ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ፀ፡ የጸ ዲቃላ ፪ኛ ዐ በግእዝ ኣልፍ ሴት በአበገደ ። በተራ ቍጥር ፲፱ኛ ሲኾን ስሙ ፀጰ፡ በአኃዝነት 600 ይባላል ። ጻፎችም ፀሓይ ፀ ይሉታል ። ነገር ግን በፊደልነት መደ በኛው ፲፱ኛ ቀ ነው ።
ፀሓየ ልዳ፡ ዐዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ አጥቢያ የነበሩ ሳታት ቋሚ የብሉይ መምር የሺዋ ተወላጅ ። በአድዋ ዘመቻ ጊዜ ዐጤ ምኒልክ ጣሊያንን ድል ያደርጉታል፡ ነገር ግን ባርባ ዓመት ተመልሶ ዘርዎን ይገ ዛዋል ብለው በጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ አማካይነት ትንቢት የተናገሩ ።
ፀሓየ ልዳ፡ የልዳ ፀሓይ (የቅዱስ ጊዮርጊስ የግብር ስም ") ።
ፀሓዩ፡ የርሱ ፀሓይ ።
ፀሓያም፡ የፀሓይ ሙቀት የሚበዛበት ስፍራ ።
ፀሓይ (ጸሐየ)፡ ጣይ የበራ የሚ በራ (የዓለም መብራት ") ። "ቀን በአፍሪቃና በእስያ ባውሮጳ ፲፪ ሰዓት፡ ሌሊት ባሜሪካ ፲፪ ሰዓት ያበራል" ። "ፀሓይ" የግእዝ ስሙ ነው፡ ባማ ርኛ "ጀንበር" ይባላል ።
ፀሓይ ሰገድ፡ ያጤ ዮስጦስ ስመ መንግሥት (ፀሓይ የሰገደለት ማለት ነው ") ።
ፀሓይ ፀ፡ ጻፎች "ጸሓይ" በማለት ፈንታ "ፀሓይ" ብለው ስለሚጽፉ ፀጰ ፀን ፀሓይ ፀ ይሉታል ። (ተረት)፡ "ልማድ ይከብዳል ከግንድ" ።
ፀሓይዋ (ፀሓዪቱ)፡ ያች ፀሓይ ።
ፀሓይዋ፡ የርሷ ፀሓይ ("(ኤር. ፲፭፥ ፱)") ።
ፀሓዮች (ፀሓያት)፡ ፀሓይን የመሰሉ እንደ ፀሓይ የሚያበሩ ኮከቦች ቅዱሳን ። "ፀሓይ ወጣ"፡ ብቅ አለ፡ እውነት ተፈረደ ።
ፀምር፡ ሱፋላ የበግ ጠጕር፡ ወይም በርኖስ ("(ግእዝ)") ። ዛሬ ግን አለስሙ ሱፍ ይሉታል ።
ፀረ መናፍቃን፡ ጠላቶች መናፍቆች ማለት ነው፡ አፅራር መናፍቃን ቢል በቀና ነበር ። "ከሰማየ ሰማያት አልወረደም፡ ከድንግል ማርያም አልተወለደም የሚሉ ፀረ መናፍቃ ንን እምገጸ ምድር ያጥፋልን" እንዲል የባላጎር ቄስ ።
ፀረ ማርያም (አንድሪማጢስ)፡ ጠረ ማሪያም የማሪያም ጠላት ("(ድኅረ ወለደት ክርስቶስሀ ተደመረት ምስለ ዮሴፍ)") እያለ የመቤታችንን ድንግልናዋንና ቅድስናዋን ንጽሕናዋን የሚክድ መናፍቅ ይሁዲ ። በዘመናችንም ክርስቲያኖች ነን እያሉ ይህን ክሕደት በስውር የሚሰብኩ እንደ አይሁድም የሚያስ ተምሩ የውጭ አገር ሰዎች ባገራችን ይገኛሉ፡ እነዚህም ወንጌልን ወንጀል ያሠኛሉ።
ፀረ ታንክ፡ ታንክን የሚያበላሽ መ ድፍ ።
ፀረ አንቄ፡ ሲላ ።
ፀረሰ፡ ተቸረቸመ ጠረሰ ።
ፀረረ (ፀሪር ፀረረ)፡ ጠላ ጠላት አደረገ ። "ጠረረን" አስተውል ። "ፀረረ" የግእዝ፡ "ጠረረ" ያማርኛ ነው ።
ፀረረ፡ ዕሩር ሠራ አለበሰ ።
ፀረፈ (ፀሪፍ ፀረፈ)፡ ክፉኛ ሰደበ አዋረደ ። "ጨረፈን" ተመልከት ።
ፀር ከል (ከላኤ ፀር)፡ የግንብ ዐጥር መከታ ጠላተ ከልክል (ያጐዶ ደንጊያ ") ።
ፀር ከልበጋር ፀርከል። ፀረ መናፍቃን፡ የመናፍቃን ጠላት (እለእስክንድሮስ ጢሞቴዎስ ቄርሎስ ዲዮስቆሮስ ") ።
ፀር፡ ጠር ጠላት ። "ለዲያብሎስ ፀሩ መታገሥ"፡ "ለረኃብ ፀሩ ማረስ" ።
ፀር፡ ፀረረ ።
ፀነሰ (ፀንሰ)፡ ጠነሰ ጠነሰሰ ። "ረገዘ" ብለኸ "አረገዘን ከበደን" እይ ።
ፀነሰች (ፀንሰት)፡ ደም በሆዷ ቀረ፡ ጠነሰች ጠነሰሰች ያዘች ቋጠረች ።
ፀዳ፡ ነጣ ጸዳ ።
ፀጰ (ፀጳ)፡ የፊደል ስም ፀ ። "እሳትማ ፀሓይማ" ማለት ነው ።
ፀፍር (ፀፈረ)፡ ጠፍር ። "ፀፍርና መሥ ነቅት እንዳለ ተማሪ" ።
ፃሰርጔ (ፀሓይ ሽልማቴ - ሰርጕየ)፡ ፀሓይ ሽልማቴ (ከፍተኛ የማዕርግ ስም ") ። "ያጤ ዘርዐ ያዕቆብ ታሪክ"፡ "አምኃ ኢየሱስ ፃሰርጔ ገብረ ዋሕድ ፃሰርጔ መርቆሬዎስ ፃሰርጔ"፡ "እሉ ፃዕርጔ ሠለስቱ ፃሰርጔ ቤተ ፃዕርጔ መንበረ ማርያም ፃሰርጔ" እንዲል ። "ገጽ ፲ ፹፬ ፹፭ ፻፷፬ ፻፸፪ ፻፸፯ ፻፹፩" እይ ።
ፃሰርጓ (ፀሓይ ሰርጓ - ሰርጕሃ)፡ ፀሓይ ሽልማቷ ጌጧ (የንግሥቲቱ የይተጌዪቱ ") ። ይኸውም ነጭ ሐርን ላንቃንና ወርቅን ያሳያል ("(ራእ. ፲፪፥ ፩)") ። የተረሳ ቋንቋ ነው ። "ሰረፃ" ብለኸ "ሰርጓይን" እይ ። ዳግመኛም "ፃሰርጓ (ጸ ሓፌ ሰርጓ)" ቢል፡ የግምጃ ቤቷ ጸሓፊ ("(ሹም)") ተብሎ ይተረጐማል።
ፃት፡ ጣት ።
ጻድቅ (ቃን)፡ ደግ ቅን ገር የ ዋህ እውነተኛ ሰው (ምግባሩ የቀና ሃይማ ኖቱ የጸና የግዜር ወገን ለነፍሱ ያደረ ") ። "ጻድቁ"፡ ያ ጻድቅ ።
ፃግታ (ፀግዐ)፡ ጥግ መከታ ጋሻ ።
ፅሩር፡ የጦር ልብስ ሐምበል ። "ፅሩር" የካህናት፡ "ጥሩር" የሕዝብ አነጋገር ነው ። "ዕሩር" ቅጽል ሲኾን በጥሬነት መነገሩን አስተውል ።
ፅራር፡ ዝኒ ከማሁ ።
ፅርር የተፀረረ ።
ፅርፈት፡ መስደብ ስድብ ።
ፅንሰቱ፡ በመጋቢት ፳፱ ቀን የጌታ ችን ያለዘር መፀነሱ (የመፀነሱ በዓል ") ።
ፅንሰታ፡ በነሐሴ ፯ ቀን የመቤታ ችን መፀነሷ በዓል ። ርግጠኛው ግን ታኅሣሥ ፯ ቀን ነው ። "ወለደ" ብለኽ "ልደታን" እይ ።
ፅንሰት፡ መፅነስ መፀነስ ።
ፅንስ፡ የቍርባን ርሾ ።
ፅንስ፡ ጥንስ ጥንስስ (የተንቀሳቃሽ ፍጥረት የአካል ውጥን ጥንት ዥምር ሽል የማሕፀን ፍሬ ") ።
ፀሓየ ልዳ፡ ዐዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ አጥቢያ የነበሩ ሳታት ቋሚ የብሉይ መምር የሺዋ ተወላጅ ። በአድዋ ዘመቻ ጊዜ ዐጤ ምኒልክ ጣሊያንን ድል ያደርጉታል፡ ነገር ግን ባርባ ዓመት ተመልሶ ዘርዎን ይገ ዛዋል ብለው በጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ አማካይነት ትንቢት የተናገሩ ።
ፀሓየ ልዳ፡ የልዳ ፀሓይ (የቅዱስ ጊዮርጊስ የግብር ስም ") ።
ፀሓዩ፡ የርሱ ፀሓይ ።
ፀሓያም፡ የፀሓይ ሙቀት የሚበዛበት ስፍራ ።
ፀሓይ (ጸሐየ)፡ ጣይ የበራ የሚ በራ (የዓለም መብራት ") ። "ቀን በአፍሪቃና በእስያ ባውሮጳ ፲፪ ሰዓት፡ ሌሊት ባሜሪካ ፲፪ ሰዓት ያበራል" ። "ፀሓይ" የግእዝ ስሙ ነው፡ ባማ ርኛ "ጀንበር" ይባላል ።
ፀሓይ ሰገድ፡ ያጤ ዮስጦስ ስመ መንግሥት (ፀሓይ የሰገደለት ማለት ነው ") ።
ፀሓይ ፀ፡ ጻፎች "ጸሓይ" በማለት ፈንታ "ፀሓይ" ብለው ስለሚጽፉ ፀጰ ፀን ፀሓይ ፀ ይሉታል ። (ተረት)፡ "ልማድ ይከብዳል ከግንድ" ።
ፀሓይዋ (ፀሓዪቱ)፡ ያች ፀሓይ ።
ፀሓይዋ፡ የርሷ ፀሓይ ("(ኤር. ፲፭፥ ፱)") ።
ፀሓዮች (ፀሓያት)፡ ፀሓይን የመሰሉ እንደ ፀሓይ የሚያበሩ ኮከቦች ቅዱሳን ። "ፀሓይ ወጣ"፡ ብቅ አለ፡ እውነት ተፈረደ ።
ፀምር፡ ሱፋላ የበግ ጠጕር፡ ወይም በርኖስ ("(ግእዝ)") ። ዛሬ ግን አለስሙ ሱፍ ይሉታል ።
ፀረ መናፍቃን፡ ጠላቶች መናፍቆች ማለት ነው፡ አፅራር መናፍቃን ቢል በቀና ነበር ። "ከሰማየ ሰማያት አልወረደም፡ ከድንግል ማርያም አልተወለደም የሚሉ ፀረ መናፍቃ ንን እምገጸ ምድር ያጥፋልን" እንዲል የባላጎር ቄስ ።
ፀረ ማርያም (አንድሪማጢስ)፡ ጠረ ማሪያም የማሪያም ጠላት ("(ድኅረ ወለደት ክርስቶስሀ ተደመረት ምስለ ዮሴፍ)") እያለ የመቤታችንን ድንግልናዋንና ቅድስናዋን ንጽሕናዋን የሚክድ መናፍቅ ይሁዲ ። በዘመናችንም ክርስቲያኖች ነን እያሉ ይህን ክሕደት በስውር የሚሰብኩ እንደ አይሁድም የሚያስ ተምሩ የውጭ አገር ሰዎች ባገራችን ይገኛሉ፡ እነዚህም ወንጌልን ወንጀል ያሠኛሉ።
ፀረ ታንክ፡ ታንክን የሚያበላሽ መ ድፍ ።
ፀረ አንቄ፡ ሲላ ።
ፀረሰ፡ ተቸረቸመ ጠረሰ ።
ፀረረ (ፀሪር ፀረረ)፡ ጠላ ጠላት አደረገ ። "ጠረረን" አስተውል ። "ፀረረ" የግእዝ፡ "ጠረረ" ያማርኛ ነው ።
ፀረረ፡ ዕሩር ሠራ አለበሰ ።
ፀረፈ (ፀሪፍ ፀረፈ)፡ ክፉኛ ሰደበ አዋረደ ። "ጨረፈን" ተመልከት ።
ፀር ከል (ከላኤ ፀር)፡ የግንብ ዐጥር መከታ ጠላተ ከልክል (ያጐዶ ደንጊያ ") ።
ፀር ከልበጋር ፀርከል። ፀረ መናፍቃን፡ የመናፍቃን ጠላት (እለእስክንድሮስ ጢሞቴዎስ ቄርሎስ ዲዮስቆሮስ ") ።
ፀር፡ ጠር ጠላት ። "ለዲያብሎስ ፀሩ መታገሥ"፡ "ለረኃብ ፀሩ ማረስ" ።
ፀር፡ ፀረረ ።
ፀነሰ (ፀንሰ)፡ ጠነሰ ጠነሰሰ ። "ረገዘ" ብለኸ "አረገዘን ከበደን" እይ ።
ፀነሰች (ፀንሰት)፡ ደም በሆዷ ቀረ፡ ጠነሰች ጠነሰሰች ያዘች ቋጠረች ።
ፀዳ፡ ነጣ ጸዳ ።
ፀጰ (ፀጳ)፡ የፊደል ስም ፀ ። "እሳትማ ፀሓይማ" ማለት ነው ።
ፀፍር (ፀፈረ)፡ ጠፍር ። "ፀፍርና መሥ ነቅት እንዳለ ተማሪ" ።
ፃሰርጔ (ፀሓይ ሽልማቴ - ሰርጕየ)፡ ፀሓይ ሽልማቴ (ከፍተኛ የማዕርግ ስም ") ። "ያጤ ዘርዐ ያዕቆብ ታሪክ"፡ "አምኃ ኢየሱስ ፃሰርጔ ገብረ ዋሕድ ፃሰርጔ መርቆሬዎስ ፃሰርጔ"፡ "እሉ ፃዕርጔ ሠለስቱ ፃሰርጔ ቤተ ፃዕርጔ መንበረ ማርያም ፃሰርጔ" እንዲል ። "ገጽ ፲ ፹፬ ፹፭ ፻፷፬ ፻፸፪ ፻፸፯ ፻፹፩" እይ ።
ፃሰርጓ (ፀሓይ ሰርጓ - ሰርጕሃ)፡ ፀሓይ ሽልማቷ ጌጧ (የንግሥቲቱ የይተጌዪቱ ") ። ይኸውም ነጭ ሐርን ላንቃንና ወርቅን ያሳያል ("(ራእ. ፲፪፥ ፩)") ። የተረሳ ቋንቋ ነው ። "ሰረፃ" ብለኸ "ሰርጓይን" እይ ። ዳግመኛም "ፃሰርጓ (ጸ ሓፌ ሰርጓ)" ቢል፡ የግምጃ ቤቷ ጸሓፊ ("(ሹም)") ተብሎ ይተረጐማል።
ፃት፡ ጣት ።
ጻድቅ (ቃን)፡ ደግ ቅን ገር የ ዋህ እውነተኛ ሰው (ምግባሩ የቀና ሃይማ ኖቱ የጸና የግዜር ወገን ለነፍሱ ያደረ ") ። "ጻድቁ"፡ ያ ጻድቅ ።
ፃግታ (ፀግዐ)፡ ጥግ መከታ ጋሻ ።
ፅሩር፡ የጦር ልብስ ሐምበል ። "ፅሩር" የካህናት፡ "ጥሩር" የሕዝብ አነጋገር ነው ። "ዕሩር" ቅጽል ሲኾን በጥሬነት መነገሩን አስተውል ።
ፅራር፡ ዝኒ ከማሁ ።
ፅርር የተፀረረ ።
ፅርፈት፡ መስደብ ስድብ ።
ፅንሰቱ፡ በመጋቢት ፳፱ ቀን የጌታ ችን ያለዘር መፀነሱ (የመፀነሱ በዓል ") ።
ፅንሰታ፡ በነሐሴ ፯ ቀን የመቤታ ችን መፀነሷ በዓል ። ርግጠኛው ግን ታኅሣሥ ፯ ቀን ነው ። "ወለደ" ብለኽ "ልደታን" እይ ።
ፅንሰት፡ መፅነስ መፀነስ ።
ፅንስ፡ የቍርባን ርሾ ።
ፅንስ፡ ጥንስ ጥንስስ (የተንቀሳቃሽ ፍጥረት የአካል ውጥን ጥንት ዥምር ሽል የማሕፀን ፍሬ ") ።
No comments:
Post a Comment