Friday, June 6, 2025

                                 

: ፲፯ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ተራ ቍጥር (የግእዝ ፊደል) በፊደልነት ስሙ "ፈፍ"፡ በአኃዝነት " " ይባላል።

: የመ ተወራራሽ (የመ ተለዋጭ) ፈነጪ መነጨ፡ ፈለሰመ ፈለሰፈ፡ ፊና ሚና

: የፐ ተለዋጭ (የፐ ተለዋጭ) "ፋናን" ተመልከት፡ "ኰረብታን" እይ።

ፈለለ: ወፈረ፡ ደነደነ፡ ሠባ፡ ተከፈለ፡ ተለየ።

ፈለል ፈለል አለ: እለይ እለይ አለ፡ ድልብኛ፡ ገችኛ ኼደ።

ፈለል: ዝኒ ከማሁ፡ የሠባ።

ፈለመ: ቀደመ፡ ዠመረ፡ ከሌሎች በፊት መታ፡ ወጋ፡ ኣቈሰለ፡ በጥይት፡ በጦር፡ አንበሳን፡ ዝኆንን፡ ጐሽን፡ አውራሪሥን፡ ግስላን።

ፈለማ: ቅድሚያ፡ ዥመራ።

ፈለሰ (ፈሊስ ፈለሰ): ተናደ፡ ተፈነቀለ፡ ነገለ፡ ተነቀለ፡ ወጣ፡ ወደ ባዕድ አገር ኼደ፡ ተሰደደ (፪ነገ ፲፯፡ ፳፫፡ ዓሞ፩፡ ፭)

ፈለሰ: ታደሰ፡ ተለወጠ (ተገብሮ)

ፈለሰ: አፈለሰ፡ መነቀረ፡ ፈረሰ (ገቢር)

ፈለሰመ: ፈለሰፈ።

ፈለሰሰ): አንፈላሰሰ፡ አጋደመ፡ አስተኛ፡ አንከባለለ፡ አገላበጠ (በቅርብ)

ፈለሰስ: ፈልሳሳ፡ ዝኒ ከማሁ፡ የተንፈላሰሰ፡ እንዳፈቀደው የሚተኛ።

ፈለሰፈ: ጠበበ፡ አራቀቀ፡ ሥጋዊ ጥበብን፡ ዕውቀትን፡ ብልኀትን ፈተነ፡ መረመረ፡ ግብር እምግብር ከወነ፡ ስልክን፡ ራዲዮንን፡ መርከብን፡ ሱማራን፡ ባቡርን፡ ኦቶሞቢልን፡ አይሮፕላንን፡ ታንክን፡ የንጨት፡ የብረት፡ የሸክላ፡ የሸማ፡ የስፌት፡ የጽፈት፡ የወፍጮ ማንኛውንም የሥራ መኪና፡ የጦር መሣሪያ፡ ቦምብን፡ አቶምን፡ ሂድሮዤንን፡ ኑክሌርን፡ ሮኬትን አዘጋጀ፡ ሠራ፡ አበጀ (ዳን፲፪፡ ፬) ባላገር ግን ፈለሰመ ይላል።

ፈለቀ (ፈሊቅ ፈለቀ): መነጨ፡ ወጣ፡ ፈሰሰ። እከሌ አምልኮ ባዕድ ስለሚወድ ዛር ፈለቀበት፡ ወጣበት።

ፈለቀ: ሰረቀ፡ ብልጭ አለ፡ በራ፡ እንጸባረቀ። በምሥራቅ በኩል ሰማዩ ይፈልቃል (ይበርቃል) (ተገብሮ)

ፈለቀ: በጥቂቱ ቀደደ፡ ሠነጠቀ (ገቢር) ፈለቀ የሚነገረው ለቀሚስና ለጥብቆ ዐንገት ማግቢያ ነው።

ፈለቀ: የወንድ ስም።

ፈለቀቀ (ፈለቀ፡ ለቀቀ): ኣፍታታ፡ ለያየ፡ በተነ የጥጥን ፍንድ በጣት።

ፈለቀቀ: ኣላላ፡ ከፈተ። እስረኛው የሰንሰለቱን ፍንጅ ፈለቀቀና አመለጠ።

ፈለቀጠ: ርጥብ ፍሬን ከፈለ።

ፈለቄ: ፈለቀች፡ የሴት ስም።

ፈለከ (ፈለክ፡ ሰማይ): ጠረበ፡ አጐደጐደ።

ፈለገ (ፈሊግ ፈለገ): ሻ፡ ፈቀደ (ዘፀ፲፪፡ ፴፭)

ፈለገ: ከፈለ፡ አነተበ፡ ሠነጠቀ።

ፈለጋም: እግሩ ፈለግ ያለበት፡ የበዛበት ሰው።

ፈለግ: መካከሉ የተከፈለ የፍየል ጥፍር፡ ሰኰና።

ፈለግ: የነተበ፡ የተላጠ፡ የተሠነጠቀ፡ የተረከዝ ቈዳ። አለመጫሚያ ስለ ኼድኩ እግሬ ፈለግ አወጣ።

ፈለጠ (ፈሊጥ ፈለጠ፡ ፈለጸ): ሠነጠቀ፡ ሠነጠረ፡ ፈነከተ፡ ተረከከ፡ ሰበረ፡ ሸነሸነ። ለየንወለለንከፈለን ተመልከት።

ፈለጠ: ቀደደ፡ ተረተረ። (ተረት): ባልንጀራዬ ሲበልጠኝ ቍንጣን ይፍለጠኝ

ፈለጠ: ዐወቀ፡ ዘየደ።

ፈለጣ: የመፍለጥ ሥራ፡ ሥንጠቃ፡ ሽንሸና።

ፈለፈለ (ፈልፈለ፡ መነጪ): ማሰ፡ ፈረፈረ መሬትን።

ፈለፈለ: ቀረጸ፡ ሰረሰረ፡ በሳ፡ ነደለ ዕንወትን።

ፈለፈለ: እሸትን ከንቡጥ፡ ጫጩትን፡ ትልን ከንቍላል ቀፈቀፈ፡ አወጣ፡ ረባ፡ ብዙ ወለደ።

ፈሊጠ ቢስ: ፈሊጠ መጥፎ፡ ፈሊጥ የሌለው።

ፈሊጠኛ: ፈሊጥ ዐዋቂ፡ ባለፈሊጥ፡ ዘዴኛ።

ፈሊጥ: ዕውቀት፡ ዘዴ፡ ቃንጤ።

ፈሊጥ: ዘዬ።

ፈላ (ፈልሐ): ተፍለቀለቀ፡ ተንተከተከ፡ ጠላው፡ ጠጁ፡ ውሃው፡ ቡናው። (ተረት): ተጥዶ የማይፈላ፡ ተሹሞ የማይበላ (ጕድ ፈላ): ወጣ፡ ተገለጠ። (ደሙ ፈላ): ተበሳጨ፡ ተናደደ፡ ተቈጣ፡ አመረረ።

ፈላ: መነጩ፡ ፈለቀ (ዘዳ፰፡ ፯፡ ሕዝ ፵፯፡ ፪)

ፈላ: በቀለ፡ ሽፍ አለ ችግኙ።

ፈላ: በብዛት ወጣ ጕንዳኑ፡ ምሥጡ፡ ዘመሚቱ፡ ዐሸኑ።

ፈላ: እሳት መሰለ፡ ጋለ። (ተረት): ብረት ካልፈላ አይላላ

ፈላለገ: ፈቃቀደ።

ፈላለጠ: ሠነጣጠቀ፡ ሸናሸነ።

ፈላላ: የፈለለ፡ ወፍራም፡ ደንዳና፡ ሥብ፡ ጐነ ሰፊ።

ፈላሚ (ዎች): የፈለመ፡ የሚፈልም፡ ቀዳሚ፡ ዠማሪ።

ፈላስማ: ፈላስፋ።

ፈላስፋ (ፎች): አስተዋይ፡ ብልኅ፡ ዐዋቂ፡ ባለአእምሮ፡ ተራቃቂ፡ የዓለማዊ ጥበብ መሪ፡ አስተማሪ፡ ኮከብ ቈጣሪ፡ ይህ ይኾናል፡ ይህ ይመጣል ብሎ ተናጋሪ። ባላገርም ፈላስማ ይላል።

ፈላስፋ ኾነ: ዐወቀ፡ ተራራቀ።

ፈላስፋ: ዓለም ዐላፊ፡ ጠፊ መኾኑን ስላወቀ ከሰው ተለይቶ በበኣት (ዋሻ) ተከቶ፡ ድንጋይ ተንተርሶ፡ ዳዋ ለብሶ፡ ቤዛ ልሶ የሚኖር፡ ሔኖክን፡ ኤልያስን፡ ቡዳሃን፡ ዲዮጋንስን፡ አቢብን፡ እንጦንስን፡ ማር ይሥሐቅን የመሰለ እውነተኛ ባሕታዊ፡ መንፈሳዊ ዕውቀት፡ ማስተዋልና ጥበብ ያለው መናኝ፡ መነኵሴ፡ ግሑሥ።

ፈላስፋ: ዋኘ።

ፈላስፋነት: ፈላስፋ መኾን።

ፈላሻ: ካገሩ፡ ከወገኑ ተሰዶ፡ በባዕድ አገር የሚኖር ስደተኛ፡ የአይሁድ ዘር፡ ባሌጅ፡ ሠራተኛ። ይኸውም በአብርሀ አጽብሐ ጊዜ ጥምቀትን ያልተቀበለ ነው።

ፈላሻነት: ፈላሻ መኾን፡ ስደተኛነት።

ፈላሽ (ፈላሲ): የፈለሰ፡ የሚፈልስ፡ ነጋይ፡ ተነቃይ።

ፈላሽ: አፍላሽ። (ምሳሌ): የኔን ነገር ወትሮ እያሉብኝ ችላ በጡንቻኹ አደገ የክንፉ ቡችላ። አወይ ዝንጀሮ ጐሹ ውድማ ፈላሹ። (ዝንጀሮ በጥይት ተመቶ በሞተ ጊዜ የሚስቱ ሙሾ ነው።)

ፈላሾች (ፈላስያን): ስደተኞች፡ ጠይቦች፡ ባለጆች።

ፈላሾች: በግዜር፡ በኦሪት አምነው፡ እስራኤልን ተከትለው ከፋርስ፡ ከባቢሎን የወጡ አሕዛብ (ሕዝ፵፯፡ ፳፪)

ፈላቂ (ጥል): የሚፈልቅ፡ ሠንጣቂ፡ ቀዳጅ።

ፈላቂ: የፈለቀ፡ የሚፈልቅ፡ በራቂ።

ፈላጊ (ጎች): የፈለገ፡ የሚፈልግ፡ የሚሻ። ነገር ፈላጊ እንዲሉ።

ፈላጭ (ጮች): የፈለጠ፡ የሚፈልጥ፡ ሠንጣቂ፡ ሸንሻኝ።

ፈላጭ ቈራጭ: የሚፈልጥ፡ የሚቈርጥ።

ፈላጭ: ሰውን ከግንባሩ እስከ መጋፊያው።

ፈላጭነት: ፈላጭ መኾን።

ፈልሰስ ፈልሰስ አለ: ገልበጥ ገልበጥ አለ።

ፈልሳፊ: የፈለሰፈ፡ የሚፈለስፍ፡ ጠባቢ፡ አራቃቂ።

ፈልቃ: ሣቂታ ሴት፡ ሥቃ የምታሥቅ።

ፈልቃቂ: የፈለቀቀ፡ የሚፈለቅቅ።

ፈልቅ: ብራቅ ከመታው መሬት የሚገኝ የመብረቅ ብረት፡ ማግኔት። ጋሎች ከሌቻ ይሉታል።

ፈልፈላ (ፋል): ርት የተደፈነ ሥራሥር ዕንቍላል።

ፈልፈላ ፈልፈልቱ ሥሩ በግእዝ ፋል ሲኾን በጋልኛ ይነገራል፡ ባማርኛም ተለምዷል።

ፈልፈልቱ: ምድር ምሶ ክፉ መድኀኒት የሚቀብር ርተኛ ሰው።

ፈልፋይ (ዮች): የፈለፈለ፡ የሚፈለፍል፡ ዕንቍላል ያለው ፍጥረት፡ አንበጣ፡ ወላድ ሰው።

ፈሎ ቢስ: ርባና ቢስ።

ፈሎ: ፋይዳ፡ ረብ፡ ጥቅም፡ ትርፍ።

ፈሰ ከንቱ (): የፈሱ ሽታ ራስ የሚበጠብጥ፡ ሆድ የሚቈርጥ፡ የሚያም፡ ቍናሳም።

ፈሰለቀ) አንፈሳለቀ: አንፈላሰሰ፡ አላጋጭ አደረገ።

ፈሰሰ (ፈሲስ፡ ፈሰ): ተደፋ፡ ተቸለሰ፡ ተከነበለ፡ ወረደ፡ ተዘቀዘቀ፡ ኮለል አለ፡ ቀለጠ፡ ነጠረ፡ ደከመ፡ ጠፋ (ሚክ፭፡ ፲፭) "እኸሉ ፈሰሰ፡ እንባው ፈሰሰ፡ ቅቤው ፈሰሰ፡ ልቡ ፈሰሰ፡ ዐይኑ ፈሰሰ" እንዲሉ። "የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም ይፈስይፈሳል እያለ ጠብቆ ይነገራል እንጂ፡ ይፈስስይፈስሳል አይልም። " (ተረት): "ውሃ ከፈሰሰ አልታፈሠ። " (ሽንብራው ፈሰሰ): ሕፃን በወደቀ ጊዜ የሚባል ቃል።

ፈሰሰ: ተነገረ። "ኑዛዜው ፈሰሰ" እንዲሉ።

ፈሰሰ: ተንሿሿ (ግእዝ)

ፈሰሴ (ፈሰሳዊ): ባገር ላይ የተጣለ ዕዳ፡ መቻያ ባላገር አዋጥቶ ላገረ ገዢ የሚከፍለው (፪ነገ፡ ፳፫፡ ፴፫፡ ፪ዜና፡ ፴፮፡ ፫)

ፈሰሴ: የሽንብራ ቂጣ፡ ኩፍታ፡ የሊጡን በምጣድ ላይ መፍሰስ ያሳያል።

ፈሰስ አለ: ፈሰሰ፡ ዟ ሰተት አለ ሰውየው።

ፈሰስ አደረገ: ፍልቅ ጠብ አደረገ።

ፈሰስ ከንበል አለ: ድፍት ውድቅ አለ።

ፈሰስ: ከጣራ የፈሰሰ የዝናም ውሃ፡ ካጥር ግቢም ተሰብስቦ በግንብና በግድግዳ ሥር የሚፈስ ፈሰስ ይባላል።

ፈሰስ: ዝኒ ከማሁ ለፈሳሽ። "ከናት ፈሰስ እስከ እግር ድረስ" እንዲሉ።

ፈሰከ: ጦምን ተወ፡ ገደፈ፡ ሥጋ በላ።

ፈሰገ የሕዝብ፡ ፈሰከ የካህናት አማርኛ ነው።

ፈሰገ: ፈሰከ።

ፈሰፈሰ (ትግ ፈስፈሰ፡ ዞረ): አስፈራራ፡ በክርን መታ፡ ደበደበ፡ አስፈሳ። "ዘሩ ፈሰሰ ነው"

ፈሰፈስ፡ ፈስፋሳ: የተፈሰፈሰ፡ ፈሳም፡ ፈሪ፡ ወስዋሳ፡ ዘዋሪ።

ፈሱን ጠበሰ: ሮጠ፡ ሸሸ፡ ጋለበ። (ያሮጊት ፈስ): ክረምት አፈራሽ ነገር፡ በበጋ እንደ ፈስ የሚበን፡ የሚተን ክብ እንክብል፡ ዐይን የሚያኸል ፍጥረት። "ልጆች በተሰበሰቡበት ፈስ ተፈስቶ የፈሳው ባይታወቅ፡ የፈስ አፈርሳታ ለማውጣት፡ ፈስ ፈሶ ፈስ ዐራራ፡ ቈርጦ ቈርጦ ደም ያሳራ፡ ደሙ ሲረጋ በለው ባለንጋ " "...ያጤ መስቀል ሲንቀለቀል የፈሳውን ልቡን ይንቀል" ይባላል።

ፈሲታ: የፈሳች። (ተረት): "የፈሲታ ተቈጢታ። "

ፈሳ (ፈሰወ፡ ዐረ ፈሳ): በታች ተነፈሰ፡ ፈሱን ለቀቀ፡ ዘረጥ አደረገ፡ አንጣረረ። (ተረት): "ባልፈሱበት ቂጥ አያፍሩበት። "

ፈሣ (ፈሥሐ): ተደሰተ። የካህናት ዐማርኛ ነው።

ፈሳ: ሸሸ የቅል፡ የቀይ ሽንኵርት።

ፈሳ: ብብቱን በመዳፉ ዐፍኖ እንደ ቂጥ አስጮኸ።

ፈሳ: የተማረውን ረሳ፡ ዘነጋ፡ አጠፋ፡ ዐጣ።

ፈሳም (ሞች): ኹል ጊዜ የሚፈሳ፡ የሚያንዛርጥ፡ ፈሱን የማይቋጥር፡ ፈሪ።

ፈሳሽ (ሾች): የፈሰሰ፡ የሚፈስ፡ ወራጅ፡ ቀላጭ፡ ውሃ፡ ሠም፡ ዘይት፡ ቅባት፡ ዐረቄ፡ ደም፡ የመሰለው ኹሉ። (ኢሳ፵፬፡ ፬፡ መዝ፩፡ ፫፡ ኢሳ፲፱፡ ፮፡ ሕዝ፴፪፡ ፪) "የግዜር ቃል እንደ ውሃ ፈሳሽ፡ እንደ እንግዳ ደራሽ አይዶለም፡ ከጥንት ካባቶች ሲያያዝ የመጣ ነው እንጂ። " (ተረት): "የተጠማ ከፈሳሽ፡ የተበደለ ከነጋሽ። "

ፈሳሽቱ: ያች ፈሳሽ፡ ውሃዪቱ (ኤር፲፰፡ ፲፬)

ፈስ (ፈስው): ታችኛ ትንፋሽ፡ ግም፡ ያይነ ምድር ወላፈን። (ተረት): "የጠበኛ ፈስ ዐይን ያፈስ። " "እንዲያውም በመላ ፈስ ዳለቻ ነው። "

ፈስ: "ዘሩ፡ ተነነ፡ ነው። ቱኒ፡ ፈሪ፡ በከን።"

ፈስማ: ፈሶሌ።

ፈስንዱስ: ዝኒ ከማሁ። "ፈሱን ዱስ አደረገ": በወፍራሙ ፈሳ።

ፈሶሌ: ተበጣሽ ጠፍር፡ ገመድ፡ ልጥ፡ ፈትል፡ ፈስማ።

ፈረመ (ፈፀመ፡ ዘጋ): በደብዳቤና በውል፡ በስምምነት፡ በስሌት፡ በማንኛውም ጽፈት መጨረሻ "ፈቅጃለኹ፡ ልክ ነው" ሲል ስሙን ጻፈ፡ ምልክት አደረገ፡ (ዐተመ)

ፈረመ: ፈለመ፡ ወጠነ ሥራን በትጋት፡ በጥራት።

ፈረሰ (ፈሪስ፡ ፈረሰ): ተናደ፡ ወደቀ፡ ጠፋ፡ ተበላሸ፡ ተቈመጠ፡ ተሻረ፡ እንዳልተሠራና እንዳልነበረ ኾነ። (ተረት): "ልጅ ደረሰ፡ ቤት ፈረሰ። "

ፈረሰ እሳት: ከእሳት የተፈጠረ የእሳት ፈረስ (፪ነገ፡ ፪፡ ፲፩)

ፈረሰ: ተበተነ፡ ተዘረዘረ ዱለቱ፡ ሤራው፡ ሸንጎው ኹሉ።

ፈረሰ: ጋለበ፡ ነጐደ፡ ወጣ፡ ወረደ (ኪ፡ ወ፡ ክ)

ፈረሰ: ፈነዳ። "ልቡ ፈረሰ እንዲሉ። "

ፈረሰኛ (ኞች): በፈረስ ተቀምጦ የሚጋልብ፡ ግልቢያ ዐዋቂ። (አዝማሪ): "ከፈረሰኞች የምናውቃቸው፡ በሻሽ አቦዬ ኀይሌ አንዳርጋቸው። " "ከፈረሰኞች አሉ በልዩ፡ መኻል አገዳ የሚለያዩ። "

ፈረሰኛ: በሰልፍ ኹኖ እንደ ፈረስ እየዘለለ የሚኼድ፡ ፈረስ የተቀመጠ የሚመስል ውሃ፡ ሙላት፡ ነፋስ ፈረሱ። በግእዝ ሞገድ ማዕበል ይባላል።

ፈረሰኛ: የዶሮ ፍርንባ።

ፈረሱ: ፈረስ፡ የርሱ ፈረስ።

ፈረሱላ: ከርሳስ የተበጀ፡ የሚዛን ጕልቻ፡ የዝኆን ጥርስ፡ የቡና፡ የቈዳ መመዘኛ፡ አንዱ ፈረሱላ በኪሎ ፲፯፡ በነጥር ይኾናል።

ፈረሳቤት (አቤት ፈረስ): ንኡስ አገባብ፡ የሐዘንና የአንክሮ ቃል። "አቤት ፈረሱ ምንኛ ታል" ማለት ነው።

ፈረሳቤት: የዕከክ ስም፡ በሙሉ ጨረቃ ማታ ማታ የሚያሳክክ፡ ቀን የሚጠፋ ዕከክ። ፪ኛም ደመ መራሪት ይሉታል። ፫ኛም የፈረስን ገላ ስለሚያለብስ ፈረሳቤት ተባለ።

ፈረስ (ሶች): ከቤት እንስሶች አንዱ፡ የጋማ ከብት፡ ሰው በዠርባው ኮርቻ ጭኖ የሚቀመጥበት። ተባቱም እንስቱም ፈረስ ይባላሉ። ኹለቱን ለመለየት ብትፈልግ ፈረስ [ብለህ መለየት ትችላለህ]

ፈረስ ዘበኛ: የፈረስ ዘበኛ፡ የባልደራስ ጭፍራ፡ የንጉሥ ፈረስ ጠባቂ።

ፈረስ: ከሰንጠረዥ መጫወቻ አንዱ፡ ይኸውም የፈረስ መልክ ያለው ነው።

ፈረስ: ፈረሰኛ

ፈረሷ፡ ፈረሲቱ: ያች ፈረስ።

ፈረሷ: የርሷ ፈረስ። (ተረት): "ፈረስ ያደርሳል እንጂ አይዋጋም። "

ፈረረ (ትግ ሐባ): ፊር አለ።

ፈረቀ (ፈሪቅ ፈረቀ): ለየ፡ ከፈለ።

ፈረቀቀ (ፈረቀ): ፈነቀለ፡ ፈለቀቀ፡ ሠነጠቀ፡ ለያየ።

ፈረቃ: የሥራ፡ የሸክም፡ የጥበቃ ተራ፡ ፈንታ።

ፈረነሰ (ግእዝ ፈርነሰ): አስተኛ፡ አጋደመ፡ ዘረረ፡ ፈነደሰ።

ፈረንሳዊ፡ ፈረንሳይ (ዮች): የግእዝ ልማድ ነው፡ የፈረንስ (ፍራንስ) ተወላጅ፡ የፍራንስ ዘር፡ የፍራንስ ወገን።

ፈረንሳዩ: ፈረንሳይ።

ፈረንሳይኛ: የፈረንሳይ ቋንቋ።

ፈረንሳይዋ፡ ፈረንሳዪቱ: ያች ፈረንሳይ።

ፈረንሳዮቹ: እነዚያ ፈረንሳዮች፡ ወንዶችና ሴቶች።

ፈረንስ (ፍራንስ): የነገድ ስም፡ በአውሮጳ ውስጥ ያለ ሕዝብ፡ ሥልጣኒ ካላቸው ወገኖች አንዱ። ከተገዢነት ወጥቶ ራሱን ስለ ቻለ ፍራንስ (ፍራንክ) ተባለ ይላሉ፡ ነጻ ማለት ነው።

ፈረንጅ (ጆች): የነገድ ስም፡ መልኩ ነጭ የኾነ የአውሮጳ ሰው፡ የያፌት ዘር ፈረንጅ እንዲሉ። ባረብኛም ፈረንጅ ይባላል። ፈረንስን አስተውል።

ፈረንጅ ለመባል መሠረቱ ፍራንስ (ፍራንቼ) ሳይኾን አይቀርም፡ እንግሊዞች ፍራንስን ፍሬንች ይሉታልና። ባረብኛ ፊደል ስለሌለ ፈረንች በማለት ፈንታ ፈረንጅ ተባለ። ዳግመኛም ከ፪ኛው የዓለም ጦርነት በፊት አውሮጶች ኹሉ ባረብና በሐበሻ አገር የፈረንሳይ ቋንቋ ስለተናገሩ ፈረንጅ የተባሉ ይመስላል።

ፈረንጅ ቀመስ: ከፈረንጅ ጋራ የበላ፡ የኖረ ሰው።

ፈረንጅ: ደማቅ ቀይ ሰው።

ፈረንጅኛ: የፈረንጅ ቋንቋ።

ፈረንጆችም ሊትር ይሉታል።

ፈረንጆችም ፍሌሽ ይሉታል።

ፈረከ) አፍረከረከ: ፈረፈረ፡ ሸራረፈ፡ አፈራረሰ። 

ፈረከሰ (ፈረከ): ሰበረ፡ አደቀቀ፡ ብክካን።

ፈረከከ) ፈረቀቀ)፡ አንፈረከከ: እግርን አለያየ።

ፈረከክ፡ ፈርካካ: የተንፈረከከ፡ የሚንፈረከክ፡ በጕያው ቂጥኝ፡ ዕባጭ ወይም ሌላ ቍስል ያለበት ሰው።

ፈረኵስ: ሥጋው ገር የኾነ ዓሣ።

ፈረዘ: እዳር ደረሰ፡ ወጣ።

ፈረዘዘ) ፈርዘዘ)፡ አንፈረዘዘ: አጠገበ፡ ቀበነነ፡ ነፋ፡ አሳበጠ፡ አስደሰተ፡ አቀማጠለ። በተደራጊነትም ይፈታል። (ከረጠጠ) ተመልከት።

ፈረዘዝ፡ ፈርዛዛ: የተንፈረዘዘ፡ የጠገበ፡ ደስተኛ፡ ጸጥተኛ። (ተረት): "እኸል የያዘ ፈርዛዛ፡ ወርቅ የያዘ ቀበዝባዛ"

ፈረደ (ፈሪድ ፈረደ): በየነ፡ ከሳሽንና ተከሳሽን ለየ፡ የተያዘውን ነገር፡ ርስትንና ገንዘብ አስለቀቀ፡ ለሚገባው ሰጠ፡ ነፍሰ ገዳይን፡ ቋንዣ ቈራጭን፡ ቤት አቃጣይን ይሙት በቃይቀጣ በቃ አለ። (ተረት): "ዐይን አይቶ ልብ ይፈርዳል"

ፈረደለት: በየነለት።

ፈረደበት: በየነበት።

ፈረድ: የጕድባ፡ የፈፋ፡ የወንዝ ወሰን። "ውሃ ፈረድ" እንዲሉ።

ፈረጀ (ዐረ): ከጭንቅ፡ ከመከራ አወጣ፡ አዳነ።

ፈረጀ (ፈረገ): እኩል፡ ትክክል አደረገ፡ በወርድ፡ በቁመት።

ፈረገ (ፈረቀ): ለየ፡ አስገለለ።

ፈረገጠ) ፈገጠ (ረገጠ)፡ አንፈራገጠ: እጆቹን፡ እግሮቹን አንቀሳቀሰ፡ ዐጠፈ፡ ዘረጋ።

ፈረገጥ፡ ፈርጋጣ: የተንፈራገጠ፡ የሚንፈራገጥ።

ፈረጎ: የጋኔን፡ የሰይጣን ስም፡ በታችኛው ወግዳ መጥቈሪያ በሚባል አገር። አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሊያስታቸው ቢመጣ ይህን ገለብ ጫኑበት እያሉ ባላገሮች ያሳያሉ። የስሙ ትርጓሜ ከቅዱሳን መላእክት የተለየ ልዩ ማለትን ያሳያል።

ፈረጠ (ፈረጸ): ተጣለ፡ ወደቀ፡ ተሰበረ፡ ተፈነከተ ደንጊያው፡ እንስራው፡ ሰዉ።

ፈረጠ: ተገለጠ፡ ተረዳ፡ ታወቀ ነገሩ።

ፈረጠ: ወጣ ፈርጡ።

ፈረጠ: ፈነዳ፡ መገለ፡ ፈሰሰ፡ የቍስል፡ የአይን፡ የንቍላል፡ የልብ [ፈሳሽ]

ፈረጠመ: ገላው ጠበቀ፡ ተጠረነቀ፡ ሥጋ ያዘ፡ ሠባ።

ፈረጠጠ (ረጠጠ): ሮጠ፡ ሸሸ፡ ጋለበ፡ ወነበደ፡ ሸመጠጠ፡ ጭራውን ለበሰ፡ ኰበለለ። (ተረት): "አህያ እንዳባቱ ይፈርጥጥ፡ ዥብም እንዳባቱ ይዘርጥጥ"

ፈረፈረ (ፈርፈረ): አደቀቀ፡ አጠቀነ እንጀራን።

ፈረፈረ: ፈለፈለ፡ ሸረሸረ፡ ማሰ፡ ቈፈረ፡ ኣጐደጐደ።

ፈረፈር (ሮች): ውሃ የቈፈረው፡ ያጐደጐደው ጕድባ (ኤር፲፬፡ ፮)

ፈሪ (ዎች) (ፈራሂ): የፈራ፡ የሚፈራ፡ ብቡ፡ ሥጕ፡ ጠርጣሪ፡ ቡከን፡ እንበልጋ፡ አንቡጋድ፡ ጡርቂ። (ተረት): "ፈሪን እውሃ ውስጥ ያልበዋል" "ለፈሪ ሜዳ አይነሡም" "ዘመቻ ፈሪ፣ ሑዳድ ፈሪ" እንዲሉ።

ፈሪህ: መፍራት (ግእዝ)

ፈሪሳዊ (ውያን): ንጹሕ፡ ድንግል፡ መናኝ (ኪ፡ ወ፡ ክ)

ፈሪሳዊ: ግብዝ፡ ባሕታዊ፡ አፈ ጻድቅ፡ ልበ ኃጥእ፡ ተመጻዳቂ። (ተረት): "አባ ልብሱ ዳባ፡ ውስጡ ደባ። "

ፈሪነት: ፈሪ መኾን።

ፈራ (ፈርሀ): ልቡ ጠረጠረ፡ ባባ፡ ገነገነ፡ ሠጋ፡ ታወከ። (ተረት): "ፈሩ ፈሩ፡ ማጀት ዐሩ" "የውሻን ጥርስ ባጥንት ይፈሯል" "ሴት የላከችው ሞት አይፈራም" "አይፈራም ጋሜ አይፈራም": የእስክስታ አዝማች። "አይፈር ለፊቱ": ግንባሩን ቢሉት የማይፈራ፣ የማይመለስ ጐበዝ። "ሲፈራ ሲቸር": ላድርግ አላድርግ፣ ልስጥ አልስጥ እያለ ሲያመነታ። ዶረሰን፣ ዐፈረን አስተውል።

ፈራ) ፈረየ (ፈርኅ): አፈራ፡ ፍሬ አገኘ፡ ወለደ፡ አወጣ፡ ሰጠ፡ አንዠረገገ፡ አንጨረገገ (ዘፀ፩፡ ፯) (ተረት): "አገር ሲያረጅ ዣርት ያፈራል" "ገንዘብ አፈራ": አገኘ። "ጠላት አፈራ": አበጀ። "ዕዳ አፈራ": አመጣ። "ያፈራ ድንጋይ": በላዩ ዕንጨትና ሣር የበቀለበት ቋጥኝ፡ ገለብ፡ ገዎቻ።

ፈራ: ዥራቱን ዐጠፈ፣ ቀለሰ፣ እጕያው አገባ፣ "ሸጐ ውሻው።"

ፈራሚ (ዎች): የፈረመ፡ የሚፈርም።

ፈራረሰ: ተናናደ፡ ወዳደቀ፡ ተበታተነ።

ፈራሽ (ሾች): የሚፈርስ፡ ጠፊ።

ፈራሽ በስባሽ: ሰው፡ ሥጋዊ ፍጥረት ኹሉ።

ፈራሽነት: ፈራሽ መኾን።

ፈራጅ ቀዳጅ: የመነኵሴ ፈራጅ እንዲሉ።

ፈራጅ: የፈረደ፡ የሚፈርድ፡ እግዜር፡ ንጉሥ፡ አገረ ገዥ፡ ዳኛ፡ ሹም፡ መኰንን፡ አለቃ፡ ባለሥልጣን፡ ሊቀ ካህናት (መዝ፯፡ ፲፩)

ፈራጅነት: ፈራጅ መኾን።

ፈራጆች: ዳኞች፡ ሹሞች (ዘፀ፳፩፡ ፳፪፡ ምሳ፰፡ ፱፡ ፲፮)

ፈራጭ: የሚፈርጥ።

ፈር(ሮች)፡ የርሻ መሥመር ስበት፡ የኼደበት ትልም። በግእዝ ግን (ፈር)፡ ኺድ፡ ተሰምር ማለት ነው። ቦደነ ብለኸ ቡደንን ተመልከት።

ፈር: ትልም፡ ወፈረ።

ፈርሳም (ሞች): ፈርስ ብዙ፡ ሆዳም፡ ከርሣም።

ፈርስ: የምግብ አተላ ከጨጓራ ውስጥ የሚወጣ።

ፈርስ: የባት ውሳጣዊ ሥጋ፡ ወይም አስኳል።

ፈርሶ (ኦሮ): ጠላ። (ግጥም): "ለሣህለ ሥላሴ ከኾንኩት ወዳጅ እኔ ፈርሶ አልጠጣም፡ እጥላለኹ ጠጅ። "

ፈርሶ: ተንዶ፡ ወድቆ።

ፈርቃቂ: የፈረቀቀ፡ የሚፈረቅቅ፡ ፈንቃይ፡ ሠንጣቂ።

ፈርናሳ፡ ፍርንስ (ፍርኑስ): የተፈረነሰ፡ የተኛ፡ የተጋደመ፡ ጋድሚያ።

ፈርዖን (ኖች): የምስር ንጉሥ ስም፡ ሰው በሞተ ቍጥር የመቃብር ዋጋ ስለ ተቀበለ ፈርዖን ተባለ ይላሉ፡ ሙት አስገባሪ ማለት ነው። እሱም ከፋርስ ወደ ግብጽ የመጣ ፈላስፋ ነው።

ፈርከሻ (ትግ): ብክካ፡ ነጭ ድንጋይ።

ፈርከክ አለ: ተንፈረከከ።

ፈርከክ ፈርከክ አለ: ተንፈርክኮ ኼደት ኼደት አለ።

ፈርካሳ: የተፈረከሰ፡ ደቃቅ።

ፈርካሽ: የፈረከሰ፡ የሚፈረክስ፡ ሰባሪ፡ አድቃቂ።

ፈርኬ: የገብስ ስም።

ፈርድ፡ ፈርጅ (ግእዝ):

ፈርጅ (ጆች): አንድ ዘንግ፡ አንድ ዐርብ የነጠላ፡ ግማሽ ሸማ።

ፈርጣማ: የፈረጠመ፡ ሥብ።

ፈርጣጣ: ሆዱ ሊፈርጥ የቀረበ፡ ዘፍጣጣ።

ፈርጣጭ (ጮች): የፈረጠጠ፡ የሚፈረጥጥ፡ ሯጭ፡ ሸምጣጭ፡ ኦሮቢ፡ ኰብላይ ከብት።

ፈርጥ (ዐረ): ሽጕጥ።

ፈርጥ (ጦች): ከደንጊያ የሚገኝ አልማዝ፡ እንደ ዕንቍና እንደ ሉል የከበረ፡ በዘውድ፡ በቀለበት ላይ የሚደረግ ብርሃናዊ ማዕድን። በግእዝም ፈርጽ ይባላል።

ፈርጥ: በሐር ልብስና በከፈይ ሠቅ፡ በድባብ፡ በጃን ጥላ የሚለጠፍ ከወርቅ ከመዳብ የተሠራ ጌጥ፡ ፈርጥ የሚመስል ጥልፍ።

ፈርፋሪ: የፈረፈረ፡ የሚፈረፍር፡ አድቃቂ፡ ሸርሻሪ።

ፈሺ: የፈሳ፡ የሚፈሳ።

ፈቀረ (ፈቂር ፈቀረ): ወደደ፡ ፈቀደ።

ፈቀረኝ: ወደደኝ። "ምን ፈቀረኝ": ምንኛ፣ እንዴት ወደደኝ። ምስጢሩ ግን ፈቀር እንጂ ፈቀረኝ አያሠኝም። ምንን ተመኩት ልከት።

ፈቀቀ (ፈገገ): ዕልፍ አለ፡ ጥቂት ራቀ፡ ተገለለ፡ ተለየ፡ ተወገደ።

ፈቀቀን አስተውል።

ፈቀቅ አለ: ገለል አለ፡ ስፍራ ለቀቀ (ሉቃ፰፡ ፴፯)

ፈቀቅ አደረገ: አገለለ።

ፈቀቅ: ዝኒ ከማሁ ፈቅ፡ ገለል [ማለት]

ፈቀቅታ: ገለልታ።

ፈቂ (ዎች): የፈቃ፡ የሚፈቃ፡ በጪ።

ፈቃ (ፈቅዐ): ቈራ፡ በጣ፡ ሠነጠቀ፡ ተፈተፈ፡ ጋረጠ።

ፈቃሪ: የሚፈቅር፡ የሚወድ።

ፈቄ: ፈቅ ይበሉ ከፊል።

ፈቅ ይበሉ: የሰው ስም፡ "ካንተ ፊት ጠላቶቻችን ገለል ይበሉ" ማለት ነው።

ፈቅ: ዕልፍ፣ ራቅ። ደስታን ተመልከት።

ፈቅ: ዕልፍ፡ ፈቀቀ።

ፈቅታ: ዝኒ ከማሁ፡ ዕልፍታ።

ፈተለ (ዐረ): አቃጠረ፡ አገናኘ።

ፈተለ (ፈቲል፡ ፈተለ): በጭን ጠፋ፡ ወዘገ፡ መዘዘ፡ ሳበ፡ እነዘረ፡ አከረረ፡ ገመደ፡ ጠመረ፡ ፪ቱን ክር አንድ አደረገ። "የተፈተለ ከኹለት፡ የተታታ ከሦስት" እንዲሉ። "ሐማ ለመርዶክዮስ በተከለው ግንድ፡ በፈተለው ገመድ ተሰቀለ" (አስቴ፯፡ ፱፡ ፲)

ፈተለከ) አፈተለከ፡ ፈታ፡ አሾለከ፡ ራሱን፡ ወይም፡ ሌላውን፡ አወጣ።

ፈተላ: የመፍተል ወይም የማስረዘም ሥራ።

ፈተረ፡ ዐነቀ፡ አስጨነቀ፡ ወጠረ፡ በሥራ፡ በነገር።

ፈተሸ፡ ቀነቀነ፡ መረመረ፡ በረበረ። ፈተነን፡ ተመልከት።

ፈተተ (ፈትቶ፡ ፈተተ)፡ ቈረሰ፡ ገመሰ፡ ከፈለ፡ ተነተነ።

ፈተተ፡ ተረጐመ፡ ገለጠ፡ አስረዳ። ምሳሌ: የሐር፡ ዐምባው፡ መምር፡ ክፍሌ፡ ብሉይ፡ ተሐዲስ፡ ይፈትቱ፡ ነበር።

ፈተነ (ፈቲን፡ ፈተነ)፡ ሞከረ፡ ፈተሸ፡ መረመረ፡ ጠየቀ፡ ፈተና፡ ሰጠ፡ (ዳን፲፪፲፬፡ ሉቃስ፲፬፲፱) ጠበሰ፡ አቀለጠ፡ አፈሰሰ፡ ጥቂት፡ ጻፈ፡ አበላ፡ ጋለበ። ምሳሌ: መድኀኒትን፡ ማዕድንንም፡ በሽተኛን፡ ፈረስን፡ ወርቅን፡ በኵየት፡ ብርን፡ በጽፈት፡ ፈተነ፡ እንዲሉ።

ፈተነ፡ መከራ፡ አሳየ።

ፈተና፡ ሙከራ፡ ፍተሻ፡ ጥያቄ፡ ምርመራ። ምሳሌ: የፈተና፡ ደንጊያ፡ እንዲሉ። ፈተናውን፡ ዐለፈ፡ የተጠየቀውን፡ ዐወቀ።

ፈተገ: ላጠ፡ መለጠ ደንጊያ፡ እግርን።

ፈተገ: ልጦ ጕርዶ አወጣ፡ ስንዴን፡ ገብስን በውሃ እያራሰ ሸከሸከ፡ ዠብ ዠብ አደረገ፡ ወቀጠ፡ ከገለባ ለየ፡ ተልባን በጭድ ዐሸ፡ ቈዳን ዠለጠ፡ አለፋ፡ ዐጪር ሣርን ዐደ። በግእዝም ለተመ፡ ፈተገ ተብሎ ይተረጐማል።

ፈተፈተ (ፈተተ)፡ እንጀራን፡ አራሰ፡ ከውሃ፡ ከጠላ፡ ከጠጅ፡ ከወጥ፡ ከወተት፡ ከቅቤ፡ ጋራ፡ አደቀቀ፡ አዳወለ፡ አዳከረ።

ፈተፈተ፡ አዋሸከ፡ ነገር፡ አበዛ።

ፈታ (ፈትሐ): ተረተረ፡ አወለቀ፡ ከፈተ ጠፍርን፡ ገመድን፡ ሰንሰለትን፡ እግር ብረትን፡ ቍልፍን።

ፈታ ፈታ አለ: ፈጥኖ ተናገረ፡ ቀለጠፈ።

ፈታ: ኀጢአተኛን ከኀጢአት ማሰሪያ "እግዜር ይፍታ" አለ፡ ናዘዘ።

ፈታ: ለቀቀ፡ ሰደደ፡ አበረረ፡ ተወ እስረኛን፡ ሚስትን፡ ሥራን።

ፈታ: ስለ ሞተ ሰው ጸለየ። (ተረት): "የዘመድ ቄስ እየፈታ ያለቅስ። "

ፈታ: አሸነፈ፡ ድል አደረገ። "ጦር ከፈታው፡ ወሬ የፈታው ይበዛል። "

ፈታ: አዘዘ፡ ፈቀደ።

ፈታ: አጠፋ፡ አፈረሰ፡ ሻረ፡ በተነ፡ ጠፋ፡ ባድማ፡ ወና አደረገ አገርን፡ ሸንጎን፡ ቤትን፡ ኀበያን፡ ከተማን፡ አስማትን፡ መድኀኒትን።

ፈታ: ገለጠ፡ ተረጐመ ምስጢርን፡ ቅኔን (ማር፬፡ ፴፬)

ፈታ: ግዝትን አስወገደ።

ፈታ: ፈረደ፡ ፍርድ ሰጠ፡ ዐደለ፡ በየነ።

ፈታል (ዐረ): ወንድና ሴትን የሚያገናኝ፣ ደላላ

ፈታሪ፡ የፈተረ፡ የሚፈትር፡ ዐናቂ፡ አስጨናቂ።

ፈታሽ (ሾች)፡ የፈተሸ፡ የሚፈትሽ፡ ቀንቃኝ፡ መርማሪ።

ፈታሽነት፡ ፈታሽ፡ መኾን፡ ቀንቃኝነት።

ፈታተለ: ደጋግሞ ፈተለ፣ አጣመመ።

ፈታተገ: ወቃቀጠ፡ ሸካሸከ። "ያጤ ቤት ገረዶች ፈተጉ ፈታተጉ፡ በቍልቢጥ አስቀመጡ" እንዲሉ ልጆች።

ፈታች (ቾች)፡ የፈተተ፡ የሚፈትት፡ ቈራሽ፡ ተንታኝ፡ ቄስ፡ ሊቅ።

ፈታኝ (ፈታኒ)፡ የፈተነ፡ የሚፈትን፡ ሞካሪ፡ ፈታሽ፡ መርማሪ፡ ጻፊ፡ (ኤር፳፯፡ ማቴዎስኛ፡ ተሰሎንቄ)

ፈታኝ (ፈትሐኒ)፡ ለቀቀኝ፡ ተወኝ።

ፈታኞች፡ የፈተኑ፡ የሚፈትኑ፡ መርማሪዎች።

ፈታይ (ዮች): ፈትል የሚፈትል ወንድ ወይም ሴት፣ ክር የሚፈትል ሰው፣ ሸረሪት

ፈታይነት: ፈትል የመፍተል ሥራ።

ፈታጊ (ዎች): የፈተገ፡ የሚፈትግ፡ ወቃጭ፡ ዐሺ፡ አልፊ፡ ዐጫጅ።

ፈታፈተ፡ አደቃቀቀ።

ፈት (ቶች): ያጠፋ፡ አጥፊ፡ የተወ፡ የለቀቀ፡ የሚለቅ። "አገር ፈት፡ ሥራ ፈት" እንዲሉ።

ፈት: የፈታች፡ የተወች። "ይህች ሴት ባል የላትም፡ ፈት ነች። "

ፈትለክ፡ አለ፡ ፍትት፡ ሹልክ፡ ውጥት፡ አለ፡ ውሉ፡ እስራቱ።

ፈትለክፈትላካ፡ የተፈተለከ፡ ሾላካ።

ፈትል: ድርና ማግ፣ ክር (ወፍራም ወይም ቀጭን) ምሳሌዎች: "የቤት ፈትል" "የባሕር ፈትል"

ፈትቶ (ቦዝ)፡ ቈርሶ፡ ገምሶ፡ (ዐማርኛ)

ፈትቶ (ዘር)፡ መቍረስ። ምሳሌ: ጸሎተ፡ ፈትቶ፡ እንዲል፡ ቅዳሴ።

ፈትፋች (ቾች)፡ የፈተፈተ፡ የሚፈትፍት፡ (ተረት)፡ የዋስ፡ ተማጋች፡ የቈማጣ፡ ፈትፋች

ፈትፋች፡ አዋሻኪ፡ ነገር፡ አመላላሽ።

ፈቸለ፡ ያዘ፡ ነቀለ። (ለበለጠ መረጃ ፈተረን እይ)

ፈቸል (ሎች)፡ ጕጠት፡ የምስማር፡ መንቀያ።

ፈቺ (ዎች): የፈታ፡ የሚፈታ፡ ለቃቂ፡ ተርጓሚ። "አግቢ ፈቺ፡ ሰንሰለት ፈቺ" እንዲሉ።

ፈነረ: ተወ፡ ጣለ፡ ወረወረ፡ አሽቀነጠረ፡ ርግፍ አደረገ።

ፈነረ: አደገ፡ ገጠጠ፡ ረዘመ፡ ፈነገጠ።

ፈነቀ (ነፈቀ): እነቃ፡ ሠነጠቀ፡ ተረረ።

ፈነቀለ (ፈንቀለ): ገለበጠ፡ ለየ፡ ቀረፈ፡ ስፍራ አስለቀቀ፡ የላዩን በውስጥ፡ የውስጡን በላይ አደረገ፡ የድንጋይ፣ የጓል [ገለባበጠ]

ፈነቃቀለ: ገለባበጠ፡ ቀራረፈ።

ፈነተተ (ትግ ፈንተተ): ዕልፍ አለ፡ ፈቀቀ፡ ዐጠረ፡ ፈጽሞ ዐጪር ሆነ፡ አነሰ፡ አልደርስ፡ አልበቃ አለ።

ፈነተወ (ትግ ፈንተወ): ለየ፡ ጠረገ፡ አጠራ፡ ገለጠ፡ አገለለ ፈንቶን

ፈነተወ: ከፈለ፡ ለየ፡ ተነተነ፡ ደለደለ፡ መደበ፡ ዐደለ፡ ሰጠ ፈንታን

ፈነቸረ (ፈነከረ): ወደ ኋላ ጣለ፡ ገደለ፡ ኣዶበነ።

ፈነነ (ትግ ሐባ ፈረረ): ፊን አለ።

ፈነነንና ፈረረን አስተውል።

ፈነከ): አፍነከነከ፡ አስደሰተ።

ፈነከረ (ፈከረ): ጨርሶ ገለጠ፡ ከፈተ፡ ዘረጋ።

ፈነከተ (ነከተ): ፈለጠ፡ ከፈለ፡ ገመሰ፡ ሰበረ፡ ተረረ፡ ተረከከ፡ ሠነጠቀ፡ ወለለ ራስን፡ ጨፈለቀ ዕዳሪን።

ፈነካከረ: ገላለጠ፡ ከፋፈተ፡ ዘረጋጋ።

ፈነወ: ተበሳ፡ ተቀደደ፡ ተከፈተ፡ መነጨ፡ ወጣ፡ ፈር አለ።

ፈነዘ: ጐንበስ ቀና አለ፡ ተንቀጠቀጠ፡ ተነቃነቀ ፈንዛው።

ፈነደሰ (ትግ ፈደሰ): ቈራ፡ በጣ፡ ጋረጠ፡ ሠነጠቀ፡ ፈነከተ፡ አነቃ እግርን።

ፈነደሰ: ኣስተኛ፡ አጋደመ።

ፈነደረ: ካንድ ፊት በለጠ፡ ወደ ኋላ አለ ጣራው፡ ግድግዳው።

ፈነደረን እይ።

ፈነደቀ: ፈጽሞ ተደሰተ፡ ዘለለ፡ ፈነ፡ ፈነጠዘ።

ፈነደደ: ጐነበሰ፡ ተመከተ ዠርባው።

ፈነደድ: ፈንዳዳ፡ የፈነደዶ፡ ቂጠ ትልቅ።

ፈነዳ (ፈንደወ): አለ፡ ወከከ፡ ፈረሰ፡ ተበተነ፡ ተተረተረ፡ ፈረጠ፡ ተሠነጠቀ ልቡ፡ ሆዱ፡ ዕባጩ፡ ጋኑ፡ ደንጊያው፡ ቦምቡ።

ፈነዳ: ፈካ አበባው፡ ፈርጡ፡ ጥጡ፡ እንዱሽዱሹ (፪ዜና፩፡ ፭)

ፈነጀረ: ተለየ፡ ራቀ፡ ጠመመ፡ ወጣ፡ ገባ ኾነ።

ፈነገለ (ጰንገለ): ከቅምጥ ጣለ፡ አወደቀ፡ ደበለለ፡ ገለበጠ፡ ባሪያ ሸጠ።

ፈነገጠ (ፈገጠ): ፈነረ፡ ወጣ፡ ገጠጠ የጥርስ፡ የደንጊያ፡ የብረት።

ፈነጠ: በጥቂቱ ናረ።

ፈነጠረ (ትግ ሐባ ፈንጠረ): በተነ፡ ፈነረ፡ ፈገጠ፡ ተወ፡ ለየ።

ፈነጠቀ (ፈነጠ፣ ነጠቀ): ረጪ ነዛ፣ በተነ፣ በቀላል ጣል ጣል አደረገ ዘርን፣ ቈሎን፣ ተልባን፣ ጮራን፣ ለምጽን፣ ደምን።

ፈነጠዘ: ተደሰተ፡ ደስ ተሠኘ፡ በበዓል ቀን ከመብል ከመጠጥ የተነሣ።

ፈነጠጠ (ትግ ፈንጠጠ): ቂጥኝ አወጣ፡ ወጣ፡ ተገለበጠ፡ ቈሰለ።

ፈነጣጠቀ: ረጫጨ፡ በታተነ።

ፈነጨ: ቦረቀ፡ ዘለለ፡ ተወረወረ።

ፈነጪ መነጨ፡ ፈለሰመ ፈለሰፈ፡ ፊና ሚና (የቃላት ምሳሌ)

ፈነፈነ (ትግ ሐባ ፈንፈነ): አጸየፈ፡ ጠላ፡ ነቀፈ።

ፈናጅራ: ጠማማ፡ ወልጋዳ ጥርስ።

ፈናጥ ፊናጥ አለ: ብድግ ብድግ አለ በቅሎው።

ፈናፍንታም: ፈናፍንት ያለበት፡ ባለፈናፍንት፡ የፈናፍንት ወግን፡ ወይም ርሱ ራሱ ፈናፍንት፡ ነውረኛ።

ፈናፍንት (ቶች): የተባትና የእንስት ምልክት ያለው፡ ወንድ አይሉት ሴት፡ ጕድ፡ ጢም አልባ ሴት፡ ድምጥ ዐጓጕል፡ በሰው ዘንድ የተጸየፈ፡ የተጠላ፡ የተነቀፈ።

ፈናፍንት በእንስሳትና በአራዊትም ይልቁንም በዥብ ይገኛል።

ፈንረው: ተወው፡ ጣለው።

ፈንቃይ (ዮች): የፈነቀለ፡ የሚፈነቅል፡ ገልባጭ።

ፈንቅል: ዝኒ ከማሁ፡ ትእዛዝ ሲኾን ገልብጥ ማለት ነው።

ፈንታ: የሰው ስም። "ሹም ዳኅና ፈንታ" እንዲሉ።

ፈንታ: ድርሻ፡ ዕድል፡ መክፈልት፡ ተራ፡ ምትክ፡ ለውጥ (ዘፀ፴፭፡ ፭፡ ፳፩፡ ኢሳ፶፯፡ ፮፡ ዳን፬፡ ፲፭)

ፈንታሌ: የተራራ ስም፡ ከአዋሽ ወንዝ በስተግራ የሚገኝ እሳተ ገሞራ ያቀለጠው ተራራ። ከውስጡ የተተፋው ያፈርና የደንጊያ ከሰል እበታቹ ባለው ሜዳ ላይ በሰፊው ተንጣሎ ይታያል። "እንደ ፈንታሌ ትቀልጣለኽ" እንዲሉ።

ፈንታታ፡ ፍንትት: የፈነተተ፡ ዐጪር።

ፈንቶ: የማይረባ፣ ምናምን ነገር፡ ይህ የማይባል ጥራጊ፣ ጕድፍ። "እንቶ ፈንቶ" እንዲሉ።

ፈንቶች: ድርሻዎች፡ ምትኮች፡ ለውጦች።

ፈንኦሮ: የተፈነገለ፡ ወዳቃ።

ፈንካሪ: የፈነከረ፣ የሚፈነክር፡ ገላጭ፣ ከፋች፣ ዘርጊ።

ፈንካራ: የተፈነከረ፡ ግልጥ፣ ክፍት፣ ዝርግ።

ፈንካታ: የተፈነከተ ራስ፣ ቅል፣ ደንጊያ፡ ወይም ሌላ።

ፈንካች: የፈነከተ፣ የሚፈነክት።

ፈንዛ: የበሬ ስም

ፈንዜ: ቀጪንና ጐባጣ የኾነ ረዥም ጐራዴ፡ ታጥቀውት ሲኼዱ የሚነቃነቅ።

ፈንዝ፡ ፈንዛ: የወፍ ስም፡ ዓሣ ለቃሚ፡ ነጭና ጥቍር ወፍ፡ ቀጥቃጣ፡ ዥራታም።

ፈንዝማ: የፈንዝ፡ የፈንዛ ዐይነት፡ ጭራው ነጭ የኾነ በሬ።

ፈንዞ: ዥራተ ነጭ ፈረስ።

ፈንዞ: ያሣ ስም፡ ነጭነት ከጠይምነት ያለው ዓሣ።

ፈንደሻ: የማሽላ ስም፡ ሲቈሉት የሚፈካ ማሽላ (ሐረር)

ፈንዳ ፈንዳ አለ: ፈታ ፈታ አለ፡ ደስ ተሠኘ።

ፈንዳሳ: የተፈነደሰ፡ ጋድሚያ።

ፈንዳራ: ፍንድር፡ የፈነደረ።

ፈንዳቂ: የፈነደቀ፣ የሚፈነድቅ፡ በላይ ፈንጪ ልጅ፣ ጥጃ።

ፈንዳጅ: የሚፈነድድ።

ፈንጂ: የፈነዳ፡ የሚፈነዳ፡ ጥንብ፡ ደማሚት።

ፈንጋይ (ዮች): የፈነገለ፡ የሚፈነግል፡ ጣይ፡ ባሪያ ሸያጭ።

ፈንጋይነት: ፈንጋይ መኾን።

ፈንግል: ትልቅ ጥዋ፡ ዋንጫ።

ፈንግል: ድንገት የሚገድል በሽታ፡ ባጤ ቴዎድሮስ ጊዜ የነበረ።

ፈንጠራ: የተለየ፡ ልዩ።

ፈንጠራ: ፌንጣ።

ፈንጠር አለ: ለየት አለ።

ፈንጠር: ዐፈር ሳይለብስ የቀረ የዘር ፍሬ።

ፈንጠቅ አለ: ተፈነጠቀ።

ፈንጠዝያ በጽርእ ፋንቲሲያ ይባላል፡ ዝንጕርጕር ሽልማት፡ ጌጣጌጥ ማለት ነው።

ፈንጠዝያ: ፍጹም ደስታ።

ፈንጣሪ: የፈነጠረ፣ የሚፈነጥር።

ፈንጣቂ (ዎች): የፈነጠቀ፣ የሚፈንጥቅ፡ ረጪ፣ በታኝ።

ፈንጣዥ: የሚፈነጥዝ፡ የሚደሰት፡ ተደሳች።

ፈንጣጣ (ዎች): እንደ ቂጥኝ የምታቈስል የቍስል በሽታ፡ አንድ ጊዜ ከወጣች ኹለተኛ አትመለስም።

ፈንጥረው: ፈንረው፣ ፈግጠው፣ ተወው።

ፈንጥቄ: የሰው ስም፡ የጠላትን ደም ፈንጥቅ ማለት ነው።

ፈንጪ: የፈነጩ፡ የሚፈነጭ፡ ቦራቂ፡ ዘላይ።

ፈከረ፡ ፎከረ (ፈክሮ ፈከረ፡ ተረጐመ): ሞያውን፡ ዠብዱን ገለጠ፡ ቈጠረ፡ አስረዳ፡ ደነፋ፡ ዐካኪ፡ ዘራፍ፡ ገዳይ፡ እዚህ ገዳይ አለ። ፈከረ የግእዝ፡ ፎከረ ያማርኛ ነው።

ፈከከ) (ዐረ ፈከ): አንፋከከ፡ እግሮችን አራራቀ፡ ወዲያና ወዲህ አስረገጠ፡ መጥፎ አካኼድ አስኬደ።

ፈከክ ፈከክ አለ: ተንፋከከ።

ፈከክ: የፈከከ፡ የተራራቀ።

ፈከፈከ (ፈከከ): ነተበ፡ ተሠነጠቀ፡ ተነሣ፡ ተላጠ። ከአፈከፈከ በቀር ፈከፈከ አልተለመደም።

ፈኪ: የሚፈካ፡ የሚያብብ።

ፈካ (ፈግዐ፣ ዐረ ፈኪሀ): ተከፈተ፡ ፈነዳ፡ የውስጡ በላይ ኾነ፡ አበበ።

ፈካ: ደስ ተሠኘ፡ ፈጽሞ ሣቀ።

ፈካሪ፡ ፎካሪ (ዎች): የፈከረ፡ የፎከረ፡ የሚፈክር፡ የሚፎክር፡ ግዳይ ተናጋሪ።

ፈወሰ (ፈውሶ ፈወሰ): ዐከመ፡ አዳነ፡ ኣሻረ፡ አተረፈ፡ ከሕማም ከደዌ፡ ጠገነ (ሉቃ፯፡ ፳፩፡ ፲፫፡ ፲፬) (መፈወስ ወይም ማዳን)

ፈወተ (ጥንታዊ ዐማርኛ): ጠጣ (መጠጣት)

ፈወተን አስተውል።

ፈዋሽ (ፈዋሲ): የፈወሰ፡ የሚፈውስ፡ አዳኝ፡ ሐኪም፡ ባለመድኀኒት፡ ወጌሻ (የሚፈውስ)

ፈዋሾች (ፈዋስያን): የሚፈውሱ ሐኪሞች (ሉቃ፰፡ ፵፫) (የሚፈውሱ ሐኪሞች)

ፈውሰ ቢስ: የማይፈወስ ሰው፡ ቢፈወስም በሽታው የሚመለስበት (የማይፈወስ)

ፈውስ መንፈሳዊ: የመጻፍ ስም፡ ብዙ የነፍስ አብነት የሚኾን ምክር ያለበት መጻፍ፡ የሲኖዶስ ዐይነት (ጥወ) (የመጽሐፍ ቅዱስ አይነት)

ፈውስ: ድኅነት፡ ጤና (ግብ ሐዋ፬፡ ፳፪) (ጤና ወይም ድኅነት)

ፈዘዘ: ዘነጋ፡ ቀዘዘ፡ ደነዘዘ ሰውነቱ፡ ተሰቀጠጠ፡ ተሸመቀቀ ዥማቱ (ዘፍ፴፪፡ ፳፭) (መርሳት ወይም መደንዘዝ) "ዐይኑ ፈዘዘ"፡ ደነገዘ፡ ዳፍንታም ኾነ፡ አላይ አለ (ዘካ፲፬፡ ፲፪) (የዓይን መደንዘዝ)

ፈዛዛ (ዞች): የፈዘዘ፡ ዝንጉ (የሚረሳ) "ዋዛን" ተመልከት።

ፈዛዛነት: ፈዛዛ መኾን (ዝንጉነት)

ፈዛዥ: የሚፈዝ (የሚረሳ)

ፈየተ: ቀማ፡ ነጠቀ (ግእዝ)

ፈየተ: ቀደመ፡ ተገለጠ፡ ታየ፡ ሰው ሲወለድ ራሱ ፊቱ (ዐማርኛ) መቅደም ጊዜን፡ መታየት ፊትን ያስተረጕማል። ፊት ቅሉ ከዚህ የወጣ ነው።

ፈየዘ ፌዘ) አፌዘ: አላገጠ፡ አቧለተ (ኢሳ፳፰፡ ፳፪፡ ኤር፲፱፡ ፰)

ፈየደ (ፈደየ): ረባ፡ ጠቀመ፡ አተረፈ።

ፈየጠ፡ ፌጠ): ወጣ፡ በላይ ኾነ፡ ፈጀ፡ አቃጠለ።

ፈያጅ: የፈየደ፣ የሚፈይድ፡ ጠቃሚ፡ አትራፊ።

ፈደለ (ፈዲል ፈደለ): ጣፈ፡ ለፈለፈ፡ ዋሸ፡ ቀጠፈ (መዋሸት ወይም አንድን ነገር አጋኖ መናገር)

ፈደነ (ደፈነ): አጥብቆ እሰረ፡ ወደነ፡ ቀፈደደ (አጥብቆ ማሰር)

ፈደነ: ፈዘዘ።

ፈደፈደ (ፈድፈደ): በዛ፡ ተረፈ፡ በለጠ (መብዛት ወይም መትረፍ) "ብርድ ፈደፈደኝ"፡ በዛብኝ፡ በረታብኝ (ብርዱ ሲበረታ)

ፈዳኝ (ኞች): የፈደነ፡ የሚፈድን፡ አሳሪ (የሚያስር)

ፈድፋጅ: የሚፈደፍድ፡ በዢ (የሚበዛ)

ፈጀ (ፈገ፣ ፈደየ): አቃጠለ ገደለ ጠነገደ አጠፋ ፈጸመ ጨረሰ ቻለ (ዘዳ፱፡ ፫፡ ሉቃ፲፬፡ ፳፰) (ማቃጠል፣ መግደል ወይም ማጥፋት) (ተረት): "እሳት ለፈጀው ምን ይብጀው" (በደረሰበት ጉዳት የተጎዳ ሰው) "ዐምሳ ኾነው ዐምሳ በግ ፈጁ": ጨረሱ (ሙሉ በሙሉ አጠፉ) "ለብሰሽ ፍጀው": ጨርሰው (አለባበስን በሙሉ መጠቀም) "የጫረው እሳት ፈጀው": ሰውን የሠራው ሥራ ጐዳው፡ አጠፋው (የራስ ሥራ ለራስ መጉዳት)

ፈጀታ: የፈጀች፡ የምትፈጅ፡ የምትጨርስ ሴት (የምትጨርስ ወይም የምታጠፋ ሴት)

ፈጅ: የፈጀ፡ የሚፈጅ፡ ጨራሽ ቻይ (የሚያጠፋ ወይም የሚያስጨርስ)

ፈገመ (ደበየ): ባፍ ጢም ደፋ፡ አወደቀ (በግንባሩ መደፋት)

ፈገረ (ትግ ሐባ ፈግረ): ወጣ ብቅ አለ (መውጣት ወይም መብቀል) በትግሪኛ ግን ፈገረ - ሰረቀ ማለት ነው (በትግርኛ ያለው ትርጉም)

ፈገገ (ትግ): ጐፈነነ (ማጎፈን)

ፈገገ (ፈጊግ፣ ፈገ፣ አክሞሰሰ): በጥቂቱ ሣቀ፡ ከንፈሩን ገለጠ (ፈገግ ማለት)

ፈገገ: ፊቱ ፍሙ በራ (መዝ፲፰፡ ) (መብራት)

ፈገገን: ውጋገን ብርሃነ ገጽ (የፊት ብርሃን)

ፈገግ (ፈጊግ): መፍገግ

ፈገግ አለ: ወገግ አለ በራ ገጹ ሰማዩ (በራ)

ፈገግጨፍጋጋ: የተጨፈገገ፡ ፊተ ቋጣራ።

ፈገጠ: ፈነረ ጣለ ተወ (መጣል ወይም መተው)

ፈገፈገ (ፈገገ): ፋቀ ጠረገ ለማጥራት፡ ለማሣሣት (መፋቅ ወይም ማጽዳት) ላይኛ መልክን ወይም ኹናቴን ለወጠ። "ሞረደን" "ሰነገለን" እይ (መልክን ወይም ሁኔታን መቀየር)

ፈጋሚ: የፈገመ፡ የሚፈግም፡ ደፊ (የሚደፋ)

ፈጋራ: ሬብ የኵስ መውጫ (የቁስል መውጫ)

ፈጋጊ: የፈገገ፡ የሚፈግ፡ የሚበራ (የሚያበራ)

ፈጋፈገ: ፋፋቀ ጠራረገ (መፋፋቅ)

ፈግግታ: ፍግግታ ወገግታ ሣቅ የጥርስ ብልጭታ (ፈገግታ)

ፈግጠው ፈግጪው: ጣለው፡ ጣዪው፡ ተወው፡ ተዪው መባባል፡ የባልና የሚስት አፈጋገጥ፡ አጣጣል፡ መፈገጥ (መጣል)

ፈግፋጊ: የፈገፈገ፡ የሚፈገፍግ፡ ጠራጊ (የሚያጸዳ)

ፈጠመ (ፈጸመ፣ ፈፀመ): ጨረሰ አሳለቀ ጠነገደ ቈረጠ ደመደመ ዘጋ (ማጠናቀቅ ወይም መዝጋት) "ፈጸመን" አስተውል (ተጨማሪ ቃላት)

ፈጠም: ዝኒ ከማሁ፡ የነገር፡ የሙግት መግቻ፡ ወይም ማሰሪያ፡ መቍረጫ፡ ማኅተምን፡ ፊርማን የመሰለ ሰማኒያ (የማለቂያ ወይም የማሰሪያ ምልክት)

ፈጠረ (ፈጢር ፈጠረ): ካለመኖር ወደ መኖር አመጣ አስገኘ ሠራ አደረገ ወለደ

ፈጠረቀ) አፈጠረቀ፣ አፈነዳ፣ አወጣ (የቍላ ፍሬን)

ፈጠራ: ልብ ወለድ ነገር

ፈጠነ (ፈጢን ፈጠነ): በመኼድ፣ በመሥራት፣ በመናገር፣ በማንኛውም ጒዳይ ቸኰላ ቀለጠፈ ከዝግታና ከቀስታ ፈጽሞ ተለየ፣ ራቀ።

ፈጠን (ፈጢን): መፍጠን

ፈጠን ፈጠን አለ: ቶሎ ቶሎ ኼደ ሠራ ተናገረ

ፈጠጋር: በቡልጋናና በምንጃር መካከል ያለ አገር (የቦታ ስም)

ፈጠጠ: ጐነቈለ ወጣ ጐረጠ ተጐለጐለ (መፈጠጥ ወይም መግጠጥ) "ፈጠፈጠ" ብለኸ "አፈጠፈጠን" እይ (ተጨማሪ ቃላት)

ፈጠጤ: የፈጠጥ ዐይነት፡ ወገን፡ ያውድማ ዳር ጕንቍል፡ ባቄላ፡ ዐተር፡ ሽንብራ (የፈጠጥ አይነት)

ፈጠጥ/ዘፍጣጣ: የተንዘፈጠጠ፣ ዘረጠጥ፣ ዘርጣጣ፣ ቦርጫም፣ ቀፈታም።

ፈጠጥ: ዝኒ ከማሁ (እንደ ፈጠጥ)

ፈጠፈጠ (ትግ ፈጽፈጸ፣ ፈተ ፈተ): ፈነከተ ሰባበረ በብዙ ወገን አቈሰለ ራስን

ፈጣሚ: የፈጠመ፡ የሚፈጥም፡ ጨራሽ (የሚያጠናቅቅ)

ፈጣሪ (ዎች): የፈጠረ፣ የሚፈጥር፡ አስገኝ ሠሪ አምላክ እግዜር

ፈጣሪ: ክፉ ስም ሰጪ፣ ሐሜተኛ።

ፈጣሪ: የፈጣሪ ስም።

ፈጣሪነት: ፈጣሪ መኾን አምላክነት መለኮትነት

ፈጣን (ኖች): የፈጠነ፣ የሚፈጥን (መክ፱፡ ፲፩)

ፈጣን: ቀልጣፋ ሰው።

ፈጣጣ: የፈጠጠ (የፈጠጠ) "ዐይነ ፈጣጣ" እንዲሉ (የዓይን መግጠጥ)

ፈጣጭ: የሚፈጥ፡ የሚጐርጥ (የሚፈጥጥ)

ፈጥኖ ኼደ፣ ፈጥኖ መጣ እንዲሉ።

ፈጥኖ ወጣ: ፈሰሰ (የሴት ደም)

ፈጥኖ ደራሽ: ቅዱስ ጊዮርጊስ

ፈጥኖ: ቶሎ ብሎ ቸኵሎ

ፈጥፋጭ: የፈጠፈጠ፣ የሚፈጠፍጥ፡ ፈንካች

ፈጨ ፈን እይ (ተጨማሪ ቃላት)

ፈጨ: በጥቂቱ መገለ፡ አዠ (ትንሽ መፍጨት)

ፈጨረ፡ ፋጨረ: በብርቱ ሥራ ለፋ ደከመ

ፈጨፈጪ) ፈጪጪ (ጨፈጨፈ): አንፈጨፈጨ አፈላ አወረዛ

ፈጨፈጭ: የተንፈጨፈጨ፡ የሚንፈፈጭ፡ ጨቆ የምድር እዥ

ፈጪ (ፈጻሒ): የፈጪ፡ የሚፈጭ፡ ከርታፊ ሰላቂ (የሚፈጭ) ሲበዛ "ፈጪዎች" "ፈጮች" ይላል (መክ፲፪፡ ) (የቃሉ ብዙ ቁጥር)

ፈጪ (ፈጽሐ): እኸልን ከካ፡ ከረተፈ፡ አጐረሠ፡ አደቀቀ ሸመሸመ ሰለቀ ደቈሰ ዳጠ አለዘበ አላመ ዳሰ ጣሰ (፪ሳሙ፡ ፳፪-፵፫፡ ፪ዜና፡ ፲፭፡ ፲፮) (መፍጨት ወይም መደቅደቅ)

ፈጪታ: ፈጪ ለወንድ፡ ፈጪታ ለሴት ይነገራል፡ የፈጨች፡ የምትፈጭ ማለት ነው (የቃሉ የጾታ ልዩነት)

ፈጫ (ፍጹሕ): ደቃቅ አሸዋ ጠጠር በፀሓይ ጊዜ እግርን የሚያቃጥል (በጣም የደቀቀ አሸዋ ወይም ጠጠር)

ፈጫይ (ዮች): ዝኒ ዓዲ ከማሁ። የፈይ፡ ፈጫይ አንድ ቁና እህል ፈጭታ የቁና አጋማሽ፡ ኹለት ቁና ጥሬ ፈጭታ አንድ ቁና የጕልበት ዋጋ ታገኛለችና፡ የፈይ የሚባል ይህ ነው (የፈጫይ ሥራ)

ፈጭ: ዝኒ ከማሁ። "ዐመደ ፈጭ" እንዲሉ (እንደ ፈጭ)

ፈጯጯ: መላልሶ ፈጨ፡ ከረታተፈ (ተደጋጋሚ የመፍጨት ተግባር)

ፈጸመ (ፈጽሞ ፈጸመ): ጨረሰ ከወነ ቈረጠ ደመደመ

ፈጸመ: የካህናት፡ ፈጠመ: የሕዝብ ነው።

ፈጻሚ (ሞች): የፈጸመ፡ የሚፈጽም፡ ጨራሽ "ጕዳይ ፈቃድ ፈጻሚ" እንዲሉ።

ፈጻምያነ ፈቃድ: ፈቃድ ፈጻሞች ነፋስ እሳት ውሃ

ፈጽሞ: ጨርሶ ጭራሽ "አካቶ ፈጽሞ" እንዲሉ። ንኡስ አገባብም ይኾናል።

ፈፋ (ፎች): የውሃ መኼጃ፡ መውረጃ፡ ከጕድባ ያነሰ ሸንጥሮ

ፈፋና ፈፍ፡ አፍ አንድ ዘር ናቸው፡ ኹሉም ከአፈፈ ይወጣሉ።

ፈፍ: የፊደል ስም ፈ፡ ትርጓሜው አፍ ማለት ነው።

አለ: በቍጣ ተነፈሰ፡ በሬው እፍኝቱ (በቁጣ መነፈስ) አንቀጹ "ነፋ (ነፍኀ)" ነው።

አለ: ነደደ () የፊደል ስም (ማፋፋት)

ፉሲ: ከንቱ ብላሽ

ፉሲ: ፈሰሰ

ፉር አለ: ባፍንጫው ጮኸ የጋማ ከብት ከፍራት የተነሣ።

ፉር ፉር አለ: በነፋስ ኀይል ድምፅ ሰጠ ፉርቴው።

ፉር: የበቅሎ፡ ያህያ ጕንፋን

ፉርሽ አለ: አትያዝ፡ አትቅለብ አለ፡ አሰናከለ

ፉርሽ: ያሊያዘ፡ ያልጨበጠ፡ ያላገኘ፡ ከንቱ ብላሽ እንዲሁ መና የቀረ

ፉርቃን (ዐረ): የእስላም መጽሐፍ ቁርኣን ከኦሪት ከወንጌል ተከፍሎ የወጣ።

ፉርቴ (ዎች): የመጫወቻ ስም፡ በመካከል ባለው ቀዳዳዋ ልጆች ዕጥፍ ገመድ አግብተው ግራና ቀኝ ሲዘውሯት በነፋስ ኀይል ፉር ፉር የምትል ታናሽ ጠፍጣፋ ዕንጨት፡ ቁመቷ መካከለኛ ጣት ያኸላል።

ፉሮ (ኦሮ ፉሪ): ንፍጥ የጋማ ከብት ያፍን ውስጥ በሽታ የሚያስል፡ የሚያስነጥስ።

ፉቅራ: የስላም ቃልቻ ዛር ፈረስ

ፉት (ፈወተ፡ ትግ ፋየተ): መማግ መቅመስ መጠጣት

ፉት ቢሉ ጭልጥ: ንብረቱ በጣም ያነሰ ሰው እንዲህ ይባላል።

ፉት አለ: ማገ በጥቂት ጠጣ፡ በፍጥነት አነበበ፡ ጨረሰ።

ፉት አደረገ: አማገ።

ፉትን እይ፡ ከዚህ የወጣ ነው (ከቃሉ የተገኘ)

ፉነቲ: አፍንጫ ደፍጣጣ (ፎነነ)

ፉነቲ: አፍንጫው ያጠረ ፉንጋ ወንድ ሴት

ፉነቴ: የፉነቲ ወገን፡ አፍንጫ ደፍጣጣ ቅድስና ያላት ባሪያ እርሷ ከተሰወረች በኋላ የምትለብሰው ጨርቅ ታምራት ስለ ሠራ በተረት የፉነቴ ጨርቅ ሲባል ይኖራል። () እሷም በቤቷ ውስጥ የሠራችውን መደብ ሌሊት ስትጸልይ ማርያም እዚህ ተቀመጪ ጊዮርጊስ እዚህ ሁን አቦ እዚህ ተቀመጡ እያለች ለታቦቱ ኹሉ እንዳንዱን ታድል ነበር ይላሉ።

ፉነና: ሥንጠቃ ቈረጣ

ፉን፡ ፉንን: ከንፈረ ሥንጥቅ ግመልም ፉን እየኾነ ይወለዳል።

ፉንቅ: የገደል ሳን አጣብቂኝ

ፉንታሮት: እዚህ ይግባ የማይባል ዐጕል ሰው መጥፎ ጌጥ

ፉንጋ: ፊተ ዐጪር በቅሎ አህያ ሰው ሲበዛ ፉንጎች ያሠኛል።

ፉኖ: ከንፈረ ዐጪር ሰው የጋማ ከብት

ፉካ: ውላ ቀዳዳ ታናሽ መስኮት ፉካ (ፈከከ) ዘር ነው።

ፉዲድ ፉዲድ አለ: ፋደደ (አንድ ነገር ሲንገዳገድ ወይም ወደ ኋላና ወደ ፊት ሲወዛወዝ የሚገልጽ አገላለጽ)

ፉዲድ: መፋደድ (መፋደድ)

ፉገርታ: ጐበዝ ፋጋሪ (ታታሪ)

ፉጋ: የነገድ ስም፡ በጕራጌ ክፍል ያለ ሕዝብ (የጎሳ ስም)

ፉጠራ: አሰራ ሽበባ

ፉጥ: የሰው ስም (የግል ስም)

ፉጥ: ፈጠጠ

ፉጥር: የተፎጠረ አፈ እስር ሽብብ

ፉጨታ: ዝኒ ከማሁ (ኢሳ፭፡ ፳፮) (እንደ ፉጨት)

ፉጨት (ፋጻ): እጅግ የሚያምር የትንፋሽ ዘፈን ዜማ ጥሪ (የሚያምር ፉጨት)

ፊላ: የረግረግ ዳር፡ የወንዝ አጠገብ ቅጠል፡ እንደ ችግኝ በዝቶ የሚበቅል፡ የሚፈላ

ፊላማ: የፊላ ወገን፡ ፊላ መሳይ ማለት ነው።

ፊላስ ፊላስ አለ: ፍንቅል ፍንቅል ብድግ ብድግ አለ መጋለብ ዠመረ

ፊላዊ: እፊላ ዐይነት ቀለም የገባ ቈዳ

ፊር (ትግ ሐባ ፈረረ): ፊን መውጣት የሽንት፡ የደም።

ፊር አለ: ፊን አለ ወጣ

ፊር ከዚህ ጋራ ይሰማማል።

ፊርማ (ዎች): የጽፈት ያውራ ጣት ምልክት

ፊርማ ጣሊያንኛ ነው፡ ከዐድዋ ጦርነት ወዲህ ባማርኛ ተለምዶ ይሠራበታል። ጋዜጣን እይ።

ፊቅ: በሐረርጌ አውራጃ ያለ ቀበሌ

ፊተ መጣጣ: ደረቅ ሰው ከሲታ ሴት

ፊተ ገምዳዳ: ፊቱ የተቋጠረ

ፊተ ጨምዳዳ: ፊቱ የተጨመደደ የከሳ ወይም ሽማግሌ

ፊተኛ (ኞች): የፊት በፊት ያለ የነበረ ፊት የመጣ የተወለደ በኵር ቀዳሚ ግንባር ቀደም

ፊቱ ብር አለ: ጠወለገ ከሳ

ፊቱ፡ ተሸበሸበ) ተጨማደደ።

ፊቱ ደነገጠ: ዝኒ ከማሁ።

ፊቱ ጭር አለ: በረደ ተነበዘ ሞገስ ዐጣ

ፊቱ: የርሱ ፊት።

ፊቱን ቋጠረ: ኰፈተረ

ፊቱን አስወጋ: መኖሩን አስታወቀ ፊቱን አሳየ

ፊቱን አቀና: አንጋጠጠ፣ ሰማይ ሰማይ ኣየ (ዘፍጥረት ፲፭፡ )

ፊቱን አዞረ: መለሰ ጠመዘዘ

ፊቱን አጠቈረ (ፀወገ): አከፋ አቀጯመ

ፊታውራሪ (ፊት አውራሪ): የፊት አዝማች በስተፊት ጦርነት የሚያደርግ፡ የጠላትን አገር የሚያስወርር፡ የሚያስወጋ፡ ማዕርጉ ከደጃዝማች በታች የኾነ የሻለቃ፡ ፊታውራሪ። ሲበዛ ፊታውራሪዎች ይላል።

ፊታውራሪ ተባለ: ፊታውራሪነት አገኘ ተሾመ አገር አወጣ ሻለቃ ኾነ

ፊታውራሪ: አበ ጋዝ የመንግሥት ጠቅላይ ጦር አዛዥ፡ ማዕርጉ ከራስና ከደጃዝማች በላይ፡ ከንጉሥ በታች የኾነ (፪ሳሙ፡ ፲፡ ፲፮)

ፊት (ትካት): ንኡስ አገባብ ቀድሞ አስቀድሞ ዱሮ ያለፈ ጊዜ (መክ፫፡ ፲፭) (ተረት): "ፊት የደረሰን ወፍ ይበላው።" "ፊት የተናገረን ሰው ይጠላው።" "የፊት ወዳጅ ኸን በምን ቀበርከው በሻሽ፡ የኋለኛው እንዳይሸሽ።"

ፊት (ቶች) ፈየተ ቀማ ገጽ ግንባር ካንገት በላይ ያለ መልክ፡ ገላ። (ተረት): "ከፍትፍቱ ፊቱ።" "ለውሽማ ሞት ፊት አይነጭለት።"

ፊት ለፊት: አንጻር ለአንጻር አቅጣጫ ላቅጣጫ

ፊት መመለሻ: የሹምን መልካም አስተያየት ለማግኘት የሚሰጥ ገንዘብ

ፊት መን: የጕንጭ ጫፍ የዦሮ አጠገብ

ፊት መግለጫ: እጅ መንሻ መተደያ (ማስደሰቻ)

ፊት በር: የፊት በር የስርቆሽ በር አቅጣጫ

ፊት ነሣ: ጠላ በክፉ ዐይን አየ

ፊት አሳየ: ወደደ አፈቀረ አቀረበ

ፊት: ቀድሞ፣ ዱሮ፣ ጥንት። "ሰብአ ትካት እንዲሉ።"

ፊት: በስተግንባር ያለ ስፍራ፡ የኋላ አንጻር፡ ትይዩ። "እዩ ለኤልያስ እፊቱ ወድቆ ሰገደለት።"

ፊት: በኩል ወገን "ጭነቱ ወዳንድ ፊት ዘነበለ" እንዲሉ።

ፊና: ፍና (ፈነወ) መንገድ ስፍራ በኩል ወገን አንጃ ሚና ጐራ

ፊናጥ አለ: መር አለ

ፊናጥ: ብድግ መር

ፊን (ፈነነ): ፊር መውጣት መፍሰስ

ፊን አለ: ፊር አለ ከፊኛ ወጣ

ፊን አደረገ: ፊር አደረገ በትንሽ በቀጪን ሸነ፡ አፈሰሰ

ፊን ፊን አለ: ፊር ፊር አለ

ፊንቀራ: ቅማንት ያለበት አገር

ፊኛ (ትግ ፍሒና): ሥጋዊ የሽነት ከረጢት ሥሥ ረቂቅ (ዘሌ፩፡ ፲፮)

ፊኛ ሆድ: ሆደ ጠባብ

ፊኛ: በነፋስ፡ በትንፋሽ የሚነፋ ላስቲክ የንዶድ፡ የሳሙና ዐረፋ

ፊው (አፊው፣ አፈወ፣ ፈዐወ): ፉጨት ማፋጨት (ማፋጨት)

ፊው አለ: አፋጩ በትንፋሽ ድምፁን አሰማ፡ ለመጥራት፡ ለማስጠንቀቅ (በፉጨት ድምጽ ማሰማት)

ፊደላዋሪያ (ፊደለ ሐዋርያ): ልጆች ከፊደል በኋላ የሚማሩት መዠመሪያው የዮሐንስ መልክት (፩ዮሐ፡ ፳፯) (ልጆች ፊደል ከተማሩ በኋላ የሚማሩት የመጀመሪያው የዮሐንስ መልዕክት)

ፊደል (ኢሳ፳፱፡ ፲፩): መዠመሪያ ትምርት ተቀዳሚ ጥፈት (የመጀመሪያው ትምህርት ወይም ጽሑፍ) ከአልፍ እስከ ያለ ፴፯ ኅርመት ባለ፯ ቅንጣት (የግእዝ ፊደላት ቁጥር እና ቅንጣት) ከዚሁ ደግሞ እነጐኈኰቈ ባላ፭ ቅንጣት ናቸው። "አበገደን" ተመልከት (ተጨማሪ የፊደላት አይነቶች)

ፊደል መባሉ እንደ ፊደል ስለ ተጻፈ ነው (ፊደል የተባለበት ምክንያት)

ፊደል ቈጠረ: ትምርት ዠመረ አበገደ ወይም አኡ አለ (ትምህርት መጀመር)

ፊደሎች (ፊደላት): ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች (ከሁለት በላይ የሆኑ ፊደላት)

ፊዶ (ኤፉድ): ቍምጣ ጥብቆ ሴደርያ ማጠቆ እድፈ ከል (ልብስ ወይም የአልጋ ልብስ)

ፊጋ (ኦሮ): የሚሸሽ የሚሮጥ የሚፈረጥጥ በሬ ሸሺ ሯጭ ፈርጣጭ ወንባጅ (ፈሪ ወይም የሚሮጥ)

ፊጥ (ፈየጠ): አንድ ነገር ላይ መውጣት (መውጣት)

ፊጥ አለ: ወጣ ተቀመጠ በላይ ኾነ (በላዩ ላይ መሆን)

ፊጥንና ፌጦን እይ፡ የዚህ ዘሮች ናቸው።

ፊጥኝ: የኋሊት እስራት ግርንግሪት

(ፋጸየ): አፋጩ አፉን አሞጠሞጠ በትንፋሽ ድምፅ ጮኸ፡ ዘፈነ (በፉጨት ድምጽ ማሰማት) ዛሮችም በርሷ ያፋጫሉ (ኢሳ፴፬፡ ፲፬) (አጋንንት ወይም መናፍስት ድምጽ ማሰማት)

ፋ፡ አደረገ፡ ከንበል፡ አደረገ።

ፋሌ: በአዲስ አበባ ምዕራብ ያለ ገጠር

ፋሌቅ: የሰው ስም፡ ፋሌግ

ፋሌግ (ፋሌቅ): የሰው ስም፡ የዔቦር ልጅ፡ ካዳም ፲፮ኛ ትውልድ። በዘመኑ ምድር ስለ ተከፈለች ፋሌግ ተባለ (ዘፍ፲፡ ፳፭) ዳግመኛም ገና ተወራራሾች ስለ ኾኑ በፋሌግ ፈንታ ፋሌቅ ይላል።

ፋል (ፈልፈለ): መስኖ ቦይ በግእዝ ግን ርት ተብሎ ይተረጐማል።

ፋልማ: ውሃ ገብ መሬት ፋል (የውሃ መስመር)

ፋልማ: ውሃ ገብ ወፍራም መሬት ለም የዠማ ዳር ምድር

ፋልቱ: የዕቃ ማመላለሻ ባቡር አመንዝራ ሴት

ፋመ (ፍሕመ): ጋመ በሰለ ተንደረከከ መረተ እሳት መሰለ ኾነ

ፋሚ (ፈሓሚ): የሚፍም፡ ጋሚ ከሰሌ ሀሎ ደሬ

ፋሲለደስ: ከታወቁት ሰማዕታት አንዱ፡ የጽርእ (ግሪክ) ተወላጅ።

ፋሲል: የሰው ስም፡ የጐንደር ንጉሥ። ይህ ስም የሰማዕቱ ፋሲለደስ ከፊል ነው።

ፋሲካ: ከትንሣኤ ሌሊት ሰዓት ወይም ቅዳሴ ውጭ ዠምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ያለው ስምንት ቀን

ፋሲጋ: ፋሲካ

ፋስ (ዐረ): ዕንጨት የሚፈለጥበት፡ ደንጊያ የሚጠረብበት፡ ቦለድ ምሣር ወይም መጥረቢያ የፈረንጅ ሥራ።

ፋረ (ፈሐረ): ውስጥ ውስጡን ታች ታቹን ጫረ ቈፈረ ማሰ ጐደፈረ በጥፍር፡ በዶማ።

ፋሪ (ዎች) (ፈሓሪ): የፋረ፡ የሚፍር፡ ! ቈፋሪ

ፋራ) አፋራ: ማካፋት ዠመረ ብን ብን አደረገ ዐፈር ዐፈር አሸተተ

ፋራ: የሰው የከብት ሰኰና የረገጠው ዱካ ፍለጋ አንዳንድ ሰዎች በፋራ ፈንታ ፋና ይላሉ፡ ስሕተት ነው።

ፋሬስ: የይሁዳ ልጅ፡ የዛራ መንትያ፡ ትርጓሜው ጣሽ ማለት ነው።

ፋር ፋር አደረገ: ጫር ጫር አደረገ

ፋር: ጫር

ፋርስ: በእስያ ውስጥ ያለ አገር ዛሬ ግን ኢራን ይባላል።

ፋርሶች: የፋርስ ተወላጆች።

ፋርጣ: በበጌምድር ያለ ተራራ

ፋሮ (ዎች): ዐረ እልፋእር፡ ዐይጥ እንደ ፍልፈል ምድር የሚቈፍርና እቤት ውስጥ ገብቶ ወተት የሚደፋ፡ ቅቤ የሚበላ፡ ጕሬዝማ አውሬ ጐፍላ የፋደት ወገን። እግሮቹ ዐጫጭር ናቸው፡ ቈዳውን የፈረንጅ ሴቶች እየቀጣጠሉ ይለብሱታል። በትግሪኛም አውጭ ፍሒራ ይባላል።

ፋሸረ) ፎከረ) አንፋሸረ: አንገራበደ ጕራ አበዛ

ፋሸከ (ተፈሥሐ): ፈጽሞ ደስ ተሠኘ አፍ ቂጡ ሣቀ በፍስክ ሰዓት።

ፋሸገ: ተከፈተ ተላቀቀ

ፋሽኮ: በቅል አምሳል የተሠራ ጠርሙስ በጣሊያንኛ ፊያስኮ ይባላል።

ፋሽኮ: አንኮላ (ጐንደር)

ፋሾዳ: የአገር ስም።

ፋቀ (ፈሐቀ): እድፍን፡ ችክን ከጥርስ ላይ፡ ፈገፈገ ጠረገ ለማጥራት፡ ለማሣሣት። ጠጕርን ከብራና ጭረትን ከእንሰት ከቃጫ፡ ከሳማና፡ ወይም ቅርፊትን ለየ አስወገደ አራቀ ጽፈትን አጠፋ ኀጢአትን ደመሰሰ ዕንወትን ላገ አለዘበ ሰውነትን አከሳ (ዘሌ፲፬፡ ፵፩፡ ሮሜ፲፩፡ ፳፯) (ልብን ፋቀ): አቃረ

ፋቀ) (ፈሀቀ) አፋቀ: ወደ ላይ ተነፈሰ ሕቅ ሕቅ አለ

ፋቂ (ቆች) (ፈሓቂ): የፋቀ፡ የሚፍቅ፡ ደበናንሣ ቈርበት አልፊ (ግብ ሐዋ፱፡ ፵፫፡ ፲፡ ፲፪)

ፋቂ: የጩ፣ የሚጭ፡ ጥርስ።

ፋቂ: ጥርስ ረግ።

ፋቂ: ጥርስ የሚፈግ ወይም የሚጠርግ ሰው።

ፋቂታ (ፈሓቂት): የምትፍቅ ሴት።

ፋቂነት: ፋቂ መኾን

ፋቂያ፡ ፍቄት: የብራና ገለፈት የሳንቃ፡ የንዝርት ልላጊ

ፋቃ (ፈካ): መንዶልዶያ የዦር የድልድል ፍንጭ ቀዳዳ ፉካ

ፋቅ (ፋህቅ): ሕቅታ ስርቅ ስርቅታ

ፋቅ (ፍሒቅ): መፋቅ መራብ

ፋቅ አደረገ: በፍጥነት ፋቀ፡ ራበ

ፋታ: ፈንታ ዕረፍት ትንፋሽ

ፋታን እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።

ፋቶ (ፈታ): ባዘቶ

ፋነነ (ትግ ፋሕነነ): ኰራ ተነሣ ቀና ተቀሰረ ቆመ ጭራውን ለበሰ ሮጠ ፈረጠጠ (፪ሳሙ፮፡ )

ፋነነ: ሳይታዘዝ ባሳቡ ዘመተ።

ፋና (ፓና): ወፍራም ጧፍ (ኢሳ ፷፪፡ ፩፡ ዮሐ፲፰፡ )

ፋና ወጊ: በቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥት የተሰቀለ ፋናን (ሻማን) በዘንግ እየወጋ (እየለኰሰ) የሚያበራ የመብራት ሹም

ፋና: ጭፍን፡ የተጨፈነ፡ ዐይን ወይም አሞራ ሰው (፪ጴጥ፡ ፩፡ ፱) "ዐይንም የለኝ፣ ጨፋና ነኝ እንዲሉ ልጆች"

ፋናኝ: የፋነነ፡ የሚፋንን፡ ሯጭ ፈርጣጣ

ፋንታ: ዝኒ ከማሁ ለፈንታ።

ፋንታዬ: የሰው ስም፡ የኔ ፋንታ ድርሻዬ ማለት ነው። ለሴትም ይነገራል።

ፋንድያ: ደረቅ የሰው ዐር (ሕዝ፬፡ ፲፪፡ ፲፭)

ፋንዶ ፋንድያ (ዎች): የጋማ ከብት ዙስ የሜዳ አህያን የመሰሉ ጋማ ያላቸው የዱር እንስሶች ኹሉ ፋንዶ ይጥላሉ (ሚል፪፡ )

ፋኖ (ዎች): አለቃ የሌለው ዘማች በፈቃዱ የዘመተ ወያኔ ጦር ጠማሽ

ፋኖ: ወዶ ዘማች

ፋኖ: የግስ ስም፡ ጠሞረ፡ ተቤተ የሚል አንቀጽ።

ፋኖስ (ሶች): ከብርጭቆና ከመስታዋት፡ ከነጭ ስኒ የተሠራ፡ ዘይት፡ ቅባኑግ፡ ጋዝ፡ ነፍት፡ ኤሌትሪክ ማብሪያ የመቅረዝና የቀንዲል ዐይነት። የጣራ፡ የግድግዳ፡ የመንገድ ፋኖስ እንዲሉ። ፓና የግእዝ፡ ፋና ፋኖስ ያማርኛ (ዮሐ፲፰፡ )

ፋኖስ: መብራት ማብሪያ ፋና

ፋይዳ ቢስ: ረበ ቢስ ያገኘው ፋይዳ መጥፎ የኾነ።

ፋይዳ: ረብ ጥቅም ትርፍ

ፋይድ (ግእዝ ፋውድ): መከራ ሥቃይ ፍዳ ውርደት ርግማን

ፋደሸ) አፋደሸ፣ በሰው ነገር ገባ፣ አጐበጐበ (በሌላ ሰው ጉዳይ ጣልቃ መግባት)

ፋደት (ቶች): ግማታም ክርፋታም አውሬ መልከ ጥርኝ ዥራተ ጐፍላ (የአውሬ ዓይነት) ኹለተኛም ቀፎ ስለሚደፋ ዐራጅ ይባላል (የአውሬው ገጽታ) "ዐረደን" እይ።

ፋደት: (ፋደት)

ፋደደ: ደፋ ደፋ አለ ዥብኛ ኼደ (ወደ አንድ ጎን መሄድ)

ፋዳ: ዐንገታም ዓሣ (አንገት ያለው ዓሣ)

ፋገ (ፈአገ): ወጣ ፈሰሰ ፍጉ ተቃጠለ ጐደፈ መሬቱ (መፍሰስ ወይም መቃጠል) "ፈአገ" ጥንታዊ ዐማርኛ ነው።

ፋገ: ሰፋ ሰፊ ኾነ በዛ ቍስሉ (ቁስል ሲሰፋ)

ፋገረ (ዕብ ፋጋር ደከመ): እንደ ውሻ ረ፡ ጐደፈረ ፋረ ማሰ ቈፈረ ለፋ ደከመ (መድከም ወይም መጣጣር)

ፋገረን ተመልከት።

ፋጕሎ (ዎች): የሠም ዝቃጭ ወይም አተላ ባንድነት የተወቀጠ ድብልብል ከዳና፡ ሰፈፍ፡ ምጣድ ማሠሻ (የሠም ዝቃጭ)

ፋጕሎ: የማይረባ ሰው እዚህ ይግባ የማይባል (የማይረባ ሰው)

ፋጕሎ: የበሰበሰ ግንድ (የበሰበሰ ግንድ)ፋጋ (ትግ ፈግአ፡ ከፈለ፡ ፋግኣ): የሸክላ፡ የቅል ስባሪ፡ የግንድ ፍንካች፡ ወይም ቀራፎ፡ ጐድጓዳ ዕንጨት (የሸክላ ስባሪ)

ፋጋ: ከላይ አንድ ከታች መንታ የኾነ ፈሳሽ ዠማ (የፍሳሽ ዓይነት)

ፋጋሪ: የፋገረ፡ የሚፋግር፡ ሰፊ፡ ደካሚ (የሚደክም)

ፋጡማ: የሴት ስም፡ የእስላሞች ነቢይ የመሐመድ ልጅ (የሴት ስም)

ፋጪ ጦር: (የጦር ዓይነት)

ፋጮ: ዳመጦ ሳይባዘት የሚፈተል (ያልተስተካከለ ክር)

ፋፊ: የሚፋፋ፡ የሚዳብር።

ፋፋ (ትግ ፈሕፍሐ): መገመገ፡ ወፈረ፡ ዳበረ፡ ደነደነ፡ ገላው አማረ፡ እንደ ልቡ ጡት ስለ ጠባ፡ ስለ መገመገ።

ፋፋቀ: ደመሳሰሰ፡ አጠፋፋ፡ መላልሶ ላገ፡ አለዛዘሰ።

ፋፋቴ (ዎች): የተንፋጁ፡ የሚንሿሿ፡ ሿሿቴ፡ ኀይለኛ የገደል፡ የተዳፋት ፈሳሽ።

ፋፋቴ: ወተታም ላም።

ፋፍ)፡ ቧቧ) አንፋፋ: አንቧቧ፡ በኀይል፡ በብዛት ዐለሰ፡ አወረደ፡ አፈሰሰ ወተትን፡ ውሃን።

ፌልቲ: ፍልስጥኤማዊ፡ የዳዊት ጭፍራ (ኪ፡ ወ፡፡ ክ)

ፌራ (ግእዝ): ቸነፈር፡ ወረርሽኝ፡ ተላላፊ የተስቦ በሽታ።

ፌሾ: ቶሎ የሚደርስ ገብስ።

ፌቆ (ዎች): የሠሥና፣ የምዳቋ አይነት የዱር ፍየል፡ ከተራራና ከገደል ላይ የምትዘል፣ የምትወረወር እንስሳ፡ መልከ ዳለቻ (ባና)፡ ዦሮዎቿ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው። ተባቱም እንስቱም ፌቆ ይባላል። መጽሐፍ ግን በሽኮኮ ፈንታ ፌቆ ይላል፡ ስሕተት ነው። (ዘዳ፲፬፡ ፯፡ መዝ፻፬፡ ፪፡ ፲፰)

ፌንጣ (ጦች): ወዲያው ወዲያው፡ ቶሎ ቶሎ የምትዘል ተንቀሳቃሽ። (ተረት): ፌንጣ ብትቈጣ እግሯን ጥላ ኼደች። ከወገኑ የተለየ አንበጣ ይኾናል ፌንጣ። ተባቱንና እንስቱን ለመለየት።

ፌንጣዋ: ፌንጣዪቱ፡ ያች ፌንጣ።

ፌንጣው: ፌንጣ።

ፌዘኛ (ኞች): ለግጠኛ፡ ቧልተኛ፡ ፌዝ ወዳድ፡ ዋዘኛ (ምሳ፲፫፡ ፩፡ ኢሳ፳፱፡ ፳)

ፌዝ: ለግጥ፡ ቧልት፡ ዋዛ (ኤር፲፱፡ ፰)

ፌዝ: ቧልት (ፈየዘ) (ፌዝ ወይም ቀልድ)

ፌጠኛ (ኞች): ቀልደኛ፡ ፌዘኛ።

ፌጥ: ቀልድ፡ ለግጥ፡ ፌዝ።

ፌጦ: የቅመም ስም፡ ሲቀምሱት የሚለበልብ፡ የሚፋጅ፡ የሚያንገበግብ ፍሬ፡ መድኀኒትነት ያለው (የቅመም አይነት) ፌጦ (ፈየጠ) ዘር ነው (የፌጦ አመጣጥ)

ፍሕሶ: ያበባ ስም፡ በበልግ ጊዜ የሚታይ ቀይ አበባ፡ የሬት ዘር ጒተናማ (የአበባ ስም) "ጐሚትን" ተመልከት፡ ፍሕሶ ግእዝኛ ነው (የአበባው ዓይነት)

ፍለማ: ዝኒ ከማሁ።

ፍለቃ: ቀደዳ፡ ሥንጠቃ።

ፍለጋ: መፈለግ፡ ለማግኘት። ዛሬ ማታ ከብቶች ስለ ጠፉ ፍለጋ ኼጄ ነበር።

ፍለጋ: እግር የረገጠው፡ የጫማ፡ የሰኰና ዱካ፡ ፋራ፡ ምልከት (ዘፍ፴፯፡ ፲፯፡ መዝ፳፭፡ ፬፡ ኢሳ፰፡ ፲፬፡ ኤር፶፪፡ ፰) በግእዝ አሠር ይባላል።

ፍሉስ (ዐረ): ገንዘብ ካንዱ ወደ ሌላው የሚፈልስ፡ የሚዛወር።

ፍላሎት: ዝኒ ከማሁ ለፍላት።

ፍላሽ: ልውጥ ብረት፡ ኹለተኛ የተሠራ፡ የታደሰ የብር ጌጥ።

ፍላቂ: የፈሰሰ፡ ፈሳሽ፡ የውሃ፡ የጠላ፡ የወተት ጠብታ ከላይ ካናት የወረደ። የልጃገረዲቱ ጥርስ የርጎ ፍላቂ ይመስላል።

ፍላቃ: የተዳጠ፡ የተደፈጠጠ።

ፍላት (ፍልሐት): ሙቀት፡ ትኵሳት፡ መፍላት፡ ፍልነት (ኢሳ፩፡ ፴፩)

ፍላት: ግለት።

ፍላጎት (ቶች): መፍቅድ፡ ተፈላጊ ነገር፡ ጕዳይ።

ፍላጭ: የፍልጥ ሥንጣሪ። (ያጥንት ፍላጭ የሥጋ ቍራጭ): ወንድም፡ ቅርብ ዘመድ (፪ሳሙ ፭፡ ፮፩)

ፍላጻ (ፈለጸ): ጫፉ ስለትና ሹለት ያለው ዐጪር የብረት ቍራ፡ የቀድሞ ሰዎች በንወት ጫፍ አዋደው በቀስት እየነደፉ የሚወረውሩት ባለመርዝ የጦር መሣሪያ፡ የበዳ ጸብት (ዘካ፱፡ ፲፬፡ ኤፌ፮፡ ፲፯) በግእዝ ሐጽ ይባላል።

ፍላጻ: የቅኔ አገባብ ስም፡ ነጠላና ድርብ።

ፍላጾች: ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች (ኢሳ፲፫፡ ፲፰)

ፍል (ፍሉሕ): የፈላ፡ የተፍለቀለቀ።

ፍል ውሃ: ሙቅ፡ ትኵስ፡ ንፍር ውሃ፡ የቤት፡ የበረሓ።

ፍል: ችግኝ።

ፍል: አተንክ፡ ሙቀት፡ ሐሩር።

ፍልማት: የፈለማ ኹኔታ።

ፍልም: የተፈለመ፡ የተመታ፡ የቈሰለ።

ፍልሰታ: በነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ከመቃብር ተነሥታ ወደ ሰማይ መውጣቷ፡ የመውጣቷ፡ የማረጓ በዓል (ፍልሰታ ለማርያም)

ፍልሰት: መነቀል፡ መውጣት፡ ስደት፡ ፍለስ።

ፍልሰፋ (ፍልሳፌ): የጥበብ ምርመራ፡ ጥልቅ ረቂቅ ሐሳብ።

ፍልስ አለ: ፍንቅል አለ።

ፍልስ ፍልስ አለ: ንቅል ንቅል አለ፡ ተነቃነቀ፡ ተወዛወዘ።

ፍልስ: የተነቀለ፡ የተፈነቀለ፡ ንቅል፡ ፍንቅል፡ ጥርስ፡ ደንጊያ፡ ጕቶ።

ፍልስልሱ ወጣ: ፈጽሞ ፈለሰ፡ ሥሩ ታየ።

ፍልስልስ: ንቅልቅል፡ ፍንቅልቅልም።

ፍልስጣ (እምከንቱ ውስተ ከንቱ): ከብላሽ ወደ ብላሽ ማለት ነው፡ ሊቃውንትም እኩይ ፍልስጣ ጸሓፌ ተምያን ይሉታል።

ፍልስጣ: የሰይጣን ስም፡ ሰው የሠራውን ኀጢአት በየቀኑ የሚጽፍ አሳጪ ጋኔን።

ፍልስፍ (ፍልሱፍ): የፈለሰፈ።

ፍልስፍ: የተፈለሰፈ፡ የፍልስፍና ሥራ።

ፍልስፍና: ፈላስፋነት።

ፍልቀቃ: የመፈልቀቅ ሥራ፡ ብተና፡ ልየታ።

ፍልቃቂ: ዝኒ ከማሁ ለፍልቅቅ፡ የተለየ፡ የተከፈለ፡ ልዩ ክፍል። ያጤ ካሌብ ልጅ ዘእስራኤል የወርቅ ፍልቃቂ ይመስል ነበር።

ፍልቅ አለ: ፍስስ አለ።

ፍልቅ አደረገ: ፍስስ አደረገ።

ፍልቅ: የተፈለቀ፡ የተቀደደ፡ ቅድ፡ ሥንጥቅ።

ፍልቅ: የፈለቀ ምንጭ።

ፍልቅልቅ አለ: ተፍለቀለቀ።

ፍልቅልቅ: የተፍለቀለቀ፡ የሚፍለቀለቅ፡ ብዙ ምንጭ በያለበት፡ በብዙ ወገን የሚፈላ።

ፍልቅልቅታ: የመብረቅ ብልጭልጭታ፡ ብርቅርቅታ።

ፍልቅልቅታ: ፍልቅልቅ ማለት።

ፍልቅቅ አለ: በጥቂቱ ሣቀ፡ ጥርሱን ገለጠ።

ፍልቅቅ: የተፈለቀቀ፡ የተበተነ፡ ፍሬው ያልወጣ ጥጥ፡ ብትን። የላላ፡ የተከፈተ እግር፡ ብረት፡ ልል፡ ክፍት።

ፍልክልክ አለ: ተፍለከለከ።

ፍልክልክ: የተፍለከለከ፡ ውንጅር።

ፍልኳ: ሞላላ የገንዳ ታንኳ። የፍልኳ ምስጢር ላይኛነት ነው።

ፍልግ (ፍልቅ): የተፈለገ፡ የተሻ፡ የተከፈለ።

ፍልጠት: መለየት፡ ልየታ፡ ልዩነት።

ፍልጠት: እኩሌታ፡ ራስ ምታት፡ የራስን ግማሽ ለይቶ የሚያም።

ፍልጥ (ጦች) (ፍሉጥ): የተፈለጠ፡ የተሠነጠቀ ዕንጨት። (ተረት): የሺ ፍልጥ ማሰሪያው ልጥ

ፍልጥ አለ: ሥንጥቅ፡ ፍንክት አለ፡ ተፈለጠ።

ፍልጥልጥ አለ: ተፈላለጠ።

ፍልጥልጥ: የተፈላለጠ፡ ፍንክትክት።

ፍልጹት (ፍላጹት): የገዲ ዐይነት አሞራ፡ እንደ ፍላጻ የምትወረወር፡ የምትበር፡ ጥፍረ ፍላጻ ሲላ፡ ወይም ሌላ።

ፍልፈላ: ፍርፈራ፡ ስርሰራ፡ ነደላ፡ ቅፍቀፋ፡ መፈልፈል።

ፍልፈል (ሎች): ምድር የሚምስ፡ የሚፈረፍር፡ የሚነድል፡ ዐፈር የሚቈልል፡ ጥርሳም፡ የዱር ዐይጥ፡ ትልቅ ባለጠጕር (ኢሳ፪፡ ፳)

ፍልፋይ (ዮች): የንቡጥ ገለባ።

ፍልፍሉ: የወንድ ስም፡ ሉ አባትን ያስተረጕማል።

ፍልፍሌ: የፍልፍል ወገን፡ የኔ ፍልፍል ማለት ነው፡ የወንድና የሴት ስም ይኾናል።

ፍልፍል አለ: ተፈለፈለ፡ አማረበት።

ፍልፍል: የተፈለፈለ፡ ቅርጽ፡ ብስ፡ ነዳላ፡ እሸት፡ ጫጩት፡ ዕንጨት።

ፍልፍሏ: የሴት ስም፡ ሏ እናትን ያስተረጕማል።

ፍማም: ባለፍም፡ ወይራ፡ ግራር፡ ፍም የሚወርደው።

ፍም (ሞች) (ፍሕም): የእሳት ምርት፡ ቍልል (ዮሐ፳፩፡ ፱)

ፍም ጫሪ (ፍንጫሪ): ከቤተ ልሔም ፍም የሚጭር ዲያቆን፡ ፍሬ ሰሞነኛ፡ ከሰሞነኞች ፭ኛው ቀዳሽ። (የፍንጫሪ): በደጀ ሰላም ለፍም ጫሪ የሚሰጥ እንጀራ፡ የዳቦ ጕዝጓዝ፡ የተላኪ ወግ አበል።

ፍሳሽ (ሾች): ቤት ያፈሰሰው ውሃ።

ፍሳሽ: ከስፍር የተንጠባጠበ እኸል፡ ወይም ሌላ ነገር።

ፍስ: የነገር ጭብጥ፡ በዳኛ ፊት የፈሰሰ፡ የሚፈስ።

ፍስ: የፈሰሰ፡ የቀለጠ፡ የነጠረ ወርቅና ብር።

ፍስ: የፈሰሰ፡ ፈሰሰ።

ፍሥሓ: ደስታ።

ፍሥሕ: የአይሁድ ፋሲካ።

ፍስስ አለ: ፈሰሰ።

ፍስስ አደረገ: አፈሰሰ።

ፍስክ (ፍሥሕ): የተፈሰከ፡ ብሎት ሥጋና ቅቤ የሚበላበት ቀን።

ፍስጥቅ (ጵስጥቂስ፡ ዐል): የሽቱ ስም፡ ሽቱ።

ፍረማ: ምልከታ።

ፍረድ: በይን (ሚክ፮፡ ፩)

ፍሪት: እጅግ ታናሽ፡ ወይም ጥቂት የኾነች። "አንድ ፍሪት" እንዲሉ።

ፍሪዳ (ዶች): ለመታረድ ከመንጋ መካከል የተለየ በሬ፡ የሥጋ ከብት፡ ሰንጋ፡ ገች። (ተረት): " ያሉት እንግዳ እራቱ ፍሪዳ" (ግጥም): "ነፍሴ ለሥጋ ስትሣሺ ፍሪዳ መጣልሽ፡ እኔ በመሣሌ ምነው መሣቅሽ፡ ዘውዲቱ ምኒልክ ፍሪዳ አለብሽ (አገኘኹ እንግዳ)"

ፍራ ኣልባ ኾነ: እኸሉ።

ፍራሽ (ሾች): ዐረ ፈርሽ)፡ በውስጡ ጠጕር፡ ጥጥ፡ ቃጫ፡ አበባ ያለበት፡ በሰው ቁመት ልክ የተሰፋ ከረጢት፡ መደላድል፡ ምቹ መኝታ፡ የሚደላ።

ፍራሽ: ከጣራ፡ ከግድግዳ፡ ከግንብ የፈረሰ ዕንጨት፡ ደንጊያ። "የቤት ፍራሽ እንዲሉ (መዝ፻፪፡ ፲፬፡ ፻፵፬፡ ፲፬) ሲበዛ ፍራሾች ይላል (ኢሳ፲፯፡ ፱) "

ፍራት (ፍርሃ): ትእዛዝ አንቀጽ፡ "ሰውዮ ይህችን ሴት ፍራት" [ማለት]

ፍራት (ፍርሀት): መፍራት፡ ሥጋት፡ ጥርጥር። "ፍራት የናላ ነው፡ ከቁም ይጥላል"

ፍራት አልባ: አለፍራት የሚኖር፡ ብሄሞት (ኢዮ፵፩፡ ፳፭)

ፍራት ፍራት አለው: ባር ባር አለው፡ ፈጽሞ ፈራ።

ፍራት: ሥጋት፡ ፈራ።

ፍራት: የቍስል ስም፡ በልጆች ራስ ላይ የሚወጣ ክፉ ቍስል፡ ሲያዩት ፍራትን የሚያመጣ።

ፍራቻ: ዝኒ ከማሁ ፍራት

ፍራንስ፡ ፍራንክ፡ ፈረንጅኛ፡ ፈረንስ፡ ፈረንሳይ አማርኛ። ወንድና ሴትን ለመለየት [ያገለግላሉ]

ፍራንክ (ፍራንስ): የገንዘብ ስም፡ በወርቅና በብር ፈንታ የሚገበይበት የፈረንሳይ መንግሥት የወረቀት፡ የናስ፡ የኒኬል ገንዘብ። ካ፲፱፻፴፮ .. ወዲህ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ በስሕተት የመንግሥቱን ገንዘብ ፲ሩን ብር ፓውንድ አላዱን ሽሊንግ ፩ዱን ብር ሽሊንግ ሩቡን ስሙኒ እያለ እንደሚጠራው፡ ዝርዝሩንም መሐለቅ መሐለቅ በማለት ፈንታ ፍራንክ ፍራንክ ይለዋል።

ፍራጣ: ጥሬ ገንዘብ።

ፍራፍሬ: የፍሬ ፍሬ፡ ብዙ ዐይነት ፍሬ፡ ውጥንቅጥ።

ፍሬ (ዎች): የማንኛውም ዕንጨትና ተክል ዘር፡ ከሥር ወይም ከጫፍ የሚገኝ ክብ፡ ሞላላ፡ ጠፍጣፋ፡ የሣር፡ የቅጠል፡ የእኸል፡ የቅመም ቅንጣት፡ ያውሬ ቡችላ፡ የእንስሳ እንቦሳ፡ የአሞራ፡ የወፍ ጫጩት፡ የሰው ልጅ። (ተረት): "የልጅ ነገር ኹለት ፍሬ፡ አንዱ ብስል፡ አንዱ ጥሬ"

ፍሬ ሰሞነኛ: ከእሑድ (ቅዳሴ ውጭ) እስከ እሑድ ሙሉ ሳምንት ከቤተ ክሲያን የማይለይ፡ የማይታጣ፡ ቍልፍ (መክፈቻ) ያዥ፡ ካ፬ቱ ሰሞነኞች አስቀድሞ ወደ ቤተ ልሔም ይመጣና የሚላክ (ኅብስተ ቍርባን የሚያዘጋጅ)፡ ዋና ሰሞነኛ፡ መሧዕት እየሠራ መሶበ ወርቅ የሚሸከም፡ መብራት ያዥ።

ፍሬ ሰው: ቁም ነገራም፡ ውለኛ።

ፍሬ ቅዳሴ: በየበዓሉ እየተለዋወጠ በቅዳሴ ጓዝ ውስጥ እየገባ የሚነገር ዋና ቅዳሴ፡ ሐዋርያት፡ የእስክንድርያ፡ የአንጾኪያ፡ የቍስጥንጥንያ ሊቃነ ጳጳሳት፡ የቂሳርያው ባስልዮስ፡ የኢትዮጵያ ሊቃውንት በየጊዜው የደረሱት ፲፬ ቅዳሴ።

ፍሬ ቢስ: ዐረማሞ።

ፍሬ ቢስ: ከንቱ፡ ብላሽ ሰው፡ ቁም ነገር የሌለው።

ፍሬ ቢስ: ፍሬው የማይበላ ዕፅ።

ፍሬ ነገር: የነገር ዋና አርእስት።

ፍሬ ከርሥ: የሆድ ፍሬ፡ ልጅ ኹኖ የሚወለድ የአባት ዘር።

ፍሬ ግብር: ዋና፡ ዐይነተኛ ግብር፡ ዓሥራት።

ፍሬ ፈርስኪ: የማይረባ፡ ፈሎ የሌለው። "ያቶ እከሌ ነገር ፍሬ ፈርስኪ ነው" እንዲሉ። ግእዛዊ ዝርዝር ነው፡ የፈርስሽ ፍሬ ያሠኛል። በፈርስ ውስጥ የተገኘ ፍሬ እንዳይረባ ይህም እንደዚያ ነው። ዳግመኛም በግእዝ ፍሬ ከርሥኪ የተባለውን ማይምን ፍሬ ፈርስኪ ይላል።

ፍሬ: ቍላ፡ ቈለጥ።

ፍሬ: በወጥ ውስጥ ያለ ሥጋ።

ፍሬምናጦስ: የከሣቴ ብርሃን ሰላማ ጥንታዊ ስም፡ ግሪኮች ፍሩሜንቴዎስ ይሉታል።

ፍሬው ክብ እንክብል የኾነ ጣፋጭ ተክል: (ምሳሌ ፳፭፥ ፲፩። መኃልየ መኃልይ ፪፡ ) በግእዝ፡ ኮል ይባላል።

ፍሬው የሚበላ ዛፍ: ኮምበልን ይመልከቱ።

ፍሬያማ: ባለፍሬ፡ ብዙ ፍሬ የሚሰጥ መሬት።

ፍሬያም: ዝኒ ከማሁ።

ፍርም: የተጻፈ፡ የተፈረመ ውል፡ ደብዳቤ።

ፍርምርም: የተፍረመረመ፡ ትጉህ።

ፍርምባ፡ ፍርንባ: የእንስሳትና የአራዊት ደረት።

ፍርምባ: የሥጋ ስም፡ የቅዱስ ከብት ደረት ሥጋ (ዘፀ፳፱፡ ፳፮፡ ፳፯) በግእዝ ተላዕ ይባላል።

ፍርስ አለ: ፈረሰ።

ፍርስ: ዝኒ ከማሁ።

ፍርስራሽ (ሾች): ዝኒ ከማሁ ለፍርስ።

ፍርስርስ አለ: ብትንትን አለ።

ፍርስርስ: የፈራረሰ፡ ብትንትን።

ፍርሻ: መፍረስ። በግእዝ ፍርሰት ይባላል።

ፍርቀቃ: ፍንቀላ፡ ሥንጠቃ።

ፍርቃ ማለት ፍልጡን ያሳያል።

ፍርቃ: በበጌምድር ክፍል ያለ አገር።

ፍርቃ: አባሎ።

ፍርቅ ጸያፍ: አለደንቡ የተጻፈ፡ የተነገረ የቅኔ አገባብ፡ ተሳቢ ኹኖ ከሳቢው፡ ቅጽልም ኹኖ ከባለቤት የራቀ ማለት ነው።

ፍርቅ: የተፈረቀቀ፡ የራቀ፡ ፍንቅል፡ ሥንጥቅ።

ፍርቅ: ግማሽ፡ እኩሌታ፡ በትግሪኛ ፍርቂ ይባላል።

ፍርቅርቅ: የተፍረቀረቀ፡ ስብርብር፡ ንፍርቅርቅ።

ፍርኑስ: የሴት ስም።

ፍርንስ አለ: ትኝት አለ፡ ተፈረነሰ።

ፍርንትት: ንፍፊት፡ የጕያ ዕብጠት።

ፍርንችት (ትግ): ቍላ፡ ቈለጥ።

ፍርንድስ: ወፍራም ሰው።

ፍርኵታ (ፈረከሰ): የተቦረቦረ ዋሻ፡ ግንድ፡ ንቃቃት፡ ጐሬ።

ፍርኵታ: የዕጨ ዮሐንስ ገዳም በመንዝ ክፍል ያለ [ስፍራ]

ፍርክስ አለ: ድቅቅ አለ።

ፍርክስ: ዝኒ ከማሁ ፈርካሳ

ፍርክስክስ አለ: ስብርብር አለ።

ፍርክስክስ: የተፈረካከሰ።

ፍርክርካም: ባለፍርክርክ።

ፍርክርክ አለ: ሽርፍርፍ አለ።

ፍርክርክ: የተፍረከረከ፡ ሽርፍርፍ፡ ቅርፍርፍ።

ፍርክርክነት: ቅርፍርፍነት።

ፍርዝ (ዐረ): ሰንጠረዥ።

ፍርዝ: በዳርቻ ያለ፡ የቆመ የሰንጠረዥ መጫወቻ፡ የንግሥት ተምሳሊት።

ፍርዝዝ አለ: ተንፈረዘዘ።

ፍርዝዝ: ቅብንን።

ፍርደት: ፍርጃ፡ መፈረድ።

ፍርድ ለበሰ: ሕግን፡ ደንብን፡ ወግን፡ ልማድን ተከተለ፡ የተፈረደበትን ፍርድ ተቀበለ።

ፍርድ ቤት: ፈራጆች፡ ዳኞች፡ ወንበሮች ፍርድ የሚያድሉበት ቤት።

ፍርድ ዐደለ): በየነ፣ ፈረደ።

ፍርድ: ብይን፡ ፍት (ሚክ፮፡ ፪)

ፍርዶ ገምድል: አድላዊ፡ ጕቦኛ ዳኛ፡ ፍርድን የሚገመድል።

ፍርጃ: ድንገተኛ አደጋ፡ ከሰማይ የታዘዘ፡ ምክንያቱ ያልታወቀ።

ፍርግርግ: የተፍረገረገ፡ ቅዝምዝም፡ ውዝግዝግ።

ፍርግጥ አለ: ተንፈራገጠ።

ፍርግጥ: ዝኒ ከማሁ ፈርጋጣ

ፍርጠጣ: ሩጫ፡ ግልቢያ፡ ሽሽት፡ ኵብለላ።

ፍርጣጣ: የዛፍ ስም (ፊልክስዩስ ገጽ )

ፍርጥ (ፍሩጽ): የፈረጠ፡ የመገለ።

ፍርጥ አለ: ፈረጠ።

ፍርጥ ፍርጥ አለ: መላልሶ ፈረጠ።

ፍርጥም አለ: ፈረጠመ።

ፍርጥም: ዝኒ ከማሁ፡ ጥርንቅ።

ፍርጥርጥ አለ: ተፍረጠረጠ።

ፍርጥርጥ: የተፍረጠረጠ፡ ድፍጥፍጥ።

ፍርፈራ: ፍልፈላ፡ ሽርሸራ፡ ምሰት፡ ቍፈራ።

ፍርፋሪ (ሮች): የእንጀራ፡ የዳቦ ድቃቂ (ሉቃ፲፮፡ ፳፩) በግእዝ ፍርፍር ይባላል። "ለጐበዝ ሰንጋ ፈረስ፡ ለፈሪ ፍርፋሪ" እንዲሉ ልጆች [ይባላል]

ፍርፋሪ ጥሬ፡ ፍርፍር ቅጽል መኾኑን አስተውል።

ፍርፋሪት: ጥቃቅኒት።

ፍርፍር አለ: ተንፈራፈረ፡ ወፍኛ ተንቀሳቀሰ።

ፍርፍር አለ: ተፈረፈረ፡ ድቅቅ አለ።

ፍርፍር: የተፈረፈረ፡ የደቀቀ።

ፍርፍርት: ድርጭት (ግእዝ)

ፍሽካ ነፋ: ፍሽካ አስጮኸ፡ በፍሽካ አፋጫ ጠራ።

ፍሽካ: ስለ ድንገተኛ ጥሪ ማጫ፡ ታናሽ ብረት። ጣሊያኖች ፊስኪዮ ይሉታል።

ፍሽካና፡ ፍንሽካና: ፍጹም ደስታ። ምእላድ ፲ን ስሯጽ ነው።

ፍሽጊያ: አፍ ከፈታ፡ የዕንጥስታ ዋዜማ፡ የፀነሰችንና ያልፀነሰችን እንስሳ ማወቂያ።

ፍቀት (ፍሕቀት): ጽፈትን የማጥፋት፡ የመደምሰስ ሥራ።

ፍቁር: የተፈቀረ፡ የተወደደ። ይህ ቃል ግእዝ ሲኾን ባማርኛም ይነገራል። መሰለ ብለኸ ምስለን እይ።

ፍቅ (ፍሑቅ): የተፋቀ፡ ልዝብ።

ፍቅ (ፍቁዕ): የተፈቃ፡ ብጥ፡ ሥንጥቅ፡ ትፍትፍ።

ፍቅረኛ: ሰው ወዳድ፡ ፍቅር ዐዋቂ፡ ሰላማዊ።

ፍቅሩ ጥኑ: ጭጐጐት፣ የጥጥ ፍንድ የሚያካክል ነጭ የእንጨት አበባ፡ ልብስንና ጠጕርን ከያዘ የማይለቅ። ዳግመኛም የካህን ቂም ይባላል።

ፍቅሩ: እንደ ፍቅሬ ያለ ከፊለ ስም።

ፍቅሩ: የርሱ ፍቅር።

ፍቅሬ ግንብ: ባንኮበር የሚገኝ ቀበሌ።

ፍቅሬ: የሽቱ ስም፡ ፍቅሬ የሚባል ሰው መዠመሪያ የሼጠው ሽቱ።

ፍቅሬ: የኔ ፍቅር።

ፍቅሬ: የክርስትና ከፊለ ስም።

ፍቅር (ፍቁር): ወዳጅ። "እከሌና እከሌ ፍቅር ናቸው"

ፍቅር: ውድ፡ ሰላም፡ ስምም። (ተረት): "ሆዳም ሰው ፍቅር አያውቅም"

ፍቅታት (ፍቅዐት): ስለት ያለፈበት፡ የሰው ፊት ሰንበር፡ ቍርታት፡ ብጥታት፡ ትፍትፋት፡ የዘር መለያ ቅርጽ።

ፍቆሽ: ዝኒ ከማሁ።

ፍተራ፡ ውጠራ።

ፍተሻ፡ ብርበራ፡ ምርመራ፡ ቅንቀና።

ፍተታ (ፍታቴ)፡ ቈረሳ፡ ገመሳ፡ ትንተና።

ፍተጋ: ወቀጣ፡ ሽክሸካ፡ ዐወዳ።

ፍቱ ርቱ ሥላሴ: ፍርዱ ቅን (ቀጥታ) የኾነ ሥላሴ። በግእዝ ሲነገር ዘፍትሑ ርቱዕ፡ ርቱዐ ፍትሕ ያሠኛል።

ፍቱን፡ የተፈተነ፡ የተመረመረ፡ አብነት፡ ገቢር፡ ኹነኛ፡ ዋና፡ መድኀኒት፡ ል፡ ለይኩን።

ፍታል (ትግ)፡ የቤት ፈትል።

ፍታቴ (ጥተ) መፈተት (ጥፈ) መፈተት፡ ቈረሳ፡ ፍተታ፡ የቅዱስ፡ ቍርባን፡ (ግእዝ)

ፍታት (ፍትሓ): ልቀቃት፡ ስደዳት። (ግጥም): "ምን ያሉ ቄስ ናቸው ተዝካር የለመዱ፡ አስታርቁኝ ብላቸው ፍታት ብለው ኼዱ። "

ፍታት (ፍትሐት): የሙታን ጸሎት፡ ትርጓሜው ከኀጢአት ማሰሪያ መፍታት፡ መፈታት። (የድኻ ፍታት): ዘራዳም ግባተ መሬት። (ጓዘ እና ዐረፈን መላን ተመልከት።) (የቁም ፍታት): ሳይሞቱ መፈታት፡ በሕይወት ሳሉ ተዝካር ማውጣት።

ፍታች (ፍት)፡ የዳቦ፡ የንጀራ፡ ቍራሽ፡ አፍ፡ የሚመጥነው።

ፍታነገሥት (ፍትሐ ነገሥት): የመጻፍ ስም፡ ትልቁ ቈስጠንጢኖስ ያስጣፈው ባለ፪ ክፍል መንፈሳዊና ሥጋዊ መጻፍ፡ እንደ ጊዜው የክርስቲያን ነገሥታት የሚፈርዱት ፍርድ በውስጡ ስለ ተጻፈ ፍትሐ ነገሥት ተባለ።

ፍታውጪ (ፍት አወጪ): እውነት ፈራጅ።

ፍታይ፡ የጥጥ፡ የፈትል ውጤት።

ፍታጎ: ዐጪር ጕጮ ሣር።

ፍት (ፍትሕ): ፍርድ፡ ብይን።

ፍት ርት (ፍትሕ ርትዕ): ቅን ፍርድ።

ፍትሐ ብሔር: የመጻፍ ስም፡ ሥጋዊ የአገር ፍርድ ማለት ነው።

ፍትሕ: ፍርድ፡ ፈታ።

ፍትል፡ የተፈተለ፡ የተጠመረ፡ የተገመደ። በግእዝ፡ "ፍቱል" ይባላል።

ፍትልት፡ የተጠመዘዘች፡ የተጠመረች፡ ደረቅ ምራን፡ የግንባር ቈዳ።

ፍትልትል፡ የተፍተለተለ፡ ቀስ፡ ብሎ፡ ኻያጅ፡ ጕትት።

ፍትር፡ አደረገ፡ ውጥር፡ አደረገ።

ፍትር፡ የተፈተረ፡ የታነቀ፡ የተጨነቀ፡ ውጥር።

ፍትሽ፡ የተፈተሸ፡ የተበረበረ፡ የተመረመረ፡ ብርብር፡ ምርምር።

ፍትት (ፍቱት)፡ የተፈተተ፡ የተቈረሰ፡ ጕርማጅ፡ ዳቦ።

ፍትወተ ሥጋ: የሥጋ መሻት፡ ሥጋዊ የዘር ፈቃድ (ዘፍ፲፰፡ ፲፪)

ፍትወተኛ: ፍትወት ያለበት፡ የበዛበት፡ ባለፍትወት ሰው፡ ፍየል።

ፍትወት (ፈተወ): ያልተሰጠውን መሻት፡ መፈለግ፡ መውደድ።

ፍትጋት: ፍተጋ።

ፍትግ: የተፈተገ፡ ልጦ ጕርዶ የወጣለት፡ ቈሎ፡ ዳቦ የሚኾን ስንዴ፡ ገብስ። በግእዝ ልቱም ይባላል።

ፍትፈታ፡ የመፈትፈት፡ ሥራ።

ፍትፍት፡ የተፈተፈተ፡ ደቃቅ፡ እንጀራ፡ በውሃ፡ የራሰ። (ተረት)፡ ከፍትፍቱ፡ ፊቱ። ማቶትን፡ እይ። (ያቃቢት፡ ፍትፍት)፡ ጠላና፡ ወጥ፡ ያነሰው፡ ደረቅ።

ፍቹ: ዝኒ ከማሁ፡ ፍራሽ፡ ወና (ዘኍ፡ ፴፫፡ ፶፪)

ፍቼ (ኦሮ ሠሥ): ከደብረ ሊባኖስ በስተደቡብ አፋፍ ላይ ያለ ቀበሌ።

ፍቼና ተፋ ባማርኛ ይተባበራሉ። (ግጥም): "በላኹ በላኹና ሆዴን ጨነቀው፡ እንደ ምን አድርጌ ተፍቼ ላውጣው (ባሻ ባሪያው) "

ፍች (ቾች)፡ ፍቱሕ: የተፈታ፡ ባድማ፡ ባዶ፡ ጠፍ (ሕዝ፳፱፡ ፲፡ ፱፡ ኢሳ፶፪፡ ፱)

ፍች፡ ፍቺ: መፍታት፡ መፈታት። "በሙሴ ሕግ ሚስቱን የሚፈታ የፍችዋን መጻፍ ይሰጣታል። "

ፍች: ትርጓሜ።

ፍናቋ: ጕድጓድ፡ የግንብ ንቃቃት፡ ብስ፡ ነዳላ።

ፍናዋተ ቢስ: ልክስክስ፡ ምናምንቴ ሰው።

ፍናዋቱ ጠፋ: ጠፉ ቢል በቀና የባላገር ባህል ነው። የሰውየው ትዳሩ፡ ንብረቱ፡ ዘሩ፡ ትውልዱ ታጣ ያሠኛል (፪ነገ ፲፡ ፯፲፬)

ፍናዋት (ፈነወ): መንገዶች፡ ጥርጊያዎች፡ ጐዳናዎች፡ መዳረሻዎች።

ፍናዋት: ዐመሎች፡ ሥራዎች፡ ፍለጋዎች።

ፍናዋትን ተመልከት፡ የፍና ብዢ ነው።

ፍናጅ: የባሪያ ስም፡ የውላጅ ልጅ፡ ፪ኛ ባሪያ።

ፍንሽካና: ፍጹም ደስታ (ፋሸከ)

ፍንቀላ: ግልበጣ፡ ቀረፋ።

ፍንቃይ: የመሬት፡ የምርጊት፡ የቍስል ልጣጭ፡ ቅራፊ።

ፍንቅል አለ: ግልብጥ አለ፡ ተፈነቀለ።

ፍንቅል: ዝኒ ከማሁ፡ የተገለበጠ፡ ግልብጥ።

ፍንቅልቅል አለ: ቅርፍርፍ አለ፡ ተፈነቃቀለ።

ፍንቅልቅል: የተፈነቃቀለ፡ ግልብጥብጥ።

ፍንትት አለ: ዕጥር አለ።

ፍንትው አለ: ቅልጥጥ አለ፡ ግልጥ ሆነ።

ፍንትው: የተጠረገ፡ የተገለጠ፡ ግልጥ፡ ጥሩ ስፍራ፡ ቤት።

ፍንችር አለ: ውድቅ፡ ሙትት፡ ድብን አለ (ጥፈ)

ፍንችር: የተፈነቸረ፡ የሞተ።

ፍንከራ: ገለጣ፡ ከፈታ።

ፍንከታ: ፈለጣ፣ ገመሳ፣ ጭፍለቃ።

ፍንካች (ቾች): ግማሽ የባቄላ ክክ፡ ሎሚ ከኹለት።

ፍንክር: ዝኒ ከማሁ (ኅፍረተ ብእሲት)

ፍንክርክር አለ: ተፈነካከረ።

ፍንክርክር: የተፈነካከረ፡ ግልጥልጥ፣ ክፍትፍት።

ፍንክት አለ: ፍልጥ፣ ክፍል አለ፡ ተፈነከተ።

ፍንክት: ዝኒ ከማሁ፡ ስብር።

ፍንክትክት: የተፈነካከተ፡ የተሰባበረ፡ ፍልጥልጥ፡ ስብርብር።

ፍንክች አለ: ተደፈረ፡ ተነካ፡ ተበገረ።

ፍንክች አይልም: አይደፈርም፡ አይበገርም፡ የብረት ቈሎ፡ የደንጊያ ንፍሮ ነው።

ፍንክች: ንክች። "ፍንክች ያባ ቢላዋ ልጅ" እንዲሉ።

ፍንክንክ: የተፍነከነከ፡ የተደሰተ፡ ደስ።

ፍንዝንዝ: የተፍነዘነዘ፡ ቅንዝንዝ፡ ክንፍንፍ፡ ክልፍልፍ።

ፍንደቃ: ፍጹም ደስታ፡ ዝላይ።

ፍንዱቅ: የንግድ ቤት፡ መብል፣ መጠጥ ያለበት (ግእዝ)

ፍንዳታ: ሥንጥቃት፡ ፍካት፡ ወከክ ማለት።

ፍንድ: (ዶች)፡ በዛፉ ላይ የፈነዳ ጥጥ ከነፍሬው።

ፍንድስ አለ: ትኝት አለ፡ ተፈነደሰ።

ፍንድስ: ዝኒ ከማሁ፡ የተኛ።

ፍንድስድስ አለ: ተፈነዳደሰ፡ መረሬው ተረከዙ።

ፍንድስድስ: የተፈነዳደሰ፡ ሥንጥቅጥቅ፡ ፍንክትክት።

ፍንድር አለ: ፈነደረ።

ፍንድቅ አለ: ጭራሽ ተደሰተ፡ ፍንጥዝ አለ።

ፍንድቅ: የፈነደቀ፡ ደስ ያለው፡ የተደሰተ።

ፍንድድ: ጕንብስ፡ የኳስ ጨዋታ።

ፍንጃል ዐረብኛ ነው፡ በግእዝ ፍያል ይባላል (መሳ፭፡ ፳፭)

ፍንጃል: እግራም ጥዋ፣ ትልቅ ስኒ፡ የሻይ፣ የቡና፣ የወተት መጠጫ።

ፍንጃሎች: ጥዎች፣ ስኒዎች (ዘፀ፳፭፡ ፳፱)

ፍንጅ: ኹለት የሰንሰለት ቀለበት።

ፍንጅር: የፈነጀረ፡ የጠመመ።

ፍንጅርጅር: ውልግድግድ፡ የተራራቀ፡ ላይና ታች የኾነ።

ፍንገላ: ግልበጣ፡ ጥሎሽ።

ፍንጋ: ብላሽ (ግእዝ)

ፍንግል አለ: ውድቅ አለ፡ ተፈነገለ።

ፍንግል: ዝኒ ከማሁ የተጣለ፡ ውድቅ።

ፍንግልግል አለ: ተፈነጋገለ።

ፍንግልግል: የተፈነጋገለ።

ፍንጠቃ: የመፈንጠቅ ሥራ፡ ብተና።

ፍንጠዛ: የመፈንጠዝ ሥራ።

ፍንጣሪ: የተፈነጠረ፡ ታናሽ የፍም ቍራጭ፡ ስባሪ - ፍንካች። "የእሳት፣ የደንጊያ፣ የቦምብ ፍንጣሪ" እንዲሉ።

ፍንጣቂ: የውሃ፣ የደም፣ የወጥ፣ የቀለም፣ የዘይት፣ የቅባት ቅንጣት፣ ጠብታ።

ፍንጥር አለ: ተፈነጠረ።

ፍንጥር ያሠኘው ርሱን ለመግዛት ወጪ የኾነው ብር ነው።

ፍንጥር: ዝኒ ከማሁ።

ፍንጥርጌ: በጠራ ውስጥ ያለ ቀበሌ፡ "የፍንጥር ምድር" ማለት ነው።

ፍንጥርጥር አለ: ብትንትን አለ፡ ተፈነጣጠረ።

ፍንጥርጥር: የተፈነጣጠረ፡ ብትንትን።

ፍንጥቅ አለ: ብትን አለ። "ጨረሯ ፍንጥቅ አለች" እንዲሉ።

ፍንጥቅ: የተፈነጠቀ፣ የተረጨ፣ ብትን።

ፍንጥቅጣቂ: የተፈነጣጠቀ፡ ብትንትን።

ፍንጥቅጥቅ አለ: ብትንትን አለ፡ ተፈነጣጠቀ።

ፍንጥቅጥቅ: ዝኒ ከማሁ፡ ነጠብጣብ።

ፍንጥዝ አለ: ፈነጠዘ።

ፍንጥዝ: የፈነጠዘ፡ የተደሰተ።

ፍንጥጣ: ፈጋራ፣ ሬብ እበትና ኵስ መውጫ፣ መቀመጫ።

ፍንጥጫ: የመፈናጠጥ ኹኔታ፡ አቀማመጥ።

ፍንጨታ: ዝላይ፡ ቡረቃ።

ፍንጫሪ: ፍም ጫሪ (ፋመ)

ፍንጭ (ጮች): የቀፎ፡ ያፍን፡ የጡት፡ የእስኪት፡ የምንጭ፡ የዕባጭ አፍ፡ ቀዳዳ።

ፍንጭት (ቶች): በጥርስና በጥርስ መካከል ያለ ክፍት፡ ባዶ፡ ጥርሰ ፍንጭት እንዲሉ።

ፍንጭት: ሞርስ።

ፍንጭት: ክፍት (ፈነጨ)

ፍንፍን አለ: ተፈናፈነ፡ ተፍጨረጨረ፡ ወዲያና ወዲህ አለ፡ ተጋተረ።

ፍንፍን: የተፈናፈነ።

ፍከራ፡ ፉከራ: ዘራፍ ማለት፡ ድንፋታ፡ ዠብዱ ቈጠራ።

ፍካሬ: ትርጓሜ። ከዳዊት አርእስት አንደኛው መዠመሪያው።

ፍካሬየስ (ፍካሬ ኢየሱስ): ጌታችን ለሐዋርያት የነገራቸው ትንቢት።

ፍካት: የማሽላ ቈሎ ኹኔታ፡ ፍንዳታ፡ የፊት ወለልታ።

ፍክ: የፈካ ቈሎ፡ የጥጥ ፍንድ አበባ።

ፍክክር፡ ፉክክር: ውድድር፡ ክርክር። (ተረት): የፍክክር በር ሳይዘጋ ዐደር

ፍወሳ (ፍዋሴ): የመፈወስ ሥራ (የመፈወስ ተግባር)

ፍዝ: ዝኒ ከማሁ ለፈዛዛ (እንደ ፈዛዛ)

ፍዝ: የዜማ ምልክት ስም (የዜማ ምልክት) "ዝን" ተመልከት።

ፍዝዝ አለ: ፈዘዘ (ፈዘዘ)

ፍየለ ፈጅ: የንጨት ስም፡ በወይናደጋ የሚበቅል ዕንጨት፡ መቍጠሪያ የሚኾን፡ ቀጥቅጠው ሲያደርቁት እንደ ክትክታ ይበራል። ፍየለ ፈጅ መባሉ ቅጠሉን ፍየል ስለማይበላው ይመስላል።

ፍየሉ: ፍየል፡ የርሱ ፍየል።

ፍየላፍ (ፍየል አፍ): አፈኛ፡ ለፍላፊ፡ ቀባጣሪ ሰው።

ፍየል (ሎች): ከበዳ ፍየል የተለየ የቤት እንስሳ ከብት። (ተረት): ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ

ፍየል ፈለግ እንዲሉ። በግእዝ ግን ወንዝ ማለት ነው።

ፍየል ፈለግ: የማኅደር፡ የመጣፍ መደጐሻ፡ ግፉ የፍየል ጥፍር የመሰለ ዕንወት።

ፍየሏ: የርሷ ፍየል። (ሜዳ ፍየል): የዱር፡ የበረሓ፡ የሜዳ ፍየል በያይነቱ።

ፍየሏ: ፍየሊቱ፡ ያች ፍየል።

ፍየሏን እንደ በግ: ብልጧን እንደ ሞኝ ማለት ነው።

ፍየዳ: የመርባት፡ የመጥቀም ሥራ።

ፍዳ (ፈደየ): የክፉ ብድራት፡ ፍርድ፡ ቅጣት (ቅጣት ወይም ፍርድ)

ፍዳውን አየ: መከራውን ተቀበለ፡ ብድሩን አገኘ (ቅጣቱን መቀበል)

ፍድል: አካለ ደጓሳ፡ ጕልሕ ሰው (ቀጭን ወይም ደካማ ሰው)

ፍድፈዳ (ፍድፋዴ): ብዛት፡ ብዙነት፡ ብልጫ፡ ላቂያ (ብዛት ወይም ትርፍ)

ፍድፋጅ: ተረፍ፡ ትራፊ፡ ርዝራዥ፡ የዶቄት ወይም የሌላ (ትርፍ)

ፍጅ: ጨርስ፡ ፈጽም (ጨርስ)

ፍጅብኝ: ጠበቃ፡ ነገረ ፈጅ (ጠበቃ) "ቀናው ፍጅልኝ" ሲኾን "ፍጅብኝ" ይባላል (የቃላት አጠቃቀም ልዩነት)

ፍጅት (ፍድየት): ጭቅጭቅ፡ ንዝንዝ፡ ጩኸት፡ ውዝግብ (ግብ ሐዋ፲፪፡ ፲፰) (ጭቅጭቅ)

ፍጅት አደረገ: ጭርስ፡ ጥንግድ አደረገ (ማጠናቀቅ ወይም ማጥፋት)

ፍጆታ: የሙግት፡ የክርክር ፈንታ፡ ተራ፡ ፈረቃ (የክርክር ወይም የሙግት ድርሻ)

ፍጋም: ፍገ ብዙ፡ ባለፍግ (ብዙ ፍግ ያለው)

ፍግ (ፈገ): የእበት፡ የፋንዶ፡ የበጠጥ፡ የጠቦት ደረቅ ድቃቂ (ደረቅ እበት)

ፍግ: የፈገገ፡ የሣቀ፡ ጥቂት የበራ (ትንሽ የበራ)

ፍግም አለ: ድፍት፡ ሙትት፡ ድብን አለ (ሙሉ በሙሉ መውደቅ)

ፍግም: የተፈገመ፡ የተደፋ፡ የወደቀ፡ ውድቅ (የወደቀ)

ፍግምግም አለ: ርግድግድ አለ (ኤር፳፫፡ ፲፪) (መወዛወዝ)

ፍግምግም: የተፍገመገመ፡ እንግድግድ፡ ርግድግድ (የተወዛወዘ)

ፍግምግምታ (ትንታኔ): የመንገድገድ ኹኔታ (የመንገዳገድ ሁኔታ)

ፍግርግር አለ: ውስብስብ አለ፡ ተፍገረገረ (መወሳሰብ)

ፍግርግር: የተፍገረገረ፡ ስያፍ፡ ማገር፡ ውስብስብ፡ መናኛ ዐጥር (የተወሳሰበ ወይም አጥር)

ፍግርግር: ጫታሪ፡ ተጣጣሪ (ታታሪ)

ፍግግ አለ: ሣቅ አለ (ፈገግ አለ)

ፍግግ ፍግግ አለ: ሣቅ ሣቅ አለ (ብዙ ሲስቅ)

ፍግፈጋ: ፍቀት፡ ጠረጋ (የማፋቅ ተግባር)

ፍግፍጋት: ፍቆሽ (የመፋቅ ተግባር)

ፍግፍግ: የተፈገፈገ (የተፈገፈገ)

ፍጡር (ሮች): የተፈጠረ፡ የፈጣሪ ሥራ።

ፍጡርነት: ፍጡር መኾን።

ፍጥ: የመፍጠጥ ኹኔታ (የመፈጠጥ ሁኔታ)

ፍጥ: ፈጣጣ፡ ፈጠጤ (እንደ ፈጣጣ)

ፍጥም (ፍጹም፣ ፍፁም): የተፈጠመ፡ ያለቀ፡ የተወረሰ፡ ዝግ (ፍጹም)

ፍጥም አለ: ዕልቅ፡ ጭርስ አለ (ሙሉ በሙሉ ማለቅ)

ፍጥም: ቀጠሮ፡ ባጤ ይሙቱ የተወሰነ (የተወሰነ ቀጠሮ) "ፍጥም አፍራሽ፡ ቤተ ክሲያን ተኳሽ" እንዲሉ (የቃል ኪዳን ጠባቂ)

ፍጥምጥም አለ: ፈጽሞ አለቀ፡ ተከናወነ (ሙሉ በሙሉ ማለቅ)

ፍጥምጥም: ዝኒ ከማሁ (እንደ ፍጥጥም)

ፍጥሞ: ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ራእዩን በደሴቱ የጻፈበት አገር (የቦታ ስም)

ፍጥረታለም (ፍጥረተ ዓለም): በዓለም የሚኖር ማንኛውም ፍጥረት ኹሉ።

ፍጥረት (ቶች): ሰማይና ምድር፡ መሬት፡ ውሃ፡ ነፋስ፡ እሳት፡ ብርሃን፡ ጨለማ፡ መልአክ፡ ዘር፡ ተክል፡ ዕንጨት፡ ፀሓይ፡ ጨረቃ፡ ኮከብ፡ እንስሳ፡ አውሬ፡ ወፍ፡ ሰው።

ፍጥረት: ተፈጥሮ፡ መፈጠር።

ፍጥሪያ: የመፍጠር ሥራ፣ አድራጎት።

ፍጥርቅ አለ: ፍንድት፡ ውጥት አለ።

ፍጥርቅ: የተፈጠረቀ፡ የፈነዳ።

ፍጥርጥር ቢል በቀና ነበር

ፍጥርጥር: ዐመል፡ ጠባይ፡ ብጤት።

ፍጥነት: ችኰላ።

ፍጥነት: ዝኒ ከማሁ።

ፍጥኒያ: ችኰላ፣ ጥድፊያ።

ፍጥጥ አለ: ጕርጥ አለ፡ ፈጠጠ (መፈጠጥ)

ፍጥጥም: የቃል፡ የማተብ ማሰሪያ፡ የጋብቻ ውል (የጋብቻ ውል)

ፍጭርጭር: የተፍጨረጨረ፡ ትጉ፡ ታታሪ፡ ተትኰርኳሪ።

ፍጭጭ አለ: ዝኒ ከማሁ (እንደ ፍጭጭ አለ)

ፍጸማ: ድምደማ።

ፍጹም (ሞች): የተፈጸመ፡ ሕጸጽ፡ ጕድለት፡ ነውር፡ እንከን የሌለበት፡ ንጹሕ፡ ቅዱስ፡ ጻድቅ፡ የበቃ፡ ከንጽሐ ልቡና ማዕርግ የደረሰ፡ እንደ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያለ መንፈሳዊ ግሑሥ።

ፍጹምነት (ፍጽምና): ፍጹም መኾን፡ ብቃት፡ ቅድስና።

ፍጻሜ: መጨረሻ፡ ምጽአት (ማቴ፳፬፡ ፲፬)

ፍጽም (ፍጹም): ያለቀ፡ የተጨረሰ።

ፍጽም አለ: ዕልቅ፡ ጭርስ አለ።

ፎለለ: አብዝቶ ተጫወተ፡ በጕልሕ ድምፅ እንዳገኘ ተናገረ።

ፎለፎል (ፈልፈለ): ቦሬ፡ ገር ሰው፡ ሸክ የሌለበት፡ ጨዋታው ደስ የሚያሠኝ።

ፎላይ (ዮች): የፎለለ፡ የሚፎልል፡ ተጫዋች።

ፎሌ (ኦሮ): ሲያውቅ አበድ፡ አመንዝራ፡ ወንድን ይዞ የሚደበድብ።

ፎሌ: አፈ ሰፊ፡ ኣንኮላ።

ፎረፎር: ሸቀን፡ ደረቅ ወዝ፡ ፎከት።

ፎሸፎሸ) አንፎሸፎሸ: ወሬ አስነዛ፡ አቀለለ።

ፎሸፎሽ፡ ፎሽፋሻ: የተንፎሸፎሸ፡ የሚንፎሸፎሽ፡ ወሬኛ፡ ቀላል፡ አባ ንፋው።

ፎቀቀ)፡ አንፋቀቀ: በቂጥና በእጅ አስኬደ።

ፎቃቃ (ቆች): ዝኒ ከማሁ፡ የተንፋቀቀ፡ አዋሻኪ።

ፎተተ፡ ነገር፡ አበዛ፡ አንጁቀቀ።

ፎታች፡ የፎተተ፡ የሚፎትት፡ አንፋቃቂ።

ፎቶ ግራፍ: ጽሕፈተ ብርሃን፡ የብርሃን ጽፈት (ሥዕል)

ፎቶ: ብርሃን፡ ጸዳል።

ፎቶና ግራፍ የጽርእ ልሳን ነው።

ፎነቀ: ዝኒ ከማሁ።

ፎነነ: ላይኛ ከንፈርን ሠነጠቀ፡ አፍንጫን ቈረጠ፡ ጐረደ፡ አሳጠረ።

ፎናቃ: ፉንጋ፡ ከንፈረ ሥንጥቅ።

ፎናና: አፍንጫ ጐራዳ። ባለቅኔዎች ፋጌ ይሉታል።

ፎናኝ (ኞች): የፎነነ፡ የሚፎንን፡ ሠንጣቂ፡ ቈራጭ።

ፎከተ: ባ፭ ጣት ዐካከ፡ ፋቀ አካልን።

ፎከተ: ዐወደ፡ ፈተገ፡ ዐጪር ሣርን።

ፎከታም (ሞች): ፎከት ያለበት፡ የበዛበት፡ ባለፎከት።

ፎከት: ነጭ ዕከክ፡ እብቅ መሳይ፡ በግእዝ ኣበቅ ይባላል።

ፎከት: የዕከክ ትቢያ፡ የገላ ፍቄት፡ ጕማጮ ሣር።

ፎከፎከ) አንፎከፎከ: አብዝቶ ሸነ፡ ኣንዠቀዠቀ።

ፎካች: የፎከተ፡ የሚፎክት፡ ዐካኪ፡ ዐፋቂ።

ፎደፎደ) አንፎደፎደ፣ አንበደበደ፣ አስፈራ፣ አንቀጠቀጠ።

ፎደፎድ: እንብድብድ፡ እንቅጥቅጥ (ፍርሃት)

ፎገራ: በበጌምድር ግዛት ውስጥ ያለ አገር፡ ከብት የሚረባበት (የቦታ ስም)

ፎጠረ (ጠፈረ): የከብትን አፍ አሰረ፡ ሸበበ።

ፎጠና: ፈጥኖ የሚያድግ፣ የሚሠራ ወጣት፡ ለሴትም ይኾናል።

ፎጢማ: ታናሽ ዋሽንት።

ፎጣ: የፊት መጥረጊያ፡ የእጅ ማበሻ፡ የገሳ ማምጠጫ፡ ባለዘርፍ ነጠላ፡ ጠጕራም (ፎጣ) ባረብኛ ፉጣ ይባላል (የአረብኛ ስም)

ፎጣሪ: የፎጠረ፣ የሚፎጥር፡ አሳሪ።

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ