ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
- ጠለለ (ጠሊል/ጠለ/ጠልይ/ጠለየ/ጸሊል/ጸለለ)፡ ረጠበ/ራሰ/ለመለመ ።
- ጠለለ (ጸሊል/ጸለለ/ጸልሎ ጸለለ)፡ ከለለ/ጋረደ/አጠላ/አለበሰ/ከደነ/ ሸፈነ ።
- ጠለለ፡ ቀለጠ/ነጠረ/ጠራ ("ጥራት አገኘ የጠለለ ወርቅ እንዲሉ") ።
- ጠለለ፡ ተለለ/ቀረረ/ሰፈፈ/ተንካፈፈ ("ዐሩ አተላው ዝቃጩ በታች ጥሩው ጠለልታው በላይ ኾነ የቅቤ የጠላ") ።
- ጠለል (ጸሊል)፡ መጥለል ።
- ጠለል አለ፡ ተለል/ቀረር/ሰፈፍ ኣለ ።
- ጠለልታ፡ የማር ወለላ/ንጥር ቅቤ ("የቅባት ፍሳሽ") ።
- ጠለመ (ደለመ)፡ ገባ/ሰጠመ ።
- ጠለመ (ጠሊም ጠለመ/ካደ/ጸልመ)፡ ጠቈረ/ጥቍር ኾነ ("ከሰል መሰለ") ።
- ጠለመ ጠለፈ፡
- ጠለምቱ (ጸሊም)፡ ዝኒ ከማሁ ("ጥቍር ከሰልማ ሻንቅላ የምጣድ ቂጥ") ።
- ጠለሰ (ጠልሰ)፡ ጠቈረ/ከሰለ ("ጠፋ ዐመድ ኾነ") ።
- ጠለሰመ፡ ጠልሰም ሣለ/መሰለ/እበጀ ("በጠለስ (በማየ ሕመት)") ።
- ጠለስ (ሶች)፡ የማንኛውም ዕንጨትና ሣር ከሰል ።
- ጠለሸት፡ የከሰል/የማገዶ/የሸክላ ጥ ላት ("ዐመድ") (ኢዮ. ፭፡ ፯፡ ፵፩፡ ፲፩) ።
- ጠለሸት፡ ፀሓይና ነፋስ የማይደርስበት ጥቍር መሬት ("የዛገ የወረዛ ደን ወይም ጥላው") ።
- ጠለቀ (ጠሊቅ ጠለቀ/ቀለየ)፡ ዐረበ/ገባ ።
- ጠለቀ፡ ረቀቀ ("የልብ ያሳብ") (መዝ. ፷፬፡ ፮) ።
- ጠለቀ፡ ቀዳ/ጨለፈ/አጠቀሰ (ሩት ፪፡ ማቴ. ፳፮፡ ፳፫) ።
- ጠለቀ፡ ተነከረ/ተዘፈቀ/ታለለ (ዘፀ. ፳፮፡ ፴፮) ።
- ጠለቀ፡ ነከረ (ዘሌ. ፬፡ ፲፯) ።
- ጠለቀ፡ ዘለቀ/ሰጠመ/ዘቀጠ ።
- ጠለቀ ጢሎሽ፡
- ጠለቀ፡ ጥልቅ ኾነ/ጐደጐደ (ዳን. ፪፡ ፳፪) ።
- ጠለቃ/ጥልቂያ/ጥልቆሽ/(ጥ ላቄ)፡ የመጥለቅ/የመግባት ሥራ ።
- ጠለቅላቃ/ጥልቅልቅ፡ የተጥለቀለቀ ("በውሃ የተሸፈነ መሬት ቅባት የበዛበት ወጥ ዳግመኛም ጠለቅላቃ ጥልቅ ብዬ ተ ብሎ ይተረጐማል") ።
- ጠለዘ፡ ጠለሰ/ተለዘ ።
- ጠለየ፡ ለመነ
- ጠለጠለ/ጠልጠለ)፡ አንጠለጠለ/ሰቀለ/ ሰቀጠጠ ("አንዘለዘለ") (፪ ሳሙ. ፳፩፡ ፲፪፡ ኢዮ. ፳፮፡ ፯፡ ኢሳ. ፵፡ ፲፪) ።
- ጠለጠል/ጠልጣላ፡ የተንጠለጠለ ።
- ጠለፈ (ጠሊፍ ጠለፈ/ዐሰቀ)፡ ሰረጀ/አሰናከለ ("ድንገት በገመድ በጠፍር ያዘ እሰረ በሬን ሌላውንም ከብት") ።
- ጠለፈ፡ ቀሚስን/ግላስን/ለምድን/መጋረጃን/መሶብን በሐር በባለቀለም አክርማ ሰፋ/ዘመዘመ ("ሣለ መሰለ ሸለመ አስጌጠ") (፪ ዜና. ፫፡ ፲፬) ።
- ጠለፈ፡ ነጠቀ ("ነጥቆ ወሰደ ልጃገረ ድን") ።
- ጠለፈ፡ ጠለቀ ።
- ጠለፋ፡ ስርጀታ ("የመጥለፍ ሥራ ንጥቂያ") ።
- ጠለፋ፡ ያቶ በዛብሽ ፈረስ ።
- ጠለፎ፡ ዝኒ ከማሁ ("ለጠላፊ ፈጣን ከተፎ") ።
- ጠሉሼ/ጠሉሽ፡ የወንድና የሴት ስም ("ዘመድ እንጂ አባት እናት ያላሳደጋቸው ልጆች በዚህ ስም ይጠራሉ") ።
- ጠሊቅ፡ ዘሊቅ/ጕድጓድ/ዋሻ ("የማይሰሙትና የማያውቁት ቋንቋ") (ኢሳ. ፳፱፡ ፲፭፡ ፴፫፡ ፲፱) ።
- ጠሊቅ፡ ጥልቅ (ኢሳ. ፶፩፡ ፲፡ ሕዝ. ፵፯፡ ፭) ።
- ጠላ (ጠል)፡ ጠላ (ጸልአ) በመነሣት ("ጠላ (ጠል) በመውደቅ ይለያሉ ኅብ ርን እይ ለሰውነት ርጥበት ልምላሜ የሚሰጥ ከገብስና ከጌሾ ከብቅል የተዘጋጀ መጠጥ በግእዝ 'ምዝር'ይባላል") ።
- ጠላ (ጦለለ/ጸሊል/ጸለለ/ጸልሎ ጸለለ)፡ ጥላ ኾነ ።
- ጠላ (ጸልአ)፡ ነቀፈ/አጸየፈ/ተሠ ቀቀ/ሰለቸ ("አታሳዩኝ አታምጡብኝ አለ ከመውደድ ከማፍቀር ራቀ (ተረት) ቀን ከጣ ለው ኹሉ ይጠላው የሚያድግ ልጅ አይጥላኸ የሚሞት ሽማግሌ አይርገምኸ") ።
- ጠላ ቤት፡ የጠላ ቤት ("ወይም የጠላ ሹም ጠላ ጠማቂ") ።
- ጠላ አነሣ፡ ቀዳ ("ጠላን ካተላ ለየ") ።
- ጠላ የጠለለና የጠለየ ዘር ነው ።
- ጠላለፈ፡ ነጣጠቀ/ሸላለመ ።
- ጠላላ፡ ሰፊ ሜዳ ።
- ጠላመጠጥ፡ ጠለለ ።
- ጠላማ፡ የጠለመ ("ጠቋራ") ።
- ጠላቂ፡ የጠለቀ/የሚጠልቅ ("ዋነተኛ ፀሓይ ዘላቂ") ።
- ጠላቋ፡ ያሞራ ስም (ዘሌ. ፲፩፡ ፲፮) ።
- ጠላት (ጸላኢ)፡ የጠላ/የሚጠላ ("ፀር ደመኛ ባለጋራ ጥላትን እይ (የማሪያም ' ጠላት) ማሪያምን የማይወድ ይህን ' ያልመታ የማሪያም ጠላት እንዲሉ እረኞች") ።
- ጠላት በጕያ፡ እሳት ("ተንኰለኛ ልጅ") ።
- ጠላት፡ ባለጋራ፡ ጠላ ።
- ጠላት፡ ጣመ ።
- ጠላትነት፡ ጠላት መኾን ("ባለጋራነት") ።
- ጠላቶች (ጸላእት)፡ ባለጋሮች/ደመ ኞች (ገላ. ፭፡ ፳) ።
- ጠላው ዞረበት፡ ማለıዕለቱን ሖመ ጠጠ ("ኰሽም ኾነ") ።
- ጠላፊ (ፎች)፡ የጠለፈ/የሚጠልፍ ("ያዥ አሳሪ ነጣቂ") ።
- ጠላፊ፡ ዘምዛሚ/ሸላሚ/አስጊያጭ (ዘፀ. ፴፰፡ ፳፫) ።
- ጠላፊነት፡ ጠላፊ መኾን ።
- ጠሌንዥ፡ የታናሽና የቀጯን ዕንጨት ስም ("በወይናደጋ የሚበቅል ቅጠል ' ያረግ ዐ ይነት የግርሻ መድኀኒት") ።
- ጠል (ጸላኢ/ት)፡ ጥጃዋን የጠላች ላም ("ወንድ የማትወድ ሴት ግብረ ጠል እንዲሉ") ።
- ጠል፡ ካፊያ፡ ጠለለ ።
- ጠል፡ የሰማይ ላብ ("ካፊያ የጉም ሽንት") ።
- ጠልሰም (ሞች)፡ ጠለሳም ባለጠለስ ("በያይነቱ ያስማት ሥዕል ለራስ ምታት ለሆድ ቍርጠት ለውጋት ለቍርጥማት በክታብ ውስጥ ጠንቋዮች የሚሥሉት እስላ ሞች ባንገታቸው የሚያደርጉት የብር ወይም የወርቅ ዐሸን ክታብ") ።
- ጠልቆ፡ ሰጥሞ/ዘቅጦ ።
- ጠልቆ ገባ፡ ጣልቃ ኾነ ።
- ጠልጠሌ (ዎች)፡ የጠለጠል ዐይነት ወገን ("ወረጋ አንዳች አልባ ያዘሉ ያንጠለጠሉ የሌለው") ።
- ጠልፎ፡ ሰርጅቶ አስሮ ።
- ጠልፎ በኪስ፡ የመኪና ስም ("ፈጣን ሠረገላ (ኦቶሞቢል)") ።
- ጠልፎ፡ ጭራና ደንጊያ ያለበት ገመድ ("ዓሣ መያዣ") ።
- ጠሎት፡ ልመና፡ ጸለየ፡ ጸሎት ።
- ጠመለ) አጥመለመለ፡ አዝለፈለፈ/ አሽመደመደ/አምልማሎ አደረገ ።
- ጠመለ)፡ ጠመነ ።
- ጠመለለ (ጠብለለ)፡ ዐጠፈ/ቈለመመ ።
- ጠመመ (ጸመ)፡ ተጠመዘዘ ፥ ገደደ ።
- ጠመሰሰ፡ ጣሰ/ለጠሰ/አጋደመ ።
- ጠመረ (ፀመረ)፡ ፩ አደረገ/ደረበ/ ደመረ/ቀረቀበ/ጠመደ/አገናኘ ።
- ጠመረ፡ ጠመሰሰ ።
- ጠመረረ/ጠሞረረ) ተጠማረረ፡ ተጠማረረ ("ደከመ ለፋ ጠወለገ ተጨነቀ ራብን ጥምን ተጣወረ ቻለ") ።
- ጠመረር/ጠምራራ፡ የተጠማረረ/የሚጠማረር ("ተጣዋሪ ራብ አይፈታሽ መከራ ቻይ") ።
- ጠመቀ (ጠመቀ/ጸመቀ/ዐጸረ)፡ ርጥብ ልብስን/የወይን እሸትን/የሴቴ ወይራ ፍሬን/ድፍድፍን/ሰፈፍን አጥብቆ ጨበጠ ("ጨቈነ ተነ አድፈጠፈጠ ጠመዘዘ እጠራ አንጠፈጠፈ ውሃን ደምን ዘይትን ጠላን ሠምን ለማውጣት") ።
- ጠመቀ (ጠሚቅ ጠመቀ)፡ ውሃ ጨመረ/ዐሸ/መታ ("መላ በጠበጠ ዘለለ ድፍድፍን ማርን ሾመ ጠላን ጠጅን") ።
- ጠመቀ፡ ረገጠ/አፍተለተለ/ጨመቀ/ጠመዘዘ/አንጠፈጠፈ/አጠራ ("የልብስ የወይን") (ዘፍ. ፵፡ ፲፩፡ መሳ. ፮፡ ፴፰) ።
- ጠመቀ፡ ደገሰ/አዘከረ ።
- ጠመቃ፡ ብጥበጣ/ዝለላ ።
- ጠመቅ/ጠምቅ (ኣርኣያ ሐሊብ)፡ አሸታዊ ወተት ("እሸት ሲያኝኩ ባፍ ውስጥ የሚታይ") ።
- ጠመነ (ዐረ)፡ አዋረደ ።
- ጠመነ (ዕብ. ጣማን/ሰወረ)፡ ዐየረ/ቀላቀለ ("ቀባ ለቀለቀ") ።
- ጠመኔ፡ የስንዴ ስም ("ነጭ ስንዴ ' ቀጪን") ።
- ጠመኔ/ጠመናዊ፡ የጠመን ("ነጭ ቀይ አረንጓዴ ብጫ ሰማያዊ ዐፈር የቤት መለቅለቂያ") ።
- ጠመን፡ ዕይር/መሬት/አቦልሴ ።
- ጠመንዣ (ጠብ መንዣ)፡ የጦር መሣሪያ ነፍጥ ("ሰናድር ውዥግራ ወጮፎ ሳበው ለበን መውዜር ግንጥል ጐበዝ አየኹ የመሰለው ኹሉ ጠመንጃ ቢል ጠብ መ ንጃ ያሠኛል በአረብኛም ጠበንጃ ይባላል") ።
- ጠመንዣ ያዥ፡ ጭፍራና ደንብ ።
- ጠመንዣ ጠጣ፡ ጥይትን በአፉ ወደ ሆዱ አገባ ።
- ጠመንዦች፡ ነፍጦች/ሰናድሮች "
- ጠመዘ) አጥመዘመዘ፡ ኣልመዘመዘ ("አፍተለተለ ዐመመ ሆድን") ።
- ጠመዘዘ፡ አዞረ/መለሰ/አጦዘ/አጠመመ/ገመደ/አከረረ ("ከታጠበ ልብስ መልሶ መላልሶ ውሃ አወጣ አፈሰሰ") ።
- ጠመዘዝ/ጠምዛዛ፡ የዞረ/የጦዘ ።
- ጠመዥ (ዦች)፡ የእኸል ስም ("መልከ ስንዴ ወገነ ገብስ እኸል ቈሎው የሚፈካ") ።
- ጠመዥ፡ ጠመጠመ ።
- ጠመደ፡ (ጠመዘ) ።
- ጠመደ (ፀመደ)፡ በሬን/ፈረስን በቀንበር በሠረገላ አቈራን አሰረ ("ገዛ") ።
- ጠመደ፡ ክፉኛ ጠላ ።
- ጠመደ፡ ጠመንዣን/መትረየስን አጐ ረሠ ።
- ጠመዳ (ፁማዴ)፡ የመጥመድ ሥራ ።
- ጠመድማዳ፡ ዐንካሳ ሲኼድ እግሩ የሚጣመር ።
- ጠመጠመ (ትግ. ጠምጠመ/ጠወመ)፡ ሻሽን በራስ ላይ እዞረ/ ፀመ ("ራስን በመጠምጠሚያ ሸበለለ ጠቀለለ እሰረ") (ዘሌ. ፰፡ ፱) ።
- ጠማ (ጠምዐ)፡ ነከረ/ዘፈዘፈ/አራሰ ።
- ጠማ (ጸ ምእ)፡ መጠጠ ብለሽ አጠማን አመጠጠን እይ ።
- ጠማ (ጸምአ)፡ ውሃ ሻ/ፈለገ ።
- ጠማ (ጸምኣ)፡
- ጠማ፡ ነሣ/ወሰዶ ።
- ጠማ አለ፡ መጠጥ አለ ።
- ጠማሚ፡ የሚጠም ("ገዳጅ") ።
- ጠማሚት፡ የጠመመች/ውልግድግድ ያለች ቃሊም ("የዥረት ደገፍ ዐቃባ በላይኛው ወግዳ በጐሽ ውሃ ቈላ ያለች ጠማ ሚት ባሕር እንዲሉ") ።
- ጠማማ (ሞች)፡ የጠመመ ("ወልጋዳ ገዳዳ መንገድ ዕንጨት ልግመኛ ቸልተኛ ቅንነት የሌለው ሰው") (ኢዮ. ፭፡ ፲፫፡ መዝ. ፸፰፡ ፰፡ ምሳ. ፪፡ ፲፪፡ ኢሳ. ፳፯፡ ፩፡ ዕን. ፩፡ ፬፡ ሉቃ. ፫፡ ፭) ።
- ጠማማ (ቀና ያይዶለ) ። "ያቶ እከሌ ነገር ግራ ነው" እንዲሉ ።
- ጠማማነት፡ ጠማማ መኾን ("ገዳዳነት ጠምዛዛነት ልግመኛነት") (ኢሳ. ፲፱፡ ፬) ።
- ጠማማዋ/ጠማማዪቱ፡ ያች ጠማማ (ዕብ. ፲፫፡ ፱) ።
- ጠማምነት፡ ዝኒ ከማሁ (ዘፀ. ፴፰፡ ፯፡ ፩ ሳሙ. ፳፡ ፩፡ ምሳ. ፪፡ ፲፬) ።
- ጠማሪ፡ የጠመረ/የሚጠምር ("ደማሪ ደራሲ") ።
- ጠማሽ፡ የጠማ/የፈለገ/የናፈቀ ።
- ጠማቂ (ቆች)፡ የጠመቀ/የሚጠምቅ ("ጠምዛዥ") (ኤር. ፵፰፡ ፴፫) ።
- ጠማጅ (ጆች)፡ የጠመደ/የሚጠ ምድ ("ገበሬ ባለመንኰራኵር") ።
- ጠማጠመ፡ የጠመጠመ ድርብ ("ጠቀላ ለለ ደማመረ") ።
- ጠምላይ፡ የጠመለለ/የሚጠመልል ("ቈልማሚ") ።
- ጠምሳሽ፡ የጠመሰሰ/የሚጠመስስ ("ጣሽ ለጣሽ ወጠምሻ") ።
- ጠምሴ/ጠምሰው፡ የሰው ስም ("ጣስ ለጥስ ጣሰው ለጥሰው ማለት ነው") ።
- ጠምር (ፀምር)፡ የጠጕር/የጥጥ ' የ ሐር ባዘቶ ሲፈትሉት ብዙው አንድ ክር የሚኾን ።
- ጠምቄ፡ የሰው ስም ("የጠምቅ ጠምቃዊ የኔ ጠምቅ የእሸት ፍሬ ወተቴ ጠምቄ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ") ።
- ጠምዘዝ አደረገ፡ በጥቂት በመጠን ጠመዘዘ ።
- ጠምዘዝ፡ ዘወር/መለስ ።
- ጠምዛዥ (ዦች)፡ የጠመዘዘ/የሚጠ መዝዝ ("ልብስ ዐጣቢ አጥማሚ") ።
- ጠምጣሚ (ሞች)፡ የጠመጠመ/የሚ ጠመጥም ("ቄስ ካህን ደብተራ ተማሪ") ።
- ጠምጣማ፡ ሸበላ/ሽንቅጥ ።
- ጠሞረ፡ ፪ቱን ፫ቱን ፈትል ደርቦ አከረረ ("ደወረ ጠመረ የካህናት ጠሞረ የሕዝብ ነው") ።
- ጠሰቀ፡ በዱላ መታ ("ደሰቀ") ።
- ጠሰቀ፡ ጠረነቀ ("ብዙ በላ ወጠቀጠቀጠቀ እያረፈ እያሸራሸረ") ።
- ጠሰጠሰ (ዕብ. ጣሽጤሽ አጠፋ ደመሰሰ)፡ (ተገብሮ) ፈጽሞ አረጀ/አፈጀ (ኢዮ. ፲፫፡ ፳፰) ።
- ጠሰጠሰ፡ (ገቢር) መታ/ደበደበ ።
- ጠሳቂ፡ የጠሰቀ/የሚጠስቅ ("ወጣቂ ደሳቂ") ።
- ጠስ፡ የፍታ ነገሥት ቃል ማሳጠሪያ ።
- ጠረመሰ፡ ሳይከካ ወረዳውን ፈጪ ።
- ጠረመሰ፡ ጠርሙስን አደቀቀ ("ቅልን ራስን ወደ ውስጥ ሰበረ አገባ የንጨት ዐጥርን ጣራን አስተኛ ጠረሰመን ተመልከትከዚህ ጋራ አንድ ነው") ።
- ጠረመሽ/ት፡ ድፍኑን የተፈጨ የባ ቄላ ዶቄት ።
- ጠረማሪያም፡ ፀረ ማርያም፡ ፀረረ ።
- ጠረሰ (ጠርሰ/ፀርሰ)፡ ተቸረቸመ/ተሸረፈ/ተሰበረ ("ውሃ ኾነ አላኝክ አልቈር አለ ደነዘ የጥርስ የስለት") ።
- ጠረሰመ፡ ሰበረ፡ ጠረመሰ ።
- ጠረረ (ፀረረ)፡ ትግ. ጠረረ) ("ዘለለ ጠላት አደረገ ጠላ") ።
- ጠረረ፡ በጣም ሞቀ/ገረረ/ጋለ/ተኰሰ ።
- ጠረረ፡ ጠረሰ
- ጠረረ፡ ጥሩር አለበስ ።
- ጠረቀ (ትግ/ሐባ. ጠርከ)፡ ወጋ/በሳ/ሰመረ/ቸነከረ ("ብረት አለበሰ") ።
- ጠረቀ (ጠሪቅ/ጠረቀ)፡ አወጋተ ብዙ ወግ ተናገረ ("ተረከ") ።
- ጠረቀመ (ጠነቀረ)፡ ወጋ ወደ ገላ አገባ ("እሾኸን ሥንጥርን") ።
- ጠረቀመ፡ አጥብቆ አሰረ ("ዘጋ ተመልሰኸ ጠረነቀን ተመልከት") ።
- ጠረቀመ፡ ዝም አሠኘ ።
- ጠረቀቀ (ጠረቀ)፡ ጨርሶ በሳ ("ተረከከ ሠነጠቀ ከፈለ") (፪ ነገ. ፮፡ ፴፪፡ ግብ. ሐዋ. ፲፮፡ ፳፬) ።
- ጠረቃ (ጠርቅዐ)፡ ሻረ/ተሻለው/እ ገገመ ።
- ጠረቈሸ፡ ነደለ/ሸነቈረ/ቀደደ/አጠፋ ።
- ጠረበ (ጸረበ)፡ በመጥረቢያ መታ ("ዐነጠ ሸለተ አሾለ አሣሣ አቀጠነ አጠፈጠፈ አለዘበ ዕንጨትን ደንጊያን ዋሻን") ።
- ጠረበበ)፡ (ዘረበበ)፡ አንጠረበበ፡ ፊቱን አጠቈረ/አከበደ/አንጠለጠለ ።
- ጠረበብ/ጥርባባ፡ የተንጠረበበ/የሚ ንጠረበብ ("ፊተ ከባዳ") ።
- ጠረባ/ጥርበት፡ የመጥረብ ሥራ ሽለታ ።
- ጠረተ (ጠረየ)፡ አገኘ/ሰበሰበ ገንዘብን ("የራሱ አደረገ") ።
- ጠረነቀ (ጠረቀ)፡ አጠበቀ/ጥብቅ አደረገ ("አጥብቆ አሰረ") ።
- ጠረነቀ፡ መታ ("አወፈረ ደረነቀን እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው") ።
- ጠረናም፡ ባለጠረን ("ጠረነ ብዙ ጠረኑ በኼደበት ባለፈበት የሚገኝ") ።
- ጠረን (ጽርኒ)፡ ሽታ/ጼና/መዐዛ ("በሩቅና በቅርብ የሚሸት ማለፊያና መጥፎ ከንጨት ከሣር ካውሬ ከንስሳ ከወፍ ከተንቀሳቃሽ ኹሉ ከሰው የሚወጣ") ።
- ጠረንገላ (ጥሬ ገላ)፡ አካሉ ገላው ያልሰለተ ያልደከመ ወፍራም ጕልማሳ ("(ጠረን ገላ) ገላው ጠረን ያለውጥረገቲ (ጥሎ) ጠረንገሎ ዝኒ ከማሁ") ።
- ጠረኘ፡ ጐለመሰ/ጠነከረ ("ጠረናም በጠ") ።
- ጠረኘ፡ ጥርኝ መሰለ ("ጥርኝ ጥርኝ ሸተተ") ።
- ጠረኘ፡ ጥርኝን በጥርኝ ከፈለ ("ያዘ") ።
- ጠረከ (ትግ./ሐባ. ጠርከ/በሳ)፡ አጐደፈ/በከለ/ኰለፈ/ፈጽሞ አሳደፈ/አጥረከረከ/አጕደፈደፈ/አለፈለፈ/በካከለ ።
- ጠረወዘ)፡ (ጠረዘ)፡ ተንጠራወዘ፡ አዘገመ/ተወጫመደ/ተንከላወሰ ("በቀጥታ መኼድ ተሳነው") ።
- ጠረዘ (ጠሪዝ/ጠረዘ)፡ ብዙውን ብራና ወይም ወረቀት አንድነት ሰፋ/ወሰበ/ጠለፈ/ታታ/ደረዘ፲ ጥራዝና ጠርዝ አበጀ ("ሰባራ ሸክላን ጠፈረ") ።
- ጠረዘ፡ መታ/ደወለ ።
- ጠረገ (ትግ. ጸረገ)፡ ዐደፈ/አበሰ ወለወለ/ዐሠሠ/አጠዳ/አጠራ ምጣድን/ቤትን/ምድርን/ወፍጮን/ፊትን/ዐይንን/ቂጥን ።
- ጠረገ፡ ዐጨደ/ከሥር ቈረጠ ("መነ ጠረ ሣርን ቅጠልን") ።
- ጠረገ፡ ዛቀ/ጠጠ ጭቃን/እበትን/ቅቤን/ድልኸን/ማርን ።
- ጠረገ፡ ጠረዘ ።
- ጠረገ፡ ፈጽሞ ገደለ ።
- ጠረገገ)፡ (ጠረበበ)፡ አንጠረገገ፡ አንጠረበበ ።
- ጠረጋ፡ ውልወላ/ዐጨዳ/ቈረጣ/ምን ጣሮ ።
- ጠረጠሰ (ጠሪስ/ጠርሰ)፡ ፈጽሞ አረጀ ("ጥርስ ዐጣ፲ ጨረጨሰ") ።
- ጠረጴዛ (ዞች)፡ ከሳንቃ የተሠራ ክብ ወይም ሞላላ ("ባላ፬ና ባለ፮ እግር ገበታአውራጅ") ።
- ጠረጴዛ፡ በቤተ ልሔም የቍርባኑን ቡሖ ዲያቆን አንከብክቦ የሚደረድርበት ዝርግ ሉሕ ("ሳንቃ") ።
- ጠረጴዛን፡ ተመልከት ።
- ጠረፈ (ጠፈረ)፡ አሰረ/ቀረቀበ/አከተ ።
- ጠሪ (ጠራኢ/ጸራሒ/ጸዋዒ)፡ የጠራ/የሚጠራ ("ና ባይ የሞት ጠሪ እንዲሉ ሲበዛ ጠሪዎች ይላል") ።
- ጠራ (ጠርአ/ጸርሐ/ጸውዐ)፡ ጮኸ ("እከሌ እከሌ ና ወዲህ አለ") (መዝ. ፬፡ ፫) ።
- ጠራ (ጸርየ)፡ ጥሩ ኾነ ("ከመደፍረስ ከመጨለም ራቀ ወለል አለ ጠለለ የጠላ የጠጅ የሰማይ የውሃ የደም (ተረት) ዳኛ ሲገኝ ተናገር ውሃ ሲጠራ ተሻገር ካልደፈረሰ አይጠራም እንዲሉ") ።
- ጠራ (ጸርይ)፡ መጥራት ።
- ጠራ፡ በደብረ ብርሃን አውራጃ ካንጎለላ በላይ ያለ አገር ።
- ጠራ፡ በጽፈት ነገረ/አዘዘ/አስታወቀ ።
- ጠራ፡ ነጻ ("ጠዳ የልብስ") ።
- ጠራ አለ፡ በጥቂቱ ጠራ ።
- ጠራ፡ ጣረ
- ጠራረበ፡ ዐናነጠ/ሸላለተ/አቀጣጠነ ።
- ጠራረገ፡ ዐጨደ/ቈራረጠ/መነጣ ጠረ ።
- ጠራረገ፡ ኣባበሰ/ወላወለ ።
- ጠራራ (ሐሩረ ፀሓይ)፡ የገረረ ገራራ ("ብርቱ ሙቀት ያለው ጠራራ ፀሓይ እንዲሉ") ።
- ጠራራ፡ መላልሶ ጠራ ።
- ጠራቂ (ቆች)፡ የጠረቀ/የሚጠርቅ ("ምስማር መቺ ቸንካሪ ብረት አልባሽ ነገር ባዋቂ ብረት በጠራቂ እንዲሉ") ።
- ጠራቢ (ቦች)፡ የጠረበ/የሚጠርብ ("ዐናጢ ቅዱስ ዮሴፍ የጌታችን ሞግዚት ዐልጋ ሳንቃ ዋልታ ኮርቻ ገበቴ ድግር ጠራቢ እንዲሉ") ።
- ጠራች (ጸርየት/ነጽሐት)፡ ነጻች ደ ("አበባዋ") ቆመ ሴቲቱ ።
- ጠራዥ (ዦች)፡ የጠረዘ/የሚጠርዝ ("ጥራዝ ሰፊ ተማሪ") ።
- ጠራጊ (ዎች)፡ የጠረገ/የሚጠርግ ("ወልዋይ መንጣሪ መንገድ ጠራጊ እንዲሉ") ።
- ጠራጠር (ፀረ ፀር)፡ የጠር ጠር/የጠላት ጠላት ("ነብር የሚዘል የሚወረወር") ።
- ጠራጠር፡ ነብር፡ ጠረረ ።
- ጠራጠር፡ ጠረኘ
- ጠራጠርማ (ፀራዊ)፡ ነብርማ ፍየል ነጭና ጥቍር ጠጕር ያለበት ("ዥጕርጕር") ።
- ጠር (ሮች)፡ ፀር፡ ጠላት/ደመኛ ።
- ጠር፡ በቁሙ፡ ጠረረ ።
- ጠር ከል፡ ፀር ከል፡ ፀረረ ።
- ጠርሙስ (ሶች)፡ በቁሙ የባሕር ዕቃ ቃሩራ ("የብርሌና የብርጭቆ የመስተዋት ዐይነት ያረቄ ማምጫ ማስቀመጫ ሲሰብሩት እንደ ምላጭ ያለ ስለት ይወጣዋል") ።
- ጠርሙዝ፡ በላዩ ፬ የብረት ጫፍ ያለው ዘንግ ከበሎታ ጋራ የሚያዝ ("ጠርሙዝ በሎታ እንዲሉ በቀድሞ ዘመን የንጉሥ የሥልጣኑ ምልክት ነበር ይባላል") (ዝ.፪፡ ፱) ።
- ጠርቀለም፡ የመዳብ ስም ("መዳብ ጠርቀለም ቀለበት እንዲሉ ጠርቀለም ትግሪኛ ነው ጥሩ ቀለም ማለት ይመስላል") ።
- ጠርቀለም፡ ጠረረ
- ጠርቂ፡ የጠረቃ/የሚጠረቃ ።
- ጠርቃሚ፡ የጠረቀመ/የሚጠረቅም ("አ ሳሪ ዘጊ") ።
- ጠርቃቂ፡ የጠረቀቀ/የሚጠርቅቅ ("በሺ") ።
- ጠርቅ፡ ወግ ዐዋቂ ተናጋሪ ("ወገ ጠርቅ እንዲሉ") ።
- ጠርቅ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አን ቀጽ ።
- ጠርቡሽ (ሾች)፡ ፊት የግሪክ ኋላም የቱርክ ቆብ ("የጦር ሰራዊት መለዮ") ።
- ጠርብ (ቦች)፡ ጸርብ፡ የጥድ/የዝግባ/የቍልቋል/የሌላውም ዕንጨት ኹሉ ቀጥታ ያለው ረዣዥም ፍልጥ ("ለግድግዳና ለጣራ ላጥር ሥራ የሚኾን") (፬ ነገ. ፮፡ ፱) ።
- ጠርቶ (ጠሪኦ/ጸሪሖ/ጸዊዖ)፡ ኑ ብሎ ("አሽከር ጎረቤቶቻችንን ጠርቶ መጣ ጥራን (ጸውዐነ) በሰፊ ነጋሪት አጠገብ የምትመታ ትንሿ ነጋሪት የደባይ አማ ሪት ለጦር ለግብር ሰው መጥሪያ") ።
- ጠርናቂ፡ የጠረነቀ/የሚጠረንቅ ("አጥባቂ አሳሪ አወፋሪ") ።
- ጠርዋዛ፡ ወጭማዳ/ከልዋሳ ("የቦና ጥጃ መሳይ") ።
- ጠርዝ (ዞች)፡ የሸማ ወርድ ዳርቻ ("በውግ ጐንና ጐን ያለ የመጣፍ ዳር የጽፈት መነሻና መጨረሻ ጥንፍን ተመልከት ጠርዛም ባለወፍራም ጠርዝ ልብስ") ።
- ጠርጠር አለ፡ ዐጕልኛ ጮኸ ("የከረረ ድምጥ ሰጠ በገናው") ።
- ጠርጣሳ፡ ጥርሱ የረገፈ ሽማግሌ ።
- ጠሮ ዐረግ፡ ጥሩ ዐረግ ("ብርቱ ጠንካራ ቁመቱ በጣም የዘለለ የረዘመ ከታሰረ የማይፈታ ቀፎ የሚኾን ጠሮ ያሠኘው እንደ ዕንጨት ደረቅ መኾኑና እጅ መውጋቱ ነው") ።
- ጠሮ፡ ዐውሎ ነፋስ/የመርከብ ጠር ("ወይም ሾተሌ") ።
- ጠሮ፡ ጠላት/ዐውሎ፡ ጠረረ ።
- ጠሮ፡ ጠር ።
- ጠቀለ፡ ዋሸ/ቀጠፈ ("(ግእዝ) መጥቍል ጠንቋይ ጋኔን ጠሪ ሙት አናጋሪ") ።
- ጠቀለ፡ ጠቀለለ ።
- ጠቀለለ (ጠቅለለ)፡ ሰበሰበ/ኰሰተረ/ሸበለለ/ጠመጠመ/ሸፈነ ("ክብ አደረገ ማቶት ሠራ ከፈነንና ገነዘን ተመልከት") ።
- ጠቀለለ፡ ገደለ/አሳረፈ ።
- ጠቀለለ፡ ፈጸመ/ጨረሰ ("የሥራ የነገር ሰውየው ባለጋራውን ቢገድል ዳኛው' ጠቀለልክ' አለው") ።
- ጠቀመ (ጠቀበ)፡ ስፌት ሰፋ/ጣፈ/ደረተ/ለገበ ።
- ጠቀመ (ጠቂም/ጠቀመ - ገነባ ጠቀመ - በቍዐ)፡ ሥራ ያዘ/አገለገለ ("እጠገበ በቃ ረባ") (ኢዮ. ፳፪፡ ፪፡ ማቴ. ፲፰፡ ፲፭፡ ግብ. ሐዋ. ፲፰፡ ፳፯) ።
- ጠቀሚታ፡ ጥቃሚ ("ዝኒ ከማሁ ለጥ ቅም (ባቊዕ)") ።
- ጠቀማ፡ የስፌት ሥራ ።
- ጠቀም (ጠቂም)፡ መጥቀም ።
- ጠቀሰ (ትግ)፡ ጐበጠ/ተቀለሰ ።
- ጠቀሰ (ጠቂስ/ጠቀሰ/ቀጸበ)፡ በጣትና ባይን ጠራ ("አመለከተ") (ሉቃ. ፩፡ ፳፪፡ ፭፡ ፯፡ ግብ. ሐዋ. ፳፬፡ ፲) ።
- ጠቀሰ፡ ነካ/ሳበ/ጐተተ/አቀረበ ("ጫረ ፍግን ግባስን (ተረት) ዘር ከልጓም ይጠቅሳል (ይስባል)") ።
- ጠቀሰ፡ እከሌ እንዲህ ብሏል እያለ መሰል ተባባሪ ቃል አመጣ ("ምስክር አደረገ") ።
- ጠቀሰ፡ ኰሰተረ/ተረኰሰ ("መብራትን") ።
- ጠቀሰ፡ ጥቂት
- ጠቀሡ፡ በቅንድብ ጠራ ።
- ጠቀሳ፡ የመጥቀስ ሥራ ።
- ጠቀስ፡ የሚነካ ("ነክ (ተረት) ዐይቦ የሚባል በሬ ጭራው ምድር ኣበስ ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ (ነክ)") ።
- ጠቀረ (ጠቂር/ጠቀረ)፡ ጠቈረ ።
- ጠቀራ/ጠቀሮ (ጠቀር)፡ የጪስ ስል ቀሰ ።
- ጠቀራም፡ ጠቀር የለበሰ ("ባለጠቀር") ።
- ጠቀነ (ቀጠነ ትግ. ጠቀነ - ለጠፈ)፡ ተከተፈ/ተፈረፈረ/አነሰ ("ታናሽ ኾነ ዳግመኛም ጠቀነ በትግሪኛ ስም አ ጠፋ ሆዱ ተጣበቀ ተብሎ ይተረጐማል ምስጢሩ ከማሳነስና ከማነስ አይወጣም") ።
- ጠቀጠቀ (ትግ. ጠቅጠቀ)፡ ብዙ ጊዜ ወጋ/በሳ/ነቀሰ ("ፊትን ፍሬን ወረቀ ትን ድድን") ።
- ጠቀጠቀ፡ ረገጠ/ረመረመ ("መሬትን") ።
- ጠቀጠቀ፡ አበዛ/በግድ ጨመረ/አገባ/በላ ' ወጠቀ ("መላ ምግብን ሆድን") ።
- ጠቀጠቀ፡ አጠጋጋ/አቀራረበ ("ወንፊትን ሸማን") ።
- ጠቀጠቀ፡ ደፈነ/ደበቀ/ሸሸገ/ሰወረ/ዘጋ/ሸፈነ/ጨፈነ ("ዦሮን ምስጢርን ምድርን") ።
- ጠቂ፡ የጠቃ/የሚጠቃ ("ኣውራ ኵርማ") ።
- ጠቃ (ጠቅዐ ደወለ)፡ ወጋ/ሰረረ ("ጊደርን") ።
- ጠቃ፡ ዐይን አወጣ/አፈሰሰ ("አሞራው") ።
- ጠቃለለ፡ ጠቀላለለ ("ጠማጠመ ሸፋ ፈነ") ።
- ጠቃሚ (ጠቃቢ/በቋዒ)፡ የጠቀመ/የሚጠቅም/የሚረባ ("ረቢ ጣፊ ለጣፊ ደራች (አዝማሪ) ክርና መርፌስ አገኘኹ ጠቃሚ ሰው ዐጣኹ") ።
- ጠቃሚዎች፡ የሚጠቅሙ ("ሰፊዎች") ።
- ጠቃሽ (ሾች)፡ የጠቀሰ/የሚጠቅስ ("አቅራቢ") ።
- ጠቃቀመ፡ ሰፋፋ/ጣጣፈ/ዶራረተ ።
- ጠቃቀነ፡ አናነሰ ።
- ጠቃቃሚ፡ የጠቃቀመ/የሚጠቃቅም ።
- ጠቃጠቀ፡ ዥግራ አስመሰለ ("አዥገረ ገረ ወጋጋ በሳሳ") ።
- ጠቃጠቅማ፡ ዥግርማ ("ባለጠቃጠቆ") ።
- ጠቃጠቆ (ዎች)፡ የጥቍርና የነጭ ነጠብጣብ ("የፈንጣጣ ጠባሳ እንስሳም ጠቃጠቆ ይባላል") ።
- ጠቃጠቋም፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጠቈመ (ጠቀመ)፡ ተፈላጊ ነገር ያለበትን ስፍራ ነገረ/አመለከተ ።
- ጠቈመ፡ ዠርባን በጥፍሩ ወጋ አደረገ ("ማረ ዐከከ") ።
- ጠቈመ፡ የድርን ጕጥ በጣቱ ነካ ("ማን አለ ሳበ ዐረቀ ኣስተካከለ") ።
- ጠቈመ፡ ጠቈረ ።
- ጠቈረ (ጠቀረ/ጸልመተ)፡ ተለ ወጠ/ጨለመ ("ጥቍር ኾነ ጥቀርሻ ከሰል ቍራ መሰለ ማዲያት ለበሰ ጐሰቈለ ጠቀረ የግእዝ ጠቈረ ያማርኛ ነው") ።
- ጠቈረ፡ ጠቀሰ
- ጠቈርት፡ ባመድ ተጐንፎ የጠቈረ ዘንጋዳ ("ጠላ የሚኾን") ።
- ጠቅ (ጠቂዕ)፡ መጥቃት ።
- ጠቅ አደረገ፡ ንክስ አደረገ ("ነደፈ") ።
- ጠቅላላ/ጠቅላላው፡ መላው/ኹሉ አንድ ሳይቀር ።
- ጠቅላይ (ዮች)፡ የጠቀለለ/የሚጠቀ ልል ("ዋና የበላይ ጠቅላይ ግዛት ጠቅላይ አለቃ እንዲሉ") ።
- ጠቅላይነት፡ ዋናነት/በላይነት ።
- ጠቅል፡ የቀዳማዊ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ ፈረስ ስም ("ሰብስብ ኰስትር መላውን ጠረፍ አንድ አድርግ ማለት ነው አባ ጠቅል ጠቅል ተፈሪ እንዲሉ") ።
- ጠቅሎ፡ ሸብልሎ ።
- ጠቅጣቂ፡ የጠቀጠቀ/የሚጠቀጥቅ ("ደ ፋኝ ወፍ ጉም ጭጋግ") ።
- ጠቅጣቃ፡ የተቀራረበ/የተጠጋጋ ("ርቀቱ የመርፌ ጐን መጠን የኾነ ወንፊት የዘርዛራተቃራኒ ባምስትያ የተሠራ ኩታ ጥቅጥቅ ያለ") ።
- ጠቋሚ (ዎች)፡ የጠቈመ/የሚጠቍም ("አመልካች ጠቋሚ ጠቃሚ እንዲሉ") ።
- ጠቋሚነት፡ ጠቋሚ መኾን ።
- ጠቋራ፡ የጠቈረ ("ከሰልማ ምጣድ ቂጥ") ።
- ጠቋር፡ ዛር ክፉ መንፈስ የጨለማ ጭፍራ ("ጥቍር እግረ ቀይ ወይም እፈቀይ ዶሮ የሚገብሩለት") ።
- ጠቋቈረ፡ ጨላለመ ("መላልሶ ጠቈረ") ።
- ጠበለተኛ (ኞች)፡ ወደ ጠበል የሚኼድ ("ጠበል ጠጭ") ።
- ጠበል (ሎች/ጠቢል/ጠበለ)፡ በዱር/በገደል/በተራራ የፈለቀ ውሃ ("ክርስቲያን ኹሉ በሥላሴ በማርያም በመላእክት በጻድቃን በሰማዕታት ስም የሚጠመቅበት") (ዮሐ. ፭፡ ፪, ፫, ፬, ፯, ፱፡ ፯) ።
- ጠበል ረጨ፡ የተቀደሰ ውሃን በቤት ውስጥና በወላድ ላይ ወረወረ በተነ ።
- ጠበል፡ በጋን የተመላ ተደግሞበት የፈላ ማየ ጸሎት ።
- ጠበል ተጠመቀ፡ በጠበል ተነከረ/ታጠበ ።
- ጠበል፡ የመቍረርት ውሃ ("ቍርባን ውጭ የሚጠጣ ቅዳሴ ጠበል እንዲሉ") ።
- ጠበል፡ የማኅበር/የዝክር/የተዝካር/የቍርባን/የክርስትና ጠላ ።
- ጠበል፡ የገብስ ስም ("ቶሎ የሚደርስ ለጠላ የሚፈለግ ገብስ") ።
- ጠበል ጠዲቅ፡ ጠበል እንዳለፈው ጠዲቅ ዳቦ ።
- ጠበል ጠጣ፡ ፉት o አለ ("ረካ ስለ ጤናው") ።
- ጠበሰ (ጠቢስ/ጠበሰ)፡ በነዳድ/በፍም/በድስት እያገላበጠ አበሰለ/ቈላ/አንቃቃ አደረቀ/አመጠጠ እሸትን/እንጀራን/ሥጋን ።
- ጠበሰ፡ በጥይት መታ ("ይኸውም ኣቃጠለ ካለው ይገባል") ።
- ጠበሰ፡ ተኰሰ/አቃጠለ/ፈተነ/አፈላ ሸክላን/ቅቤን/ወርቅን ።
- ጠበሳ፡ የመጥበስ ሥራ ።
- ጠበረ (ፀመረ)፡ መጠብር/መጣብር ሠራ ("አስጌጠ ሸለመ አሳመረ ግንብን ግድ ግዳን ጋሻን ሕንጻን ክዳንን ሸማን") ።
- ጠበረ፡ ቀነፈ/ጠረቀ/ገጠመ/ጣፋን ።
- ጠበረረ፡ በጣም ሠማ/ጋለ ("ግለቱ ከልክ ዐለፈ ገረረ ሊጥ ባሰፉበት ጊዜ ቸሰስ አደረገ በንጀራ ሰበከት ዐይን አወጣ ያዘ አለቅም አለ እንጀራን ምጣዱ") ።
- ጠበራ፡ ሥሥ ክዳን አካርሚኝ ("ዐልፎ ዐልፎ ደረጃ ያለው ጌጠኛ ጠበራ ክዳን እንዲሉ") ።
- ጠበራ፡ ታቹ ግንብ ላዩ ግድግዳ የኾነ የቤት ሕንጸ ።
- ጠበራ፡ ጣፋ ("የጋሻ ጌጥ ጠበራ ዋልታ እንዲል ትግሬ ጣፋ ጋሻ ሲል") ።
- ጠበቀ (ዐቀበ/ኀለወ/ኖለወ)፡ (ገቢር) አየ/ተመለከተ/አገደ/ከለከለ/ሐይ አለ ("እንዳይኼድ እንዳይጠፋ እንዳይነካ አደ ረገ") (ሕዝ. ፴፫፡ ፭) ።
- ጠበቀ (ጠቢቅ/ጠበቀ)፡ ጥብቅ ኾነ/ከረረ ("(ተገብሮ) ልልነት ዐጣ") ።
- ጠበቀ፡ ቈየ ("ቀን ለምሳ ጠብቀንኸ ነበር ሳትመጣ ቀረሽ (አፉን ጠበቀ) አፉ እንዳመጣ ከመናገር ተጠነቀቀ") ።
- ጠበቀት (ቶች)፡ ነትራካ ነገር ወ ዳድ ።
- ጠበቃ (ቆች)፡ አፍ ነገረ ፈጅ/የነገር አባት/ተማጋች ።
- ጠበቃ አቆመ)፡ ነገረ ፈጅ ወኪል አደረገ ።
- ጠበቃነት፡ ጠበቃ መኾን ።
- ጠበቄ፡ የሰው ስም ።
- ጠበቅ (ትግ)፡ ዝበሎ ከደንጊያ ከ ገደል የሚጣበቅ ።
- ጠበቅ (ጠቢቅ)፡ መጥበቅ ።
- ጠበቅ አለ፡ ጠበቀ ።
- ጠበቅ አደረገ፡ አጠበቀ ።
- ጠበቅ፡ አግድ/ከልክ ("እጀ ጠብቅ ሕገ ጠብቅ እንዲሉ") ።
- ጠበቅኝ እጠብቅኻለኹ አለ፡ ዛተ ሰውን ለመምታት ለመግደል ።
- ጠበበ (ጠቢብ/ጠበ)፡ ለቀመ/አዋሰበ/አሠባጠረ ("ቀጠቀጠ አነጠረ አፈሰሰ ብረትን ብርን ወርቅን የጊዜና ኀላፊ ትን ቢቱም ይጠብብ ይጠብባል ይላል") ።
- ጠበበ (ጸበ)፡ ጠባብ ኾነ ("ስፋት ዐጣ እነሰ ጨነቀ የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱ ይጠብ ይጠባል ቢል እንጂ ይጠብብ ይጠብባል አይልም") ።
- ጠበበ (ጸበ)፡ ጠባብ ኾነ ("ስፋት ዐጣ እነሰ ጨነቀ የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱ ይጠብ ይጠባል ቢል እንጂ ይጠብብ ይጠብባል አይልም").
- ጠበበ፡ ዐዲስ ጥበብ አወጣ/ፈለሰፈ ።
- ጠበበ፡ ጠበጠበ ።
- ጠበብ (ጸቢብ)፡ መጥበብ ።
- ጠበብ (ጸቢብ)፡ መጥበብ.
- ጠበብ አለ፡ አነስ ኣለ ("ሳይበቃ ቀረ") ።
- ጠበብ አለ፡ አነስ ኣለ ("ሳይበቃ ቀረ").
- ጠበተ (ትግ)፡ ሊጥን አፈስሰ አ ሰፋ ጋገረ ።
- ጠበንጃ፡ ነፍጥ/ጠመንዣ ።
- ጠበኛ (ኞች)፡ ጠብ ወዳድ/ባለጠብ/ጥለኛ (ምሳ. ፳፮፡ ፳፬) ።
- ጠበኛነት፡ ጠበኛ መኾን ።
- ጠበደለ፡ ወፈረ/ደነደነ/ደለመጠ ።
- ጠበጠበ (ጠብጠበ)፡ ገረፈ/ሸነ ቈጠ/መታ ("ባለንጋ ባርጩሜ") ።
- ጠበጠበ፡ በለተ/አወራረደ/ጠባጠበጠበ ።
- ጠበጠበ፡ ቸኰለ/ፈጠነ/ቀለጠፈ/ገሠ ገሠ ("ቶሎ ቶሎ ኼደ ተራመደ") ።
- ጠበጠበ፡ ነፈገ/ሠሠተ ።
- ጠበጠበ፡ ጥብጣብ ሰፋ/ጐነጐነ ።
- ጠቢ (ጠባሒ)፡ የበለተ/የሚበልት ።
- ጠቢ (ጠባሒ)፡ የበለተ/የሚበልት.
- ጠቢ (ጸባሒ)፡ የጧት ጠባቂ ዘ በኛ ።
- ጠቢብ፡ ብልኅ/ዐዋቂ/ፈላስፋ/አስተዋይ (ኤር. ፱፡ ፳፫) ።
- ጠባ (ጠብሐ/ዐረደ)፡ ገፈፈ ("በ ለተ ብልት አወጣ አወራረደ ቈረጠ በላች") ።
- ጠባ (ጠብሐ/ዐረደ)፡ ገፈፈ ("በ ለተ ብልት አወጣ አወራረደ ቈረጠ በላች").
- ጠባ (ጸብሐ)፡ ወገገ/ፈገገ ("ነጋ ጧት ኾነ ጠባ ለኪዳን መሸ ለቍርባን") ።
- ጠባ (ጸብሐ)፡ ወገገ/ፈገገ ("ነጋ ጧት ኾነ ጠባ ለኪዳን መሸ ለቍርባን").
- ጠባ (ጸብአ)፡ ጠላ/ወጋ/ወጋጋ ሆድን ።
- ጠባ፡ ባተ ገባ ("መስከረም ጠባ እንዲሉ ይኸውም ፪ ወር ክረምት መጨለሙን ፀሓይ አለመታየቱን ያስረዳል።") ።
- ጠባ.
- ጠባሲት (ጥብስት)፡ የተጠበሰች/የተ ንቃቃች ጋሬ መያዣ ።
- ጠባሳ (ሶች)፡ የተቃጠለ/የአስቴ ተ ኵስ ("ቈስሎ የነበረ የገላ ምልክት ተተኵሶ የዳነ በሕመሙ ጊዜ የነበረውን ትኵሳትም ያሳያል") ።
- ጠባሴ (ጠባሲ)፡ ዝኒ ከማሁ ("በግእዝ ግን ጠባሽን ማለት ነው ነገደ ብለኸ ነጋዴን እይ") ።
- ጠባሴ ኮሶ (ጠባሳዊ ኮሶ)፡ እሳት የፈጀው ጠባሳ የኮሶ ዛፍ ("በደብረ ብርሃን አጠገብ ያለ") ።
- ጠባሴ ኮሶ፡ ኮሶን ከንጀራ ጋራ የሚያግፈለፍል ("ወይም ለጠጪው በፍም ተ ኵሶ የሚሰጥ (የምትሰጥ)") ።
- ጠባሪ፡ የጠበረ/የሚጠብር ("አስጊያጭ አሳማሪ") ።
- ጠባሽ (ሾች)፡ የጠበሰ/የሚጠብስ ("እፍሊ ቅቤ ጠባሽ እንዲሉ (ተረት) እንወራረድ አህያ እንረድ እኔ ጠባሽ አንተ ጐራሽ") ።
- ጠባቂ፡ ከሰንጠረዥ መጫወቻ አንዱ ።
- ጠባቂ፡ ዘበኛ/ስልብ/ጃን/ደረባ ("(እንባ ጠባቂ) ፍርድ ጐደለ ድኻ ተበደለ የ ሚል ያገር ተቈርቋሪ") ።
- ጠባቂ፡ የጠበቀ/የሚጠብቅ ("አጋጅ እረኛ መላከ ውቃቢ") (መዝ. ፻፵፩፡ ፫፡ ሕዝ. ፴፬፡ ፭, ፲፪፡ ዳን. ፬፡ ፲፫, ፳፫) ።
- ጠባቂነት፡ ጠባቂ መኾን ("እረኝነት") ።
- ጠባቃ፡ ዝኒ ከማሁ ("ለጥብቅ ለጣቃ") ።
- ጠባቆች፡ እረኞች/ስልቦች/ዘበኞች/ጳጳሳት/ነገሥታት/መኳንንት (ኤር. ፳፫፡ ፩፡ ሕዝ. ፴፬፡ ፪, ፯, ፰፡ ዳን. ፬፡ ፲፯፡ ኤፌ. ፬፡ ፲፩) ።
- ጠባበሰ፡ መላልሶ ጠበሰ ("ተኳኰሰ") ።
- ጠባቢ፡ የጠበበ/የሚጠብብ ("ሸማኔ ጥበብ ሠሪ ፈልሳፊ") ።
- ጠባባ፡ እጅግ በጣም ጠባብ ("የተራራ መካከል መንገድ በጐን የሚያስኬድ") ።
- ጠባባ፡ እጅግ በጣም ጠባብ ("የተራራ መካከል መንገድ በጐን የሚያስኬድ").
- ጠባብ (ቦች)፡ የጠበበ/የሚጠብ ("ሸልቋቍቻ እጀ ጠባብ እንዲሉ") ።
- ጠባብ (ቦች)፡ የጠበበ/የሚጠብ ("ሸልቋቍቻ እጀ ጠባብ እንዲሉ"). (ተመልከት፡ ደረትን እይ).
- ጠባብነት፡ ጠባብ መኾን ።
- ጠባብነት፡ ጠባብ መኾን.
- ጠባቴ፡ ዳኛ ጸባቴ ።
- ጠባይ (ዮች/ጠብዐ/ጠባይዕ)፡ በቁሙ የፍጥረት ኹሉ ሥር መሠረት ("ባሕርይ ባሕሬ መሬት ውሃ ነፋስ እሳት") ።
- ጠባይ፡ ዐመል ("ከጠባይ የሚገኝ የተፈጥሮ ግብር ጠባየ ክፉ ጠባየ መልካም እንዲሉ") ።
- ጠባይ፡ ጠበቀ ።
- ጠብ (ጸብእ)፡ ጥል/ዐምባ/ጓሮ/ውጊት ("ዕለተ ጠብ እንዲሉ") ።
- ጠብ ርግፍ አለ፡ ፈራ/ወደቀ ("ምድር ሳመ") ።
- ጠብ አለ (ነጥበ)፡ ነጠበ/ወደቀ እመሬት ዐረፈ ።
- ጠብ አንሺ፡ አጫሪ/ጠብ ዠማሪ/ተንኳሽ/ቈስቋሽ ።
- ጠብ አይልም፡ ከንቱ አይኾንም ("ሳይፈጸም አይቀርም እከሌ የተናገረው ነገር እምድር ጠብ አይልም") ።
- ጠብ አደረገ፡ አነጠበ ("የውሃ የእንባ የደም") ።
- ጠብ ጠብ አለ፡ ተንጠባጠበ ።
- ጠብ ጠብ አደረገ፡ አንጠባጠበ ።
- ጠብታ፡ የውሃ/የመድኅኒት ነጥብ ("፩ ጠብታ ፪ ጠብታ እንዲሉ") ።
- ጠብታ፡ ጠብ ማለት ።
- ጠብታዎች/ጠብቶች፡ ነጥቦች/ጠ ፈጠፎች ።
- ጠብታየውሃ ነጥብ፡ ጠብ ።
- ጠብት፡ የጦር መሣሪያ ብት ።
- ጠብደል፡ ወፍራም/ያልተማረ/ዲላ ("አካሉ ልቅልቅ ያለ የደለመጠ") ።
- ጠብደሎች/ጠባድልት፡ ወፍራሞች ውዲሎች ።
- ጠብጣቢ፡ የጠበጠበ/የሚጠበጥብ ("ገራፊ በላች ገሥጋሽ") ።
- ጠብጣባ፡ ችኩል/ፈጣን/ቀልጣፋ/ሯጭ ("ንፉግ ቀብቃባ") ።
- ጠቦ፡ የሰው ስም ("አስቀድሞ የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ኋላም ያጤ ምኒልክ በገና መቺ የነበረ ድንክ") ።
- ጠቦ፡ የራስ ደረሶ ፈረስ ስም ።
- ጠቦተ፡ ደረቀ ("እንደ ጡብ ኾነ ሆዱ ጠቡታል እንዲሉ") ።
- ጠቦት፡ የበግና የፍየል በጠጥ ከመሬት ጋራ ተቀላቅሎ የደረቀ ጐደዳ ።
- ጠቦት፡ ጥቦት ጡት የተወ ግልገል፡ ጠባ ።
- ጠቦት ፊት፡ መልኩ የማያምር ሰው ።
- ጠነሰ፡ አረገዘ፡ ፀነሰ ።
- ጠነሰሰ (ፀንሰ)፡ እንስራን ሀጠበ ("ጌሾና ብቅልን አዋሐደ በጠበጠ") ።
- ጠነሰሰ፡ ፀነሰ/አረገዘ ።
- ጠነቀ (ትግ. ጠንቀመ)፡ አጫረ/ ጐዳ/መረዘ ።
- ጠነቀ/ጠነቀቀ ።
- ጠነቀለ (ነቀለ)፡ በጥቂቱ ቈነጠረ/ ወሰደ/ነካ/ረገጠ ።
- ጠነቀለ፡ ዐንካሳ አደረገ ።
- ጠነቀረ (ጠቀረ)፡ ገባ/ጠለቀ ("የጀ ረሰ") ።
- ጠነቀቀ (ጠንቀቀ)፡ አለስሕተት ሠራ/ጻፈ/አነበበ ።
- ጠነቀቀ፡ አተጋ/አነቃ ።
- ጠነቀቀ፡ አዘጋጀ/ኰሰተረ/ከወነ/አስተካከለ ("መላ ፈጸመ ጨረሰ") ።
- ጠነቀቀ፡ ጠነሰሰ ።
- ጠነቈለ (ጠንቈለ)፡ መላ መታ/አ ረተ ("የናትንና ያስጠንቋይን ስም ጠየቀ ኮከብ ቈጠረ መጣፍ ገለጠ ሞራ ኣየ ጠጠርና ወሌ ጣለ በዚህ ቀን ያስፈራኻል በዚህ ጊዜ ይቀናኻል የኋላ የኋላ ትሾማለኸ ስም ታወጣለኸ ማዕርግ ታገኛለኸ አለ") ።
- ጠነቈለ፡ ጠቅ አደረገ ("ወጋ ደነቈለ ' ዘነቈለ አነቈረ") ።
- ጠነበሰ፡ ጠነበዘ ።
- ጠነበረ (ነበረ/ጸበረ)፡ ደነበረ ("ጠ ነበዘ") ።
- ጠነበር/ጠንባራ፡ ደነበር/ደንባራ ።
- ጠነበዘ !፡ ጠነዛ ።
- ጠነበዘ (ትግ. ጠንበሰ)፡ ታወረ'ደነ በዘ ("ሰከረ") ።
- ጠነበዝ/ጠንባዛ፡ ዕውር ' ደንባዛ ' ሰካር ።
- ጠነበፈ፡ ገደለ/አወደቀ ("ጥንብ አስመ ሰለ ወታደሩ ዝንጀሮውን በጥይት ጠነበፈው") ።
- ጠነበፈ፡ ጥንብን ጣለ ("አጋደመ") ።
- ጠነባ (ጸንጰወ/ትግ. ጠ ንበወ)፡ ገማ ("ጥንብ ኾነ ክፉኛ ሸተተ") ።
- ጠነነ (ጸነ)፡ ዘነበለ/ቅር አለ ("ቅር አሠኘ ትግሪኛ ግን ጠነነን ደፈረ ይለዋል") ።
- ጠነከረ፡ ጠና/ከረረ/ደረቀ/ጠጠረ ።
- ጠነከረ፡ ጨከነ/በረታ ።
- ጠነወተ/ጼነወ) ተጠናወተ፡ በክፉ ተጠባበቀ/ተተናኰለ/ተቃወመ (፪ ጢሞ. ፬፡ ፲፭) ።
- ጠነዘ፡ ደነቈረ/ደነዘ ።
- ጠነዘ፡ ፈጽሞ ደረቀ/ቀለዘ/ከቸለ ።
- ጠነዛ፡ ጠነከረ ("አልበስል አለ እሳት") ።
- ጠነገረ፡ ጠነበረ ("ታወረ") ።
- ጠነገር/ጠንጋራ፡ ጠነበር/ጠንባራ ' ዕውር ።
- ጠነገደ፡ ገደለ/ፈጀ/ጨረሰ/ፈጸመ ("በቸነፈር") ።
- ጠነጋ (ተፀንግዐ/ተፀፍረ)፡ ተበጀ/ ተታታ/ተዋሰበ/ተጠፈረ ("ተለጋ ጥንጉ") ።
- ጠነጠነ (ትግ. ጠንጠነ)፡ ፈገጠ/ተወ/ፈነረ/ወረወረ/አሽቀነጠረ ("ገቢር") ።
- ጠነጠነ (ጸንጸነ)፡ ነቀዘ/ዐመድ/ዶቄት ኾነ/ተበላሸ ።
- ጠነጠነ፡ መታ/ደበደበ/አቦነነ ።
- ጠነጠነ፡ ፈጽሞ አረጀ/አፈጀ ።
- ጠነፈፈ/ጠፈፈ) ትግ. ጸንፈፈ - ጨለጠ፡ አጠነፈፈ ("ማሰሮን ዘቀዘቀ የንፍሮ ውሃን አፈሰሰ አንጠፈጠፈ ከመኻል ወደ ዳር አወጣ") ።
- ጠኒ (ዎች)፡ ጸናሒ፡ የሚቀመጥ/የሚ ቈይ ።
- ጠኒያም፡ ጠኔ የያዘው ሰው ("ባለጠኔ ራብተኛ ትጋረኛ") ።
- ጠና (ጸንሐ)፡ ተቀመጠ/ቈየ ።
- ጠና (ጸንዐ)፡ ጠነከረ/በረታ/ጨከነ ።
- ጠና፡ አረጀ ።
- ጠናዛ፡ ክችሌ ("ደንቈሮ ደነዝ ደደብ ነገር የማይገባው") ።
- ጠናግል፡ የፈረስ አንባር ማያ ("ጠናግል ብዛትን እንጂ አንድነትን አያሳይም") ።
- ጠኔ (ጠነየ/ትግ. ጠመየ - ራበ/ጢመት - ራብ)፡ ብርቱ ራብ ("ከልክ ያለፈ ራስ የሚያዞር ዐይን የሚያጨልም ጥኑ ችጋር") ።
- ጠኔ፡ ጠነባ ።
- ጠንሳሽ፡ የጠነሰሰ/የሚጠነስስ ።
- ጠንቀቅ በል፡ ኰስተር በል ።
- ጠንቀቅ አለ፡ ዝኒ ከማሁ í ኰስተር አለ ።
- ጠንቀኛ (ኞች)፡ አጫሪ/ክፋተኛ ነገረኛ/ተንኰለኛ/መርዘኛ ።
- ጠንቀኛነት፡ ጠንቀኛ መኾን ("መርዘ ኛነት") ።
- ጠንቃቂ፡ የጠነቀቀ/የሚጠነቀቅ ("ኰስ ታሪ") ።
- ጠንቃቃ፡ የተጠነቀቀ ("ኰስታራ ትጉ ንቁ ዝግጁ") ።
- ጠንቃቃነት፡ ኰስታራነት ።
- ጠንቃይ፡ የጠነቀለ/የሚጠነቅል ("ቈን ጣሪ") ።
- ጠንቅ (ተንክ)፡ ክፉ ነገር/ጥል/ተንኰል/ሰበብ ("መርዝ መዘዝ ሳንክ") ።
- ጠንቅ፡ ነዋሪ ዕመም/ምች/ዐደር ("ጠ ባላ ዕትራት የወባ ጠንቅ የፈንጣጣ ጠንቅ እንዲሉ") ።
- ጠንቋይ (ዮች)፡ ጠንቅ ዋይ፡ የጠነቈለ/የሚጠነቍል ("መሠሪ ማርተኛ አስማተኛ አፍዝ አደንግዝ ዐዚም ደጋሚ ኮከብ ቈጣሪ የተናገረው ጠብ የማይል የምድር ዐዋቂ የማይሞት ሰው የሚያድን ጠጠርና ጨሌ ጣይ í መጣፍና ሞራ ገላጭ ሥር ማሽ ቅጠል በጣሽ") (ዘዳ. ፲፰፡ ፲፩፡ ፪ ዜና. ፴፫፡ ፮) ።
- ጠንቋይነት፡ መለኛነት/ጝርተኛነት/ አስማተኛነት (ኤር. ፲፬፡ ፲፬) ።
- ጠንበለል (ጠብለለ)፡ ያረግ ስም ("በዋልታ ዙሪያ ጮምጮሞ የሚኾን ዐረግ (ግጥም) እኔ እንቢ አሻፈረኝ እወጣለኹ ደጋ ዐንገቷ ' ይመስላል የጠንበለል ለጋ") ።
- ጠንባሳ/ጠንባዛ ።
- ጠንቧ አለ፡ እንደ ጥንብ ፈነዳ ("ተሠ ነጠቀ ተተረተረ ዕባጩ ቀርበታው") ።
- ጠንቷል፡ አርጅቷል ።
- ጠንከር፡ መጠንከር ።
- ጠንከር አለ፡ ጠነከረ ።
- ጠንካሪ፡ የሚጠነክር ።
- ጠንካራ (ሮች)፡ የጠነከረ ("ከራራ ደረቅ ብርቱ ጐበዝ የማይበገር የማይፈታ") (ኢዮ. ፵፩፡ ፯፡ ምሳ. ፲፰፡ ፲፬፡ ሕዝ. ፳፮፡ ፲፩) ።
- ጠንካራነት፡ ጠንካራ መኾን ።
- ጠንክ (ጠነፈፈ) ።
- ጠንክር፡ ጥና/በርታ ።
- ጠንክሮ፡ በርትቶ ።
- ጠንገላ፡ ግልገል ሰኰና ።
- ጠንገሎ፡ ወፍራም ሰው ("ጠረንገላ") ።
- ጠንጣኝ፡ የሚመታ/የሚደበድብ ("መቺ ደብዳቢ") ።
- ጠንጣኝ፡ የጠነጠነ/የሚጠነጥን ("ነቃዥ ብሳና የመሰለው ኹሉ") ።
- ጠንፉ፡ የሰው ስም ("ጠርዙ ክፈፉ የርሱ ጠርዝ") ።
- ጠንፉ፡ ያ ጠንፍ ።
- ጠንፋ፡ ጠርዟ/ክፈፋ ("የርሷ ጠርዝ") ።
- ጠንፌ፡ የወንድና የሴት ስም ("ትርጓሜው የጠንፍ የኔ ጠንፍ") ።
- ጠንፍ (ጥንፍ)፡ ጠርዝ ("የንጨት የብረት ዙሪያ ክፈፍ ያማረ ያጌጠ የተሸለመ ባለሰንበር ሥራ ዘንዶ ማቶት ክባስ ፈረንዶች ኮርኒስ ይሉታል ጥንፍ ግእዝኛ ነው") ።
- ጠንፍ የለሽ፡ የሴት ስም ።
- ጠንፍ የለኽ፡ የሰው ስም ("ጠርዙ (ወሰን) የለኽ") ።
- ጠንፎች፡ ጠርዞች/ሰንበሮች "
- ጠኸነነ፡ ጀነነ/አኰራ ("ጠፈነነ ተጠኸነነ ተጀነነ ኰራ") ።
- ጠኸኘ (ጨከነ/ጠሐነ)፡ መታ ጠዘለ ("ደሰቀ ደበደበ") ።
- ጠኸኘ፡ ፈጨ/አደቀቀ ("ጠኸኘ ጠገረረ አስቋፈ") ።
- ጠወለ) አጥወለወለ (አንኮለለ)፡ ልብ መታ/አናወጠ ("አዞረ") ።
- ጠወለገ (መጽለወ/ጸምሐየ)፡ ልምላሜው/ርጥበቱ ተቀነሰ (ኢሳ. ፲፭፡ ፯) ።
- ጠወለገ፡ ተለወጠ/ጠቈረ ("ፊቱ ብር አለ") ።
- ጠወለገ፡ ጠወረ ።
- ጠወለግ/ጠውላጋ (ጽምሑይ)፡ የጠወለገ ።
- ጠወረ ።
- ጠወረ (ጾረ/አጾረ)፡ አስቻለ/አስለ መደ ።
- ጠወረ፡ አስማለ ("ጡር ይድረስብኝ አሠኘ") ።
- ጠወረ፡ ጦረ ።
- ጠወሬታ፡ ማላ ("የሐሰተኛ ሸክም") ።
- ጠዋሪ፡ የሚጠውር ("አስቻይ አስለማጅ") ።
- ጠዋሪ፡ የሚጦር ("ጧሪ ረዳት") (አስ. ፪፡ ፳) ።
- ጠውለግ አለ፡ ለወጥ እለ ።
- ጠውላጊ፡ የሚጠወልግ ("ቅጠል ልጅ") ።
- ጠዘለ (ደዘለ)፡ መታ/መደወተ ("ጠ ረዘ") ።
- ጠዘለ፡ አደነደነ/ኣወፈረ ።
- ጠዘል፡ የወፈረ/ወፍራም ("ጥረገቲ") ።
- ጠዘረ፡ ነፋ/ዘጠረ ።
- ጠዘዘ) ጥዝ አለ፡ ዕዝ አለ ጮኸ ("የንብ የዝንብ የተርብ የጥንዝዛ የዥማት") ።
- ጠዘጠዘ (ጠዘዘ)፡ ነደፈ/ወጋ ("የጥን ዝዛ የንብ የተርብ የጥይት") ።
- ጠዘጠዘ፡ ነዘነዘ/ነዘረ ("የቍስል የዕብ ነት") ።
- ጠዛይ፡ የጠዘለ/የሚጠዝል ("መቺ አወ ፋሪ ዱላ") ።
- ጠዝጣዥ፡ የጠዘጠዘ ፥ የሚጠዘጥዝ ("ነዳፊ") ።
- ጠየመ፡ በቅላትና በጥቍረት መካከል ኾነ ("የመልክ") ።
- ጠየም፡ መጠየም ።
- ጠየም አለ፡ ጠየመ ("ጠይም ኾነ") ።
- ጠየረ፡ አዘጋጀ፡ አደራጀ ።
- ጠየቀ፡ (ጠይቆ ጠየቀ)፡ እህ፡ አለ፡ መረመረ፡ የከሰ፡ (ዮሐ፬፡ ፶፪) ። የት፡ ነበርኸ፡
- ጠየቀ፡ ሞገተ፡ ተጠየቅ፡ አለ ። ጠየቀ፡ ጐበኘ፡ ፈቀደ፡ እግዜር፡ ይማርኸ፡ አምላክ፡ ያውጣኸ፡ አለ፡
- ጠየተ፡ መታ/ገደለ ("በጥይት") ።
- ጠየተ፡ ብዙውን እሸት ባንድነት ሰብስቦ አሰረ ።
- ጠየተ፡ ጠላ ።
- ጠየተ፡ ጥይት ሠራ/አበጀ/አሳመረ ።
- ጠየፈ፡ ጠየረ፡
- ጠያር፡ (ሮች)፡ የግመል'ሠጋር፡ በራሪ።
- ጠያቂ፡ (ቆች)፡ የጠየቀ፡ የሚጠይቅ፡ መርማሪ፡ የካሽ፡ ሞጋች ። (ተረት)፡ አጥብቆ፡ ጠያቂ፡ እናቱን፡ ይረዳል ። ወሬ፡ ለጠያቂ፡ ገበጣ፡ ላዋቂ ።
- ጠያቂ፡ ዐርክስና፡ ርኩስነት፡ ርካሽ መኾን።
- ጠያቂና፡ ተጠያቂ፡ አስጠንቋይና ፥ ጠን ቋይ፡ ሞጋችና፡ ተሞጋች ።
- ጠያች፡ የጠየተ/የሚጠይት ("የሚያስር አሳሪ ጥይት ሠሪ") ።
- ጠያየቀ፡ መራመረ፡ ሞጋገተ ።
- ጠያይም (ሞች)፡ ብዙ ጠይም ።
- ጠዬ (ዎች)፡ የታናሽ ዛፍ ስም ("በትር የሚኾን ወንዴ ሰፋ ሻካራ ጕጣም") ።
- ጠይማት፡ ብልጫነት ንጣት የሌለው ቅጠልማ ዓሣ ።
- ጠይም (ሞች)፡ ጥቍር አይሉት ቀይ መካከለኛ ሕብር ቅጠልያ ("የመልክ አቦልሴ ጠይም አህያ ጠይም ሰው እንዲሉ ይኸውም ከቅላት ይልቅ ወደ ጥቍረት የሚ ያደላ ስለ ኾነ (ጸሊም ጸሊማዊ) ተብሎ ሊተረጐም ይቻላል ወደ ቅላት ቢያደላ ግን የቀይ ዳማ ይባላል") ።
- ጠይምነት፡ ጠይም መኾን ።
- ጠይብ (ጠቢብ)፡ ባለጅ/ቀጥቃጭ/ብረተ ሠሪ/ሸክለኛ/አንጥረኛ/ሸማኔ/ፋቂ/ዐራቢ/ዐናጢ ("ትርጓሜው ብልኅ ፈላስፋ ሥራን ኹሉ ዐዋቂ ማለት ነው በብሉይም ጥበብና ዕውቀት ማስተዋል የመላባቸው ባስልኤልና ኤልያብ ሌሎችም ነበሩ") (ዘፀ. ፴፩፡ ፪, ፮) ።
- ጠይቦች (ጠቢባን)፡ ባለጆች/አንጥረኞች/ዐዋቆች/ቍንጣሮች ።
- ጠይቦች፡ ተጣሉ ("ተጥዶ በወጣ ም ጣድና ድስት ቂጥ ላይ ብዙ የእሳት ነጠብጣብ ሲጋጭ ታየ") ።
- ጠይት፡ ጤት ("የፊደል ስም ጠ ውብ ማለት ነው") ።
- ጠደቀ፡ (ጠወለ) ።
- ጠደቀ፡ የሕዝብ ("ጸደቀ የካህናት ዐማርኛ ነው (ጠለጠለ) ብለኸ ተንጠለጠለን እይ") ።
- ጠደቀ፡ ጸደቀ ።
- ጠደቅ፡ የጠደቀ ።
- ጠደፈ (ጸድፈ)፡ ገደል ገባ/ተንከባ ለለ/ትኰለ ።
- ጠደፍዳፋ፡ የችኩል ችኵል ።
- ጠዲቅ (ጸዲቅ/መጥደቅ)፡ ስለ ጽ ድቅ የሚጋገር ዳቦ ("አነባበሮ ድፎ መክፈልት ሰአልናከ ጠበል ጠዲቅ እንዲሉ") ።
- ጠዳ (ዐረ. ጸደዐ/ገለጠ.ጻዕደወ)፡ በራ/ጠራ/ነጣ/አማረ ("ጥሩ ጥዱ ኾነ") ።
- ጠዳ፡ ያገር ስም ።
- ጠዳቂ፡ ጸዳቂ ።
- ጠዳፊ፡ የሚጠድፍ ("ተንከባላይ ቸኳይ") ።
- ጠዴቻ (ኦሮ)፡ የዕንጨት ስም ("ዐጣጥ ጠዴቻ መልካ እንዲሉ") ።
- ጠድፍ (ጸድፍ)፡ ገደል መያዣ መ ጨበጫ መርገማ መቈንጠጫ ("መቆሚያ የሌለው የገባበትን የሚያንር የሚያንከባልል") ።
- ጠዶ (ዎች)፡ ዕንጨቱና ቅጠሉ እንደ ጌሾ ጠላ የሚኾን ዛፍ ።
- ጠዶጠደፈ ።
- ጠጀ (ሜሰ)፡ ማርን እጋን ውስጥ ጨመረ/አገባ ("ዐሸ በጠበጠ አዘጋጀ አጣራ ሥሩ በግእዝ ጸገየና ጸገወ ጸደና ናቸው") ።
- ጠጃም፡ ባለጠጅ መኰንን ሴት ወይዘሮ ።
- ጠጅ (ጆች)፡ ከውሃ ከማር ከጌሾ ተዘጋጅቶ የተጣራ መጠጥ ።
- ጠጅ መልከኛ፡ የጠጅ ሹም።
- ጠጅ ሣር (የጠጅ ሣር)፡ ሽታው እንደ ጠጅ የሚጣፍጥ ሻካራ ሣር ("ከተክል የሚቈጠር ባውዳመት ቀን በጠጅ ቤት የሚ ጐዘጐዝ ዳግመኛም በበረሓ ስለሚለመልም ጣይ ሣር ይባላል") ።
- ጠጅ ቤት፡ የጠጅ ቤት አዛዥ ሴት ።
- ጠጅ፡ አነሣ/ቀዳ ("ከአንብላ ለየ ጠጅ አሳላፊ ጠጅ ሰጪ ዐዳይ ጠጅ ቤት (ቶች) ጠጅ የሚጣል በትና የሚቀመጥበት ቤት") ።
- ጠጅ፡ ከወይን ፍሬ የተደራጀ መጠጥ ("ወይን ጠጅ እንዲሉ") ።
- ጠጅ ጠጅ አለ፡ ሸተተ/ጣፈጠ ።
- ጠጅ ጠጅ፡ የዜማ ሥረይ ።
- ጠጅ ጣለ፡ ጠጀ ።
- ጠጆ፡ የጥጃ በሽታ ("የሚያከሳው የሚ ያመነምነው") ።
- ጠጆ፡ የጥጃ በሽታ፡ ጠዳ ።
- ጠገረ፡ ሼጠ ("ለጠገራ ለወጠ የጠገራ ላም እንዲሉ ጠገረን ሼጠ ማለት የጕራጌ ቋንቋ ነው") ።
- ጠገረ ጠዳ ።
- ጠገረ፡ ጠገራ ሠራ/ቀጠቀጠ/አበጀ ።
- ጠገረረ፡ ቀስ አሠኘ/አስቋፈ ("ቶሎ ቶሎ ና ምን ይጠገርርኻል እንዲል ባላገር ጠገረረ አበዛ አከበደ") ።
- ጠገራ (ሮች)፡ መሣሪያ ያልኾነ ያል ተበጀ ብረት ።
- ጠገራ፡ ባንድ ወገን ስለት ያለው ("በራሳም ዕንጨት ቀዳዳ የተዋደደ መፍለጫ ባለ፪ ማእዘን ጠገራ መባሉ እንደ ምሣር ጕረሮ ስለሌለውና ለጠገራው ልሳን ስላወጡለት ነው") ።
- ጠገራ ብር፡ መዳብና ንሓስ ኒኬል ወረቀት ያይዶለ ጥሩ ብር ("ወይም የብር ጠገራ") ።
- ጠገሮ፡ በይፋት ክፍል ያለ አገር ።
- ጠገበ (ጸግበ)፡ ሆዱ መላ/ረካ ("መብል ተወ ሰለቸ በቃኝ አለ ተነፋ ወፈረ ከዚህ የተነሣ ሰውን ናቀ ተቤተ ኰራ (ተረት) ካልጠገቡ አይዘሉ ካልዘለሉ አይሰ በሩ ባለጌ የጠገበ ለት ይርበው አይመስለውም") ።
- ጠገበ፡ አረገዘ/ከበደ/ደረሰ ("የሴት ሆድ ጠገበ ቀረበ ተጠጋ ጠገበች ከበዶች የሴት የእንስት ጠጋቢ የሚጠግብ ሀብታም") ።
- ጠገብ (ጸጊብ)፡ መጥገብ ።
- ጠገብ አለ፡ ኵራት ዠመረ ።
- ጠገብ፡ ዝኒ ከማሁ ("ጥቀርሻ ጠገብ እንዲሉ") ።
- ጠገተ፡ ላምና ጥጃን አገናኘ ("ዐለበ ኣንፋፋ ወተትን እከሌ ስንት ይጠግታል (ልባል) እንዲሉ") ።
- ጠገነ (ትግ. ጸገነ)፡ አሰረ/ጠቀለለ ("ዐከመ ፈወሰ አዳነ ዐደሰ ስብራትን ቤትን ጠገነ ጠቀመ ዐገዘ ረዳ ደገፈ ሰውን") (፪ ዜና. ፳፱፡ ፫፡ ኢሳ. ፴፡ ፳፯) ።
- ጠገን፡ ፈውስ/ጥቅም/ጠቀሜታ ።
- ጠገዴ፡ በስሜን አውራጃ ያለ አገር ("ሕዝቡ ዐማርኛና ትግሪኛ የሚናገር") ።
- ጠገገ (ጠግዐ ይመ)፡ ደረቀ/ተሰበሰበ ("መሻር መዳን ዠመረ ቅርፊት ያዘ የቍስል") ።
- ጠገገ፡ ጠገነ ።
- ጠገገ፡ ጠገግ ኾነ ("ተጠፈረ ተታታ ያልጋ") ።
- ጠገግ (ጎች)፡ አንዲት የሰንሰለት ብረት ሞላላ ቀለበት ("የመጋረጃ ቀለበትም ጠገግ ይባላል") ።
- ጠገግ፡ ምንጣፍ የሌለበት ባዶ ያልጋ ጠፍር ደረቅ ("ጠገግ ዐልጋ እንዲሉ") ።
- ጠገግ አለ፡ ጠገገ ።
- ጠጕረ ላሑ፡ ጠጕሩ ሯ የሣሣ የተለጠሰ ።
- ጠጕረ መንጝራ፡ ወቸገል የዥብ ኣለቃ። "እሱ ወደ ጥንብ በመጣ ጊዜ ሌሎቹ ይበተናሉ"። ቀመርን ተመልከት።
- ጠጕረ ሠሪ፡ ሽሩባ የምትሠራ/የምትመሽጥ ሴት ።
- ጠጕራም (ጸጓር)፡ ባለጠጕር ("ጠጕሩ የበዛ የረዘመ ናዝራዊ ጐፈር ዳፍሎ") ።
- ጠጕር (ጸጕር)፡ ጭገር ("ባሕርያዊ የገላ ልብስ የሥጋ ሣር በእንስሳና ባውሬ በወፍ በሰው አካል ላይ የሚበቅል (የድመት ጠጕር) ከሣር ጋራ የሚገኝ ታናሽ ቅጠል") ።
- ጠጋ (ትግ. ፀግዐ)፡ ዕዳሪ አወጣ ጨፈለቀ ተረተረ ።
- ጠጋ (ጠግዐ/ፀግዐ)፡ ጥግ አደረገ ያዘ (ዕብ. ፲፩፡ ፳፩) ።
- ጠጋ (ጸገወ)፡ ሰጠ/ቸረ ።
- ጠጋ (ፀጊዕ)፡ መጠጋት ።
- ጠጋ (ጸጋ)፡ ስጦታ ።
- ጠጋ፡ ሞጋጋ/ከሲታ/ሞጌያም ("ጕንጪ ደረቅ") ።
- ጠጋ አለ፡ ለጠቅ አለ ።
- ጠጋ፡ ጠገበ ።
- ጠጋ ጠጋ አለ፡ ለጠቅ ለጠቅ አለ ።
- ጠጋች (ቾች)፡ የጠገተ/የሚጠግት/ የሚያልብ ("ዐላቢ") ።
- ጠጋኝ (ኞች)፡ የጠገነ/የሚጠግን ("ቊስል አሳሪ ዐዳሽ ረዳት") ።
- ጠጋዛብ (ጸጋ ዘአብ)፡ የሰው ስም ("ያቡነ ተክለ ሃይማኖት ኣባት የአብ ስጦታ ማለት ነው") ።
- ጠጋጋ፡ የጠገገ ጐድኑ ጠገግ የመሰለ ጋ ።
- ጠጐረ (ጸጕሮጸጐረ)፡ ጠጕር አወጣ/አበቀለ ("ጨጐረ") ።
- ጠጠ፡ (መጠጠ)፡ ወርሶ፡ ጠረገ፡ አወጣ፡ ምንምን፡ ሳያስቀር፡ ቅቤን፡ ድልኸን፡ ማርን፡ ቡሖን፡ ጭቃን፡ ዐዛባን ።
- ጠጠረ (ትግ. ዐፀረ)፡ ጠና/ጠነከረ ("በረታ ደነጋ") ።
- ጠጠራም፡ ጠጠር ያለበት የበዛለት ስፍራ ("ባለጠጠር") ።
- ጠጠር (ሮች/ፀፀር)፡ ታናሽ የደን ጊያ ቅንጣት ("ባቄላና ዐተር የሚያካክል ከነዚህም የሚበላልጥ") ።
- ጠጠር ጣይ (ዮች)፡ ጠጠር የሚጥል/የሚበትን ("እንዲህ ይኾናል ይደረጋል የሚል መለኛ ጠንቋይ ርተኛ") ።
- ጠጠተ (ጸጸተ)፡ ቈጪ እተከዘ ("ምነው ባልሠራኹት ባላደረግኸት አሠኘ ጠ ጠተ የሕዝብ ጸጸተ የካህናት ነው") ።
- ጠጠት (ጸጸት)፡ ቍጭት/ንስሓ/ዐ ዘን/ትካዜ ።
- ጠጠን፡ አስተውል።
- ጠጡ፡ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች ኀላፊ አንቀጽ ("ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች ትእ ዛዝ አንቀጽ ይኾናል። እነሱ ጠጡ እናንተ ጠጡ") ።
- ጠጣ (ትግ. ጸጸወ)፡ ፉት/ጕንጭ አለ ("ጕርጕጭ አደረገ ተጐነጨ ሰቸ ማገ ሸመጠጠ ጨለጠ") (ሰቈ. ፩፡ ፬) ።
- ጠጣ፡ ለቅርብ ወንድ የሚነገር ትእዛዝ አንቀጽ ("ጠጣኸ ትጠጣለኸ ጠጣ") ።
- ጠጣ ጠጣ አደረገ፡ ጭልጥ ጭልጥ አደረገ ።
- ጠጣሪ፡ የሚጠጥር ("ጠንካሪ") ።
- ጠጣጣ፡ መላልሶ ጠጣ ።
- ጠጥ፡ ዝኒ ከማሁ ለጠጪ ("ሰች ቀለመ ጠጥ እንዲሉ") ።
- ጠጪ (ጮች)፡ የጠጣ/የሚጠጣ ("መ ጠጥ ወዳጅ") ።
- ጠጪነት፡ ጠጪ መኾን ("መጠጥ ማ ብዛት") ።
- ጠጭ፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጠፈረ (ጠፊር/ጠፈረ/ፀፈረ)፡ በጠፍር አጥብቆ አሰረ ("ገረፈ ታታ ጠለፈ ማገረ ጐለበ ከብትን ሰውን ዐልጋን ጣራን ከበሮን") ።
- ጠፈረ (ጸፈረ)፡ ጥፍርን በጥፍር ቈረጠ/ከረከመ ("እንስሳ በተወለደ ጊዜ") ።
- ጠፈረ፡ ጠቃ ።
- ጠፈራ፡ የመጠፈር ሥራ ።
- ጠፈር (ሮች)፡ ትት ማገር ("ጨምጨሞ ጭምጭማት የቤት ጣራ በቈዳ በገ መድ የታሰረ የተማገረ") ።
- ጠፈር፡ ላይኛው የበገና ጋድም ("ከታናናሽ ዕንጨትና ከጠፍር ቍራጭ ጋራ ፲ሩ የበገና አውታሮች (ዥማቶች) በላዩ ተጠም ጥመው የታሰሩበት ዕንጨቶቹና ቍርጥራጭ ጠፍሮቹም ማጥበቂያና ማላሊያ ቅኝት መስጫ ናቸው") ።
- ጠፈር፡ ሰማይ ("የምድር ባጥ በውሃ የተጠፈረ") (ዘፍ. ፩፡ ፯፡ ፯፡ ፯-፰) ።
- ጠፈር ደፈር፡ ጠፈር እንዳለፈው ("ደ ፈር የገመገም ጫፍ") ።
- ጠፈነ (ጸፈነ ትግ. ጠፈነ ጭቃ ለጠፈ)፡ ጠለፈ/አሰረ/ዘጋ ።
- ጠፈነነ፡ ጀነነ/ኣኰራ ።
- ጠፈነን/ጠፍናና፡ የተጠፈነነ ("ጅንን ኵሩ") ።
- ጠፈጠፈ (ጸፍጸፈ)፡ ጥፍጥፍ አበጀ ("አሞለሞለ ጋገረ በጣቱ ወጋ አሰነበረ አቦየ ዐተመ እበትን ሊጥን") ።
- ጠፈጠፈ፡ ሸሸ/ተጣጋ ("የሆድ (ተገ ብሮ)") ።
- ጠፈጠፈ፡ በጥፊ መታ/ወለወለ ጕንጭን ("ገቢር") ።
- ጠፈጠፈ፡ አነጠፈ/መረገ/ለበጠ ("መሬትን በደንጊያ በስሚንቶ በሉሕ") (፪ ዜና. ፫፡ ፮) ።
- ጠፈጠፍ (ነጸፍጻፍ/ነጠብጣብ)፡ የገደል/የዋሻ/የጣራ ፍሳሽ ("ብዙ ጠብታ") (ዘዳ. ፴፪፡ ፪) ።
- ጠፈጠፎች፡ ፍሳሾች/ጠብታዎች ።
- ጠፈፈ (ትግ. ጸፈፈ - ጽሕየ)፡ ቈለጩ ጠራ/ጥሩ ኾነ ሰማዩ ።
- ጠፈፈ፡ መድረቅ ዠመረ ("ጤዛው ጭ ቃው ሥጋው ጠፈፈ አልተለመደም") ።
- ጠፈፈ፡ ዐለቀ/ተጨረሰ/ቆመ/በራ ("(አባራ) ዝናሙ") ።
- ጠፈፍ አለ፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጠፊ፡ የሚጠፋ ("ኰብላይ ይህ ዓለም ዐላፊ ጠፊ ነው") ።
- ጠፋ (ጠፍሐ)፡ አነዘረ/ፈተለ ።
- ጠፋ (ጠፍአ)፡ ኰበለለ/ታጣ/ሞተ '
- ጠፋ (ጸፍዐ)፡ በጥፊ መታ ።
- ጠፋ፡ ተሰረቀ/ተወሰደ/ተበላ ("ገንዘቡ ከብቱ (ተረት) ገንዘብ የተውሶ ጠፋ ተጨ ርሶ") ።
- ጠፋ፡ ተደመሰሰ/ተበላሸ/ፈረሰ/ተፈታ/ባዶ ኾነ ("ከተማው አገሩ መልኩ ነገሩ") ።
- ጠፋ፡ ታወረ/ተሰወረ/ወደመ/ዕልም አለ/ተደረገመ ("ዐይኑ እሳቱ ጠፋ ተረሳ ተዘነጋ") ።
- ጠፋ፡ አጨበጨበ ("እጁን ቸብ ቸብ አደረገ") ።
- ጠፋ፡ ጣፈ ።
- ጠፋሪ (ዎች)፡ የጠፈረ/የሚጠፍር ("የሚታታ አሳሪ ገራፊ ጣራ ሠሪ") ።
- ጠፍ ማለት፡ ተግ ማለት ("ማባራት") ።
- ጠፍ፡ ባዶ ወና ቤት ("ያልቀና ያልታረሰ መሬት ለም ከጠፍ እንዲሉ") ።
- ጠፍ አለ፡ መጠጥ አለ ።
- ጠፍ አለ፡ መጠጥ አለ ።
- ጠፍ አለ፡ ከነውር ከጸያፍ ነገር ከልጅነት ጠባይ ራቀ ("ዐፍላው ዐለፈ") ።
- ጠፍ አደረገ፡ ፈጸመ/ከወነ/አቀለጠፈ ("ሥራን") ።
- ጠፍ ኾነ፡ ባድማ ኾነ ።
- ጠፍ፡ የጠፋ/የታጣ ።
- ጠፍ ያለ፡ መጠጥ ያለ ጠፍተኛ የኾነ የጠዳ ።
- ጠፍ ጨረቃ፡ የታጣች/ያልወጣች/ያልታየች ጨረቃ ።
- ጠፍር (ሮች)፡ በቁሙ ከተለፋ ቅ ሪላ የተቀደደ የተተለተለ የተተነተነ እንደ ልጥ እንደ ገመድ ማሰሪያነት ያለው ("ልም ዕቃ የመጫኛ የቀርቃባ የማነቆ የምራን የመርገጥ ጠፍር እንዲሉ (ያልጋ ጠፍር) ደረቅ ትት ፊት ርጥብ የነበረ ቈዳ") ።
- ጠፍር ነካሽ፡ የበቅሎና የፈረስ ዕቃ ሰፊ ("የሐሜት ስም") ።
- ጠፍተኛ (ኞች)፡ ጠፍታ ያለው ("ባለ ጠፍታ ዐዋቂ ጨዋ ምራቁን የዋጠ") ።
- ጠፍተኛነት፡ ጠፍተኛ መኾን ።
- ጠፍታ (ጽሕየት)፡ ጥራት/ጥሩነት ("ጨዋነት") ።
- ጠፍታ፡ ጥራት፡ ጠፈፈ ።
- ጠፍጣፊ፡ የጠፈጠፈ/የሚጠፈጥፍ ።
- ጠፍጣፋ (ፎች)፡ ጽፍሕ፡ ዝርግ ሰ ታታ ("ምጣድን ሰፌድን የመሰለ ዐሰላ ጠፍጣፋ ደንጊያ እንዲሉ") ።
- ጡሊ፡ ቅል፡ ጦለ ።
- ጡሊ፡ አጠላ (አጽለለ) ።
- ጡሊ፡ የቃልቻ ቅል ።
- ጡሊያም፡ ጡሊ ተሸካሚ ("ባለጡሊ እስላም") ።
- ጡል፡ በጐዣም ክፍል ያለ ወንዝ ።
- ጡል፡ ንዝህላል፡ ጦለ ።
- ጡል፡ ንዝህላል/ዝንጉ ።
- ጡልጡል አለ፡ ተንጦለጦለጡንጡን ሊያ ።
- ጡረተኛ (ኞች)፡ ጡረታ ወዳድ/ባለጡረታ/ተጠዋሪ ("ያገር አባት ወይም እናት በሰው ትከሻ ዐዳሪ ራሱን የማይችል የልጅ ጡረተኛ እንዲሉ ወንድና ሴትን ለመ ለየት ጡረተኛው ጡረተኛዋ ይሏል") ።
- ጡረት/ጡረታ (ጹረት)፡ ያረጀ/ያፈጀ ሽማግሌን መጦር ("ርዳታ ሸከማ ጡረታ ገባ ተጦረ በሰው እጅ ዐደረ") ።
- ጡረኛ (ኞች)፡ ግፈኛ/በደለኛ ።
- ጡር (ጽዉር)፡ ሸክም የኾነ ሽል ጌጥ ።
- ጡር (ጽዉር)፡ የክፉ ሥራ ብድራት/ፍዳ ("በሰው ላይ የጫኑት ቀንበር ጭቈና በደል ቅጣት መስቃ ተግዳሮት እከሌ በድኻ ላይ ግፍ አብዝቶ ነበርና ጡር ደረሰበት") ።
- ጡር፡ ቅጣት፡ ጦረ ።
- ጡር ተፋ፡ ማለ ።
- ጡር ትፋ፡ ማል ።
- ጡር ነው፡ ግፍ ነው ።
- ጡር አለበት፡ ሰውን በድሏል ።
- ጡር/ጥር (ጸዋሪት)፡ የተሸከመች/የያዘች ("ነፍሰ ጡር ደንገ ጥር እንዲሉ") ።
- ጡብ (ቦች/ጥብዖት)፡ ከቀይ ዐፈር የተበጀ አራት ማእዘን ሸክላ ለግንብ የሚኾን (ዘፀ. ፭፡ ፰, ፲፬, ፲፰, ፲፱) ።
- ጡብ፡ ለጣራ ክዳን የሚደረግ ሸክላ ቀናፋ ።
- ጡብ አለ፡ ዱብ አለ ።
- ጡብ ጡብ አለ፡ ዱብ ዱብ መር መር አለ ("ዘለለ ጮቤ መታ") ።
- ጡታም፡ ወሻም ("ባለትልቅ ጡት") ።
- ጡታም፡ ወሻም ("ባለትልቅ ጡት").
- ጡታም፡ ጡት ያለው ("ሰንና ማንቈርቈሪያ ኵስኵስት መስቴ የንሓስ የቈር ቈሮ የሸክላ") ።
- ጡታም፡ ጡት ያለው ("ሰንና ማንቈርቈሪያ ኵስኵስት መስቴ የንሓስ የቈር ቈሮ የሸክላ").
- ጡት (ጥብ)፡ የእንገር የወተት ሥጋዊ ቋት ("የበሰለ ደም ከረጢት ኪስ በሴት በእንስት ደረትና ሆድ ጕያ ተደርድሮና ተንጠ ልጥሎ ያለ ባለ፪ ባለ፬ ባለ፰ ፍንጭ") ።
- ጡት በቁሙ፡ ጠባ (ጠበወ) ።
- ጡት ተጣባ፡ ተዛመደ ("አባትና ልጅ ተኳዃነ") ።
- ጡት ተጣባ፡ ተዛመደ ("አባትና ልጅ ተኳዃነ").
- ጡት አስጣለ፡ አስተወ/አስለቀቀ ።
- ጡት አስጣለ፡ አስተወ/አስለቀቀ.
- ጡት አስጣይ፡ ታናሽ ወንድምና እት ጡት ያስተወ/ያስተወች ።
- ጡት አስጣይ፡ ታናሽ ወንድምና እት ጡት ያስተወ/ያስተወች.
- ጡት አዘራር፡ የተንኰል ዐሳብ ወይም ዘዴ ።
- ጡት አዘራር፡ የተንኰል ዐሳብ ወይም ዘዴ.
- ጡት አጣባ፡ የጡት ልጅ አኳዃነ ።
- ጡት አጣባ፡ የጡት ልጅ አኳዃነ.
- ጡት ጣለ፡ ተወ (ኢሳ. ፳፰፡ ፱) ።
- ጡት ጣለ፡ ተወ (ኢሳ. 28፡ 9).
- ጡቶች (አጥባት)፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ (ማሕ. ፩፡ ፲፫፡ ሕዝ. ፲፮፡ ፯) ።
- ጡቶች (አጥባት)፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ (ማሕ. 1፡ 13፡ ሕዝ. 16፡ 7).
- ጡንቻ (ዎች)፡ ጠና (ጸንዐ)፡ ወርች ("ከብብት እስከ ኵርማ ያለ የእጅ ክፍል መካከሉ ዐይጥ የሚባል የግእዝ ስሙ መዝራዕት ነው") ።
- ጡንቻ፡ ጠፋ ።
- ጡንቻም፡ ባለወፍራም ጡንቻ ።
- ጡንጡን አለ፡ ቸኰለ/ሮጠ ።
- ጡጢያም/ጣጤ፡ ፈሳም ።
- ጡጥ፡
- ጡጥ አለ፡ ጣጥ አለ ("ተፈሳ ጡጢ ፈስ") ።
- ጡጦ፡ የላስቲክ ጡት ።
- ጢል፡ መንጠልጠል ።
- ጢል አለ፡ ስቅል ሲል አለ ("ተንጠለጠለ") ።
- ጢሎሽ፡ መንጠልጠል፡ (ጠለ ጠለ) ።
- ጢሎሽ፡ የመንጠልጠልና የግልብጮ ጨዋታ ።
- ጢማም (ጸሓም)፡ ጢመ ረዥም ("ጢመ ብዙ አሮንን አባጽሕማን ኣቦን የመ ሰለ ሰው ሪዛም") ።
- ጢም (ጽሒም)፡ መምላት ።
- ጢም (ጽሕም)፡ የጕንጭና ያገጭ ጠጕር ("የተባት ምልክት ከ፳፭ ዓመት በላይ የሚያቀነቅን የሚያድግ ሪዝ (ተረት) ጢም የሌለው መምር ዐጸድ የሌለው ደብር") ።
- ጢም አለ (ጸሐመ)፡ መላ ተንተ ረፈፈ ("ቲፍ አለ ውሃው") ።
- ጢሞ፡ ዝኒ ከማሁ ("ባለጢም ጢሙ የበዛ ' የረዘመ ዳግመኛም ሞ ኣክብሮን ወ ይም አኅስሮን ያሳያል") ።
- ጢሞች፡ ሪዞች ።
- ጢቅ፡ መርጨት ።
- ጢቅ አለ፡ ምራቁን ረጩ ("ሰው ናቀ") ።
- ጢቅ፡ ጠቀጠቀ ።
- ጢቅመርጨት፡ ጤቀ ።
- ጢቅታ፡ ጢቅ ማለት ("ወይም ምራቅ") ።
- ጢቆሽ፡ ጠባብ የውሃ መርጫ ("እንደ ውዥሞ ያለ ከዚያም የጠበበ") ።
- ጢብኛ (ኞች)፡ ክብ የኾነ ታናሽ ዳቦ ("በቅጠል የተጋገረ በለከትና በሽልጦ መካከል ያለ") ።
- ጢን (ጢም)፡ መጥገብ/መስከር ("የ ሆድ መምላት መኵራት") ።
- ጢን አለ (ጢም አለ)፡ ጠገበ ፥ ሰከረ ("ፈጽሞ ኰራ በልቡ ኵራት መላበት") ።
- ጢንጦ፡ የመሬት ድርሻ ("ትንትን ዕጣ ታናሽ ክፍ") ።
- ጢጢ፡ ዐለንጋ/ጅራፍ ("ከተልባ እግር የተዘጋጀ (ግእዝ)") ።
- ጢጢ ጠጠረ ።
- ጣ አለ፡ ድምፅ ሰጠ ("የክፋይ (ጧጧ) አንጧጧ አንጣጣ ተንጧጧ ተንጣጣ") ።
- ጣለ (ጸዐለ/ጠሐለ)፡ ገደፈ/ፈነረ ወረወረ/አሽቀነጠረ/ጠነጠነ/ተወ ("ዕቃን አገርን ሃይማኖትን") (፪ ዜና. ፳፩፡ ፲) ።
- ጣለ፡ በርካሽ ሺጠ ።
- ጣለ፡ አደረገ ።
- ጣለ፡ ከስም ።
- ጣለ፡ ጨመረ/አገባ ።
- ጣለበት፡ ፍቅር አሳደረበት ።
- ጣሊያኑ፡ ያ ጣሊያን ።
- ጣሊያን (ኖች)፡ የኢጣሊያ ሰው፡ ወይም ሕዝብና ነገድ። ጣሊያኖችም አገሪቱን ኢታሊያ፡ ኣንዱን ሰው ኢታሊያኖ፡ ብዙዎቹን ኢታሊያኒ ይላሉ ።
- ጣሊያን የሮም ሰው፡ ኢጣ
- ጣሊያኖቹ፡ እነዚያ ጣሊያኖች ።
- ጣሊያኗ፡ ያች ጣሊያን ።
- ጣላ (ጸዐልኦ)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ("ልቀቃ ወርውራ ማለት ነው") ።
- ጣላ (ጽዑል)፡ የተጣለ ("የጥጥ በሽታ ቀይ ጣላ እንዲሉ") ።
- ጣል (ጥሒል)፡ መጣ ።
- ጣል አደረገ፡ ርግፍ አደረገ ።
- ጣል፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጣል ጣል አደረገ፡ አረካከሰ ።
- ጣልቃ፡ በ፫ ፊደል መካከል የገባ ልዩ ፊደል ።
- ጣልቃ፡ አለተራው/አለስፍራው መግባት/መገኘት ።
- ጣልቃ ገባ፡ በሌላ ሥራ ወይም ነገር መካከል ዘው አለ ።
- ጣልቃ ገባ፡ ጦም ገባ፡ ክራይ ገባ፡ ክረምት ገባ፡ ልቡ ገባ፡ መከራ ገባ፡ ንስሓ ገባ፡ ሥራ ገባ፡ ዕዳ ገባ፡ ቅዳሴ ገባ ። (ቀለም ገባ)፡ ተነከረ ታለለ ። (ሱባዔ ገባ)፡ ከሰው ተለየ ።
- ጣመ (ጥዕመ/ጠዐመ)፡ ቀመሰ ("በጥቂቱ በላ እከሌ ወባ ስለ ተነሣበት ዛሬ እኸል ሳይጥም ዋለ") ።
- ጣመ (ጥዕመ/ጠዐመ)፡ ጣፈጠ ("ጣፋጭ ኾነ (ተረት) ጣመኝ ድገመኝ ለህያ ማር አይጥማት (ግጥም) እግዜር ሲ ቈጣ በትር አይቈርጥም ያደርጋል እንጂ ነገር እንዳይጥም") ።
- ጣመ ቢስ፡ ለነገሩ ጣም የሌለው ("ለዛ ሲስ ለዛ ሙጥጤ") ።
- ጣመተ (ጻመተ)፡ ተጨረሰ/ዐለቀ/ ጠፋ/ተቃጠለ ።
- ጣመተ፡ ተፈጨ/ደቀቀ ።
- ጣመተ ጠና ።
- ጣመነ (ጻመወ/ጸመወ)፡ አደከመ/ አጓጐለ/አለተተ ("እግርን") ።
- ጣመነ፡ ጠመቀ ።
- ጣመን (ጻማ)፡ የሙሓይት ድካም ("ጕጕለት ጓጓላነት መንገደኛው ጣመኑን አረገፈ") ።
- ጣሚ፡ የሚጥም ("ጣፋጭ") ።
- ጣሚ፡ የቀመሰ/የሚቀምስ ("ቀማሽ") ።
- ጣማ (ጻመወ/ጻማ)፡ ድካም/ልፋት ።
- ጣማ ገንዘብ (ንዋየ ጻማ)፡
- ጣማ፡ ጠመደ ።
- ጣም (ጣዕም)፡ መጣፈጥ ጥፍጥነት ዞ
- ጣም፡ ብዛት/ብዙነት ።
- ጣም ዐጣ፡ ሳይጣፍጥ ቀረ ("መጣፈጥን አላገኘም") ።
- ጣምራ (ሮች)፡ ባልና ሚስት ("በሕግ በሥርዐት የተጣመሩ የፍቅርና የኑሮ የሩካቤ አንድነት ያላቸው") ።
- ጣምራ ጦር፡ ባላንድ ጕረሮ ባለኹለት አፍሬ ("መንታ ጦር") ።
- ጣሰ (ፀሐሰ/ትግ. ጠሐሰ)፡ ወደደ/ገፋ/ከፈለ ("ሰበረ ረገጠ አስተኛ ነደለ ቀደደ አፈረሰ ጥሻን ሰብልን የጦር ሰራዊትን ድልድልን ዐጥርን ዳኛን ልጓምን ጣሰሰን እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ጣሰ ሠራ መሸጠ ሽሩባን ጣሰ ያገዳ እኸልን ፈጩ ጣሽ አፍራሽ") ።
- ጣሠ፡ ነደለ አፈረሰ፡ ጣሰ ።
- ጣሰሰ፡ ጣሰ አወደቀ ።
- ጣሳ (ሶች)፡ ከታኒካ የተሠራ ዕቃ ክብና ፬ ማእዘን ("የጥዋ የዋን፵ መጠን ከነዚህም የሚበልጥ ከባሕር ዘይትና ፍራፍሬ ምግብ የሚመጣበት") ።
- ጣሴ/ጣሰው፡ የወንድ መጠሪያ ስም ።
- ጣስ (ዝ)፡ ባሬታ መክፈያ ("የሽንት የልባም መቀበያ") ።
- ጣስ፡ ልቦ
- ጣስ፡ ዝኒ ከማሁ ("አጋም ጣስ እን ዲሉ") ።
- ጣስ፡ የቅርብ ሰው ትእዛዝ አንቀጽ ።
- ጣረ (ጽዕረ)፡ ተጨነቀ/ተጋ/ለፋ ደከመ ።
- ጣረ ሞት (ጻዕረ ሞት)፡ የሞት ጭንቅ ("ወይም ክፉ የሞት መልክተኛ (መል
- ጣረ ሞት፡ ጥርሰ ገጣጣ ("ጥርሱ ተከንፈሩ ተርፎ ጣይ የሚሞቅ ሰው") ።
- ጣረት፡ ጋይ ብዙ ድካም ያለበት ።
- ጣረት ጋይ፡ ጣረ ።
- ጣረኛ (ኞች)፡ ጭንቀታም ("ጣረ ብዙ ባለጣር") ።
- ጣሪ፡ የጣረ/የሚጥር/የሚለፋ ("ትጉህ ሠራተኛ") ።
- ጣራ (ዎች)፡ ጠየረ) ("ባጥ ጠፈር እንደ ጃን ጥላ እንዳጐበር እንደ ወስከንባይ በላይ የተዘረጋ ከንጨት ከሸማ ከበርኖስ - የተበጀ (የተሰፋ) በግእዝ ጢሮት ይባላል ደራንና ዘባን ተመልከት") ።
- ጣራ፡ መጨረሻ ስንኝ ("ወይም ግጥም ገደገደ ብለኸ ግድግዳን እይ") ።
- ጣራ፡ ጥሬ፡
- ጣር (ጻዕር)፡ ጭንቅ/ምጥ ።
- ጣር ኾነ፡ ለሞት ቀረበ ።
- ጣር ጋር (ገዓረ ጻዕር)፡ የጣር ጩኸት ።
- ጣርማ፡ የጸድቅ ስም ("ጻዕራዊ ባለጭንቅ ባላገር አባ ሕፃን ሞአን አባ ጣርማ እንዲል ይኸውም ስም ጻድቁ ከበሬ ጋራ ተጠምደው ፫ ፈር ማውጣታቸውንና መን ፈሳዊ ተጋድሏቸውን ያሳያል") ።
- ጣርማበር (ማኅበረ ጻዕር)፡ የተራራ ስም ("ጉምና ካፊያ የማይለየው አስታና ጓሳ የሚበቅልበት ገመገም የተጕለትና የይፋት ጫፍ ጭንቅ ያለበት ማበር (ድግስ) ወይም ማን አጥብቆ የጣር ባለጣር ጣረኛ በር ሥርጥ ማለት ነው (ጣር ማበር (ጥማ) ጣርማ በር) አባን እይ") ።
- ጣቍሳ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ።
- ጣቃ (ዐረ)፡ የሸማ/የሐር ልብስ/የሻሽ ጥቅል ("መዳ") ።
- ጣቃ (ግእዝ)፡ ጨለማ/ጭጋግ ።
- ጣቈሰ (ጠቀሰ)፡ በነገር ነካ/ጐሸ መጠ/ደፈረ ።
- ጣቈሰ፡ አሳበቀ/ኣዋሸከ ።
- ጣቈሰ፡ ዘር ደገመ ("መልሶ ዘራ") ።
- ጣቅማ፡ የንጨት ስም ("ጕጣም ሻካራ ዕንጨት ዐጣጥ መሳይ") ።
- ጣቋሽ፡ የጣቈሰ/የሚጣቍስ ("አፈኛ አሳባቂ") ።
- ጣቢ፡ ጦላ ("ቀልቃላ ሴት ጣቢ ከጠበጠበ ጦላ ከጦለ ይወጣል።") ።
- ጣቢታ፡ ዐይናማ እንጀራ ("በግእዝ ግን ፌቆ ማለት ነው") ።
- ጣቢያ (ዐረ. ጣቢያህ)፡ በወንዝ ያለ የአለት ዋዲያት የውሃ መታቈሪያ ።
- ጣቢያ፡ የባቡር መቆሚያ ስፍራ ("የአይሮፕላን ማረፊያ") ።
- ጣቢያ፡ የዘበኛ/የወታደር/የጦር ሰራዊት መሰብሰቢያ/መከማቻ/ሰፈር ዐልፎ ዐልፎ የሚገኝ ።
- ጣባ (ጸብኀ/መጽብኅ)፡ ጻሕል/ወጭት ("የወጥ ማቅረቢያ ማጥቀሻ ከፍተኛና ዝቅተኛ የሸክላ ዕቃ") ።
- ጣብ (ኀዝል)፡ የመቃ ሥንጣሪ ("ልጆች እምድር ላይ እየጣሉ የሚጫወቱበት ቍጥሩ ፮ ዠርባው ወደ ላይ ሲኾን ንጉሥ ሆዱ (ውስጡ) ወደ ላይ ሲኾን ራስ ይባላል በትግሪኛም ስሙ ሸደድ ነው በጐዣም ኋደሬ ይሉታል።") ።
- ጣቦ፡ በጣሳ የሚቀርብ ምግብ ("እንደ እንቀት ያለ ወይም ሌላ") ።
- ጣተ፡ ጣትን አነሣ ("ቀ ሰረ") ።
- ጣት (ቶች)፡ የእጅና የእግር የመንሽ የሹካ ፵ፍ ("ዐጽቅ ቅጥይ መያዣና መህበ አውራ ጣት ሌባ ' ጣት መካከለኛጣት የቀለበት ጣት ታናሽ ጣት እንዲለ ጣት የወጣት ከፊል ነው ምስጢሩም መጣትንና በላይ መኾንን ያሳያል በግእዝም ፃት ይባላል (ተረት) ዘሩ የጣቴ ምድሩ ያባቴ በቈማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ነው") ።
- ጣት ይጠባል፡ ሕፃን ነው ("አላዋቂ ነው") ።
- ጣና (ጠኒን/ጠነ)፡ የባሕር ስም ("በጐዣምና በበጌምድር መካከል ያለ የረጋ ውሃ በውስጡ ፫ ደሴቶች ያሉበት ጥቍር አባይ በላዬ የሚኼድበት") ።
- ጣናት፡ ሕፃን ዐራስ ልጅ ("እንቦቀቅላ") ።
- ጣናቶች፡ ሕፃናት/ጨቅሎች/ዐራሶች "
- ጣዕማ (ጥዕመ)፡ የንጨት ስም ("የቅጠሉ ሽታ ጣፋጭ የኾነ አነስተኛ ዛፍ ሴቴ ጦሚት ጣዕማ በግእዝ ጣ ማለት ነው") ።
- ጣዖታም፡ ጣዖት አምላኪ ("ባለጣፆት አረመኔ") ።
- ጣዖት (ቶች)፡ ጠዐወ፡ በጥጃ አምሳል ከወርቅና ከብር ከሌላም ማዕድን ከንጨት የተበጀ ምስል ("የግብጽ አሕዛብ ያመልኩት የነበረ እስራኤልም በገዳም ሠርተው የሰገዱለት የወርቅ ጥጃ ማንኛውም ሥዕል ምሳሌ የአሕዛብ ሥራ ከወገብ በታች ጣዖት ከወገብ በላይ ታቦት እንዲሉ") ።
- ጣውንት (ቶች/ጸወነ)፡ ጐባን ("የሌ ላውን ሰው ሚስት ያገባ የተጠጋ ወንድ የሌላዋን ሴት ባል ያገባች የተጠጋች ሴት") ።
- ጣውንትነት፡ ጐባንነት ።
- ጣዎስ፡ እጅግ የምታምር የህንድ ወፍ ("ዥጕርጕር በሶራ ላይ የምትሣል ዐረብ የገነት ወፍ ይላታል ቅዱስ መጽሐፍም በጣ ዎስ ፈንታ ጠዋዊስ ይላል") (፪ ዜና. ፱፡ ፳፩) ።
- ጣዝ፡ የውሃ መቅጃ ጣሳ ።
- ጣዝሙት (ጣዝማዊት)፡ የጣዝማ ወገን/ጣዝማማ ("ባለያ ሴት እንጀራና ወጥ ዳቦና ጠላ ጠጅ ፈትል ስፌት በያይነቱ የምታውቅ ከጠብ ከጭቅጭቅ ከንዝንዝ የምትርቅ ዶንሴ ሰላማዊት የሴት ቍንጮ (ንግሥት)") ።
- ጣዝማ (ሞች)፡ በመሬት ውስጥ ማር የምታበጅ ትንኝ ("እንደ ንብ የማትናደፍ በግእዝ ጸደና ትባላለች") ።
- ጣዝማ፡ የጣዝማ ማር ("ጣዝማ በዞፍ ከረጢት የምታሰናዳው ለሳልና ለዕባጭ ይበጃል (ተረት) ጣዝማ ፥ ይሰረስራል ዳኛ ይመረምራል") ።
- ጣዝማ፡ የፍየል መልክ ።
- ጣዠ፡ ዠ ሞዠቅ ("ጥሬ ዕርሻ ዐረሰ ወረ ወር") ።
- ጣዠ፡ ገረፈ/መታ/መለጠ ።
- ጣዩ፡ ያ ጣይ ("ፀሓዩ") ።
- ጣይ (ፀሓይ)፡ በቁሙ ጀንበር ።
- ጣይ (ጸዓሊ/ጠሓሊ)፡ የጣለ/የሚጥል ("የሚወረውር በጥባጭ ጠጅ ጣይ እን") ።
- ጣይ ሞቄ፡ ጣይ የሚሞቅ ("ገጣጣ ጥርስ እንቅርብጭ") ።
- ጣይ ሶራ፡ ድብልብል ነጭ ስንዴ ("፪ኛ ስሙ ያቡን እግር ባለያ ሴት ስትጋግረው ዳቦው በፀሓይ የበሰለ ይመስላልና ስሙ ጣይ ሶራ (የጣይ ሶራ ባለፀሓይ ግምጃ) ነጭ ሐር ተባለ") ።
- ጣይ ቤዛ (የጣይ ቤዛ)፡ ጥላ ቅጠል ።
- ጣይቱ ብጡል፡ የዳግማዊ ምኒልክ ባለቤት ("ሚስት ይተጌ ጣይቱ እንዲሉ") ።
- ጣይቱ፡ ያች ፀሓይ ("ፀሓይዋ ጣይቱ የሴት ስም") ።
- ጣይየሚጥል፡ ጣለ ።
- ጣደ (ጸዐደ)፡ ምጣድን ሌላውንም ሸክላ በጕልቻ ላይ አሰረረ ("፵ነ አስቀመጠ ጣደ ዋቢ አሳለፈ አቀረበ ሰጠ ደቀነ") ።
- ጣዲቁ፡ የሰው ስም ("የወልደ ጣዲቅ (ጻድቅ) ከፊል") ።
- ጣዲቅ፡ ጻድቅ ።
- ጣዲቋ/ጣዲቄ፡ የሴት ስም ("የወለተ ጣዲቅ (ጻድቅ) ከፊል") ።
- ጣድቃን፡ ጻድቃን ።
- ጣጅ (ጸዓዲ)፡ የጣደ/የሚጥድ ።
- ጣጋ፡ አንዠቱ የተጣጋ ደረቅ ኰስማና ወንድ ("ወይም ከሲታ ሴት") ።
- ጣጠኛ (ኞች)፡ ባለጣጣ ("ጣጣው የበዛ") ።
- ጣጣ (ጣእጥአ/መቀቀ)፡ አደረቀ ላጠ ("አንገበገበ አቃጠለ ጕረሮን") ።
- ጣጣ (ፃእፃእ)፡ ጕዳይ/ሐሳብ/ችግር/መከራ ።
- ጣጣ፡ የዛፍ፡ ስም፡ ሜርቆ ።
- ጣጣ ፈንጣጣ፡ የፈንጣጣ ጣጣ ጠንቅ ።
- ጣጣለ፡ መላልሶ ጣለ/ወራወረ ።
- ጣጣቴ፡ ሲተኵሱት የሚንጣጣ በሽታ ("በ፲፱፻፲፪ ዓ. ም. የነበረ") ።
- ጣጣቴ፡ የሚንጣጣ ጣጣ ።
- ጣጣፈ፡ ከታተበ ።
- ጣጣፈ፡ ጠቃቀሙ ሰፋፋ ።
- ጣጤ፡ ጣጢያም/ፈሳም ።
- ጣጥ አለ፡ ጡጥ አለ ("ተፈሳ") ።
- ጣጥ አደረገ፡ ጡጥ አደረገ ("ፈሳ ፈሱን ለቀቀ") ።
- ጣጥ፡ ጡጢ/ፈስ ።
- ጣጥራስ፡
- ጣጥራስ፡ ያረመኔ ነገድ ።
- ጣጭ፡ የጠጠ፡ የሚጥጥ፡ ጠራጊ፡ ጠጥ፡ (ጦች)፡ ደድ፡ ጨርሶ፡ የሰረቀ ።
- ጣፈ (ጸሐፈ)፡ ጻፈ/ከተበ ("ቃልን ነገርን ሰብራና በወረቀት ላይ ሣለ በማንኛውም ሰሌዳ ውስጥ አኖረ") ።
- ጣፈ፡ ሰፋ/ጠቀመ/ለጠፈ ("የልብስን ቀዳዳ ደፈነ") ።
- ጣፈ፡ ጣፈጠ ።
- ጣፈጠ (ጻፈጠ)፡ ማር ማር ጨው ጨው አለ ("ጣመ ጣም አገኘ ምግቡ ሽ ቶው ነገሩ") (ዘፀ. ፲፭፡ ፳፭፡ ማር. ፱፡ ፵፱) ።
- ጣፈጠ፡ ጣፈጥ ("የሰው ስም") ።
- ጣፊ (ፎች)፡ ጸሓፊ፡ የጣፈ' የሚ ጥፍ ("ጻፊ ለጣፊ ጠቃሚ ሰፊ ቁም ጣፊ'ደብዳቤ ጣፊ እንዲሉ") ።
- ጣፊነት፡ ጣፊ መኾን ።
- ጣፊያ (ጣፍያ)፡ የዝንጀሮ ቂጣና ጥርኝ መሳይ የሆድ ዕቃ ("በግራ ጐን በጨጓራ ላይ ተለጥፎ የሚገኝ መናኛ ሥጋ (ተረት) ሥጋ ቍጠር ቢሉት ጣፊያ አንድ አለ ሲበዛ ጣፊያዎች ይላል") ።
- ጣፊያ፡ ጠፈረ ።
- ጣፋ፡ ከወርቅና ከብር ከሌላም ማዕድን የተሠራ የጋሻ ልባጥና ጌጥ ።
- ጣፋ፡ የጋሻ ጌጥ ("ጠፈጠፈ") ።
- ጣፋ ጋሻ፡ ጣፋ ያለበት ("የጣፋ ጋሻ") ።
- ጣፋጭ/ጣፋጣ (ጽዑጥ)፡ የጣፈጠ/ የሚጣፍጥ ("ጣም ያለው ማር ሸንኰራገዳ ጥንቅሽ ተምር በለስ ሱካር ድንች የመስለው ኹሉ") (ሕዝ. ፫፡ ፫) ።
- ጣፋጭነት፡ ጣፋጭ መኾን ።
- ጣፌ ትዛዝ (ጸሓፌ ትእዛዝ)፡ ትዛዝ ጣፊ ("የጥፈት ሹም") ።
- ጣፎርዴ፡ ጥፍራም ባለጌ ።
- ጣፎንጋ (ጥፉነ ሥጋ)፡ የማያምር ሰው አፎንቻ ("ሰውነቱ በስንፍና የታሰረ ቀፍዳዳ ሰነፍ") ።
- ጣፎንጋ፡ እኸል የማያበቅል መጥፎ መሬት ።
- ጤቀ (ጸየቀ)፡ ተበከለ/አደፈ/ተበላሸ ።
- ጤቀ፡ ተሰደበ/ተጨነቀ ።
- ጤቀኛ (ኞች)፡ ተሳዳቢ/ነገረኛ ("ስም አጥፊ ባለጌ") ።
- ጤቅ (ትግ. ጠይቂ)፡ የገጣባ መሸ ፈኛ ድብዳብ ።
- ጤቅ፡ ክፉ ስድብ ("ስም የሚያጠፋ ዐጥንት የሚያሳድፍ") ።
- ጤት፡ የፊደል ስም ጠ ("በ") ።
- ጤነ/ጠየነ) አጤነ፡ ዐሰበ/እስ ታወሰ/ልብ አደረገ/መረመረ/አስተዋለ ።
- ጤነኛ (ኞች)፡ ዝኒ ከማሁ ለጤናማ ።
- ጤና (ጥዕየ/ጥዒና)፡ ፈውስ/ሕይወት/ ደኅና ።
- ጤና ቢስ፡ በሽተኛ ("የበሽታ ጐሬ ተውሳካም ታሞ አይድኔ") ።
- ጤና አገኘ፡ ታሞ ዳነ ተነሣ ።
- ጤና ይስጥልኝ፡ በመገናኘትና በመለየት ጊዜ የሚነገር የቃል ሰላምታ ።
- ጤናማ (ሞች)፡ ጥዑይ፡ ጤናም/ባለጤና ("ቃር አያውቅሽ ደኅና ደኅነኛ") ።
- ጤናማ ኾነ፡ ተሻለው/ተፈወሰ/ሻረ ።
- ጤናዳም (ጤና አዳም)፡ የአዳም (የሰው) ጤና ("ለመጋኛና ላልታወቀ ድንገተኛ ዕመም ኹሉ መድኀኒት የሚኾን ሽታው ጣፋጭ ቅመማዊ ተክል") ።
- ጤንነት፡ ደኅንነት ።
- ጤንነት፡ ደኅንነት ።
- ጤዛ፡ የዝናም/የካፊያ ጠብታ ("በሣር/በቅጠል ላይ የሚታቈር የሚንቈረዘዝ ቤዛ ጢሰ (ተነ) ጊሜ ከማለት ይሰማማል") ።
- ጤፉት፡ በግሼን ማሪያም የምትገኝ የትንቢት መጽሓፍ ስም ።
- ጤፍ (ፎች)፡ የታናሽ እኸል ስም ("የሣር ዐይነት ሙርዬ የሚመስል ነጭ ቀይ ጥቍር ሰርገኛ (ተረት) ሳይቸግር ጤፍ ብድር በግእዝ ጠይፍ ይባላል ዳግመኛም ስሙ አቦልሴ ቡንኝ ጐራዴ ጨንገር ነው ኹሉንም በተራው ተመልከት") ።
- ጤፍ ዐጋይ (ጠይፈ ሐጋይ)፡ በግንቦት የሚዘራ የበጋ ጤፍ ።
- ጥሕሎ (ጥሒል/ጠሐለ)፡ በወጥ እየተጠቀሰ የሚበላ በሶ ("ጥሕሎ ትግሪኛ ነው") ።
- ጥለት (ቶች)፡ በያይነቱ ቀለም የገባ ፈትል ("በሸማ ዳር የሚጣል ዕድያት ቀይ ጥለት ጥቍር ጥለት እንዲሉ") ።
- ጥለት (ጽዕለት)፡ መጣል/ውርወራ ።
- ጥለት፡ ባለቀለም ፈትል፡ ጣለ ።
- ጥለት፡ ያይን ጉም/ጢስ/ሐበላ ("በገላ ላይ ያለ ድል ቋቍቻ") ።
- ጥለኛ (ኞች)፡ የተጣላ ("ጥል ያለው የነበረው ባለጥል") ።
- ጥሉላት፡ ሥጋና ቅቤ ወተት ዕንቍላል (ግእዝ) ።
- ጥላ (ጽላል/ጽላሎት)፡ ጃን ጥላ/ድባብ ("ከግምጃ ከሰሌን ከቀጤማ የተበጀ የሚ ጨበጥ የፀሓይ ከለላ የዳስ የድንኳን የቤት ውስጥ የዛፍ ሥር ከጥላ ያረፉ ከሞት የተረፉ እንዲሉ (የማሪያም ጥላ) ድድኾ እመቤታችን በስደት ጊዜ የያዘችው") ።
- ጥላ፡ ሩካቤ ብእሲ ወብእሲት ("የቍስል ጠንቅ ያጥንት ልጅ") ።
- ጥላ በረደ፡ አየሩ ነፈሰ/ቀዘቀዘ ("ዐሥር ሰዓት ኾነ") ።
- ጥላ፡ በቁሙ፡ ጠላ፡ አጠላ ።
- ጥላ ቢስ፡ ቀላል ከውካዋ ሰው ።
- ጥላ ተመለሰ፡ ወደ ምሥራቅ ዞረ ።
- ጥላ፡ ትታ አስቀምጣ ።
- ጥላ ኹን፡ የሰው ስም ።
- ጥላ ወጊ፡ ባንካሴ ("የሰውን ጥላ ወግቶ የሚያሳምም ማርተኛ ጠንቋይ ምትሀ ተኛ") ።
- ጥላ፡ የአካል ምሳሌ ("የሰው የዛፍ የገደል የማንኛውም ፍጥረት የቁመና ሥዕል ባይን የሚታይ በእጅ የማይጨበጥ ጧት ወደ ምዕራብ ማታ ወደ ምሥራቅ ዞሮ ይታያል በቀትር ግን ይታጣል ጨለማ በኾነ ጊዜም በእሳት በመብራት አንጻር ይገኛል") ።
- ጥላቂ፡ ጭላፊ ("በጥልቂት በጭልፋ የተቀዳ") ።
- ጥላት (ጸለሎ)፡ የከሰል/የሸክላ የ ጣራ ጥቍር ጠለሸት ።
- ጥላት፡ ታቦት ("ጸለየ ጽላት") ።
- ጥላቻ፡ ነቀፋ/ስልቸታ ።
- ጥላው ቀለለ፡ ሰውነቱ ጭር አለ ።
- ጥላው ከበደ፡ ሰውን ተነ ።
- ጥላዬ፡ የሰው ስም ("የኔ ጥላ ማለት ነው") ።
- ጥላይ፡ የተጠለለ/ቀረራ ።
- ጥል (ጽልእ)፡ ቍርሾ/ብርቱ ጠብ ("ዐምባ ጓሮ የዘመድ ጥል የሥጋ ትል ጥል ያለሽ ዳቦ እንዲሉ") ።
- ጥል አበቀለ፡ አወጣ/አመጣ ።
- ጥልል (ጥሉል)፡ የጠለለ/የጠራ ።
- ጥልል አለ፡ ጥርት አለ ("ጠለለ") ።
- ጥልመት (ጽልመት)፡ ጥቍረት/ጨለማ ።
- ጥልም (ጥሉም/ጽሉም)፡ የጠለመ ("የሰጠመ ስጥም") ።
- ጥልም አለ፡ ስጥም አለ ።
- ጥልምያኮስ፡ መልአከ ጽልመት + ከሓዲ ማለት ነው ።
- ጥልቀት፡ መጥለቅ ("የጀንበር ዕርበት") ።
- ጥልቀት፡ ጥልቅነት (ምሳ. ፳፭፡ ፫) ።
- ጥልቂት (ቶች)፡ ታናሽ አንኮላ/ሽክና ("የውሃ መጥለቂያ የጠለቀች ማለት ነው") ።
- ጥልቅ ባይ (ብዬ)፡ አለነገሩ የሚገባ ("ችኩል የርጎ ዝንብ") ።
- ጥልቅ አለ፡ ዘው አለ ("ሳይታሰብ ድንገት ገባ") ።
- ጥልቅ አደረገ፡ ስጥም አደረገ ።
- ጥልቅ ኾነ፡ ዝልቅ ኾነ ።
- ጥልቅ፡ የጠለቀ/ዝልቅ/ሩቅ ("የቀጠነ ቀጪን ረቂቅ ጥልቅ ባሕር ጥልቅ መርፌ ጥልቅ ነገር እንዲሉ") (መዝ. ፻፯፡ ፳፬፡ ፻፴፡ ፳) ።
- ጥልቅ፡ ግብት/ጥንቅር ።
- ጥልቅልቅ አለ፡ ተጥለቀለቀ ("ፈጽሞ ዐረበ ገባ ፀሓዩ") ።
- ጥልቅልቅታ፡ ፍጹም ዕርበት/ሠርክ ምሽት ("ወራውራን") ።
- ጥልቅነት፡ ጥልቅ መኾን ።
- ጥልቆ፡ አነስተኛ መጥረቢያ ስለታም ("ዕንጨት ውስጥ የምትጠልቅ") ።
- ጥልቆች፡ የጠለቁ ውቅያኖሶች (ኢሳ. ፵፬፡ ፳፫) ።
- ጥልዝ አለ፡ ትልዝ አለ ("ደከመ የእሳት") ።
- ጥልጣል (ሎች)፡ በትግሬ ቈላ ያለ የአዳል ነገድ ።
- ጥልፊያ፡ ዝኒ ከማሁ ለጠለፋ ።
- ጥልፍ (ዕሱቅ)፡ የተጠለፈ/የተጌጠ ("ሐረግ አበባ ዛላ ዘለላ የተሣለበት ጥልፍ ግላስ ጥልፍ ቀሚስ ጥልፍ ዝናር እንዲሉ") ።
- ጥልፍ፡ መር በዋልታ ብስ ዐልፎ ዐልፎ የገባ ገመድ ርስ በርሱ የተጠለፈ ።
- ጥልፍ ቀሚስ)፡ በሐር የተጠለፈ የተዘመዘመ ።
- ጥልፍልፍ፡ የተጠላለፈ/ውስብስብ ("ቍልፍልፍ ያያዝ") ።
- ጥልፎች፡ የተጠለፉ ግላሶች/ቀሚሶች ("ዝምዝሞች") ።
- ጥሎ፡ ትቶ ።
- ጥሎ አይጥል፡ ፈጣሪ መሓሪ አምላክ ፍጡሩን ፈጽሞ የማይጥል (ኢዮ. ፩፡ ፲፬, ፲፱፡ ፪፡ ፯፡ ፵፪፡ ፲፲፯) ።
- ጥሎሽ፡ ለልጃገረድ የሰርግ ለት በዕድመኛ በሰርገኛ ፊት የሚጣል ወርቅና ብር ቀሚስና ኩታ ካባ ጌጥ በያይነቱ ።
- ጥሎሽ፡ ያመንዝራ ፍቅር ።
- ጥሎኸ፡ አንተን እሱ ትቶኸ ።
- ጥሎኸ ይለቅ፡ ልብሱ ይለቅ ("አንተ ቁም ዐዲስ ልብስ ለለበሰ ሰው ይነገራል። ጥሎሽ ትቶሽ አውድቆሽ ጥሎሽ መጣል ማንደባለ") ።
- ጥመመኛ (ኞች)፡ ባለጥመም ("ተንኰ ለኛ ሀኬተኛ") ።
- ጥመም፡ ክፉ ጥበብ/ተንኰል/ጥመት ።
- ጥመራ፡ የመጠመር ሥራ ("መጠመር መደረብ መደመር") ።
- ጥመት፡ ልግም/ሀኬት/ቸልታ ።
- ጥሙር (ሮች)፡ ፅሙር/ክዑብ፡ የተጠሞረ ("ድርብ ኹለትዮ ሦስትዮ ማግ ሐር ጥለት") ።
- ጥሙጋ፡ በይፋት ክፍል ያለ አገርና' ነገድ ።
- ጥሙጎች፡ የጥሙጋ ጋሎች ("ነገዶች ' ወገኖች") ።
- ጥማቂ፡ ጭማቂ/ውጤት ("ዘይት አንጥፍጣፊ ፍሳሽ የታጠበ ልብስ ሲጠመዘዝ የሚወጣ ውሃ ከወይን የተዘጋጀ መጠጥ") (ማር. ፲፬፡ ፳፭) ።
- ጥማተኛ፡ ውሃ ጥም የያዘው ("ያቃጠ ለው") ።
- ጥማድ (ፅምድ)፡ ፪ የቀንበር በሬ ።
- ጥማዶች፡ ፬ በሮች ("ካ፬ም በላይ ያሉ ብዙዎች የርሻ ከብቶች") ።
- ጥም፡ ጥማት/መጥማት/መጠማት ("የውሃ መሻት ፍላጎት") (ነሐ. ፱፡ ፲፭፡ ፪ ቆሮ. ፲፩፡ ፳፯) ።
- ጥምለላ፡ ዐጠፋ/ቍልመማ ።
- ጥምልል (ጥብሉል)፡ የተጠመለለ ("ቍልምም") ።
- ጥምልል አለ፡ ዕጥፍ/ቍልምም አለ ።
- ጥምልማይ፡ የጥምልምል ዐይነት ወገን ("አምልማሎ እግር") ።
- ጥምልምል (ሎች)፡ የተጥመለመለ ("ሽባ ዝልፍልፍ ሽምድምድ") ።
- ጥምልምል አለ፡ ተጥመለመለ ።
- ጥምልምል አደረገ፡ ዝልፍልፍ/ሽም ድምድ አደረገ ("አጥመለመለ") ።
- ጥምቀተ ባሕር (ባሕረ ጥምቀት)፡ የጥምቀት ባሕር ።
- ጥምቀተ ክርስትና፡ የክርስትና ጥምቀት ።
- ጥምቀት፡ መጥመቅ/መጠመቅ ።
- ጥምቀት፡ የበዓል ስም ("በጥር ፲፩ኛ ቀን የሚውል ጌታችን ስለኛ ያደረገው ጥም ቀት መታሰቢያ (ተረት) ለጥምቀት ያልኾነ ቀሚስ ይበጣጠስ") ።
- ጥምቅ (ጥሙቅ)፡ የተጠመቀ ("ክርስ ቲያን የኾነ") ።
- ጥምቅ፡ ንጥር ማር "
- ጥምብራ፡ የመክድ ጌጥ፡ ጥን ብራ ።
- ጥምዘዛ፡ የመጠምዘዝ ሥራ ።
- ጥምዝ፡ ዝኒ ከማሁ ("የተጠመዘዘ የከረረ ጥምዝ ወርቅ እንዲሉ") ።
- ጥምዝ፡ የቅኔ አገባብ ስም ።
- ጥምዝዝ አደረገ፡ ጥምም ዘወር መ ረግ ።
- ጥምዝዝ፡ ዝኒ ከማሁ ለጥምዝ ።
- ጥምድ (ፅሙድ)፡ የተጠመደ ("ቀንበር የተጫነው ጥምድ እንደ በሬ ቅንት እንደ ገበሬ እንዲሉ") ።
- ጥምጠማ፡ ሽብለላ/ጥቅለላ/አሰራ ።
- ጥምጥማት፡ የመጠምጠም/የመደመር ኹኔታ ።
- ጥምጥም (ጥዉም)፡ የተጠመጠመ ዐ ጥምዝዝ ።
- ጥምጥም፡ መጠምጠሚያ ።
- ጥምጥም አለ፡ ተጠመጠመ ።
- ጥምጥሞሽ፡ ዝኒ ከማሁ ("ጥምጠማ") ።
- ጥሞና (ጽሙና)፡ ብቻነት ("ብቻ መኾን ጸጥታ ርጋታ ይህን ነገር በጥሞና ቀን እንነጋገረዋለን ጠመነና ጣመነ እንደ በረከና ባረከ ናቸው") ።
- ጥስቅ አደረገ፡ ሆዱን መላ አጠገበ ።
- ጥስቅ፡ የተጠሰቀ ("የጠገበ ሆድ ጥር ንቅ ያለ ገላ") ።
- ጥስጥስ፡ የጠሰጠሰ ("አሮጌ ከብት ሰው") ።
- ጥሶ፡ ሰብሮ/ረግጦ ("ናደለ ብለኸ አናዳይን እይ") ።
- ጥሶሽ፡ መጣስ ("መዠመሪያ የሽሩባ ሥራ") ።
- ጥሶሽ፡ አማስኖ ድንግል ዳግመ በሣልስት ዕለት ።
- ጥረ ገቲ (ጥሬ ገትም)፡ ጥሬ ኀታሚ አብዝቶ ቃሚ ("ወፍራም ጕልበታሙ") ።
- ጥረሾ (ዎች)፡ ጥሬ ርሾ) ("ያልቦካ ያልሖመጠጠ ደረቅ የገብስ ቂጣ ገሃ ደገ ኞች እንደ ቈሎ የሚቈረጥሙት") ።
- ጥረሾ ጣሳ
- ጥረቃ፡ ችንከራ ።
- ጥረት (ጽዕረት)፡ ጭንቀት/ትጋት/ልፋት/ድካም (፪ ቆሮ. ፯፡ ፲፩፡ ፪ ጴጥ. ፩፡ ፭) ።
- ጥረገቲ፡ ጥሬ ገታሚ፡ ጥሬ ።
- ጥሩ (ዎች)፡ የጠራ/የጠዳ/ንጹሕ ("ነጭ ጸዐዳ ወለላ ጥሩ እንደ ብርሌ ቀይ እንደ በርበሬ (ተረት) ነገር ከሥሩ ውሃ ከጥሩ") ።
- ጥሩ፡ ማለፊያ/መልካም ("ጥሩ ቤት ጥሩ ልብስ ጥሩ ነገር ጥሩ ሰው እንዲሉ ጥሩ የብር እኸል ስንዴና ገብስ ጤፍ ጥሩ ታደፍ እንዲሉ") ።
- ጥሩ ቀን፡ ዝናምና ጉም ደመና ዐ ፈና የሌለበት ቀን ("ብራ") ።
- ጥሩ ታደፍ፡ የብር እኸል ካበባና ካገዳ እኸል ጋራ ።
- ጥሩ ኾነ፡ ጠራ ("ኮለል አለ ጥሩ ነኽ ነሽ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም") ።
- ጥሩ ወርቅ፡ በውስጡ ተንኰልና ቅልቅል ግብዝ ቂራጥ መዳብ የሌለበት ወርቅ ።
- ጥሩ ውሃ፡ አንዳች ነገር ያልተደባ ለቀበት ("ኵል የሚመስል ውሃ") ።
- ጥሩ ዝናብ፡ በረዶና የሰማይ ቍጣ ያላስከተለ ።
- ጥሩ ገንዘብ፡ በሥራ በድካም የተገኘ ("አፈፋ ጐደፋ የሌለበት ገንዘብ") ።
- ጥሩምባ፡ ከንሓስ የተበጀ የሰራዊት መጥሪያ/መሰብሰቢያ ("በትንፋሽ የሚጮኸ በጣሊያንኛ ትሮምባ ይባላል") ።
- ጥሩር (ዕሩር/ድርዕ)፡ የብረት ጥብቆ/የጦር ልብስ/ልብድ (ነሐ. ፬፡ ፲፮፡ ኤር. ፵፮፡ ፬) ።
- ጥሩር፡ በተጕለት ውስጥ ያለ አገር ("ጥሩር አንዳርጌ እንዲሉ ይህ አገር በቀድሞ ዘመን ጥሩር የተሠራበት ወይም የ ጥሩር ሹም የነበረበት ይመስላል") ።
- ጥሩነት፡ ጥሩ መኾን ።
- ጥሪ (ጥራእ/ጽራሕ/ጽዋዔ/ጽውዓ)፡ በድምፅ/በደብዳቤ መጥራት ("የጥሪ ቃል የጥሪ ወረቀት እንዲሉ") ።
- ጥሪ (ጽርየት)፡ ጥራት/መጥራት ("የ ደም ጥሪ እንዲሉ") ።
- ጥሪ፡ ጥራት ("ጠራ (ጸረየ) መጥራት መጮኸ ና ማለት") ።
- ጥሪት፡ ቁም ከብት ("ማጀት የጐረሠው በራፍ የመለሰው ማንኛውም ገንዘብ ሀብት") (ግብ. ሐዋ. ፪፡ ፵፭) ።
- ጥራ/ፋራ)፡ አፋራ፡ ማካፋት ዠመረ (ብን ብን አደረገ፡ ዐፈር ዐፈር አሸተተ ") ።
- ጥራር (ተረረ)፡ አገልግል መሶብ ቅርጫት ቀፎ ጥላ ካረግ ከቀርክሓ ሥንጣሪ የተበጀ ("(ጐዣም) ግእዝ ሙዳየ ዔረግ ከሚ ለው ጋራ ይሰማማል") ።
- ጥራር (ፅራር)፡ የንጉሥ ጥሩር ("ጃን ጥራር እንዲሉ ጃንን ተመልከት ጥራር ጥሩር ሲባል ጥሩር ደግሞ ጥሩር ለባሽ ባለጥሩር ማለት ይኾናል ፅሩርን እይ") ።
- ጥራቢ (ጽራብ)፡ የንጨት/የደንጊያ ስብርባሪ/ፍርፋሪ/ልላጭ/ልባጭ/ድቃቂ/ክልካይ ።
- ጥራት (ጽርየት)፡ ጥሩነት/ጥዳት ("ጥራትና ንጋት እንዲሉ") ።
- ጥራን ቀንድ፡ በድባብና በጃን ጥላ በካባና በልባልማ ላይ የሚጠለፍ ወርቅ ("ባለሿሿቴ") ።
- ጥራን፡ ትንሽ ነጋሪት፡ ጠራ ።
- ጥራን፡ የገንዘብ ሣጥን ።
- ጥራን፡ ጠረቃ
- ጥራዝ (ዞች)፡ የመጣፍ ስፌት ቶ ታን ።
- ጥራዝ፡ ባንድነት የታሰረ ፭ ቅጽ ("ወይም ፬ና ፰ ቅጠል ብራና ወረቀት ሲታ ጠፍ ፲ ፰ ፲፮ ይኾናል") ።
- ጥራዝ ነጠቅ፡ ያልተማረ ሰው ሲሉ ("ሰምቶ የሚያወራ") ።
- ጥራዝኛጠረዘ (ትግ)፡ ካገር አሶጣ ።
- ጥራጊ፡ የተጠረገ የቤት ውስጥ ጕድፍ ቍሻሻ ገለባ የሣር ድቃቂ ዐፈር መሬት ምናምን ኹሉ (ኤር. ፵፱፡ ፪) ።
- ጥራግ፡ ጽራግ፡ ጸረገ ።
- ጥራጎ፡ ከሥሩ የተጠረገ/የታጨደ ቅጠላቅጠል ("መንጠር") ።
- ጥራጥሬ፡ የጥሬ ጥሬ ("ያበባ እኸል") ።
- ጥሬ (ጠረየ/ጥራይ)፡ ያልደቀቀና ያልበሰለ ማንኛውም ነገር ("ሲበዛ ጥሬዎች ይላል ጥሪትን እይ") ።
- ጥሬ ሰዋስው፡ የመጽሐፍ ስም ("የግእዝ ጥሬ ዘርና ነባር ያለበት መጽሐፍ ጥሬ ሰዋስው ቅጽል የማይኾን ስም") ።
- ጥሬ ሰው፡ ያልተማረ ባላገር ።
- ጥሬ ሥጋ፡ ያልተጠበሰ/ያልተቀቀለ ሙዳ (ዘፀ. ፲፪፡ ፱) ።
- ጥሬ ሥጋውን በሉት፡ ዐሙት ነቀፉት ("ሰዎች አንዱን ሰው") ።
- ጥሬ ብር፡ የብር ለውጥ የሚኾን ሌላ ገንዘብ ወይም ዕቃ ያይዶለ ብር ብቻ ("ጥሬ ጐመን ያልተቀቀለ") ።
- ጥሬ ዕርሻ፡ ዕዳሪ ።
- ጥሬ እኸል፡ ያልተፈጨና ያልተቦካ ያልተጋገረ እኸል ።
- ጥሬ፡ ከውጭ አገር ቋንቋ ሳይተረጐም በግእዝ መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈ ቃል ።
- ጥሬ ካብ፡ ቃና ኖራ ያልገባበት ("በደንጊያ ብቻ የተበጀ ካብ") ።
- ጥሬ ዘር፡ ካባት ዘር የወጣ ስም ነባር ያይዶለ ።
- ጥሬ፡ የቈሎ ስም ("ቈሎ ተማሪው ጥሬ በልቶ ውሃ ጠጥቶ ይማራል።") ።
- ጥሬ ገንዘብ፡ ብርና አላድ ሩብ ተሙን መሐለቅ ቤሳ ለወረቀት ገንዘብ ያልተመነዘረና ለዕቃ ያልተለወጠ ።
- ጥሬ ጤፍ፡ ያልተፈጨ/ያልተሸመ ሸመ ።
- ጥሬ፡ ጥሪ ("ላራስ የሚሰጥ ምግብ ኅብስት ዳቦ ሙክት ከብት ገንዘብ ሌላም በያይነቱ ስጦታ ኹሉ ያራስ ጥሪ እንዲሉ ጥሬ አስቀድሞ እየተነገረ ለስም በቂና ቅጽል ይኾናል") ።
- ጥሬ ጥጥ፡ ያልተፈለቀቀ ።
- ጥሬ ፈጅ፡ ጨረባ በቋል ።
- ጥሬነት፡ ጥሬ መኾን ("አለመብሰል ጥሬና ብስል ተቈልቶ ተቀቅሎ ተጠብሶ የበሰለና ያልበሰለ ባንድነት") ።
- ጥሬና ብስል፡ የልጅ ነገር የሚረ ባና የማይረባ ።
- ጥር (ሮች)፡ የተጠራ ("ስመ ጥር እንዲሉ") ።
- ጥር ፲ ፭ኛ ወር ከመስከረም፡ ጠረረን አስተውል ።
- ጥር የወር ስም፡ ጣራ ።
- ጥር፡ ጠረገ
- ጥርሰ ሸራፋ፡ ጥርሰ ሰባራ ።
- ጥርሰ ወላቃ፡ ጥርሱ የወለቀ/የተነቀለ/የተመነገለ ።
- ጥርሰ ዘርዛራ፡ ጥርሱ የተራራቀ ።
- ጥርሰ ገጣጣ፡ ጥርሱ ያፈነረ/ያፈነገጠ ("ጣይ ሞቴ") ።
- ጥርሰ ፍንጭት፡ የፊት ጥርሱ መካ ከል ክፍት የኾነ ።
- ጥርሳም፡ ጥርሰ ረዥም/ገጣጣ ሰው ("ጣረ ሞት") ።
- ጥርስ (ዕሩስ)፡ የጠረሰ ("ችርችምጥርስ አለ ጠረሰ") ።
- ጥርስ፡ ባውሬና በንስሳ በሰው አፍ ውስጥ ያለ ዐፅማዊ ወፍጮ ("ምግብን ኹሉ የሚፈጭ የሚያደቅ የሚሰልቅ የሚያልም የፊት ጥርስ ክራንቻ መንጋጋ ነቀሰን እይ (ውሃ ጥርስ) ችክ የማይዝ (የባብ ጥርስ) ዝምዝማት (የዝኆን ጥርስ) ቀንድ መሳይ በውድ የሚሼጥ (ዕሪያ ጥርስ) ከማነሱ በቀር የዝኆን ጥርስ ይመስላል ዕባጭ ይተኰስበታል (ዕሪያ ጥርስ) ጥርሱ የገጠጠ ሰው") ።
- ጥርስ፡ ትክክለኛ ያልኾነ የልጠየቅ መልስ ("የሙግት የጥይቅ ስሕተት ጥርስ ነው እንዲል መስካሪ") ።
- ጥርስ ነው፡ ስሕተት ነው ("ለጥይቁ ተገቢ መልስ አልተሰጠም") ።
- ጥርስ አወጣ፡ ጥርስ አበቀለ ("(ተረት) እኔ እበላው ሳጣ ልጄ ጥርስ አወጣ ጥርስ አወጣ ሞረደ ዘረዘረ አበጀ ጥርሰ በረዶ ጥርሱ ጥርሷ በረዶ የሚመስል ወንድ ሴት") ።
- ጥርስ፡ የሌማት/ያገልግል/የሰገጥ መ ግጠሚያ "
- ጥርስ፡ የመኪና ኹሉ መግጠሚያና መዘወሪያ ።
- ጥርስ፡ የመጋዝ/የማጭድ ዝርዝር ("ዕንጨት መቍረ ሣር ማጨጃ") ።
- ጥርስ የማያስከድን፡ አጫዋች/አሥቂኝ ካታ ።
- ጥርስ፡ የሸማኔ ממቻ ማግን የሚ ያቀራርብ/የሚሰገስግ ("ከጐሽ መቃ ተፍቆ የተበጀ") ።
- ጥርስ፡ የብጕንጅ/የዕባጭ ሰንኰፍጥርስ ።
- ጥርስ ገባ፡ ተጠላ ("መወደድን ዐጣ") ።
- ጥርስ)፡ ቍርስ መቍረስ/መቈረስ ።
- ጥርሶ፡ ረዥምና ወፍራም/ጠፍጣፋ/ነጭ ("አደንጓሬ ደንጐሎ") ።
- ጥርሶች፡ ፪ና ከ፪ በላይ ያሉ መንጋጋዎች/ክራንቾች (ምሳ. ፴፡ ፲፬) ።
- ጥርር (ፅርር)፡ የተጠረረ ጥሩርን የለበሰ ሐርበኛ ።
- ጥርቃሚ፡ የተጠራቀመ ("ከያለበት የመጣ ስብስብ") ።
- ጥርቃሞ፡ ዝኒ ዓዲ ከማሁ ።
- ጥርቅ፡ የተጠረቀ/የተሰመረ/ብረት ለበስ ("ሣጥን ስማርድ የጦር መሣሪያ መኪና ጡርቅ ቂ የተወጋ ፈሪ ሴትማ ጡርቂያም የፈሪ ወገን ፈሪ ያለ በት የፈሪ ፈሪ ጨረቀን እይ") ።
- ጥርቅም አለ፡ ተጠረቀመ ("ዝም አለ") ።
- ጥርቅም አደረገ፡ ጠረቀመ ገረኘ ' ኣጠበቀ ("መናገር ከለከለ") ።
- ጥርቅም፡ ዝኒ ከማሁ ("ትርክም") ።
- ጥርቅም፡ የተጠረቀመ/የገባ/የታሰረ ("እስር ዝግ") ።
- ጥርቅምቃሚ፡ የተጠረቃቀመ ("ውጥን ቅጥ") ።
- ጥርቅምቅም፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥርብ (ጽሩብ)፡ የተጠረበ/የታነጠ ("ጥርብ ድንጋይ ጥርብ ዋሻ ጥርብ ዕንጨት እንዲሉ") ።
- ጥርብርብ፡ የተጥረበረበ ("ሽቍጥቍጥ ርግብግብ") ።
- ጥርት (ጸርይ)፡ ጥሩ መኾን ።
- ጥርት አለ፡ ፈጽሞ ጥሩ ኾነ ።
- ጥርንቅ (ድርንቅ)፡ የተጠረነቀ/የታሰረ ("ጥብቅ የኾነ ወፍራም ገላ") ።
- ጥርንቅ አለ፡ ጥብቅ አለ አካሉ።
- ጥርንቡሌ (ትሪፖሊ)፡ ከትግሬ ካ ማራ ወደ ትሪፖሊ የዘመተ የጣሊያን ወታደር አሽከር ("ባንዳ ትሪ ፫ ፖሊ ከተማ ማለት ነው ይላሉ") ።
- ጥርኝ (ኞች)፡ ጽርኒ፡ የዝባድ አውሬ ("ድመት መሳይ ጠረናሙ") ።
- ጥርኝ፡ ዝባድ ሽቱ፡ ከጥርኝ ገላ የሚ ጠረግ ላብ ኵክ መሳይ ("በውድ የሚሼጥ መድኀኒትነት ያለው") ።
- ጥርኝ፡ የቀኝ ወይም የግራ ውስጥ እጅ ("የዕፍኝ እኩሌታ ይህ ጠጅ በጥርኝ ይኼዳል") ።
- ጥርኝ፡ የፈረስ መልክ ጥርኟን የሚመስል ፈረስ (ዘካ. ፩፡ ፰) ።
- ጥርኝ፡ ያንድ እጅ ዝግኝ ጭብጥ ("ጥርኝ ዐፈር እንዲሉ") ።
- ጥርክርክ/ጥርኸርኸ፡ የተጥረከረከ ("ዝርክርክ ጕድፍድፍ ኵልፍልፍ") ።
- ጥርውዝ፡ የተንጠራወዘ ።
- ጥርውዝ ጥርውዝ አለ፡ ክልውስ ክልውስ አለ ።
- ጥርየወር ስም፡ ጣራ ።
- ጥርጊያ፡ ሌሊት ከጥቃቅን ኮከቦች ጋራ እንዳውራ መንገድ በሰማይ ተዘርግቶ የሚታይ ጭጋግ ("ሰዎች ኹሉ የጦርነት ምልክት ነው ይሉታል") ።
- ጥርጊያ፡ ተጠርጎና ተደልድሎ ለጥ ቀጥ ብሎ ሰፊ ኹኖ የተሠራ የመንገድ ስፋትና ወለል (ኢሳ. ፲፩፡ ፲፮) ።
- ጥርጊያ ጐዳና፡ የጐዳና ጥርጊያ ("ወይም የጥርጊያ ጐዳና") ።
- ጥርጊያ፡ ጠረጋ/መጥረግ ።
- ጥርግ (ትግ. ጽሩግ)፡ የተጠረገ የተመ ነጠረ ("ምንጥር") ።
- ጥርግ አለ፡ እብስ አለ ("ፈጽሞ ኼደ ነጐደ") ።
- ጥርግ አደረገ፡ ሙጥጥ አደረገ ።
- ጥርጥስ አለ፡ ጭርጭስ አለ ("ጠረጠሰ") ።
- ጥርጥስ፡ የጠረጠሰ ።
- ጥሻ (ሾች)፡ ትግ. ጣሻ፡ ባንድነት ያደገ የረዘመ ብዙ ሣርና ቅጠል ዳዋ ደን ("ሊጥሱት የሚቻ") ።
- ጥሽ፡ የንጨት፡ ስም፡ በወይናደጋ፡ አረኸ፡ የሚበቅል፡ ታናሽ፡ ዕንወት፡ ርጥቡን፡ የሚነድ ። ዘሩ፡ ማጠጠ፡ ነው፡ የመጥረግ፡ ምስጢር፣ ኣለበት። ሲበዛ፡ ጥሾች፡ ይላል።
- ጥቀርሻ፡ ዝኒ ከማሁ ለጠቀራ ("ጪስ ያጠቈረው ሰንበሌጥ የሸረሪት ድር በጣራ ውስጥ ያለ ነገር ኹሉ") ።
- ጥቀርሻ ጠገብ፡ ጥቀርሻ የጠገበ ጦር ("ጥቀርሻም") ።
- ጥቁ (ጥቁዕ)፡ የተጠቃ/የተበደለ ("ግፍ የጠገበ የተቀበለ") ።
- ጥቍማት፡ የጥፍር ውግታት ("የዠርባ ዕከክ ጭረት") ።
- ጥቍም አደረገ፡ በጥቂቱ ወጋ ("ጠቈመ") ።
- ጥቍም፡ የተጠቈመ ("የጥፍር የእሾኸ ታናሽ ውግ") ።
- ጥቍረት፡ ጥቍርነት/ማዲያት መልበስ (ማሕ. ፩፡ ፲፩፡ ሰቈ. ፬ - ፰) ።
- ጥቍሪት፡ ታሪኳ በተረታዊ ቃል የሚነገር ንግሥት ("ሽማግሌን ኹሉ አጥፍታ ቤቴን እሰማይ ላይ ሥሩ ያላት በባሶ የሠ ራችው ከተማ ጥቍሪት ባዶ ይባላል በቡል ጋም ድልድይ ኣላት ይላሉ") ።
- ጥቍራት፡ ንቅሳት/ውቅራት ("የገላ ላይ ማኅተም") ።
- ጥቍሬ፡ የጥቍር ወገን ("ወይም ዐይነት ጥቍሬ ዝንጀሮ እንዲሉ") ።
- ጥቍሬታ፡ ማር በጐታ ("እንጀራው ማር ማር የሚል ጥቍር ያገዳ እኽል በጤፍ መሣ ይለወጣል") ።
- ጥቍር (ሮች)፡ ጽልሙት፡ ዝኒከ ማሁ ("ከነጭ ከቀይ ከብጫ የተለየ ሥፍጥረት ጥቍር አስቀድሞ እየተነገረ ለማን ኛውም ስም ቅጽል ይኾናል ቅጽልነቱም የዐይነት ነው (ማስረጃ) ጥቍር በግ ጥቍር በሬ ጥቍር ብረት ጥቍር ገብስ ጥቍር ጥለት ጥቍር ጤፍ ጥቍር ቀለም") ።
- ጥቍር መጣፈጥ፡ ጥቍር አዝሙድ ።
- ጥቍር ሰማይ፡ ኒል መሳይ ።
- ጥቍር ሰው፡ ሻንቅላ የአፍሪቃ ነገድ ።
- ጥቍር ስንዴ፡ አቶሳል ።
- ጥቍር ራስ፡ መነኵሴ ያይዶለ ረድ ዓለማዊ ።
- ጥቍር ቍራ፡ ፍጹም ጥቍር ።
- ጥቍር አለ፡ ግምን ክስል አለ ።
- ጥቍር ዐረብ)፡ የሻንቅላ እስላም ።
- ጥቍር አባይ (ኤፌሶን)፡ ውሃው ሰ ማይ የሚመስል ዠማ ።
- ጥቍር አዝሙድ፡ አበ ሱድ ።
- ጥቍር እንግዳ፡ ጕንዳን ("በጨለማ የመጣ ዋና የዘመድ እንግዳ መጥቶ የማያውቅ ንጋይ") ።
- ጥቍር ዕንጨት፡ ዞጲ ።
- ጥቍር ውሻ፡ ከጥቍረት በቀር ንጣት የሌለው ።
- ጥቍር ውሻ ውለድ አለ፡ ፈጽሞ ረገመ ("ካደ") ።
- ጥቍር ደንጊያ፡ አለት ("ባሪያ ድ") ።
- ጥቍር ፈረስ፡ ዱሪ (ራእ. ፮፡ ፭) "
- ጥቍር ፍየል፡ ከሰልማ ።
- ጥቍርቍር አለ፡ የጥቍር ጥቍር ኾነ ("ጕስቍልቍል አለ") ።
- ጥቍርነት፡ ጥቍር መኾን ።
- ጥቂት (ጠቀ)፡ ትንሽ ።
- ጥቂቶች፡ ትንሾች (መክ. ፲፪ - ፫) ።
- ጥቃሽ፡ የነገር ስላች ።
- ጥቃቅን፡ ታናናሽ/ቅንጣት ።
- ጥቃቅኖች፡ ታናናሾች ("ልጆች ብላቴ ኖች ወይም ሌሎች ነገሮች") ።
- ጥቃተኛ፡ ጥቃት የበዛበት ("ተጠቂ") ።
- ጥቃት (ጥቅዐት)፡ ግፍ/በደል/ውር ደት ።
- ጥቈማ፡ የመጠቈም ሥራ ("ግብር") ።
- ጥቅ፡ መንደቅ፡ ግንብ/ናስ) ።
- ጥቅለላ፡ ሽብለላ/ጥምጠማ/ሽፈና ።
- ጥቅል (ጥቅሉል)፡ የተጠቀለለ ("ሽብ ልል ጥምጥም የወርቅ እንክብል የሸማ ጥቅል እንዲሉ") ።
- ጥቅል ነፋስ፡ ኵርፊት/ዐውሎ ነፋስ ።
- ጥቅል፡ አንድነት ያለ ወፍራም ሊጥ ።
- ጥቅልል አለ፡ ሽብልል አለ ("ተጠ ቀለለ") ።
- ጥቅልል አደረገ፡ ሽብልል አደረገ ።
- ጥቅማት፡ ስፌት ።
- ጥቅም (ባቍዕ)፡ ረብ/ርባና/ትርፍ/ፋይዳ/ፈሎ ("የሚጠቅም የሚረባ ነገር ኹሉ አገልግሎት") (መዝ. ፲፱፡ ፲፩፡ ምሳ. ፴፡ ፪) ።
- ጥቅም (ጥቁብ)፡ የተጠቀመ/የተረባ/የተሰፋ ስፍ ።
- ጥቅምቅም፡ የተጠቃቀመ/የተጣጣፈ ጨርቅ ድሪቶ ።
- ጥቅምት፡ የወር ስም ("፪ኛ ወር ከመ ሬት ብዙ ጥቅም የሚገኝበት እኸልና ተክል ኹሉ ፍሬ የሚሰጥበት በግእዝ ግን የተገነባች ማለት ነው ፍጥረተ ዓለምን ያሳያል") ።
- ጥቅስ (ሶች)፡ የቃል/የነገር ምስክር ("ምሳሌ ማስረጃ ትች ሐተታ የጐመን ጥቅስ እንዲሉ") ።
- ጥቅሻ (ቅጽበት)፡ ምልክት ያይን ጥሪ ("ቅጥጥብ") (ምሳ. ፯፡ ፳፭) ።
- ጥቅንጥቅ (ጠቀጠቀ)፡ ዝብዝብ ውስጥ ብስብ ።
- ጥቅጠቃ፡ የመጠቅጠቅ ሥራ ("ሽፈና ደፈና ረገጣ ርምረማ") ።
- ጥቅጥቅ (ቆች)፡ የተጠቀጠቀ ("በ መርፌ የተበሳሳ ተቈርጦ ተጐርዶ የሚሰጥ የደረሰኝ ወረቀት") ።
- ጥቅጥቅ፡ ተቀራርቦ የተሠራ ብዙ መን
- ጥቅጥቅ አለ፡ ችፍግ' አለ ።
- ጥቅጥቆሽ/ጥቅጥቃት፡ የመርፌ ውግታት/ንቅሳት/ነዳላ ("የድፎ ያንኮላ ጌጥ") ።
- ጥቋቍር (ሮች)፡ ውስጠ ብዙ ጥቍር ።
- ጥበሌ) ቀበሌ፡ የገደል ማሚቶ ድምፅን የም ትቀበል ።
- ጥበቃ፡ እረኝነት/ክልከላ/ዘብ ("የመጠበቅ ሥራ") (፪ ሳሙ. ፯፡ ፰) ።
- ጥበበ ሰሎሞን፡ ጥበብ መንፈሳዊን ጥበብ ሥጋዊን የተመላ የሰሎሞን መጽሐፍ ።
- ጥበበኛ (ኞች/ጥበባዊ)፡ ጥበብ ዐዋቂ/ብልኀተኛ ("ሸረኛ ተንኰለኛ ጥመመኛ") ።
- ጥበብ (ቦች)፡ ብልኀት/ዘዴ/ዕውቀት/ፍልስፍና ("ሰነፎች ግን ጥበብንና ትምርትን ይንቃሉ") (ምሳ. ፩፡ ፯) ።
- ጥበብ መንፈሳዊ፡ ያምላክ/የመልአክ ረቂቅ ጥበብ ።
- ጥበብ ሥጋዊ፡ ያዳም/የሰው ጕልሕ ጥበብ ።
- ጥበብ ቀሚስ)፡ ጥበብ ያለበት የጥበብ ቀሚስ ("(ዘፀ. ፵፥ ፲፬)") ።
- ጥበብ፡ በኩታ-በቀሚስ ዳር ያለ በብዙ ዐነይት ጥለት የተሠራ ጌጥ ።
- ጥበብ፡ ተንኰል/ክፉ ብልኀት/ጥመም ("ጥበብን ጥመም የሚያሠኘው እንደ እቶም ያለ ሥራ ነው") ።
- ጥበት (ጽበት)፡ ዝኒ ከማሁ ("ጭንቀት ጠባብነት") ።
- ጥበት (ጽበት)፡ ዝኒ ከማሁ ("ጭንቀት ጠባብነት").
- ጥባት (ጽብሐት)፡ ንጋት/ወገግታ/ ፈገግታ ("የመስከረም መባት") ።
- ጥብ፡ ዝኒ ከማሁ ("የጨነቀ ጭንቅ") ።
- ጥብ፡ ዝኒ ከማሁ ("የጨነቀ ጭንቅ"). (ተመልከት፡ ዐጸባን ተመልከት).
- ጥብልቃና፡ ጥንታዊ በገና ("ጥብሉለ ቃና ባለብዙ ቅኝት") ።
- ጥብሳት (ጥብሰት)፡ ትኵሳት ("የመጥበስ ሥራ") (ዘሌ. ፲፫፡ ፳፭) ።
- ጥብስ (ሶች/ጥቡስ)፡ የተጠበሰ ("ጥብስ እንጀራ ጥብስ እሸት ጥብስ ሥጋ እንዲሉ") ።
- ጥብስ ወጥ፡ ቍሌት ።
- ጥብር፡ የተጠበረ ("ጌጠኛ") ።
- ጥብቅ (ጥቡቅ)፡ የጠበቀ/የማይፈታ ("ብርቱ ግትር ፍንክች የማይል ከራራ ጠንካራ ማሰሪያ ዐደራ ጥብቅ ሰማይ ሩቅ እን ዲሉ") ።
- ጥብቅ አለ፡ ልጥፍ/ልጥቅ አለ ።
- ጥብቅ፡ እስራት/አገዛዝ ።
- ጥብቅ ወዳጅ፡ ወረት የለሽ/የታመነ ።
- ጥብቅ፡ የማይሰጥ/የማይቸር ።
- ጥብቅ፡ የተጠበቀ/ክልክል እግድ ዝ ሪት መስኖ/ቁባት ።
- ጥብቅ ገባ፡ ነገር አዛነፈ ("ከውሳኔ ዐለፈ ኹለት መልስ ሰጠ") ።
- ጥብቅነት፡ ጥብቅ መኾን ("አለመበገር አለመፈታት አለመስጠት") ።
- ጥብቅና፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥብቆ (ዎች)፡ በጥብቅ ተሠርቶ የተሰፋ ግብግብ ("ወይም ዐጪር የ ልጅ ቀሚስ ኪታ") (ዘፀ. ፳፭፡ ፯) ።
- ጥብብቅ (ጠፋልሕ)፡ በመጣብቅ የተያ ያዘ ገንዘብ ።
- ጥብነት፡ ጥብ መኾን ።
- ጥብነት፡ ጥብ መኾን.
- ጥብጠባ፡ የስቅለት ለት ገረፋ/ሽንቈጣ/ግሥገሣ ሩ ንበር ።
- ጥብጣብ (ቦች)፡ የሱሪ መታጠቂያ/መሽቀቅ ("የካባ ጌጥ በጥብጣብ አምሳል የተሠራ ባለወርቅ ጥብጣብ እንዲሉ") ።
- ጥብጥባት (ጥብጣቤ)፡ ግርፋት ሰ ንበር ።
- ጥብጥብ፡ የተጠበጠበ/የተበለተ ("ግርፍ ብልት") ።
- ጥብጥቦ፡ ሽታ ያለው ቅጠል ጠበ ።
- ጥቦቶች፡ ብዙዎች ("ካንድ በላይ ያሉ") (ዘፍ. ፴፡ ፵፡ ዮሐ. ፳፩፡ ፲፭) ።
- ጥቦቶች፡ ብዙዎች ("ካንድ በላይ ያሉ") (ዘፍ. 30፡ 40፡ ዮሐ. 21፡ 15).
- ጥታኝ) አፋታኝ (አስተፋትሐኒ)፡ አለያየኝ ።
- ጥት) ዕትብ (ዕቱብ)፡ የታተበ (ዕትብቱ የተቈረጠ ") ።
- ጥኑ (ዎች)፡ ጽኑዕ፡ የጠና/ብርቱ/ ጠንካራ ("የማይበገር የማይፈታ ልበ ጥኑ ነፍሰ ጥኑ እንዲሉ") ።
- ጥና (ጽናዕ)፡ በርታ/ጠንክር/ቻል።
- ጥና (ጽንሓሕ)፡ የቤተ መ ቅደስ ዕጣን ማጠኛ ("ጽና ሲበዛ ጥናዎች ጥኖች ይላል") ።
- ጥና፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥና፡ ጠንክር፡ ጠና ።
- ጥናት (ጽንሓት)፡ መማለድ/መቀ መጥ/መቈየት ።
- ጥናት (ጽንዕ/ጽንዐት)፡ ጥንካሬ/ ብርታት ("መጥናት") ።
- ጥናት፡ ማጥናት ("የቃል ትምርት") ።
- ጥንሰሳ፡ የመጠንሰስ ሥራ ("ብጥበጣ") ።
- ጥንስስ፡ የተጠነሰሰ ("የጠላ ርሾ ፅንስ ጥንስስ መሰለ ደመነ ጠቈረ የሰማይ የባሕር የፊት") ።
- ጥንቀቃ፡ የመጠንቀቅ ሥራ ።
- ጥንቍል፡ የተጠነቈለ/የተወጋ ("ድንቍል ጥንቍሌ የጥንቍል በጕራጌ ቋንቋ ግን ጭንቍላ ማለት ነው") ።
- ጥንቁቅ፡ ዝኒ ከማሁ ለጠንቃቃ ("ኵስ ትር ስሕተት ግድፈት ጸያፍ የሌለበት") ።
- ጥንቁቅነት (ጥንቅቅና)፡ ኵስትርነት ።
- ጥንቃቄ፡ ዝኒ ከማሁ ("ዝግጅት ትጋት ንቃት ጥንቃቄ ግእዝኛ ነው") ።
- ጥንቈላ፡ ርት/አስማት/ደገማ/ኮከብ ቈጠራ ።
- ጥንቅል አለ፡ ተጠነቀለ ።
- ጥንቅል አደረገ፡ ቍንጥር አደረገ ("ጠ ነቀለ") ።
- ጥንቅል፡ የተጠነቀለ ("ቍንጣሪ ቍንጥር ጥርኝ ጭብጥ (ተረት) ኹለት ቍና ሰጥቼ አንድ ጥንቅል") ።
- ጥንቅል ጥንቅል አለ፡ እንክል እንክል አለ ("ዥብኛ ረገጠ በእግሩ ጣት ጫፍ") ።
- ጥንቅር አለ፡ ጥልቅ አለ ("ፀረበ (ጠነቀረ) ጠረቀመ)") ።
- ጥንቅር፡ የገባ/የጠለቀ ።
- ጥንቅሽ (ሾች)፡ ትግ. ጠቀሰ - ተቀ ለሰ፡ ዐንገተ ቀላሳ አገዳ ("ማር ማር የሚል ጣፋጭ ዘንጋዳ ማሽላ መጥቀሻ መሳይ") ።
- ጥንቅቅ አለ፡ ዙስትር አለ ("ተጠነ ቀቀ") ።
- ጥንቅቅ፡ ዝኒ ዓዲ ከማሁ ለጥንቁቅ ።
- ጥንበ በላ (ሎች)፡ ጥንብ የሚበላ ።
- ጥንበኒ፡ ግመኒ ("ግም አስተኔ") ።
- ጥንቡን ጣለ፡ ረከሰ ("የሚገዛው ዐጣ ወደቀ") ።
- ጥንቡዝ (ጐንደር)፡ ዕድር ።
- ጥንባም፡ ጥንብ የወደቀበት/ያለበት ።
- ጥንባታም፡ ግማታም ("ባለጥንብ") ።
- ጥንባት፡ ግማት ("ጥንብ ጥንብ መሽ ተት") ።
- ጥንብ (ቦች)፡ የጠነባ ("ግም ውዳቂ") (ኤር. ፲፮፡ ፰፡ ሉቃ. ፲፯፡ ፴፯) ።
- ጥንብ፡ መጥፎ ሰው ።
- ጥንብ፡ የኮርቻ ዕንጨት ("ጥንብ መባሉ ልብድና ጠፍር ከሌለበት የትም መው ደቁን ፥ ያሳያል") ።
- ጥንብራ (ጠበረ)፡ በሰይፍ እጀታ ላይ የሚደረግ ክብ የወርቅና የብር ጌጥ ።
- ጥንብርብር፡ ድንብርብር ።
- ጥንብዝ አለ፡ ፈጽሞ ሰከረ ።
- ጥንብዝ፡ የጠነበዘ ።
- ጥንብዝብዝ፡ ጥንግርግር ።
- ጥንብፍ፡ የተጠነበፈ ("በሰይፍ ተመቶ በጦር ተወግቶ ፥ የተጋደመ ጥንብኛ የወደቀ") ።
- ጥንቦ፡ የመንቀፍና የማዋረድ ቃል።
- ጥንት አስቀድሞ፡ ወጠነ ።
- ጥንቸል (ሎች)፡ ያውሬ ስም ("የሽኮኮ ዐይነት") ።
- ጥንከራ፡ ጥንካሬ/ጥናት/ብርታት ።
- ጥንክር፡ የጠና ጥጥር ("ጠንካራ") ።
- ጥንክርና፡ ጥንክር መኾን (ኢዮ. ፮፡ ፲፪) ።
- ጥንዝዛ፡ (ጦነጦነ) ።
- ጥንዝዛ፡ ሲኼድ ዕዝ ጥዝ የሚል ("በክንፍ በራሪ መናኛ ማር ሠሪ በደረቅ ዕንጨት ውስጥ ዐዳሪ ሦስት ዐይነት መልክ ፍጹም ጥቍር ነጭና ጥቍር አረንጓዴ ፍጥረት ጥቍሩ መርዝ አለው፲ አረንጓዴው ግን ሰላማዊ ነው ልጆች እግሩን በክር እያሰሩ ይጫወቱበታል") ።
- ጥንዡት (ቶች)፡ የንጨት ስም ("በወይናደጋ ቈላ የሚበቅል ነጭ ዕንጨት እሾ ኻማ የጠላ ጋንን ዐራስን ያጥኑበታል ሲሰብሩት ቅልጥም ይላል ዘሩ ጠነዛ ነው") ።
- ጥንድ፡ የዕጽፍ ቍጥር ("፪ በሬ ፪ ድር ቀንጃ ነጠላ ያይዶለ ጥንድ በሬ ጥንድ ተቀንጃ መቶ ጥንድ ድር ፩ ፪ ፫ · · ፲ ጥንድ እንዲሉ") ።
- ጥንድ፡ ጥምድ፡ ጠመደ "
- ጥንግ (ጎች)፡ ፅንጉዕ/ፅፉር፡ የጠፍር ኳስ ("ዕሩር") ።
- ጥንግ ድርብ፡ በጥንግ ዐይነት የተ ሠራ ድርብ ጥበብ ውስብስብ ።
- ጥንግርግር፡ ጥንብርብር ።
- ጥንጣን (ኖች)፡ የትል ስም ("ዕንጨትን ዐመድ የሚያደርግ ትል በግእዝ ጽን ጽንያ ቍንቍኔ ይባላል ጥንጣን በላው እን ዲሉ") ።
- ጥንጣን ኾነ፡ በጣም ደቀቀ ("ላመ ተሰለቀ") ።
- ጥንጣን፡ ጥንጣን ያደቀቀው የንጨት ዶቄት ።
- ጥንጥናት፡ የማጠንጠን ሥራ ("ጥቅልላት ጥምጥማት") ።
- ጥንጥን (ጽንጹን)፡ የጠነጠነ/የነቀዘ ።
- ጥንጥን፡ የተጠነጠነ ("ልቃቂት ድውር") ።
- ጥንፋፊ፡ የንፍሮ/የግንፍል ሥጋ ውሃ አጠናፈፈ ("እንስራን አፍላልን አያያዘ አዘቃዘቀ ውሃን አፋሰሰ አጫረሰ") ።
- ጥንፍ (ጸነፈ/ጽንፍ)፡ ዳር/ዳርቻ/ መጨረሻ ።
- ጥንፍፍ አለ (ተጠነፈፈ)፡ ዐለተ ተወረሰ/ተጠነገደ ።
- ጥንፍፍ አደረገ፡ ሰውን ከብትን በጦር በበሽታ ፈጀ/ጨረሰ/ጠነደ ።
- ጥንፍፍ፡ የተጠነፈፈ ("ውሃ የወጣለት ንፍሮ") ።
- ጥዋ (ጸውዐ/ጽዋዕ)፡ ከወርቅ ከብር ከማዕድን ከሸክላ በዋንጫና በመንቀል ዐይነት የተሠራ ("የቍርባን የማኅበር የደጀ ሰላም ዕቃ ሲበዛ ጥዎች ይላል") ።
- ጥዋ ሕይወት (ጽዋዐ ሕይወት)፡ በቍርባን ጥዋ አምሳል የተበጀ ማኅበረተኛ የሚሳተፍበት ("(ጠበል የሚጠጣበት) ፩ የሕይወት ጥዋ በየወሩ እማኅበር ቤት የሚዞር") ።
- ጥዋ ተርታ፡ በተርታ መጠጥ ማደያ ጥዋ ("ዕድል ፈንታ ጥዋ ተርታ እንዲሉ") ።
- ጥውለጋ፡ መጠውለግ (፩ ነገ. ፰፡ ፴፯) ።
- ጥውልውል፡ የተጥወለወለ/የዞረ የሚ ጥውልውል አደረገ ("አጥወለወለ") ።
- ጥውልግ (ምጽልው)፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥውልግ እለ፡ ልውጥ አለ ።
- ጥውር (ጽዉር)፡ የተጦረ/የታገዘ/ የተረዳ ("የሰው በልቶ ጠጥቶ የሚኖር") ።
- ጥዝ አለ፡ ጠጣ ።
- ጥዝ አለ፡ ጮኸ፡ (ጠዘዘ) ።
- ጥዝ ጥዝ ባይ፡ ንብ ክራር ።
- ጥዝ ጥዝ አደረገ፡ ብዙ ጊዜ አጮኸ ።
- ጥዝ) ዕዝ (ሕንዝዝ)፡ የጥንዝዛ ድምፅ ።
- ጥዝል ሆድ፡ ከረቦ ሆድ ።
- ጥዝል፡ የተጠዘለ/የተመደወተ ("ምድ ውት") ።
- ጥዝር፡ ንፍ፡ ዝጥር ።
- ጥዝታ፡ ጥዝ ማለት ("ጩኸት") ።
- ጥዝጠዛ፡ ነደፋ ("የንብና የተርብ ጦር ጋት") ።
- ጥዝጣዜ፡ ንዝናዜ ።
- ጥዝጥዝ አደረገ፡ መልሶ መላልሶ ጠዘጠዘ ።
- ጥዝጥዝ፡ የተጠዘጠዘ/የተነደፈ ።
- ጥየቃ፡ (ጥያቄ)፡ ምርመራ፡ ሐተታ፡
- ጥየታ፡ ስብሰባ/አሰራ ።
- ጥያራ፡ አይሮፕላን ("ሰው ሠራሽ አሞራ በነፋስ በእሳት በቤንዚን ኀይል በአየር የሚበር የሚከንፍ የሰማይ ባቡር እንደ አውሮ ሮጳ አቈጣጠር ባ፲፱፻፫ ዓ. ም. አይሮፕላንን መዠመሪያ ያወጡ አርቢልና ዊልበር ወንድማማች ኣሜሪካውያን ናቸው ይባላል") ።
- ጥያቄ፡ (ዎች)፡ ጥየቃ፡ መጠየቅ ። ጥ የቃ ' ዐማርኛ፡ ጥያቄ፡ ግእዝ፡ ነው ።
- ጥያቄ፡ በመጠየቅ፡ ጊዜ፡ በቃል፡ መጪ ረሻ፡ የሚጨመር፡ ንኡስ፡ አገባብ፡ ወይ፡ ን ። መጠየቅ፡ ነገርን፡ ታሪክን፡ ማደን፡ መ ማረር፡ መመርመር፡ መሞገት፡ (፩ሳሙ፡ ፱ " ፱ ። ዮሐ፰፡ ፯) ።
- ጥይር፡ የተጠየረ ("ዝግጁ ቈፍጣና ኵሩ") ።
- ጥይቅ ።
- ጥይቅ፡ የተጠየቀ፡ ምርምር ። ጥይቅ፡ ሙግት፡ ክርክር፡ ተጠየቅታ ። ልጠየቅ፡ የተጠያቂ፡ መልስ፡ የሙግት፡
- ጥይት (ስም)፡ የታሰረ እሸት ።
- ጥይት (ቶች/ቅጽል)፡ የተጠየተ ("ጥይት የኾነ ርሳስ ዐረር ከቀለሕ ጋራ የተዋደደ ቱባ ክልስ (ቸሬ) ከሽጕጥና ከጠመ ንዣ ከመትረየስና ከመድፍ ውስጥ የሚተ ኰስ") ።
- ጥይት፡ በጥይት የተመታ/የተገደለ ።
- ጥይፍተኛ፡ (ኞች)፡ የጥይፍ፡ ወገን፡
- ጥይፍታ፡ ነቀፋ፡ ጥላቻ፡ ሥቅቅታ ።
- ጥደት (ጽዕደት)፡ መጣድ ።
- ጥዱ (ጽዕድው)፡ የጠዳ/የጠራ ("ጥሩ ነጭ እድፍ ጕድፍ እንከን የሌለበት") ።
- ጥዱ፡ የሰው ስም፡ ጠዳ ።
- ጥዱ፡ የባላባት ስም ("ከሺዋ ባላባቶች አንዱ ሞረት የጥዱ ልጅ እንዲሉ") ።
- ጥዱ፡ ያ ጥድ ("የርሱ") ።
- ጥዱፍ (ጽዱፍ)፡ የጠደፈ ገደል የ ገባ የተንከባለለ ("ችኵል") ።
- ጥዱፍነት፡ ችኩልነት ።
- ጥዳቂ፡ የቈየ ሥር የሰደደ ሳል ።
- ጥዳት (ጽዕዳዌ)፡ ጥራት ፥ ጥሩነት ን ጽሕና ንጣት ።
- ጥድ (ዶች/ጽሕድ)፡ የዛፍ ስም ("በዓለም ኹሉ የታወቀ ዕንጨት ሽታው የሚጣፍጥ ልዝብ የኾነ ሳን ቃው በውድይሸጣል ለቤት ሕንጻ ይሰማማል") ።
- ጥድቅ፡ ጽድቅ ።
- ጥድፈት (ጽድፈት)፡ ዝኒ ከማሁ ("ገደል መግባት") ።
- ጥድፊያ፡ ችኰላ/መቸኰል/ፍጥነት ።
- ጥዶ ዘለል፡ እብድ ወፈፌ ።
- ጥዶ፡ ጭኖ አስቀምጦ ።
- ጥዶሽ፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥጃ (ጆች)፡ የላም ልጅ ("ከእንቦሳ የሚበልጥ የተወለደ ለት እናቱ ልሳ ያጠዳችው") (፩ ሳሙ. ፲፱፡ ፴፪) ።
- ጥጃ ሣር (የጥጃ ሣር)፡ ያገር ስም ("የወግዳ ማፍ") ።
- ጥጃ፡ እንቦሳ፡ ጠዳ ።
- ጥገታም፡ ጥገት ያለችው ("ባለጥገት") ።
- ጥገት (ቶች)፡ የምታጠባ/የምትታለብ ጥጃ ያላት ላም ።
- ጥገና፡ አሰራ/ጥቅለላ/ቆከማ/ፍወሳ/ዕገዛ/ድገፋ/ርዳታ/ዕደሳ ።
- ጥገን፡ የጕልበት ዕብጠት በጥቶ ማው ጣት ("መጠገን መፈወስ የሚገባው በሽታ ጥገናም ባለጥግን ፈረስ በቅሎ በራ አህያ") ።
- ጥገን ያዘው፡ ዐበጠ/ታመመ ("ውሃ ወጣበት ጕልበቱ ግልገል ሰኰናው") ።
- ጥገኛ (ጥጉዕ/ፅጉዕ/ጽዉን)፡ የተጠጋ/የተማጠነ ("ሰውን ጥግ ያደረገ በሌላ መንግሥት ጥግ ያደረ ባለጥግ ጠባቂ ያለው") ።
- ጥገኞች፡ የተጠጉ ("ጥግ የያዙ") ።
- ጥጉብ (ጽጉብ)፡ የጠገበ/የወፈረ ("ወፍ ራም መጣፍ ጥራዘ ብዙ") ።
- ጥጊ፡ አበባ ጽጌ ።
- ጥጋበኛ (ኞች)፡ ጥጋብ የበዛበት ("ባለ ጥጋብ ድኻ አጥቂ") ።
- ጥጋብ፡ የሆድ ምላት ("በመብል በመጠጥ") (መክ. ፭፡ ፲፪) ።
- ጥጋት (ትግ. ፅግዒ)፡ ጭፍልቅ ትር ታሮ (ኤር. ፬፡ ፫) ።
- ጥጋት፡ ዕዳሪ ("ማረሻ ያልዞረበት መሬት") (ጐዣም) ።
- ጥጋት፡ ጥግ ።
- ጥጋት፡ ጥግ/ጠጋ ።
- ጥጋጥግ፡ የጥግ ጥግ ("ብዙ ጥግ") ።
- ጥግ (ፅግዕ/ጸወን)፡ ሥር/ታች/ግርጌ (፩ ሳሙ. ፳፡ ፳) ("የገደል ጥግ የቤት ጥግ እንዲሉ") ።
- ጥግ፡ የድኻ ረዳት/ደጋፊ ("ሀብታም፥ ሰው") ።
- ጥግ ያዘ፡ ጥግን ገንዘብ አደረገ ።
- ጥግ ጥጉን ኼደ፡ ታች ታቹን ሥር ሥሩን ዐለፈ ።
- ጥግ) ፍግ፡ የፈገገ የሣቀ ጥቂት የበራ ።
- ጥግር፡ የተጠገረረ/የተደበለለ ("ተሸካሚ ጥግር ድብል እንደ ጠገራ ያለ ከባድ ሸክም") ።
- ጥግታ፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥግነት፡ ጥግ መኾን ።
- ጥግናት፡ ዝኒ ከማሁ ("እስራት ጥቅልላት") ።
- ጥግን (ኖች)፡ የተጠገነ/የታደሰ/የዳነ እስር ጥቅል ።
- ጥግንግን፡ የተጠጋገነ ("እስርስር") ።
- ጥጐር፡ በቡልጋ ክፍል ያለ ቀበሌ ።
- ጥጎች፡ ሥሮች/ታቾች ።
- ጥጥ (ጦች)፡ የታወቀ ተክል ("በቈላ አገር ፍሬው ተዘርቶ የሚበቅል ተፈልቅቆ ተዳምጦ ተባዝቶ ተፈትሎ ድርና ማግ ኹኖ ተሠርቶ የሚለበስ በግእዝ ጡጥ ይባላል") ።
- ጥጥ ፍሬ፡ የጥጥ ፍሬ ("ጥፍጥሬ") ።
- ጥጥር (ሮች)፡ የጠጠረ ("ጥኑ ጠንካራ") ።
- ጥፈራ፡ ዝኒ ከማሁ ።
- ጥፈት (ጽሕፈት)፡ የቃል/የነገር ሥ ዕል ምሳሌ በብራና ላይ ተሥሎ የሚታይ ፊደል ።
- ጥፈት ቤት (ቤተ ጽሕፈት)፡ ደብዳቤ ማዘዣ ማንኛውም ጕዳይ የሚጣፍበት የጥፈት ቤት ።
- ጥፉ (ጥፉእ)፡ የጠፋ ("ብላሽ ከንቱ በክ ክፉ የማያምር (ተረት) ኹለት ጥፉ ካገር ይጥፉ የልጅ ጥፉ፥ በስም ይደግፉ") ።
- ጥፉ፡ በረሓ ምድረ በዳ ደረቅ ስፍራ ("ነውረኛ ሥራ") (ዘኍ. ፳፡ ፭፡ ሕዝ. ፳፡ ፵፬)
"
- ጥፉዎች/ጥፎች፡ የጠፉ/ከንቱዎች (፩ ቆሮ. ፩፡ ፲፰) ።
- ጥፊ (ጥፍሕ)፡ ውስጥ እጅ ("የውስጥ እጅ በትር") (ዮሐ. ፲፰፡ ፳፪፡ ፲፱፡ ፫) ።
- ጥፊ (ጽፍዐት)፡ ሽውታ ("ያይን ዕብጠት ምች") ።
- ጥፋተኛ (ኞች)፡ በደለኛ/ክፉ አድ ራጊ ።
- ጥፋት (ጥፍአት)፡ ሞት/ኅልፈት ("እንዳልነበረ መኾን") (ዘፍ. ፮፡ ፲፯፡ ፩ ቆሮ. ፲፭፡ ፵፪) ።
- ጥፋት፡ የማይገባ ሥራ ("ስርቆሽን ስካርን ዝሙትን የመሰለ ነውር ነገር") ።
- ጥፌ፡ ቅጠሉ ጫት የሚመስል ዕንጨት ችፌ የሚያጠፋ ።
- ጥፌ፡ ዝኒ ከማሁ ለጥፉ ("ከባለቤቱ የራቀ የጥፌ ብር እንዲሉ") ።
- ጥፍረ መጥምጥ፡ የጥፍር ሥር ቍስል መርዝ የሚባል ("ጥፍርን የሚመጠምጥ የሚነቅል ደዌ መድኀኒቱም ዕፀ ዘዌ ነው") ።
- ጥፍራማ፡ ነብር/አሞራ/ካቤላ/ከብት ።
- ጥፍራም (ሞች)፡ ባለረዥም ጥፍር ("ጥፍሩን የሚያሳድግ የማይቈርጥ ናዝራዊ ባሕታዊ") ።
- ጥፍራም ኾነ፡ ጥፍሩ አደገ/ረዘመ ።
- ጥፍር (ሮች)፡ ጽፍር፡ የእጅና የእግር ቤዛ ("ወይም ጌጥ የእንስሳት ሰኰና ኮቴ ይባላል የአራዊት የቀንጠፋ እሾኸ የአዕዋፍ ሜንጦ ይመስላል") ።
- ጥፍር (ጥፉር/ፅፉር)፡ የተጠፈረ/የታሰረ/የተማገረ/የተታታ ዐልጋ ።
- ጥፍር ቍርጫ፡ የልጃገረድ ጥፍር ቈ ረጣ ።
- ጥፍር አንዶ/ጥፍር እንዶ፡ ወተታም ዕንጨት ልጡ ነጭ ሐርና ጥፍር የሚመስል ("እረኞች ልጡን ቍግ'ያደርጉታል አንዶ እንዶ እንደ ማለት ነው") ።
- ጥፍት (ጥፍአት)፡ ዕልም ድርግም ።
- ጥፍት አለ፡ ውድም አለ ።
- ጥፍን፡ የተጠፈነ ("በኹለት በኩል የታሰረ የተተበተበ በላይና በታች ከተፈለፈለ ዕንጨት ጋራ የተዋደደ ግፍና ጫፉ የተዘጋ የሸማ ጥርስ እሥራት") ።
- ጥፍጠፋ፡ የመዘርጋት/የማሣሣት ሥራ ።
- ጥፍጣፍ (ጸፍጸፍ)፡ ንጣፍ/ደንጊያ ("የተወቀረ የተጠረበ የመሬት ልባጥ") ።
- ጥፍጥ (ጽፍጥ)፡ ጣፋጣ (መዝ. ፻፵፩፡ ፥ ፬፡ ነሐ. ፰፡ ፲፱፡ መክ. ፭፡ ፥ ፲፪)
- ጥፍጥሬ፡ ጥጥ ፍሬ በማለት ፈንታ ባላገር ጥፍጥሬ ይላል ።
- ጥፍጥሬ፡ ጥፍጥ ፍሬ ("በክፉ ቀን እን ትክትኩ ዋና ምግብ መኾኑን ያሳያል") ።
- ጥፍጥነት፡ ጥፍጥ መኾን ።
- ጥፍጥፍ (ጽፍጹፍ)፡ የተጠፈጠፈ ("እበት ወይም ኩበት የሠም የትንባኾ ልጥልጥ") ።
- ጦለ (ጠለጠለ)፡
- ጦለ (ጠወለ/ዕብ. ጣል/ነሣ/ወሰደ)፡ ዞረ/ተንሰዋለለ ።
- ጦለበ (ጸለበ)፡ ሰቀለ/አንጠለጠለ/ገደለ ("ወስፈንጠርኛ ዘመን አመጣሽ ቋንቋ ነው (ግጥም) ፍቅር አይገድልም ሲሉ ቄሱን ጦለበው አሉ") ።
- ጦለጦለ/ጦለ)፡ አንጦለጦለ ("ቶሎ ቶሎ አስኬደ ዕረፍት ነሣ አንቀዠቀዠ") ።
- ጦለጦል/ጦልጧላ፡ የተንጦለጦለ/የሚንጦለጦል ("ጦንዉና") ።
- ጦሊት (ጦልዐ)፡ ያንገት ልብስ መ ጠብር ነጠላ ጥቍር ጥለት ያለው ።
- ጦሌ፡ የጦላ ዐይነት ።
- ጦልጠንክ፡ ጠባሳ፡ ጠንቅ ።
- ጦሎታ (ጠወለ)፡ ቍግ ("የጅራፍ ጕ ተና ማፍ የሚጮኸ ውልብልቢት በነፋስ ኀይል") ።
- ጦመ (ጾመ)፡ እኸል/ውሃ ሳይቀምስ ዋለ ("ከሥጋ ከቅቤ ተከለከለ") ።
- ጦመ ሕርቃል፡ ዘወረደ ያርባ ሑዳዴ መዠመሪያ ሳምንት ።
- ጦመ ልጓም (ልጓመ ጦም)፡ የምሳሌ አነጋገር ("ልጓም ሠም ጦም ወርቅ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ ጾም ልጓም ካለው የመጣ ነው አርባ ሑዳዴ ወይም ኣክፍለት እንኳን ጦመ ልጓሙን ፈታልኸ እንዲሉ (የጦም) በጦም የማይበላ የሥጋና የቅቤ ወጥ መጦም የሚያሻው የሚያስፈልገው ማለት ነው (የጦም ወጥ) በጦም ቀን የሚበላ የክክና የአትክልት ወጥ በቅባኑግ በዘ ይት የተሠራ") ።
- ጦመ ነነዌ፡ የነነዌ ሰዎች የጦሙት የ፫ ቀን ጦም (ዮና. ፫፡ ፭, ፯) ።
- ጦመ ፈቃድ፡ የነቢያትና የሐዋርያት የጽጌ ጦም ።
- ጦመኛ (ኞች)፡ ባለጦም ("ጦም ወዳድ ጧሚ ውሎ ውሎ የሚበላ ሥጋና ቅቤ የማ ይቀምስ (ተረት) ከመረቁ አውጡልኝ ከሥጋው ጦመኛ ነኝ ሰይጣን ጦመኛ ሲኾን ዘላለም ሰይጣን ነው") ።
- ጦሚት (ጠወመ)፡ የታናሽ ዛፍ ስም ("ዕንጨቱን ቀልሰው አጕብጠው ሙጭ የሚያደርጉት የጣዕማ ' ዐይነት") ።
- ጦም (ሞች)፡ ጾም፡ የጽድቅ ልጓም ("ጊዜ ሳይደርስ እንዳይበላ እንዳይጠጣ የሚከለክል ሕግ በቅዱስ መጽሐፍ የታዘዘ የጸሎት ወንድም (ተረት) ከነገሩ ጦም ዕ ደሩ ጦም የሚባሉ፯ ናቸው የሐዋርያት ጦም፥ ዐርብ ሮብ ፍልሰታ የነቢያት ጦም የልደትና የጥምቀት ገሃድ ነነዌ ሑዳዴ የቀ ድሞ ተዋሕዶዎች ግን ስለ ፍልሰታና ብሥራተ ገብርኤል ባርብ ሮብ ሥጋ ይበላሉ ስለ ጰራቅሊጦስም ስምንት ቀን ፋሲካ ' ያደ ርጉ ነበር ይባላል") ።
- ጦም አረዠን፡ የገብስ ስም ("ወደ ጥቍረት የሚያደላ ገብስ ትርጓሜው ጦም አራዠን ማለት ይመስላል") ።
- ጦም ዐዳሪ፡ ምንም የሌለው ምስ ኪን ።
- ጦሰኛ (ኞች)፡ ባለጦስ ርተኛ ("ሰበበኛ") ።
- ጦስ (ፀወሰ/ዕብ. ጣሽ/ተወ)፡ በያይነቱ ውጥንቅጥ እኸል ቅቤም ሳይቀር ("ደንቃራ ማርት በበሽተኛ ላይ አዙረው በመንገድ የሚጥሉት የሚተዉት ደዌን ከታመመው ወዳልታመመው ማስተላለፊያ የረገጠው ልምሾ (ሽባ) ይኾናል በጕራጌ አገር ግን ፉጋ የሚባል ነገድ ተቀብሎ ወስዶ ይበላዋል") ።
- ጦስ፡ ሰበብ/መዘዝ/ምክንያት "
- ጦስራኤል፡ የቀበሌ ስም ("በላይ ወግዳ በስተምሥራቅ ያለ አፋፍና ገደል የእስራኤል መዘዝ ማለት ይመስላል ጕዲትን እይ") ።
- ጦስኝ (ጥስን)፡ የቅጠል ስም ("ዐጪ የሚጣፍጥ ለወጥ ቅመም የሚኾን ሕፃናትንም ትክትክ በያዛቸው ጊዜ እናቶቻቸው ከ ወተት ጋራ አፍልተው ያጠጧቸዋል") ።
- ጦረ (ጾረ)፡ ዐዘለ/ተሸከመ/ቻለ ("ዐገዘ ረዳ አገለገለ ያዘ") ።
- ጦረ፡ ተሸከመ፡ ጠወረ ።
- ጦረ፡ ጤዛ ።
- ጦረኛ (ኞች)፡ ሐርበኛ/ዠግና ("የጦር ገበሬ የጦር ዐቅድ ዐዋቂ") (፩ ሳሙ. ፲፯፡ ፴፫፡ ሕዝ. ፴፱፡ ፳) ።
- ጦር (ሮች/ጾር/ኲናት)፡ በሶማያ ላይ የተዋደደ ("በጐንና በጐን ስለት በስተጫፍ ሹለት ያለው በትከሻ ላይ የሚያዝ አበታ ኦፎቄ ዘገር ጣምራ ሠላጢን ጭሬ የቦ") (ዮሐ. ፲፰፡ ፫) ።
- ጦር (ን)፡ ደፋ/ዘቀዘቀ ("ጀንፎን ወደ ላይ አፍሬን ወደ ታች አደረገ") ።
- ጦር (ንዋየ ሐቅል)፡ የጦር መሣ ሪያ የበዳ ጸብት ("ፍላጻ በሎታ ወንጭፍ ጐመድ ሰይፍ ጠመንዣ ሽጕጥ መትረየስ ታንክ አይሮፕላን ቦምብ የመሰለው ኹሉ መምህራን ግን ጾር ይሉታል") ።
- ጦር (ፍትወት)፡ ሥጋዊ ፈቃድ ("ማንኛውም ፍላጎት በባሕታዊና በመነኵሴ ላይ የሚነሣ ምኞት ያሳብ ትግል ጦር የተባለውም በውስጠ ምስጢር እስኪት ነው") ።
- ጦር መሪ፡ አበ ጋዝ/ፊታውራሪ/አዝማች ።
- ጦር ማቋሚያ፡ አባት ለልጁ በተላይ የሰጠው መሬት ።
- ጦር ሠራ፡ ክተት አለ ("አዘጋጀ") ።
- ጦር ተፈታ፡ ተሸነፈ/ድል ኾነ ።
- ጦር ነቀለ፡ በጦር መዠመሪያ ቈሰለ ።
- ጦር ነቀለ፡ የተወረወረ ጦርን በጋሻው መለሰ ።
- ጦር ነቀለ፡ ጦርን አነሣ/ያዘ ።
- ጦር ነቀል፡ ጦር መላሽ/ዐፍለኛ/ጐበዝ ("ያባቱን ጦር ያነሣ") ።
- ጦር፡ የዕንጨት እሾኸ/የንስሳ ቀንድ/የንብ/የተርብ/የናዜራ/የባብ/የጊንጥ መርዝ ።
- ጦር ጠማሽ፡ ውጊያ/ዘመቻ/ግዳይ ወያኔ/ፋኖ ።
- ጦር፡ ጭፍራ/ሰራዊት/ወታደር/ነፍ ጠኛ/ዘማች ("ጋሻ ጦር የያዘ የእግር ጦር ጦር መጣ እንዲሉ") ።
- ጦሸጦሸ) አንጦሸጦሸ፡ እንጣጣ ' በ
- ጦሽ አለ (ዕብ. ጣሽ በረረ)፡ ጮኸ ድምጥ ሰጠ ("እሳት የገባ ዕንጨት ተበተነ ' የፍም") ።
- ጦቢት፡ ደግ/ጻድቅ/የሚያምር ማለት ነው ።
- ጦቢያ (ኢትዮጵያ)፡ ጦቢያ የሕዝብ ኢትዮጵያ የካህናት አነጋገር ነው ።
- ጦቢያ፡ ቅንቦ ወተታም ዕንጨት ("ወተቱ ለመጋኛና ለቍርባ መድኀኒት ይኾናል የቈላ የበረሓ ማለት ነው ከፍሬው ጋራ ነጭ ሐር የሚመስል ጥጥ ይገኛል") ።
- ጦቢያው ሰገድ፡ የሴት ስም ("ይኸውም ማክዳን ያያል") ።
- ጦቢያው ሰገድ፡ ጦቢያው የሰገደላት እመቤታችን ድንግል ማርያም ።
- ጦቢያው፡ ው የሰው ከፊል ነው ("የጦቢያ ሰው ያሠኛል") ።
- ጦነጦነ) አጦነጦነ፡ አስቸኰለ/ዕረ ፍት አሳጣ ።
- ጦና፡ የወላሞ ባላባት ስም ።
- ጦንጧና፡ ችኵል ።
- ጦዘ (ፀዊስ/ፆሰ)፡ ተጠመዘዘ/ከረረ ደሰነ ።
- ጦዘጦዘ) ጦዘ፡ አንጦዘጦዘ አንከ ወከወ ።
- ጦዘጦዝ/ጦዝጧዛ፡ የተንጦዘጦዘ ("ከ ውካዋ የማይሞላለት") ።
- ጦጢት፡ እንስት ጦጣ ።
- ጦጣ (ጦች)፡ እንደ ዥንጀሮ ሰው የሚመስል ("የዱር አውሬ እዛፍ ላይ የሚያድር ፊተ ነጭ አቦልሴ ከብልጠቱ የተነሣ ጦጣ ጠይብ ነው ይባላል (ተረት) ጦጣ ባለቤትን ታሶጣ ሲወጡ እንደ ጦጣ ሲወ ርዱ ዐሳር መጣ") ።
- ጦጤ፡ ከነጭ ማሽላ ቂጣ የተዘጋጀ ጠላ ንጣት ያለው ።
- ጦጤ፡ የገብስ ስም ("እንደ ጦጣ ነጭነትና ኣቦልሴነት ያለው ገብስ") ።
- ጦጥልሽ፡ በጐዣም ክፍል በመተከል ውስጥ ያለ ቀበሌ ።
- ጦፈ (ዕብ. ጻፍ - ፈሰሰ ተንጠባ ጠበ)፡ ቀለጠ ("ጧፍ ኾነ ነደደ ተቃጠለ ተንቀለቀለ ሙር") ።
- ጦፈ፡ አበደ/ተማረ ።
- ጧ አለ (ዕብ. ጻዋሕ)፡ ወደቀ ተኛ ("ተዘረረ ተዘረጋ ዟ አለ") ።
- ጧ አለ፡ ተቀደደ/ተበጠሰ ("ቷ አለ ጧ አለ አለ ልክ ሣቀ") ።
- ጧ አደረገ፡ መታ ("በጠሰ") ።
- ጧሚ (ዎች)፡ ጸዋሚ ።
- ጧሪ፡ የጦረ/የሚጦር ("ጠዋሪ ዐጋዥ ረዳት ተሸካሚ ቻይ") ።
- ጧት (ጽባሕ)፡ ማለዳ ("ወፍ ሲጮኸ ከንጋት እስከ ፀሓይ መውጣት ያለ ጊዜ ዐማርኛን አስተካክለው የማያውቁ ሰዎችግን ጠዋት ጥዋት እያሉ ይጽፋሉ") ።
- ጧፍ (ፎች)፡ በሠም የተነከረ የ ሸማ መብራት ("ፋና እየቀለጠ የሚነድ ጧፍ'ዕጣን እንዲሉ") ።
- ጧፍ፡ የሠም መብራት፡ ጦፈ ።
No comments:
Post a Comment