Friday, June 6, 2025

                                 

የበ ዲቃላ በግእዝ አልፍቤት በአበገደ ተራ ቍጥር ፳፩ኛ ፊደል ። ጰን ፳፩ኛ ማለት ከታች የጠን ፱ኛነት ለኀ የቀኝ ፲፱ኛነት ለጸ ሰጥቶ በማፌጋፈግ መኾኑን አስተውል ። በፊደልነት ስሙ ጰይት አኃዝ ሲኾን ጳ ፯፻ ይባላል ።

ጰ ፡ በበና በፐ ፈንታ ይነገራል የኹለቱም ተወራራሽ ነው”  መዝገበ ፊደልተመልከት 

ጰራቅሊጦስ (የመንፈስ ቅዱስ ቅጽል): "መጽንዒ" "መንጽሒ" የሚያጸና የሚያነጻ ማለት ነው። አማላጅ፡ አስታራቂ። (ዮሐ )

ጰንጠቈስጤ ትርጉም: ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ያለው ዐምሳ ቀን።

ጰንጤናዊ: የጴንጤን ተወላጅ (ነው)

ጲላጦስ: በጌታችን ጊዜ ኢየሩሳሌምን ይገዛ የነበረ የካም መንግሥት።

ጳልታን ትርጉም: የርኩምና የመረቡ ዓይነት። (ዕብራይስጡ) ማብራሪያ: መያዣ ከረጢት ያለው። (የውዳሴ ማርያም ተርጓሚዎች) የአዳምን መከራ የተቀበለ የጌታችን ምሳሌ ያደርጉታል። (ፈረንጆችም) ፔሊካን ይሉታል። የጥርስ ሐኪም መማሪያም በርሱ ስም ይባላል።

ጳኵሚስ: በምንኩስና ለእንጦንስ የተስፋ ቃል የሆነ ጻድቅ።

ጳውሎስ (የሰው ስም): አስቀድሞ መምህረ ኦሪት የነበረ፡ ኋላም መምህረ ወንጌል የሆነ፡ ቁጥሩ ከአርድእት ሲሆን ማዕርጉ እንደ ጴጥሮስ ነው። (ከዚህ የተነሣ) የአገራችን ሰዎች "ጴጥሮስ ጳውሎስ" የሐዋርያት አለቆች ይሏቸዋል።

ጳጕሜ (የወር ስም): ፲፫ኛ ወር፡ ተረፈ ዓመት። በነሓሴ መጨረሻ በ፫ ዓመት ቀን፣ በአራተኛው ዓመት ግን ቀን ይኾናል። (ትርጓሜው) ጭማሪ ማለት ነው።

ጳጳስ (ሶኻ): ቄስ፡ ካህን፡ የሚሠልስ፡ የሚተያስ። (ቲቶ ፩፡ ፩ጢሞ ፫፡ ) "ጳጳስ" ከጽርእ "ፓስ" (እረኛ) ማለት ነው። የቤተ ክርስቲያን አባት፡ ማዕርጉ ከሊቀ ጳጳሳት በታች፡ ከኤጲስቆጶስ በላይ የኾነ አቡን።

ጳጳስ ኤጲስቆጶስ: የጠቅላይና የውራ ግዛት አቡኖች፡ የሃይማኖት አባቶች።

ጳጳስነት: ከጵጵስና ጋር ተመሳሳይ ነው።

ጴጥሮስ ጳውሎስ (የታቦት ስም): በጴጥሮስና በጳውሎስ ስም የተቀረጸ ጽላት። (ይከም በሐምሌ ቀን በአያመቱ ይገባሃል)

ጴጥሮስ: ከ፲፪ቱ ሐዋርያት አንዱ፡ አለቃቸው። ጌታ ከትንሣኤ በኋላ "በጎቼን ጠብቅ" ብሎ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሾመው። "ጴጥሮስ ኰኵሓዊ" ማለት "አለታዊ" ማለት ነው ይላሉ። ኰኵሕ የተባለም ክርስቶስ ነው።

ጵጰሳ: ከላይ ካለው ጋር ተመሳሳይ።

ጵጵ: የከንፈር ድምፅ።

ጵጵስና: ጳጳስ መሆን።

ጶያት (የፊደል ስም): " ቤት" ማለት ነው።


No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ