹለተኛ፡ ለየ።
ሌሌ፡ አለ፡ አዘመረ፡ በማሲንቆ፡ ዘፈነ፡ ቀነቀነ።
ሌሌ፡ ዘፋኝ፡ አመስጋኝ፡ ማለት፡ ነው ።
ሌሌ፡ (ሌለየ። ዕብ፡ ሀሎል)፡ የማሲንቆ፡ ዘፈን፡ አዝማች ።አያ፡ ሌሌ፡ ሌሌ፡ እን ዲል፡ አዝማሪ።
ሌቃ፡ በኦሮ፡ ቤት፡ ያለ፡ አገር።
ሌቃያቅኒው፡ ስም፡ ነው፡
ሌባ ሻይ ("ፈላጊ የውሸት መድኀኒት ጠጥቶ ወገበንበመቀነት ይያዝና ሌባ ይሻል ወይም ተ 700 ") ።
ሌብነት፡ ሌባ፡ መኾን፡ ሰራቂነት።
ሌቦ ቃለ አኅስሮ ("የማዋረድ ቃል ሌቦ ሣህሉ የታወቀ ሌባ በሥደር መንግሥት የነበረ አንዲት አሮጊት ሌቦ ሣህሉ እንዳይወስድብኝ ስልቻዬን ብ ቅልኝ ብትለው ወይ አለመተዋወቅ ሌቦ ሣህሉ ይሉሻል እኔ ነኝ ዕንቺ ስልቻሽ አለ ይላሉ ሌባሻይ ") ("ዮች") ።
ሌታ፡ ሌት፡ ሌሊት ለየ።
ሌታቀን፡ (ሕብረ፡ ከብድ)፡ ጕበት፡ የሚመስል፡ ግምጃ፡ የቀንና፡ የሌት፡ ኹናቴ፡(ብርሃንና፡ ጨለማ)፡ የሚታይበት ።
ሌት፡ ቀኑ፡ ሌት፡ እንደ፡ ቀን፡ የሚያይ፡ የሌት፡ ወፍ፡ ጕጕት። ሊልንና፡ ሲሎን፡ እይ፡ የዚህ፡ ዘሮች፡ ናቸው።
ሌት፡ ቀኑ፡ ያሜሪካ፡ ኣዝርና፡ ሕዝብ።
ሌት፡ ተቀን፡ ሌት፡ ከቀን፡ ጋራ ' ወ ይም፡ ሌትና፡ ቀን። እከሌ፡ ሌት፡ ተቀን፡ ይሠራል ።
ሌት፡ ሌት፡ ያማርኛ፡ ሌሊት፡ የግእዝ፡
ሌንች፡ በአካንዱራ፡ ጨዋታ፡ ጊዜየሚነገር፡ ቃል፡ ይኸውም፡ አንዲቱን፡ የልት፡
ሌዊ፡ የሰው፡ ስም፡ ካ፲፪ቱ፡ ነገደ፡ እስራኤል፡ ፩ዱ፡ ሀብተ፡ ክህነት፡ የተሰጠው፡ ትር ጓሜው፡ (ልጹቅ)፡ የቀረበ፡ ማለት፡ ነው፡ (ኪ፡ ወ፡ ክ) ።
ሌዋታን፡ ለዘበ፣
ሌዋታን፡ ያውሬ፡ ስም፡ በዓለም፡ ዙሪያ፡ በባሕር፡ በኩል፡ ተጋድማ፡ ያለች፡ እንስት፡ ዓሣ፡ ነባሪ፡ ("ኢዮ. ፵፡ ፳፭ ።ሱቱ፡ ዕዝ. ፮፡ ፵፱-፶፪")፡ ዳግመኛም፡ ዘንዶ፡ ትባላለች፡ ክፉ፡ ቀንን፡ ዙሪ ያው፡ ዘንዶ፡ ማለት፡ ከዚህ፡ የመጣ፡ ነው። ብሂሞትን፡ እይ ።
ሌዋዊ፡ (ውያን)፡ የሌዊ፡ ወገን፡ ነገድ።
ሌዋውያን፡ ካ፭ቱ፡ ኦሪት፡ ፫ኛው፡ ክ
ሌጣ፡ (ትግ፡ ሐባ፡ ብቻ)፡ ልጅ፡ የማታጠባ፡ የማታዝል፡ ሴት፡ ልጂ፡ ከዠርባዋ፡ የወረደላት።
ሌጣ፡ ወረጋ፡ ላጠ።
ሌጣ፡ ጭነት፡ ኮርቻ፡ በዠርባው፡ የሌለ፡ ፈረስ፡ በቅሎ፡ አህያ። ወረጋን፡ አስተውል።
ሌጦ፡ ቈዳ፡ ላጠ።
ሌጦ፡ የተለፋ፡ የበግ፡ ቈዳ፡ ዕላቂ፡ ጠጕሩ፡ የበነነ ።በግእዝ፡ መሊጦ፡ ይባላል፡ ስለ ዚህ፡ ዘሩ፡ መለጠ፡ ሊኾን፡ ይችላል። (እከሌ፡ ከቍንጫ፡ ሌጦ፡ ያወጣል)፡ ይቀልዳል፡ ይነቅፋል ።
ልለሳለስ፡ የሴት፡ ባሪያ፡ ስም፡
ልላጭ፡ የሽንኩርት፡ የድንች፡ ልብስ፡ ገለባ።
ልል፡ (ልእል)፡ እኔ፡ ለሚል፡ ፫ኛ፡ ዘንድ፡ አንቀጽ ።ኣልኹ፡ እል፡ እል፡ ዘንድ፡ እን ድል፡ ልል፡ እፈቅዳለኹ። አለን፡ ተመልከት።
ልመት፡ (ልሕመት)፡ ልዘባ፡ ደቃቅነት፣ ልዝብነት፡ ልስላሴ።
ልመና፡ ምልጃ፡ ጸሎት፡ መለመንፈፋ፡ ቧገታ፡ ("፩ነገ. ፰፡ ፵፭ ። ዳን. ፮፡ ፲፫ ። ኤፈ. ፲፰") ። ዛርልመና፡ ሳይያዙ፣ገና።ያንበሳ፡ ልጋማ፡ ይዞ። የልመና፣ እኽል፡ እንዲሉ።
ልመደው፡ ያሞሌ፡ ስም፡ ፪፡ አሞሌ፡ የሚያነሣ - ፩፡ አሞሌ ።
ልሙጥ፡ (ልሙጽ)፡ ጌጥ፡ የሌለው፡ የበቅሎ፡ ዕቃ፡ ዝናር ።
ልሙጥ፡ ብርሌ፡ ሰንበር፡ አልባ።
ልሙጥ፡ አለጥለት፡ የተሠራ፡ ሸማ።
ልማም፡ ሰው፡ ብዙ፡ ጊዜ፡ ሲታመምከትኵሳት፡ ብዛት፡ የተነሣ፡ በጥርሱ፡ ላይ፡ የታይ፡ እድፍ፡ ብ። ቸክን፣ ተመልከት።
ልማም፡ ያዘ፡ ለመመ፡ ቈሸሸ።
ልማት፡ ልምላሜ፡ ብጀታ፡ ብዛት ።
ልማደኛ፡ (ኞች)፡ ልማዳም፡ ባለልማድ፡ ልማድ ያለው፡ ዐመለኛ፡ ይኸውም፡ ክፉና፡ በጎ፡ ነው።
ልማድ፡ (ዶች)፡ ዐመል፡ ደንብ፡ ሕግ፡
ልማድ፡ በኀላፊ፡ አንቀጽ፡ መነሻ፡ የሚጨመር፡ ፊደል፡ እ፡ አን፡ አስ፡ አስተ፡ አሽ፡ ተ፡ ተን ።
ልማድ፡ ትንባኾ፡ ጫት፡ ቡና፡ ጠጅ፡ ዐረቄ፡ ልዩ፡ ልዩ፡መብልና፡ መጠጥ ፣በያንዳንዱ፡ ሰው፡ ዘንድ፡ ዘወትር፡ ተፈላጊ፡ የኾነ፡ ነገር፡ ኹሉ፡ ልማድ፡ ይባላል ። (ተረት)፡ ክፉ፡ ልማድ፡ ያሰርቃል፡ ከማድ።
ልም፡ ዕቃ፡ ምራን፡ የመርገጥ፡ የማነቆ፡
ልም፡ (ልሑም)፡ የላመ፡ ልዝብ፡ ልስልስ፡ የድመት፡ ጠጕር፡ ደቃቅ።
ልም፡ (ልሙዕ)፡ የለማ፡ ዐዲስ፡ ግብር፡ ባባት፡ የሌለ፡ ከተዠመረ፡ እየለማ፡ የኼደ።
ልም፡ የለማ፡ ለማ።
ልም፡ የደከመ፡ ደካማ።
ልምለማ፡ መለምለም።
ልምላሜ፡ ዝኒከማሁ፡ ጠል፡ ርጥበት፡ ለምለምነት ።
ልምምጥ፡ መለማመጥ።
ልምሹ፣ ልምሾ፡ (ዎች)፡ የለመሸ፡ ጥምልምል፡ አምልማሎ፡ እግር፡ ሽባ፡ እጀ፡ ሰላላ።
ልምሾ፡ አደረገ፡ (አዕወሰ)፡ አጥመለመለ፡ ሽባ፡ አደረገ ።
ልምሾነት፣ ልምሾ፡ መኾን፡ ሽባነት።
ልምን፡ የተለመነየተቀፈፈ የልመና፡ እኸል፡ ወይም፡ ሌላ፡ ነገር።
ልምክክ፡ አለ፡ ልክክ፡ ምርግ፡ አለ። ላመል፡ ጥቂት፡ ዐመል።
ልምክክ፡ የተለመከከ፡ የተላከከ።
ልምዘጋ፡ ቍንጠጣ፡ ቍንጥ።
ልምዝግ፡ አደረገ፡ ቍንጥጥ፡ አደረገ -
ልምድ፡ ልማድ፣ የተለመደ፡ የተጠና፡ የታወቀ፡ ዕውቅ ።
ልምጥ፡ አለ፡ ጕብጥ፡ አለ።
ልምጥምጥ፡ አለ፣ ብዙ፡ ጊዜ፡ ተለ
ልምጥምጥ፣ የተለማመጠ።
ልምጥጥ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ልምጥጥ፡ አለ፡ (ውዕየ)፡ ቅጥል፡ አለ፡ ተለመጠጠ ።
ልምጭ፡ አይነካሽ፣ የሥጋ፡ ስም፡ ጡንቻ፡ ነብሮ
ልምጭ፡ (ልብኔ)፡ የንጨት፡ ስም፡ ልጠ፡ ጥቍር፡ ዛፍ፡ እየተቀረጸ፡ መስቀል፡ ይኾናል፡ አቋቋሙ፡ ድግጣ፡ ይመስላል ።የስሙ፡ ምስጢር፡ መለመጥንና፡ መለስለስን፡ ያሳያል ።
ልምጭ፡ (ጮች)፣ ከእሓያና፡ ከወይራ፡ ከቀጨሞ፡ ከሌላውም፡ ቀጥታ፡ ካለው፡ ዕንጨት፡ የተቈረጠ፡ ቀጫጪን፡ አርጩሜ፡ አሽንቋጦ፡ ጨንገር።
ልምጭጭ፡ አለ፡ ተለመጪ።
ልምጭጭ፡ አለ፡ እንደ፡ ሙጫና፡ እንደ፡ ቅቤ፡ ኾነ፡ ሞቀሞቀ፡ ዳቦው ።
ልምጭጭ፣ የተለመፊ፣ ለጣሳ።
ልሰቃ፣ የመለሰቅ፡ ሥራ፡ ጭፈቃ።
ልሰና፡ የመለሰን፡ ሥራ፡ ልቅለቃ።
ልሳሽ፡ ለውጥ፡ ድጋሚ ።የነገር፡ ልሳሽ እንዲሉ።
ልሳሽ፣ በመስከረም፡ የታጨደውን፡ የብስ፡ ብር፡ ወዲያው፡ እየላሰሱ፡ የሚዘሩት፡ የሽን ብራና፡ የጓያ፣ ዘር።
ልሳነ፡ ምድር፡ ወደ፡ ባሕር፡ የገባ፡ የምድር፡ ሠላጤ።
ልሳነ፡ ባሕር፡ ወደ፡ የብስ፡ ወይም፡ ወዳገር፡ የገባ፡ የባሕር፡ ሠላጢ። ፈረንጆች፡ ጎልፍ፡ ይሉታል።
ልሳነ፡ ዓለም፡ መንፈስ፡ ቅዱስ፡ ያንዱን፡ ቋንቋ፡ ለሌላው፡ ገልጦ፡ የሚያናግር ።
ልሳነ፡ ዓለም፡ ሰው፡ ኩሉ፡ በያገሩ፡ የሚናገርበት፡ ቋንቋ።
ልሳነ፡ ዓለም፡ የዓለም፡ መገናኛ፡ ቋንቋ ።ከ፲፱፻፴፫፡ ዓ፡ ም፡ በፊት፡ ፈረንሳይኛ ከዚያ፡ ወዲህ፡ እንግሊዝኛ።
ልሳኑ፡ ተዘጋ፡ መናገር፡ አቃተው ዝም፡ አለ ።
ልሳን፡ ቋንቋ፡ በልሳን፡ (ምላስ)፡ የሚነግር ።ለዝማሪና፡ ለሐሚና፡ ከግእዝና፡ ካማርኛ፡ የማይገጥም፡ ሌላ፡ የምስጢር፡ ልሳን፡ አላቸው።
ልሳን፡ የመጥረቢያ፡ ጕረሮ። ይህ፡ ምሣር፡ ልሳኑ፡ ጠቧል፡ ዛቢያ፡ አያስገባም።
ልሳን፡ የሰይፍ፡ ስለት፡ ("ራእ. ፪፡ ፲፪") ።
ልሳን፡ መባል፡ የሚገባው፡ ለስለቱ፡ ነበር።
ልሳን፡(ኖች)፡ ምላስ፡ አንደበት፡ የነገር፡ ሕዋስ። እከሌ፡ ልሳኔን፡ ይዝጋው፡ ብሎ፡ ማለ።
ልሳን፡ የሚዛን፡ መርፌ ።
ልሳኖ፡ (ትግ)፡ ትርፍ፡ ምላስ ።
ልስ፡ የተላሰሰ፡ ንቅል ።
ልስለሳ፡ ልዘባ።
ልስላሴ፡ ልዝብነት ።
ልስልስ፡ አለ፡ ልዝብ፡ አለ ።
ልስስ፡ አለ፡ ንቅል፡ አለ፡ ተላሰሰ።
ልስቅ፡ አለ፡ ተለሰቀ፡
ልስቅ፡ (ልጹቅ) ቀጥ፡ ያለ።
ልስን፡ (ስም)፡ የምርግ፡ ወይም፡ የልጥፍና፡ የትምትም፡ መጨረሻሥራ ።የዚህ፡ ቤት፡ ልስኑ፡ ያምራል ።
ልስን፡ (ቅጽል)፡ የተለሰነ፡ ቅብ፡ ልቅልቅ ።
ልሻ፡ ጠጕር፣ ጠጕሩ፡ እንደ፡ ልሻ፡ ቍልቍል፡ የሚያድግ፡ ሰው።
ልሻ፡ ለስላሳ፡ ያረኸ፡ የገደል፡ ሣር፡ እ ንደ፡ ጭድ፡ ከጭቃጋራ፣ የሚስማማ፡ እንስት፡ ገርሣ ።
ልሻን፡ ሽልማት ኒሻን ።
ልሽልሽ ፣ የተለሸለሸ፡ የተኛ።
ልቍጥ፡ በርበሬ ፣ውሃ፡ የገባበት፡ ድልኸ፡ የታሸ፡ የተለወሰ።
ልቍጥ፡ የላቈጠ፡ ልውስ፡ ጭቃ፡ ሊጥ፡ መድኀኒት።
ልቍጦሽ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለልቍጥ ።
ልቃቂት፡ (ቶች)፡ ክንዝርት፡ የወጣ፡ የወለቀ፡ የተለየ፡ የድርና፡ የማግ፡ ፈትል።
ልቅ፡ ልቃቂት፡ ልቅ፡ ያኽል፡ ጐረሠእንዲሉ ።
ልቅ፡ የተለቀቀ፣ስድ፣ አግድሞ፡ አደግ መረን ።
ልቅ፡ ወጣች፡ አንድም፡ ነገር፡ ሳትካፈል፡ ሳትይዝ፡ ባዶ፡ እጇን፡ ኼደች፡ ነውረኛዪቱ፡ ሴት ላቀቀ፡
ልቅ፡ (ለቃቂ)፡ የለቀቀ፡ የተወ፡ ባዶ፡ እንዳች፡ አልባ።
ልቅ፡ ስድ ለቅዳ- ለግዳ፡ ቅምሖ ።
ልቅለቃ፡ (ልቅላቄ) ፣ የመለቅለቅ ሥራ፡ ዐጠባ፣ እስክስታ፡ ውዝዋዜ። ዋንጫ፡
ልቅሶ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ("፪ዜና. ፴፭፡ ፳፭ ። ኤር. ፱፡ ፲፰") ።በግእዝ፡ ብካይ፡ ይባላል ።
ልቅና ፣(ልህቅና)፣ዝኒ፡ ከማሁ፡ አለቃ፡ መኾን።
ልቆ፡ (ልቃሕ)፡ ብድር ።
ልቆኛ፡ ኹል፡ ጊዜ፡ የሚበደር፡ ከልቆ፡ የማይወጣ።
ልበ ቢስ፡ (ሶች)፡ ቀልበ፡ ቢስ፡ ዝንጉ ።
ልበ ብርቱ፡ የማይፈራ፡ የማይፈታ ጨካኝ ።
ልበ ክፍት፡ ብልኅ፡ ማንኛውም፡ ሥ ራና፡ ነገር፡ ቶሎ፡ የሚገባው።
ልበ ውልቅ፡ ስልቹ።
ልበ ደረቅ፡ ዐዘኔታና፡ ርኅራኄ፡ የሌ
ልበ ደንዳና፡ ዐሳብ፡ የለሽ። ሲበዛ፡ ልበ፡ ደንዳኖች፡ ይላል፡ ("ኢሳ. ፵፯፡ ፲፪") ።
ልበ ደንጊያ፡ የነገሩትን፡ የማይሰማ።
ልበ ደፋር፡ ጐበዝ፡ ኀይለኛ "
ልበ ጡል፡ ልቡ፡ የዞረ፡ እብድ፡ ዐይነት።
ልበ ጥኑ፡ ጨካኝ፡ ወርጅ ።
ልበ ጨካኝ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለልበ፡ ደ
ልበል፡ ዕብለት ልናገር ("ባለን" አስተውል) ።
ልበኢ፡ ልብ፡ የለሽ፡
ልቡ ተሰቀለ)፡ ባንድ ሐሳብ ተያዘ።
ልቡ ተሰበረ)፡ ፈጽሞ ዐዘነ።
ልቡ ተሰወረ)፡ አበደ (አእምሮ ጠፋ) ።
ልቡ ገባ፡ አእምሮው፡ ተመለሰ ።
ልቡሰ ሥጋ ሥጋ የለበሰ ("ጋኔን ") ("በሰው ያደረ") ።
ልቡን ሰረቀው)፡ ከዳው ነሣው ።
ልባልባ፡ (ዐልባ፡ ልብ)፡ በሐርና፡ በወርቅ፡ የተጠለፈ፡ ባለማዕርግ፡ ሴት፡ የምታጠልቀው፡ ጌጠኛ፡ ሱሪ፡ ልብ ዐልባ፡ መባሉ፡ ገንዘብ፡ የልብ፡ ሥር፡ ስለ፡ ተባለ፡ ነው ።ልብ አልባ፡ ተብሎ፡ ቢጻፍ፡ ግን፡ እሱን፡ ያጠለቀች፡
ልባም፡ (ሞች)፡ ለባዊ)፡ ልብ፡ አ ድራጊ፡ አስተዋይ፡ የማይዘነጋ፡ ዠግና፡ ሐርበኛ ።ለበመን፡ ተመልከት፡ ከዚህ፡ የወጣ፡ ቅጽላዊ፡ ግስ፡ ነው ።
ልባም ዐዋቂ ("ልበኛነት ልባምነት ልቡና/ልቦና ልብ ልብነት የልብ ማስተዋል ትግሥት ልቦና ይስጥኸ እንዲሉ። ልቡና የግእዝ ልቦና ያማርኛ ነው ለበበ ") ("ለቢብ/ለበ/ሐሰለ") ።
ልባምነት (ልባዌ)፡ ልባም፡ መኾን፡ ("ሮሜ. ፲፪፡ ፰") ።
ልባጥ የጣራ የግንብ የግድግዳ መሸፈኛ ሉሕ ግምጃ ("የሣጥን የታቦት ተለጣፊ ማዕድን ሥሥ ብላጥን እይ ተለባበጠ ተሸላለፈ መለባበጥ መሸላለፍ መለባበጫ መሸላለፊያ አላበጠ አላጠፈ አሻፈነ አላበሰ አላበጠ አሠናበጠ አላጠጠ አለባበጥ ኣለጣጠፍ አሠነባበጥ መለበዋ ለበለበ ") ("ለበበ") ።
ልብ፡ (ቦች)፡ ለበበ፡ ለበወ)፡ ከው ስጥ፡ አካላት፡ አንዱ፡ የደም፡ መመላለሻ፡ ያሳብ፡ መፍለቂያ፡ ("መዝ. ፯፡ ፱") ። አልባብን፡ ተመልከት። (ግጥም)፡ ያውና፡ እዚያ፡ ማዶ፡ ፍሪዳ፡ ተጥሏል፡ ቢላዋው፡ ደንዞ፡ ልብ፡ አልቈርጥ፡ ብሏል።
ልብ ሰጠ ("ዐ ዋቂ አደረገ አልመተ 703 ") ።
ልብ አለ፡ ዐሰበ፡ ኣስታወሰ፡ አጤነ።
ልብ አሳጣ፡ ኣፈዘዘ፡ ኣሞኘ፡ አታ
ልብ አስደረገ፡ አሳሰበ ።
ልብ አቍስል፡ ጨቅጫቃ፡ አተካራም ።
ልብ አብርድ፡ ውሃ፡ ወተት ።
ልብ አብሽቅ፡ አሳዛኝ።
ልብ አብግን፡ አናዳጅ።
ልብ አንድድ፡ ዐረቄ፡ መጥፎ፡ መጠጥ ።
ልብ አውልቅ፡ (ቆች)፡ አሰልቺ ነዝናዛ ።
ልብ አደረገ ("ዐወቀ ዐዋቂ ኾነ መተ አስተዋለ ልብን እይ መላ ለበመ ሰፈረ አዘጋጀ አሰናዳ ሠየመ መላ ለባሚ ") ("መላኢ") ።
ልብ አደረገ፡ (ለበወ)፡ አጤነ፡ በልብ፡ አዋለ አሳደረ፡ አቈየ፡ ኣኖረ። ዋለ፡ ብለኸ፡ አስተዋለን፡ እይ።
ልብ አድራጊ፡ ያየውን፡ የሰማውን፡ የተማረውን፡ የማይረሳ፡ የማይዘነጋ።
ልብ አድርቅ፡ መንቻካ፡ ሰው፡
ልብ አድርግልኝ፡ እማኝ፡ ነኸ።
ልብ አጠፋ፡ ቀልበ፡ ቢስ፡ አደረገ።
ልብ ወለድ፡ ፈጠራ፣ መጽሐፈ፡ ጨ ዋታ፡ ወዳጄ፡ ልቤ፡ ጦቢያው፡ ረቅ ።
ልብ ወረደው፣ ደከመ፡ በሬው።
ልብ ውጋት፡ ዱሮ፡ ባገራችን፡ ይሠራ፡ የነበረ፡ ችንካር፡ ምስማር፡ እንደ፡ ካስማ፡ ያለ፲ ፪ቱን፡ ፬፡ ማእዘን፡ ያገናኛል።
ልብ፡ ዕውቀት፡ ማስተዋል፡("መዝ. ፴፪፡ ፰") ።ልብ፡ ሆድ፡ ደረት ።እከሌ፡ አሽከሩን፡ በ ልቡ፡ አስተኛና፡ ገረፈው።
ልብ፡ እውነት፡ ሐቅ፡ ልብ፡ ሳይዙ፡ ነገር፡ አያበዙ።
ልብ፡ ውስጥ፡ ቡጥ። (ተረት)፡ በገዛ፡ ዳቦዬ፡ ልብ፡ ልቡን፡ ዐጣኹት።
ልብሱን፡ ለወጠ)፡ የሠርክ፡ ልብሱን፡ አስቀምጦ፡ የክት፡ ልብስ፡ አሮጌውን፡ አኑሮ፡ ዐዲስ፡ ለበሰ።
ልብድ የብረት ቀሚስ ውስጤ ነት'ያርበኛን ገላ መለበጃ ("(፩ነገ. ፳፪፡ ፴፬) ጥሩርን ተመልከት ልብደ ሠሪ ልብድን የሚሠራ የሚያበጅ የሚሰፋ አለባበድ አለጓጐም መለበድ ለበጠ ") ("ለቢጥ/ለበጠ") ።
ልት፡ (ቶች)፡ የቅጠል፡ ስም፡ ዕንጨቱ፡ ጥንካሬ፡ የሌለው፡ የደረቀ፡ ቍስል፡ የሚያለሰልስ፡ ማላጋ፡ ቅጠል፡ የታወቀ፡ ዕውቅ፡ እንደ፡ ጐመን፡ እየቀቀሉ፡ ሲበሉት፡ ለሆድ፡ መድኀኒት፡ ይኾናል።
ልት፡ ቅጠል፣ ለተተ።
ልትት፡ አለ፡ እንደ፡ ልት፡ ኾነ፡ ድክም፡ አለ፡ ባዘተ።
ልትት፡ የለተተ ።መዠመሪያው፡ ት፡ ይጠብቃል ።
ልትጥፍ ("(አንተ) ልትጥፊ ልጥፍ እወዳለኹ ልጣፍ ልትጥፉ ልንጥፍ እንወዳ ለን የሣልሱና የሳድሱ ") ("ሊ/ል") ።
ልቼ፡ (ኦሮ፡ ልምጭ)، በደብረ፡ ብርሃን፡ አጠገብ፡ ያለ፡ ቀበሌ።
ልንቅጥ፣ የተለነቀጠ፡ የተላመ፡ ሊጥ።
ልዑላን ፣ ልዑላት፡ ከፍተኞች፡ ወንችና፡ ሴቶች።
ልዑል፡ (ለዐለ)፡ የነገሥታት፡ ብላጆች፡ የታላላቆች፣መሳፍንትና፡ ባላባቶች፡ የስነ ቅጽል፡ ትርጓሜውም፡ ከፍ፡ ያለ፡ በላይ፡ የኾ፣ላይኛ፡ ከፍተኛ፡ ማለት፡ ነው ።
ልዑል፡ እምልዑላን፡ ከከፍተኞች ልቅ፡ ከፍ፡ ያለ።
ልዑል፡ ወል ወራሽ፡
ልዑል፡ መኰንን፣ መስፍነ፡ ሐረር፡ ዲሉ።
ልዕልት፡ ከፍ፡ ያለች፡ ከፍተኛዋ፡ ኵና
ልዕልና፡ ከፍታ።
ልከኛ፡ (ምጡን)፡ የልክ፡ ዐይነት፡ ልክ፡ ያለው፡ ባለልክ፡ መጠነኛ፡ እኩያ፡
ልኵስ፡ አደረገ፡ ትኵስ፡ አደረገ።
ልኵስ፡ የተለኰሰ ።
ልኵስኵስ፡ የተልኰሰኰሰ፡ መስክ፡ ዝሪት።
ልኵፍ፡ የተለኰፈ፡ ትንኰስ።
ልኵፍኵፍ፡ አለ፣ ኵልፍልፍ፡ አለ። ኰለፈን፡ እይ።
ልኵፍኵፍ፡ የተልኰፈኰፈ፡ ኵልፍልፍ።
ልክ፡ ናቸው፡ መንቶች፡ ልጆች፡ ትክክል፡ ናቸው፡ አይበላለጡም ።
ልክ፡ የለሽ፡ የሴት፡ መጠሪያ፡ ስም።
ልክ፡ የለኸ፡ የወንድ፡ መጠሪያ፡ ስም፡ ለሰውነትኸ፡ አቻ፡ ለሀብትኸ፡ ወሰን፡ የለውም፡ ማለት፡ ነው ።
ልክ፡ ነው፡ ምሉ፡ ነው፡ አልጐደለም፡ አልተረፈም ።
ልክ፡ ዐቅም፡ ቅጥብ፡ ዕለተ፡ ሞት። ሰው፡ ከልኩ፡ አያልፍም።
ልክ፡ ኾነ፡ መላ፡ ደረሰ፡ ገጠመ።
ልክ፡ መጠን፡ ስፍር፡ ("ነሐ. ፫፡ ፲፱, ፳, ፳፩") ። ሲበዛ፡ ልኮች፡ ይላል። ውሃን፡ ተመልከት።
ልክስክስ፡ (ሶች)፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ አመንዝራ፡ ርኩስ፡ ዐሣማ፡ ውሻ፡ ዝንብ ።
ልክስክስ፡ ነገር፡ የማይረባ፡ ፈሎ፡ ቢስ ።
ልክስክስ፡ አለ፡ ተልከሰከሰ ።
ልክስክስ፡ (ሰልቢባ)፡ የሚዞር፡ የሚጥወለወል፡ ባንድ፡ ስፍራ፡ ቀጥ፡ ብሎ፡ የሚቆም፡ ዐውሎ፡ ነፋስ ።
ልክና፡ መልክ፡ የሕዋሳትን፡ ኹለትነትና፡ ትክክልነት፡ አንድ፡ ዐይነት፡ መኾንን፡ ያሳያል ።
ልክክ፡ አለ፡ ግጥም፡ አለ።
ልክክ አደረገ፡ ግጥም፡ አደረገ።
ልክክ፡ የተላከከ። ፩ኛውንክ፡ አጥብቅ ።
ልክፍ፡ አለ፡ ድቅን፡ አለ፡ ተለከፈ፡ ስ
ልክፍት፡ ጥንተ፡ ደዌ፡ የበሽታ፡ ዥምር'ውጥን ።በግእዝ፡ ግን፡ የተለከፈች፡ ማለት፡ ነው፡
ልክፍክፍ፡ የተልከፈከፈ፡ የተልከሰከሰ፡ ልክስክስ፡ የውሻ፡ ያሣማ፡ ዐይነት።
ልኰሳ፡ ትኰሳ።
ልኮሽ፡ መላክ፡ እሱ፡ አንቺን፡ ልኮሽ፡ ቢል፡ ቦዝ፡ ይኾናል።
ልኰፋ፡ ትንኰሳ ።
ልወሳ፡ የማላቈጥ፡ የማዋዋድ፡ ሥራ።
ልወጣ፡ ቅየራ፡ የመለወጥ፡ ሥራ
ልውስ፡ አለ፡ ቅስቅስ፡ ንቅንቅ፡ አለ።
ልውስ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለለዋሳ፡ ቅልቅል፡ ልቍጥ፡ ሊጥ፡ ቅቤና፡ አዶስ ።
ልውጡ፡ የራስ፡ ወሌ፡ ዘዬ፡ ፈሊጥ ።
ልውጥ፡ ግልብጥ፡ እንዲሉ።
ልውጥ፡ (ውሉጥ)፡ የተለወጠ፡ ቅይር።
ልውጥ፡ አለ፡ ተለወጠ ።
ልውጥ፡ አደረገ፡ ለወጠ ።
ልውጥነት፡ ልውጥ፡ መኾን ።
ልውጥውጥ፡ አለ፡ ተለዋወጠ።
ልውጥውጥ፡ የተለዋወጠ።
ልዘባ፡ ልስለሳ ።
ልዝብ፡ ጠርብ፡ በዕቃ፡ መጥረቢያ፡ የተጠረበ፡ በመላጊያ፡ የተላገ፡ ሰፊና፡ ጠባብ፡ የን ጨት፡ ሉሕ።
ልዝብ፡ (ቦች)፡ የለዘበ፡ ልስልስ፣ልም' ደቃቅ፡ ዐይንቢጨምሩት፡ የማይቈረቍር ዶቄት፡ የድመት፡ ጠጕር፡ ሰላማዊ፡ ሰው፡
ልዝብ፡ አለ፡ ላም፡ ልስልስ፡ ድቅቅ፡ አለ፡
ልዝብ፡ ደንጊያ፡ ልሙጥ፡ የለሰለሰ፡ አለት፡ ("ኢሳ. ፶፯፡ ፮") ።
ልዝብነት፡ ልዝብ፡ መኾን ።
ልዩ፡ ልዩ፡ (ዘዘ፡ ዚኣሁ)፡ የልዩ፡ ልዩ፡ እየብቻ፡ እየብቻው፡ እየራስ፡ እየራሱ፡ እየቅል፡ እየቅሉ፡ የኾነ፡ ነገር፡
ልዩ፡ ፍጥረት፡ የሌት፡ ወፍ።
ልዩ፡ (ሊሉይ)፡ የተለየ፡ እንግዳ፡ ባዕድ፡ ከሌላው፡ የዘር፡ የልማድ፡ አንድነት፡ ኅ ብረት፡ የሌለው፡ ("ዘሌ. ፳፡ ፳፬") ። ልዩ፡ ነገር፡ ልዩ፡ ሥራ፡ እንዲሉ። የሥላሴ፡ ባሕርያቸው፡ አንድ፡ ሲኾን፡ አካላቸው፡ ልዩ፡ ነው። ሲበዛ፡ ልዩዎች፡ ይላል።
ልዩ፡ ባሕታዊ፡ ግሑሥ።
ልዩነት፡ ልዩ፡ መኾን፡ ባዕድነት።
ልያ፡ የሴት፡ ስም፡ የላባ፡ ልጅ፡ የያዕቆብ፡ ሚስት ።
ልይት፡ አለ፡ ክፍል፡ አለ፡ ተለየ።
ልይት፡ ልዩ፡ የተለየ፡ የተከፈለ።
ልይትአደረገ፡ ክፍል፡ አደረገ፡ ለየ።
ልይትይት፡ አለ፡ ንጥልጥል፡ አለ።
ልይትይት፡ የተለያየ፡ የተፈራረቀ፡ የተነጣጠለ ።
ልደተ ወልድ፡ የወልድ መወለድ ("የክርስትና ስም") ።
ልደታ፡ የታቦት፡ ስም፣ወለደ።
ልደት፡ መወለድ፡ ወለደ ።
ልዳ፡ ያገር፡ ስም፡ በእስያ፡ ውስጥ፡ ያለ፡ የጊዮርጊስ፡ አገር።
ልድፋት፡ ልጥፋት ።
ልድፍ፡ አለ፡ ልጥፍ፡ አለ፡
ልድፍ፡ ልጥፍ።
ልጅ (ጆች) (ወልድ)፡ ያራስ የጨ ቅላ የሕፃን የትንሹም የትልቁም የወንዱም የሴቱም የባሕርይ ስም ("ሰው ተወልዶ እስ ኪያድግ ድረስ የሚጠራበት አንተ ልጅ አ ንቺ ልጅ ልጅ ደረሰ ቤት ፈረሰ” እንዲሉ) ።
ልጅ፡ በቁሙ፡ ወለደ ።
ልገሳ፡ ስጦታ፡ ችሮታ፡
ልገገ (ጠገገ/ጸጐጐ)፡ ቅፍፍ አለ ("ጭጋግ ኾነ") ።
ልጕማት፡ የመለጐም፡ ስፌት፡ አኳዃን።
ልጕም፣ የተለጐመ፡ በቅሎ፡ ፈረስ፡ አህያ፡ አገልግል፡ የስፌት፡ ዕቃ፡ ጕልብ፡ ነት፡ ተንቤን፡ የለበሰ ።
ልጕድ፡ የተለጐደ፡ ልድፍ።
ልጋጋም፡ (ሞች)፡ ለሐጫም።
ልጋግ፡ (ሠወን)፡ ለሐጭ፡ እንደ፡ ድር፡ ያለ፡ ካፍ፡ ካንጓ፡ የሚወጣ፡ ("፩ሳሙ. ፳፩፡ ፲፫") ።
ልግ፡ (ልጉዕ)፡ የተለጋ፡ የተቀላ፡ ጥ
ልግስና፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ቸርነት፡ ("፪ቆሮ. ፱፡ ፲፩ ።፩ጢሞ. ፮፡ ፲፯") ።
ልግዕ፡ (ትግ፡ ልግዒ)፡ እንገር፡ ዐዲስ፡ ወተት " ልግዕ፡ ለግእዝም፡ ሊኾን፡ ይችላል ።
ልግድ፡ የተለገደ፡ በፈፋ፡ መካከል፡ የተቀረቀረ፡ ቋጥኝ፡ ገለብ ።
ልጐማ፡ የመለጐም፡ ሥራ።
ልጎሽ፡ ንጣጭ፡ ሊፍ፡ የሳንቃ፡ የማእ ዘን፡ ፍቄት።
ልጓም፡ (ሞች) የከብት፡ አፍ፡ መዝጊያ፡ እንዳይኼድ፡ እንዳይበላ፡ መከልከያ፡ መግቻ፡ መመለሻ፡ ("ምሳ. ፳፮፡ ፫") ። (ተረት)፡ ጠፍር፡ በሊታ፡ ብትኼድ፡ ልጓም፡ በሊታ፡ መጣች ።
ልጓም፡ ለቀቀ፡ በቀላል፡ ያዘ፡ ጨበጠ።
ልጓም፡ አላላ፡ ወደ፡ ፊት፡ ያዘ፡ ሽምጥ፡ ለመጋለብ ።
ልጓም፡ አወለቀ፡ ከፈረስ፡ ከበቅሎ፡ አፍ፡ አወጣ።
ልጓም፡ አጥባቂ፡ ልጓምን፡ ዐኝ፡ እያለ፡ ሽምጥ፡ የሚጋልብ፡ ("፪ዜና. ፳፰፡ ፲፱") ።
ልጓም፡ ጣሰ፡ አልመለስ፡ አልገታ፡ አለ፡ ፈረሱ።
ልጡ፡ የተራሰ፡ መቃብሩ፡ የተማሰ፡ በጣም፡ ያረጀ - ያፈጀ - የደከመ፡ ሽማግሌ ።
ልጣም፣ ብዙ፡ ልጥ፡ የሚወጣው፡ ዛፍ። ለጠመን፡ ተመልከት።
ልጣጭ፡ ሥንባጭ፡ ንጣይ፡ የልጥ፡ ዐይነት፡ ዕንጨት፡ ትርፍ፡ ድር ።
ልጥ፡ (ጦች)፡ ልሕጽ)፡ በቂዳ፡ እም ሳል፡ ከንጨት፡ ኹሉ፡ ላይ፡ የሚገፈፍ፡ በቅርፊት፡ ውስጥ፡ ያለ፡ ማሰሪያ፡ የሚኾን ።የሺ - ፍልጥ፡ ማሰሪያው፡ ልጥ፡ እንዲሉ ።
ልጥለጣ፡ የመለጥለጥ፡ ሥራ፡ ወቀጣ፡ ጥ ፍጠፋ።
ልጥቅ፡ አለ፡ እጅጉ፡ ጥቂት፡ መሰለ።
ልጥጥ፡ የተለጠጠ፡ የተነጠለ፡ ንጥል፡ የተቈነነ፡ ቍንን።
ልጥፋት ሽፍ ናት ("") ("ኢሳ. ፴፡ ፳፪") ።
ልጦ፡ ጕርዶ፡ ጕርዶ፡ እንቅጥቃጭ፡ ልጦ፡ እንዳለፈው። ስንዴ፡ እንደ፡ ቀይ፣ ሽንርት፡ ተልጦ፡ የሚያልቅ፡ ስለ፡ ኾነ፡ ንፋሹ፡ ልጦ፡ ተባለ። ኅዕቦን፡ እይ።
ልጦ፡ ጕርዶ፡ አወጣ፡ ፈተግ አነፈሰ፡ አበጠረ ።
ልጦ፡ የፍትግ፡ ስንዴ፡ እብቅ፡ ገለባ፡
ልጨኛ፡ (ኞች)፡ ልጭ፡ አድራጊ፡ ባለ ልጭ፡ ውለታ፡ ከፋይ።
ልጨኛነት፡ ልጨኛ፡ መኾን።
ልጩ፡ (ልጹይ)፡ የተላጨ፡ ጠጕሩ፡ የተጠረገ፡ ጐፈሬ፡ የሌለው። ከጨርቅ፡ ነጩ፡ ከበራ፡ ልጩ፡ እንዲሉ ።
ልጩ፡ (ትግ)፡ አጫዋች፡ ድንክ፡ ሰው፡
ልጭ፡ ረብ፡ ጥቅም፡ ወረታ፡ ውለታ ።
ልጭታት፡ የመላጨት፡ ኹናቴ አኳዃን። (ጥላ)መላጨት፡ መጠረግ፡ መወገድ፡ መው ደቅ፡ የጠጕር።
ልፊያ፣ የጨዋታ፡ ምት፡ ቍልመማ ።
ልፋም፡ ልፋጭ፡ ያለው፡ ባለልፋጭ፡
ልፋት፡ (ልፍዐት)፡ ጥረት፡ ድካም። አማረን፡ አስተውል።
ልፋጭ፡ ንፍጥ፡ መሳይ፡ ሥጋ ።
ልፍ፡ (ልፉዕ)፡ የለፋ፣የተለፋ፡ ደበሎ፡ ስልቻ፡ ቈርበት።
ልፍለፋ፡ የነገር፡ ብዛት።
ልፍት፡ አለ፡ ድክም፡ አለ።
ልፍት፡ ድክም።
ልፍጥ፡ (ልፉጽ)፣ የተለፈጠ፡ ልውስ።
ሎላልት፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ("ኢሳ. ፲፬፡ ፪ ። ዮሐ. ፯፡ ፵፭, ፵፮") ።
ሎሌ፡ በትን፡ ታናሽ፡ ዋንጫ።
ሎሌ፡ (ወዓሊ)፡ ምንደኛ፡ ታዛዥ፡ አሽከር ። (ተረት)፡ ቅልና፡ ድንጋይ፡ ተማቶ፡ ሎሌና፡ ጌታ፡ ተግቶ።
ሎሌነት፡ ሎሌ፡ መኾን፡ ምንደኛነት፡ አሽከርነት ።
ሎሌዎች፡ (ወዐልት)፡ ምንደኞች፡ ታ
ሎል፡ (ልዑል)፡ የታላቅ፡ ዛፍ፡ ስም፡ ዕንጨትነቱ፡ ክብደት፡ ያለው፡ በጊዜው፡ ከተቈረጠ፡ ጽላት፡ ይኾናል ።ሲበዛ፡ ሎሎች፡ ይላል ።
ሎሚ፡ (ዎች)፡ ለመለመ)፡ የተክል፡ ስም፡ የታወቀ፡ ተክል፡ ሽታው፡ የሚጣፍጥ፡ ለሥራይና፡ ለመርዝ፡ መድኀኒት፡ የሚኾን፡ ዕንጨቱም፡ ፍሬውም፡ ሎሚ፡ ይባላል። (ተረት)፡ ፶፡ ሎሚ፡ ላ፩፡ ሰው፡ ሸክም፡ ነው፡ ላ፶፡ ሰው፡ ጌጥ፡ ነው። በከረን፡ እይ። በትግሪኛ፡ ግን፡ ሎሚ፡ ዛሬ፡ ማለት፡ ነው፡ ዮማዊ፡ እንደ፡ ማለት ።
ሎሚታ፡ (ዎች)፡ እንደ፡ ሎሚ፡ ክብ፡ ኹኖ፡ የሚታይ፡ ጕልበት።
ሎሚታ፡ በሙጣ፡ ጫፍ፡ ላይ፡ ያለ፡ ፩፡ ወይም፡ ፪፡ የብር፡ እንክብል።
ሎሚናት፡ መጠጥ፣፡(ጥሸ)ለመሸ፡ (ፀወሰ)፡ ተጥመለመለ፡ ሽባ ' ኾነ ፣ ሰለለ።
ሎሚናት፡ ከሎሚ፡ የሚወጣ፡ መጠጥ፡ ፈረንጆች፡ ሎሚናድ፡ ይሉታል፡ በግእዝም፡ ሎሚዎች፡ ማለት፡ ነው ።
ሎም፡ ሎም፡ አለ፡ ላላ፡ እንደ፡ ሎሚ፡ ኾነ።
ሎምቢ፡ ያሣ፡ ስም፡ ጌታችን፡ ከሰባት፡ እንጀራ፡ ጋራ፡ ፬፡ ሺሕ፡ ሰው፡ ያጠገበበት፡ ዓሣ፡ ("ማቴ. ፲፭፡ ፴፬, ፴፭") ።
ሎቲ፡ (ዎች)፡ ከወርቅና፡ ክብር፡ ከንሓስ፡ ከሌላም ፣ማዕድን፡ ከዝኆን፡ ጥርስና፡ ካውራሪሥ፡ ቀንድ፡ የተበጀ፡ ሰፊ፡ ቀለበት፡ አንበሳ፡ ዝኆን፡ ግስላ፡ አውራሪ፡ ጉዳይ፡ በዦሮው፡ የሚያንጠለጥለው።
ሎቲጋልኛ፡ ነው ።
ሎክሎክ፡ አለ፡ (ላሕልሐ)፡ ላላ፡ ከመጠጠር፡ ራቀ፡ ፍሬው፡ ዕባጩ ።
ሎክሏካ፡ ልል።
ሎዛ፡ ያገር፡ ስም፡ በፍልስጥኤም፡ ያለ፡ አገር፡ ያዕቆብ፡ በሕልሙ፡ ከምድር፡ እስኪ፡ ሰማይ፡ የተተከለ፡ መሰላል፡ ያየባት፡ ምድረ፡ ለውዝ፡
ሎዜ፡ ገብሩ፡ ባጤ፡ ቴዎድሮስ፡ ዘመን፡ በጐንደር፡ የነበሩ፡ ያሬዳዊ፡ ሊቅ።
ሎዜ፡ ለውዛዊ፡ ዘለውዝ፡ በዓለ፡ ለውዝ ፣የለውዝ፡ ባለለውዝ ።
ሎጋ፡ (ሊወጋ)፡ ረዥምና፡ ጠንካራ፡ ጦር፡ ከነሶማያው።
ሎጋ፡ ቁመተ፡ ረዥም፡ ሰው፡
ሎጋው፡ ሽቦ፣ የጦረኛና፡ የሐርበኛ፡ ዘፈን፡ ሽቦ፡ ያለበት፡ የተጠመጠመበት፡ ባለሽቦ፡ ሎጋ፡ ማለት፡ ነው ።ሎጋው፡ ሽቦ፡ አመጣው፡ ስቦ፡ እንዲሉ ።
ሎጋው ሽቦ)፡ በጦር ጕረሮ ላይ ያለ ሽቦ፡ "ሎጋ" የተባለ ጦሩ ነው ።
ሎጤቀላዋጭ፡ ሎጠሎጥ።
ሎጥ፡ የሰው፡ ስም፡ የአብርሃም፡ ወንድም ።
ሎፌ፡ (ለአፈ)፡ ሎጤ፡ ቀላዋጭ።
ሎፍ፡ አለ፡ ሰለፈ፡ ቀረበ፡ ተደቀነ። ሎፊሳን፡ ተመልከት ።
ሎፍ፣ ድቅን።
ሏ ("(ሎልዎ) መቃጠል ሏ ") ("ሎለወ") ።
No comments:
Post a Comment