ደ : ፬ኛ ፊደል በአበገደ። በፊደልነት ስሙ "ድል(ን)ት"፡ በቍጥርነት "ደ፬" ይባላል።
ደ : የዘጠተ ተወራራሽ። (ማስረጃ): ደፈቀ፣ ዘፈቀ፡ ጨቦደ፣ በጠ፡ ቦደሰ፣ በጠሰ፡ ለደፈ፣ ለጠፈ፡ ገረደፈ፣ ከረተፈ።
ደ፡ ፍልቅ፡ አለ፡ እጅግ፡ አማረች።
ደኃራ (ደኃራይ): በቀዳማ አንጻር፡ በስተኋላ ያለ የኮርቻ ጫፍ።
ደኅነኛ: ጤናማ፣ ባለጤና፣ ጤነኛ።
ደኅነኞች: ጤነኞች።
ደኅኒት: ደጓ፣ ማለፊያዋ።
ደኅና (ዳኅነ): (ንኡስ አገባብ) ጤና፣ በጎ፣ ሰላም። "ከኀላፊና ከትንቢት፣ ከትእዛዝ ከነባር አንቀጽ አስቀድሞ እየገባ ይነገራል"።
ደኅና (ድኅነ፣ ዳኅና): (ቅጽል) ደግ፣ ማለፊያ (የጠባይ፣ የግብር፣ የሰውነት)።
ደኅና መጣ: በሰላም፣ በጤና፣ በሕይወት።
ደኅና ሰንብት: ከእሑድ እስከ ቅዳሜ፡ ወይም ብዙ ሳምንት። ረፈደን፣ ዋለን፣ መሸን፣ ዐደረን፣ ከረመን፣ ሰነበተን በየስፍራው ተመልከት።
ደኅና ሰው: እውነተኛ፣ ደግ፣ ቅን፣ ትሑት፡ እሰው ጠባይ የማይደርስ።
ደኅና ቀን: ዝናም የሌለበት፣ ወለል ያለ ሰዓት።
ደኅና ቀን: የሰላም፣ የደስታ፣ የጥጋብ ጊዜ፣ ዘመን።
ደኅና ነው: እሱ ደኅና ነው፡ ምንም የለበት።
ደኅና ነገር: ማለፊያ ወሬ።
ደኅና አምሽ: (ከምሽቱ ፲፪ እስከ ሌሊቱ ፫ ሰዓት)።
ደኅና አርፍድ: (ከጧቱ ፲፪ እስከ ፫ ሰዓት)።
ደኅና ዕደር: (ከማታ እስከ ጧት)።
ደኅና ክረም: ከዕለት እስካመት።
ደኅና ኹን: ለብዙ ጊዜ።
ደኅና ዋል: (ከጧት እስከ ማታ)።
ደኅና ያሳድርኸ: ዝኒ ከማሁ።
ደኅና ያውልኸ: ዝኒ ከማሁ።
ደኅና ገባ: ያለችግር ያለሁከት ወደ ቤቱ ተመለሰ።
ደኅኔ: የሰው ስም፡ የደኅና ማለት ነው።
ደኅንነት: ደኅና መኾን (ጢንነት) (ዘዳ ፳፯:፯፣ ፪ቆሮ ፯:፲)።
ደኅኖች: ደጎች፣ ማለፊያዎች።
ደለለ (ዐረ): መራ፣ አመለከተ፣ ጠቈመ፣ አሳየ፡ ሸያጭና ገዢን አስማማ።
ደለለ (ደልሎ ደለለ): ጸልሎ ጸለለ፡ አሞኘ፣ አታለለ፣ ሸነገለ፡ የማያደርገውን አደርጋለኹ አለ (መዝ ፲፰:፵፬፣ ኤር ፬:፴)። (ተረት): "ዶሮን ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት"።
ደለለ: ጫነ፣ ከመረ፡ ሸፈነ፣ አለበሰ፣ አጠለቀ።
ደለለኝ: የሰው ስም። "አሞኘኝ፣ ሸነገለኝ" ማለት ነው።
ደለላም (ደለልማ): ደለል ያለበት፣ የበዛበት (ባለዶለል ስፍራ)።
ደለል: ያፈር፣ የደንጊያ፣ ያሸዋ፣ የሣር፣ የንጨት ክምር። "ጐርፉ በቡቃያው ላይ ደለል ነበት"።
ደለመ (ጸልመ): ጠለመ፣ ጨለመ፡ ወደመ፣ ጠፋ፣ ተሰወረ (የዐይን፣ የመብራት፣ የስለት፣ የትዳር)።
ደለመጠ (ደመጠ ለመጠ): ሥጋ ያዘ፣ ወፈረ (ከቅጥነት፣ ከክሳት ራቀ)፡ ተጠረነቀ፣ ፈረጠመ።
ደለማ: ጭለማ፣ ስወራ። "ሳይሰማ በደለማ" እንዲሉ።
ደለሰ (ደለዘ): ቅቤን በራስ ላይ አድርጎ ላከከ፣ አብዝቶ ቀባ፣ መረገ። "ትግሬ ግን ደለሰን ሰበሰበ ይለዋል"። ደለፈሰን እይ፡ የዚህ ዘር ነው።
ደለሠ: ቀባ (ደለሰ)።
ደለሽ: የእኸል ማነባበሪያ (ከሰፌድ የሚበልጥ ሥሥ ምርጊት)።
ደለቀ (ደሊቅ ደለቀ): መታ፣ ደሰቀ፣ ጐሰመ፣ አስጮኸ (የከበሮ፣ የዠርባ፣ የደረት)።
ደለቀ: ቈነነ፣ በዝግታ አስኬደ። "ቶሎ ቶሎ ና፡ ምን ይደልቅኻል" እንዲል ባላገር።
ደለቀቀ (ለቀቀ): ዛቀ (የቅቤ)።
ደለቀቀ: ባለ፣ እንደ ልቡ ኾነ (የልጅ)።
ደለቀቅ፣ ደልቃቃ: ባለጌ፣ ቅምጥል፣ እንቅብር፡ "አያት ያሳደገው ሞልቃቃ"።
ደለበ: ተዘገበ፣ ተሰበሰበ፣ ተጠራቀመ፣ ተከማቸ።
ደለበ: ወፈረ፣ ሠባ (የበሬ)።
ደለንቲ: ደነዝ፣ ፈዛዛ (ሰው ወይም ከብት)።
ደለኸ (ደሊኅ ደልኀ): በርበሬ ወቀጠ በሽንኵርት (ደለዘ)፡ ከጨው ጋራ ፈጮ፣ ሰለቀ፡ አላቈጠ፣ አላመ፡ ድልኸ ኣዘጋጀ፣ አደራጀ። "ደለኸ በትግሪኛ ደለኄ ይባላል"።
ደለዘ (ዶለሰ): በርበሬን ከሽንኵርት ጋራ ወቀጠ።
ደለዘ: መረገ፣ በየደ፣ ደፈነ (ብረትን)። ፪ኛውን ገበዛ ተመልከት።
ደለይ ነፋስ: የነፋስ ደለይ፡ ያባይ ጠንቋይ ባህል ነው።
ደለይ: ከዐዘቅት፣ ከጕድጓድ የውሃ መቅጃ፣ መጐተቻ (ከንጨት፣ ከብረት የተበጀ ዕቃ፣ ባልዲ ባለማንጠልጠያ)። "በግእዝ ደለው ማሕየብ ይባላል"።
ደለይ: የኮከብ ስም፡ "በደለይ ውሃ ቀጂ የሚመሰል የጥር ኮከብ"። መዝገበ ፊደል እይ።
ደለደለ (ደለለ): መላ፣ ጨመረ፣ ትክክል አደረገ፣ መደመደ (መሬትን) (ኢሳ ፳፯:፯)። ጐዘጐዘ፣ አነጠፈ፡ ድልድልና ድልድይ አበጀ።
ደለደለ: ሰሐቅ ከፈለ፣ መደበ፣ ተነተነ (ርስትን፣ ገንዘብን)።
ደለደለ: አሳበጠ፣ ቅል አስመሰለ (ገላን)።
ደለደለ: ገደበ፣ ከበበ፣ አገደ፣ ከተረ (ውሃን)።
ደለጐም (ዘልጉም): ዝምተኛ (አልጉም)።
ደለፈሰ: ዛቀ፣ ሰረረ።
ደለፈስ፣ ደልፋሳ: የተደለፈሰ፣ የተዛቀ (መሬት)።
ደላ (ተደልወ): ተሰፈረ፣ ተመዘነ።
ደላ (ደለወ): ተመቸ፣ ተሰማማ፡ ኾነ፣ ተገባ። (ተረት): "የደላው ሙቅ ያኝካል"።
ደላ (ድሕለ): ሸሸ፣ ተናደ፣ ኼደ፣ ነጐደ። (የባልቴት ጸሎት): "ማሪኝ እመቤቴ ማሪኝ እላለኹ፡ ፊትሽን መልሺልኝ ትቼሽ ለደላኹ (ሸሽ)"። (ባሏ መብል መጠጥ አብዝቶ የሞተባት ሴት): "በሶ ጥረሾ አጓት ፪ ዐፍሾ፡ ጥንስስ ያልፈላ፡ ባሌን ይዞት ደላ (ኼደ)"።
ደላላ(ሎች): አመልካች፣ ጠቋሚ፣ ኣስማሚ።
ደላማ: የደለመ (የጠፋ ዐይን)።
ደላሽ: የደለሰ፣ የሚደልስ፡ ቀቢ።
ደላቂ: የደለቀ፣ የሚደልቅ፡ ደሳቂ፣ ጐሳሚ።
ደላቢ: የሚደልብ (ሠቢ)።
ደላንታ: በየጁ ውስጥ ያለ አገር (የዋድላ ጎረቤት)። "ዋድላ ደላንታ" እንዲሉ።
ደላኺ(ዎች): የደለኸ፣ የሚደልኸ፡ አላቋጭ።
ደላዥ(ዦች): የደለዘ፣ የሚደልዝ፡ ወቃጭ፣ መራጊ፣ በያጅ።
ደላይ(ዮች): የደለለ፣ የሚደልል፡ አታሳይ፣ ሸንጋይ፡ "እፈ ቅቤ ልበ ጩቤ" (መዝ ፲፪:፫)።
ደላደለ: ጐዛጐዘ፣ አነጣጠፈ።
ደላጎ(ዎች): የቈርበት፣ የማስ፣ የነት፣ የዳባ ዕላቂ ቅዳጅ።
ደላጎ: ጅል፣ ቂል፣ ሞኝ፣ ከርፋፋ ሰው።
ደል (መድሎት): ፭ ቍና እኸል የሚይዝ (ጕርዝኝ ወይም ቅርጫት)። ፮ ልክ፣ ፴ው ቍና የጫን እኩሌታ ይኾናል (፩ነገ ፲፰:፴፪)።
ደል (ዶል፣ ድልው): የተገባ፣ የሚኾን (ነገር፣ ሥራ)።
ደልማጣ፣ ድልምጥ: የዶለመጠ፡ ወፍራም፣ ጥርንቅ።
ደልዳላ: ትክክል ሰው (በሰውነቱ፣ በውቀቱ)፡ ወይም ቦታ (ዘዳ ፬:፵፫፣ መዝ ፳፮:፲፪፣ ዘካ ፬:፯)።
ደልዳይ(ዮች): የደለደለ፣ የሚደለድል፡ የሚጨምር (ከታሪ)።
ደልድል: የራስ ዘውዴ የፈረስ ስም። "አባ ደልድል" እንዲሉ። "አስተካክል" ማለት ነው።
ደልገን (ዘልጕን): የድብኝት ስም (ቅጥልጥል ድብኝት)።
ደልጊ: በጣና ውስጥ ያለ የመቤታችን ደብር።
ደልጐም: የማሽላ ስም፡ እንጀራው የማያምር፣ የማይሰምር (ቀይ ማሽላ)።
ደመ መራር: ቍጡ፣ ጠበኛ።
ደመ፡ ሰች፡ (ሰታዬ፡ ደም)፡ የዶሮ፡ ያሞራ፡ የወፍ፡ ጭራ፡ በነቀሉት፡
ጊዜ፡ ደም፡ የሚጠጣ፡ የሚጐርሥ።
ደመ ቢስ: ክቾ፣ ለዛ፣ ሙጥጤ።
ደመ ነፍስ (ነፍሰ ዶም): በዶም የምታድር የእንስሳ ነፍስ (ደም ሲደርቅና ሲያልቅ የምትጠፋ)፡ "እንደ ሰው ነፍስ ትንሣኤ የሌላት"።
ደመ ነፍስ: በዶማዊት ነፍስ የቆመ እንስሳ።
ደመ ከልብ: ተበቃይ የሌለው የወንጀለኛ ደም፡ ደሙ ከልብ ይባላል።
ደመ ወዘኛ(ኞች): ባለደመ ወዝ፣ በደመ ወዝ ዐዳሪ (ዘሌ ፳፪:፲)።
ደመ ወዝ (ደመወዝ): ወዘ ደም፡ የደም ወዝ (ጥሮ ግሮ ላብን አፍሶ የሚገኝ ገንዘብ) (፩ቆሮ ፱:፳፬)። (ተረት): "ኣንድ ዓመት በወዝ፡ አንድ ዓመት በደሙ ወዝ"።
ደመ ግቡ: ደሙ (መልኩ) እሰው ዐይን የሚገባ፣ የሚያምር (እዩኝ አዩኝ የሚል)፡ ውብ፣ መልከ መልካም።
ደመለለ፡ (ደበለ)፡ ጠቀለለ፡ ብዙውን፡ አንድ፡ አደረገ። ጀመለን፡ እይ።
ደመመ፡ (ደሚም፡ ደመ። ዕብ፡ ዳ ማም፡ ዝም፡ አለ)፡ ደነቀ፡ ገረመ።
ደመመ፡ መደምም፡ መደንን ı አበጀ፡ ቀበረ፡ ዘጋ፡ መረገ፡ ደፈነ፡ ዐፈር፡
አለበሰ፡ አስ ጣጣ፡ ኣስተካከለ።
ደመመ፡ አጮኸ፡ አስፈራ። ተመመን፡ ተመልከት።
ደመመን፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ደመሰ፡ (ደሚስ፡ ደመሰ)፡ ተመሰ፡ ለከሰ። (ከሰ)፡ (ስከስ)።
ደመሰሰ፡ (ደምሰሰ)፡ ፋቀ፡ አጠፋ፡ እንዳልነበረ፡ አደረገ፡ አበላሸ።
ደመሰሰ፡ ጠቀለለ፡ የበላይ፡ ገዢ፡ ሆነ።
ደመሳሰሰ፡ አጠፋፋ።
ደመስማሳ፡ የተድመሰመሰ፡ ደበስባሳ።
ደመረ፡ (ደምሮ፡ ደመረ)፡ ሰበሰበ፡ እከበ፡ አከማቸ፡ አንድ፡ ላይ፡
አደረገ፡ ባንድነት፡ አቆመ፡ ጠመጠመ፡ የንጨት፡ የቍጥር፡ የሻሽ።
ደመራ፡ መደመር፡ አንድነት፡ ማድረግ፡ ማቆም።
ደመራ፡ ብዙ፡ ርጥብ፡ ዕንወት፡ ተሰ ብስቦ፡ የሚቆምበት፡ የመስቀል፡ ዋዜማ፡ የመስከረም፡
፲፮ኛ፡ ቀን።
ደመርጽማ፡ ደም፡ ዕርጥ፡ የሚመስል። መዠመሪያውን፡ ዐረጠ፡ እይ።
ደመቀ፡ (ደሚቅ፡ ደመቀ)፡ ገነነ " ጐላ፡ አማረ፡ (ዘፀ፳፮፡ ፴፮ " ፳፰ ' ፯። መሳ፭ " ፴፩። ዳን ፲፪፡ ፫)፡ በዛ፡ ከበረ፡ ቀለጠ፡ የማሕሌት ' የዘፈን፡ የልብስ፡ ያጀብ። (ተረት) ፣ ማቅ ' ይሞ ቃል፡ ጋቢ፡ ይደምቃል፡ ገቢውን፡ ባለቤት▪ ያው ቃል። ብርቅና፡ ድንቅ፡ አላንድ፡ ቀን፡ አይደምቅ። የሰው፡ ወርቅ፡ አያደምቅ "
ደመቅ፡ (ደሚቅ)፡ መድመቅ።
ደመቅ፡ አለ፡ ጐላ፡ አለ፡
ደመቅ፡ ደመቅ፡ አለ፡ መላልሶ፡ ደመቀ።
ደመነ፡ ዳመነ፡ (ደምኖ፡ ደመነ)፡ ጠቈረ፡ ጨለመ፡ ደመና፡ ኾነ፡ ከበደ።
ደመና፡ ዳመና፡ ከምድር፡ ወደ፡ ሰ ማይ፡ የሚበን፡ የውሃ፡ ላበት፡ እንፋሎት፡
ዝናም፡ የሚኾን፡ በምድር፡ ላይ፡ ሲታይ፡ ጉም፡ ይባላል። (ዘፈን)፡ እንዳላይሽ፡ እንዳላይሽ፡ ዳመና፡ ጥሏል፡
በላይሽ። ደመና፡ የግእዝ፡ ዳመና፡ ያማርኛ፡ ነው። (ቍጥር፡ ደመና)፡ ዝናም፡ የቋጠረ፣ ጨለማ መሳይ (ነጭ፡ ደመና)፡ ጉም፡ ንድፍ፡ የሚመስል።
ደመና፡ ጠቀሰ፡ ደመናን ' ኣዘዘ፡ በደመና፡ ተጫነ፡ ተቀመጠ። ቶማስ፡ ደመና፡ ጠ ቅሶ፡ መጣ።
ደመናዋ፡ ደመናዪቱ፡ ያች • ደመና (ኢዮ፳፮፡ ፰)።
ደመን፡ ድመን፡ ድመም፡ ድራር፡ መና፡ ነ፡ ይወራረሳሉና፡
ድመም፡ በማለት፡ ፈንታ፡ ድመን ' ይላል። ዳግመኛም፡
ውስጡ፡ መጨለሙን፡ ያሳያል።
ደመኖች፡ (ደመናት)፡ ላበቶች፡ እንፋሎቶች፡ (ኢዮ፴፭'፭። ፴፮፡ ፳፰) "
ደመኛ(ኞች): ደበኛ፣ ባለደም፣ ጠላት፣ ባለጋራ (የገዳይ ወይም የጝች ወገን) (መዝ ፭:፮)።
ደመኛነት: ባለጋራነት፣ ጠላትነት።
ደመደመ፡ (ትግ፡ ደምደመ፡ ደነዘ)፡ ረገጠ፡ አስተካከለ፡ ምድርን። ዘሩ፡ ደመመ ' ነው። ተመተመን፡ ተመልከት።
ደመደመ፡ አደነዘ፡ ሹለትና፡ ስለት ' ኣላጣ።
ደመደመ፡ ጨረሰ፡ ፈጸመ፡ ቈረጠ፡ ግን ብን፡ ግድግዳን፡ ጣራን።
ደመጠ፡ (ደሚፅ፡ ደምፀ፡ ተሰማ)፡ ጮኸ፡ ድምጥ፡ ሰጠ።
ደመጠ፡ ፈገፈገ፡ አለሰለስ፡ አለዘበ 1 ብራናን።
ደሙ መሪራት: ዕከክ፣ ፈረሳቤት። "ቍጡ ደም ማለት ነው"።
ደሙ ደመ ከልብ ኾነ: ብላሽ ቀረ።
ደሙ፡ ፈላ፡ ተቈጣ።
ደሙ: ያ ደም፡ የርሱ ደም።
ደሚ: የደማ፣ የሚደማ።
ደሚና፡ (ኖች)፡ የገራዳ ▪ ዋስ፡ ተጠሪ፡ ማለት፡ ነው፡ ይህ፡ ስም፡ ከሐረርጌ በቀር፡ በሌላ፡ አገር፡ አይነገርም። በዐረብ፡ ደሚን ' ይባላል። ጎራዳን፡ እይ።
ደማ (ደመወ): ደም ኾነ፡ ደም ወጣው፣ ፈሰሰው (ገላው፣ ሰውየው)።
ደማ: የርሷ ደም።
ደማሚ፡ የደመመ፡ የሚደምም።
ደማሚት፡ አሲድ፡ ከሚባል፡ ከድኝ ባሕርይ፡ የተሠራ፡ ማር፡ መሳይ፡ እሳት፡ ሲነካው ደንጊያ፡ የሚሰብር፡ ተራራ፡ የሚፈነቅል፡ ሲጮኸ 1 ድም፡ የሚል፡ ፈረንጆች ዲናሚት፡ ይሉታል።
ደማም: ውብ፣ ቈንዦ (ደሙ ፍልቅ ያለ)።
ደማስ፡ ቀይነትና፡ ቢጫነት፡ ያለው፡ የደማስቆ፡
ስራ፡ ባለቀለም፡ ልብስ።
ደማስቆ፡ የላይኛው፡ ሶርያ፡ ከተማ።
ደማሪ፡ የደመረ፡ የሚደምር፡ ጠምጣሚ።
ደማቂ፡ የሚደምቅ፡ የሚያምር፡ ጕልሕ፡ በሩቅ፡ የሚታይ።
ደማቅ፡ ድምቅ (ድሙቅ)፡ የደመቀ። ድምቅ፡ ቀይ፡ እንዲሉ።
ደም መለሰ: ተበቀለ፡ ገዳይን ገደለ።
ደም መላሽ: ተበቃይ፡ የደም ብድር ከፋይ (ዘኍ ፴፭:፳፭)።
ደም መታት: ብዙ ደም ወረዳት (ሴትዮዋ)።
ደም፡ ረግጦ፡ ገባ፡ በደም፡ ላይ፡ ዐለፈ፡ ታቦቱ፡ ሙሽራው።
ደም በደም ኾነ: ብዙ ሰው ተፈነከተ፣ ቈሰለ።
ደም፡ ተቃባ፡ ባለደም፡ ተኳዃነ።
ደም፡ ተፋሰሰ፡ ተጋደለ፡ ተጝተ።
ደም አስተኔ: የደም ዐይነት።
ደም አስተፊ: ሥረ ቀይ ቅጠል (የጥፈት መማሪያ)።
ደም አስተፊት: የማይበላ እንጕዳይ።
ደም አፈሰሰ: ሰው ገደለ፡ ከብት፣ ዶሮ ዐረደ፡ ጭዳ አለ።
ደም አፈታበት: ደሙ ከመውረድ አልቆመም፣ አልታገደም።
ደም ዐፋሽ (ደማፋሽ): ልጅ ከተወለዶ በኋላ ደም ደምታፍሥ ሴት።
ደም ዐፋሽ(ለዐት): ውላጋ፡ የአፋ እጄታ (ክንፍ) የታራጅን ደም የሚቀባ።
ደም፡ ኣስተፊ): ሊበሉት የማይገባ እንጕዳይ።
ደም፡ እሰከረው)፡ አሳበደው፣ አጠገበው (ሐርበኛውን ውሻውን)።
ደም ዕርጥ (የደም ዕርጥ): ቀይና ሳንባ መሳይ ሞላላ ዶቃ፡ የደም ኣብነት።
ደም ያፈላል: ያስቈጣል።
ደም ይጐርሣል: መጠጥ የሌለበት ምግብ ደም ይስባል።
ደም ደም አለው: ሸተተው (ሰውየው ይሞታል ወይም ይገድላል)።
ደም ደረቀ: ቂም ጠፋ፡ ዕርቅ ኾነ፡ ሰላም፣ ስምምነት ተደረገ (የገዳይ ወገን ከማች ዘመድ በመጋባቱ)።
ደም ገሣ: ደም ተፋ፣ አፈሰሰ።
ደም ጋን (የደም ጋን): የሽንጥና የዳሌ መገናኛ (ደም የሚታቈርበት)።
ደም ግባት: ላሕይ፣ ወዝ፣ ማማር፣ ቍንዥና፣ ውበት (ዳን ፮:፴፮)።
ደም ጥልቀት: የደም (የዘር) መቀላቀል። "ደም ጥልቀት ሥጋ ልደት" እንዲሉ።
ደም ጥሪ: ከደም መጥራት፡ የሴት ግዳጅ መቆም አለመውረድ።
ደም: ከሰው፣ ከእንስሳ፣ ከተንቀሳቃሽ ኹሉ፣ ከዕፀዋትም የሚወጣ ቀይና ነጭ ፈሳሽ። "የበለስ፣ የቍልቋል፣ የወርካ፣ የቅንጭብ ደም" እንዲሉ። (ተረት): "ምንም ብጠላው በወንድሜ ግንባር ደም አልይበት"። (የምድር ደም): ከርስት የተገኘ ውጤት፡ ወይም ገንዘብ። (የሌባ ደም): ሌባ የሚከፍለው ዕዳ።
ደም: የዘቢብ ጭማቂ።
ደምለው፡ የሰው፡ ስም፡ ጠቅለው፡ ማለት ነው።
ደምላይ፡ የቍጥር፡ ስም፡ ፩፡ ፪፡ ፫።
ደምላይ፡ የደመለለ፡ የሚደመልል፡ ጠ ቅላይ።
ደምማ: ድምቅ ቀይ።
ደምሰው፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ አጥፋው፡ ማለት፡ ነው።
ደምሳሳ፡ ምሉ፡ ጠቅላላ፡ አንድ፡ ሳይቀር።
ደምሳሽ፡ (ሾች) ፣ ደምሳሲ)፡ የደመሰሰ፡ የሚደመስስ፡ አጥፊ።
ደምሳሽ፡ ጠቅላይ፡ የበላይ፡ ዳኛ፡ ሌላው፡ የፈረደውን፡
የሚሽር፡ የሚገለብጥ።
ደምሴ፡ ደምስ፡ የሰው፡ ስም።
ደምበጫ፡ በጐዣም፡ ውስጥ፡ ያለ፡ አገር።
ደምቡራ፡ ሬ፡ ከጥጥና፡ ከጭረት፡ የተ ሠራ፡ መናኛ፡ ልብስ፡ ኰስኳሳ፡ ሻድሬ። ደም ቡራ፡ የደመረ፡ ዘር፡ ነው። አመከዝን፡ እይ።
ደምቢያ፡ በበጌምድር፡ ክፍል፡ ያለ ' አ ገር። ደምቢያና ▪ ፎገራ፡ እንዲሉ። በግእዝ ድንቢ ይባላልና፡ ደንቢያ፡ ተብሎ፡ ሊጻፍም፡ ይቻላል።
ደምዳሚ፡ (ዎች)፡ የደመደመ፡ የሚደመድም፡ አስተካካይ፡ ጨራሽ።
ደምዳማ፡ ደነዝ፡ ስለት፡ አልባ፡ የእ ብድ፡ ጐራዴ።
ደሞ - ደግሞ ደገመ።
ደሞ: ደመደመ (ነስርና አደፍ ሲበዛ አስደግሞ ቢይዙት ደም የሚያርጥ፣ የሚያቆም የጥላ መድኀኒት)። "በካህናት አነጋገር ዕን ጐርዶ ጥን ለጽ ለውጦ ደመርጽ ይባላል"። ከደም (ደም) ጋር የተያያዙ ቃላት።
ደሞ: ደግሞ። "ደሞ ደሞ" እንዲል ዘፋኝ። "ደሞ" የባላገር፣ "ደግሞ" የከተማ ዐማርኛ ነው።
ደሞዬ - ገብስ - ደማ።
ደሞዬ፡ ወደ፡ ቀይነት፡ የሚያደላ፡ ገብስ፡ ደም፡
አስተኔ።
ደሠመ ፣ መታ ፣ ደሰመ።
ደሰመ፡ በሾኸ፡ ዐጠረ፡ ዘጋ፡ ደፈነ።
ደሰመ፡ ገጨ፡ ለተመ፡ ተመተመ።
ደሰማ: በመራቤቴ ውስጥ ያለ አገር።
ደሰሰ (ደሲስ፡ ደሰ፡ ደሰሰ)፡ ዘመመ፡ ዘነበለ፡ ተኛ: ዐጪር፡ ኾነ። ደሳንና፡ ዳስን፡ እያ፡ የዚህ፡ ዘሮች፡ ናቸው።
ደሰስ፡ አለ ፣ ዘንበል፡ አለ።
ደሰቀ፡ በጕልበት፡ በጩ፡ በክርን፡ መታ፡
ደሰቀ፡ ተጫነ፡ ደበተ፡ አሞቀ።
ደሰተ፡ (ደሰየ)፡ ደላ፡ ተመቸ፡ ተስማማ፡ ጊዜው፡ አገሩ፡
ኑሮው።
ደሳ፡ ከሣር፡ የተበጀ፡ ዳውጃ፡ የሱማሌ፡ ዘላን፡
ጐዦ፡ መደረቢያ፡ የሚነቀልና፡ የሚተከል፡ አጐበር፡ ያለው። ዳስን፡
ደሰሰን፡ እይ።
ደሳለኝ (ደስ፡ አለኝ)፡ ተፈሣሕኩ)፡ የሰው፡ ስም፡ ተደሰትኩ። ልጅ፡ ብወልድ ደሳለኝ። (ግጥም)፡ ደሳለኝ፡ ደስ፡ ያሞሌው፡ ደንደስ።
ደሳሚ፡ የደሰመ፡ የሚደስም፡ የሚጋጭ፡ ለታሚ፡ ተምታሚ።
ደሳሳ፡ የዘመመ፡ የዘነበለ፡ ቤት፡ ዐጪር፡ የድኻ፡
ጐዦ፡ ጐንባሲት።
ደሳቂ፡ የደሰቀ፡ የሚደስቅ፡ የሚመታ ሌባሻይ፡ ወይም፡ ሌላ።
ደስ ፣ የደስታ፡ ከፊል ፣ ደሰተ።
ደስ፡ ተሠኘ፡ ተደሰተ። (ሠኘ)ን፡ እይ።
ደስ፡ አለ፡ ኾነ፡ ተደረገ፡ ደስታው።
ደስ፡ አለው፡ (ተፈሥሐ፡ ተሐሥየ)፡ ደስ፡ ተሠኘ ፣ ደላው፡ ተመቸው።
ደስ፡ አሠኘ፡ (አሥመረ)፡ አስደሰተ።
ደስ አሠኘ/ደስ ተሠኘ: አስደሰተ/ተደሰተ ማለት ነው።
"ደስታን"
ተመልከት።
ደስ፡ ይበልኸ፡ ፈንድቅ፡ (ዘዳ፲፮፡ ፲፬)።
ደስ፡ ፈቅ፡ አለው፡ (ተደለወ፡ ፍ ጹመ)፡ ፈጽሞ፡ ደስ፡ አለው፡ ሐዘን፡ ትካዜ፡ ራቀው፡
የልብ፡ ተድላ፡ አገኘ።
ደስሜ፡ የሰው፡ ስም፡ ደስም፡ ግጭ፡ ለ ትም፡ ማለት፡ ነው።
ደስቃም፡ እንቅልፋም፡ ሙቀታም፡ ስፍራ።
ደስቅ፡ (ክ)፡ የንቅልፍ፡ ጋኔን፡ ደባች፡ ደባስ፡ ወይም፡
እንቅልፍና፡ ሙቀት።
ደስተኛ፡ (ኞች)፡ ደስታ፡ ያለው፡ ባለ ደስታ፡ (ዘዳ፲፮፡ ፲፭ = ኢሳ፳፬ ' ፰)።
ደስተኛዋ፡ ደስተኛዪቱ፡ ደስ፡ ያላት፡ የተደሰተች፡
(ሶፎ፪፡ ፲፭)።
ደስታ፡ በቶሎ፡ የምትለቅ፡ ኩፍኝ።
ደስታ፡ ተድላ፡ ድሎት፡ ፍሥሓ፡ ምቾት፡ ሐዘን፡
ትካዜ፡ የሌለበት፡ (ኢሳ፳፬ ' ፰)፡
ደስታ፡ የሚያስለቅስ፡ የከብት፡ በሽታ፡ ከማመም፡
በቀር፡ የማይገድል።
ደስታ፡ የንጉሥ፡ ግምጃ፡ ድንኳን፡ በ ጕዞ፡ ጊዜ፡ በጧት፡ የምትነቀል፡ በቀትር፡
የምት ተከል፡ በርሷ፡ መተከል፡ መንገድ፡ ያደከው፡
ሰራዊት፡ ስለሚደሰት፡ ደስታ፡ ተባለች። በቀድሞ፡
ዘመን፡ ደበና፡ ትባል፡ ነበር። መሬትን፡
እይ።
ደስታ፡ የወንድና፡ የሴት፡ መጠሪያ፡ ስም። አቶ፡ ደስታ፡ እመት፡ ደስታ።
ደስቶች፡ ደስታ፡ ድንኳን፡ ጫኞች።
ደስክ ጋኔን ፣ ደሰቀ።
ደረመ)፡ አድረመረመ፡ አጕረመረመ፡ አቶመቶመ።
ደረመሰ፡ (ደረሰመ)፡ ደረባ፡ ወደ፡ ታች፡ አፈረሰ፡ ናደ፡ አወደቀ፡
አሠረገ፡ የመሬት፡ የመቃብር፡
ደረመናም፡ ዕከካም፡ ፎከታም።
ደረመን፡ (ድራሞ)፡ ዕከክ፡ ፎከት፡ ፈረሳቤት።
ደረሞኛ፡ እንቅልፋም፡ ጋኔን፡ የሚያሳክክ።
ደረሰ፡ (ዐረ)፡ ተማረ፡ ትምርት፡ አ ጠና፡ አነበበ፡ ሌሎች፡ የጻፉትን፡ የደረሱትን።
ደረሰ፡ (ደሪስ፡ ደረሰ፡ በጽሐ፡ ለ ጸቀ። ትግ፡ ሐባ፡ ደርሰ፡ ተቀኘ)፡ ዐጕልና፡ ገቢር፡ አደገ፡ ጐለመሰ፡ በቃ፡
አከለ።
ደረሰ፡ መላ፡ ተጨረሰ፡ ተፈጸመ፡ (መዝ ፵፬፡ ፲፯)። ንግሬ፡ ደረሰ። የፈሩት፡ ይደርሳል፡ (ይፈጸማል)፡ የጠሉት፡ ይወርሳል።
ደረሰ፡ ሴት፡ ዐወቀ፡ ነካ።
ደረሰ፡ አድርሰናል፡ ሰጥተናል፡ ተዘክረናል፡ ጨርሰናል።
ደረሰ፡ ኼደ፡ መጣ፡ ተመለሰ፡ ቀረበ፡ ከተፍ፡ አለ፡
ተጠጋ፡ ገባ። እቤተ፡ ክሲያን፡ ደርሼ፡ መጣኹ። ያበደርኹት፡ ገንዘብ፡ ደረሰኝ፡ (መጣልኝ፡ ገባልኝ)፡ ማለት፡ ነው።
ደረሰ፡ ድርሰት፡ ተናገረ፡ ቅኔ፡ ተቀኘ።
ደረሰ: መጣ።
ደረሰመ፡ (ደሰመ)፡ ደረመሰ፡ ደነቀፈ።
ደረሰሰ)፡ አንደረሰሰ፡ አዘገመ፡ እ ንቀረሰሰ፡ በተገብሮነትም፡ ይፈታል።
ደረሰኝ፡ (ኞች)፡ የገንዘብ፡ መቀበያ፡ ወረቀት ▪ ጽፈትና፡ ማኅተም፡ ፊርማ፡ ያለበት።
ደረሰኝ፡ ተቀበልኩ፡ ተረከብኩ።
ደረሰው፡ አገኘ፡ ተቀበለ።
ደረሳ፡ መድረስ፡ ድርሰት።
ደረስጌ፡ (ደራስጌ)፡ የደራስ፡ ምድር፡ የደራስ፡ ስፍራ፡ በስሜን፡
ውስጥ፡ ያለ፡ አገር። ሌላም፡
አፈታት፡ ይኖረዋል።
ደረቀ፡ (ደረከ)፡ ከለለ፡ ከቸለ፡ ከቸረ፡ ከቸቸ፡ ከሸለለ፡
ከረረ፡ ርጥበት፡ ዐጣ፡ ከልም ላሜ፡
ራቀ፡ (ኢሳ፵፩፡ ፲፯)። ነጠፈን፡ ደምን፡ እይ።
ደረቀ፡ ጨከነ፡ ጨካኝ፡ ኾነ።
ደረቀ: ሰለለ፣ ቀጠነ፣ ዐጪር ኾነ፣ ተንጠለጠለ።
ደረቀች፡ ከሳች፡ ኰሰመነች። ሚስትን፡ ደረቀች፡ ብሎ፡ መፍታት፡ አይገባም።
ደረቅ፡ (ድሩክ)፡ የደረቀ ክቾክችሌ ከራራ፡ ውሃ፡ ያልነካው፡ ነገር፡ ልብንና፡
ቀልብን፡ ተመልከት።
ደረቅ፡ ምች፡ ደም የሚያስተፋ፡ ምታት በሽታ።
ደረቅ፡ ምድር፡ መሬት፡ (ዘፍ፩፡ ፱፡ ፲)።
ደረቅ፡ ምድር፡ የብስ፡ ውሃ፡ የሌለባት፡ ዝናም፡ ያልጣለባት።
ደረቅ፡ ሳል)፡ አክታ የሌለው።
ደረቅ፡ ሴት፡ ንፉግ፡ ሥሥታም፡ ጨ ካኝ፡ እጇን፡ ቢሏት፡ የማይወድቃት፡ ጠብ፡
የ ማይላት፡ ቀጪን፡ የከሳች፡ ተብሎም፡ ይተረጐ ማል።
ደረቅ፡ ትንቢት፡ ስውር፡ ያይዶለ፡ ን ግግር፡ ግልጥ፡ ዕርገተ፡ ኢሳይያስ፡ ራእየ፡
ኤልያስ፡ ተረፈ፡ ኤርምያስ።
ደረቅ፡ እንጀራ፡ መባያ፡ የሌለው፡ ኣለወጥ።
ደረቅ፡ ዕንጨት፡ ቅጠል፡ ልምላሜ፡ የሌለው፡ የቆመ፡ ወይም፡
የወደቀ።
ደረቅ፡ ወዝ፡ ሸቀን፡ ፎረፎር።
ደረቅ ወዝ: ሸቀን።
ደረቅ፡ ግንባር፡ ጌታችን፡ በምራቁ፡ ጭቃ፡ አላቍጦ፡ ዐይን፡
ያፈካበት፡ (ዮሐ፱፡ ፮፡ ፯)።
ደረቅ፡ ጠጅ፡ የተጣራ፡ ሲጠጡት፡ የ ሚያሰክር፡ የቈየ፡ የኖረ፡ የከረረ፡ የወጣለት፡
አ ንዱ፡ በቃኝ።
ደረቅ፡ ጥይት፡ ቱባ፡ ክልስ፡ ያይዶለ።
ደረቅ፡ ጦር፡ መሣሪያ፡ ያሊያዘ፡ ሰው፡ ወረጋ፡ ባዶ፡
እጅ፡ ወግቶ፡ ደም፡ የማያወጣ፡ ማለት፡ ነው። እከሌ፡
ደረቅ፡ ጦሩን፡ መጣ፡ እንዲሉ።
ደረቅ: ወዝ የሌለው። "ፊተ መጣጣ" እንዲሉ።
ደረቅነት፡ ደረቅ፡ መኾን፡ ጨካኝነት።
ደረቅያ፡ ኰቻሮ፡ እንኵርኵሪት፡ የመ ነኵሴ፡ መኖ።
ደረቆት፡ ተቀቅሎ፡ የደረቀ፡ የጠላ - ንፍሮ።
ደረበ፡ ካበ፡ አነባበረ፡ በላይ፡ አደረገ፡ በልብስ፡
ላይ፡ ልብስን፡ ጫነ፡ አለበሰ፡ ጨመረ! (ሕዝ፲፮፡ ፲፰)።
ደረበ፡ ደርብ፡ ደረባ፡ ድርብ፡ ሠራ፡ ዕጥፍ፡ አደረገ።
ደረበ፡ ጓድ፡ አበጀ።
ደረባ፡ (ዎች)፡ የጐታ፡ የጐተራ፡ የድብኝት፡ የኵበት፡ ጣራ፡
ከነክዳኑ፡ በጋልኛም፡ ደባል፡ ማለት፡ ነው።
ደረባ፡ (ደርበየ)፡ ናደ፡ አንሸራተተ፡ አወረደ፡ አወደቀ፡ ወረወረ።
ደረባ፡ ቤቴ፡ ፯ኛ፡ ባሪያ፡ የማን፡ ቤቴ፡ ልጅ፡ ደረባ፡
ደፍቶ፡ በጓሮ፡ የሚያድር።
ደረባ፡ ቤት፡ በታችኛው፡ ወግዳ፡ ያለ፡ አገር። የደረባ፡ ቤት፡ ጐዦ፡ የነበረበት፡ ማለት፡
ይመስላል።
ደረቤ፡ በጐዣም፡ ክፍል፡ ያለ፡ አገር። ጓዴ፡ ማለት፡ ነው።
ደረብ፡ (ትግ)፡ ሆድ፡ ከርሥ።
ደረብ፡ ደረባ፡ (ቢጽ)፡ ጓድ፡ ጓደኛ፡ ባልንጀራ፡ ወዳጅ። ባልደረብ፡ ባልደረባ፡ ጃን፡ ደረባ፡ እንዲሉ።
ደረቦች፡ ጓዶች፡ ባልንጀሮች።
ደረተ፡ (ደርዐ፡ ጠቀበ። ትግ፡ ደ ረተ፡ ወሰነ)፡ ደበደበ፡ ጠቃቀመ፡ መላልሶ፡ ሰፋ፡ ደረት፡
አስመሰለ፡ አደረገ። ደረዘንና፡
ጠረ ዘን፡ እይ።
ደረተ ሰፊ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ደረተ፡ ሳንቃ፡ ደረቱ፡ ደረቷ፡ ሳንቃ፡ የሚመስል።
ደረተ፡ ጠባብ፡ ደረቱ፡ ደረቷ፡ የጠበበ።
ደረታም፡ ደረተ፡ ሰፊ።
ደረት፡ (ቶች)፡ ትግ ፣ ወሰን፡ ድን በር)፡ በቁሙ፡ ከማንቍርት፡ በታች፡ ከሆድ፡ በ ላይ፡ ያለ፡ ገላ፡ ያጥንቱ፡ መጠጋጋት፡ እንደ፡
ድ ሪቶ፡ የኾነ፡ ፍርምባ፡ የእጅና፡ የክንፍ፡
የወ ርች፡ ወሰን፡ (ዮሐ፲፫፡ ፳፭)። እከሌና፡ እከሌ፡ ሲታገሉ፡ ደረት፡ ለደረት፡
ተያያዙ። ጣለን፡ እይ።
ደረት፡ በድጓ፡ ተጽፎ፡ የሚገኝ፡ ምል ክት፡ ካጪርነቱ፡ በቀር፡ የሀን፡ ቅርጽ፡ የሚመ ሰል።
ደረት፡ የመሬት ' ዕርከን።
ደረቷን፡ ጣለች፡ አራቈተች።
ደረነቀ፡ ዐመቀ፡ ተጫነ፡ ረጠጠ፡ የስ ፍር። ጠረነቀን፡ እይ።
ደረከ፡ ጠና፡ ጥኑ፡ ኾነ፡ (ግእዝ)።
ደረከከ)፡ ብለኸ አንደረከከን እይ።
ደረከክ ፣ ደርካካ፡ የተንደረከከ፡ ያጠረ፡ ፀር፡ የኾነ፡ ወፍራም።
ደረዘ፡ (ጠረዘ፡ ደረተ)፡ ክርን፡ ዐጥፎ፡ መልሶ፡ ልብስን፡ ጠቀመ፡
ስፌትን፡ ለጐመ፡ በ፪፡ መርፌ፡ መጫሚያ፡ ሰፋ። በትግ ሪኛ፡ ግን፡ ደረዘ፡ ገላን፡ ዐሸ፡ ማለት፡
ነው፡ ምስ ጢሩ፡ መመላለስን፡ ያሳያል።
ደረደረ፡ (ትግ፡ ደርደረ፡ አነባበረ)፡ ሰደረ፡ ኰለኰለ፡ ደከነ፡ በተራ፡ በመደዳ፡ አስቀመጠ፡ አነባበረ፡ ከመረ።
ደረደረ፡ በገና፡ መታ፡ (፩ነገ፡ ፩፡ ፵)።
ደረደረ፡ አሰለፈ፡ አቆመ፡ ገረገረ።
ደረደረ፡ ዕርቅን፡ አዘጋጀ።
ደረጀ፡ (ደረገ)፡ ደንጊያ፡ ጠረበ፡ ደረጃ፡ ሠራ፡ አበጀ፡ ጸፈጸፈ፡ አነጠፈ፡ ገጠመ፡ ደረበ፡ (አድራጊ)።
ደረጀ፡ ተደላደለ፡ ተመቻቸ፡ በሀብት፡ ላይ፡ ሀብት፡ ጨመረ፡ ወገን፡ አበዛ፡ ሥር፡ ሰደደ ጸና፡ (ተደራጊ)።
ደረጃ፡ (ጆች)፡ ጸፍጸፍ፡ ባደባባይ፡ በሰበሰብ፡ በቤት፡ ውስጥ፡ የተነጠፈ፡ ጥርብ፡ ደንጊያ፡
ደረጃ፡ ማዕርግ፡ የማዕርግ፡ ስም።
ደረጃ፡ ዕርከን፡ መውጫና፡ መውረጃ።
ደረገ፡ (ደርጎ፡ ደረገ)፡ ገጠመ፡ አንድ፡ ኾነ፡ ዐበረ።
ደረገመ ፣ (ረገመ) ፣ በጥፊ፡ መታ፡ መረገተ።
ደረገመ፡ አባ፡ ጠረቀመ፡ ዘጋ።
ደረገመ፡ ዐይንን፡ መብራትን፡ አጠፋ፡ አወደመ።
ደረገመ፡ ከንባብ፡ የሚጣላ፡ ትርጓሜ፡ ተናገረ። (ተረት)፡ አንቱ፡ ትተረጕሙ፡ አንቱ፡ ትደረግሙ። ለነውረኛ፡ መምርም፡ ይነገራል።
ደረጠ፡ (ትግ፡ ደረጸ)፡ ተልባን፡ ዐሸ፡ መታ፡ ሊጥ፡ አደረገ።
ደረጠ፡ በጠበጠ፡ አወከ፡ ነቀነቀ፡ አገ ሮን፡ ሰውነትን። ናጠን፡ እይ።
ደረጣ፡ ብጥበጣ፡ ሁከት።
ደረፎ፡ (ዘረፍኦ) ፣ በጐላ፡ ክፍል፡ ያለ፡ ተራራ።
ደረፎጪ፡ ተኰሰተረ፡ ተሰበሰበ።
ደሪ፡ የሚደራ፡ ዘቢ፡ ተለማጭ።
ደራ፡ (ደርዖ፡ ደርዐ)፡ ዘባ፡ ተለመጠ፡ እንደ፡ ሰፌድ፡ ሆነ፡ ማስጫ፡
መሰለ። የዚህ፡ ቤት፡ ጣራው፡ ደርቷል።
ደራ፡ (ጐዣም)፡ ለቤት፡ ክዳን፡ የሚሆን፡ ሣር።
ደራ፡ ሠማ፡ ጋለ። ምጣዱ፡ ደራ፡ እንዲሉ።
ደራ፡ ሰፋ ፣ በዛ፡ ደመቀ። ገበያው፡ ደራ። ጨዋታ፡ ሲደራ፡ እናቴ፡ ባሪያ፡ ነች፡ ያሠኛል።
ደራ፡ ሻፈደ፡ ሠየ፡ ጐመዠ። እንደ፡ የቦ፡ ሰልቶ፡ እንደ፡ ቈንጆ፡ ደርቶ፡
እንዲሉ።
ደራ፡ በመርሐ፡ ቤቴ፡ ባሻገር፡ በወንጭት፡ ዳር፡
ያለ፡ አገር፡ አምባ፡ (ተራራ)፡ ያለው።
ደራ ብለኸ ድርና ማግን አስተውል።
ደራ፡ አቅኒው፡ ነው።
ደራሳ፡ ያገር፡ ስም፡ በሲዳሞ፡ ክፍል፡ ያለ፡ አገርና፡
ነገድ።
ደራስ፡ ጮሌ፡ ፈረስ፡ ቶሎ፡ የሚደርስ። ባልን፡ ተመልከት።
ደራረበ፡ ካካበ፡ ጨማመረ።
ደራሽ፡ (ደራሲ፡ በጻሒ)፡ የደረሰ፡ የሚደርስ፡ መጪ። እንደ፡ እንግዳ፡ ደራሽ፡ እንደ፡ ውሃ፡ ፈሳሽ። ባለቅኔ፡ መምር፡ ሊቅ።
ደራሾች፡ (ደራስያን)፡ የቅኔ፡ መም ሮች፡ ሊቃውንት።
ደራቂ፡ የሚደርቅ።
ደራቃ፡ ደራቍቻ፡ ከሲታ፡ ጣጋ፡ ጠጋ፡ ቋንጣ፡ ብረ፡
ሸሽ።
ደራቢ፡ (ዎች)፡ የደረበ፡ የሚደርብ፡ ድርብ፡ ሠሪ፡ ወይም፡
ለባሽ፡ አጣፊ።
ደራች፡ (ቾች)፡ ጠቃቢ)፡ የደረተ፡ የሚደርት፡ ደባደቦ፡ ሰፊ፡ ጠቃቃሚ።
ደራዥ፡ (ዦች)፡ የደረዘ፡ የሚደርዝ ፣ በመኪና፡ ሰፊ።
ደራደረ፡ ኰላኰለ።
ደራጭ፡ የደረጠ፡ የሚደርጥ፡ ዐሺ፡ በጥ ባጭ፡ ነቅናቂ።
ደሬ፡ (ደርዐ)፡ ጠንካራ፡ የቈላ፡ ግራር፡ ከስሌ። በሐረርጌ፡ ሀሎ፡ ይባላል፡ ነዋሪ፡ የማይበላሽ፡
የማይነቅዝ፡ ማለት፡ ነው።
ደርሰኒ፡ የሽቱ፡ ስም፡ የጥንት፡ ሽቱ፡ ቀረፋ።
ደርሰኸ፡ ደርሰሽ፡ የወንድና፡ የሴት፡
ስም፡ አድገኸ፡ አድገሽ፡ ማለት፡ ነው።
ደርሶ፡ መልስ፡ እቅርብ፡ ስፍራ፡ ኺዶ፡ መመለስ። ዋለ፡ ብለኸ፡ ውሎን፡ እይ።
ደርሶ፡ ንኡስ፡ አገባብ፡ ድንገት። (ግጥም)፡ አይበሉ፡ በልቼ፡ የድንብላል፡ በሶ፡ ሆዴን፡
ይቈርጠኛል፡ እንዲያው፡ ደርሶ፡ ደርሶ።
ደርሶ ኼዶ፡ መጥቶ፡ ቀርቦ፡ ገብቶ፡ ደርሶ፡ መልስ፡
እንዲሉ።
ደርበት፡ (ጐዣም)፡ ፪፡ እንስራ፡ ውሃ፡ የሚይዝ፡ ማድጋ።
ደርቡሽ፡ (ሾች)፡ የነገድ፡ ስም፡ የሱዳን፡ ሕዝብ፡ የኖባ፡ ዘር። ባረብኛም፡ ደርዊሽ፡ ዘላን፡ ማለት፡ ነው። አንዳንድ፡ ሰዎች፡ ግን፡ የመሕዲ፡ ወታደር፡ ስም፡ ነው፡ ይላሉ።
ደርባባ፡ እንድርብ፡ የተንደረበበ፡ የረጋ፡ ጭምት፡ ዝምተኛ።
ደርባቦች፡ ጭምቶች፡ ዝምተኞች።
ደርብ፡ (ቦች)፡ ላይኛ፡ ቤት፡ ሰገነት፡ ፎቅ፡ በሳንቃና፡
በመረባርብ፡ በስሚንቶ፡ የተሠራ፡ እሳተ፡ ከል፡ (ዘፍ፮ ፥ ፲፯። ፩ነገ፡ ፮፡ ፩፡ ፲)።
ደርቦ፡ አነባብሮ።
ደርቦ፡ ገዳይ፡ ባንድ፡ ጊዜ፡ ፪፡ ጠላት፡ የገደለ፡ ዳጃች ብጡልን፡ የመሰለ።
ደርናቂ፡ የደረነቀ፡ የሚደረንቅ፡ ዐማቂ፡ ረጣጭ።
ደርከክ፡ ደርከክ፡ አለ፡ የውፍረትና፡
የድንክ፡ አካኼድ፡ ኼደ።
ደርዘን፡ የዝርዝር፡ ወይም፡ የጥቅል፡ ዕቃ፡ ስም፡
፲፪፡ ማለት፡ ነው። ደርዘን፡
የፈረንጅ፡ ቋንቋ፡ ሲኾን፡ ባማርኛም፡ ስለ፡ ተለመደ፡ ተ ጻፈ።
ደርዘኛ፡ (ኞች)፡ ነገር፡ ዐዋቂ፡ ሰው፡ ቋጣሪ፡ ውለኛ።
ደርዝ፡ (ዞች)፡ የሱሪ፡ የእጀ፡ ጠባብ፡ የጥብቆ፡ የሽብሽቦ፡
የመጫሚያ፡ የበቅሎ፡ ዕቃ፡ ስፌት ፣ በእጅ፡ ወይም፡ በመኪና፡ የተሰፋ፡ የቍና፡
የጕርዝኝ፡ የንቅብ ያገልግል፡
የመሶብ፡ ልጕማት።
ደርዝ'ውግ፡ ዕጥፍ፡ ስፌት።
ደርዳሪ፡ (ዎች)፡ የደረደረ፡ የሚደረድር፡ ሰዳሪ፡ ኰልኳይ፡ በገና፡ መቺ።
ደርገ፡ ሙሴ፡ ዐሥራ ኹለት፡ ወይም፡ ኻያ፡ አራት፡ ማኅበረተኞች። ለሙሴ፡ ለደርገ፡ ሙሴ፡ እንዲሉ።
ደርጋሚ፡ የደረገመ፡ የሚደረግም ፣ አጥፊ።
ደርጋንበሳ፡ (ደርገ፡ አንበሳ)፡ አንበሳዊ፡ አንበስማ፡ አንበሳ፡ መሳይ፡ አውሬ፡ ኀይለ፡ አንበሳ፡ ያለው፡ የተሰጠው፡ መጠኑ፡ የነብር። ኦሮ ' በጕዳ፡ ይለዋል፡ በጋራ፡ ጐርፎ፡ ይገኛል።
ደርግ፡ አንድጋ፡ አንድነት፡ ኅብረት፡ ማኅበር።
ደርፋጫ፡ ኵስትር፡ ዐጪር፡ ሽክና፡ አንኮላ።
ደሸደሸ)፡ አደሸደሸ፡ አደዘደዘ፡ አው ደለደለ፡ ሥራ፡ ፈት፡ ኾነ።
ደሽ፡ ብዙ፡ ድርሻ፡ ዕጣ፡ የለሽ።
ደቀ፡ መዛሙርት፡ የዳዊት፡ ተማሮች፡ ሐዋርያት፡ አርድእት፡
(ዮሐ፱፡ ፳፯፡ ፳፰)።
ደቀ፡ መዝሙር፡ ዳዊት፡ የሚማር፡ ልጅ፡ የዳዊት፡ ተማሪ፡
(ማቴ፲፡ ፵፪። ዮሐ፱፡ ፳፰)። ከመምሩ፡ ደቀ፡ መዝሙሩ፡ እንዲሉ።
ደቀ፡ ሳፍ፡ (አውፋሪ)፡ ሊቀ፡ አርድእት፡ ተማሮችን፡ የሚያስገባና፡
የሚያስወጣ፡ የተማሮች፡ አለቃ። (ደቅ፡
ሳፍ)፡ ጥሩ፡ ንጹሕ፡ ምርጥ፡ ልጅ፡ ማለት፡ ነው።
ደቀ፡ እስጢፋ፡ ባጤ፡ እስክንድር፡ ዘመን፡ የነበረ፡ ፈላስፋ፡
አስማተኛ፡ ምትሀተኛ።
ደቀ፡ እስጢፋ፡ እርሱ፡ ራሱ፡ ደቅ፡ በጣና፡ ባሕር፡ የሚገኝ፡
የእስጢፋኖስ፡ አጥቢያ፡ መቅደስ፡ በውስጡ፡ ብዙ፡ ምትሀትና፡ አስማት፡ ጥንቈላ፡ መድኀኒት፡ የሚያውቁ፡ ልጆች፡ ስመ፡ ጥሮች፡ የነበሩበት።
ደቀለ፡ ዴቀለ፡ ዲቃላ፡ ወለደ፡ አመጣ።
ደቀል ፣ የመርከብ፡ ምሰሶ ፣ ደንቀል።
ደቀሰ፡ (ደቅሶ፡ ደቀሰ)፡ ተኛ፡ አንቀላፋ።
ደቀቀ፡ (ደቂቅ፡ ደቀ)፡ ተሰበረ፡ ነከተ፡ ተፈጨ፡ ተሰለቀ፡ ላመ፡
ለዘበ፡ እነሰ።
ደቀነ፡ አቀረበ፡ አስጠጋ፡ አቋተ፡ ደከረ።
ደቀደቀ፡ (ደደቀ። ትግ፡ ደግደገ)፡ ወቀጠ፡ ወቃቀጠ፡ ወጋ፡ ወጋጋ፡ ጠቀጠቀ፡
ቍልቍል፡ ቍልቍል፡ አለ፡ ለማድቀቅ፡ ለመጥረግ፡ ለመወልወል።
ደቀደቀ፡ መላልሶ፡ ከረና።
ደቂ፡ (ደቃሒ)፡ የደቃ፡ የሚደቃ።
ደቂቀ፡ ሴት፡ ፊት፡ በደብር፡ ቅዱስ፡ የነበሩ፡ መላእክት፡
የግዜር፡ ልጆች፡ የተባሉ፡ ኋላም፡ በስሕተታቸው፡ የሰይጣን፡ አሻንጉሊት፡ የሆኑ፡ (ሔኖ፡ ፭። ዘፍ፡ ፮፡ ፪)።
ደቂቀ፡ ነቢያት፡ ከሆሴዕ፡ እስከ፡ ሚልክያስ፡ ያሉ፡ የነቢያት፡
መጻሕፍት።
ደቂቀ፡ ነቢያት፡ የነቢያት፡ ልጆች፡ ወይም፡ ተማሮች።
ደቂቃ፡ (ዎች)፡ ባ፭፡ ባ፭፡ የተወሰነ፡ የሰዓት፡ ክፍል፡
ስሳው፡ ነጥብ፡ አንድ፡ ሰዓት፡ ነው። በግእዝ፡
ካልኢት፡ ይባላል። ከዋናው፡
ሰዓት፡ ነጥብ፡ ስላነሰ፡ ደቂቃ፡ ተባለ።
ደቂቅ፡ ልጅ፡ ተኰልኰሎ፡ ውሪ፡ ውርጋጥ፡ ኵታራ። ከሊቅ፡ እስከ፡ ደቂቅ፡ እንዲሉ።
ደቂቅ አገባብ ሲሆን: እንደ ግእዝ ትርጉሙ "እንደዚያው" ወይም "ልክ እንደሱ" ማለት ነው።
ደቂቅ፡ አገባብ፡ አንቀጽ፡ የማያስቀር፡ ገባ፡ ብለኸ፡ አገባብን፡
እይ።
ደቂቅ አገባቦች በ፣ የ፣ ከ ሲሰማሙት: በጥንት፣ የጥንት፣ ከጥንት ይላል።
ደቂቅ አገባቦች: እንደ "በ"፣ "ከ"፣ "ስለ" መነሻ እየሆኑ ሲነገር፡ እንደ "ምን በምን"፣ "ከምን"፣ "ስለ ምን" ይላል።
ደቃ፡ (ደቅሐ)፡ ምድርን፡ በእግሩ፡ መታ፡ ወጋ፡ ደቅ፡ አደረገ፡
የፍየል፡ የጋማ፡ ከብት፡ አውሬ፡ ባየ፡ ጊዜ። ለሰውም፡
ይነገራል፡ (፩ዜና፡ ፲፯ - ፱)።
ደቃቂ፡ የሚደቅ፡ ለዛቢ።
ደቃቃ፡ ደቃቅ፡ ድቃቂ፡ የደቀቀ፡ ስልቅ፡ ልዝብ፡ ዶቄት፡ ገለባ፡
አሠር፡ አሸዋ፡ አቧራ፡ (፪ዜና፡
፴፬፡ ፬)። ደካማ፡ አቅመ፡ ቢስ፡ ሰውነት።
ደቃኝ፡ (ኞች)፡ የደቀነ፡ የሚደቅን፡ አቅራቢ፡ አቋች፡ ደካሪ።
ደቈሰ፡ በጣም፡ መታ፡ በክርን፡ ደበደበ፡ በድጅኖ፡
ዳመጠ።
ደቈሰ፡ እጅግ፡ አመመ።
ደቈሰ፡ ፈጩ፡ ሰለቀ፡ አደቀቀ፡ አላመ፡ አለዘበ፡
የኮሶ፡ የቅመም፡ የበርበሬ፡ የመድኀኒት።
ደቅ ፣ በቁሙ ፣ ደቀቀ።
ደቅ፡ መድቃት።
ደቅ፡ አደረገ፡ ደቃ።
ደቅ፡ ከጣባ፡ የሚበልጥ፡ ከዋዲያት፡ የሚያንስ፡
አቃፋ፡ የሸክላ፡ እቃ። ሲበዛ፡
ደቆች፡ ይላል።
ደቅ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለደቂቅ፡ (ግእዝ)።
ደቅ፡ የደሴት፡ ስም ፣ በጣና፡ ውስጥ፡ ያለ፡ ታላቅ፡ ደሴት፡ ደቅ፡
የሚሠራበት።
ደቅደቅ፡ አለ፡ ተንደከደከ፡ ዶዮው።
ደቅዳቂ፡ የደቀደቀ፡ የሚደቀድቅ፡ ወጊ፡ ጠቅጣቂ።
ደቋሽ፡ (ሾች)፡ የደቈሰ፡ የሚደቊስ፡ አድቃቂ፡ አላሚ፡ አለዛቢ።
ደቋቈሰ፡ አማመመ።
ደበለ (ደቢል፣ ደበለ): አከለ፣ ጨመረ፣ ደረበ፡ ሰበሰበ፡ ዕጥፍ አደረገ፡ ሸረበ፣ ጠሞረ። (ግጥም): "ደብል በሌ እኔ አለቅም ዛሬ"።
ደበለ: ቀየጠ፣ ቀላቀለ፣ ደባለቀ።
ደበለ: እቤቱ ባዕድ ሰው አኖረ።
ደበለለ: ጣለ፣ አወደቀ። (የባለጌ ግጥም): "የዳቦ የዳቦ እላለኹ የዳቦ፡ እጊዮርጊስ ጓሮ ይደብሉኽ አቦ"።
ደበለል፣ ደብላላ: የተደበለለ፣ የተጣለ፡ ወዳቃ።
ደበላ: ለራስ ጥምጥም፣ ለወገብ መቀነት የሚኾን፡ ከባሕር የመጣ ዐርበ ጠባብ ልብስ (ከመሐሙዲ የሚሣሣ፣ ከሻሽ የሚወፍር)።
ደበሌ: ትልቅ ብራብሮ (አረንጓዴ ቀለም)።
ደበል: የወፍራም ገመድ ስም፡ ጥሙር ሽርብ (ወዶሮ)፡ የዛፍና የሰንጋ መጣያ ደንዳና ገመድ።
ደበል: ደበን።
ደበሎ (ዎች): በለምድ ዐይነት የተበጀ የበግ ዐጐዛ፡ ከነጠጕሩ የለፋ መደረቢያ በልብስ ላይ የሚጠለቅ። (ቅጥልጥል ደበሎ): በካባ አምሳል ተቀጣጥሎ የተሰፋ ረዥም ደበሎ (የተማሪ ልብስ)።
ደበሏም: ደበሎ ለባሽ፣ ባለደበሎ፣ አባ ደበሎ (እረኛ፣ ተማሪ፣ መነኵሴ)።
ደበሰ (ደመሰ): ገሰሰ፣ ለቀቀ፣ ጠፋ፣ አልታይ አለ (የጽፈት)። በትግሪኛ ግን "በረዘ" ማለት ነው፡ የሙቀትን ማነስና መቀነስ ያሳያል።
ደበሰ: ደመሰ።
ደበሰ: ዶቄት ጨመረ፣ አጐበገበ።
ደበሠ: ገሰሰ (ደበሰ)።
ደበሰሰ፣ ደበዘዘ): አንደበሰሰ፣ አንደበዘዘ።
ደበሰስ፣ ደብሳሳ: ደበዘዝ፣ ደብዛዛ።
ደበረ (ደቢር፣ ደበረ): ደብር አደረገ፡ ገደመ፣ አከበረ፣ አበለጠ፣ አላቀ።
ደበረ: ደበለ፣ ደረበ፡ አነባበረ፣ ሰደረ፣ ደረደረ (በተራ አኖረ ዕቃን)።
ደበሸ: ሰነፈ፣ ችላ አለ፡ ፈዘዘ፣ ተንደበዘዘ።
ደበሽ፣ አዲበሽ: ትጋትና ንቃት የሌለው፡ ሰነፍ፣ ችላ ባይ፣ ፈዛዛ (ደበዘዝ) ሰው፣ በሬ።
ደበቀ: ከተተ፣ ሸጐጠ፣ ዐባ፣ ሰወረ፣ ሸሸገ። (ተረት): "ባሪያ ዐጋዥ ብታገኝ መጅ ደበቀች"።
ደበቅ ጦር: የደበቀ ጦር።
ደበቅ: ስውር ቦታ።
ደበቅ: ራሱን፣ ሰውነቱን የደበቀ ሐርበኛ።
ደበበ (ደቢብ፣ ደበ): ድባብ ሠራ፣ ዘረጋ፣ ወጠረ፣ ገተረ፣ አጠላ፣ አጠየመ። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም "ይደብብ፣ ይደብባል" ይላል፡ መዠመሪያውን "ሰለለ" እይ።
ደበብ አለ: የወይን ፍሬ መሰለ።
ደበተ (ደበወ፣ ድቡት): ጨቈነ፣ ተጫነ፣ ከበደ፡ መንቃትና መስማት ከለከለ።
ደበተረ: ደብተር ዘረጋ፣ ጻፈ፣ ከተበ፡ ደብተራ ደብተር አደረገ።
ደበነ (በደነ): በፍጥነት ሞተ፡ ደረቀ።
ደበነ: ከረረ፣ ጥብቅ ኾነ፡ አነሰ። በትግሪኛ ግን "አደፈ፣ ቈሸሸ" ማለት ነው።
ደበና: ከማቅ የተሰፋ ሰቀልኛና ሞላልኛ የንጉሥ ድንኳን። ያውታሩን መክረርና መወጠር ያሳያል፡ ዳግመኛም የድሩንና የማጉን ጠጕርነት ያመለክታል።
ደበናንሣ (ደበን አንሣ): ጠይብ፣ ባለጅ ፋቂ፡ የቈዳን ጠጕር በመጥረቢያ ፍቆ የሚያነሣ፡ ደደቡን፣ እድፉን የሚያሶግድ።
ደበኔ (ዋኖስ): ሱያ፣ ዋኔ፣ ዋሊያ፡ "የኔ ደበን፣ ደበናዊ" ማለት ነው። ከርግብ ማነሷን ያሳያል።
ደበን (ሐረር፣ ጢም): የጠጕር ስም፡ ጠጕር፡ እድፍ፣ ቍሻሻ።
ደበኛ: ደመኛ። "ደማን" ተመልከት።
ደበከ): ደበቀ)፡ አድበከበከ፣ ጠለላውን በውስጥ፣ አተላውን በላይ አደረገ፣ አወፈረ (የመጠጥ፣ የቅቤ)።
ደበከከ: የ(ደበከ) ደጊመ ቃል፡ ወረኃ ኾነ።
ደበከክ፣ ደብካካ: ወረኃ።
ደበዘዘ፣ ደበሰሰ): አንደበዘዘ፣ አንቀፈደደ፣ አሰነፈ።
ደበዘዝ፣ ደብዛዛ: ሰነፍ፣ ደንጊያ (በግሩ የፍጥነት ጠላት)፣ ደደብ።
ደበየ (ደብይ፣ ደበየ፣ ደበወ): ትግ ደበየ (ደፈነ፣ ቀበረ)።
ደበየ: የክፉ ብድር ከፈለ፡ ደባ ሠራ፡ ወረረ፣ ዘረፈ። "ደበደበን" እይ።
ደበየ: ደቦ አዋለ።
ደበደበ (ደብደበ): መላልሶ መታ፣ ወገረ፣ ገደለ፡ ነጋሪት ድም ድም አደረገ።
ደበደበ: ዐፈር መለሰ፣ ከመረ፣ ቈለለ።
ደበደበ: ደፈነ፣ መረገ። ሦስተኛውን "ቈረቈረ" ተመልከት።
ደበደበ: ጣፈ፣ ደረተ፣ ጠቃቀመ፣ አወፈረ፡ በድብዳብ ለበደ፡ ድብዳብ ጐዘጐዘ።
ደበደበ: ጻፈ፣ ከተበ።
ደበደበ: ፍሬ ዠመረ፡ ሸፈነ፣ አድበለበለ።
ደቡል(ሎች) (ጥካካ): አካል፣ አካልማ፣ ሥጋማ ሰው፡ ጭቃው ብዙ።
ደቡብ: ፬ኛ የምድር ማእዘን፡ የሰሜን አንጻር (በስተቀኝ ያለ)።
ደባ (ደበወ፣ ደበየ፣ ዴፐ): ተደበቀ፣ ተሸሸገ፣ ደፈጠ፣ ሸመቀ (ለመንጠቅ)። "አደሳ እንጂ ደባ አልተለመደም"።
ደባ (ዲፓ): ሽመቃ፣ ደፈጣ፣ ተንኰል፣ እከይ፣ ክፋት፡ ዘረፋ፣ ቅሚያ፣ ንጥቂያ። "ስለት ድጕሱን ደባ ራሱን" እንዲሉ (እስ፯:፱)። "ደጐሰ" ብለህ "ድጕስን"፡ "ሳለ (ሰሐለ)" ብለህ "ስለትን" እይ።
ደባ ሠራ: ዝኒ ከማሁ።
ደባ ዋለ (ደበየ): ተተነኰለ፣ ተጠበበ፡ ዘረፈ፣ ቀማ፣ ነጠቀ።
ደባለቀ (ዘባረቀ): ቀላቀለ፣ ቀየጠ፣ ዘነቀ (ዘፍ፲፩:፯)። (ተረት): "ከነገረኛ ሰው ሥንቅ አይደባልቁም"።
ደባላቂ: የደባለቀ፣ የሚደባልቅ፡ ቀላቃይ፣ ቀያጭ፣ ዘናቂ።
ደባላቂነት: ቀላቃይነት።
ደባል(ሎች): በሌላ ሰው ቤት ተጨማሪ ኹኖ የሚኖር አንድ ባዕድ ሰው። "ድልባንን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።
ደባልቄ፣ ደባልቅ: የሰው ስም፡ "ቀላቅል" ማለት ነው።
ደባሳ (ድሙስ): የደበሰ፣ የገሰሰ፣ የጠፋ፡ ጥፉ።
ደባስ: በጠፍ፣ በወና፣ በባዶ ከተማ የሚቀመጥ ጋኔን፡ ወይም ሰላቢ ሰይጣን (ለራሱ ጠፍቶ የሰውን በረከት የሚያጠፋ)። "ደስቅን" እይ።
ደባሪ: የደበረ፣ የሚደብር፡ ኣክባሪ።
ደባርቅ: ያገር ስም፡ በበጌምድር አውራጃ ያለ አገር። "ደባ አርቅ" ማለት ይመስላል።
ደባሽ: የሚደብስ፡ ጠፊ።
ደባቂ: የሚደብቅ፡ ሰዋሪ፣ ሸሻጊ።
ደባቃ: ሰዋራ ቦታ (አሳቻ)።
ደባበቀ: ሰዋወረ።
ደባቢ: የደበበ፣ የሚያብብ፡ ዘርጊ፣ ወጣሪ።
ደባባ: ጠይም፡ ጥቍር አይሉት ቀይ (መካከለኛ)።
ደባብቆ: ሰዋውሮ።
ደባት: ጥርጥር፡ የደባ ፍራት።
ደባክድ: ቀጠጥና ያህያ ዦሮ።
ደባያት: በቀል፣ ፍዳ፡ የክፉ ብድር፡ እንደ ሠራው መሥራት፣ እንዳደረገው ማድረግ። ፪ኛውን "ደባይ" ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።
ደባይ (ደባዪ): ወራሪ፣ ዘራፊ፡ ደባ ሠሪ።
ደባይ: መረሬ (ጐንደር)።
ደባይ: ሰፊ ነጋሪት። "ደባይ ምታ አታመንታ" እንዲሉ (ወደ ዘመቻ ሲኼዱ)። ከዘረፋና ከወረራ ሲመለሱ መመታቱንና በሙሉ ግብር ቀን መጐሸሙን ያሳያል።
ደባይ: የሰው ስም ነው።
ደባይ: የደበለ፣ የሚደብል፡ ጨማሪ፣ ደራሲ፣ ሸራቢ፣ ቀያጭ።
ደባይ: ድንገተኛ አደጋ። "ቢኾን ይኾናል፣ ባይኾን አይተነው አንኼደውሞይ ደባይ መተነው" እንዲል ሐርበኛ።
ደባደበ: መታታ።
ደባደቦ: መጣፊያና ክር የበዛበት ርቅ ድሪቶ።
ደባደቧም: ድሪቷም፡ ደባደቦ ለባሽ።
ደብለል ከብለል አለ: በቀኝ በግራ ጐን ተንደባለለ (የጋማ ከብት፣ ያመንዝራ)።
ደብላይ: የደበለለ፣ የሚደበልል፡ ጣይ፣ ውዳቂ።
ደብረ (ር) ዐባይ: በትግሬ ያለ ትልቅ ገዳም።
ደብረ ሊባኖስ: አስቀድሞ አባ ሊባኖስ የጸለየበት፣ ኋላም አባ ተክሌ ያቀኑት (እግራቸው እስኪሰበር የቆሙበት) ገዳም (እት ጋፊኝ ዜጋመል)።
ደብረ ማርቆስ: በጐዣም ያለ የማርቆስ ቤተ ክሲያን።
ደብረ ሲና: የሲና ተራራ፡ ሙሴ ፲ቱ ቃላትን ከግዜር የተቀበለበት። በይፋት ያለ ያቡነ አረጋይ መቅደስ አጥቢያ።
ደብረ በግዕ: ያባ ሕፃን ሞአ ገዳም የሚገኝበት አገር (ሺዋ በጠራ ወረዳ)። "በግዕ" የተባሉ ጻድቁ ናቸው።
ደብረ በጥብጥ: ቤተ ክሲያን አዋኪ፣ አስቸጋሪ፣ በጥባጭ፣ ክፉ ደብተራ።
ደብረ ቢዘን: በላዩ ገዳም ቤተ ክሲያን ያለበት የትግሬ ተራራ። "ደብረ ባዜን" ማለት ነው ይላሉ።
ደብረ ብርሃን: ያገር ስም፡ በላይኛው ተጕለት መዠመሪያ ያለ አገር (ዐጤ ዘርዐ ያዕቆብ የቅድስት ሥላሴን መቅደስ የሠሩበት)። ብርሃን ስለ ወረደበት በመቅደሱ ስም "ደብረ ብርሃን" ተባለ ይላሉ፡ ሌላም ሐተታ አለው።
ደብረ ታቦር: የበዓል ስም፡ በነሐሴ ፲፫ ቀን የሚውል በዓል። "ቡሔን" እይ።
ደብረ ታቦር: የታቦር ተራራ፡ ጌታችን የግዜር ልጅነቱን ያስመሰከረበት። በበጌምድር ያለ አገር።
ደብረ ነጐድጓድ: ሐይቅ፡ የሐይቅ መቅደስ፡ ደሴት።
ደብረ ዐስቦ (ደብረ ዐጸባ፣ ደብረ ዐስብ): የደብረ ሊባኖስ ፊተኛ ስም፡ የጭንቅ፣ የምንዳቤ፣ የረኃብ፣ የጥም፣ የጾም፣ የጸሎት ስፍራ ማለት ነው ("ዐሰብ፣ ዐሰቦት" "ጭንቅ" ማለት ነውና)። ፪ኛም "ዐጸባው" ዋጋ ያለው ስለ ኾነ "ዋጋ የሚያሰጥ ገዳም" ማለት ይኾናል።
ደብረ ከርቤ: ከርቤ የበቀለበት ያለበት ተራራ።
ደብረ ወርቅ: በጐዣም ያለ የቅድስት ማርያም መቅደስ፡ የቅባቶች ሰበካ።
ደብረ ዘይት: በኢየሩሳሌም አቅራቢያ የሚገኝ (ዘይት (ሴቴ ወይራ) የበቀለበት)፡ ጌታችን ለሐዋርያት የምጽኣትን ነገር ያስተማረበት ተራራ።
ደብረ ዘይት: የበዓል ስም፡ ያርባ ሑዳዴ እኩሌታ እሑድ ለት የምጽኣት መታሰቢያ፣ ማሰቢያ። "በሰንበት ላይ ደብረ ዘይት" እንዲሉ።
ደብረ ዝቋላ: በሺዋ ያለ ረዥም ተራራ (ያቦ ገዳም)።
ደብረ ዳሞ: ያቡነ አረጋይ ገዳም ያለበት የትግሬ ተራራ።
ደብረ ድኁኃን: ጥንታዊ የአንጎት (ወሎ) ታላቅ ደብር መቅደስ።
ደብረ ገነት: በኢየሩሳሌም ያለ የኢትዮጵያ ገዳም (ከግራኝ በፊት በወሎ የነበረ ቤተ ክሲያን)።
ደብረ ጽዮን: የጽዮን ተራራ።
ደብረ ጽጌ: አበባ ያለበት ተራራ።
ደብሪቱ: የሴት ስም፡ ታላቂቱ ማለት ነው።
ደብራሆም: ሐሚና ተናጋሪ፣ ለፍላፊ፣ ለማኝ፣ ላሊበላ። ግእዝ "ደበራ አንደበራ" ካለው በምስጢር ይገጥማል።
ደብር ቅዱስ: ከማየ አይኅ በፊት ደቂቀ ሴት የነበሩበት የተቀደሰ ተራራ። "ትቤትን" ተመልከት።
ደብር: መወድስ የሚቆምበት፣ ከለት እስካመት የሚቀደስበት ገዳም፡ ታላቅ ቤተ ክሲያን (ተራራ የሚመስል)፣ ዐጸዳም (ጢምን አይ)። የቀድሞ ሰዎች (ቅዱሳን አበው፣ ነቢያት፣ መናንያን፣ መነኮሳት፣ ባሕታውያን) በደብር ላይ ስለ ኖሩ፣ በዚህ ምክንያት የከተማ ቤተ ክሲያን ኹሉ "ደብር" ተባለ። ዋና ምስጢሩ ግን ከገጠር መቅደስ የበለጠና በተራራ ላይ የተሠራ ማለት ነው። (አርባ አራቱ ደብር): በጐንደር ያለ ታላላቅ ቤተ ክሲያን። (ሴት ደብር): የሴት ገዳም፡ በደብረ ሊባኖስ የሚገኝ የመነኵሲቶች መኖሪያ።
ደብር: በሞረት ያለ ያቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም፡ ወይም ቤተ ክሲያን፣ ሰበካ፣ አጥቢያ አገር።
ደብር: የተራራ ስም፡ ተራራ። "ደብር" ግእዝ፣ "ተራራ" ያማርኛ ነው፡ በጋልኛ "ጋራ" ይባላል።
ደብሮች: ገዳሞች፡ ታላላቆች ቤተ ክሲያኖች።
ደብብ: ያገር ስም፡ አዳባይ አቅራቢያ ያለ አገር (የወግዳ ክፍል)፡ "ድባብ ዘርጋ፣ ወጥር" ማለት ነው። "ደብብ የጠጋ ልጅ" እንዲል ዘር ቈጣሪ።
ደብተራ ኦሪት: የሙሴ መቅደስ፣ የታቦት፣ የጽላት መኖሪያ።
ደብተራ: ዜማ፣ ቅኔ፣ ሳታት የሚያውቅ፡ በደብተራ (በድንኳን) ውስጥ የሚመራ፣ የሚቀኝ፣ የሚዘምር፡ መንፈሳዊ አገልጋይ ካህን፡ አወዳሽ፣ ሳታት ቋሚ። (ተረት): "ደብተራ የዘኬ ጐተራ"። "አይጥፍ ደብተራ ክንፍ የለው አሞራ"። (ግጥም): "አየሽወይ ደብተራ ቅኔውን ሲመራ"።
ደብተራ: የድንኳን ስም፡ ድንኳን (ግዝ)። ሲበዛ "ደባትር" ይላል።
ደብተር: መሥመር ያለው ባንድነት የተጠረዘ፡ ገቢና ወጪ ወይም ሌላ ቃል መጸፊያ ብራና፣ ወረቀት፡ ትንሹም ትልቁም የነገር፣ የጕዳይ መዝገብ። ቢጻፍበትም ባይጻፍበትም "ደብተር" ይባላል።
ደብተርነት፣ ድብትርና: ካህንነት፣ አወዳሽነት፡ ደብተራ መኾን።
ደብተሮች (ደባትር): ካህናት፣ መዘምራን፣ አወዳሾች፣ ድንኳን ዐዳሪዎች (ካህናተ ደብተራ)።
ደብቴ: ከፊለ ስም፡ ወይም ቍልምጫ፡ የደብተራ ወገን፡ "የኔ ደብተራ" ማለት ነው።
ደብያት: ዝኒ ከማሁ። "ደቦ" በሺዋ፣ "ደብያት" በጐንደር ነው።
ደብደቦ: በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ።
ደብዳቢ (ዎች): የደበደበ፣ የሚደበድብ፡ ሽፍታ፣ ወንበዴ፣ ቀማኛ፣ ባለደም፡ መቺ፣ ገዳይ፣ ደራች፣ ጠቃቃሚ፣ መራጊ።
ደብዳቤ (ዎች): ቃል፣ ነገር፣ ጕዳይ፣ መላክት የተጸፈበት ብራና፣ ወረቀት፡ ማመልከቻ፣ ማስታወሻ።
ደብዳቤ ጻፊ: መላክት የሚጽፍ፣ የሚከትብ።
ደብዳቤ: ትልቅ ቍና መገበሪያ።
ደቦ: ብዙ ሰው ተሰብስቦ እንደ ወረራ ላንድ ሰው የሚሠራው የኅብረት ሥራ (ጅጊ)።
ደቦ: ጅጊ (ደበየ)።
ደቦል(ሎች): ገላው ጥርንቅ ያለ፡ ያንበሳ፣ የውሻ፣ የዝንጀሮ፣ የሰው፣ የከብት ልጅ፡ ሲያዩት የሚያምር (መሳ፲፩:፭:፮፣ መዝ፻፬:፳፩፣ ምሳ፳፰:፩)። "ወጠምሻን" እይ።
ደቧቡል(ሎች): ዝኒ ከማሁ፡ ውፋሬ፣ ድንዳኔ ያለው ሞንዳላ፣ መንደላት (ኢዮ ፳፩:፲፩)። ደቧቡል ውስጠ ብዙነትም አለው።
ደችን እይ።
ደነሰ፡ (ደንሶ፡ ደነሰ)፡ ዘለለ፡ ጨፈረ፡ ተወዘወዘ፡ ተረገረገ።
ደነሰረ፡ አሸራሽቶ፡ አስቀመጠ፡ ቸሰረ፡ ረፈቀ።
ደነቀ፡ (ደኒቅ፡ ደነቀ)፡ ገረመ፡ ደመመ፡ እጹብ፡ ሆነ።
ደነቀረ፡ (ነቀረ)፡ ደከረ፡ አጕራን፡ መስቀልኛ፡ አድርጎ፡ በበር፡
አቆመ፡ ወነከረ።
ደነቀረ፡ ደንቃራ፡ በመንገድ፡ ላይ፡ ጣለ፡ አስቀመጠ፡
ዕርድ፡ አርዶ፡ ድር፡ አድርቶ።
ደነቀፈ፡ (ነቀፈ)፡ አነቀፈ፡ ወለከፈ።
ደነቀፍ፡ ደንቃፋ፡ ወለከፍ፡ ወልካፋ፡ እንቅፋታም።
ደነቈለ፡ ጠነቈለ፡ ዘነቈለ፡ ወጋ፡ ዛቀ፡ አነቈረ።
ደነቈረ፡ (ነቈረ፡ ደንቀወ፡ አብደ)፡ ወለነ፡ ዦሮው፡ ተዘጋ፡ ተደፈነ፡ አልሰማ፡
አለ። ደነቈረ፡ ሰነፈ፡ ዕውቀት፡ አጣ፡ አላዋቂ፡ ሆነ፡
ጀለ።
(ተረት)፡ ፯፡ ዓመት፡ ባይማሩ፡ ፸፡ ዓመት፡ ይደነቍሩ።
ደነበ፡ ፈጽሞ፡ ደነዘ፡ ፈዘዘ፡ ለገመ፡ ዳተኛ፡
አባያ፡ ሆነ፡ እንቢ፡ አልሄድም፡ አለ።
ደነበረ፡ (ደበረ፡ ነበረ)፡ ደነገጠ፡ ፈራ፡ በረገገ፡ አገረገረ፡ ወገሸ፡
አፈገፈገ፡ ሸሸ፡ ዘለለ፡ ወደ፡ ጐን፡ ሄደ፡ ወነበደ።
ደነበረ፡ ለካ፡ ወሰነ፡ ደካ፡ (ገቢር)።
ደነበረ፡ ታወረ፡ ጠነበረ፡ (ተገብሮ)።
ደነበሸ፡ ታመገ፡ ደለበ፡ ሻገተ።
ደነበቀ፡ (ደበቀ)፡ አብዝቶ፡ ቀዳ፡ አንኮላን፡ በማጥለቅ።
ደነበዘ፡ (ደበሰ፡ ነበዘ)፡ ጨለመ፡ ጠነበዛ።
ደነበዝ፡ ደንባዛ፡ ድንብዝ፡ የደነበዘ፡ የጨለመ፡ ሰውየው፡ ወይም፡ አይኑ።
ደነባ፡ (ትግ፡ ደንበወ)፡ እጅና፡ እግሩ፡ አበጠ፡ ተድበለበለ።
ደነባ፡ ህግ፡ ወሰነ፡ ደነገገ፡ ደንብ፡ አቆመ፡
ስርአት፡ ሰራ፡ አወጀ።
ደነባ፡ በታችኛው፡ ወግዳ፡ ደቡብ፡ ያለ፡ አገር።
ደነባ፡ በጋልኛ ዘላይ፡ ማለት፡ ነው።
ደነባ፡ ያልጋ፡ ጋድም፡ አነጸ፡ ጠረበ፡ በልክ፡
በመጠን፡ በማስተካከል።
ደነብ(ፍ)ስ፡ ዳት፡ ልግም፡ ዝምታ።
ደነብስ፡ አለ፡ ዝም፡ አለ፡ ነገር፡ አልመልስም፡ አለ።
ደነነ፡ (ደኒን፡ ደነ)፡ ናቸ፡ በዛ፡ ችፍግ፡ አለ፡ ዘነበለ፡ ጐነበሰ፡
ዘመመ።
ደነከ፡ (ደነቀ)፡ አጠረ፡ አጭር፡ ሆነ።
ደነከለ፡ (ትግ፡ ደንከለ)፡ ጣለ፡ ፈነገለ፡ አሰናከለ።
ደነከረ፡ (ደነቀረ፡ ደነገረ)፡ ወለገደ፡ አጠመመ።
ደነከረ፡ ወዲያና፡ ወዲህ፡ ግራና፡ ቀኝ፡ ማሰ፡ ኳተ፡
ቈፈረ።
ደነከረ፡ ዘለለ፡ አረገደ።
ደነዘ፡ (ደንዘዘ)፡ ደና፡ በረደ ' ጠረሰ ' ስለት፡ አጣ፡ አልቈርጥ፡ አለ።
ደነዘዘ፡ (ደንዘዘ)፡ ፈዘዘ፡ ዳተኛ፡ ሆነ፡ አልሄድ፡ አልሰማ፡
አለ።
ደነዘዝ፡ ደንዛዛ፡ ፈዛዛ ደብዛዛ፡ በድን።
ደነዝ፡ (ዞች)፡ የደነዘ፡ የደና፡ አር፡ የማይቈርጥ፡ ካራ።
ደነዝ፡ ደንቈሮ፡ ደደብ።
ደነደነ፡ (ትግ፡ ደንደነ፡ ሞከረ፡ ፈተነ)፡ ወፈረ፡ ገዘፈ፡ ረጋ፡ የጭቃ፡ የሊጥ፡ የቡሆ።
ደነጀ፡ (ደንገገ)፡ ደነገገ፡ ወሰነ።
ደነገለ፡ (ደንገለ)፡ ጠበቀ፡ በድንግልና፡ አኖረ፡ ድንግል፡ አደረገ።
ደነገረ፡ (ለበየ)፡ ሳተ፡ አጣ፡ ረሳ።
ደነገተ፡ (ደዲቅ፡ ደደቀ፡ ደኒቅ፡ ደነቀ)፡ ድንገት፡ ሆነ፡ መጣ፡ ተደረገ፡ ሳያስቡት፡
አለብኝ፡ ሳይሉት።
ደነገዘ፡ በርጅና፡ ፈዘዘ፡ ጨለመ፡ ላይን፡ ያዘ።
ደነገዝ፡ ደንጋዛ፡ (ዞች)፡ የደነገዘ፡ ፈዛዛ፡ ዳፍንታም።
ደነገየ፡ ደነጋ።
ደነገገ፡ (ደንገገ)፡ ስራት፡ ሰራ፡ ወሰነ፡ ሀገገ፡ ደነባ፡ ጠነቀቀ።
ደነገጠ፡ (ደንገፀ)፡ ፈራ፡ ባባ፡ ተንቀጠቀጠ፡ ነው፡ አለ፡ አዘነ፡
ከሳ።
ደነገጠ፡ ሣሣ፡ አነሰ። ገበታው፡ ደነገጠ፡ እንዲሉ።
ደነጋ፡ (አበነ)፡ ደንጊያ፡ ሆነ፡ ወደ፡ ደንጊያነት፡ ተለወጠ፡
ከረረ፡ ጠነከረ፡ ፈዘዘ።
ደነጐረ፡ ደደቀ፡ ቈፈረ፡ ፈነቀለ፡ ገለበጠ፡ አደንጓሬ፡
ዘራ።
ደነፈቀ፡ (ደፈቀ)፡ ሳያቋርጥ፡ ፈጽሞ፡ አለቀሰ፡ ነፈረቀ፡ ተስረቀረቀ፡
ፊቱን፡ በንባ፡ ዘፈቀ፡ ተንሠቀሠቀ።
ደነፋ፡ (ደፍዐ፡ ወክሀ። ትግ፡ ደንፍዐ)፡ ተንቈራጠጠ፡ ዘለለ፡ አወካ፡ ፎከረ፡ ተንደቀደቀ፡
ዘራፍ፡ እዚህ፡ ገዳይ፡ አለ።
ደናም፡ ደን፡ የበዛበት፡ ስፍራ፡ ባለደን፡ ዱር።
ደናራ፡ (ዲናር)፡ የገንዘብ፡ ስም፡ የቀድሞ፡ ገንዘብ።
ደናሽ፡ የደነሰ፡ የሚደንስ።
ደናቂ፡ የሚደንቅ፡ ገራሚ።
ደናቢ፡ የደነበ፡ የሚደንብ፡ ደናዥ፡ ፈራዥ።
ደናብ፡ በመራቤቴ፡ ውስጥ፡ ያለ፡ አገር።
ደናዥ፡ የሚደንዝ፡ በራጅ።
ደን፡ (ኖች)፡ ብዙ፡ ዛፍና፡ ቅጠላቅጠል፡ ዎማ፡ ጫካ፡
ውድማ።
ደንሳራ፡ ድንስር፡ የተደነሰረ፡ ቅምጥ፡ ርፍቅ።
ደንሳገነን፡ የሚሸት፡ ቅጠል፡ የምች፡ መድኀኒት።
ደንሴ፡ አመለ፡ ልስልስ፡ ሰው፡ ገራም፡ ከብት፡
የማይዋጋ፡ የማይራገጥ፡ የደንስ፡ ደንሳዊ፡ ማለት፡ ነው።
ደንስ፡ የቀበሌ፡ ስም፡ ካንኮበር፡ በታች፡ ያለ፡
ስፍራ፡ ደናም፡ ዛፋም። ትርጓሜው፡
ደግ፡ ማለፊያ።
ደንሶ፡ ዝኒ፡ ማከሁ፡ ደንዞ፡ ከዚህ፡ የወጣ፡ ነው።
ደንቀል፡ ደቀል፡ የመርከብ፡ ምሰሶ፡ (ኢሳ፳፫፡ ፳፫)።
ደንቀዝ፡ የከተማ፡ ስም፡ ከጐንደር፡ አስቀድሞ፡ በበጌምድር፡
የነበረ፡ ከተማ።
ደንቃሪ፡ የደነቀረ፡ የሚደነቅር፡ ወንካሪ፡ ሸጓሪ፡
ቀርቃሪ።
ደንቃራ፡ (ሮች)፡ ጦስና፡ ርት፡ በጐዳና፡ ላይ፡ የታረደ፡
በግ፡ ፍየል፡ ዶሮ፡ የተደራ፡ ድር፡ በበሽተኛ፡ ራስ፡ የዞረ፡ ውጥንቅጥ፡ እኸልና፡ ቅቤ፡ በመተላለፊያ፡ መንገድ፡ የተጣለ።
ደንቈሬ፡ የደንቈሮ፡ ወገን፡ ጐበዝ፡ ቢመቱት፡ የማይሰማ፡
ፍንክች፡ የማይል፡ አይፈር፡ ለፊቱ። (ግጥም)፡ የወግዳ፡ ጐበዝ፡ ስሙ፡ ደንቈሬ፡ ይደበደባል፡
ቁሞ፡ እንደ፡ በሬ።
ደንቈር፡ (ጐረጥ)፡ ቍልቋል፡ ቈርቍሮ፡ የሚገባ፡ አረንጓዴ፡
አይነት፡ ወፍ፡ ደረተ፡ ወይባ፡ ዕሽ፡ ሲሉት፡ ከማሽላ፡ ላይ፡ ቶሎ፡ ስለማይበር፡ ደንቈር፡ ተባለ። ጐረጥን፡ ዱንቄን፡ ተመልከት።
ደንቈሮ፡ (ድንቅው፡ ጽሙም፡ አብድ)፡ የደነቈረ፡ ውለናም፡ አላዋቂ፡ ሰነፍ፡ ብልሃት፡
እርሙ፡ ጅል፡ (ማቴ፭፡ ፳፪። ፩ቆሮ፡ ፲፬ - ፲፩)።
ደንቈሮ፡ በባላ፡ አንጻር፡ ያለ፡ እንጨት፡ እንደ፡
ባላው፡ ድር፡ የማይሠባጠርበት፡ ብልኀት፡ አልባ፡ ፈትሉም፡ ደንቈሮ፡ ይባላል። ባላና፡ ደንቈሮ፡ እንዲሉ።
ደንቈሮነት፡ ውለናምነት።
ደንቈሮዎች፡ ደንቈሮች፡ ደናቍርት፡ ውለናሞች፡ ዕውቀተ፡ ቢሶች፡ (ኢሳ፵፪፡ ፲፰። ኤር፲፡ ፰)።
ደንቋሪ፡ የሚደነቍር።
ደንቋይ፡ የደነቈለ፡ የሚደነቍል፡ ዘንቋይ፣ አንቋሪ፡ ዛንቂል።
ደንበር፡ መደንበር።
ደንበር፡ ደንበር፡ አለ፡ እንዳገኘ፡ ረገጠ፡ እውርኛ፡ ሄደ፡ ተራመደ።
ደንበር፡ ደንባራ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ጠንበር፡ ጠንባራ፡ እውር።
ደንበር፡ ድንበር (ዘንቡር)፡ በርስት፡ በመሬት፡ በርሻና፡ በርሻ፡ ባገር፡
በወረዳ፡ በአውራጃ፡ በቀበሌ፡ መካከል፡ ያለ፡ የማይታረስ፡ የማይፈልስ፡ የምድር፡ ወሰን፡ ትክል፡ ድንጊያ፡ ተራራ፡ ባሕር።
ደንበርበር፡ አለ፡ ተግተመተመ።
ደንበሾ፡ ድልብ፡ ሻጋታ፡ እህል።
ደንበቆ፡ መቃ፡ መስዬ፡ በዥረት፡ አቅራቢያ፡ የሚበቅል።
ደንበኛ፡ (ኞች)፡ ዋና፡ ሰው፡ ወይም፡ ለስራው፡ ደንብ፡ ያለው፡
ሰራተኛ፡ ወታደር፡ በደንብ፡ የሚሰራ፡ የሚተዳደር፡ ባለደንብ።
ደንበኛ፡ ሰው፡ ታማኝ፡ ቁም፡ ነገራም፡ ሀቀኛ።
ደንበኛ፡ ዘወትር፡ ከአንድ፡ መደብር፡ እቃ፡ የሚገዛ፡
ሰው።
ደንበጃን፡ የብርሌ፡ ገንቦ።
ደንቢ፡ (ዎች)፡ የደነባ፡ የሚደነባ፡ ደንብ፡ አውጪ፡ ህጋጊ፡
ወሳኝ።
ደንባሪ፡ የደነበረ፡ የሚደነብር፡ የሚሸሽ።
ደንባቂ፡ የደነበቀ፡ የሚደነብቅ፡ ቀጂ።
ደንብ፡ (ቦች)፡ ህግ፡ ውሳኔ፡ ትእዛዝ፡ አዋጅ፡ የመንግስት፡
ስራ።
ደንብ፡ እግር፡ እግሩ፡ ያበጠ፡ የደነደነ፡ የተድበለበለ፡
ሰው።
ደንብ፡ ወታደር፡ ወር፡ ተራ፡ የሚገፋበት፡ የዘብ፡
ወይም፡ የስራ፡ ክፍል።
ደንብ፡ ያልጋ፡ ራስጌና ግርጌ፡ ጋድም።
ደንቧ፡ መጮኸ።
ደንቧ፡ አለ፡ ጮኸ።
ደንቧ፡ ደንቧ፡ አለ፡ መላልሶ፡ ጮኸ የከበሮ፡ የነጋሪት።
ደንታ፡ ተስፋ፡ ጥቅም፡ አለኝታ።
ደንከሊ፡ (ዎች)፡ የነገድና፡ ያገር፡ ስም፡ የደንከል፡ ደንከላዊ።
ደንከል፡ (ትግ)፡ ውል፡ ገደብ፡ እድር።
ደንካራ፡ (ሮች)፡ ወልጋዳ፡ ወረኃ፡ እግረ፡ ድር።
ደንዞ፡ ከአፄ፡ ሠርጸ፡ ድንግል፡ በፊት፡ የነበሩት፡
ነገስታት፡ ደንዞ፡ ይባሉ፡ ነበር፡ ጃን፡ ሆይ፡ እንደ፡ ማለት።
ደንደሎ፡ (ገንዶራ)፡ ያባያ፡ መቅጫ፡ የንዶድ፡ ግንድ፡ ወይም፡
ላንቊሶ።
ደንደሳም፡ በማዥራቱ፡ ግድ፡ ያለበት፡ ሰው።
ደንደሳም፡ ደንደሳማ፡ (ሞች)፡ ባለ ደንደስ፡ የበሬ፡ አውራ፡ ወይም፡ ዥብ።
ደንደሳምነት፡ ደንደሳም፡ መሆን።
ደንደስ፡ (ትግ፡ አፋፍ)፡ ያልተወቀጠ፡ ወይፈን፡ ወፍራም፡ ማዥራት፡
ትከሻ፡ ጫንቃ።
ደንደስ፡ ያሞሌ፡ ጠርዝ፡ ዳር።
ደንደሶች፡ ትከሾች፡ ጫንቆች።
ደንደሬ፡ (ደንደራዊ)፡ ለስላሳ፡ ሴቴ፡ ኰሸሽላ፡ ወይም፡ ሌላ።
ደንደር፡ ኰሸሽላ፡ ኹለንተናው፡ እሾኸ፡ የሆነ፡ እንጨት።
ደንደሮ፡ (ዎች)፡ ወፍራምና፡ ሻካራ፡ ደደብ፡ ሴት።
ደንዳና፡ የደነደነ፡ ወፍራም።
ደንዳኔ፡ ወፍራምና፡ ሰፊ፡ አንዠት፡ የደንዳና፡ ደንዳናዊ፡
ማለት፡ ነው።
ደንዳኖች፡ የደነደኑ፡ ወፍራሞች።
ደንዳኝ፡ የሚደነድን፡ ወፋሪ።
ደንገላሳ፡ (ኦሮ)፡ በሶምሶማና፡ በሽምጥ፡ መካከል፡ ያለ፡ ግልቢያ።
ደንገል፡ (ሎች)፡ የመንኰራኵር፡ ዋልታ፡ እንብርቱ፡ መካከሉ።
ደንገል፡ በውሃ፡ ውስጥ፡ የሚበቅል፡ የገሳ፡ አይነት፡
ወፍራም፡ ሳር፡ እንደ፡ መቃ፡ ታንኳ፡ የሚሆን።
ደንገሎ፡ (ደንግ፡ ሎ)፡ ደረቅ፡ የገብስ፡ ቂጣ፡ ጨው፡ ያለበት፡
ጥጥር፡ የፈረስ፡ የበቅሎ፡ መኖ።
ደንገጥር፡ በጥበብ፡ ዳር፡ የሚጣል፡ ጥለት፡ የጥበብ፡
አሽከር።
ደንገጥር፡ ደንገጡር፡ (ጸዋሪተ ጌጽ)፡ የመቤቷን፡ ጌጥ፡ ባንገቷ፡ አጥልቃ፡ የምትሸከም፡
ገረድ፡ አሳሳች፡ እመቤት፡ መሳይ።
ደንገጥር፡ ገረድ ፣ ደነጋ።
ደንገጥሮች፡ (አእማት)፡ የንግስታትና፡ የወይዛዝር፡ ገረዶች፡ አሳሳቾች።
ደንጊያ፡ (ዎች)፡ በመሬት፡ ውስጥ፡ የሚገኝ፡ ጠንካራ፡ የምድር፡
አጥንት፡ ጥቁርና፡ ነጭ፡ ብና፡ አረንጓዴ፡ ባለብዙ፡ ህብር፡ ቦረቦጭ።
ደንጊያ፡ ልብሱ፡ ደንጊያ፡ የለበሰ፡ ኤሊ፡ የሚባል፡ አውሬ።
ደንጊያ፡ በግሩ፡ ሰነፍ፡ ሰው፡ ፍጥነት፡ እርሙ።
ደንጊያ፡ ከሰል፡ ከሰልን፡ ተመልከት።
ደንጊያ ከሰል: ፈረንጆች ምድርን ቈፍረው ከመሬት የሚያወጡት፡ እግዜር ያከሰለው የደንጊያ ከሰል፡ መርከብና ባቡር መንጃ፣ ማስኬጃ።
"ደንጊያ ከሰል ከክርስቶስ ልደት በፊት አንድ ሺሕ ዓመት ሺኖች ሥራ ይሠሩበት ነበር" ይባላል።
ደንጊያ፡ ድንጋይ ፣ በቁሙ፡ ደነጋ፡ ደነገየ።
ደንጋጊ፡ (ዎች)፡ የደነገገ፡ የሚደነግግ፡ ወሳኝ፡ ህጋጊ።
ደንጋጭ፡ ደንጋጣ፡ የሚደነግጥ።
ደንግ፡ ከወርቅና፡ ከብር፡ የተሰራ፡ የንግስታትና፡
የወይዛዝር፡ ያንገት፡ ጌጥ፡ ሽልማት፡ ቀለበት፡ መስቀል፡ አንባር፡ ድሪ፡ ጠልሰም፡ ድኮት፡ ግርጃ፡ ማርዳ፡ የመሰለው፡ ሁሉ።
ደንግ፡ ከደንጊያ፡ የሚገኝ፡ ፈርጥ፡ አልማዝ፡ ከሰደፍ፡
ከብርጋና፡ የሚወለድ፡ እንቁ።
ደንጐለት፡ (ደንግ፡ ሎቱ)፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ለደንጐላጕል፡ ወጣ፡ ገባ።
ደንጐሊጥ፡ (የሊጥ፡ ደንጊያ)፡ አጕል፡ ሰው፡ አመለ፡ መጥፎ።
ደንጐላጕል፡ (ደንጐል፡ አጕል)፡ አጕል፡ ደንጐል፡ ያለበት፡ ስፍራ፡ ሲረግጡት፡
የሚያስቸግር፡ ስርጓጕጥ።
ደንጐል፡ (ትግ፡ ደንጐላ)፡ ገለብ፡ ቋጥኝ።
ደንጐሎ፡ ባለትልቅ፡ ፍሬ፡ ፫፡ አይነት፡ ጥቁር፡
ነጭ፡ ኢየሩሴ፡ መሳይ፡ አደንጓሬ፡ በይፋትና፡ በሐረርጌ፡ የሚበቅል።
ደንጐራ፡ በጫፉ፡ ማረሻ፡ በስሩ፡ ደንጊያ፡ የተዋደደበት፡
አጣና።
ደንጎች፡ ደንጊያዎች፡ ጌጦች፡ አልማዞች፡ ፈርጦች።
ደንጎዜ፡ በሺዋ፡ አውራጃ፡ በመንዝ፡ ውስጥ፡ ያለ፡
አገር።
ደንጓሪ፡ የደነጐረ፡ የሚደነጕር፡ ደዳቂ፡ ፈንቃይ።
ደንጓራ፡ ዘንኳራ፡ ነገሩ፡ ከሰው፡ የማ ይሰማማ።
ደንፊ፡ የደነፋ፡ የሚደነፋ፡ ፎካሪ።
ደንፋቂ፡ የደነፈቀ፡ የሚደነፍቅ፡ አልቃሽ።
ደንፍ፡ (ፎች)፡ ታህታይ፡ ጕበን፡ ሀርበኛ፡ እየደነፋ፡ የሚገባበትና፡
የሚወጣበት።
ደከመ (ዶኪም ደክመ): ለፋ፣ ጣረ፣ ታከተ፡ ሰነፈ፣ ላመ፣ ሰለቸ፡ መኼድ፣ መሥራት፣ መናገር አቃተው፣ ተሳነው፡ ኀይል ዐጣ፡ ዛለ፡ ለሞት ቀረበ፡ ስልም አለ (ዮሐ ፬:፮)። ዳከረንና ማሰነን እይ።
ደከመ: "ጠለሰን" የሚለውን ይመልከቱ።
ደከረ: ደቀነ፣ ገተረ፣ አቆመ፣ አዘገበ፣ ለጠጠ፣ አነጣጠረ፣ አቀረበ (የጦር፣ የቀስት፣ የእስኪት፣ የጠመንዣ)።
ደከር (ዐረ ዘከር፣ እስኪት ተባዕት፣ ዕብ ዛካር፣ ወንድ): ጥኑ፣ ጠንካራ። "ደከር ጐበና" እንዲሉ ሐረርጌዎች።
ደከነ (ደቀነ): ሰደረ፣ ደረደረ፣ እነባበረ፡ ደራረበ።
ደከከ (ደኀኀ): ዐጠረ፣ ድንክ ኾነ፡ ወፈረ።
ደከደከ (ደቀደቀ): አንደከደከ፡ ወፍራም ዶዮ ሠራ፣ ቀቀለ። ደከከን እይ።
ደከደክ፣ ደክዳካ: የተንደከደከ።
ደካ (ደቅሐ፣ ደወለ): ደቃ፣ ለካ፣ ረገጠ፣ ወሰነ፣ ከለለ። ደነበረን እይ።
ደካ: ዠለጠ፣ ኣለፋ።
ደካሚ: የሚደክም፣ የሚታክት (ኢሳ ፩:፭)።
ደካማ(ሞች): የደከመ፡ ታካች፣ ሰነፍ፣ ስልቹ፡ ቈማጣ (መዝ ፻፭:፴፯፣ ኢሳ ፲፬:፲፣ ሕዝ ፲፮:፴፣ ማቴ ፲፩:፳፰፣ ሮሜ ፲፬:፪፣ ፩ቆሮ ፩:፳፯)።
ደካማ: ጕልበቱ ያለቀ ሰው፣ ዐቅመ ቢስ።
ደካማነት: ደካማ መኾን፡ ታካችነት፣ ሰነፍነት።
ደካሪ: የደከረ፣ የሚደክር፡ ገታሪ፣ አዝጋቢ፣ አቅራቢ።
ደካኝ(ኞች): የደከነ፣ የሚደክን፡ ሰዳሪ፣ ደርዳሪ፣ ኣነባባሪ።
ደካካ: ድኁርና ወፍራም፡ ሲኼድ መንገድ ጠብ የማይልለት (ልጅ ወይም ዐዋቂ)።
ደኬ: ውሃ ያነሰው ዶዮ፡ የሹሮ ወጥ።
ደኬ: ዶዮ (ደከደከ)።
ደክደክ አለ: ተንደከደከ።
ደኮ: የለፋ፣ ደበሎ፣ ድብዳብ።
ደኳኳ: ብርኵማ፡ መዳኺያ (መንፈቀቂያ)።
ደኸየ (ደኀየ): ዐጣ፣ ተቸገረ፡ ድኻ ኾነ፡ ከሌላው አነሰ።
ደወለ (ደዊል ደወለ): አቃጨለ፣ አንኳኳ፣ ጸፋ፡ ድው ድም አደረገ፡ ደወል መታ፡ ከመቅደሰ ኦሪት ከቤተ ክሲያን ተጠጋ፣ ተማጠነ። ጠዘለ፣ መደወተ (ሰውን፣ ከብትን)።
ደወለ: ጨመረ። "ዶለን አይ፡ የዚህ ዘር ነው"፡ ፪ኛውን "ከለለ" ተመልከት።
ደወል(ሎች): መርዋ፣ ነጋሪት፣ ከበሮ (ዕንጨት፣ ደንጊያ)፡ የስልክ ቃጭል (ደወል)።
ደወረ (ዘወረ): አዞረ፣ አሽከረከረ፡ በጭን በጣት ጸፋ (ማዳወሪያን፣ እንዝርትን)።
ደወረ: ጠቀለለ፣ አቀለመ፣ አጠነጠነ (የጥጥ፣ የጠጕር፣ የማግ፣ የሐር፣ የጥለት)።
ደወየ (ተደወየ): ታመመ፣ ተበሸተ፡ ደዌ ዐደረበት፡ ቁመቱ ዐጠረ።
ደዋሪ(ሮች): የደወረ፣ የሚደውር፡ አዟሪ፣ አጠንጣኝ፣ አቅላሚ።
ደዋይ(ዮች): የደወለ፣ የሚደውል፡ ፍሬ፣ ሰሞነኛ፣ ተማጣኝ፡ መቺ።
ደዋይነት: ደዋይ መኾን።
ደዋጨት: የቅጠል ስም፡ በወይናደጋ የሚበቅል የንብ አስል ዐይነት (የተስቦ መድኀኒት)።
ደዌ ሥጋ: የሥጋ ደዌ፡ ቢስ ገላ (ቍምጥና)።
ደዌ: በሽታ (ደወየ)።
ደዌ: በቁሙ፡ በሽታ (የቈየ የኖረ ዕመም)።
ደዌያም ኾነ: ተደወየ።
ደዌያም: ባለደዌ፣ ታማሚ።
ደውዳዋ: አደዝዳዥ፣ ምናውዬ።
ደዘለ (ደለዘ): ጠዘለ።
ደዘደዘ (ጠዘጠዘ): ከበሮ መታ፣ ጠዘለ፣ ወቀጠ።
ደዘደዝ፣ ደዝዳዛ: ምድርን በርጊጫ የሚደዘድዝ፡ ደውዳዋ።
ደዝዳዥ: የደዘደዘ፣ የሚደዘድዝ፡ መቺ፣ ጠዛይ።
ደይን (ደየነ): ሲኦል፣ የኵነኔ ስፍራ። "በግእዝ ግን ፍርድ ማለት ነው"። ዕለትን ተመልከት።
ደይን ወረደ: ሲኦል ወረደ፣ ገባ። "ነፍሴ ደይን ትውረድ" እንዲል ማለኛ።
ደደ: ሰረቀ፣ ወሰደ።
ደደ: ጠጠ፡ ከሥር ጨርሶ ቈረጠ፣ ጠረገ ሥጋን፣ ዕንጨትን።
ደደረ (ትግ ፀፀረ): ጠጠረ፣ ደረቀ፣ ጠና፣ ጠነከረ (የውስጥ እጅና እግር፡ የበሬ ትከሻ፡ ያጋሰስ ዠርባ)።
ደደር: በሐረርጌ አውራጃ ያለ አገር።
ደደቀ (ደዲቅ ደደቀ): ወጋ፣ ፈነቀለ፣ ደነጐረ፣ ገለበጠ፣ ዕዳሪ አወጣ።
ደደቆ: ኵልኵልት ወዶማ፡ የበግ ዐንገት ዕብጠት (ዶዶት)።
ደደበ: ደረቀ፣ ደደረ።
ደደብ (ስድብ): ሲነግሩት የማይሰማ፡ ዕውቀት የማይገባው፡ ልበ ድፍን ሰው።
ደደብ(ቦች): ከቈዳ ጋራ ያለ ደረቅ ሥጋ ዐብሮ የተገፈፈ።
ደዳቂ(ዎች): የደደቀ፣ የሚደድቅ፡ ፈንቃይ፣ ደንጓሪ።
ደድ ሌባ: ምንም ሳያስቀር ጠርጎ የሚወስድ ሰራቂ።
ደድ: ደዶች፡ የደደ፣ የሚድድ፡ ጠጣ።
ደጀ ሰላም: ከተም በር። "ደጅ ያሠኘው ዐውዱ አደባባዩ ነው" (መሳ ፲፮:፫፣ ሕዝ ፵:፯:፱)።
ደጀ ሰላም: የሰላም ደጅ፡ መሳለሚያ (የቤተ መቅደስ የቤተ ክሲያን መሳሚያ)፡ የወንዶች መግቢያ፣ የሰላምታ መቀባበያ፡ የመክፈለት መሳተፊያ ቤት። "ደጅ የተባለው ማርገጃው ነው"። "ሲበዛ ደጅ ሰላሞች ይላል"።
ደጀ ብርሃን (አንቀጸ ብርሃን): በስተምሥራቅ ያለ የቤተ ክሲያን ጓሮ በር (የካህናት መግቢያ)።
ደጀ ብርሃን: ቤተ ልሔም ምስጢር ቤት።
ደጀ ጠኒ (ጸናሒ): በደጅ የሚቀመጥ፣ የሚቈይ፡ ሥራ ፈላጊ።
ደጀኔ: የሰው ስም፡ የኔ ደጀን።
ደጀን (ደጊን ደገነ): በስተኋላ የሚጠብቅ፡ የኋላ ዘበኛ፡ ረዳት ጦር ሰራዊት። "ትርጓሜው (ዴጋኒ) 'ተከታይ' ማለት ነው" (፪ዜና ፲፫:፲፫፣ ፳:፳፪)። "ወቦን ተመልከት"።
ደጀኖች: ተከታዮች፣ ጭፍሮች።
ደጃች: ዝኒ ከማሁ ለደጃዝማች፡ የጽሑፍና የቃል ማሳጠሪያ (ኹለት ፊደል በመጕረድ)፡ ፊደሎቹም "ዝማ" ናቸው።
ደጃዝማች (ደጅ አዝማች): የሹመት ስም፡ በራስና በፊታውራሪ መካከል ያለ የጦር አለቃ። "ትርጓሜው 'ዋና ትልቅ አዝማች' ማለት ነው፡ ጀና ገ ይወራረሳሉና"። "ደግ አዝማች" እንዲል ትግሬ።
ደጃዝማቾች: ሻለቆች፣ የጦር መኰንኖች።
ደጃፍ (ደጅ አፍ): በመቃን መካከል ያለ ክፍት በር፡ የደጅ መንገድ፡ አፈ ደጅ (በራፍ)። "ደጃፍ የመለሰው ማጀት የጐረሠው" እንዲሉ።
ደጃፍ: መዝጊያ (ዘፍ ፲፱:፱)።
ደጅ (ዴዴ): ውጭ፣ ሜዳ (ከቅጥር በአፍኣ ያለ ስፍራ)። "ገገምተኛው እደጅ እቤት ይላል"። "እሰር በፍንጅ፡ ጣል በደጅ" እንዲሉ። "ሲበዛ ደጆች ያሠኛል" (መዝ ፹፯:፪፣ ኢሳ ፵፭:፩:፪)።
ደጅ መታ: መዝጊያን አንኳኳ፡ እጁን ጸፋ።
ደጅ አጋፋሪ: የውጭ፣ ያደባባይ ከልካይ።
ደጅ ይጥኑ: የሴት ስም።
ደጅ ጠና (ጸንሐ): በደጅ ተቀመጠ፣ ቈየ፡ ሹመት ሽልማት ፈለገ፡ ዘወትር በደጅ ታየ፣ ተገኘ።
ደጅ ጥናት (ጽንሐት): በንጉሥ፣ በመኰንን አደባባይ መገኘት፣ አለመታጣት።
ደጅ: መዝጊያ፣ በር። "ደጅ ምቱ ይከፈትላችኋል" (ማቴ ፯:፯:፰፣ ዘፍ ፮:፲፮፣ ፲፱:፮:፲:፲፩፣ ዮሐ ፲:፯:፱፣ ፳:፲፱:፳፮)።
ደጅ: አደባባይ (ዘፍ ፲፬:፩)።
ደገለ (ዐረ ደጀለ፣ ሸሸገ፣ ደበቀ): ቂምን በልቡ አሳደረ፣ አኖረ።
ደገለለ: ጠቀለለ፣ ጠመጠመ፡ ዘንዶ አስመሰለ፡ አከበበ።
ደገላ (ኦሮ): ቋያ ሣር፣ ቅጠላቅጠል፡ ዳዋ፣ ክረምት አፈራሽ።
ደገሌ: ማቶት (ደገለለ)።
ደገሌ: የጋን፣ የጣራ፣ የዳቦ ማቶት፡ ጫፍና ጫፉ የገጠመ ክብ ጥምጥም ሥራ። ፪ኛውን "ዘንዶ" እይ።
ደገል ገባ: ቂም ያዘ።
ደገል: ቂም፣ በቀል።
ደገመ (ደጊም፣ ደገመ): በቀስታ፣ በለኈሳስ ድምጥ ሳያሰማ አነበበ፣ ጸለየ።
ደገመ: መለሰ፣ አከለ፣ ጨመረ። "ጣመኝ ድገመኝ" እንዲሉ። (ግጥም): "ሽንኵርት አንድም በሉት ደገሙትም ገማ፡ የተባባልነውስ አልቀረም ተሰማ"።
ደገመ: ኹለተኛ ዐረሰ፣ ዐየመ፣ ቀበቀበ።
ደገመ: ዘለቀ፣ ወጣ፣ ተማረ፣ ለመደ፣ ጨረሰ፣ ዐወቀ። "ዳዊት ደገመ" እንዲሉ።
ደገማ፣ ድግሚያ: መድገም፡ እከላ፣ ጭመራ።
ደገሰ: ቈላ፣ ፈጨ፣ ጠመቀ፣ ጋገረ፡ መብል መጠጥ አዘጋጀ፣ አሰናዳ፣ አቀናበረ። (ተረት): "እግዜር ሳይደግስ አይጣላም" (ኢዮ፩:፲፱፣ ፵፪:፬–፲፭)።
ደገሠ: አዘጋጀ (ደገሰ)።
ደገነ (ዴገነ): ደጋንን፣ ቀስትን አጐበጠ፡ በዥማት፣ በገመድ አሰረ፡ አበጀ፣ አዘጋጀ፡ አዘገበ፣ ደከረ። ጠመንዣን አጐረሠ፡ ቃታ ያዘ፣ ዐለበ፣ አነጣጠረ። (ነፍጥን የቀስት፡ ጥይትን የወስፈንጠር፡ ቃታን የገመድ ምሳሌ አደረገ)።
ደገኛ(ኞች): የደጋ፡ በደጋ ተወልዶ የሚኖር (አውሬ፣ ከብት፣ ሰው)።
ደገኛ: የደግ፡ ዋነኛ፣ ዐይነተኛ።
ደገዘ (ደነገዘ): መሸ፣ ጨለመ (ላይን)።
ደገዛ: ኵብኵባ፡ የኵብዙባ ወገን።
ደገደገ (ትግ ደግደገ): ወቀጠ፣ አደቀቀ። "ደቀደቀን" ተመልከት።
ደገደገ (ደግደገ): ደከመ፣ ከሳ፣ ኰሰሰ፣ ተጐዳ፣ ጠቈረ (የሰውነት) (ግእዝ)።
ደገደገ ብለኸ ድግድግን፣ አርባን፣ ሥጋን፣ ሠላሳን ተመልከት። (አዝማሪ): "ከፈሪም ፈሪ ፈሪ ይበልጣል፡ እኒያ ሲመጡ ሸሽቶ ያመልጣል"።
ደገደገ: ተጣበቀ፣ ተላከከ (የሞራ፣ የቅቤ)።
ደገደገ: አደፈ፣ ቸከ፣ ልማም ያዘ (የጥርስ)።
ደገደገ: ወየበ፡ ፈዘዘ (ያይን)።
ደገገ: አላቀ፣ አበለጠ፡ አኰራ፣ ዐጀረ (ገቢር)።
ደገገ: ደግ ኾነ፡ ከክፋት፣ ከተንኰል፣ ከሐሜት፣ ከሥሥት፣ ከክፉ ነገር ኹሉ ራቀ (ተገብሮ)።
ደገፈ: የገደፈ ተቃራኒ፡ ዐቀበ፣ ያዘ፣ ዐግዘ፣ ረዳ፡ እንዳይወድቅ አደረገ።
ደገፉ፣ ደገፌ: የሰው ስም። "ደገፋው" የኔ ደገፍ ማለት ነው።
ደገፋ፣ ድጋፌ: የወንድ መጠሪያ ስም፡ "ድጋፌ" ግን ለሴትም ይኾናል።
ደገፋ: ኀይል፣ ጥንካሬ፣ ብርታት፣ በረከት፣ ረድኤት (ከንጀራና ከውሃ የሚገኝ) (ኢሳ፫:፩)።
ደገፋ: ድጋፍ፡ ባላ፣ ወጋግራ፣ ምሰሶ፣ ተራዳ፣ ያልጋ ሸንኰር፡ ትራስ፣ መከዳ፣ ግንብ፣ ግድግዳ፣ ወንበር (፩ነገ ፯:፳፰:፴:፴፪)።
ደገፍ (ናህብ፣ ድንጋግ): ዐቃባ፣ ቃሊብ፣ የወንዝ ዳርና ዳር ዠማው። "ካፍ እስከ ደገፉ ጢም ብሎ መልቷል"።
ደገፍ አለ: ተደገፈ።
ደገፍ አደረገ: ደገፈ።
ደገፍ: ያዝ፡ መደገፍ።
ደገፎች (ድጋፎች)
ደጊመ ቃል: ቃልን፣ ፊደልን መመለስ፡ ኹለተኛ መናገር (ወንዛወንዝ፣ ቅጠላቅጠል)።: "ኼደ፣ ነጐደ፡ ዐረገ፣ ወጣ"። "ነደዶ፣ ነበበ፡ የመሰለው ኹሉ"። "ነደደንና ነበበን የመሰለ ግስ፡ የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱ፡ በረረ፣ ይበር፣ ይበራል፡ ገረረ፣ ይገር፣ ይገራል፡ ጠመመ፣ ይጠም፣ ይጠማል፡ ተመመ፣ ይተም፣ ይተማል" ቢል እንጂ "ይበርር፣ ይበርራል፡ ይጎርር፣ ይገርራል፡ ይጠምም፣ ይጠምማል፡ ይተምም፣ ይተምማል" አይልም። ቢልም የስሕተት ስሕተት ነው። "ፊደልን ጐርዶና አሳጥሮ መናገር ስንኳን ባማርኛ በግእዝ አለና"።
ደጊም: መድገም።
ደጋ (ትግ ደጕዓ): አስታ፣ ጓሳ፣ ጦስኝ፣ ያበባ እኸልና የብር እኸል የሚበቅልበት ላይኛ፣ ከፍተኛ አገር (እንደ ጣርማበርና እንደ መገዘዝ ያለ)፡ የመንግሥተ ሰማይ ምሳሌ፡ ወይም በቈላና በዋና ደጋ መካከል የሚገኝ (እንቧጮ ከስክሶ፣ ብሳና ከወሎ፣ ወይራ፣ ጥድ፣ ሽነት የሚገኝበት)፡ እኸል በያይነቱ (አገዳ ጭምር) የሚኾንበት (ወይናደጋ) (ጮቄ)። (ተረት): "ካገር ደጋ፡ ከመኝታ ዐልጋ"።
ደጋ: ደገኛ ።
ደጋሌት: ነጭ ማሽላ፡ ጨረቂት ወገሬ።
ደጋሚ(ሞች): የደገመ፣ የሚደግም፡ የሚያነብ፡ አንባቢ፣ ጸላይ ካህን፣ ተማሪ። "ዳዊት ደጋሚ" እንዲሉ።
ደጋሚ: አስማተኛ፣ መሠሪ፣ ዐዚማም (መክ፲:፲፩)።
ደጋሽ(ሾች): የደገሰ፣ የሚደግስ፡ አዘጋጂ፣ አቀናባሪ።
ደጋን ወገብ: ጐባጣ ሰው፡ ወገበ ደጋን።
ደጋን(ኖች) (ዲጋን): የጐበጠ ዕንጨት፡ ጥጥ ጠጕር መንደፊያ (ቅስት)፡ ቅሥፍ መሳይ።
ደጋን: ደጋን።
ደጋኝ(ኞች) (ዴጋኒ): የደገነ፣ የሚደግን፡ አጕባጭ፡ አነጣጣሪ።
ደጋገመ: የደገመ ድርብ፡ አነባበበ፣ መላለሰ፣ ጨማመረ።
ደጋገፈ: መላልሶ ደገፈ።
ደጋጋ (ኦሮ): ጥርሱ ያደገ፣ የረዘመ።
ደጋግ(ጎች): መልካካም የግብር፣ የጠባይ። "ደጋግ ሰዎች" እንዲሉ።
ደግ (ቀዳሚ): ትልቅ፣ ዋና ባላባት። "አንድ ከደግ ተወለድ፣ አንድ ከደግ ተጠጋ" እንዲሉ። ትግሬም "ትልቅ" ሲል "ደግ" ይላል። "ደጅን" ተመልከት።
ደግ ሠራ: መልካም አደረገ፡ ለተራበ አበላ፡ ለተጠማ አጠጣ፡ ለታረዘ ለበሰ፡ የታሰረ አስፈታ።
ደግ ሰው: የሰው መጨረሻ፡ ጻድቅ፣ አይቈረቊሬ።
ደግ ነው: በጎ ነው፡ ተሽሎታል።
ደግ ነው: ጥሩ ነው፡ ማለፊያ ነው።
ደግ አደረገ: አበጀ፣ አሳመረ።
ደግ ዋለለት: ረባው፣ ጠቀመው።
ደግ ጊዜ፡ የሰላምና የጤና ዘመን።
ደግ(ጎች): ቸር፣ ነባይ፣ ማለፊያ፣ መልካም፣ ቁም ነገራም፣ ሐቀኛ፣ ቅን፣ እውነተኛ ሰው፡ ዐጥንቱን የሚቈራኙት።
ደግ: ቸር፣ ደገገ።
ደግ: የትዛዝ መልስ፡ ዕሺ፣ በጎ፣ በጄ።
ደግሞ: ተምሮ፣ አንብቦ፣ ዐውቆ።
ደግሞ: ዳግመኛ፡ ንኡስ አገባብ።
ደግነት: ቅንነት፣ ትሑትነት፣ ታዣዥነት።
ደግዳጊ: የሚደገድግ፡ ተላካኪ።
ደግዳጋ (ድግዱግ): የደገደገ፡ የከሳ፣ የኰሰሰ፡ የተላከከ፣ ያደፈ።
ደግፍ: የዦሮ ግንድ በሽታ፡ ዕብጠት። "ዦሮ ደግፍ" እንዲሉ።
ደጐለ (ትግ): አዳፈነ፣ ቀበረ። "ጀጐለን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው።
ደጐመ (ጠቈመ): ረባ፣ ጠቀመ፣ ዐገዘ፣ ረዳ፣ ደገፈ፡ ዐልፎ ዐልፎ ሰጠ (በልክ፣ በመጠን)።
ደጐሰ (ደጐጸ): የመጽሐፍን ገበታነት አለበሰ፡ ወይም በተንቤን በባሕር ዐረብ አስጌጠ፣ ሸለመ። "ለሰገባ ሲኾን 'ሸመጠጠ' ይላል"።
ደጐሠ: አስጌጠ (ደጐሰ)።
ደጐባ (መሓዝ): ጐበዝ ወጣት፡ ሦታ፡ ትምርት ያልገባው፣ ያልዘለቀው ሰው፡ ወገበ ነጭ፡ ጸናጽል፣ መቋሚያ አቀባይ በከበሮ ቤት የሚቆም።
ደጐባ (ደጐብያ): ኵብኵባ (ክንፍ የሌለው አንበጣ፡ ከማኰብኰብ በቀር መብረር የማይችል) ያንበጣ ተወራጅ።
ደጐቤ (ደጐባዊ): የደጐባ ወገን ዐይነት (ዮኤ፩:፬)።
ደጐቦች: ብኵቦች፣ ጐበዛዝት።
ደጎጎ (ኦሮ): ጐታ፣ ጐተራ (ከንጨት፣ ከጭቃ የተበጀ)።
ደጓሚ(ሞች): የደጐመ፣ የሚደጕም፡ ዐጋዥ፣ ረዳት፣ ደጋፊ፣ ሰጪ።
ደጓሳ: ወፍራም፣ ቋራም ዱላ።
ደጓሽ(ሾች): የደጐሰ፣ የሚደጕስ፡ ሸላሚ፣ አስጊያጭ፣ ተማሪ፣ ደብተራ፣ ካህን።
ደጭ (ኦሮ): መሬት፡ የመሬት ስም።
ደጭ መረጭ: የቅጠል ስም፡ ፍሬው አንዠት የሚመስል የዕባጭ መድኀኒት።
ደጭ መሬት: መረጭ፣ አንዠት፡ የመሬት አንዠት ማለት ነው። መረጭን ተመልከት።
ደፈ፡ ራሰ፡ ጨቀየ፡ ተጨማለቀ።
ደፈ፡ እብቅ፡ ገርገመጥ።
ደፈረ፡ (ደፊር፡ ደፈረ)፡ ጨከነ፡ ሰደበ፡ ነጠበ፡ ናቀ፡ አቀለለ፡
አዋረደ፡ አላቅሙ፡ ሠራ፡ (ዮሐ፳፩፡
፲፪። ሮሜ፲፡ ፳)።
ደፈረ፡ ሴትን፡ ነካ፡ ደረሰ፡ አለውድ፡ በግድ።
ደፈረ፡ አበዛ፡ ቈለለ፡ ደብር፡ አስመሰለ።
ደፈረሰ፡ (ደፈረ፡ ፈረሰ)፡ ተበጠበጠ፡ እተለ፡ ጐሸ፡ አደፈ፡ ጐደፈ፡
ቀላ፡ ተበላሸ። ካልደፈረሰ፡ አይጠራም፡ እንዲሉ። ሰውየው፡ መጠጥ፡ ስላበዛ፡ አይኑ፡ ደፍርሷል።
ደፈረሰ፡ ታወከ፡ ተሸበረ፡ አገሩ፡ ከተማው።
ደፈረሱ፡ የሰው፡ ስም፡ ጠላቶች፡ ታወኩ፡ ተሸበሩ፡
ማለት፡ ነው።
ደፈራ፡ መድፈር፡ (፪ሳሙ፡ ፯ ፥ ፳፯)።
ደፈራ)፡ አንደፋራ፡ ባፈር፡ ላይ፡ አንደፋደፈ፡ አንፈራፈረ፡
አንከባለለ፡ አንደባለለ።
ደፈር፡ (ሮች)፡ የተራራ፡ የገመገም፡ ራስ፡ ጫፍ፡ ከፍታው፡
ምንም፡ ቢርቅ፡ በማየት፡ የሚደፈር፡ ሰማይ፡ ደጋፊ፡ የሚመስል። ጠፈር፡
ደፈር፡ እንዲሉ።
ደፈቀ፡ ቈበርን፡ አረፋን፡ ካፍ፡ አወጣ። አረፋ፡ ደፈቀ፡ እንዲሉ።
ደፈቀ፣ ዘፈቀ።
ደፈቀ፡ ዘፈቀ፡ እውሃ፡ ውስጥ፡ ነከረ፡ አገባ፡
ወደ፡ ታች፡ አለ፡ ሰውን፡ ሌላ፡ ነገርን።
ደፈቀ፡ የምስር፡ ንፍሮን፡ ዳጠ፡ ፈጨ፡ በመጠኑ፡
አላመ።
ደፈነ፡ (ደፊን፡ ደፈነ)፡ ቀበረ፡ መረገ፡ መላ፡ ጠቀጠቀ፡ ሸፈነ፡
ወተፈ፡ ዘጋ፡ ጨፈነ፡ አለበሰ፡ የውሃ፡ የገንዘብ፡ የነገር፡ የሬሳ፡ የዦሮ፡ የዐይን፡ (ዘፍ፳፮፡ ፲፭፡ ፲፰)።
ደፈነ: ዐባ፣ ሰወረ፣ ደበቀ፣ ቀበረ (ዘጸአት ፪፡ ፲፪። ፪ኛ ዜና መዋዕል፡ ፳፪፡ ፲፩፡ ፲፪። ምሳሌ ፩፥ ፲፩። ኢሳይያስ ፵፱፡ ፪)። "(ተረት)፡ ሆድና ግንባር አይሸሸግም።"
ደፈና፡ መረጋ፡ ጭፈና።
ደፈና፡ ጠቅላላ፡ ሙሉ፡ መክፈልና፡ ማጕደል፡ መለየት፡
ሳይኖር። ሰውን፡ በደፈናው፡ ጥራ፡ እንዲሉ።
ደፈደፈ፡ (ደፍደፈ፡ አፈር፡ ከደነ፡ አለበሰ፡ የእድሞ)፡ ለጠፈ፡ ቀባ፡ መረገ፡ ቍስልን፡ በመድኀኒት።
ደፈደፈ፡ ጥንስስንና፡ ቂጣን፡ እንኵሮን፡ ቀላቀለ፡
አዋዋደ፡ ውሃ፡ ጨምሮ፡ ባንድነት፡ አሸ፡ ለወሰ፡ ድፍድፍ፡ አደረገ።
ደፈደፈ፡ ጥፋቱን፡ በሰው፡ ላይ፡ አደረገ፡ ላከከ።
ደፈደፍ፡ ደፍዳፋ፡ የተንደፋደፈ፡ የሚንደፋደፍ፡ ርብትብት።
ደፈጠ፡ ሰካ፡ አዋደደ፡ ገጠመ።
ደፈጠ፡ የተልባ፡ ነዶን፡ በደንጊያ፡ አሸ፡ ፈልፈለ።
ደፈጠ፡ ጐነበሰ፡ ተደበቀ፡ ሸመቀ።
ደፈጠጠ፡ ረገጠ፡ ዳመጠ፡ ረመጠጠ፡ ዝንጀሮ፡ አስመሰለ፡
አፍንጫን።
ደፈጠጠ፡ ጨቈነ፡ አስተኛ፡ ተጫነ፡ ወፈለቀ፡ አን።
ደፈጠጥ፡ ደፍጣጣ፡ ድፍጥ፡ የተደፈጠጠ፡ ዳመጦ፡ አይጥ፡ ሰው። አፍንጫ፡ ደፍጣጣ፡ እንዲሉ።
ደፈጣ፡ ተጐንብሶ፡ የሚገቡበት፡ የራስጌ፡ በር፡
መሿለኪያ።
ደፈጨ፡ (ፈጪ)፡ ደቀቀ፡ የገለባ።
ደፊ፡ (ዎች)፡ የደፋ፡ የሚደፋ፡ አፍሳሽ፡ ገልባጭ፡ ዘርጋፊ።
ደፊ፡ ዘርፍን፡ አስቀድሞ፡ ባለቤትን፡ የሚያስከትል፡
ፊደል፡ የ። አምላከ፡ ሰማይ፡ ንጉሠ፡ ኢትዮጵያ፡ ያለውን፡
የሰማይ፡ አምላክ፡ የኢትዮጵያ፡ ንጉሥ፡ የሚያሠኝ። ምስጢሩ፡
አዛዋሪ፡ እንደ፡ ማለት፡ ነው።
ደፋ፡ (ደፊዕ)፡ መድፋት።
ደፋ፡ (ደፍዐ)፡ አወደቀ፡ ፈነገለ፡ አፈሰሰ፡ ከነበለ፡ ዘቀዘቀ፡
ገለበጠ፡ ዘረገፈ።
ደፋ፡ ሴትን፡ ደፈረ።
ደፋ፡ ቀና፡ አለ፡ ወደቀ፡ ተነሣ።
ደፋ፡ በራሱ፡ ላይ፡ ዘውድን፡ ራስ፡ ቍርን፡ ጫነ፡
አደረገ፡ ተቀዳጀ፡ (፩ሳሙ፡
፲፯፡ ፭)።
ደፋ፡ አስቀመጠ፡ አኖረ፡ ተወ፡ አህያዬ፡ ቢደክምብኝ፡
እኸሌን፡ እከሌ፡ ቤት፡ ደፍቼው፡ መጣኹ። የስልቻው፡
አፍ፡ መዘቅዘቁን፡ ያስረዳል።
ደፋ፡ አንድ፡ ነገር፡ ለመግዛት፡ ብዙ፡ ገንዘብ፡
ከፈለ።
ደፋ፡ ወዳንድ፡ ፊት፡ አመዘነ፡ አንገቱን፡ አዘነበለ፡
አቀረቀረ።
ደፋ፡ ደፋ፡ አለ፡ ቸኰለ፡ ቶሎ፡ ቶሎ፡ አለ።
ደፋ፡ ዳቦ፡ ጋገረ፡ ያክንባሎን፡ በላዬ፡ መደፋት፡
ያሳያል።
ደፋሪ፡ የሚደፍር፡ አዋራጅ።
ደፋር፡ (ሮች)፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ የደፈረ፡ ጨካኝ፡ (መዝ፲፱፡ ፲፫። ምሳ፳፩፡ ፬። መክ፯ - ፰)። ደፋር፡ ወጥ፡ ያውቃል፡ ደፋርና ጪስ፡ መውጫ፡ አያጣም፡ እንዲሉ።
ደፋርነት፡ ደፋር፡ መሆን።
ደፋቂ፡ (ቆች)፡ የደፈቀ፡ የሚደፍቅ፡ ዘፋቂ፡ ነካሪ፡ አላሚ።
ደፋታ፡ ሸርታቴ።
ደፋና፡ ደፈነት፡ ማየት፡ የማይችል፡ የማትችል፡
ጨፋና።
ደፋኝ፡ (ኞች)፡ የደፈነ፡ የሚደፍን፡ ቀባሪ፡ መራጊ፡ ዘጊ፡
ሸፋኝ፡ ጉም።
ደፋጣ፡ ዶባቃ፡ ስፍራ።
ደፋጭ፡ የደፈጠ፡ የሚደፍጥ፡ ሸማቂ፡ አሺ።
ደፋጮች፡ ሸማቂዎች።
ደፋፈነ፡ ቀባበረ፡ መራረገ።
ደፋፋ፡ መላልሶ፡ ደፋ፡ አፈሳሰሰ።
ደፍ፡ (ፎች)፡ ታሕታይ፡ ጕበን፡ መቃኖች፡ በላዬ፡ የተዋደዱበት። በግእዝ፡ መርፈቅ፡ መድረክ፡ ይባላል። ዶፍ፡ ለላዕላይ፡ ጕበንም፡ ይነገራል።
ደፍ፡ አለ፡ ሳይበላ፡ ሳይጠጣ፡ ጦም፡ አደረ።
ደፍረስ፡ አለ፡ ጥቂት፡ ጐሸት፡ አለ፡ ወፈረ፡ አካሉ።
ደፍረስ፡ አተል፡ ወፈር።
ደፍራሳ፡ የደፈረሰ፡ የጐሸ።
ደፍራሽ፡ የሚደፈርስ፡ ውሃ፡ መጠጥ።
ደፍደፍ፡ አለ፡ ተንደፋደፈ፡ ክንፉን፡ አማታ፡ አርገበገበ።
ደፍደፍ፡ አለ፡ ቸኰለ፡ ተጣደፈ።
ደፍዳፊ፡ (ዎች)፡ የደፈደፈ፡ የሚደፍድፍ፡ ለጣፊ፡ ቀቢ፡ መራጊ።
ደፍጣጭ፡ የደፈጠጠ፡ የሚደፈጥጥ፡ የሚዳምጥ።
ደፍጥ፡ ድፍጥ፡ ያይጥ፡ ወጥመድ፡ የሚጫን፡ ተጫኝ፡ ጨቋኝ፡
ድንጋይ።
ደፎጭ፡ የዓሣ፡ ስም።
ዱሓ (ትግ ድኋ፣ ቦዳ): ሜዳ፣ ረባዳ፣ ዘባጣ፣ ጐድጓዳ፣ ሸለቆ፣ ቈላ፣ ታች (፩ነገ ፳:፳፰፣ ፪ነገ ፳፫:፲)።
ዱሃ: ረባዳ (ዱሓ)።
ዱለተኛ(ኞች): ዐድመኛ፣ ሤረኛ፣ ቋጣሪ (ብዙ ሕዝብ፣ ሸንጎኛ)።
ዱለታ: ነገር ቋጠራ።
ዱለት: መዶል (አዷዷል)፡ ጀመራ።
ዱለት: ስብሰባ፣ ዐድማ፣ ክፉ ምክር፣ ሤራ። (ተረት): "ዋና ከቤት፣ ጠበቃ ከዱለት"።
ዱለት: የበግ፣ የፍየል ጨጓራና ጕበት፡ የሽንጥ ሥጋ ተከትፎ እመጥበሻ ድስት የተመረ፡ "ወይም ድልኸና ቅቤ፣ ጨው፣ ቅመም የተዶለበት፣ የተቀላቀለበት፣ የታመሰ ክትፎ፣ ሥልሶ"። መቈናቍንን እይ።
ዱለት: ጨጓራና ጕበት (ጾለት)።
ዱለቻ (ኦሮ): ያረጀ ከብት።
ዱለኛ(ኞች): ባለዱላ፡ ተማች፣ ደብዳቢ።
ዱላ (ኦሮ): ዘመቻ፣ ጦርነት። "አባ ዱላ" እንዲሉ።
ዱላ ቀረሽ: ከፍ ያለ ጥል (ዱላ የቀረው)።
ዱላ(ዎች): ወፍራም በትር፡ መደወያ፣ መምቻ፣ መመድወቻ (በሎታ፣ ጐመድ፣ ሜንዶ፣ ቈመጥ)። "በጋልኛ 'ዘመቻን ዱላ' (አባ ዱላ) ማለት ከዚህ ይሰማማል"።
ዱላ: በትር (ደወለ)።
ዱላ: ያገር ስም (የሚገኘውም በሜጫ ክፍል)።
ዱላብ (ዐረ): ቁም ሣጥን (የገንዘብ ማድለቢያ)።
ዱልዱም: ሹለቱ የተቀነጠበ (የተዋጊ በሬ ቀንድ)።
ዱልዱም: ዝርዝር ያይዶለ የዶሮ ኰኰኔ (የሥጋ ቍንጮ)።
ዱማች፡ (መራቤቴ)፡ የጦም፡ ምሳ፡ ቀኝ።
ዱስ፡ ማንዱስ፡ ያንበሳ፡ ንጉሥ።
ዱስ፡ የዶሰ፡ ዘር፡ ነው። መንዲስን፡ እይ።
ዱስ፡ የፈስ ድምፅ። ፈሱ፡ ዱስ፡ አለ፡ እንዲሉ። ቶሰቶሰን፡ ተመልከት።
ዱሪ፡ ጥቍር፡ ፈረስ፡ (ዘካ፮፡ ፪፡ ፯)። በጋልኛ፡ ጕራች፡ ይባላል።
ዱር፡ (ዐረ፡ ዴር)፡ ከመንደርና፡ ካምባ፡ የራቀ፡ የተለየ፡ ስፍራ፡
ጠፍ፡ መሬት። ሲበዛ፡ ዱሮች፡ ይላል።
ዱር፡ ቤቴ፡ ለውላጅ፡ ፰ኛ፡ ለፍናጅ፡ ፯ኛ፡ የባሪያ፡
ዘር፡ የማን፡ ቤቴ፡ ልጅ፡ ቤቱ፡ ዱር፡ የኾነ፡ ዱር፡ አዳሪ።
ዱር፡ ደን፡ ዎማ፡ ጨለማ።
ዱርር፡ የተዶረረ፡ ኵሩ፡ ቍጡ።
ዱርሽት፡ (ዱር፡ ሸተት)፡ የሐረግ፡ ስም፡ ያረግ፡ ሬሳ፡ ዐይነት፡
የተስቦ፡ መድኀኒት፡ ግማታም፡ ክርፋታም፡ ቅጠል።
ዱሮ፡ ዘመን፡ የዱሮ፡ ዘመን።
ዱሮ፡ ፊት፡ ቀድሞ፡ አስቀድሞ፡ ጥንት። ዘንድሮን፡ አስተውል።
ዱሽ፡ (ሾች)፡ የእጅና፡ የእግር፡ ጣት፡ የሌለው፡ ሰው፡
ስለት፡ ወይም፡ ምች፡ ቍምጥና፡ የቈረጠው፡ ቈማጣ። ኵንትሽን፡
ተመልከት።
ዱቄት ፣ በቁሙ ፣ ደቀቀ።
ዱቄት፡ ዶቄት፡ ተፈጭቶ፡ ተሰልቆ፡ የደቀቀ፡ የላመ፡ የለዘበ፡
ኖራን፡ አመድን፡ ጥንጣንን፡ የመሰለ፡ እኸል።
ዱቅ(ን)ዱቂት፡ አምድማ፡ ትል፡ ከምድር፡ ወጥቶ፡ እንደ፡
ትዃን፡ ሰው፡ የሚበላ፡ እግር፡ የሌለው፡ እዦሮና፡ እንጨት፡ ውስጥ፡ ገብቶ፡ የሚደቀድቅ።
ዱቅ(ን)ዱቅ፡ በትረ፡ ቃቃን፡ ድጅኖ፡ አለት፡ የሚወጋ፡
የሚደቀድቅ፡ የሚበሳ፡ የሚነድል።
ዱቅንዱቂት፡ አምድማ፡ ትል ፣ ደቀደቀ።
ዱቅንዱቅ ፣ በትረ፡ ቃቃን ፣ ደቀቀ።
ዱቅዱቄ፡ ሲሄድ፡ የሚንደቀደቅ፡ ባለ፪፡ እግር፡ መኪና፡
ሠረገላ ፣ በኤሌትሪክና፡ በቤንዚን፡ ኀይል፡ የሚሽከረከር።
ዱበር (ኦሮ): የወንዝ ስም፡ ከጋራ ጐርፎ ተነሥቶ ወደ ሙገር ቈላ የሚወርድ ታላቅ ዥረት። "ወገረ" ብለህ "ሙገርን" እይ።
ዱቢት (ደባ): ዐጪርና ጐባጣ አፋ (፩ነገ ፲፰:፳፰)።
ዱቢት: የሽንብራ ባቡቴ እንክብል፡ "ዱባዊት" ማለት ነው። "ዱባን" እይ።
ዱባ (ዐረ ዱባህ): ክብና ሞላላ የኾነ ባር፣ ቅል፡ ቡጡ ተቀቅሎ፣ ፍሬው ታምሶ የሚበላ። ዱባ ፪ ዐይነት ነው፡ ፩ኛው አረንጓዴ፡ ፪ኛው ብ ይመስላል።
ዱባለ (ዕብ ዙብ): የሰው ስም፡ "ጠብ አለ" ማለት ነው።
ዱባለ (ዱብ አለ): እንደ ድብ ዘለለ፣ ወረደ፡ ጡብ አለ።
ዱቤ (ኦሮ): ብድር፣ ልቆ። "በዱቤ ገዛ" እንዲሉ።
ዱቤ (ዱባዊ): የዱባ ዐይነት፡ የማይፋጅ ያገራችን ወይም የፈረንጅ በርበሬ።
ዱቤ: ትልልቅ የፈረንጅ ሽንብራ።
ዱብ ዱብ አለ: ጨፈረ፡ ጠብ ጠብ፣ ጡብ ጡብ አለ። "ልጁ እንባው በረዶው ዱብ ዱብ ይላል"።
ዱብ: ከላይ ወደ ታች መውረድ።
ዱብሌ (ዱብላዊ): ፪ ጊዜ ፪ (፬) ቀንድ ያለው በግ።
ዱብሌ: ዐርቡ ወርዱ ስምንትያ የኾነ ልብስ።
ዱብሌ: የበግ ዐይነት፡ የዱር በግ። ምስጢሩ በቤት ላለው በግ "፪ኛ" ማለት ነው፡ በጕራጌ አገር ይገኛል። ኦሮም "ድኵላን" ዱብሌ ይለዋል።
ዱብል: ዕጥፍ መንታ ፊደል፡ "በረደደ፣ ሰገደደ፣ ገሰሰ፣ ፈሰሰ" እያለ ተጽፎ የሚገኝ ደጊመ ቃል።
ዱብራ (ኦሮ): የደረሰች ልጃገረድ።
ዱብታ: ዱብ ማለት፡ ዝላይ።
ዱብዳ (ዱብ ዕዳ): ያልታሰበ ዕዳ፡ ድንገተኛ ጥል፣ ቍጣ።
ዱንቄ፡ ቍልቋል፡ ፈልፍሎ፡ የሚገባ፡ ወፍ፡ እጅግ፡
የሚያምር፡ አረንጓዴና፡ ብጫ፡ መልክ፡ ደንቈር።
ዱካ: ፍለጋ (አሠረ ሰኰና)፡ የኰቴ፣ የጫማ ምልክት።
ዱያታም: በሽታም፣ በሽተኛ፡ የበሽታ ጐሬ፡ ደዌ የማይለየው (ተውሳካም)፡ ብዙ ዐይነት ዕመም ያለበት ሰው (ጤና ቢስ)።
ዱያት (ደዌያት): ደዌ፣ በሽታ፣ ዕመም። "ዱያት ውስጠ ብዙ ነው"።
ዱያት: ደዌ (ደወየ)።
ዱዳ: መናገር የማይችል፡ ራሱ ትክክል ያይዶለ ሰው። "ድዳን እይ"።
ዱዳ: ዘንድ፣ አጠገብ፣ ቀበሌ። "ደጅን ተመልከት"።
ዱዳሌብ(ም): የምድር ዕንብርት (ኢየሩሳሌም)። "መሬትን ከዱዳሌብ ውሃን ከናጌብ" እንዲሉ።
ዱድማ: ዝኒ ከማሁ።
ዱድማ: የማይናገር (ዱዳ)።
ዱግ(ጎች) (ኮሬ): ያቡን ወኪል፡ "ሙሉና ዱግ" እንዲሉ። ግእዝ "ኀዱግ" ካለው ቢወጣ ግን "በወኪልነት የተተወ" ማለት ነው።
ዱግ: ታናሽ ሹም (ዶገዶገ)።
ዱግ: የሻለቃ እንደራሴ፡ የበታች ዳኛ፡ ወይም በምስለኔና በጭቃ ሹም መካከል ያለ አዛዥ።
ዱጭ (ዳጠ): ድው። የሕፃን ኣካኼድ ከመዳኸ በኋላ።
ዱጭ ዱጭ አለ: ሲኼድ ድው ድው አለ።
ዱፍና፡ መልከ፡ ቢስ፡ ሴት።
ዲማ፡ (ኦሮ)፡ ቀይ፡ ከብት።
ዲሞትፎር፡ የነፍጥ፡ ስም ፣ የቀድሞ፡ ዘመን፡ ጠመንጃ።
ዲር ፣ ግንብ ፣ ደራ።
ዲር፡ (ዐረ፡ ዲርዕ)፡ ጥሩር፡ በግእዝ፡ ድርዕ፡ ይባላል።
ዲር፡ በሰንጠረዥ፡ መጫወቻ፡ ውስጥ፡ ያለ፡ ግንብ፡
(ማኅፈድ)።
ዲር፡ ድር፡ (ትግ፡ ደር)፡ የካብ፡ አጥር። ታይቶ፡ የመጣውን፡ በበር፡ ተሰውሮ፡ የመጣውን፡
በድር፡ (በዲር፡ በጥሩር)፡ ይመልሱታል። ግንብና፡ ካብ፡ አንድ፡ ወገን፡ ነው።
ዲር፡ ፈረሰኛ። ግንቡም፡ ፈረሰኛውም፡ የጦርነት፡ ስልት፡ ነው።
ዲቃላ፡ (ሎች)፡ የምንዝር፡ ወይም፡ የበረት፡ ልጅ፡ ማንዘራሽ፡
በሕግ፡ በሥርዓት፡ ከሚስት፡ ያልወለደ፡ በስርቆሽ፡ የመጣ፡ (ዘዳ፳፫፡
፪)። (ተረት)፡ ከልጅ፡ ክፉ፡ ዲቃላ፡ ከልብስ፡ መጥፎ፡
ነጠላ። ጠላት፡ ይገፋል፡ ዲቃላ፡ ራብ፡ ይከላል፡ ባቄላ፡
ቀን፡ ያሳልፋል፡ ነጠላ። (የነብር፡
ዲቃላ)፡ አነር፡ ትንሽ፡ ነብር፡ ዴሮ።
ዲቃላ፡ የማይበስል፡ ትንንሽ፡ ባቄላ። (ተረት)፡ ከባቄላ፡ አይጠፋም፡ ዲቃላ።
ዲቃላ፡ የዛፍ፡ ተቀጽላ፡ ወይም፡ ተገድራ፡ (ትግሬ)።
ዲቃላ፡ ግስ፡ ከጥሬ፡ መስም፡ የወጣ፡ አንቀጽ፡ አከለ፡
መካከል፡ አማከለ። ዘገበ፡
መዝጎብ፡ መዘገበ። አጠነ፡
ማጠን፡ አማጠነ። አተበ፡
ማተብ፡ አማተበ፡ የመሰለው፡ ሁሉ።
ዲበል (ሲሲት): ዘማች አሞራ በውዳቂ ላይ የሚደበል።
ዲብ (ደየበ): አነስ ያለ ቍልልታ፡ ያፈር፣ ያሸዋ ክምር፡ ይሳ።
ዲቦች: ቍልልቶች፡ ከምድር ጥቂት ከፍ ያሉ ኵይሶች።
ዲናሚት ፣ ደማሚት ፣ ደመመ።
ዲናሞ፡ እንደ፡ ቡላድ፡ ለመኪና፡ (ለሞተር)፡ ሁሉ፡ እሳትን፡ መብራትን፡ ሃይልን፡ የሚሰጥ፡
በጫፉ፡ ከሰል፡ ያለበት፡ ብረት።
ዲዋኒ (ገመስ): ታናሽ መጨረሻ ገንዘብ (እንደ ቤሳ ያለች) (ማቴ ፭:፳፮፣ ሉቃ ፲፪:፶፱)።
ዲያ: ከፊለ ስም (የዲያ)።
ዲያቆናዊት: ሴት ዲያቆን፡ የስሳ ዓመት ባልቴት። ዳቈነንና ዛቈነን አስተውል።
ዲያቆን: የቅዳሴ አገልጋይ፡ ተንሥኡ፣ ጸልዩ ባይ። "ነፈቀ ብለኸ ንፍቅን እይ"።
ዲያቆኖች (ዲያቆናት): ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች።
ዲያብሎስ: ሳጥናኤል (ያጋንንት አለቃ)።
ዲደን: ኀይለኛ ዐውሎ ነፋስ ሲኼድ "ድድድ" የሚል።
ዲግዲግ: ትግሪት፡ ታናሽ የበረሓ ሠሥ ስትኼድ "ድቅድቅ" የምትል (እንሹን ተመልከት)። "ዲግዲግ" የሐረርጌ ቋንቋ ነው።
ዳ (ሀዲእ): በሥራ፣ በነገር፣ ባካኼድ አለመፍጠን።
ዳ አለ (ሀድአ): ዝግ፣ ቀስ፣ ቸል አለ። "ዳትን" እይ።
ዳኄራ: ባሩድ (ዳኼራ)።
ዳለቻ (ኦሮ): ዐመድማ ፈረስ። (ተረት): "እንዲያውም በመላ ፈስ ዳለቻ ነው"።
ዳለች: የዳለቻ መጥሪያ።
ዳለጠ (ዳሌጥ): ዳጠ፡ ለጠ (የተላገ መዝጊያ ሳንቃ) መሰለ።
ዳላጣ: የዳለጠ፡ ድጥ፣ ላጣ (ወፍጮ)።
ዳሌ: የገላ ስም፡ ከጭን በላይ ከወገብ በታች ያለ የሙሓይት ሥጋ (ማሕ ፯:፪)። (ግጥም): "እንዳሰኑ ፈረስ እንዳባ ኵራራ፡ ከወገቧ ቀጠን ከዳሌዋ ኰራ"።
ዳሌጥ: የፊደል ስም (ደ ድልት)።
ዳልጋ(ጎች): በበሬና በላም፣ በጐሽ፣ በቶራ ዐንገት ከማንቍርት እስከ ፍርንባ የተንጠለጠለ ቈዳ። "ደላጎና ዳልጋ ግእዝ ደለገ ካለው የወጡ ናቸው"።
ዳልጋ: የጤፍ ዛላ።
ዳልጋንበሳ: ያውሬ ስም፡ ደምረገ።
ዳመና፡ ዳመኑ፡ የወንድና፡ የሴት፡ መጠሪያ ' ስም።
ዳመጠ፡ ረገጠ፡ ዳጠ፡ ደፈጠጠ፡ ለሰቀ፡ ለጥ፡ ቀጥ፡
አደረገ፡ ኣስተካከለ፡ ጥጥን፡ ከፍሬ፡ ለየ። መከረን፡
እይ።
ዳመጣ፡ ረገጣ፡ ልሰቃ።
ዳመጦ፡ ኣፍንጫ፡ ደፍጣጣ፡ ወንድ፡ ወይም፡ ሴት፡
ዝንጀሮ፡ መሳይ።
ዳመጦ፡ የተዳመጠ፡ ፍሬው፡ የወጣ፡ ጥጥ።
ዳሙሬ፡ ድሪቶ፡ በላዩ፡ ብዙ፡ ክር፡ የሚገኝበት።
ዳማ፡ በጋልኛ፡ ቀይ፡ ፈረስ፡ ማለት፡ ነው።
ዳማ፡ ከለለኝ፡ ሰፊ፡ የምድር፡ ይዘታ፡ ያባ፡ ሰንጋ፡ መሬት፡
በዳማ፡ ፈረስ፡ የተከለለ፡ (የተወሰነ)።
ዳማ፡ ከሴ፡ ቀይ፡ ከሴ፡ ለምች፡ መድኀ ኒትነት። ቈርጠው፡ ዐሽተው፡ ሲጨምቁት፡ ው ሃው፡ ዕርድ፡ ደም፡ የሚመስል።
ዳማ ከሴ: ቀይ ከሴ። ይኸውም ቅጠሉ ይቀቀልና ገገምተኛ ይታጠብበታል፡ በሽታው እንዳያገረሽ ይከለክላል ይላሉ።
ዳማ፡ የደም፡ ዐይነት፡ ቀይ።
ዳማ፡ ደም፡ አዋጣ አፋሰሰ።
ዳማ፡ ጠይም፡ ወንድ፡ ወይም፡ ሴት። (ለምሳሌ፡ የቀይ፡ ዳማ፡ እንዲሉ)። በጋልኛ፡ ግን፡ ዳማ፡ የሚባል፡ ፈረስ፡ ነው።
ዳማ፡ ፈረስ፡ ቀይ፡ ፈረስ።
ዳማጭ፡ (ጮች)፡ የዳመጠ፡ የሚዳምጥ፡ ደፍጣጭ፡ ለሳቂ።
ዳምዛ፡ የንጨት፡ ስም፡ ዐጣጥ፡ የሚመ ስል፡ ዕንጨት።
ዳምጠው፡ የንጉሥ፡ ኀይለ ' መለኮት፡ ፈረስ "
ዳምጤ፡ ዳምጠው፡ የሰው፡ ስም።
ዳሞት፡ በጐጃም፡ ክፍል፡ ያለ፡ አገር።
ዳሞት፡ ወይራ፡ እንደ፡ ወይራ፡ ጠንካራ፡ የሆነ፡ ዛፍ፡
ጥቁር፡ እንጨት፡ መሳይ።
ዳሞትራ፡ (ሮች)፡ የሚናደፍ፡ መርዘኛ፡ ጥቁር፡ ከሰልማ፡ ባለጠጕር ሸረሪት።
ዳሞቶች፡ የዳሞት፡ ሰዎች፡ የዳሞት፡ ተወላጆች።
ዳሰ፡ (ትግ፡ ደሀሰ፡ ናደ፡ አፈረሰ። ዐረ፡ ዳሰ)፡ ረገጠ፡ ዳጠ፡ ዳመጠ፡ ደፈጠጠ፡ (ኢሳ፳፰፡ ፲፯)።
ዳሰ፡ ዐሻሮ፡ ፈጨ፡ አደቀቀ፡ ወረዳውን።
ዳሰሰ፡ (ትግ፡ ዳሕሰሰ)፡ ነካ፡ ዳበሰ፡ (ዘዳ፳፰፡ ፳፱። ዳን፰ ፲ ፲፰። ፱ ' ፳፩። ኢሳ፶፱፡ ፲። ማቴ፰ - ፫ - ፲፭)።
ዳሰሳ፡ ዳበሳ።
ዳሰሳ: ፍለጋ፡ የመዳሰስ ሥራ። "ዕውር በዳበሳ ይኼዳል"።
ዳሳሽ፡ የዳሰሰ፡ የሚዳስስ፡ ዳባሽ።
ዳስ፡ (ሶች)፡ ሰቀላ፡ የቅጠል፡ ቤት፡ የሰርግ፡ የዝክር፡
የተዝካር፡ የማኅበር፡ ድግስ፡ የሚበላበትና፡ የሚጠጣበት። (ዘዳ፲፮፡
፲፫)። በግእዝም፡ ዳስ፡ ይባላል። ደሰሰን፡ እይ፡ ሥሩ፡ ርሱ፡ ነው። ጣለን፡ ተመልከት።
ዳስ፡ የቅርብ፡ ወንድ፡ ትእዛዝ፡ አንቀጽ፡ ዐሻሮ፡
ፍጭ።
ዳረ፡ (ደኀረ)፡ ሙሽራውንና፡ ሙሽራዪቱን፡ ባረከ፡ መረቀ፡
ውለድ፡ ክበድ፡ ውለጂ፡ ክበጂ ' አለ።
ዳረ፡ (ደሐረ)፡ ወንድ፡ ልጁን፡ ሰረገ፡ ሞሸረ፡ ሚስት፡
አጋባ፡ ንብረት፡ ትዳር፡ አሲያዘ።
ዳረገ፡ (ዳርጎ፡ ዳረገ ፣ አሥበጠ)፡ ድርጎ፡ ፈቀደ፡ አዘዘ፡ ከእከሌ፡ ተቀበል፡ አለ።
ዳረገ፡ ለካ፡ ሰፈረ፡ መጠነ፡ ቈነነ፡ ሰጠ።
ዳረጎት፡ (ሥበጥ)፡ ከንጀራ፡ ከዳቦ፡ ተቈርሶ፡ ለሰው፡ የሚሰጥ፡ ጕርሻ፡ የረኛ፡ መክሠሥ፡ እንጐቻ፡ የውሻ፡ እራት።
ዳሩ፡ ንኡስ፡ አገባብ። ዳሩ፡ ግን፡ መጨረሻው፡ ግን፡ እንደ፡ ማለት፡
ነው፡ (ዘዳ፩፡ ፴፪)። ዳግመኛም፡ ነገር፡ ተብሎ፡ ይተረጐማል።
ዳሩ፡ እሳት፡ መኻሉ፡ ገነት፡ በዙሪያው፡ መስቀል፡ የዞረበት፡ ገዳም፡
ታላቅ፡ ደብር፡ የከተማ፡ ቤተ፡ ክሲያን፡ (ዘፍ፫፡
፳፬)።
ዳሩ፡ እሳት፡ እንዲሉ።
ዳሩ፡ ዳርቻው፡ ጫፉ፡ መጨረሻው።
ዳሩ፡ ግን፡ (ኢሳ፵፡ ፰)።
ዳሪ፡ (ደሓሪ፡ ደኃሪ)፡ የዳረ፡ የሚድር፡ ሰራጊ፡ ሞሻሪ፡ ባራኪ፡
መራቂ።
ዳራ፡ (ደኃራይ)፡ በቀዳማ፡ አንጻር፡ ያለ፡ የኮርቻ፡ ኋለኛ፡
ድጋፍ።
ዳራጊ፡ የዳረገ፡ የሚዳርግ፡ ሰጪ፡ አሰጪ።
ዳር፡ መኻል፡ ይኾናል፡ እንዲሉ።
ዳር፡ አገር፡ (ዳራገር)፡ በዳር፡ ያለ፡ አገር።
ዳር፡ ዳርቻ፡ ከውስጥ፡ ከመካከል፡ የራቀ፡ ወሰን፡
ደንበር፡ ወደብ፡ ገደብ፡ አፋፍ፡ ጠረፍ፡ ጠርዝ፡ ጫፍ፡ መጨረሻ፡ (ዘፀ፳፫፡
፴፩። ኢሳ ፲፫ = ፭)።
ዳርም፡ የለሽ፡ የሴት፡ ስም፡ ወሰን፡ መጨረሻ፡ የለሽም፡
ማለት፡ ነው።
ዳርቻ ፣ ጠረፍ ፣ ዳረ፡ ዳር።
ዳርና፡ ዳር፡ ጠርዝና፡ ጠርዝ፡ ፍና፡ ግፍ።
ዳርጋ፡ አንበሳ፡ ቢል፡ ግን፡ አንበሳ፡ ያህል፡ ማለት፡ ነው፡ (ትግሪኛ)። ለና፡ ረ፡ ተወራራሽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ ባላገር፡ ዳልጋንበሳ፡ ይላል።
ዳርጌ፡ የሰው፡ ስም፡ ዳርግ፡ ወይም፡ የዳራጊ፡ ወገን፡ ማለት፡ ነው።
ዳሮች፡ ወሰኖች፡ ጠርዞች፡ (ዘፍ፳፭፡ ፲፱)።
ዳሸቀ፡ ተረገጠ፡ ዳከረ።
ዳሸን፡ የስሜን፡ ተራራ፡ ቧሒት። (ዘዐ ሸን)፡ ዐሸናም፡ የበረዶ፡ ዐሸን፡ መዝነሚያ፡ መ ጠራቀሚያ፡ ደቃ።
ዳሽ፡ የዳሰ፡ የሚድስ፡ የሚፈጭ፡ ፈጪ።
ዳቈነ፡ ዛቈነ፡ ተካነ፡ ዲያቆን፡ ሆነ፡ ድቍና፡
ተቀበለ።
ዳቈን፡ (ዲያቆን)፡ የዳቈነ፡ የተካነ፡ ምስጢር፡ ያየ፡ ቀዳሽ። ዳቈን፡ የሕዝብ፡ አማርኛ፡ ነው።
ዳቋኝ፡ (ኞች)፡ የሚዳቍን፡ ዛቋኝ፡ ተካኝ፡ ክህነት፡ ተቀባይ።
ዳበሰ: ዳሰሰ፣ ነካ፡ ፈለገ። "ማሪያም ትዳብስሽ" እንዲሉ።
ዳበስ አደረገ: ዳበሰ።
ዳበስ: መዳሰስ።
ዳበረ: አደገ፣ ወፈረ፣ ገዘፈ፣ አሞላ፡ እካለ መጠን አደረሰ፡ ሰፋ፣ ሰፊ ኾነ፡ አማረ።
ዳበሩ: የሰው ስም፡ እናት ለልጇ ስም ስታወጣ "አባትኸ ትልቅ ኾኑ" እንደ ማለት "ዳበሩ" ትላለች።
ዳቢት (ደበለ): የሥጋ ስም፡ የበሬ ትከሻ ሥጋ ከብራኳ ጋራ፡ የጐድን ዘርፍ። "ጐድን ተዳቢት" እንዲሉ። (ግጥም): "ዲያብሎስ በክፋቱ ተወጋ ዳቢቱ"።
ዳባ (ዎች): ቈዳ፣ ጀንዲ፣ ቈርበት፣ ነት፣ ተንቤን፣ ማስ፣ ሌጦ (ዐጽፍ)፡ ምንጣፍና መደረቢያ (ቀሚስ) የሚኾን። "አባ ልብሱ ዳባ ውስጡ ደባ" እንዲሉ። (ተረት): "ወዶ ገባ ልብሱ ዳባ"። "ያልወለድኩት ልጅ አባባ ቢለኝ! አፌን ዳባ ዳባ አለኝ"።
ዳባ ለባሽ: መናኝ፣ መነኵሴ፣ አረመኔ።
ዳባ ሳም: ከድርበብ በታች ያለ ስፍር፡ "ዳባ ነክ" ማለት ነው። "ዳባ" የተባለው የቍናው ክፈፍ።
ዳባሪ: የዳበረ፣ የሚዳብር፡ ያደገ።
ዳባሼ: የኔ ዳባሽ፡ ጐብኚዬ፣ ጠያቂዬ።
ዳባሽ: የዳሰሰ፣ የሚዳብስ፣ የሚዳስስ፡ ሐኪም፣ ወጌሻ፣ ነኪ፣ ፈላጊ።
ዳባት: በበጌምድር ውስጥ ያለ አገር።
ዳቤ (ዎች) (ዳባዊ): ወፍራም የማኅበር እንጀራ። "ጐራ" ብለህ "ጕሬን" እይ።
ዳብሬ: ከዶጮና ከገንቦ የሚበልጥ፣ ከንስራ የሚያንስ የሸክላ ዕቃ።
ዳብዛ: ፍለጋ፣ ጭገሬታ፣ ምልክት። "ይህ ነገር ዳብዛው ጠፋ"። "ዘሩ ደበሰ ነው"።
ዳቦ (ዎች): በቅጠል ተጠቅሎ በገበር ምጣድ የተጋገረ፡ በላይ በታች እሳት የሚነድበት፡ ትልቅነትና ስፋት ከውፍራሬ ጋራ ያለው ኅብስት። (ስላቶ በዛብኸ አልቃሽ): "አንተም ጨካኝ ነበርክ ጨካኝ አዘዘብሽ፡ እንደ ገና ዳቦ እሳት ነደደብኸ"። (ተረት): "ከዳቦ የተገኘ ወጥ ዐብረኸ ግመጥ"። "በገዛ ዳቦዬ ልብ ልሱን ዐጣኹት"። "እኛ ባገራችን ዳቦ ፍሪዳችን"። (ትልቁ ዳቦ ሊጥ ኾነ): ጨዋው ባለማዕርጉ ነውር ሠራ። "ደነጋ" ብለህ "ድንጋይን" እይ።
ዳቦ ሽሮ: በዘይት በቅቤ የተቀቀለ ሽንብራ ከዳቦ ጋራ የሚበላ።
ዳቦ ቈሎ: ከስንዴ ሊጥ የተቈላ የዳቦ ቈሎ ድብልብል እንክብል። ዳቦነትን ከቈሎነት ያስተባበረ ምግብ። (ሥንቅ ሳሙ ፳፭:፲፰)።
ዳቦ በሊት: የሴት ስም ነው።
ዳቦ በሌ: የሚጣቅ ወንዝ። ዳቦ ስለወሰደ በዚህ ስም ተጠራ ይላሉ።
ዳቦ: የጤፍ ስም (ቀይ ጤፍ)።
ዳቦት: የችቦ ስም፡ ሽግ፣ ሽጕ።
ዳነ፡ (ድህነ)፡ ጤና፡ አገኘ፡ ተፈወሰ፡ ተረፈ፡ ከተያዘና፡
ሳይያዝ፡ አመለጠ።
ዳነ: ቀረ፣ ተፈታ፣ ተፈወሰ፣ ተተወ።
ዳነተ፡ ዛተ፡ ዘበተ፡ ፎከረ፡ ተቈጣ፡ ሰደበ።
ዳን፡ የሰው፡ ስም፡ ከአስራ ፪ቱ፡ ነገደ፡ እስራኤል፡ አንዱ። ትርጉሙ፡ ፈራጅ፡ ማለት፡ ነው ፍርድም፡ ይሆናል።
ዳንስ፡ የፈረንጅ፡ ጭፈራ፡ ውዝዋዜ፡ ዝላይ።
ዳንኤል፡ ከታላላቆቹ፡ ነቢያት፡ አንዱ፡ በባቢሎን፡
የተነሳ፡ ነቢይ።
ዳንኪራ፡ ዳንኬራ፡ (ፃህስ)፡ ሽብሸባ፡ ርግዶሽ፡ ጭፈራ።
ዳንኬራ፡ መታ፡ (አፅሐሰ)፡ አሸበሸበ፡ አረገደ፡ ጨፈረ።
ዳንዳ፡ ማማ፡ ያዝመራ፡ መጠበቂያ፡ ቄራ፡ የዱር፡
አልጋ፡ ወይም፡ ቈጥ።
ዳንዴ፡ ዳንዳዊ፡ የዳንዳ፡ ወንበዴ፡ ቀማኛ።
ዳንግላ፡ በጐጃም፡ ጠረፍ፡ ያለ፡ አገር፡ ።
ዳንግሌ፡ ቀይ፡ በግ፡ እሳትማ፡ ዳንግላዊ፡ የዳንግላ፡
ማለት፡ ይመስላል። ዳግመኛም፡
ተባት፡ አውራ፡ በግ፡ ተብሎ፡ ይተረጐማል።
ዳንግሎች፡ ተባት፡ በጎች።
ዳኘ፡ (ዳነየ)፡ ከሳሽ፡ ተከሳሽን፡ ዋስ፡ አስጠራ፡ አስቻለ፡
አነጋገረ፡ ፈረደ፡ በየነ።
ዳኘ፡ ቃኘ፡ ዳኝነት፡ እየ፡ ህዝብን፡ ጐበኘ።
ዳኘው፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ዳኛ፡ (ኞች)፡ የዳኘ፡ የሚዳኝ፡ ፈራጅ፡ ቀዳጅ፡ አገረ፡
ገዢ፡ አለቃ፡ ሹም።
ዳኛ፡ ሆነ፡ ዳኝነት፡ ተሾመ።
ዳኛ፡ ማርያም፡ የማርያም፡ ዳኛ፡ እንደራሴ።
ዳኛ፡ ሲቀመጥ፡ ሲያስችል፡ ሲያነጋግር፡ አቀርባለሁ።
ዳኛ፡ ረገጠ፡ አልዳኝም፡ እንቢ፡ አለ።
ዳኛ፡ ቀጠነኝ፡ ዳኛን፡ መናቅ፡ ማስተናቀፍ።
ዳኛው፡ የአፄ፡ ምኒልክ፡ የፈረስ፡ ስም፡ አባ፡
ዳኛው፡ እንዲሉ።
ዳኜ፡ የሰው፡ ስም፡ ዳኛዬ፡ የኔ፡ ዳኛ፡ የዳኛ፡
ወገን፡ ማለት፡ ነው።
ዳኝ፡ የሚድን፡ የሚተርፍ።
ዳኝነት፡ ለዳኛ፡ የሚከፈል፡ የውርርድ፡ እዳ።
ዳኝነት፡ ዳኛ፡ መሆን፡ ፈራጅነት።
ዳኝነት፡ ገባ፡ በቅሎ፡ ፈረስ፡ ማር፡ እሰጥ፡ ብሎ፡ ተረታ።
ዳከመ: ቈፈረ፣ ጫረ፣ ኰተኰተ (ያገዳ)። "ዛሬ ቈላ ወርጄ አገዳ ስዳክም ውዬ መጣኹ"።
ዳከረ (ትግ ደከረ፣ መታ): ተለወሰ፣ ላቈጠ፡ ተረገጠ፣ ተወቀጠ፡ ደከመ፣ ለፋ።
ዳከኸ (ድሕከ): በደረት ተሳበ፣ ተጐተተ፡ ምድርን በጕልበትና በመዳፍ ረገጠ፡ አጐንብሶ በእጅና በእግር ኼደ (የሕፃን)።
ዳካ (ዐይገን): ዋዲያት፣ ደቅ፣ ትልቅ ሳሕን፣ ጻሕል (ከተረገጠ ቀይ ዐፈር የተሠራ) (ዘፀ ፳፬:፮፣ ኤር ፶፪:፲፰)።
ዳካ: ዋዲያት (ደካ)።
ዳክዬ(ዮች) (ዳከ): በውሃ ላይ የምትድሽ ዋነተኛ አሞራ (ዝዪ)። ዳክዬ ማለት ጋልኛ ነው።
ዳኺ: የዳኸ፣ የሚድሽ። "ባለቅኔዎች ግን ጓያ ይሉታል"።
ዳኼራ: ከጨውና ከከሰል ተወቅጦ የሚዘጋጅ፣ በቀለሕ ውስጥ ከዐረር በታች የሚቀመጥ ባሩድ። የጠመንዣ፣ የመድፍ ቃታ በከምሱር ሲመታው ተተኵሶ ርሳስን የሚያበር።
ዳወለ: ተፈተፈተ፣ ተለወሰ።
ዳወረ) አዳወረ (አድራጊ): ደወረ።
ዳወሮ: የቀድሞ የሐረጌ ስም (በግእዝ መጻሕፍት ይገኛል)። (ተረት): "ዕዳው ዶሮ፡ መጋቢያው ዳወሮ"።
ዳዊት
ዳዊት ደገመ: ጨረሰ፣ ዐወቀ።
ዳዊት ደጋሚ (ደጋሜ ዳዊት): ዳዊት የሚደግም፣ በዳዊት የሚጸልይ (ተማሪ፣ ካህን)። ፪ኛውን ደገመ ተመልከት።
ዳዊት(ቶች): የመጽሐፍ ስም። ሙሴ ሳይቀር ዳዊትና ሌሎች መዘምራን በየጊዜው የደረሱት (የዘመሩት) ፻፬ መዝሙር ያለበት የጸሎት መጽሐፍ።
ዳዊት: የሰው ስም፡ የእሴይ ልጅ፡ የእስራኤል ንጉሥ፡ በገና ደርዳሪ።
ዳዋ: ከጭልጋ በታች ያለ በረሓ።
ዳዋ: የወንዝ ስም (ካሩሲ ተራራ የሚፈልቅ ዠማ)።
ዳዋ: ጥሻ፡ ሣር ቅጠላቅጠል፣ ክረምት አፈራሽ።
ዳውላ (ጐንደር): እንቢ ነገር፡ ከስልቻ ከሌላም ቈዳ የተበጀ (በውስጡ ሣርና ገለባ ያለበት የጭነት መደላድል)።
ዳውላ(ሎች) (ሐስል): ፳ ቍና እኸል የሚይዝ የፍየል ሙክት ስልቻ (ባውድማ፣ ምርት፣ መጨመሪያ፣ መስፈሪያ)። (ተረት): "አህያውን ቢፈሩ ዳውላውን መቱ"።
ዳውሌ: በጠራ አጠገብ የሚገኝ ቀበሌ።
ዳውንቴ: የዳውንት ተወላጅ፣ የዳውንት ወገን።
ዳውንት: ያገር ስም (በሣይንት አጠገብ ያለ አገር)።
ዳውንቶች: የዳውንት ሰዎች።
ዳውጃ፣ ዳውዣ: ከቀጤማ የተሠራ ምንጣፍ (ኬሻ፣ ደሳ) (፪ሳሙ ፲፯:፲፱)።
ዳዳ (ዕብ ዳዴህ): አስከጀለ፣ አሳሰበ (የርምጃ፣ የሩካቤ፣ የመናገር)።
ዳዴ ዳዴ አለ: የሕፃንን እጅ ይዞ ፩:፩:፪:፪ እያለ መኼድን አስለመደ፣ አስተማረ። "አቱ ሥግራ ታቱ ሥግራ አለ"፡ "ወንከር ወንከር አደረገ"።
ዳዴ: የሕፃን ርምጃ፡ እጁን ተይዞ እየተወናከረ የሚኼደው አካኼድ።
ዳገተ: ዳገት ኾነ።
ዳገት ዕርሙ: ሜዳ ወንድሙ፡ ሰነፍ ዳውላ ሐሞት።
ዳገት(ቶች): ዐቀበት፡ ሽቅብ ሽቅበት።
ዳገትና ቍልቍለት: የደጋና የተራራ የቈላ መንገድ።
ዳጕሳ(ሶች): የእኸል ስም፡ ዛላው ሙርዬ ፍሬው የወፍ ዘረር የሚመስል፡ ባገዳም በፍሬም ከጤፍ የሚዳጕስ እኽል፡ በሐረርጌና በትግሬ፣ በሌሎችም ባንዳንድ አገሮች የሚበቅል።
ዳጋ: በጣና ውስጥ ያለ ትልቅ ደሴት።
ዳጋ: ደሴት (ደገገ)።
ዳጌ: ሙክት።
ዳጌ: ሙክት (ደገገ)።
ዳግመኛ (ዳግማይ፣ ዊ): የዳግም፡ ኹለተኛ።
ዳግመኛ ተማረ: "ከለሰ"።
ዳግመኛም፡ (ጤነ) አጤነ ግእዝ፡ ጼነወ አጼነወ ከሚለው ጋራ ይሰማማል።
ዳግመኛም መዠመሪያ በህንድ አገር የነበረ ሕዝብ "አርያ" ይባል ነበር ይላሉ። (ነፃ ሰው ወይም የመኳንንት ልጅ)።
ዳግመኛም ሠራ ተኛ ተብሎ ኹለት አንቀጽ ይኾናል።
"ተኛን"
ተመልከት።
ዳግመኛም በተጸብሐ ዘይቤ ቢፈቱት "ጧት ታየ ተጋደደ" (አስደነገጠ) ያሰኛል። "እከሌን ኮሶ ተጣብቶታል" እንዲሉ።
ዳግመኛም በግእዝ ነፍጥ፣ ነፍት፣ ጋዝ ይባላል። የነፍጡም የጋዙም ምስጢር - መቃጠልና ማቃጠል ነው።
ዳግመኛም ዣግሬ (ዘአጋር፣ ዘእግር፣ ዘአግሬ፣ ዘገራዊ): ሐርበኛ፣ እግረኛ፣ ጋሸኛ፣ ዠግና፣ ጦረኛ ማለት ነው። (ዘገርንና አግሬን ተመልከት)።
ዳግመኛም፡ ጋለባና ግልቢያ "መጋለብ" ተብለው ይተረጐማሉ።
ዳግመኛም ጥጃ (ጥዶ) ጠዶ ጠደፈ፡ ከሁለተኛው ጠጋና ከጠገተ ሊወጣ ይችላል፡ ጕራጌ "ጥጃ" ሲል "ጠግ" ይላልና። ይኸውም የጀንና የገን ተወራራሽነት ያሳያል።
ዳግማ ተንሣይ (ዳግም ትንሣኤ): የትንሣኤ ፪ኛ እሑድ።
ዳግማ ተንሣይ): የትንሣኤ ሳምንት።
ዳግማ: ዳግም፣ ዳግመኛ።
ዳግም: ኹለት፡ ኹለት ጊዜ።
ዳግሞሽ: ዝኒ ከማሁ።
ዳጐሠ: ወፈረ (ዳጐሰ)።
ዳጐሰ: ወፈረ፣ ከቅጥነት ራቀ።
ዳጐስ አለ: ወፈር ኣለ፡ በእጅ መላ።
ዳጐስ: ወፈር።
ዳጎን: የጣዖት ስም፡ በዓሣ ዐይነት የተሠራ የፍልስጥኤም ጣዖት።
ዳጠ (ድኅፀ): ዳለጠ፣ ድጥ ኾነ።
ዳጠ: ረገጠ፣ ደፈጠጠ፣ ጨፈለቀ፣ አጨማለቀ።
ዳጠ: ርጥብን፡ ዳሰ: ደረቅን ነው።
ዳጠ: ቅመምን፣ ተልባን፣ ኮሶን፣ የምስር ንፍሮን ፈጪ፣ አላመ።
ዳጥ: ትእዛዝ አንቀጽ፡ ፍጭ፣ አልም።
ዳጥ: ዝኒ ከማሁ ለድጥ፡ መሰናክል፣ ዕንቅፋት።
ዳጪ (ኦሮ): የሰው ስም። "ከቦረን ልጆች አንዱ፡ የግዝረት በግ ነው ይላሉ።" "የራስ ጐበና አባት ጐበና ዳጪ" እንዲሉ።
ዳጪ(ጭ): የዳጠ፣ የሚድጥ፡ ረጋጭ፣ ፈጪ(ጭ)።
ዳጪ: ዝኒ ከማሁ። ዳመጠን እይ።
ዳፈ፡ (ደሐፈ)፡ ገፋ፡ አዳፋ፡ ገፈተረ፡ አጣደፈ።
ዳፈለ፡ ጨጐረ፡ ጠጕራም፡ ሆነ።
ዳፈን፡ እጕል፡ ያልተቀደሰ፡ ያልተሠራ፡ ሳይገበር፡
የቀረ።
ዳፈን፡ ከፈለ፡ ባለመሥራቱ፡ ዕዳ፡ መቅጮ፡ ከፈለ።
ዳፋ፡ (ዳሕፍ)፡ ግፍ ' ጡር፡ ጥፋት። (ተረት)፡ የኃጥኡ፡ ዳፋ፡ ጻድቁን፡ አዳፋ።
ዳፍል፡ ጠጕር፡ ጭገር፡ ጐፍላ።
ዳፍሎ፡ የውሻ፡ ስም፡ ጠጕራም፡ ውሻ።
ዳፍንታም፡ (ሞች)፡ ዳፍንት፡ ያለበት፡ የሠለጠነበት፡ ባለዳፍንት፡
የቈሎ፡ ተማሪ፡ ጕዳተኛ፡ ሰው።
ዳፍንታም፡ ደንቈሮ፡ ዕውቀት፡ የማይገባው።
ዳፍንት፡ ያይን፡ በሽታ፡ ጀንበር፡ ስትጠልቅ፡ ማየት፡
የሚከለክል፡ ምድርን፡ ባሕር፡ አስመስሎ፡ የሚያሳይ፡ ከጕዳት፡ የሚመጣ። በግእዝ፡ ግን፡ ርሚጦ፡ ማለት፡ ነው።
ዴሮ፡ (ኦሮ)፡ ዝንጕርጕር፡ የዱር፡ ድመት፡ ዶሮና፡ ወፍ፡
አይጥ፡ የሚበላ፡ ቁመቱ፡ ፩፡ ክንድ፡ ከጭራው፡ እስከ፡ ራሱ፡ ፪፡ ክንድ፡ ይኾናል። ባማርኛ፡ አነር፡ ይባላል።
ዴበ (ዴፐ): ተደበቀ፣ ሸመቀ። "ዴበ እንጂ ዴበ አልተለመደም"።
ዴበን እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው፡ "ዱቢትን" ተመልከት።
ዴንሳ፡ በጐዣም፡ ውስጥ፡ ያለ፡ አገር።
ዴንዳ፡ የብሄሞት፡ ፪ኛ፡ ስም፡ ዳንዴ፡ ከዚህ፡
የወጣ፡ ይመስላል።
ዴግሬ: ደረጃ፣ ዕርከን፣ ማዕርግ፡ ከፍታና ዝቅታ፡ የትምርት፣ የውቀት፣ የመድኀኒት ወይም የሙቀት፣ የብርድ ልክና መጠን። ዴግሬ ፈረንጅና ነው።
ድ(ን)ቡልቅኝ: ዐቧራና እብቅ (ያመድ፣ ያሸዋ፣ ያፈር፣ የሣር ድቃቂ)።
ድ(ን)ከን(ኖች): ብዙ ዕቅፍ፡ የጤፍ፣ የብር እኸል፣ የሽንብራ ነዶ (በላዩ ደንጊያ የተጫነበት)።
ድኁር(ሮች): ዐጪር ሰው (ከማድግ ወደ ኋላ ያለ)።
ድኅነት: መዳን፣ ሽረት።
ድሕንጻ: ከቀንድ፣ ከዝኆን ጥርስ፣ ከጥቍር ዕንጨት የተበጀ የበገና መምቻ (መደርደሪያ)። ምስጢሩ የታነጸ ማለት ነው።
ድኋን (ዐረ ድኁን): ብልቱግ።
ድለላ: ሽንገላ፡ የሽንገላ ነገር።
ድለቃ፣ ድልቂያ: ምት፣ ድሰቃ፣ ጕሰማ።
ድላል: ለጠቋሚ፣ ላስማሚ የሚሰጥ ገንዘብ።
ድላም: ድል ያለበት።
ድሌ: የኔ ድል፡ "አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ" እንዲል ገና ተጫዋች።
ድሌ: የድል፣ ድላዊ፡ ድል አድራጊ።
ድል (ዳሕል): መሸነፍ፣ ሽሽት።
ድል ተነሣ: ድል ኾነ፡ በጦር ተሸነፈ፣ ተረታ።
ድል ተነሺ(ሾች): ተሸናፊ (ዘፀ ፴፪:፲፰)።
ድል ነሣ: ድል አደረገ፣ ድል አሳጣ።
ድል ነሤ፣ ድል ነሣኹ: የሰው ስም።
ድል ነሺ(ሾች): አሸናፊ (ዘፀ ፴፪:፲፰)።
ድል ነዓድ: በ፲፻ ዓ.ም የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ስም። "ድልን የሚንድ፣ የሚያፈርስ" ማለት ነው። ናደን እይ።
ድል አለ: ልጅን በጣት ነካ፡ ነክቶ ሸሸ።
ድል አደረገ (አድሐለ ሞኣ): አሸነፈ፣ አሸሸ።
ድል አድራጊ(ጎች): አሸናፊ፣ ሐርበኛ፣ ጐበዝ (የጦር ገበሬ)።
ድል ኾነ (ተድሕለ ተሞአ): ተሸነፈ፣ ተረታ።
ድል ድልቅ አለ: መላልሶ ተመታ፣ ተደሰቀ፡ ጮኸ (ነጋሪቱ፣ ከበሮው)።
ድል: የልጆች ጨዋታ።
ድል: የቍምጥና ምልክት (በገላ ላይ ብብ መስሎ የሚታይ)፡ አካልን የሚያበላሽ (ሕዋሳትን፣ ይልቁንም ጣቶችን)። "ድል የሚመታ"።
ድል: የድግስ መሰናዶ (በሽበሽ)፡ የበዛ፣ የተረፈ። "ድል ያለ ድግስ" እንዲሉ።
ድልል(ሎች): የተደለለ፣ የተሸነገለ፡ ሽንግል፣ ምልስ።
ድልም አለ: ጭልም፣ ጥፍት፣ ዕልም አለ።
ድልም: የደለመ (ውድም)።
ድልምጥ አለ: ደለመጠ፡ ጥርንቅ አለ።
ድልስ: የተደለሰ (ራስ ወይም ቅቤ)።
ድልቅ: የተደለቀ፡ ድስቅ፣ ጕስም (ድል ድልቅ አለ)።
ድልባም: ድልብ ያለው፣ ባለድልብ።
ድልባን: ደባል (ወሎ)።
ድልብ(ቦች): የደለበ፡ ደንበሾሻጋታ (እኸል፣ ብር)፡ ወፍራም (ሰንጋ፣ ፍሪዳ፣ ገች)።
ድልኽ በሊት: አቃጣሪ፣ አሳባቂ፣ ነገረኛ ሴት (በሌላዪቱ ሴት ማጀት የምትገኝ፡ ከድልኽ ዠምሮ ኹሉን የምትቀምስ፣ የምትበላ)።
ድልኽ: የተፈጨ፣ የተደለኸ (የበርበሬ ዶቄት ወይም ልቍጥ)።
ድልዝ: የተደለዘ፣ የተወቀጠ (በርበሬ፣ ዶቄት ወይም ልቍጥ)።
ድልዝ: ግብዝ፣ ብይድ፣ ምርግ (ድፍን ብረት፣ ሸክላ፣ ውስጠ ሰባራ)።
ድልድል አለ: ዕብጥ አለ።
ድልድል(ሎች): የተደላደለ፡ ቅምጥል፣ ሀብታም (ጌታ)፡ ትክክለኛ ክፍያ።
ድልድል: የተደለደለ ስፍራ (ዐባጣ ጐባጣ የሌለበት) (፪ሳሙ ፳:፲፭፣ ፪ነገ ፲፱)፡ ዦር፣ ክትር (የውሃ መከማቻ፣ የኩሬ መሰብሰቢያ፣ ግድብ)። "ድልድል ያሠኘው ጕድጓዱን የከበበ ዐፈር ነው"።
ድልድይ(ዮች): የዠማ፣ የዥረት፣ የወንዝ ላይ መንገድ (በንጨት፣ በግንብ፣ በብረት የተሠራ)፡ ከወዲህ ወዲያ፣ ከወዲያ ወዲህ መሻገሪያ፣ መሸጋገሪያ፡ "ላዬ የተደለደለ ታቹ ባዶ ክፍት"።
ድሎት (ድልወት): ምቾት፣ ተድላ።
ድመም፡ መደምም፡ መደንን።
ድመራ፡ (ድማሬ)፡ ስብሰባ፡ እከባ፡ ጥምጠማ።
ድመት፡ (ቶች)፡ የሴት፡ አውሬ፡ ለማዳ ዕቃ፡ ዘበኛ፡ ድብርቅ፡ ዐይን፡ ያይጥ፡ ጠላት፡
ዐይጥን፡ የሚያስደምም፡ የሚያስፈራ፡ የሚያፈዝ፡ ዐይጥ፡ ለመያዝ፡ ዝም፡ ጸጥ፡ የሚል፡ ዐይነ ምድሩን፡ መሬት፡ ቈፍሮ፡ የሚቀብር። ነገዱ፡ ያንበሳ፡ የነብር፡ ነው። (የዱር፡ ድመት)፡ ፍጹም፡ አውሬ፡ የዶሮ፡ ጠላት።
ድመት፡ ቅዱስ፡ ነው፡ ንዋየ፡ ቅድ ሳትና፡ መንበረ፡ ታቦት፡ ስለሚጠብቅ፡ እንዲህ፡
ይባላል።
ድመና፡ ጥቍረት፡ ጥቍርነት "
ድማ፡ የዛፍ፡ ስም፡ በከረን፡ ያለ፡ ዕን ጨት፡ ቀይ፡ ፍሬው፡ የሚበላ።
ድማም፡ ድንቂያ።
ድም፡ አለ - ጮኸ።
ድም፡ አለ፡ ጮኸ፡ ፈነዳ፡ አስተጋባ።
ድም፡ የሴት፡ ስም፡ ድንቋ፡ ድንቂቱ' ትክክሿ።
ድም፡ ድም፡ አለ፡ መላልሶ፡ ጮኸ፡ ተተኰሰ።
ድምም፡ የተደመመ፡ የተስጣጣ፡ ትክ ክል፡ የመደምም፡ ክዳን።
ድምም፡ የተደነቀ፡ ድንቅ "
ድምሰሳ፡ (ድምሳሴ)፡ ፍቆሽ።
ድምስስ፡ አለ፡ ተደመሰሰ፡ ጥፍት፡ አለ።
ድምስስ፡ ድምስ፡ (ድምሱስ)፣ የተደመሰሰ፡ የጠፋ፡ የማይታይ፡ አይን፡ የሌለው፡
እንጀራ፡ እውር፡ እከክ።
ድምር፡ (ድሙር)፡ የተደመረ፡ አንድ፡ ላይ፡ ያለ፡ ቍጥር፡
የደመራ፡ ዕንጨት፡ ትልቅ፡ ጥምጥም።
ድምር ሥሉሴ፡ ሦስትዮ፡ ድርድር፡ በንጉሥና፡ በንግሥት፡
በ ቅሎ፡ ዐንገት፡ የሚጠለቅ፡ የወርቅ፡ ጌጥ፡
ሾጣጣ፡ ቍርጥ፡ ንብብር፡ መገ ናኛው፡
ዐልፎ፡ ዐልፎ፡ የወርቅ፡ ሽቦ፡ የተሰካበት፡ ታቹ፡ ባሕር፡ ዐ ረብ፡
መደቡ፡ ቀይ፡ ከፈይ፡ ነው።
ድምሮች፡ የተደመሩ፡ ርጥቦች፡ ዕንጨቶች።
ድምቡ፡ የድንቡጭ፡ ወገን "
ድምቡጭ፡ አለ፡ ዝም፡ አለ።
ድምቡጭ፡ አካለ፡ ጥብቅ፡ (እንደ፡ ድም ቢጥ)፡ ዝምተኛ።
ድምቢጥ፡ (ቢጸ፡ ደም)፡ የደም፡ ዐይነት፡ ታናሽ፡ መጨረሻ፡ ቀይ፡
ወፍ፡ ጤፈ
' በል። ሲበዛ፡ ድምቢጦች፡ ይላል፡ (ኤር፰፡ ፯። ማቴ፲፡ ፴፩፡ ፳፱)። (ተረት)፡ ድምቢጥም፡ እንዳ ቅ፡ በብር፡ ትታገማለች። መና፡ ነ፡ ተወራራ ሾች፡ ስለ፡ ኾኑ፡ ድንቢጥ፡ ተብሎም፡ ሊጻፍ ይቻ ላል። በግእዝ፡ ጻጹት፡ በትግሪኛ፡ ጺጹ፡ ትባላ ለች።
ድምታ፡ (ድመት)፡ ጩኸት ' ድም ' ማለት። ድመት፡ ግእዝኛ፡ ነው።
ድምንምን፡ (ደመንሚን)፡ ጨለማ፡ ድግዝታ፡ ዐፈና።
ድምንምን፡ አለ፡ (ኮነ፡ ደመንሚነ)፡ ጥቍርቍር፡ ጭልምልም፡ አለ።
ድምደማ፡ የመጨረስ፡ የማስተካከል፡ ሥራ፡ ፍጸማ።
ድምድማት፡ (ቶች)፡ የግንብ፡ የግድ ግዳ፡ የማንኛውም፡ ሥራ፡ ጫፍ፡ መጨረሻ፡ (መዝ፻፳፱ " ፯)፡
ድምድም፡ የተደመደመ፡ ትክክል፡ ወጣ፡ ገባ፡ የሌለበት።
ድምጠ፡ መልካም፡ ድምጠ፡ ማለፊያ፡ ሲዘፍን፡ ሲያዜም፡ ወዝና፡
ጣዕም፡ ላሕይ፡ ያለው።
ድምጠ፡ ሰላላ፡ ድምጠ፡ ቀጪን፡ ሴት ድምጥ፡ ሽማግሌ።
ድምጠ፡ ቢስ፡ ድምጠ፡ መጥፎ፡ ድ ምጡ፡ የማያምር።
ድምጠ፡ ጐርናና፡ ድምጠ ' ወፍራም፡ ጕልማሳ፡ ወይም፡ ሌላ፡
ድምጡ፡ የማይሰማ፡ ዝምተኛ፡ ጭምት።
ድምጣም፡ (ድምፃዊ)፡ ጯኺ ፣ ድ ምጠ፡ ረዥም፡ ድምጠ፡ ጕልሕ።
ድምጥ፡ (ድምፅ)፡ ካፍ፡ የሚወጣ፡ የሰው ' ቃል 1 የእንስሳ፡ ያውሬ፡ የወፍ፡ የደመና፡ የውሃ፡
የገደል፡ ማሚቶ፡ የሙዚቃ፡ ጩኸት፡ ጓታ። ሲበዛ፡
ድምጦች፡ ይላል።
ድምጥ፡ መለሰ፡ (ዐለወ)፡ እንደ፡ ጮኹ፡ ጮኸ፡ እንደ፡ ተናገሩ፡ ተናገረ፡
ገደሉ።
ድምጥ፡ ሰጠ፡ ቃል፡ አሰማ፡ እህ፡ አለ፡ ተናገረ።
ድምጥማጡ፡ ጠፋ፡ ማጥ፡ እንደ፡ ዋ ጠው፡ ኾነ፡ የደረሰበት፡ ታጣ። ደረሰ፡ ብለኸ፡ ድራሽን፡ እይ።
ድምጥማጥ፡ (የማጥ፡ ድምጥ)፡ ጭም ጭምታ፡ ወሬ፡ ፍለጋ።
ድምጫ፡ (ድምፀት)፡ ስሚ፡ መስማት።
ድምጽ - በቁሙ - ድምፅ።
ድምፅ - ድምጥ - ደመጠ።
ድምፅን፡ ስለበ)፡ ቃልን ዘጋ።
ድሰቃ፡ የቡጢ፡ ምት።
ድስም፡ ቅጽልና፡ ስም፡ መኾኑን፡ አስተ ውል።
ድስም፡ በሾኸ፡ የታጠረ፡ የዘላን፡ ዐጥር፡ ወዘፍ።
ድስም፡ የተዘጋ፡ ዝግ፡ ድፍን፡ የበረት፡ የሾኸ፡
መዝጊያ፡ ከላይ፡ በንጨት፡ ተንጠልጥሎ፡ ከታች፡ በባላ፡ የሚከፈት።
ድስም፡ የተደሰመ፡ የተለተመ፡ ልትም።
ድስቅ፡ የተደሰቀ፡ የተደቃ፡ ዠርባ፡ ደረት።
ድረ፡ ገብ፡ አንድ፡ ወንድ፡ ያወቃት፡ የደረሰባት፡ ሴት፡
ፈት።
ድረስ፡ (እስከ)፡ ደቂቅ፡ አገባብ - እን፡ ወይም፡ እስከን፡ ከአንቀጽና፡ ከስም፡
ጋራ፡ እያስቀደመ፡ ይነገራል። ኤልያስ፡
እስኪጠግብ፡ ድረስ፡ መብል፡ በላ። እቤቴ፡
ድረስ፡ መጥተሽ፡ እንገናኝ። እስከ፡
የግእዝ
ï ድረስ፡ ያማርኛ፡ ነው።
ድረስ፡ ትእዛዝ፡ አንቀጽ ፬ ና፡ ቅረብ፡ ግባ።
ድረስ፡ ንቃ፡ ተነሣ፡ ብድግ፡ በል። ድረስ፡ እንዲል፡ ሌባሻይ።
ድረስ፡ ድረሴ ፣ የሰው፡ ስም።
ድረታ፡ የመደረት፡ ሥራ።
ድሪ፡ የወርቅና፡ የብር፡ ፈትል፡ በሐር፡ ላይ፡
የተጠመጠመ፡ የልጃገረድ፡ አንገት፡ ጌጥ፡ ማተብ። ሲበዛ፡
ድሪዎች፡ ይላል፡ (ዘፀ፳፰፡
፲፫፡ ፲፬)።
ድሪ፡ ድሪያ፡ ቅንጥ፡ ቅንጦት፡ የምንዝር፡ ልፊያ።
ድሪ ጌጥ ፣ ደራ።
ድሪም፡ (ድርህም)፡ የፋርስ፡ ገንዘብ፡ ስም፡ ፪፡ ቀመት፡ ፩፡
ድሪም፡ ነው። ሚዛኑም፡ ገንዘቡም፡ ድሪም፡ ይባላል። ሲበዛ፡ ድሪሞች፡ ያሠኛል።
ድሪቶ፡ (ትግ፡ ድርዕቶ)፡ ያዲስና፡ ያሮጌ፡ ልብስ፡ ደባደቦ፡ ፪፡
ጣት፡ ዐለፍ፡ የተሰፋ። (የጥጥ፡
ድሪቶ)፡ ሥሥ፡ ፍራሽ፡ ከታች፡ ምንጣፍ፡ ከላይ፡
መደረቢያ፡ የሚኾን፡ የሚሰፋውም፡ በግም ጃና፡
ባዲስ፡ ቡልኮ፡ ነው።
ድሪቷም፡ ድሪቶ፡ ለባሽ፡ ባለድሪቶ።
ድሪያ ፣ መቃበጥ፡ ደራ።
ድራማ፡ (ሞች)፡ ያገዳ፡ ራስ፡ የጭን ኵሮ፡ ክምር። ታላቅ፡ ከፍተኛ፡ ልዑል፡ ዘራማ፡ ራማዊ፡ ማለት፡
ነው፡
ድራር፡ (ደሪር፡ ደረ)፡ መደንን፡ የሬሳ፡ ቤት፡ የመሬት፡ ቅርጽ። በግእዝ፡ ግን፡ እራት፡ ማለት፡ ነው፡ ይኸውም፡
ማች፡ የመቃብር፡ እራት፡ መኾኑን፡ ያሳያል።
ድራር፡ ዐቃፊ፡ ሥሥ፡ ደንጊያ፡ በድራር፡ ዙሪያ፡ ተደርድሮ፡
የሚቆም፡ የሬሳ፡ ሣጥን።
ድራሽ፡ አምላኩ፡ ጠፋ፡ በሴዴ ቅያስ፡ ጊዜ፡ ቤተ፡ መቅደስ፡ ተቃጠለ፡ (፪ዜና ፲፮፡ ፲፱)። በቈስጠንጢኖስ፡ ዘመን፡ ያረመኔው፡ ቤተ፡ ጣፆት፡
ፈረሰ፡ ተደመሰሰ።
ድራሽ፡ አምላክ፡ የአምላክ፡ ምልክት፡ ወይም፡ አምላክ፡ የደረሰበት፡
ተገልጦ፡ የታየበት፡ ቤተ፡ አብርሃም፡ ደብተራ፡ ኦሪት።
ድራሽ፡ አሠር፡ ፍለጋ፡ ድምጥማጥ፡ ጭ ገሬታ። ድራሹ፡ ጠፋ፡ እንዲሉ።
ድራተኛ፡ ባለድራት፡ ሻፋዳ።
ድራት፡ (ምርዐት)፡ ሽፍጃ።
ድራት፡ ለማጣነት ፣ ደራ።
ድራት፡ መድራት፡ ለማጣነት።
ድሬ፡ ዳዋ፡ ከሐረርጌ፡ በታች፡ በበረሓ፡ ውስጥ፡ ያለ፡
ከተማ፡ የባቡር፡ ጣቢያ፡ ድሬ ፥ ሜዳ፡ ዳዋ፡ መማቻ፡ ማለት፡ ነው፡ በዙሪያው፡
ያሉ፡ ዘላኖች፡ ለመንጋቸው፡ ውሃ፡ ሲያጠጡ፡ ይደባደቡበት፡ ነበርና፡ በዚህ፡ ስም፡ ተጠራ፡ ይባላል።
ድር ፣ ዝሓ፣ ደራ።
ድር፡ (ደራ)፡ የደራ፡ የተለመጠ፡ ለማጣ፡ ልምጥ፡ እግር፡
ጣራ፡ እግረ፡ ድር፡ እንዲሉ።
ድር፡ (ድርዕ)፡ የተደራ፡ ቀኝ፡ ዝሓ፡ ጠንካራ፡ ፈትል፡
ዝርግ። ዳግመኛም፡ በግእዝ፡ ስፍሕ፡ ይባላል። (ተረት)፡ ድር፡ ቢያብር፡ አንበሳ፡ ያስር። (የሸረሪት፡ ድር)፡ ቀጪን፡ ረቂቅ፡ የሸረሪት፡ ፈትል፡ ፀሓይ፡
ሲመታው፡ የሚበጠስ፡ የሸረሪት፡ ከጣራ፡ ወደ፡ ምድር፡ ከምድር፡ ወደ፡ ጣራ፡ መውረጃና፡ መውጫ።
ድር፡ እስኪት፡ ብልት፡ የወንድነት፡ ምልክት።
ድርምስ፡ አለ፡ ተደረመሰ፡ ፍርስ፡ አለ፡
ድርምስ፡ የተደረመሰ፡ ውድቅ።
ድርምቢታም፡ ግዳም፡ ወፍራም።
ድርምቢት፡ (ደረበ)፡ ግድ፡ ድርብርብ፡ ሥጋ። ም፡ ሲቀር፡ ድርቢት፡ የተደረበች፡ ማለት፡
ይኾናል።
ድርሰት፡ (ቶች)፡ መልክ፡ ሰላምታ፡ ቅኔ፡ ዐርኬ፡ ግጥም፡
ቃል፡ ነገር፡ ስብከት፡ ገድል፡ ድርሳን፡ ታምር፡ የመሰለው፡ ኹሉ።
ድርሱ፡ ተገኘ፡ ርግጡ፡ ታወቀ፡ እው ነቱ፡ ተረዳ፡ ተገለጠ።
ድርሳነ፡ መድኀኔ ዓለም፡ የመድኀኔ፡ ዓለም፡ ድርሳን፡ አባ፡ መባአ፡
ጽዮን፡ የጻፈው።
ድርሳነ፡ ሚካኤል፡ የሚካኤል፡ ድርሳን።
ድርሳነ፡ ማሕየዊ፡ የጌታችንን፡ ነገረ፡ መስቀል፡ የሚናገር።
ድርሳነ፡ ማርያም፡ ነገረ፡ ማርያም።
ድርሳነ፡ ሰንበት፡ የሰንበት፡ ድርሳን፡ ያዕቆብ፡ ዘስሩግ፡
የደረሰው።
ድርሳነ፡ ሥላሴ፡ የሥላሴ፡ ድርሳን።
ድርሳነ፡ ሩፋኤል፡ የሩፋኤል ፣ ድርሳን።
ድርሳነ፡ ራጉኤል፡ የራጉኤል ፣ ድርሳን።
ድርሳነ፡ ኡራኤል፡ የኡራኤል ፣ ድር ሳን፡ የኢትዮጵያን፡ መጻእያት፡ የሚናገር።
ድርሳነ፡ ገብርኤል፡ የገብርኤል ' ድርሳን።
ድርሳን፡ (ኖች)፡ በሥላሴ፡ በማርያም' በጌታችን፡ በመላእክት፡ ስም፡ ስለ፡ ሃይማኖትና፡
ስለ፡ ምግባር፡ ከሊቃውንት፡ የተደረሰ፡ መጽሐፍ፡
ድርስ፡ (ሶች)፡ ለማርገዝ፡ የደረሰች፡ ጊደር፡ ረባ፡ አራት፡
ሸረፍ፡ ከብት።
ድርስ፡ ርጉዝ፡ ልትወልድ የቀረበች ክበድ፡ ላም፡ ርግዝናዋ፡ ከ፰፡ ወር፡ በላይ፡
የኾነ፡ ወይም፡ ወረ፡ ግቡ።
ድርስ፡ ርግጥ፡ እውነት፡ ጭራሽ።
ድርስ፡ የዛፍ፡ ስም፡ በሉጥ።
ድርስ፡ የዜማ፡ ምልክት፡ (ርስ)፡ በዜማ፡ መጽሐፍ፡ ተጽፎ፡ የሚገኝ።
ድርሻ፡ ክፍል፡ ዕድል፡ ፈንታ፡ ዕጣ፡ የቦታ፡ የርስት፡
የገንዘብ፡ የከብት፡ የማንኛውም፡ ነገር፡ (መክ፱፡
፪
· ፫)። ፈረንጆች፡ አክሲዮን፡ ይሉታል።
ድርሽ፡ ዝር፡ ትርው። እዚህ፡ ስፍራ፡ ዳግመኛ፡ ድርሽ፡ አትበል።
ድርቀ፡ ሐዋርያት፡ ሐምሌ፡ ፪ኛና ፫ኛ፡ ፬ኛ፡ ፭ኛ፡ ቀን፡ ዝናም፡ ተግ፡ የሚልበት፡
ፀሓይ፡ የሚታይበት፡ የሐዋርያት፡ በዓል።
ድርቀት፡ መድረቅ፡ ደረቅነት፡ የሆድ በሽታ፡ ዐይነ፡ ምድርን፡ እንደ፡ በጠጥ፡ የሚያደ ርግ።
ድርቄ፡ (ዎች)፡ ያልተሸመጠጠ፡ ያልተሸለመ፡ ዐረብ፡ ያለበሰ፡
የጐራዴ፡ መክተቻ፡ በንጨት፡ ላይ፡ ተሰፍቶ፡ የደረቀ፡ ከተጌጠ፡ በኋላ፡ ግን፡ አፎት፡ ሰገባ፡ ይባላል።
ድርቅ ፣ በጋ፡ ቦና፡ ዝናም፡ የጠፋበት፡ የታጣበት፡
ዘመን።
(ተረት)፡ ቅቤ፡ መዛኝ፡ ድርቅ ያወራል።
ድርቅ፡ በረሓ፡ ምድረ-በዳ፡ (መዝ፷፫፡ ፩)።
ድርቅ፡ አለ፡ ደረቀ፡ ክሽልል፡ አለ።
ድርቅና ፣ ደረቅነት፡ ጭከና።
ድርቆሽ፡ ደረቅ፡ ሣር፡ የተወቀጠ፡ ኰቸሮ።
ድርቋ፡ (ትግ)፡ ድርቆሽ፡ የከብት መኖ፡ (ኢሳ፭፡ ፳፬። ሆሴ፲፩ - ፬)።
ድርበብ፡ ከዳባ፡ ሳም፡ በላይ፡ ከመንተርፈፍ፡ በታች፡ ያለ፡ ስፍር፡ ይዘውት፡ ሲኼዱ፡ የማይፈስ።
ድርብ፡ (ቦች)፡ ሰፊ፡ ጥበብ፡ ያለው፡ ዋጋው፡ ፫፻፡ ጥሬ፡
ብር፡ የኾነ፡ ጌጠኛ፡ የማዕርግ፡ ልብስ፡ ዝቅዝቅ።
ድርብ፡ ፪፡ ቍና፡ የሚይዝ፡ ጕርዝኝ።
ድርብ፡ ተሸለመ፡ ድርብ፡ ለበሰ፡ ድርብ፡ ሠሪ፡ እንዲሉ።
ድርብ፡ ታቦት፡ የዋናው፡ ታቦት፡ ሁለተኛ።
ድርብ፡ ትርጓሜ፡ ብዙ፡ አወራረድ፡ ያለው፡ ፍች።
ድርብ፡ ዜማ፡ ንባቡ፡ አንድ፡ ሲኾን፡ ዜማው፡ ዕጥፍ፡
የኾነ።
ድርብ፡ የተደረበ፡ ዕጥፍ፡ የሆነ፡ ብርድ ልብስ፡ (ሩት፫፡ ፬)። ሰይጣን፡ ለወዳጁ፡ ድርብ፡ ነው፡ እንዲሉ።
ድርብ፡ ጃኖ፡ ዳርና፡ ዳሩ፡ የድርብ፡ ጥበብ፡ ያለበት፡
ጃኖ።
ድርብ፡ ጥርስ፡ በኋላ፡ የበቀለ፡ ላይኛ፡ ጥርስ።
ድርብርብ፡ የተደራረበ፡ ንብብር፡ ሥራ፡ ጠፈ።
ድርት፡ የተደረተ፡ የተደበደበ፡ የተጠቃ ቀመ፡ ጥቅምቅም።
ድርና፡ ማግ፡ ቀኝና፡ ግራ። ሰውየውና፡ ሴትዮዋ፡ ድርና፡ ማግ፡ ሆነው፡
(ተጣምረው፡ ተዋስበው)፡ ተገኙ።
ድርንቅ፡ የተደረነቀ፡ የታመቀ፡ የተረ ጠጠ፡ ዕምቅ፡ ርጥጥ።
ድርንቅ፡ ድርጭት፡ (ግእዝ)።
ድርዝ፡ የተደረዘ፡ የተለጐመ፡ ልጕም።
ድርደራ ፣ ድርዳሮ፡ ስደራ፡ ኵልኰላ፡ ግርገራ።
ድርደራ፡ የበገና፡ ምት።
ድርድር፡ (ሮች)፡ የተደረደረ፡ የመደ ብር፡ ዕቃ፡ ስድር፡ ኵልኵል፡ (፪ነገ፡ ፲፱፡ ፳፭። መዝ፸፱፡ ፩። ምሳ፳፮፡ ፰)።
ድርድር፡ የዕርቅ፡ ውል፡ ስምም። ኹለ ተኛው፡ ድ ' ይጠብቃል።
ድርጁ፡ (ድሩግ)፡ የደረጀ፡ ጽኑ።
ድርጁ፡ የተደራጀ፡ ዝግጁ፡ ስንዱ።
ድርጅት፡ ዝግጅት፡ መደራጀት።
ድርጅቶች፡ ዝግጅቶች።
ድርገት፡ አንድነት፡ ማኅበር፡ ሸንጎ፡ ጉባኤ፡ ብዙ፡ ሕዝብ፡ ገበያተኛ፡ ሰርገኛ፡ ዱለተኛ፡ ልቅሶኛ፡ አንድ፡ መኾን፡ ግጥሚያ።
ድርጊያ፡ ድርጊት፡ ሥራ፡ ብጀታ፡ አድራጎት።
ድርግ፡ (ድሩግ)፡ የተደረገ፡ ብጁ።
ድርግም፡ አለ፡ ዕልም፡ ጥፍት፡ አለ።
ድርግም፡ አደረገ፡ አሳወረ፡ አጨለመ።
ድርግም፡ የተደረገመ፡ የጠፋ።
ድርጎ፡ (ዎች)፡ በርቦ፡ በመቍነን፡ የሚለካ፡ ንፍሮ፡ ኵርማን፡ ጕርሻ፡ ምግብ፡ የንፊት፡ የውሃ፡ የርድ፡ የማንኛውም፡ ጥቅም፡ የመጠን፡ ስጦታ፡ በዕለትና፡ በወር፡ ባመት ፣ የሚደረግ።
ድርጎ፡ ርቦ፡ ታናሽ፡ መስፈሪያ።
ድርጎ፡ እንዶድ፡ እሰጥ፡ እንዳለ፡ ጐንደሬ፡ ባጤ፡ ቴዎድሮስ፡ ጊዜ፡ ሲወራረድ።
ድርጎኛ፡ (ኞች)፡ ድርጎ፡ ተቀባይ፡ ባለድርጎ።
ድርጥ፡ የተደረጠ፡ የታሸ፡ የተልባ፡ ሊጥ። የማር፡ ብጥብጥ፡ የተልባ፡ ድርጥ፡ እንዲሉ።
ድርጭቱ፡ ያ፡ ድርጭት፡ የርሱ፡ ድር ጭት።
ድርጭት፡ (ቶች)፡ ከርግብ፡ የሚያንስ፡ ወፍ ' ሥጋው፡ ንብብር፡ ድርብርብ፡ የኾነ፡ ተባ ቱም፡ እንስቱም፡ ድርጭት፡ ይባላል፡ (ዘፀ፲፮፡ ፲፫። መዝ፻፭፡ ፵)። የግእዝ፡ ስሙ፡ ድርንቅ፡ ፍርፍርት፡ ነው።
ድርጭቷ፡ ያች፡ ድርጭት፡ የርሷ፡ ድርጭት።
ድርፉጭ፡ አለ፡ ሰውነቱን፡ ሰብስቦ፡ ተቀመጠ፡ ቍጭ፡ አለ።
ድርፉጭ፡ የተሰበሰበ፡ የተቀመጠ፡ ስብ ስብ፡ ቅምጥ።
ድሮ፡ (ድራር)፡ የበዓል፡ ፊተኛ፡ ቀን፡ ዋዜማ። ዱሮን፡ እይ።
ድሮች፡ የተደሩ፡ ዝሓዎች።
ድሮች፡ የደሩ፡ የተለመጡ፡ እግሮች፡ ጣራዎች።
ድቀት ፣ መውደቅ ፣ ወደቀ።
ድቀና፡ ድክራ፡ የማቅረብ፡ ሥራ።
ድቍስ፡ አደረገ፡ ደቈሰ፡ ድቅቅ፡ ላም፡ ልዝብ፡ አደረገ።
ድቁስ፡ የተኛ፡ እንቅልፋም፡ (ግእዝ)።
ድቍስ፡ የተደቈሰ፡ የላመ፡ የለዘበ፡ ልዝብ፡ ደቃቅ፡
ብትን፡ ድልኸ። ትኵስ፡ በድቍስ፡ እንዲሉ።
ድቍና፡ ዲያቆንነት፡ ዲያቆን፡ መሆን፡ ክህነት። ድቍና፡ ቅስና፡ እንዲሉ።
ድቄታም፡ ባለድቄት፡ እንቅልፋም፡ ያዞ፡ ወገን።
ድቄት ፣ ከባድ፡ እንቅልፍ፡ ሰውነት፡ አድቃቂ። ደስቅን፡ እይ።
ድቅ፡ (ድቁቅ)፡ የደቀቀ።
ድቅስቃሽ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ድቅስቅስ፡ አለ፡ ተድቀሰቀሰ።
ድቅስቅስ፡ የተድቀሰቀሰ፡ የዛለ፡ ደካማ፡ ደቃቃ፡ አቅም፡
የለሽ።
ድቅቅ፡ አለ፡ ፈጽሞ፡ ደቀቀ፡ አመድ፡ ሆነ፡ ደከመ።
ድቅቅ፡ አደረገ፡ ፍጭት፡ አደረገ፡ አደቀቀ።
ድቅን፡ አለ፡ ተደቀነ።
ድቅን፡ አደረገ፡ ደቀነ።
ድቅን፡ የተደቀነ፡ የቋት፡ እኸል፡ ድክር።
ድቅደቃ፡ ወቀጣ፡ ጥቅጠቃ።
ድቅድቅ፡ (ደቃ)፡ የሕፃን፡ አካሄድ፡ ሩጫ።
ድቅድቅ፡ አለ፡ ሩጫ፡ ዠመረ፡ ሕፃኑ።
ድቅድቅ፡ የተደቀደቀ፡ የተጠቀጠቀ፡ ጥቅጥቅ፡ ውድቅት። ድቅድቅ፡ ጨለማ፡ እንዲሉ፡ (ኢሳ፰፡ ፳፪። ዮኤ፪፡ ፪)።
ድቋ፡ (ትግ)፡ ያልጠራ፡ መጠጥ፡ ጕሽ፡ ሲፈላ፡ ጋን፡ የሚደቃ።
ድበላ: ያበባ እኸል (ባቄላ፣ ዐተር፣ ሽንብራ፣ ጓያ፣ ምስር፣ አደንጓሬ፣ አገዳ፣ የገብስ፣ የስንዴ) መቀየ፡ አደፍ፣ ቀሊል።
ድበላ: ጭመራ፣ ቅየጣ።
ድበቃ: ስውራ፣ ሽሽጋ።
ድበታ: ጭቈና፣ ጫና።
ድቡ: የሰው ስም፡ "አዛዥ ድቡ" እንዲሉ።
ድቡ: ያ ድብ፡ የርሱ ድብ።
ድቡሽት: በዠማ፣ በዥረት ዳር የሚገኝ ደቃቅ አሸዋ፣ ድንቡልቅኝ። ፪ኛውን "ደበሰን" እይ።
ድባ: ትልቅና ክብ ዶቃ (ቀይ፣ ብጫ፣ ቅጠልያና አረንጓዴ፣ ዐመድማ፣ ሌላም ሕብር ያለው)። "ዘለለ፣ ነደደ" ብለህ "ዘሎ ባይኔን ነድን" ተመልከት። ዳሴና ዳቦ ድባ የደበደበ ዘሮች ናቸው፡ "ደበደበ" "አወፈረ" ተብሎ ይፈታልና። "ዳባም" የ"ድብዳብ" ከፊል ነው።
ድባርዋ: በሐማሴን ክፍል ያለ አገር፡ ጥንብራ።
ድባቡ፣ ድባቤ: የወንድና የሴት ስም፡ "የርሱ ድባብ፣ የኔ ድባብ" ማለት ነው።
ድባብ (ቦች): የታቦት፣ የንጉሥ ጥላ፡ ከቀርክሓና ከግምጃ ከባለቀለም ልብስ የተሠራ፡ ጕልላትና አጫዋች ዘርፍ ያለው የጃን ጥላ ዐይነት። "ወለዶ" ብለህ "ወላድን"፡ "ጫረ" ብለህ "አጫረን" እይ።
ድባኖ (ዐረ ድባን፣ ዝንብ): የደበነ ትንሽ፡ ዝንብ አከል።
ድቤ: ታናሽ ነጋሪት (ያረኾ ወይም የቃልቻ)።
ድቤ: ታናሽ ነጋሪት (ደበደበ)።
ድቤ: የመቃብር ዐፈር (ደበየ)።
ድቤ: የመቃብር ዐፈር በሬሳ ላይ የሚመለስ። "እከሌ በድቤ ቅበሩኝ ብሎ ተናዘዞ"።
ድብ (ቦች፣ ድብ ድባት): ኣድብቶ ሸምቆ የሚነጥቅ ብርቱ፣ ኀይለኛ አውሬ (የዥብ ወገን)፡ ነጭና ጥቍር (ኢሳ፶፱:፲፱)። "ዶባን" እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው። ተባቱንና እንስቱን ለመለየት።
ድብ አንበሳ: ታላቅ የንጉሥ ነጋሬት፡ የአንበሳ ድቤ።
ድብ: በሰሜን በኩል ጅብ ብለው የሚታዩ ኮከቦች፡ እነሰባቶ መርከበኞች የሚመለከቷቸው፣ መርከብ የሚመሩባቸው (ኢዮ፱:፱)።
ድብ: በቁሙ ደባ።
ድብለቃ: ቅልቀላ፣ ቅየጣ፣ ዝነቃ።
ድብል: ታላቅ ሸክም፡ ጥግር።
ድብል: የተደበለ ሽርብ።
ድብልቅ: የተደባለቀ፡ ቅልቅል፣ ቅይጥ፣ ዝንቅ፣ ውጥንቅጥ (የልመና እኸል)።
ድብልቅልቅ አለ: ትርምስምስ አለ፡ ፈጽሞ ተጣላ።
ድብልቅልቅ: የተደበላለቀ፡ ሽብር፣ ትርምስምስ (ኢሳ፳፪:፭፣ ሕዝ፯:፯)።
ድብልብሌ: የልጆች ማስፈራሪያ። "አያ ድብልብሌ" እንዲሉ።
ድብልብል፣ ድቡልቡል: የተድበለበለ፣ የተድቦለቦለ፡ ክብ እንክብል (ደንጊያ ወይም ሌላ ነገር)።
ድብልዝኝ: ኹለት ዝግኝ።
ድብስ: የተደበሰ፡ ጕብጕብ ሊጥ።
ድብርቅ (ዝ በረቅ): አበባው በሩቅ ሲያዩት "በረቅ" ወይም የድመት ዐይን የሚመስል በወይናደጋ የሚበቅል ቅጠል። ፍሬው ከብቅልና ከጥቍር ስንዴ ጋራ አንተክትኮ ሲጠጡት ለጕንፋን መድኀኒት ይኾናል።
ድብርቅ ዐይን: ዐይጥ ድመትን የሰደበው ስድብ (ተረት)።
ድብቅ ብዬ: የቀበሌ ስም፡ በቡልጋ ውስጥ ያለ ስፍራ።
ድብቅ አለ: ተደበቀ።
ድብቅ ድብቅ አለ: መላልሶ ተደበቀ።
ድብቅ(ቆች): የተደበቀ፣ ያደፈጠ ጦር፡ ዕቡ፣ ስውር፣ ሽሽግ (መሳ፳:፴፫:፴፮)።
ድብቅታ: ድብቅ ማለት፡ ስውር ቦታ።
ድብቆሽ: ዝኒ ከማሁ።
ድብብ: የተደበበ፣ የተዘረጋ፡ ዝርግ፣ ውጥር።
ድብት: ትንሽ ድግስ (የቈራቢ እራት) (ላስታና ዋድላ)።
ድብት: የተደበተ፡ የማይሰማ።
ድብን አለ: ሙትት፣ ክርር አለ።
ድብን አደረገ: ግድል አደረገ። በኀይል ገረፈ፣ ቈነጠጠ።
ድብን: የደበነ።
ድብኝት(ቶች): ከጭቃ ተበጅቶ የደረቀ የእኸል ማስቀመጫ (መክተቻ)፡ በርሚል መሳይ። "ጐሰጐሰን" እይ።
ድብክብክ: የተድበከበከ፡ አተላማ።
ድብደባ: ምት፣ አመታት (ዓብድ፩:፱)።
ድብዳብ (ቦች): ከነጠጕሩ የለፋ የበግ ቈዳ (ሌጦ)፡ ዘርፍ የሌለው ደበሎ፣ መቀመ።
ድብድባ: ያፈር፣ የጕድፍ ክምር (ኵይሳ)፡ አሸዋ፣ ድቡሽት፡ የፍግና የጠቦት ቍልል (ዘዳ፲፫:፲፮፣ ኢያ፰:፳፰፣ ዕዝ፮:፲፩)።
ድብድብ: ሽፍን፣ ጥቅልል (የብር፣ ያገዳ እኸል ራስ ከመዘርዘር በፊት የሚኾን)፡ ከዘረዘረ በኋላ "ጨርቋ" ይባላል።
ድብድብ: በድብዳብ የተለበደ የኮርቻ ዕንጨት (ጥንብ)።
ድብድብ: በጨርቅና በሞራ፣ በሠም፣ በዶሮ ማር፣ በሙጫ የተደፈነ፣ የተመረገ፡ ድፍን፣ ምርግ (ሰባራ ሸክላ)።
ድብድብ: ክርክር፣ ንዝንዝ።
ድብድብ: ወገራ፣ ግድያ። ፪ኛው "ድ" ይጠብቃል።
ድብድብ: የተደበደበ፣ የተመታ፡ ድርት።
ድቧ: ያች ድብ፡ የርሷ ድብ።
ድንሰራ፡ ችሰራ።
ድንስር፡ አለ፡ ተደነሰረ፡ ተረፈቀ።
ድንቀኛ፡ ድንቅ፡ አድራጊ፡ ባለድንቅ።
ድንቁ፡ ድንቄ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ድንቍል፡ የተደነቈለ፡ ውግ፡ ንቍር።
ድንቍርና፡ ደንቈሮ፡ መሆን፡ አላዋቂነት።
ድንቂቲ፡ የፈንጣጣ፡ ስም፡ ልጅን፡ ሁሉ፡ የምትሸልም፡
ስለ፡ ሆነች፡ ድንቂቱ፡ ተባለች።
ድንቂያ፡ ድንቅነት፡ ድማም።
ድንቅ፡ ነኸ፡ ነሽ፡ የወንድና፡ የሴት፡ ስም።
ድንቅ፡ አደረገ፡ ታምር፡ ሰራ፡ ሙት፡ አነሳ፡ እውር፡ አበራ።
ድንቅ፡ የደነቀ፡ ጉድ፡ ግሩም፡ አጀብ፡ እጹብ፡
ታሪክ፡ ታምር።
ድንቅር፡ የተደነቀረ፡ ሽጕር፡ ቅርቅር።
ድንቅነት፡ ድንቅ፡ መሆን።
ድንቅፍቅፍ፡ ውልክፍክፍ፡ ስንክልክል።
ድንቆች፡ ጉዶች፡ ታምሮች።
ድንበረተኛ (ኞች)፡ ወሰነተኛ፡ በድንበር፡ አጠገብ፡ ያለ፡ አዋሳኝ።
ድንበረኛ፡ (ኞች)፡ ወሰነኛ።
ድንበራ፡ ፍራት፡ ሽሽት፡ ዝላይ።
ድንበሮች፡ ወሰኖች።
ድንቡል ድንቡል አለ: ደቡልኛ፣ ደቦልኛ ኼደ፣ ተራመደ።
ድንቡል: ደቡልን፣ ደቦልን የመሰለ።
ድንቡሎ: የሴት ስም፡ ያሞላች፣ የወፈረች ሌት፡ ትንቡሼ። በደቦል አንጻር "ድንቡሎ" ተባለች።
ድንቡሽ፡ የደነበሸ፡ የሻገተ።
ድንብላል(ሎች): የቅመም ስም፡ ታናሽ ቅመም፣ ጣዕመ ማለፊያ፡ ክብ ድብልብል ማለት ነው።
ድንብልብል: ድብልብል።
ድንብርብር፡ ጥንብርብር።
ድንብዝብዝ፡ አለ፡ ጭልም፡ አለ።
ድንት፡ (ድልት)፡ ንኡስ፡ አገባብ፡ ዘላለም፡ ዝንት። ድንት፡ ያኑርኸ፡ ድንት፡ እስከ፡ ድንት፡ እንዲሉ።
ድንት፡ የፊደል፡ ስም፡ ደ፡ ዘላለምነትን ' ሳይለቅ፡ መዝጊያ፡ ማለት፡ ነው። ድልት፡ የግእዝ፡ ድንት፡ ያማርኛ።
ድንች፡ የተክል፡ ስም፡ የእንቅርብጭ፡ አይነት፡
ተክል፡ በስሩ፡ የሚያፈራ፡ ፍሬው፡ ተቀቅሎና፡ ተጠብሶ፡ የሚበላ። ሲበዛ፡
ድንቾች፡ ይላል።
ድንን፡ (ድኑን)፡ የተያያዘ፡ ጠጕር፡ ሳርና፡ እንጨት።
ድንከን፡ የጤፍ፡ ድርድር።
ድንኩል፡ (ትግ፡ ጓል)፡ አሰናካይ፡ መሬት።
ድንኩል፡ ድንኩል፡ አለ፡ ህፃንኛ፡ ሄደ፡ ድቅድቅ፡ ስንክል፡ ስንክል፡
አለ።
ድንክ፡ (ኮች)፡ አጭር፡ አልጋ፡ የዙፋን፡ ርካብ፡ መቀመጫና፡
መወጣጫ።
ድንክዬ፡ (ድንቃዊ)፡ ድንካዊ " የድንክ፡ አይነትና፡ ወገን፡ ቁመተ፡ ዶሮ፡
አጭርነቱ፡ የሚያስደንቅ፡ ዣርት፡ ቅልጥም፡ ሰው።
ድንኳኑ፡ ያ፡ ድንኳን፡ የርሱ፡ ድንኳን።
ድንኳኒቱ፡ ድንኳኗ፡ ያች፡ ድንኳን።
ድንኳን፡ (አረ፡ ዱካን)፡ ከዝተት ' ከሸማ፡ ካቡጀዲ፡ ከሀር፡ ከሸራ፡ የተበጀ፡
(የተሰፋ)፡ የነጋዴና፡ የዘማች፡ የመንገደኛ፡ ቤት።
ድንኳኗ፡ የርሷ፡ ድንኳን።
ድንዘዛ፡ ድንዛዜ፡ ድንዛዥ፡ የደም፡ መርጋት፡ ፈዛዛነት፡ አለመስማት።
ድንዛዣም፡ ባለድንዛዥ፡ ድንዛዜ፡ የማያጣው።
ድንዝ፡ አለ፡ ደነዘ፡ ጥርስ፡ አለ።
ድንዝ፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ድንዝዝ፡ (ድንዙዝ)፡ የደነዘዘ።
ድንዝዝ፡ አለ፡ ደነዘዘ።
ድንዳኔ፡ ውፈራ፡ ውፋሬ፡ ውፍረት።
ድንድን፡ (ኖች)፡ ውፍረት፡ ያለው፡ አጭር፡ መቀነት፡ የሴቶች፡
ቀሚስ፡ መታጠቂያ።
ድንጁ፡ (ድንጉግ)፡ ድንግግ፡ ውስን።
ድንጁድ፡ ያገር፡ ስም።
ድንጃን፡ (ደነጀ)፡ በላይኛው፡ ወግዳ፡ ያለ፡ አገር።
ድንገላ፡ (ድንጋሌ)፡ የሰውነት፡ ጥበቃ።
ድንገተኛ፡ (ኞች)፡ ግብታዊ)፡ የድንገት፡ ባለድንገት፡ ያልታሰበ፡ ነገር፡
አደጋ፡ ሞት።
ድንገት፡ (ድንቀት፡ ግብት)፡ ያልታሰበ፡ ጊዜ።
ድንገቶ፡ ድንጋታዊ፡ ዘክዛካ፡ የጧፍ፡ ሸማ፡ ባለ፪፡
በቅል።
ድንገጋ፡ (ድንጋጌ)፡ ውሳኔ፡ ውሰና፡ ጥንቀቃ።
ድንጉላ፡ ያልተኮላሸ፡ ቈላው፡ ያልወጣ፡ ፈረስ ' ግመል።
ድንጉል፡ (ሎች)፡ የማይናደፍ፡ ንብ፡ ውሃ፡ ቀጂ።
ድንጉል፡ ድምጸ፡ ወፍራም፡ የበገና፡ ዥማት፡ እንደ፡
ንብ፡ ድንጉል፡ የሚጮኸ።
ድንጕር፡ አባጣ፡ ጐባጣ፡ ጕራንጕር፡ ደንጐላጕል።
ድንጕር፡ የተደነጐረ፡ ድድቅ፡ ፍንቅል፡ ግልብጥ።
ድንጕርጕር፡ ፍንቅልቅል፡ ግልብጥብጥ፡ አይነት፡ ወጣ፡
ገባ፡ መንገድ፡ መጥፎ፡ ስፍራ፡ ማዕበል፡ ያበላሸው።
ድንጉጥ፡ (ጦች)፡ ድንጉፅ)፡ የደነገጠ፡ ፈሪ፡ ቀጥቃጣ።
ድንጋዩም ተረን ይባላል: ፻፲፫ ተኩል ግራም ያነሣል።
ድንጋይ፡ (ዮች)፡ ደንጊያ፡ የካህናት፡ ድንጋይ፡ የህዝብ፡
ቋንቋ፡ ነው።
ድንጋይ፡ ዳቦ፡ የድንጋይ፡ ዳቦ።
ድንጋግ፡ አቃባ፡ ደገፍ፡ ቃሲም፡ (ግእዝ)።
ድንጋጤ፡ (ድንጋፄ)፡ ፍራት፡ አዘን።
ድንጋጤ: ዝላይ፣ መደንገጥ፣ መዝለል (የልብ)።
ድንግላይ፡ (ዮች፡ ዎች)፡ የድንግል፡ ወገን፡ ባለድንግል።
ድንግል፡ መሬት፡ ያልተማሰ፡ ያልተቆፈረ፡ ሰው፡ ያልተቀበረበት፡
ስፍራ።
ድንግል፡ ማርያም፡ ከመውለድ፡ አስቀድሞ፡ በመውለድ፡ ጊዜ፡
ከመውለድ፡ በኋላ፡ ድንግል፡ የኮነች፡ ማሪያም።
ድንግል፡ ሴት፡ ያላወቀ፡ ወንድ፡ ወንድ፡ ያላወቃት፡
ልጃገረድ።
ድንግል፡ አጠፋ፡ አወቀ፡ ገሰሰ፡ ዳሰሰ፡ ጠረቈሸ።
ድንግል፡ ክብርና፡ ህግ፡ ማህተም።
ድንግልነት፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ልጃገረድነት።
ድንግልና፡ ድንግል፡ መሆን፡ መጠበቅ፡ ወይም፡ ክብርና።
ድንግሎች፡ (ደናግል)፡ ወንዶች፡ ልጆች፡ ልጃገረዶች።
ድንግሎች፡ ክብርናዎች።
ድንግር፡ የተደናገረ፡ የተሳተ።
ድንግርግር፡ አለው፡ ተሳሳተው፡ መላ፡ አጣ።
ድንግርግር፡ የተደነጋገረ፡ የተሳሳተ፡ ነገር።
ድንግዝ፡ አለ፡ ጭልም፡ አለ፡ ጊዜው።
ድንግዝ፡ የደነገዘ።
ድንግዝግዝ፡ አለ፡ ድግዝግዝ፡ እለ፡ ፈጽሞ፡ ጨለመ፡ አይን፡
ቢወጉ፡ የማይታይ፡ ሆነ።
ድንግዝግዝ፡ ድግዝግዝ፡ ጭልምልም።
ድንግዝግዝታ፡ ድግዝግዝታ፡ ጭልምልምታ።
ድንግግ፡ (ድንጉግ)፡ የተደነገገ፡ ውሱን፡ ጥንቅቅ።
ድንፋታ፡ (ወክህ)፡ ውካታ፡ ፉከራ፡ ዝላይ።
ድኝ፡ ከምድር፡ የሚገኝ፡ ቢጫዊ፡ አፈር፡ መድኀኒት፡
የሚሆን፡ የሚቃጠል።
ድኵላ(ሎች): የዱር ፍየል (በወይናደጋና በበረሓ የሚገኝ፡ ሥጋው የሚበላ)፡ ተባቱም እንስቱም፡ የዋላ፣ የብሖር ዐይነት።
ድኵሌ: የሃሌታ ዜማ ቤት፡ ምልክቱ "ዙ" ነው።
ድኵል: ዐጪርና ጐነ ሰፊ (ከብት)።
ድኩዬ: ዐጪር ዘንጋዳ፡ ወይም ማሽላ (ጥቃቅን ፍሬ ያለው)።
ድካ: እብነ ወሰን፡ የወሰን ደንጊያ።
ድካ: ወሰን (ደካ)።
ድካም: ልፋት፣ ጥረት፡ ስንፍና፣ ሀኬት፡ ዝለት።
ድክመት: ዝኒ ከማሁ፡ ምስነት።
ድክም (ደኪም): መድከም።
ድክም አለ: ደከመ።
ድክር(ሮች): የተደከረ፡ ድቅን፣ ግትር፣ ሰልፈኛ (የማይላላ፣ የማይረግብ፣ የማይደክም ጐበዝ፣ ብርቱ)።
ድክር: ያቶ በዛብኸ የፈረስ ስም። "በዙ አባ ድክር" እንዲሉ።
ድክን: የተደከነ፡ ስድር፣ ድርድር፣ ንብብር፣ ድርብርብ።
ድኰት: የእግር ጌጥ (የገምባሌ ዐይነት)፡ ቢተዋ መሳይ፣ መካፈቻና መጋጠሚያ ያለው (ከንሓስ፣ ከብር የሚሠራ)። ግርጃን እይ።
ድኳ (ትግ): የራስ ብርኵማ፡ ግርምዑድ በርጩማ፡ የሰው መቀመጫ፡ የሽባ መንፋቀቂያ፡ የዋንጫ መቆሚያ (ፍልፍል ዕንጨት)፡ የሸክላ ዐንገት (በልክ በመጠን የተበጀ)።
ድኳ: ሉሕ፣ ምንጣፍ (የእግር ማረፊያ) (ማር ፲፮:፴፮፣ ሉቃ ፳:፵፫፣ ግብ ሐዋ ፪:፴፭፣ ፯:፵፱)።
ድኳ: ግርምቡድ (ደካ)።
ድኺት: አንዲት ብቻ ቂጥኝ ከጕያ በቀር እፊት ላይ የማትወጣ።
ድኺት: ዐጪርና ቀን የዋልታ ዙሪያ ማገር።
ድኻ ሰብሳቢ: ድኻን እየሰበሰበ በቤቱ የሚያኖር፣ የሚያበላ፣ የሚያለብስ።
ድኻ ቀባሪ: ድኻ ጐጂ፣ ጨቋኝ።
ድኻ ነቀል: አቀንጭራ የሚባል ዐረም።
ድኻ አክባሪ: ድኻ ጠቃሚ (ደግ ሰው)።
ድኻ አደግ (ድክቱም): የሙት ልጅ፣ እናት አባት አልባ፡ ጕልቻ የላቀው (ዐመድ ያጠለቀው)፡ በድኽነት ያደገ (ሆሴ ፲፬:፫)።
ድኻ አደግ ኾነ (ደክተመ): ድኻ ኹኖ አደገ፡ አባት እናት ዐጣ።
ድኻ አደጎች (ድክቱማን): የሙት ልጆች (ኢዮ ፳፪:፱፣ ፳፬:፫፣ ምሳ ፳፫:፲)።
ድኻ(ኾች): ነዳይ፣ ምስኪን፣ ዕጦተኛ፣ ችግረኛ፡ ለማኝ፣ ቧጋች፣ ተመጽዋች (የሰው እጅ ጠብቆ ጥሮ ግሮ ዐዳሪ)፡ አይቶ ዐጣ፣ የሰው ታናሽ፣ ባይተዋር (መከ ፱:፲፭፣ ምሳ ፴:፲፬)። "ድኻ ጥኑ"። "ድኻ ይበላው እንጂ ይከፍለው አያጣም"። "ድኻ ቢናገር አያደምቅ፡ ቢጨብጥ እያጠብቅ"።
ድኻ: በቁሙ (ደኸየ)።
ድኽነት: ንዴት፣ ዕጦት፣ ችግር፡ ድኻ መኾን (ዘዳ ፲፭:፯፣ ምሳ ፮:፲፩፣ ማር ፲፪:፵፬)።
ድወላ: ምጥንታ፡ መደወል፣ ጥዘላ፣ ምድወታ።
ድው (ደወለ): ድም
ድው አለ: ድም አለ፣ ተሰማ።
ድው አለው: ቅዝዝ ኣለው፡ ፈዘዘ (እንደ ተመታ ሰው)።
ድው ድው አለ: አደዘደዘ፡ ርምጃሙን ኣሰማ።
ድውር(ሮች): የተደወረ፡ የማግ፣ የጥለት፣ የሐር፣ የጥሙር ጥቅል፣ ጥንጥን።
ድውይ (ድዉይ): የተደወየ፡ ዐጪር፣ ከርሞ፣ ጥጃ (ማቴ ፬:፪-፲፪)።
ድውይነት: በሽተኛነት፣ ዐጪርነት።
ድውዮች (ዱያን): በሽተኞች፣ ዐጪሮች።
ድዝደዛ: ጥዘላ፣ ወቀጣ፡ የከበሮ ምት።
ድዝድዝ: የተደዘደዘ፡ ሥራው የማያምር (ጸናጽል፣ መስቀል፣ ጻሕል)።
ድደቃ: ፍንቀሳ፣ ድንጐራ፣ ግልበጣ።
ድዱን፡ አሰጣ፡ ሣቀ፣ ገለፈጠ (ኣድራጊ)።
ድዳ: መናገር ሲያስብ ቃል መስጠት የማይችል (እእ የሚል)፡ አፈ እስር፣ አንደበተ ዝግ፡ እንደ እንስሳ የማይናገር ሰው (ኢሳ ፴፭:፮)። "አፍን ተመልከት"።
ድዳም: ድደ፣ ወፍራም፣ ድደ ፈጣጣ ሰው፡ ችኮ።
ድድ(ዶች): የጥርስ ሥር (መሠረት፣ መገኛ፣ መብቀያ)።
ድድር: የደደረ፡ ጥጥር፣ ጠንካራ፣ ደረቅ።
ድድቅ(ቆች): የተደደቀ፡ ፍንቅል፣ ድንጕር፣ ግልብጥ።
ድድቅ: የጓል ካብ፡ ወይም ዐጥር፣ ቅጥር፡ ንብብር፣ ድርብርብ (ጓል ዕንጨትና ደንጊያ በሌለበት አገር የሚሠራ)።
ድድብ: የደረቀ፡ ድድር። "ደበደበን ተመልከት፡ የደደበ ዘር ነው"።
ድድኾ (ደደካዊ): የንጨት ስም፡ አገዳው ቀልጣማ፣ ቅጠሉ ለስላሳ የኾነ፡ በወይናደጋ ቈላ የሚበቅል ታናሽ ዛፍ፡ የማርያም ጥላ።
ድድድ አለ: ሮጠ፣ ተንደረደረ። "ዲደን እይ"።
ድድድ: ሩጫ፣ መንደርደር።
ድዶች: የማይናገሩ፣ ቃል የማይሰጡ ሰዎች (ኢሳ ፴፪:፬)።
ድጅኖ(ዎች): በትረ ቃቃን፡ የደንጊያ መስበሪያ፣ መንደያ፣ መፈንቀያ፡ ንጥር ብረት ዘንግ መሳይ (ቀጪንና ወፍራም) (፩ነገ ፮:፯)።
ድገመና: ጨምርልና፣ አድርሰና (ና ቃለ አጋኖ ነው)። "ዓመት ዐውዳመት ድገመና" እንዲሉ ልጆች።
ድገመኝ: መልሰኸ ምታኝ፡ ጨምርልኝ።
ድገመኝ: አድርሰኝ፣ አብላኝ። "ዓመት ዓመት ድገመኝ" እንዲል ገበሬ።
ድገፋ: የመደገፍ ሥራ፡ ዕገዛ፣ ርዳታ።
ድጕልጕል: የተድጐለጐለ፡ ወፍራም፡ ዐጓጕል፣ ቅጥ የለሽ፡ እጅ እግር አልባ፡ ቅንቡርስ ዐይነት።
ድጕም: የተደጐመ፣ የተረዳ፡ ዕግዝ።
ድጕሰት፣ ድጕሳት: የድጕስ ሥራ፡ ጌጥ፣ ሽልማት፣ ሐረግ፣ አበባ።
ድጕስ: ሰገባ፣ ሽፋፍ፣ አፎት። "ስለት ድጕሱን፡ ደባ ራሱን" እንዲሉ።
ድጕስ: የተደጐሰ፣ የተጌጠ።
ድጕስ: ጌጠኛ (የመጽሐፍ ገበታ ልብስ)፡ ወይም የማኅደሩ ውግ ስንብር በተንቤኑ ላይ የሚታይ።
ድጋሚ: ፪ኛ ሥራ፡ ምላሽ፣ ዕርሻ።
ድጋም(ሞች): የለኈሳስ ንባብ፣ ጸሎት።
ድግ(ጎች): ፴ ክንድ መቀነት በወገብ ላይ የሚታሰር፣ የሚጠመጠም ደበላ የቤት ሥር (፩ሳሙ ፲፰:፬፣ ኢሳ፫:፳፬)።
ድግ: መቀነት (ደገደገ)።
ድግል: የተደገለለ፡ ትልቅ ጥምጥም (ሰፌዶ፣ የደገሌ ዐይነት)።
ድግም: የተደገመ፣ የተመለሰ፡ ፪ኛ የተሠራ።
ድግምታም: አስማታም፣ ጠንቋይ፣ መተተኛ።
ድግምት: የተደገመች፡ ድጋም፣ አስማት፣ መስታድርት።
ድግሱ ገማ፡ ሳይበላ ቀረ።
ድግስ(ሶች): የተደገሰ፡ ዝግጁ፣ ድርጁ፣ ስንዱ (እንጀራ፣ ወጥ፣ ጠላ)።
ድግር(ሮች) (ድጉር): ከግራር ተጠርቦ የተበጀ የበሬ ዕቃ፡ በስተሥር በቅትርት ከሞፈር ጋራ የተዋደደ፣ በስተጫፍ ከዕርፍ ከማረሻ ጋራ በወገል የተረገጠ፡ እንደ መቅዘፊያ ኹኖ ፈር የሚያሰፋ። (ተረት): "ገባርና ድግር ሲተካከል ያምር"። "የረዘመውን በጦር ያጠረውን በድግር"።
ድግና (ዴጋኒ): በ፯፻ ዓ.ም. የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ስም፡ "ተከታይ አሽከር" ማለት ነው (ድግና ሚካኤል እንዲል ክብረ ነገሥት)።
ድግን መትረየስ: እግራም ባለእግር መትረየስ (አግሬ ባላ የማያሻ)።
ድግን መጋዝ: ቀስት የሚመስል።
ድግን: የተደገነ፣ የታሰረ፣ የጐረሠ።
ድግዝታ: ምሽት፣ ጭልምታ። በግእዝ "ሕዋይ" ይባላል።
ድግዝግዝ አለ: ጭልምልም እለ።
ድግዝግዝ: የጨለመ፡ ጭልምልም።
ድግዝግዝታ: ጭልምልምታ፡ ፍጹም ድግዝታ።
ድግድጋት: የሸማ ትጥቅ፣ አስራት፡ የማደግደግ አኳኋን።
ድግድግ አለ: ልክክ አለ።
ድግድግ: የተደገደገ (የሸማ ትጥቅ)።
ድግድግ: የደገደገ፣ የተላከከ፣ ያደፈ (ልማም፣ ችክ፣ ሞራ)።
ድግጣ(ጦች): ቀጥታነት ያለው ዕንጨት። ከማነሱና ከመገርጣቱ በቀር ነገረ ሥራው ብርብራ ይመስላል። "ዕጣ በድግጣ" ንዲሉ።
ድግፍ: የተደገፈ፣ የተያዘ፡ ዕቅብ።
ድግፍግፍ: የተደጋገፈ፣ የተያያዘ፡ ቅርብርብ። "የከሌና የከሌ ዕድሜ ድግፍግፍ ነው"።
ድጓ
ድጓ (ሐማሴን ድጕዓ): ሙሾ፣ ቍዘማ፣ የሐዘን ዜማ። "ዐዘለ" ብለህ ፫ኛውን "ዕዝል" እይ፡ "ሐዲሱን መጽሐፈ ሰዋስው ገጽ ፫፻፴፱" አስተውል።
ድጓ ውሃው: ድጓ ዐዋቂ።
ድጓ(ዎች): የዜማ መጽሐፍ ስም፡ ቅዱስ ያሬድ የደረሰው፡ ካመት እስካመት በ፫ ዐይነት ዜማ የሚጸለይ መንፈሳዊ ድርሰት። ጽፈቱ ደቃቅ ረቂቅ በመኾኑ "ድጓ" ተባለ። "ድጓ ጾመ ድጓ" እንዲሉ። "ዶገዶገን" እይ። ዳግመኛም "ደገደገ" የ"ደገገ" ደጊም ስለ ኾነ፡ "ድጓ" ትልቅ ተብሎ ይተረጐማል (መዝገብ፣ ድጓ፣ ወደል፣ ድጓ) እንዲሉ። "ደግን" ተመልከት። ቅዱስ ኤፍሬምም በሱርስት ቋንቋ "ድጓ" እንደ ደረሰ ይነገራል።
ድጓ: በቁሙ ደገደገ።
ድጓ: እብቅ፣ ደቃቅ ገለባ።
ድጣም: ድጥ ያለው፣ ባለድጥ (ስፍራ፣ መንገድ)።
ድጥ (ዳኅፅ): ዝናም የመታው እርጥብ መሬት (ተዳፋት፣ አንሻታች፣ አንሸራታች)።
ድጥ ኾነ: ዳለጠ፣ ሙልጭልጭ አለ።
ድጦ፣ ድጦሽ: የተዳጠ፣ የተፈጨ (ምስር፣ ያተር ክክ፣ ንፍሮ) ወጥ የሚኾን።
ድፊት፡ የወንፊት፡ ወጥመድ፡ ወፍ፡ መያዣ፡ (ሆሴ፱፡ ፰)።
ድፋ፡ የጠነከረ፡ ስንደዶ፡ ሳይታጨድ፡ የተተወ።
ድፋርሳ፡ ድፋሳ፡ የበረሓ፡ እንስሳ፡ የበሬ፡ አይነት፡ ቀንዱ፡
ከሥር፡ እስከ፡ ጫፍ፡ ክርክር፡ ያለው።
ድፋባቸው፡ የሰው፡ ስም።
ድፋት፡ (ድፍዐት)፡ መድፋት፡ መደፋት።
ድፋት፡ መጨረሻ፡ ግጥም፡ ወይም፡ ስንኝ።
ድፋት፡ የከረጢት፡ ቀሚስ፡ የዱሮ፡ ዘመን፡ አንገትጌ፡
የሌለው፡ በ፪፡ ወገን፡ ክፍት።
ድፋት፡ የዜማ፡ ምልክት፡ ዝቅዝቅ፡ ጽፈት፡ የደረት፡
ተቃራኒ።
ድፋት፡ ያገባብ፡ ስም፡ ነጠላ፡ ድፋት፡ ድርብ፡
ድፋት፡ እንዲሉ።
ድፋዬ፡ የሰው፡ ስም።
ድፌት፡ ቍንናት፡ ያለው፡ የራስ፡ ጠጕር፡ በራስ፡
ላይ፡ የተደፋ፡ ቆብ፡ የሚመስል፡ ጥምጥም፡ ሥራ።
ድፍ፡ (ድፉዕ)፡ የተደፋ፡ የፈሰሰ፡ ክንድፎ፡ (ዎች)፡ ሥሥ፡ ዳቦ፡ ባለሰንበር፡ ሲጋገር፡ በወዙ፡
የተደፋ።
ድፍረሳ፡ መደፍረስ።
ድፍረት፡ ጭካኔ፡ አለማፈር፡ (ግብ፡ ሐዋ፬፡ ፲፫፡ ፳፱፡ ፴፩)። ሲያውቁ፡ በድፍረት፡ ሳያውቁ፡ በስሕተት፡ እንዲሉ።
ድፍር፡ ብዙ፡ ምርት፡ ቍልል።
ድፍር፡ የተደፈረ፡ የተነካ።
ድፍርስ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ያተለ፡ ጕሽ፡ ጥብጥ።
ድፍርስነት፡ ድፍርስ፡ መሆን።
ድፍቅ፡ የተደፈቀ፡ ዝፍቅ፡ የተፈጨ፡ የምስር፡ ወጥ።
ድፍት፡ መደፋት።
ድፍት፡ አለ፡ ተደፋ።
ድፍት፡ አደረገ፡ ክንብል፡ አደረገ።
ድፍነት፡ መድፈን፡ መደፈን፡ (ግእዝ)።
ድፍነት፡ ቀበራ፡ ደፈና። (የድፍነት)፡ የተቀበረ፡ መድኀኒት፡ ሀብተ፡ ሰንክል።
ድፍን፡ (ኖች)፡ የተደፈነ፡ ዝግ። ልበ፡ ድፍን፡ አፍንጫ፡ ድፍን፡ እንዲሉ።
ድፍን፡ ሁሉ፡ መላው፡ ጠቅላላው፡ ጕድለት፡ የሌለበት። ድፍን፡ ጐንደር፡ ድፍን፡ ሺዋ፡ እንዲሉ። (እንደ፡ እንቍላል፡ ድፍን፡ እንደ፡ ባር፡ ማሽላ፡
ሽፍን)፡ ያልተገለጠና፡ ያልታወቀ፡ ተንኰል።
ድፍን፡ ቅል፡ ያልተቈረጠ፡ ያልተከፈተ።
ድፍን፡ አለ፡ ዝግት፡ አለ።
ድፍን፡ አቋራሽ፡ ወንድም፡ ተካፋይ።
ድፍን፡ ዓመት፡ ሙሉ፡ ዓመት፡ ፲፪፡ ወር።
ድፍን፡ እንጀራ፡ ያልተሸረፈ ' ያልተቈረሰ።
ድፍን፡ ጥቍር፡ ድመት፡ ኹለት፡ አይነት፡ ቍራ፡ የደጋና፡
የቈላ።
ድፍን ጥቍር)፡ ድመት፣ ቍራ። ቀይና ነጭም እንደዚሁ ቅጽል ይኾናሉ።
ድፍንት፡ አፍንጫ ▪ ቢስ፡ ሴት።
ድፍንት፡ የተደፈነች፡ ቤት፡ መተናፈሻ፡ መስኮት፡
የሌላት።
ድፍንፍን፡ የተድፈነፈነ፡ ጭፍንፍን።
ድፍደፋ፡ መረጋ፡ ልወሳ።
ድፍድፍ፡ የተደፈደፈ፡ በውሃ፡ የራሰ፡ ዝፍዝፍ፡ የጠላ፡
ቡሖ፡ ሊጥ።
ድፍጥፍጥ፡ ፍርጥርጥ።
ዶለ (ደዊል ዶለ): ጨመረ፣ አገባ፣ ከተተ፣ አሰናዳ።
ዶለተ (ዶለ): ሰበሰበ፣ ዐደመ፡ ከንቱ ዐሳብ ዐሰበ፡ ክፉ ምክር መከረ፣ አሤረ፡ ነገር ቋጠረ።
ዶለተ: የዶለ ሳቢ ዘር ወይም ጥሬ ግስ ነው። "በረከተ የባረከ ጥሬ ግስ እንደ ኾነ"።
ዶለተ: ጨመረ፣ ቀላቀለ።
ዶለተን እይ፡ የዶለ ሳቢ ዘር ነው።
ዶለቾሜ: የዶለችም ዐይነት።
ዶለቾም: ዐጕል ሰው፣ ደነዝ።
ዶለዝ(ዞች): ደነዝ መጥረቢያ፡ ደደብ፣ ወፍራም ሰው (ልበ ደንቈሮ)።
ዶለዶለ) (ዶለ): አንዶለዶለ፡ አብዝቶ አፈሰሰ፣ አወረደ፡ ሰጠ።
ዶለዶመ: ፈጽሞ ደነዘ፣ ጐለደፈ፣ ተደመደመ።
ዶለዶሜ: የዶለዶም ዐይነት።
ዶለዶም: የዶለዶመ፣ የደነዘ።
ዶላች(ቾች): የዶለተ፣ የሚዶልት፡ መካሪ፣ ኣሢያሪ፣ ቋጣሪ፣ ሤረኛ፣ ነገረኛ።
ዶል: ያፈር ስም፡ ቀይ ዐፈር (ለሥዕልና ለጽፈት የሚኾን)።
ዶልዷላ: የሚንዶለዶል (ብዛት፣ ብዝነት ያለው) (የቦይ፣ የመስኖ ውሃ)።
ዶልዷሌ: የዶልዷላ ዐይነት፡ ለስጦታው ልክና መጠን፣ ወሰን የሌለው (ቸሩ ኣምላክ)።
ዶልዷማ: የዶለዶመ፡ ደነዝ፣ ጐልዳፋ (የዱልዱም ወገን)።
ዶልዷሜ: የዶልዷማ ዐይነት።
ዶመኛ፡ (ኞች)፡ ባለዶማ፡ ቈፋሪ፡ ድኻ፡ ጥማድ፡ የለሽ፡
በዶማ፡ ቈፍሮ፡ የሚበላ።
ዶማ፡ (ዎች)፡ ደምሐ፡ መድምሕ)፡ መማሻ፡ መቈፈሪያ፡ ዛቢያ፡ ያለው፡ ባለጕረሮ፡
ሹል፡ ብረት፡ ወደ፡ መሬት፡ የሚጠልቅ፡ የመሬት፡ ማንካ፡ ወይም፡ ጭልፋ። ዳግመኛም፡ ሹለ ትና፡ ስለት፡ ያለው፡ የፈረንጅ ' ዶማ፡ አለ (ከጅ፡ አይሻል፡ ዶማ)፡ ዕላቆ፡ ጕማ።
ዶሰ ፣ ዐየለ፡ በረታ።
ዶሰ፡ (አፅወሰ)፡ ለመሸ፡ ሽባ፡ አደረገ፡ አጥመለመለ።
ዶሰ፡ (ፀዊስ፡ ፆሰ። ትግ፡ ደወሰ። ዕብ፡ ዳሽ ፣ እኽል፡ አኼደ) ፣ ኣማሰለ፡ ደ ባለቀ።
ዶሰ፡ ብረትን፡ ደንጊያን፡ ቀጠቀጠ፡ አ ሣሣ፡ አጠፈጠፈ፡ አደቀቀ።
ዶሰ፡ ጣሰ፡ ጠመሰሰ።
ዶሰኛ፡ (ኞች)፡ ኀይለኛ፡ ጣሽ፡ ጠም ሳሽ፡ ባደባባይ፡ ተናጋሪ፡ አይፈር፡ ለፊቱ። (ተረት)፡ የበሬ፡ ዶሰኛ፡ የሴት፡ ምላሰኛ፡ አታምጣ፡
ወደኛ።
ዶሴ፡ የኔ፡ ዶስ።
ዶስ ፣ ኀይል፡ ብርታት፡ ዕጥፍ፡ ድርብ።
ዶረረ)፡ ፀረረ)፡ አስዶረረ፡ አኰራ፡ አስመካ፡
አስቈጣ፡ ኣስኰረፈ።
ዶረከከ)፡ አንደረከከ፣ አበሰለ፣ አሳጠረ፣ ዐጪር አደረገ፣ አወፈረ።
ዶሪ፡ የሰው፡ ስም፡ የትግሬ፡ ተወላጅ፡ የቅኔ፡
መምር፡ ወርቃዊ፡ ወርቅማ፡ ማለት፡ ነው።
ዶራሪ፡ የሽቱ፡ ዕንጨት፡ ስም።
ዶራር፡ ማሽላ፡ የማሽላ፡ ስም።
ዶር፡ ጥሩ፡ ወርቅ።
ዶርዜ፡ (ዎች)፡ የነገድና፡ ያገር ▪ ስም፡ በኦሮ፡ ቤት፡ በወላሞ፡ አጠገብ፡ ያለ፡
አገር፡ ወይም፡ ሸማኔ፡ ሕዝብ።
ዶሮ፡ (ዎች)፡ (ዶርሆ)፡ ለማዳ፡ የቤት፡ አሞራ፡ ነጭ፡ ቀይ፡ ጥቍር፡
ወሰራ፡ ገብስማ፡ ዛጐልማ፡ ተባቱም፡ እንስቱም።
ዶሮ፡ ማታ፡ ጧት፡ ለኮሶ፡ ጠጪ፡ የሚነገር፡ ፈሊጥ፡
ዘዬ። ትርጓሜው፡ ማታ፡ ዶሮ፡ ትበላለኸ፡ ማለት፡
ነው። ሆድ፡ ሲያውቅ፡ ዶሮ፡ ማታ፡ እንዲሉ።
ዶሮ፡ ማነቂያ፡ ባዲስ፡ አበባ፡ አራዳ፡ ውስጥ፡ ያለ፡ ስፍራ።
ዶሮ፡ ሲሉ፡ ሰምታ፡ ሞተች፡ ከጪስ፡ ገብታ።
ዶሮ፡ በሌ፡ የበሬ፡ በሽታ፡ የሚያፈዝ፡ የሚያደነግዝ። ዶሮውን፡ በራሱ፡ ላይ፡ አዙሮ፡ ሥጋውን፡ ቀቅሎ፡
ከንጀራ፡ ጋራ፡ ቢያበሉት፡ በሬው፡ ስለሚድን፡ በሽታው፡ ዶሮ፡ በሌ፡ ተባለ።
ዶሮ፡ በጋን፡ ትንሹን፡ ጥቂቱን፡ በትልቅ፡ በሰፊ፡ ውስጥ፡
መጨመር።
ዶሮ፡ ዋጭ፡ ዶሮ፡ ነጣቂ፡ አሞራ፡ ጭልፊትን፡ ገዲን፡
ሲላን፡ የመሰለ።
ዶሮ፡ ዳቦ፡ (የዶሮ፡ ዳቦ)፡ ከዶሮ፡ ወጥ፡ ጋራ፡ የተጋገረ፡ ዳቦ።
ዶሮ ዳቦ): ከዶሮ ወጥ ጋራ የተጋገረ የዶሮ ዳቦ።
ዶሮ፡ ጩኸት፡ እኩለ፡ ሌሊት።
ዶሮ፡ ጮኸ፡ ኵኵሉ፡ አለ።
ዶሮዋ፡ የርሷ፡ ዶሮ።
ዶሮዋ፡ ዶሮዪቱ፡ ያች፡ ዶሮ።
ዶሮው፡ ያ፡ ዶሮ፡ የርሱ፡ ዶሮ።
ዶሸዶሸ)፡ አንዶሸዶሸ፡ የራሰ፡ ባ ቄላን፡ ዐተርን፡ ሽንብራን፡ በቈሎን ፣ ቈላ፡ እንጦ ሸጦሸ። በተገብሮነትም፡ ይፈታል።
ዶቀረ ፣ ደራ።
ዶቀረ፡ ሰምቶ፡ ዝም፡ አለ፡ ወይ፡ ሳይል፡ ቀረ።
ዶቃ፡ (ደቀቀ)፡ የልጆች፡ አንገት፡ ጌጥ፡ ውስጠ፡ ቀዳዳ፡
ከሸክላ፡ ተሠርቶ፡ ሰማያዊ፡ ቀለም፡ እየተቀባ፡ ሺንና፡ ከህንድ፡ አገር፡ የሚመጣ። (የበቅሎ፡ ዶቃ)፡ ከንሓስ፡ ከብር፡ የተበጀ፡ አልቦ።
ዶቃን፡ ተመልከት፡ የደቀቀ፡ ዘር፡ ነው።
ዶቅማ፡ የዛፍ፡ ስም፡ ፍሬው፡ የሚበላ፡ እንጨት። የእስላም፡ ሴቶች፡ ጪሱን፡ ይሞቁታል፡ ፪ኛ፡
ስሙ፡ አዝጋሮ፡ ነው።
ዶበረ): አዶበረ፡ ተከፋ፣ አኰረፈ፣ ተቀየመ፡ ብቻውን ኾነ፡ ዝም አለ።
ዶበዶብ: ክርፋታም የበልግ አንበጣ (መብረርና መመሠጥ የማይችል)።
ዶቢ (ኦሮ): ሳማ፡ የሳማ ስም ነው።
ዶባ (ዕብ ዶብ፡ ድብ): የበሬ ስም፡ ያዳል (የበረሓ ቀንደ ረዥም በሬ) ያጋዘን ዐይነት።
ዶባ: ሰሞፈር ውሃ አጠገብ ያለ አገር፤ የመንዝ ክፍል ነው።
ዶባች: የደሰተ፣ የሚደብት፣ የሚጫን (ከባድ እንቅልፍ፣ ድቄት፣ ደስቅ)።
ዶብማ (ድብማ): ድብ (ዥብ) የሚመስል በሬ ያጋዘን ዲቃላ፡ የጅን ዘር።
ዶኬ: ዝኒ ከማሁ።
ዶዮ ቀቃይ: ዶዮ የምትቀቅል፡ ዶዮ ሠሪ (ሴት፣ ሥራ ቤት)። "ዶዮ ቀቃይ ትሙት" እንዲል ወታደር።
ዶዮ: ተራና መናኛ ወጥ (ቅቤና ቅመም የሌለበት)። ዘሩና ምንጩ በግእዝ ወደየ ነው።
ዶዶት: የበግ ዐንገት ዕብጠት (ዕንቅርት የሚመስል ኵልኵልት)፡ በቅጠልና በሣር፣ በውሃ ምክንያት የሚመጣ በሽታ። "ቡንኝን ደደቆን እይ"።
ዶገዶገ: ወረ፣ ሞወረ፡ አቀጠነ፣ አረቀቀ፣ አሳነሰ (የጽፈት፣ የማዕርግ፣ የመጠን)።
ዶጉ: የበሬ ስም
ዶግ ዐመድ ኾነ: ድራሹ ጠፋ።
ዶግ(ጎች): የንስላል ዐይነት፡ እንዳገዳ የቀለለ ዕንጨት፡ ቀጫጭን ቅጠሉ የፈረስ ጭራ የሚመስል። "ዶግ ዐመድ" እንዲሉ።
ዶግ: ዕንጨት (ዶገዶገ)።
ዶግማ: በጥቍርና በቀይ መካከል ያለ የከብት መልክ።
ዶግዷጋ: ሙጭርጭር ጽፈት፡ የድጓ ምልክት ዐይነት ረቂቅ።
ዶግዷጌ: የዶግዷጋ ወገን፡ ሙጭርጭሬ። "ድጓ ዶግዷጌ" እንዲሉ። "ቀኘ" ብለህ "ቅኔን" እይ።
ዶጮ(ዎች): ከመስቴ፣ ከቻች፣ ከብጕሪት፣ ከቡይት የሚበልጥ፣ ከገንቦ የሚያንስ የሸክላ ዕቃ (የጠጅ፣ የጠላ፣ የውሃ ማኖሪያ)።
ዶጮ: በወላምኛ ሆድ ማለት ነው።
ዶፈዶፈ፡ ገዘፈ፡ ወፈረ፡ ከበደ፡ እንደ፡ ድፍድፍ።
ዶፈዶፍ፡ ዶፍዷፋ፡ የዶፈዶፈ፡ ወፍራም።
ዶፍ፡ (ሐረር፡ ዱፍ፡ ነፋስ)፡ የማያቋርጥ፡ ኃይለኛ፡ ዝናም፡ ከነፋስ፡
ጋራ፡ የሚዘንም።
ዷ አለ: ጠንሷ አለ፣ ጮኸ።
ዷ አለ: ጮኸ (ዷዷ)።
ዷዷ): አንዷዷ (አፈነዳ፣ አጮኸ፣ ተኰሰ)።
No comments:
Post a Comment