ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ፀ ፡ የጸ፡ ዲቃላ፡ ፪ኛ፡ ዐ፡ በግእዝ፡
አልፍ፡ ቤት፡ በአበገደ። በተራ፡
ቍጥር፡ ፲፱ኛ፡ ሲኾን፡ ስሙ፡ ፀጰ፡ በአኃዝነት፡ ፷፻፡ ይባላል። ጻፎችም፡ ፀሓይ፡ ፀ፡ ይሉታል። ነገር፡ ግን፡ በፊደልነት፡ መደበኛው፡ ፲፱ኛ፡
ቀ፡ ነው።
ፀሓየ፡ ልዳ፡ ዐዲስ፡ አበባ፡ በቅድስት፡ ሥላሴ፡ አጥቢያ፡
የነበሩ፡ ሳታት፡ ቋሚ፡ የብሉይ፡ መምር፡ የሺዋ፡ ተወላጅ፡ በዐድዋ፡ ዘመቻ፡ ጊዜ፡ ዐጤ፡ ምኒልክ፡ ጣሊያንን፡ ድል፡ ያደርጉታል፡
ነገር፡ ግን፡ ባርባ፡ ዓመት፡ ተመልሶ፡ ዘርዎን፡ ይገዛዋል፡ ብለው፡ በጸሓፌ፡ ትእዛዝ፡ ገብረ፡ ሥላሴ፡ አማካይነት፡ ትንቢት፡ የተናገሩ።
ፀሓየ፡ ልዳ፡ የልዳ፡ ፀሓይ፡ የቅዱስ፡ ጊዮርጊስ፡ የግብር፡
ስም።
ፀሓዩ፡ የርሱ፡ ፀሓይ።
ፀሓዩ፡ ያ፡ ፀሓይ።
ፀሓያም፡ የፀሓይ፡ ሙቀት፡ የሚበዛበት፡ ስፍራ።
ፀሓይ (ጸሐየ)፡ ጣይ፡ የበራ፡ የሚበራ፡ የዓለም፡ መብራት፡
ቀን፡ በአፍሪቃና፡ በእስያ፡ ባውሮጳ፡ ፲፪፡ ሰዓት፡ ሌሊት፡ ባሜሪካ፡ ፲፪፡ ሰዓት፡ ያበራል። ፀሓይ፡ የግእዝ፡ ስሙ፡ ነው፡ ባማርኛ፡ ጀንበር፡
ይባላል።
ፀሓይ፡ ሰገድ፡ ያጤ፡ ዮስጦስ፡ ስመ፡ መንግሥት፡ ፀሓይ፡
የሰገደለት፡ ማለት፡ ነው።
ፀሓይ፡ ወጣ፡ ብቅ፡ አለ፡ እውነት፡ ተፈረደ።
ፀሓይ፡ ፀ፡ ጻፎች፡ ጸሓይ፡ በማለት፡ ፈንታ፡
ፀሓይ፡ ብለው፡ ስለሚጽፉ፡ ፀጰ፡ ፀን፡ ፀሓይ፡ ፀ፡ ይሉታል። (ተረት)፡ ልማድ፡ ይከብዳል፡ ከግንድ።
ፀሓይዋ፡ የርሷ፡ ፀሓይ፡ (ኤርምያስ ፲፭፡ ፱)።
ፀሓይዋ፡ ፀሓዪቱ፡ ያች፡ ፀሓይ።
ፀሓዮች (ፀሓያት)፡ ፀሓይን፡ የመሰሉ፡ እንደ፡ ፀሓይ፡ የሚያበሩ፡
ኮከቦች፡ ቅዱሳን።
ፀምር፡ ሱፋላ፡ የበግ፡ ጠጕር፡ ወይም፡ በርኖስ፡
(ግእዝ)። ዛሬ፡ ግን፡ አለስሙ፡ ሱፍ፡ ይሉታል።
ፀረ፡ መናፍቃን፡ የመናፍቃን፡ ጠላት፡ እለእስክንድሮስ፡ ጢሞቴዎስ፡
ቄርሎስ፡ ዲዮስቆሮስ።
ፀረ፡ መናፍቃን፡ ጠላቶች፡ መናፍቆች፡ ማለት፡ ነው፡ አፅራር፡
መናፍቃን፡ ቢል፡ በቀና፡ ነበር። ምሳሌ: "ከሰማየ፡ ሰማያት፡ አልወረደም፡ ከድንግል፡
ማርያም፡ አልተወለደም፡ የሚሉ፡ ፀረ፡ መናፍቃንን፡ እምገጸ፡ ምድር፡ ያጥፋልን"፡ እንዲል፡ የባላጎር፡ ቄስ።
ፀረ፡ ማርያም (አንድሪማጢስ)፡ ጠረ፡ ማርያም፡ የማርያም፡ ጠላት፡ (ድኅረ፡ ወለደት፡ ክርስቶስሀ፡ ተደመረት፡ ምስለ፡
ዮሴፍ)፡ እያለ፡ የመቤታችንን፡ ድንግልናዋንና፡ ቅድስናዋን፡
ንጽሕናዋን፡ የሚክድ፡ መናፍቅ፡ ይሁዲ። በዘመናችንም፡
ክርስቲያኖች፡ ነን፡ እያሉ፡ ይህን፡ ክሕደት፡ በስውር፡ የሚሰብኩ፡ እንደ፡ አይሁድም፡ የሚያስተምሩ፡ የውጭ፡ አገር፡ ሰዎች፡ ባገራችን፡
ይገኛሉ፡ እነዚህም፡ ወንጌልን፡ ወንጀል፡ ያሠኛሉ።
ፀረ፡ ታንክ፡ ታንክን፡ የሚያበላሽ፡ መድፍ።
ፀረ፡ አንቄ፡ ሲላ።
ፀረሰ፡ ተቸረቸመ፡ ጠረሰ።
ፀረረ (ፀሪር፡ ፀረረ)፡ ጠላ፡ ጠላት፡ አደረገ። ጠረረን፡ አስተውል። ፀረረ፡ የግእዝ፡ ጠረረ፡ ያማርኛ፡ ነው።
ፀረረ፡ ዕሩር፡ ሠራ፡ አለበሰ።
ፀረፈ (ፀሪፍ፡ ፀረፈ)፡ ክፉኛ፡ ሰደበ፡ አዋረደ። ጨረፈን፡ ተመልከት።
ፀር፡ ከል (ከላኤ፡ ፀር)፡ የግንብ፡ ዐጥር፡ መከታ፡ ጠላተ፡ ከልክል፡
ያጐዶ፡ ደንጊያ፡ እሳት፡ ባለጅን፡ እንዳያቃጥል፡ የሚከለክል። ፀር፡ ከል፡ በጋር፡ ጸርከል።
ፀር፡ ጠር፡ ጠላት። ምሳሌ: ለዲያብሎስ፡ ፀሩ፡ መታገሥ፡ ለረኃብ፡
ፀሩ፡ ማረስ።
ፀነሰ (ፀንሰ)፡ ጠነሰ፡ ጠነሰሰ። ረገዘ፡ ብለኸ፡ አረገዘን፡ ከበደን፡
እይ።
ፀነሰች (ፀንሰት)፡ ደም፡ በሆዷ፡ ቀረ፡ ጠነሰች፡ ጠነሰሰች፡
ያዘች፡ ቋጠረች።
ፀዳ፡ ነጣ፡ ጸዳ።
ፀጰ (ፀጳ)፡ የፊደል፡ ስም፡ ፀ፡ እሳትማ፡
ፀሓይማ፡ ማለት፡ ነው።
ፀፍር (ፀፈረ)፡ ጠፍር። ምሳሌ: ፀፍርና፡ መሥነቅት፡ እንዳለ፡ ተማሪ።
ፃሰርጔ (ፀሓይ፡ ሽልማቴ)፡ ከፍተኛ፡ የማዕርግ፡ ስም። ምሳሌ: ያጤ፡ ዘርዐ፡ ያዕቆብ፡ ታሪክ፡ አምኃ፡ ኢየሱስ፡
ፃሰርጔ፡ ገብረ፡ ዋሕድ፡ ፃሰርጔ፡ መርቆሬዎስ፡ ፃሰርጔ፡ እሉ፡ ፃዕርጔ፡ ሠለስቱ፡
ፃሰርጔ፡ ቤተ፡ ፃዕርጔ፡ መንበረ፡ ማርያም፡ ፃሰርጔ፡ እንዲል። ገጽ፡ ፲፡ ፹፬፡ ፹፭፡
፻፷፬፡ ፻፸፪፡ ፻፸፯፡ ፻፹፩፡ እይ።
ፃሰርጓ (ፀሓይ፡ ሰርጓ፡ ሰርጕሃ)፡ ፀሓይ፡ ሽልማቷ፡ ጌጧ፡ የንግሥቲቱ፡ የይተጌዪቱ፡
ይኸውም፡ ነጭ፡ ሐርን፡ ላንቃንና፡ ወርቅን፡ ያሳያል፡ (ራእይ ፲፪፡ ፩)። የተረሳ፡ ቋንቋ፡ ነው፡ ሰረፃ፡
ብለኸ፡ ሰርጓይን፡ እይ። ዳግመኛም፡
ፃሰርጓ (ጸሓፌ፡ ሰርጓ)፡ ቢል፡ የግምጃ፡ ቤቷ፡ ጸሓፊ፡ (ሹም)፡ ተብሎ፡ ይተረጐማል።
ፃት፡ ጣት።
ፃግታ (ፀግዐ)፡ ጥግ፡ መከታ፡ ጋሻ።
ፅሩር፡ የጦር፡ ልብስ፡ ሐምበል። ፅሩር፡ የካህናት፡ ጥሩር፡ የሕዝብ፡
አነጋገር፡ ነው። ዕሩር፡
ቅጽል፡ ሲኾን፡ በጥሬነት፡ መነገሩን፡ አስተውል።
ፅራር፡ ዝኒ፡ ከማሁ።
ፅርር፡ የተፀረረ።
ፅርፈት፡ መስደብ፡ ስድብ።
ፅንሰቱ፡ በመጋቢት፡ ፳፱፡ ቀን፡ የጌታችን፡
ያለዘር፡ መፀነሱ፡ የመፀነሱ፡ በዓል።
ፅንሰታ፡ በነሐሴ፡ ፯፡ ቀን፡ የመቤታችን፡
መፀነሷ፡ በዓል። ርግጠኛው፡
ግን፡ ታኅሣሥ፡ ፯፡ ቀን፡ ነው። ወለደ፡
ብለኸ፡ ልደታን፡ እይ።
ፅንሰት፡ መፅነስ፡ መፀነስ።
ፅንስ፡ የቍርባን፡ ርሾ።
ፅንስ፡ ጥንስ፡ ጥንስስ፡ የተንቀሳቃሽ፡ ፍጥረት፡
የአካል፡ ውጥን፡ ጥንት፡ ዥምር፡ ሽል፡ የማሕፀን፡ ፍሬ።
No comments:
Post a Comment