Friday, June 6, 2025

                                

ጋጠ
ገሃ/ግሃ (ገህህ/ገህግሀ) በረቅ ወይም ነጭና ቀይ ብሓ (ዐፈር ያነሰው መሬት የብሓ ቦረቦር)
ገሃ፡ ርሚጦ/ብርኩታ (ባመድ በመሬት ውስጥ ተዳፍኖ ወይም ሊጡ በደንጊያ ተድበልብሎ የበሰለ) "ብርኩታ '' መባልን ከደንጊያው የወሰደ ይመስላል።"
ገሓ፡ ነጭ ጠመኔ
ገሃነመ እሳት፡ የእሳት ጕድጓድ (የኃጥኣን መኖሪያ ክፉዎች የሥራቸውን ዋጋ)
ገሃነም፡ ሄኖም የሚባል ሰው ያቀናው ጐድጓዳ ቈላ/ሸለቆ ከኢየሩሳሌም በስተ ደቡብ ያለ እስራኤል ልጆቻቸውን ለሞሎኸ ይሠዉበት የነበረ ቦታ
ገሃድ፡ ግልጥ፡ ጋድ
ገለለ፡ ተዘረጋ/ጠፍጣፋ ኾነ (ተገብሮ)
ገለለ፡ ዐወደ/ቈረጠ/ነቀለ/አጠራቀመ (ገቢር)
ገለለመጠ፡ ኣሞቀ/ኣጋለ/ኣላበ/ኣተኰሰ
ገለለጠ (ቀለጠጠ) ጥርስን ፍምን ፈጽሞ ገለጠ/ዛቀ/ገለፈጠ/ሣቀ
ገለለጠመ (ቀለጠመ) ናቀ/ነቀፈ/አኰሰሰ
ገለለጠጥ/ገልጣጣ፡ መገለጢጥ/ገልፋጣ
ገለሌ (ሐቃላዊ) የገለል ወገን (በረኸኛ ዐርበኛ)
ገለል አለ፡ ራቅ አለ/ተገለለ
ገለል አደረገ፡ ራቅ አደረገ
ገለል ገለል አለ፡ ፈቀቅ ፈቀቅ አለ
ገለል/ገለሌ፡ የገዳይ ያርበኛ ሽለላ ዘፈን ቅርርት
ገለል፡ ራቅ/ፈቅቅ/ዕልፍ (፪ዜና. ፳፫፡ ፲፭)
ገለል፡ የራቀ/የተወገደ (ውግድ ዐዳኝ)
ገለልተኛ (ኞች) የተለየ/የራቀ (በገለልታ የሚቀመጥ ብቸኛ) "የቦታ ቅጽልም ይኾናል 'ገለልተኛ ስፍራ' እንዲሉ።"
ገለልተኛነት፡ ውግድነት/ብቸኛነት
ገለልታ፡ ልዩ ስፍራ (ደባቃና ሰዋራ)
ገለልታ፡ ፈቀቅታ/ርቀት
ገለሚጡ፡ ዲያቆን መሥዋዕት ሲሠራ የሙጋድ ወላፈን የሚገለምጠው "የቅኔ ቤት ዐማርኛ ነው።"
ገለማ፡ ጣመ ቢስ ኾነ/ተበላሸ እጅ እጅ አለ (የንፍሮ)
ገለሞተ (ጋለ) ወንደ ላጤ ፈት ኾነ (ብቻውን አለሚስት ተቀመጠ ኖረ)
ገለሞተች፡ ባል አልባ ኖረች (አመነዘረች) (ዘፍ. ፴፰፡ ፳፬)
ገለሞታ/ጋለሞታ (ቶች) (ጋለ ሞቷ) ባልየሌላት አመንዝራ ሸርሙጣ (ባንድ ወንድ የማትጸና የማትኖር ኻያጅ ቅንዝረኛ ሞቷ የጋለ የተቃጠለ) (ዘፍ. ፴፰፡ ፲፭, ፳፩፳፪)
ገለሰሰ፡ ገለፈፈ (ድዱን በለሰሰ ገለጠ አሰጣ)
ገለስላሳ/ግልስልስ (ቀለሰ) የተኛ/የተመሳቀለ (ቀለስላሳ ቅልስልስ ሣር ጤፍ ጠጕር)
ገለበ (ገሊብ/ገለበ) (ዐረ. ቀለበ) ገለጠ/ገለበጠ (የጭን/የቋጥኝ)
ገለበ፡ መግለቦ ሠራ/ሸሸገ/አጠመደ/ሳበ/ጐተተ ዓሣን
ገለበ፡ አቀለለ/ፍሬ ቢስ አደረገ
ገለበ፡ አቃጠለ/አሳረረ እኸልን "እሳቱ ዐሻሮውን ገለበው" እንዲሉ።
ገለበጠ
ገለበጠ፡ ቀዳ/ጨመረ/አጋባ/ደፋ/አፈሰሰ/ጨርሶ ጠጣ/ከለበሰ/ከነበለ (ኤር. ፴፰፡ ፲፪)
ገለበጠ፡ ተረጐመ (ካንዱ ቋንቋ ወደ ሌላው ከቀኝ ወደ ግራ መለሰ ከፈተ ገለጠ የጥፈት የብራና የመዝጊያ)
ገለበጠ፡ የላዩን በውስጥ የውስጡን በላይ አደረገ/አፈረሰ/ቀየረ/ለወጠ/አዛወረ (ኢዮ. ፲፪፡ ፲፭፡ ማቴ. ፳፩፡ ፲፪)
ገለበጠ፡ ጣለ/አወደቀ/አጋደመ/ገደለ "ወታደሩ ዝንጀሮውን በጥይት ገለበጠው።" "ገለበጠ 'ገለጠ' የወጣ ስርዋጽ ግስ ነው።"
ገለበጠ፡ ፈነቀለ/አስገለለ (ዘፍ. ፳፱፡ )
ገለበጥ፡ ገልባጣ (ገላላ ሰፌድ ሳሕን ዝርግ ወጭት)
ገለባ (ቦች) ያገዳ/የብር ድቃቂ ንፋሽ እንግውላይ ዐሠር ከልብ እብቅ ቀላል ነገር ኹሉ (ኢዮ. ፵፩፡ ፲፱፳፡ ማቴ. ፫፡ ፲፪) (ተመልከት፡ ከልብን)
ገለባ ቤት፡ (የገለባ ቤት) በውስጡ የገለባና የድርቆሽ ቍልል ያለበት ዐጥራም ቦታ
ገለባም፡ ከፍሬው ገለባው የሚበዛ
ገለባበጠ፡ ቀያየረ/ለዋወጠ/ኣነኳኰረ/ኣፈራረሰ (ዘፍ. ፲፱፡ ፳፭፡ ፩ነገ. ፲፰፡ ፲፯፲፰)
ገለባት፡ በበለው አገር ውስጥ ያለ
ገለባት፡ ዠማ ነጋዴ ቅፍለት (የነጋዴ ማኅበር)
ገለባት፡ የከተማ ስም (በበጌምድር ክፍል ያለ ከተማ)
ገለብ፡ ከገደል ከተራራ ተገምሶ ተገልብጦ የወረደ ቋጥኝ ገዎቻ "በትግሬ ግን ጋሻ ማለት ነው '' አይጠብቅም" (፪ዜና. ፳፫፡ )
ገለቦች፡ ቋጥኞች
ገለተመ (ለተመ) ቸኰለ/ጠደፈ (ገጯ ገለበጠ አምታታ)
ገለወደ፡ ሥራ ፈታ/ተንቀዋለለ (ተመልከት፡ ገለደወን)
ገለደ (ትግ.) ጠረበ/ሸለተ "በግእዝ ግን ደጐሰ አለበሰ ሸፈነ ማለት ነው።"
ገለደወ (ገለወደ) አወደቀ/አጋደመ/አስተኛ
ገለዶ፡ የበግ ጠጕር መሸለቻ እንደ መቃድ ያለ ጐባጣ ቢላዋ ካራ
ገለጀጅ/ገልጃጃ (ጆች) ሰለጀጅ/ሰልጃጃ ቀውላላ
ገለገለ (ገልገለ) በደረቅ/በበጋ ወይም በበልግ ጊዜ መዠመሪያ ገመሰ ዐረሰ
ገለገለ፡ ለመነ/ጋበዘ/አባበለ
ገለገለ፡ ሎሌ ቀጠረ/አሽከር አሳደረ
ገለገለ፡ ነቀለ/ነቅሎ ወሰደ (የችግኝ)
ገለገለ፡ ወለደ/ፈለፈለ (የግልገል/)
ገለገፍታ (ገል ገፍታ) ገልፋጣ (ሣቂታ ጋለሞታ ሥራ ፈት)
ገለገፍቶች፡ ገልፋጦች/ጋለሞቶች
ገለጠ (ገሊጽ/ገለጸ) ገፈፈ/ገለበ/ከፈተ/አራቈተ/ኣሳየ ነገረ/ተረጐመ/አስረዳ/ከሠተ/አበራ/አጠራ/አወጣ/ለቀቀ (የደረት/የአፍ/የመጣፍ/የአይን/የሰማይ/የምስጢር/የመንገድ) (፪ነገ. ፮፡ ፲፯፡ ዮሐ. ፳፩፡ )
ገለጣ፡ ከፈታ/ገፈፋ
ገለጸ፡ ገለጠ/ከሠተ
ገለፈ (ገሊፍ/ገለፈ) ተቈጣ/ወፈፈ/አመረረ
ገለፈት (ግልፋፊ) የሽንኵርት ልላጭ ወይም ገለባ
ገለፈት፡ የባቄላ በቈልትና ኣሹቅ ጥሪ
ገለፈት፡ ያሣ የእባብ ቅርፊት "በግእዝ 'ቅሣር' ይባላል።"
ገለፈንት
ገለፈንት፡ ርባና ቢስ ወንድ ወይም ሴት (በኾነ ባልኾነው የሚሥቅ የምትሥቅ)
ገለፈጠ፡ ዝንጀርኛ ሣቀ (ከንፈሩን ገለጠ ገለፈፈ)
ገለፈጥ/ገልፋጣ (ጦች) ዝኒ ከማሁ (ጥርሱን የማይከድን)
ገለፈፈ፡ ላጠ/ላፈ/ገፈፈ/ፋቀ (የሽንኵርት የእባብ የብራና)
ገለፈፈ፡ ሣቀ (ድዱን አሰጣ)
ገለፈፍ/ገልፋፋ፡ የተላጠ (የሣቀ)
ገሊላ፡ በይፋትና በጠራ ክፍል ያለ ቀበሌ
ገሊላ፡ ያገር ስም (በፍልስጥኤም ውስጥ የሚገኝ አገር ትርጓሜው ዙሪያ ማለት ነው) (. . .)
ገላ (ዎች) ገልዓዊ የገል ተፈጥሮው እንደ ገል ከመሬት የኾነ ከራስ እስከ እግር ያለ ቁመት ቁመና አካል ኹለንተና ሰውነት
ገላ ሳሙና፡ የአካል መታጠቢያ ባለሽቱ የገላ ሳሙና
ገላ ነክ፡ ኀበር (የቀሚስ ውስጥ)
ገላለጠ፡ ገላለበ/ከፋፈተ/አብራራ
ገላላ፡ ዝርግ/ሰታታ/ሰፌድ ዐይነት
ገላልት፡ ገሎች ስባሪዎች
ገላመጠ፡ በክፉ ዐይን ከፍና ዝቅ አድርጎ አየ/ተኰረ/ገሠጸ/ተቈጣ/ገረመመ
ገላማ፡ አካል ወፍራም ደንዳና
ገላማጭ (ጮች) የገላመጠ/የሚገላምጥ (ተኳር ቍጡ ገርማሚ)
ገላበጠ፡ ወላወለ/ዘላበደ/አነኰረ
ገላቢ፡ የገለበ/የሚገልብ/የሚገልጥ/የሚያጠምድ/የሚያሳርር/የሚያቀል (ገላጭ/አጥማጅ/አሳራሪ/አቅላይ)
ገላቢጦሽ፡ ዝኒ ከማሁ "ወንዱን 'አንቺ' ሴቱን 'አንተ' ማለት።"
ገላባጭ (ጮች) ወላዋይ/ወረተኛ (ምሳ. ፲፫፡ )
ገላባጭነት፡ ወላዋይነት/ዘላባጅነት
ገላን፡ የኦሮ ነገድና አገር (ትርጓሜው ጐርፍ ማለት ነው ብዛትን ያሳያል) "አብቹና ገላን" እንዲሉ።
ገላው ነውር አወጣ፡ ዐበጠ ቈሰለ
ገላውን ሰደደ፡ ዐረፈ ተዘለለ ፍር አልባ ተቀመጠ
ገላገለ፡ ከለከለ/አስጣለ/አስተወ/አስለቀቀ/አስታረቀ/አሰማማ
ገላገለ፡ ዘረገፈ/ባዶ አደረገ/ለየ/ነጠለ/አሶለደ
ገላጋይ (ዮች) የገላገለ/የሚገላግል (አስጣይ አስታራቂ አዋላጅ ዳኛ ዘመድ ሽማግሌ ጨዋ ሐኪም) "ተው በገላጋይ" እንዲሉ ልጆች
ገላጋይነት፡ አስታራቂነት/ሽምግልና
ገላግል/ገላግሌ፡ የሰው ስም
ገላግልት (ቶች) ታናናሽ ዶሮች ከጫጩት በላይ ከዘረንቦ በታች ያሉ። "ገላግልት ለጥቂትና ለብዙ ይኾናል 'ገላግልቶች' ግን የብዙ ብዙ ናቸው። ትግሪኛ ውርንጭላ (ሎች) ሲል 'ገልገል ገላግል' ይላልና 'ገላግልት' 'ገልገል' ብዥ ነው።"
ገላጣ፡ ሣር ቅጠል የሌለበት ባዶ ስፍራ መላጣ
ገላጣዋ፡ ገላጣዪቱ (የተገለጠች አንዳች አልባ) (ኢሳ. ፵፩፡ ፲፰)
ገላጭ (ጮች) የገለጠ/የሚገልጥ (ከፋች) "መጣፍ ገላጭ" እንዲሉ።
ገል (ሎች) (ገልዕ) የንስራ/የማድጋ/የጋን/የምጣድ የማንኛውም ሸክላ ስባሪ
ገልማጣ፡ የተገላመጠ
ገልማጭ፡ ıለመጠ/የሚገለምጥ (የሚያሞቅ የሚያተኵስ)
ገልማጭ፡ ገላማጭ (ካህንኛ)
ገልባጭ (ጮች) የገለበጠ/የሚገለብጥ (ቀጂ/አጋቢ/ደፊ/አፍሳሽ/ለዋጭ/ቸርቻሪ/አንሸራታች/ብራና መላሽ/ተማሪ)
ገልባጭነት፡ ለዋጭነት/ቸርቻሪነት
ገልብጥ፡ ዝኒ ከማሁ ለገልባጭ "ዳግመኛም ለቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ይኾናል። ኮርቻ ገልብጥ" እንዲሉ። (ተመልከት፡ ገመረ ብለኸ ገመርን)
ገልተምተም አለ፡ ቸኩሎ ሠራ/ተምታታ
ገልቱ (ዎች) (ኦሮ) ቢስ/ያልሠለጠነ (ሥራ የማያውቅ)
ገልቱ ሴት፡ (ተመልከት፡ ጋፈ)
ገልታማ፡ ችኵል/ጥዱፍ
ገልዋዳ፡ ሥራ ፈት ምናውዬ ቀውላላ
ገልጋይ (ዮች) የገለገለ/የሚገለግል (ገማሽ ዐራሽ)
ገልፋጭ፡ የገለፈጠ/የሚገለፍጥ (ሣቂታ ዝንጀሮ ዐይነት)
ገልፋፊ፡ የገለፈፈ/የሚገለፍፍ (የሚልጥ የሚገፍ የሚሥቅ ፋቂ ገፋፊ ሣቂ)
ገመ
ገመለ፡ ለበለበ (ግመልና ለምጽ አስመሰለ የእግር የቂጣ)
ገመመ (ከመመ) የሸክላ ዕቃን ዐንገት ሰበረ/ጐረደ
ገመመ፡ ቈረጠ/ላጣ/ከረከመ "ጋማ ጋሜ ከዚህ የወጣ ነው።"
ገመሞ ራስ፡ ራሰ ትልቅ/ራሰ ሰፊ
ገመሞ፡ ዐንገቱ የተሰበረ እንስራ
ገመሰ (ገሚስ/ገመሰ) ተለመ/አቦየ ዐረሰ (ቈረሰ ከፈለ ፈነከተ ኹለት አደረገ የመሬት የዳቦ የራስ የንጀራ)
ገመሰ፡ ጐመተ
ገመሳ/ግምሻ፡ ተለማ/ቈረሳ/ፍንከታ
ገመረ፡ አስቋፈ/በቀስታ ኣስኬደ
ገመሬ፡ ዝኒ ከማሁ (የገመር ወገን ዐይነት)
ገመር (ሮች) ትልቅ አውራ ዝንጀሮ (የጅር መሪ አሳዳሪ) "ታላቅ ሰው ዋና ጐምቱ ሽማግሌ ያገር ቀንድ ዐዛውንት ሊቅ መምር።" "መምሩ ገመሩ እንዲሉ።"
ገመር ገልብጥ፡ የሣህለ ሥላሴ ስም "ገመሩን ገልብጦ በላይ የኾነ ማለት ነው።" (ተመልከት፡ ገበረ ብለኸ ገበርን እይ)
ገመተ (ገሚት/ገመተ) አሰላ/ገመገመ (ዋጋ ቈረጠ "ይህ ይህን ያኸል ያወጣል አለ" ሸለገ) "ገመሰና ገመተ አንድ ዘር ናቸው።"
ገመታ፡ ርቦ ሢሶ (ተጋዥ ለባለመሬት የሚከፍለው የርሻ ክራይ)
ገመነ (ገምኖ/ገመነ/ተገመነ) ነደደ/ተቃጠለ/ዐረረ/ተከነ/በገነ/ጠቈረ/ከሰለ (ዐዘነ)
ገመነ፡ ተነወረ/ረከሰ
ገመና ከታች፡ (ከባቴ ነውር) ቤት (ባለተረከዝ መጫሚያ የእግርን ነውር የሚከት ያየውን የሰማውን የሚደብቅ ወዳጅ አዝማሪ ጣዲቄ ቤታቸው በተቃጠለ ጊዜ የገጠሙት ግጥም) "ቤቴ ቤቴ ገመና ከታቼ ገመና መክተቱ ምንድነው ትርጒሙ ወደ ጓዳ ገብቶ ዱቄትስ ሲቅሙ።"
ገመና፡ ነውር (የማያምር አግር የተረከሰ ፈለግ ንቅ ሥንጥቅ)
ገመናው ተገለጠ፡ ነውሩ ታየ ታወቀ (ሚስት ልጅ ሞቱበት)
ገመደ፡ ቈረጠ (ግእዝ) (ተመልከት፡ ጐመደን እይ)
ገመደ፡ ፈተለ/አከረረ/ጠሞረ/ሸረበ/ጠመዘዘ/ደበለ
ገመደለ (ገመደ/ገመጸ) አብዝቶ ቈረሰ/ገመሰ ዳቦን
ገመደለ፡ ፍርድን አጐደለ/ቀመጠለ/አጠመመ/አደላ " ከበደለ መጥቶ በገመደ ላይ ተደርቧል።"
ገመደደ፡ ተቋጠረ/ተኰመተረ/ተኰሰተረ/ተጨመደደ/ተጨመተረ (የፊት)
ገመድ፡ ቅጣት/እስራት/ስቅላት (አስቴ. ፯፡ ) "ግባ በገመዴ" እንዲል ተከሳሽ
ገመድ፡ ከጓሳና ከስንደዶ ከናጫና ከቃጫ ከእንሰት ከሳማ ልጥ ከፈትል ከሐር ከተልባ እግር ከሽቦ የተጠሞረ ማሰሪያ መማገሪያ የሚኾን ቀላድ ደበል ወደሮ (መታጠቂያ ጥብጣብ)
ገመዶች፡ ቀላዶች/አውታሮች (ዘፀ. ፴፭፡ ፲፰)
ገመገመ (ዐይኖ/ዐየነ) ገመተ/ሸለመ/አሰላ (ዋጋ ቈረጠ) (ዘሌ. ፮፡ )
ገመገመ የገገመ ደጊም ነው
ገመገመ፡ ተመመ/ጮኸ (ተመልከት፡ ጎመጎመን)
ገመገመ፡ አያያዘ/አረዘመ/ከፍ አደረገ/አቆመ
ገመገም (ሞች) እንደ ሰንሰለት የተያያዘ ተራራ (የብዙዎች አገሮች መካከለኛ ወሰን ጣርማበርን የመሰለ ፈረንጆች ሼን ደሞንታኝ ይሉታል)
ገመጠ (ገምጾ/ገመጸ) ነከሰ (በጥርሱ ቈረሰ ሰበረ ሸረፈ በላ)
ገመጠጠ፡ በክፉ ዐይን አየ/ነቀፈ/አጥላላ/አንጓጠጠ/አሽማጠጠ "ጕይዲ ግን 'ቀነፈ ቀለበሰ' ብሎታል።" (ተመልከት፡ ገረጠጠን እይ) "ገመጠጠ የገመጠና የገጠጠ ዲቃላ ነው።"
ገሙ፡ ያገር ስም (በኦሮ ቤት በወላሞና በጎፋ መካከል ያለ አገር)
ገሚ፡ የሚገማ/የሚጠነባ

ገሚስ፡ ግማሽ (ያንድ ወይም የብዙ ነገር)

ገሚሶች፡ ግማሾች/እኩሌቶች

ገማ (ገሚእ/ገምአ) በከተ/በሰበሰ ክፋኛ ሸተተ/ጠነባ/ከረፋ/ቀረና/ተበላሸ (አፍንጫው ኣፉ ብብቱ ሥጋው ሬሳው ዕንቍላሉ ማንኛውም ነገር)

ገማመሰ፡ ተላለመ/ዐራረሰ/ቈራረሰ/ከፋፈለ/ፈነካከተ

ገማሳ፡ የተፈነከተ ፍንክት "ራሰ ገማሳ" እንዲሉ።

ገማሽ (ሾች) የገመሰ/የሚገምስ (ወራሽ ቈራሽ)

ገማች (ቾች) የገመተ/የሚገምት (የሚያሰላ አስሊ ገምጋሚ)

ገማይ፡ የገመለ/የሚገምል (ለብላቢ)

ገማጅ (ጆች) የገመደ/የሚገምድ (ሸራቢ ጠምዛዥ)

ገማጣ፡ የተገመጠ (ሸራፋ ገመሞ)

ገማጭ (ጮች) የገመጠ/የሚገምጥ (የሚነክስ ነካሽ ሸራፊ)

ገምል፡ የፊደል ስም "፫ኛ ፊደል '1' ግመል ማለት ነው።"

ገምባሌ፡ በቁሙ፡(ተመልከት፡ ገነበለ)

ገምቤላ፡ ያገር ስም (በዳር አገር ያለ የኢሉባቦር ጠረፍ ገምቤሎ ከማለት ጋራይሰማማል ዛሬ ግን እንደ ፈረንጅ ጋምቤላ ይሉታል)

ገምቤሎ፡ የዛፍ ስም (በኃላ ቤት የሚገኝ ለሳንቃ የሚኾን ዕንጨት)

ገምብ (ትግ. ገምቢ ጥንብ) ያሞራ ስም (ጥንበ በላ አሞራ) (ዘዳ. ፲፬፡ ፲፰)

ገምና (ሐረር. ግሙና) ነውረኛ (በምንዝር የረከሰ የረከሰች ዘማ)

ገምናኔ (ግሙናዊ) የገምና ወገን (ያመንዝራ ኵሩ ትቢተኛ ተጐማሪ)

ገምዳላ/ግምድል፡ የተገመደለ/የተቈረሰ (ቅምጥል)

ገምዳይ (ገማዲ/ገማጺ) የገመደለ/የሚገመድል (ቈራሽ ገማሽ)

ገምዳዳ፡ ቋጣራ/ኰምታራ/ጨምታራ "ፊተ ገምዳዳ" እንዲሉ።

ገምድል፡ አድላዊ/አጥማሚ "ፍርደ ገምድል" እንዲሉ።

ገምጋሚ፡ የገመገመ/የሚገመግም (ገማች አስሊ)

ገምጣጣ፡ የተገመጠጠ (ንቁፍ)

ገምጣጭ፡ የገመጠጠ/የሚገመጥጥ (ነቃፊ አንጓጣጭ)

ገምጦ ወጥ፡ መረን ዕገውጡ

ገምጦ ወጥ፡ የሚያወጣ ወይም ግማጩን ከወጥ የሚያገባ ባለጌ

ገምጦ፡ ነክሶ/ቈርሶ/ሸርፎ

ገሞራ፡ በውሃ የማይጠፋ እሳት (ከምድር የሚፈልቅ ገሞራን እሳት ማለት ኀዳሪ በማኅደር ነው) (ተመልከት፡ ፈንታሌን)

ገሞራ፡ ብርቱ/ኀይለኛ/ጐበዝ (አደጋና መከራ ቻይ "ገሞራው ወልዴ" እንዲሉ)

ገሞራ፡ ያገር ስም (ከሰዶም ጋራ እሳትና ድኝ የዘነበበት አገር)

ገሞራዊት፡ በገሞራ የተወለደች አውሬ

ገሰለ (አአርወየ) ግስላ አደረገ (ጠባይ በግብር)

ገሰሰ ደበሰ

ገሰሰ (ዐረ. ጀለስ) ተቀመጠ ቍጭ አለ

ገሰሰ (ገሲስ ገሰሰ) አጠፋ/ወረ ቈሸ/ዳበሰ/ዳሰሰ/ደመሰሰ ክብርናን

ገሰሰ፡ ላጠ/ለወጠ/ገለበጠ/ሻረ (ፍርድን)

ገሰሰ፡ ቀተለ/ቀደስ/ባረከ/ወደሰ ያለ የሩቁን ወንድ አንቀጽ አረባ/አበዛ (ከመጽሐፍ ቃል ጠቅሶ ወረበ/ተቀኘ (ገቢር)) "የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም ይገስ ይገሳል በል እንጂ ይገስስ ይገስሳል አያሠኝም።"

ገሰሰ፡ አዋረደ/ዝቅተኛ አደረገ

ገሰሰ፡ ደበሰ/ለቀቀ (የወርቅ የቀለም)

ገሰስ፡ ብርድ የመታው ያጠፋው ገብስና የስንዴ ፍሬ (ወይም ገለባ) "ዐሠሥ ገሰስ" እንዲሉ

ገሰረ (ቀተረ) አብዝቶ ጠጣ/ለገሸ (የበሬ የሰው)

ገሰበ (ትግ. ገሰመ) ጠጣ (ግጥም ሽምጥጥ ዥው አደረገ ጨለጠ) (ተመልከት፡ ገተመን እይ)

ገሠገሠ (ገሥገሠ/ጌሠ) ማለደ (በማለዳ ጨለማ ሳለ ኼደ አረበደ ቸኰለ ተጣደፈ ፈጠነ)

ገሰገሰ፡ ማልዶ ኼደ፡ ገሠገሠ

ገሠገሠ፡ ቶሎ ቶሎ አደገ (የጠጕር)

ገሠገሡ፡ የሴት ስም "ሰዎች ወደ ርሷ ማለዱ ማለት ነው።"

ገሠጠ (ገሠጸ) ሳለ/ዐነጠሰ (የበሬ) "ወይፈኑ ዐልቅት ስለ ያዘው ይገሥጣል "

ገሠጠ፡ የሕዝብ

ገሠጠ፡ ገሠጸ/ቀጣ

ገሠጸ (ገሥጾ) ተቈጣ/ዘለፈ/ሠራ/ቀጣ/መከረ

ገሠጸ፡ የካህናት አነጋገር ነው

ገሳ ሣር ገሣ

ገሣ (ገሠገሠ) እንደ ሰይፍ ስለት ያለው (ስፋቱ ጋት የሚያኽል ሣር በረግረግ ውስጥ የሚበቅል እንደ ግንብ መመለሻ ዐጣፋ ቀናፋ)

ገሣ (ጐሥዐ) አዠ/አፈሰሰ/አወረደ/ተፋ "ልቡ አፉ ቍስሉ ደም ይገሣል።"

ገሣ፡ ከጐሣና ከቀጤማ የተሠራ የዝናም ልብስ (እረኛ በዝናም ጊዜ የሚደርበው) "ዘሩ ገሠገሠ ነው።"

ገሣሠጸ፡ ተቈጣጣ/መካከረ

ገሳሪ፡ የገሰረ/የሚገስር (ጠጪ)

ገሳሽ (ሾች) የገሰሰ/የሚገስ (አጥፊ ደምላሽ ለዋጭ ገልባጭ ሻሪ አርቢ ጕልማሳ ዳኛ የቅኔ መምር)

ገሳሽ፡ ደባሽ/ለቃቂ

ገሣጭ፡ ሣጺ

ገሣጭ፡ የገሠጠ/የሚስል/የሚያነጥስ

ገሣጺ፡ የገሠጸ/የሚገሥጽ (ገሣጭ ተቈጪ) (ኢሳ. ፳፱፡ ፳፩፡ ሮሜ. ፪፡ )

ገሥጋሽ (ሾች) ለሣልስት የሚገሥግሥ (ማላጅ በጧት ኻያጅ) (፩ነገ. ፲፬፡ ፳፯, ፳፰)

ገሥጋሽነት፡ ፈጣንነት/አዳጊነት

ገሥጥ (ገሥጽ) የራስ አበበ "አረጋይ የፈረስ ስም ቅጣ ማለት ነው" (ተመልከት፡ አባን እይ)

ገሦ፡ እጀታው (ዕርፉ) አፍሬው (ጫፉ) ጣምራ የኾነ የጕራጌ መደደቂያ

ገረ()ገሬ/ገራ()ገሬ፡ ግራ

ገረመ (ገሪም ገረመ) ደነቀ/ተፈራ/ተለየ ("ይገርማል!" "ይደንቃል!" (መዝ. ፷፡ , ))

ገረመ (ገርሀ) ገር ኾነ/ለሰለሰ (ቍጡነትን ተወ ጨመተ "ይህ ቅጽላዊ ግስ ይባላል።" (ተመልከት፡ ለበመን))

ገረመመ (ገረመ) ገላመጠ (ከንፈ ሩን ነክሶ በክፉ ዐይን ከላይ እታች አየ አስፈራራ ዐይኑን አፈጠጠ) (ተመልከት፡ ገረፈን እይ)

ገረማ፡ የዱር ሲናር "የስሙ ምስጢር ልዩ ማለት ነው።"

ገረሰሙ፡ ገጨ/ለተመ/ወለከፈ

ገረሠሠ ሰበረ ገረሰሰ

ገረሰሰ (ዕብ. ጋራስ ለየ) ዛፍን ነቀለ/አነገለ/አፈለሰ/ጣለ/እወደቀ/አጋደመ "ገረሠሠ ተብሎ ሲጻፍም ይቻላል።" (ተመልከት፡ ገነደሰን እይ)

ገረረ (ገሪር ገረረ) ጠረረ/ጋለ (በጣም ሞቀ ተኰሰ ተፋጀ የፀሓይ) "ሠማ ጠበረረ ለእሳት ተገዛ የምጣድ።"

ገረረ፡ ተሳበ/ተጐተተ/ታለበ

ገረረ፡ ተጮኸ (ተመልከት፡ ቀረረን እይ)

ገረራ፡ ሙቀት/ጩኸት

ገረሸ (ገረሠ ዕብ. ጋራሽ ሚስት ፈታ) ተመለሰ/ታደሰ (የበሽታ)

ገረበብ፡ ገርባባ (ግጥም ልጥቅ ልክክ ያላለ ማንኛውም መክደኛ ያልተጠጋ ያልቀረበ የተለየ ሰው ገረበበ)

ገረበደ፡ በጣም ከፈተ/ወለለ/በረገደ "ገረበደና በረገደ አንድ ዘር ናቸው።"

ገረበድ/ገርባዳ፡ የተከፈተ (ክፍት ውልል ብርግድ)

ገረነ (ቀረነ) ወጋ/አተኰሰ/አቃጠለ/አሳመመ (ፀሓይና ንዳድ ሰውን)

ገረን፡ በመራቤቴ ክፍል ያለ አገር

ገረንገሬ የንጨት ስም ገራ

ገረኘ (ረጊን/ረገነ) ቈረኘ (አግር ተወርች አሰረ ወይም የኋላ እግርን ከፊት እግር ገጥሞ ባንድነት ጠፈረ/ኰደኰደ ለመተኰስ ለመብጣት ለማረድ)

ገረዘ (ገዘረ) የወሸላን የሽፍንን ጫፍ በክር አስሮ ቀነጠበ/ቈረጠ

ገረዘዘ (ገረሰሰ) አሸለበ/ተነ አንቀላፋ/አሸነፈ/አዘመመ ሰውን (ነፋስ ዛፍን እንደሚገረስስ "እከሌን እንቅልፍ ገረዘ ዘው" እንዲሉ)

ገረዘዘ፡ ገረዶዶ/ከረዶዶ (ጠና ጠነ ከረ ሥጋው "ደና ባማርኛ ይወራረሳሉ! ደፈቀ ዘፈቀ።") (ተመልከት፡ ገነተረን እይ)

ገረደ፡ ኣጦለ/ለየ ግርድን

ገረደ፡ ገረድ ቀጠረ/አሳደረ

ገረደመ፡ ገመጠ/ሰበረ/አነከተ/አደ ቀቀ/በላ (የጋማ ከብት ዕንጨትን) "ዛሬ ሌሊት አጋሰሶቹ ግድግዳውን ሲገረድሙ ዐደሩ።"

ገረደደ (ከረደደ) ደረቀ/ጠነከረ (አልታኘክ አለ)

ገረደደ፡ አጠረሰ/ቸረቸመ/ኣበላሸ ጥርስን (ሥጋው ስንደዶው አክርማው)

ገረደፈ (ገረደ/ገደፈ) አጐረሠ መዠመሪያ ፈጩ ከረተፈ (ተመልከት፡ ከረተን ሸረከተን እይ)

ገረድ (ዶች) (አመት) ሚስት ያይ ዶለች (በምንዳ የተቀጠረች ሴት አሽከር ሎሌ ወይም ሴት ባሪያ ደንገጥር) (ዘዳ. ፳፩፡ ፯፡ ምሳ. ፳፯፡ ፳፯፡ ኢሳ. ፲፬፡ ) "በጕራጌ ግን ሴት ልጅ ማለት ነው።"

ገረድነት፡ ግርድና (ገረድ መኾን ቅጥርነት) (ዘፀ. ፳፩፡ )

ገረጀፈ (ገረገፈ) ወፈረ/ከበደ ()

ገረገመ (ረገመ/ገረመ) ጥርስን ጨርሶ ሸረፈ/ሰበረ "ገረገመ ብሎ ሰበረ ማለት ዕብራይስጥ ጋራም ካለው የመጣ ነው።"

ገረገመ፡ ግርግም ሠራ/አበጀ

ገረገረ (ገርገረ) ቀረቀረ/ገደገደ/ደረደረ/ተከለ ዕንጨትን ኵበትን

ገረገረ፡ ሻከረ/ደነበረ

ገረገረ፡ ከለከለ/አገረ/አወከ/አገደ/አቆመ ሰውን (ኢዮ. ፴፱፡ ፳፬)

ገረገራ (ዎች) የቤተ ክሲያን ዐጥር ቅጥር (ከደረቅ ዕንጨት የተበጀ)

ገረገራ፡ ዐጠድ (እንዳጥር ኹኖ የተተከለው የተሰደረው የተደረደረው ማንኛውም ዛፍ)

ገረገንብ፡ ግድንግድ

ገረጣ (ጻዕደወ) ነጣ/ነጭ ኾነ (የእኸል የሰው ከፀሓይ ከበሽታ የተነሣ)

ገረጨ (ገረጣ) ግራጭ መሰለ ወይም ጥቍረቱና ንጣቱ መሣ ኾነ (የበቅሎ)

ገረፈ (ገሪፍ ገረፈ) በጅራፍ ባለንጋ በጠፍር ባርጩሜ በመንገር ተገተገ/መታ/ቈነደደ/ገጋ ለመጠጠ/ቈጋ ለቈጠጠ/ሸመተረ/ሾጥ አደረገ/ሸነቈጠ/ቀጣ/ጠበጠበ ሰውን ከብትን (ዘፀ. ፭፡ ፲፬፡ ፩ነገ. ፲፪፡ ፲፩, ፲፬፡ ፪ዜና. ፲፡ ፲፩, ፲፬፡ ማቴ. ፳፯፡ ፳፮)

ገረፈ፡ በመቃ ሥንጣቂ በቢላዋ ንደስ ባንኮላ አፍ አሰነበረ/ሸለመ/አስጌጠ/ዐተመ/ሠረጐደ/ጐበጐበ ድፎን

ገረፈ፡ በቀላል ተኰሰ/ፈጀ

ገረፈ፡ ኣቀና ወይፈንን/ኣሠለጠነ ጅን አሽከርን

ገረፈ፡ ገላመጠ "ድኻውን የሀብታሙ ፊት ገረፈው።"

ገረፋ፡ ግርፊያ/ጥብጠባ/ሽንቈጣ

ገረፍታ፡ የፀሓይ የጨረቃ ምታት

ገሪ (ዎች) (ረያፂ) የገራ/የሚገራ (አስተማሪ አስለማጅ አሠልጣኝ) (ተመልከት፡ ወንድን እይ)

ገሪ፡ የሚገጭር/አስቋፊ

ገሪማ፡ የኢትዮጵያ ጻድቅ ስም (ከተስ ዐቱ ቅዱሳን ኣንዱ የፈረንጅ አገር ሰው ጧት ዘርቶ በሠርክ ስላልደና ዛፎችም ሉን ሰምተው ስለ ተወገዱ ሌላም ብዙ ተኣምር በመሥራቱ ገሪማ ተባለ ድንቁ እንደ ማለት ጥንታዊ ስሙ ይሥሐቅ ነው)

ገሪፍ

ገራ (ረየፀ/አግርሀ) ለፈረስ ለበቅሎ ለግመል ለስናር አህያ ለዝኆን መቀመጫነትን ግልቢያን ሥግሪያን አረማመድን አስተማረ/አስለመደ ወይም እነሱን ፈተነ/ሠራ/ቀጣ/አሠለጠነ/አሮ ኣስኬደ (ገቢር)

ገራ (ገሪህ/ገርሀ) ለዘበ/ላላ/ገር ኾነ (ጥናት ዐጣ ተገብሮ) "መጽሐፍ ግን በጎራ ፈንታ ተገራ ይላል ስሕተት ነው" (፪ሳሙ. ፲፰፡ )

ገራ (ገሪዕ/ገርዐ) (ዕብ. ጋራዕ) ከፈለ/ከፍሎ ሰጠ (አጐደለ አሳነሰ) (ተመልከት፡ ግራን እይ የዚህ ዘር ነው) "ገርዐ ጥንታዊ ዐማርኛ መኾኑን አስተውል ልብ አድርግ።"

ገራሚ፡ የሚገርም/የሚደንቅ

ገራም (ገርሃዊ/ልቡብ) ደግ ሰው (ምሳ. ፳፭፡ ፲፭) "ደንሴ አውሬ ያይዶለ ዐመለ ልስልስ ከብት የገር ባለገር ገራዊ ማለት ነው መዠመሪያውን ገራ እይ።"

ገራም ፋሲል፡ ያፄ ሱስንዮስ አባት (ደግ የዋህ ማለት ነው)

ገራሪ፡ የሚገር (ምጣድ)

ገራራ፡ የገረረ (ጠራራ)

ገራዥ (ዦች) የገረዘ/የሚገርዝ (ቈራጭ "እከሌና እከሌ ተጣሉና ለያዥ ለገራዥ አስቸገሩ።")

ገራዳ (ገራዳዊ) ገራድ የተከለው የሐረርጌ ባላባት (እንደ መልከኛ የሚታሰብ ባለምድር በርስቱ ውስጥ ብዙ ገባር ያለው ለመንግሥት የሚገብርና የሚያስገብር የርሱም ተጠሪ ዋሱ ደሚና ይባላል)

ገራድ፡ የሐረርጌ አውራጃ የቀድሞ የማዕርግ ስም "ዐረብ ጀረደ ብሎ ሰይፍ መዘዘ ይላልና ምስጢሩ ሰይፈኛ አዝማች ማለት ይመስላል ግራኝን መሐመድ ገራድ ይሉታልና።"

ገራገሬ፡ የገራገር ወገን (ጥንካሬ የሌለው ዕንጨት ሙጫው ማረ ግላ እደርጝር የዶሮ ማር የሚባል) "ግራ ግእዝ ነው።"

ገራገር፡ የገር ገር (የየዋህ የዋህ)

ገራፊ (ፎች) የገረፈ/የሚገርፍ ( ሌባ ያባያ ቀጪ) (ኢሳ. ፶፡ )

ገሬ (ገርሃዊ) ወባ ያለበት ሰው (የወባ ጐራ ሰውነተ ልል)

ገሬንጭ፡ በምድር ላይ ደርቆ የቆመ የበርበሬ ዕንጨት

ገር

ገር (ሮች) (ገርህ) የገራ (የዋህ ደግ ሰው ቂም በቀል ተንኰል ሽንገላ የሌለው የጐመን ዕርሻ) (መዝ. ፳፭፡ ፱፡ ማቴ. ፭፡ ) (ተመልከት፡ መዠመሪያውን ገረመ እይ)

ገር በባላገር የሚኖር ሰው፡ ባለጌ ካህናት ግን ሀገረ ሰብ ይላሉ

ገርማሚ፡ የገረመመ/የሚገረምም (አስ ፈራሪ)

ገርማማ፡ ያገር ስም (ባዲስ አበባ ምሥራቅ በቡልጋ ያለ አገርና ዠማ)

ገርማሜ፡ የገርማሚ ስም ("ደጃች ገርማሜ" እንዲሉ)

ገርሰምሰም አለ፡ ውልክፍክፍ ቅፍቅፍ አለ

ገርሣ፡ የገደል ላይ ሣር (ዘሩ ጐረሠ ነው) (ተመልከት፡ ለሸለሸ ብለኽ ልሻን እይ)

ገርሳማ፡ የገርሳም ወገን (ደንቃፋ)

ገርሳም፡ የሚገጭ (ለታሚ)

ገርሳሽ፡ የገረሰሰ/የሚገረስስ (ነፋስ ውሃ ናዳ)

ገርበብ አደረገ፡ በጥቂቱ ዘጋ

ገርነት፡ የዋህነት/ደግነት (፪ቆሮ. ፲፡ ፩፡ ኤፌ. ፬፡ ፪፡ ያዕ. ፩፡ ፳፩) (ተመልከት፡ እንዶድን ተመልከት)

ገርኚ፡ የገረኘ/የሚገረኝ (አሳሪ ኰድ)

ገርዋ፡ ጠማማ ዐመለ ቢስ ክፉ መጥፎ ሰው (ጠባዩ ከሌላ የማይሰማማ)

ገርዳሚ፡ የገረደመ/የሚገረድም (ሰባሪ )

ገርዳማ፡ ገማጣ/ሰባራ

ገርዳሳ (ኦሮ) ጠጕርን ወደ ላይ ደግፎ በራስ ዙሪያ የታሰረ ሻሽ (ተመልከት፡ ጋሜን ናኑን እይ)

ገርዳዳ፡ የገረደደ/የሚገረድድ (ጠንካራ)

ገርዳፊ፡ የገረደፈ/የሚገረድፍ (ከርታፊ አጕራሽ)

ገርጀሞ (ጐዣም) ሣር

ገርጃፋ፡ ወፍራም/ወዘፍዛፋ (ቶሎ የሚ ያረጅ ሰው)

ገርገመጥ (ግርግመ መጥ) ወደ ግርግም የሚመጣ የባቄላና የሽንብራ የምስር አገዳ እግር ስብርባሪ

ገርገብ፡ መለስ/በረድ

ገርጋሪ፡ የገረገረ/የሚገረግር (ቀርቃሪ ተካይ አዋኪ አጋሪ)

ገርጋራ፡ መሳል/ሻካራ ደንጊያ ሞረዳይ

ገርጋር፡ ደንባሪ/ሁከተኛ/ድንጉጥ ከብት ሰው

ገሮ፡ በተጕለት ውስጥ ያለ አገር

ገሸለጠ (ገለጠ) ላጠ/መለጠ/

ገሸለጠ፡ ገለፈፈ/ ገለፈጠ

ገሸለጥ፡ ገሽላጣ (ጥርሱን የማይከድን ሣቂታ ሴት)

ገሸረ (ዕብ. ጋሻር መሰላል ሠራ) አስቀመጠ/ቍጭ አደረገ/ረፈቀ ሰውን " ነሣ እዚህ ምን ገሽሮኻል" እንዲል ባላገር

ገሸረ፡ ተወ/አቈየ ሥራን ውሃን

ገሸሸ (ገሰሰ) ናቀ/አቀለለ (ፍቅርን አጐደለ)

ገሸሽ አደረገ፡ ችላ አለ/ነቀፈ

ገሽላጭ፡ የገሸለጠ/የሚገሸልጥ (ገፋፊ ገልፋፊ)

ገበ ሰገደ።

ገበሰ፡ ገብስ መሰለ፡ ነጣ፡ ፈገገ።

ገበረ

ገበረ

ገበረ (ገሚር/ገበረ) ላቀ/ትልቅ ኾነ (ከፍ አለ በለጠ)

ገበረ (ገብሮ ገበረ፡ ገቢር ገብረ ጸብሐ) በቁሙ ሠራ፡ አዘመረ፡ ዐረሰ

ገበረ፡ ባሪያ/ዜጋ ኾነ፡ ግብር ሰጠ/ከፈለ፡ አስቀረጠ (፬ነገ. ፭፡ ፲፫)

ገበረ፡ ያደረ/ደረቀ፡ ጕጥ አባ (የገርባ/የእጅ የገባ)

ገበራርት፡ በጐዣም ውስጥ ያለ ቀበሌ

ገበሬ (ገባር/ገባራዊ) ዐራሽ/ቈፋሪ/ባላዝመራ። " ገዢ፡ በሬ ገዢ፡ በሬን የሚገዛ ጠማጅ/አቅኒ/ገራፊ ማለት ነው" (ዘፍ. ፱፡ ፳፡ ያዕ. ፭፡ )

ገበሬ መጣኝ፡ ገበሬን የሚንቅ፡ በቀንበር ቀዳዳ የሚያይ ልግመኛ በሬ አውልግ።

ገበሬ ሸንጎ፡ የገበሬ መሰብሰቢያ/ማሤሪያ/መዶለት/ማደሚያ ስፍራ

ገበሬ አስደንግጥ፡ የእባብ ዐይነት (ገራም እባብ) "አታላይ ሰው ወይም ነገር እስፈሪነቱ እውነት ያይዶለ መስፈራርቾ።"

ገበሬነት፡ ግብርና/ዐራሽነት።

ገበሬዎች/ገበራርት፡ ዐራሾች/ቈፋሪዎች/ለፍቶ አደሮች

ገበር (ገመር) ዋና/ትልቅ/ወፍራም/ደንዳና/ጠንካራ። (ተመልከት፡ ቀመርን)

ገበር (ገበሬ) ዐርሶ በላ። "ጃን ገበር" እንዲሉ።

ገበር (ገበዝ) ውሳጣዊ ልብስ ወይም ገላ ነክ ከሐር ልብስ ጋራ በስተው ስጥ የተሰፋ

ገበር ምጣድ፡ ብዙ ሊጥ የሚያምር (የሚችል) ትልቅና ወፍራም ዳቦ የሚጋግር፡ አንድ ጕርዝኝ/ሀሻሮ የሚነዛ/የሚያነኵር/የሚያበስል

ገበር ዕቃ፡ የገበሬ ዕቃ (ሞፈር/ቀንበር/ዕርፍ/ቅትርት/ድግር/ወገል/ማረሻ/መርገጥ (ጠፍር ልጥ)/ምራን/ማነቆ (ጠፍር ዕንጨት)) የበሬ ዕቃም ይባላል

ገበር እንቧይ፡ ታላቅ እንቧይ ከዘርጭና ከምድር እንቧይ የሚበልጥ የእንቧይ ገመር።

ገበር፡ የኦሮ/ዐማራ፡ ኦሮነቱን ትቶ ዐማራ የኾነ፡ ወይም በኦሮና በአማራ መካከል የተቀመጠ ያማራ ከለላ፡ "ኦሮ መጣላችኹ" የሚል፡ የኦሮን ምስጢር ለአማራ የሚነገር። ትርጓሜው መጻተኛነት ነው።

ገበር፡ የጥራዝ ልብስ ጣፎች - ጥራዙን በርሱ ይዘው አስደግፈው የሚጥፉበት፡ የተጣፈውን የሚያስቀምጡበት

ገበርማ፡ በር ያለው ልብስ

ገበርማ፡ በጐዣም ክፍል ያለ የአርና የነገድ ስም፡ የገበሬ ገበራም የገበር ባለገበር ማለት ነው።

ገበርሾ (ገበር ርሾ) የርሾ መተመጫ ዳቦ ማቡኪያ እንደ ዋዲያት ያለ ኣፈ ለቃቃ ሸክላ ሰፊ ቡሖቃ።

ገበሮች፡ ጋሎች/ያማራ ከለላዎች

ገበታ (ገበታ/ማእድ) የመቃ/የሳንቃ/የስፌት/ሰደቃ፡ የንጨት/የወርቅ መሶብ፡ የንጀራ/የሥጋ ማቅረቢያ።

ገበታ (ገበጣ) የገበጣ ዕንጨት ለጨዋታ ጠጠር የሚመላበት።

ገበታ ረጋጭ፡ ገበታ ሳይነሣ የኼደ ባለጌ/ነውረኛ።

ገበታ ቤት፡ መኻል ሜዳ መታደያ።

ገበታ ዐቃፊ፡ ገበታን ዐቅፎና ከቦ የሚበላ/የሚመገብ ሰው

ገበታ፡ ከግንድ ተጠርቦ የተበጀ ዋልታ። "የባጥ ገበታ" እንዲሉ።

ገበታ፡ የዕንቍ/የእብነ በረድ/የንጨት/የልብ ሰሌዳ/ጽላት (ኤር. ፲፯፡ )

ገበታ፡ ጠፍጣፋና ዝርግ ልዝብ የመጽሐፍ ዳርና ዳር የወንዛ/የኮሶ ሉሕ፡ በሉሑ አምሳል የተበጀ ካርቶን።

ገበታን ከፍ አደረገ፡ አነሣ፡ ለአሽከር አቀረበ

ገበታዋሪያ (ገበታ ሐዋርያ ) የመጽሐፍ ስም (ባንድነት የተጠረዘ ፯ቱ የሐዋርያት መልእክት) "ይህም ሐዋርያት ተሰብስበው ማታ ማታ ባንድ ገበታ የሚመገቡትን ('ሰአልናከ' ጸሎተ ማእድ) ያሳስባል። መጽሐፉን ገበታ ያሠኘው በ፪ ወገን ያለው ሉሕ ነው ብለዋል - - - ክ።"

ገበታዋሪያ፡ በ፲፱፻፳፰ . ደስታ ተክለ ወልድ ያሳተመው ያማርኛ ግስና ርባታ ተረት ምሳሌ ታሪክ

ገበታው ደነገጠ፡ የተጣለው እንጀራ ሣሣ/ኣነሰ።

ገበቴ (ገበታዊ/ዋልታዊ) ከንጨት የተነጠረ/የተቀረጸ ወጭት/ደቅ/ዋዲያት/ዳካ/ሳሕን "መምህራን ግን ገበታ ይሉታል" (ዘኍ. ፯፡ ፴፩, ፴፯, ፶፭, ፷፩, ፲፯, ፸፫፡ ማር. ፲፬፡ ) "ሲበዛ ገበቴዎች ይላል። መጠናቸውም የቍና/የጕርዝኝ ነው፡ ትንሹ ቈሬ ይባላል።"

ገበቶች፡ ሰሌዶች/ጽላቶች (ዘፀ. ፴፩፡ ፲፰፡ ፴፬፡ )

ገበቶች፡ ሰደቃዎች/መሶቦች። (በግእዝ "ገባትው" ይባላሉ)

ገበና፡ ነውር/ገመና።

ገበዘ (ገቢዝ ገበዘ) ግብዝና (ጠባቂነት) ሾመ።

ገበዘ አኩስም፡ የአኵስም ገበዝ ጽዮን ወይም ካህን።

ገበዘ፡ ደለዘ፡ ለሰነ፡ መረገ፡ ለቀለቀ፡ ሰባራውን/መጥፎውን ደኅና አስመሰለ፡ ቀላቀለ፡ ግብዝ አደረገ (መዝ. ፳፭፡ )

ገበዘዘ፡ አረጀ፡ አፈጀ።

ገበዝ (ዞች) የቤተ ክርስቲያን ሹም/ጠባቂ/መንፈሳዊ ዘበኛ/በረኛ፡ አስተንታኝ/የሰሞነኛ አለቃ። "ቄሰ ገበዝ" እንዲሉ። (ተመልከት፡ ውስጠ ብለህ ውስጥን እይ)

ገበዝ ዐምባ፡ የገንቢዎች አለቃ/መሐንድስ። "ገበዝ ሹሙ ዐምባ መንደሩ"

ገበዝ፡ የሐር ቀሚስ ውስጣዊ ክፈፍ በዳር የተሰፋ።

ገበዝነት፡ ግብዝና፡ በቁሙ የቤተ ክርስቲያን ሹመት/ግምጃ ቤትነት። "ከበሽታ ክፉ ቍምጥና ከሹመት ክፉ ግብዝና" እንዲሉ።

ገበየ፡ ኼደ/ገዛ/ለወጠ/ሸመተ/አቀና፡ ወሰደ/እጅ አደረገ

ገበየኹ፡ የሰው ስም (ተመልከት፡ ጐበዘ ብለህ ጐበዝን እይ)

ገበየኹ፡ ያጤ ምኒልክ የጦር አበጋዝ (ፊታውራሪ) በዐድዋ ጦርነት የሞቱ።

ገበያ (ዮች) መግዣ፡ መሸጫ፡ መለወጫ ስፍራ/መደብር/ሱቅ።

ገበያ ቆመ) መሸጥ መለወጥ መግዛት ዠመረ

ገበያ ቆመ፡ መሸጥና መግዛት ተዠመረ። (ተመልከት፡ ደራን)

ገበያ ወጣ፡ ከቤት ወደ ገበያ ኼደ። (ተረት) "ይሉሽን ባወቅሽ ኀበያም ባልወጣሽ።"

ገበያተኛ (ኞች) ገበያ የሚኼድ፡ በገበያ የሚውል/የሚቀመጥ፡ ገዢና ሸያጭ። "ገበያ ነሽ" (የሴት ስም)

ገበያው ተፈታ፡ ተበተነ (በደግ/በክፉ)

ገበያየ፡ ገዛዛ፡ ለዋወጠ፡ ሸማመተ።

ገበይ (ትግ. ሐባ መንገድ) አማካይ፡ የምራን የቀንበር መካከል፡ የጠፍሩን ብዛት ያሳያል።

ገበደ / ገበዘ

ገበደ፡ ወፍራም ኣድርጎ ፈለጠ፣ ሠነጠቀ፣ ከፈለ። (ተመልከት፡ ገበዘ)

ገበገበ፡

ገበገባ፡ ፍለጋ፡ ፍላጎት፡ ምኞት።

ገበገባኒ፡ (ዓመ ከመ ዮም) ዓመታመት ድገመኝ፡ እዛሬ ዓመት አድርሰኝ ማለት፡ እሸትን ቀምሶ አጣጥሞ።

ገበጠ፡ መታ፡ ለየ፡ ከመረ፡ አከማቸ

ገበጠ፡ ዝበጣ ተጫወተ

ገበጠ፡ ግብጣ ኣወጣ

ገበጣ (ገበታ) ግብጻዊ የጠጠር ጨዋታ ጊዜ ማሳለፊያ። ፮፡ ጕድጓድ ያለው የንጨት ሉሕ (ጠፍጣፋ ስሌዳ) የጠሩ ቍጥር ፵፰፡ ሰሌዳውም ጠጠሩም ባንድነት ገበጣ ይባላል። በጨዋታው የተሸነፈውን "ዐይጥበላ" ይሉታል። ጠጠሩም የድንጋይና የእርሳስ ነው። (ተመልከት፡ ጅምን፣ ሥሉስን፣ ውግን)

ገበጣ ገበጥባጣ (ገበጥባጥ ወስፋት ሹጥ) የገበጣ ስም እኩይ። ወስፋትና ሹጥ ሰው የበላውን እንዲበላ የገበጣ ጠጠ ርም ከአንዱ ተጫዋች ወደ ሌላው ይተላለፋል።

ገቢ (ገባኢ) የገባ የተመለስ ተመላሽ መጪ፡ ጥቅም ረብ ለገቢኸ ተንገብገብ ገቢኸን ስታይ ይሉኝ አትበል

ገቢ ኹነኛ ዘመድ፡ በደስታና በመከራ የሚገኝ፡ ጠቃሚ ዃኝ ገቢውን ባለቤት ያውቃል እንዲሉ ቃልን ተመልከት

ገቢር፡ ል፡ ፍቱን መድኀኒት፡ አብነት (ለይኩን)

ገቢር፡ ማድረግ (ግእዝ) "በኀልዮ በነቢብ በገቢር" እንዲል (ናዛዥ ቄስ)

ገቢር፡ የተገብሮ ተቃራኒ ፊደል፡ ይኸውም "" ነው።

ገቢርና ተገብሮ፡ "" ያለበትና የሌለበት ነገር። "አንቀጽም ገቢርና ተገብሮ ይባላል፡ ማድረግና መደረግ ማለት ነው።" (ተመልከት፡ ሰለሰ ለን ሰፈረን ሰለተን)

ገቢና ወጪ (ገባኢ ወወፃኢ) ወደ ሣጥን ገብቶ የሚወጣ፡ ወጥቶ የሚገባ፡ ተመላሽ ገንዘብ፡ በግብር በቀረጥ በንግድ ምክያንት

ገባ (ገቢእ ገብአ) በቁሙ፡ ወደ ውስጥ ጠለቀ ዘለቀ ሰጠመ፡ ተጨመረ ተዶለ ተከተተ (ዘፀ ፲፭ - ፲፱ ኤር ፳፭ )

ገባ (ገቢእ) መግባት

ገባ ሠረጸ "ትምርት ቀንቶታል" ቀና ገደለ አስወጣ አሻረ ኮሶን

ገባ አለ ቶሎ ገባ

ገባ በጥሬና በቦዝ በቅጽል በነገርም ኹሉ መጨረሻ ይነገራል (ማስረጃ) እባሕር ገባ፡ እቢት ገባ፡ እዱር ገባ (እሆድ ገባ) ተዘነጋ ተረሳ ነገሩ (እሰው አፍ ገባ) ስሙ ተነሣ ታማ በሽታ ገባ፡ ግብር ገባ፡ ገደል ገባ፡ ገዳም ገባ፡ ግራ ገባው፡ ደኅና ገባ፡ ወዶ ገባ፡ ውል ገባ፡ ውሎ ገባ፡ ወሸባ ገባ፡ ጥብቅ ገባ፡

ገባ ተመለሰ ተመልሶ መጣ፡ ወደ ኋላ ዞረ ታጠፈ እዪው ወሮ ሲገባ እንዲሉ ሴቶች ታቦት ሲነግሥ ዥብ እሰር ብሎ ተሰሮ ገባ

ገባ ታወቀ ተረዳ፡ ነገሩ ትምርቱ

ገባ ወጠነ ዠመረ

ገባ የወንዝ ስም፡ በኦሮ ቤት ያለ ዥረት

ገባ ጠቀመ ኾነ

ገባ ጨረሰ ፈጸመ

ገባሪ/ገባር (ሮች) የገበረ/የሚገብር፡ የሚያምር፡ የሚያስስ፡ ዜጋ/ተገዥ/ሠራተኛ/ባለርስት (የሸማምት መወጫ ሢሶ/ማጅ)

ገባር/ገበሬ፡ (ግእዝ)

ገባርነት (ግብርናት) ባርነት፡ ተገዥነት፡ ሠራተኛነት

ገባባ መላልሶ ገባ፡ ገባ ገባ፡ ጥልቅ ጥልቅ ዘው ዘው አለ

ገባዥ፡ የገበዘ/የሚገብዝ፡ ገበዝ ሿሚ።

ገባዥ፡ ደላዥ፡ ለሳኝ፡ መራጊ፡ ቀቢ/ቀላቃይ።

ገባጅ (ጆች) የገበደ/የሚገብድ፡ ፈላጭ፡ ሠንጣቂ።

ገባጭ፡ የበጠ/የሚገብጥ፡ ግብጣ

ገብ የገባ የሚገባ እኹል ገብ ድረ ገብ እንዲሉ ኹልንና ድርን እይ

ገብሰ በላ፡ ድምጠ ረዥም ሰው

ገብሳም፡ ገብስ ያለበት/የመላበት ስፍራ/መሬት (ባለገብስ)

ገብስ (ሶች) (ሰገም) በቁሙ እንጀራ/ጠላ/በሶ/ጥረሾ/ቈሎ/ገንፎ/እንቀት የሚኾን ዋና የብር እህል።

ገብስ፡ ቀላል ነገር በቅርብ የሚገኝ። "ይህ ነገር ዕዳው ገብስ ነው" እንዲሉ።

ገብስማ፡ ዐይነቱ/መልኩ/ላባው/ጠጕሩ/ሕብሩ/ቀለሙ ገብስ የሚመስል ዶሮ (ጠንቋዮች ለዛር የሚፈልጉት)

ገብረ መስቀል፡ የመስቀል ባሪያ (በ፮፻ . የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ) "ገብሩ ባሪያው ሎሌው አገልጋዩ ወዳጁ።"

ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡ የመንፈስ ቅዱስ ወዳጅ አቦ

ገብረ ማሪያም፡ የማሪያም ሎሌ/የማሪያም ወዳጅ።

ገብረ አምላክ (ገብረ፡ አምላክ) ያምላክ ሎሌ/ያምላክ አገልጋይ።

ገብረ እግዚሐር፡ የእግዚአብሔር ሰው፡ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚያስገዛ ነቢይ/ሐዋርያ/ጻድቅ/ሰማዕት፡ እውነተኛ ባሕታዊ/መናኝ/መነኵሴ። (በግእዝ "ገብረ እግዚኣብሔር" ይባላል)

ገብረ ኪዳን፡ የክርስትና ስም (የኪዳነ ምሕረት ለት የተሰየመ)

ገብረ ጕንዳን (ቃሕም) የጕንዳን ባሪያ፡ አግዝ እኸል እያጋዘ እጕድጓድ የሚያገባ/የሚከት (የገባር ዐይነት) (ምሳ. ፮፡ )

ገብራብ (ገብረ አብ) የክርስትና ስም (ጋር በገባ በ፲፫ኛ ቀን የእግዚአብሔር አብ ለት የተሰየመ)

ገብሬ (ገብርየ) ባሪያዬ/ባለሌ/የኔ ባሪያ። "ጎብሩና ገብሬ ከፊለ ስም ይኾናሉ።" "ገብርዬ ዝኒ ከማሁ የሰው ስም (ያጤ ቴዎድሮስ አበ ጋዝ)" "እሳቸውም ዐፄ ቴዎድሮስን ለመሻርና ልጃቸውን ደጃች መሸሻን ለማንገሥ ከመኳንንቱ ጋራ በመከሩ ጊዜ ንጉሡ ጠርተው 'አንተ የኔ ገብርዬ ነኸ የመሻሻ ገብርዬ ግን ሌላ ነው' በሏቸው፡ ከርሳቸው ጋራ የመከሩትን መኳንንት እየጠሩ አሰሯቸው ይባላል።"

ገብሬል (ገብርኤል) ያምላክ ባለ ኀይል፡ ያምላክ ሐርበኛ፡ የቅዱስ ሚካኤል ጓደኛ። "ጌታችንም ገብሬል ይባላል። የነበረ ገብሬል ተወገረ" እንዲሉ። (ተመልከት፡ ወገረን) "ዘርፍቀድሞት ሲነዤ ታኅሣሥ ገብሬል" ይላል።

ገብሬል ያየው ምስጢር፡ የቃል ሥጋ መልበስ ከድንግል ማርያም መወለድ። "ገብሬሏ" (የሴት ስም)

ገብሬሎች፡ የገብሬል ካህናት።

ገብር (ጸብሕ) የታላቅ ነጋሪት ድምጥ፡ ሲጮኸ "ግብር ገብር" ያለ የሚመስል። "ታዘዝ ተገዛ ግብር ስጥ" ማለት ነው አቦ

ገብር፡ ባሪያ/ተዥ/ኣልጋይ። "ጎብር የግእዝ ባሪያ ያማርኛ ነው" (ተመልከት፡ በረን) "ገብር አሽከር ሎሌ ባለ።"

ገብሮናሂ (ገብሮንሂ) " ዋዌ ነው፡ ባሪያቸውም ያሠኛል። ባለቅኔዎች ግን መለከተኛ ይሉታል።"

ገብዛዛ፡ ያረጀ፡ ፊተ ጨምዳዳ።

ገብዪ (ዎች) የሚኼድ/የሚገበይ/የሚገዛ/የሚለውጥ፡ ገዢ/ለዋጭ።

ገብገብ፡ ጎብጋባ፡ ንፉግ፡ ሥሡ፡ ቅሥሥታም፡ ደረቅ፡ የማይጠግብ፡ የማይረካ። (ተረት) ከሰው ቀለብላባ ከመሬት ገብጋባ።

ገብገቦ፡ የአጋቦስ ገዳይ፡ መዠመሪያ የትግሬ ገዢ የሐማሴን ሰው።

ገተመ (ገጠመ ትግ. ጐሰመ) ባፉ ሙሉ ቃመ/ቻመ "እረኛው አሹቅ ይገ ትማል።"

ገተም፡ በወግዳ ውስጥ ያለ ቀበሌ

ገተረ (ቀተረ) ሳበ/ለጠጠ/ወጠረ/ወተረ/ገደገደ (መዝ. ፯፡ ፲፪) "አቆመ ቀሰረ ደከረ።"

ገተርታራ/ግትርትር፡ የተግተረተረ (እንግድግድ)

ገተተ (ገቲት ገተ) ዐለቀ/ግትቻ ኾነ/ተንከረፈፈ/ተሞኘ

ገተነ (ነትገ አንተገ) ነጩ ጨቀ/ዘነተረ/ዘበተረ/በላ/ዋጠ "በምጽኣት ጊዜ ዥብ የገተነው አሞራ የበተነው የሰው አስከሬን ኹሉ ይነሣል።"

ገተገተ (ቀጠቀጠ) ነከሰ/ገጠገጠ/ዐኘከ "ዐኝ ዐኝ አለ ቈረጠመ።"

ገቲ ገታሚ ገተመ

ገታ (ገቲዕ ገትዐ) ያዘ/ከለከለ/አገረ/አቆመ/አገደ (የበቅሎ የፈረስ) "ገትዐን ትግሪኛ ገትዔ ይለዋል።" (ተመልከት፡ ገተነ ብለኸ ገታኝን እይ)

ገታሚ፡ የገተመ/የሚገትም (ቃሚ ቻሚ)

ገታሪ፡ የገተረ/የሚገትር (ለጣጭ ጣሪ አቋሚ)

ገታራ፡ የተገተረ የቆመ ("አይወሳወስ")

ገታተረ፡ ወጣጠረ/ሳሳበ

ገታኝ (ገትዐኒ) ኣገረኝ አላስኬድ

ገታኝ፡ የገተነ/የሚገትን (ቦጫቂ ዘንታሪ)

ገት ፊት፡ ፊተ መጥፎ አስቀ ያሚ

ገትጋታ፡ የያዘውን የማይለቅ (ጥብቅ እውነተኛ ሰው)

ገትጋች፡ የገተገተ/የሚገተግት (ነካሽ ዐኛኪ ውሻ ቍርጥማት)

ገቸገች/ገችጋቻ፡ ሥግሪያ የሌለው በቅሎ ፈረስ አጋሰስ መጋዣ

ገቺ (ገታዒ) የገታ/የሚገታ (ከል ካይ ኣጋጅ)

ገችገች አለ፡ እንገፍ አንገፍ አለ (መጥፎ እካኼድ ኼደ)

ገቾች፡ ጋኖች/ሰንጎች (የሠቡ ፍሪዶች ድልቦች) (መዝ. ፳፪፡ ፲፪፡ ማቴ. ፳፪፡ )

ገነበለ (ገንጰለ) ገለበጠ/አጋደመ/አስተኛ

ገነበለ፡ ገንባሌ ለበሰ

ገነበረ (ቀነበረ) ጠና/ጠነከረ (ግንባር ኾነ) "እከሌ የግንባር ሥጋ ነው" እንዲሉ (ተመልከት፡ ገበረን "ዘሩ ርሱ ነው።")

ገነበበ፡ ውሃ ስለ ወጋው ፍሬ አልባ ቀረ (ያገዳ እኽል)

ገነበጠ፡ አገዳው የፍሬ ምልክት አወጣ አሳየ

ገነተረ (ገተረ) በጥቂቱ ላይ ላዩ በሰለ (ኵምትር ስብስብ አለ ገረደደ ጠነከረ)

ገነታ (ገንሐ) ድምጡን አበርትቶ በኀይል ጮኸ/ተቈጣ/ሰበከ

ገነቴ፡ ያገር ስም (የጁ)

ገነት፡ በቁሙ ገነነ

ገነት፡ በያይነቱ ተክል ያለበት ምቹ ስፍራ (ቀድሞ አዳምና ሔዋን የነበሩበት ዛሬም የጻድቃን ነፍሳት እስከ ምጽአት ድረስ የሚኖሩበት የተድላና የደስታ ቦታ)

ገነት፡ የከተማ ስም (ካዲስ አበባ በስተምዕራብ ያለ ቀበሌ)

ገነነ (ገኒን/ገነ) ከፍ አለ/ታላቅ ኾነ/ዐየለ/በረታ (በጣም ከበረ ጌተየ በዛናቸ ለማ) "ቤቱ ገነነ እሳቱ ገነነ" እንዲሉ

ገነነ ጐነነ፡

ገነነ፡ ዐጠረ/ቀጠረ/ጀጐለ (የተክል)

ገነን/ገናና/ገናን፡ የገነነ (ጌታ ከበርቴ ሀብቱ እዱኛው እጅግ የበዛ የተረፈ ዐምባ ገነን) "ሐረርጌዎች ግን 'ገነነ አብሲት ጣለ' 'ገናና አብሲት' ይላሉ ምስጢሩ ብዛትን ብርታትን ያሳያል።"

ገነዘ (ገኒዝ/ገነዘ) የእጅን የእግርን አውራ ጣት በክር ገጠመ/ከፈነ/ሸፈነ/ጠቀለለ/አለበሰ/ሰፋ/ሸለለ "በፍትል ገመድ ዐልፎ ዐልፎ ጠለፈ አሰረ ቋጠረ።"

ገነዘበ፡ ዐሰበ/ዐወሰ/ልብ አለ/አጢነ

ገነዠበ፡ አረጀ (ተመልከት፡ ገነጀበ)

ገነደሰ፡ ከመንታ ግንድ አንዱን ሰበረ/ሠነጠቀ/አጋደመ/አስተኛ/አወደቀ (ተመልከት፡ ገረሰሰን)

ገነደሰ፡ ገደለ

ገነደረ (ገነበረ) ወፈረ/ደነደነ "ዘሩ ግንድ ነው '' ተቀጽላ ኹኖበታል "

ገነጀረ (ገዘረ) ዐረደ/ጠባ

ገነጀበ፡ ፈጽሞ አረጀ/ዘነጋ/ረሳ (ገንዘብን ሰውነትን) "ገነጀበ የገነዘበ ተቃራኒ ነው ዝነዠበ ተብሎ ሊጻፍም ይችላል።"

ገነጀብ/ገንጃባ፡ የገነጀበ ያረጀ (ዝንጉ)

ገነገነ (ገነነ) ፈራ/ጠረጠረ/ታዘበ (ነቅቶ ተጠበቀ "ያርዱኛል ይወጉኛል ይገድሉኛል ብሎ ሠጋ።") (ተመልከት፡ ከነከነን)

ገነጠለ (ነጠለ) አለስለት/ቍልቍል ወይም ወደ ጐን በእጅ ስቦ ጐትቶ ቈረጠ/ሰበረ (የዐጽቅ) "ለየ ኣበላሸ - የመጽሐፍና የማንኛውም ነገር።" (ተመልከት፡ ቈነጠለን)

ገነጣጠለ፡ የገነጠለ ድርብ (ፈጽሞ ቈራረጠ ሰባበረ ለያየ አበለሻሸ)

ገነፈለ (ገንፈለ) ፈላ/ፈለቀ (ፈልቶ ፈሰሰ "ቡናው ወጡ ጠላው ሊጡ ገነፈለ" እንዲሉ)

ገነፈለ፡ ተሸ (በውስጡ ዶቄት ፈላበት መዠመሪያ ተቀቀለበት ንፍሮው)

ገነፈለ፡ የሰው ስም (በሣህለ ሥላሴ ጊዜ የነበረ መንፈሳዊ እብድ "ፈሊጡ ግፉ በዛ ገነፈለ! ሆዴን በልቶኝ ጐኔን ቢያኩኝ አይገባኝ አይገባኝ ማለት የነበረ።")

ገነፋ (ገንፈለ) ፈላ/ተጠበሰ/በሰለ

ገኑ (ኦሮ) ከዳተኛ

ገና (ዓዲ) የጊዜ ንኡስ አገባብ (ያልተዠመረና ያልደረሰ ሰዓት)

ገና (ጌና) ታላቅ በዓል (በክርስቲያን ኹሉ ዘንድ የከበረ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት የታኅሣሥ ፳፱ኛ ቀን) "የወንዶች ገና የሴቶች ገና" እንዲሉ "የገና ለት የተገዛች ባሪያ ዘወትር ገና ይመስላታል ካለ እንደ ገና ነው።"

ገና ለገናው፡ አስቀድሞ ለሚመጣው ወደ ፊቱ

ገና መምቻ፡ ዕሩር በገና የሚመቱበት ሜዳ

ገና በርቆ ገና ዘንሞ፡ ያልተወጠነ ሥራ እንዲህ ይባልለታል

ገና ተሳዳቢ፡ የገና ለት በጥንግ ጨዋታ የተሸነፈውን ወገን የሚሳደብ

ገና ያቀነቀነ የበቀለ ጢም - ገና ማቆጥቆጥ የጀመረ ጢም።

ገና ጥዶ ገና ግሞ፡ ዝኒ ከማሁ

ገና፡ ቀድሞ/አስቀድሞ/ፊት/ዛር ልመና "ሳይያዙ ገና።" "እንደ ገና ይመታል በገና።"

ገና፡ ዕሩር ጥንግ "ገና መምቻ" እንዲሉ

ገና፡ የገና ለት ጥንግና ዕሩር በርሱ እየመቱ ልጆች (እረኞች) የሚጫወቱበት ከጫፉ ቀለስ ያለ ዱላ በትር "በገና ጨዋታ አይቈጡም ጌታ" እንዲሉ (ተመልከት፡ ጐሚትን)

ገናሌ፡ የዠማ ስም (እንደ ዳዋ ካሩሲ ተራራ የሚፈልቅ ትልቅ ዥረት)

ገናነዘ፡ ከፋፈነ/ጠቀለለ

ገናና፡ ግዛተ ሰፊ ንጉሥ

ገናናነት፡ ገናና መኾን

ገናን ሰባ፡ የቀበሌ ስም (በላይኛው ወግዳ ያለ የቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ "የገነኑ ሰባ ሰዎች ማለት ይመስላል።")

ገናንነት፡ ዝኒ ከማሁ (ኢዮ. ፵፡ ፲፡ ራእ. ፬፡ )

ገናኝ፡ የሚገን

ገናዥ (ዦች) የገነዘ/የሚገንዝ (ሸፋኝ ጠቅላይ አሳሪ)

ገን ሆይ፡ ትልቀቱ ሆይ (የአቤቶ አንጻር ነው) "ጃን ሆይ (ጋን ሆይ) ከማለት ጋራ በምስጢር ይሰማማል።"

ገን፡ ትልቅ፡ (ተመልከት፡ ገነነ)

ገን፡ ትልቋ እመቤት (በድሜና በማዕርግ)

ገንባሌ፡ እግርን ከቍርጭምጭሚት እስከ ቋንዣ የሚሸፍን የሚሸበልል ባለዘለበት ተንቤን ሸራ ወይም ሌላ ወፍራም ትልታይ ሹራብ

ገንቦሬ፡ ቀይ ዐፈር ወይም መሬት

ገንታ ገንታ አለ፡ ጮክ ጮክ አለ

ገንታ፡ ቀንዳ መለከት ቱልቱላ (ጩኸቱ በሩቅ የሚሰማ)

ገንታሪ፡ የሚገነትር

ገንታራ (ሮች) በነገሩ ከሌላ የማያሰማማ ዐመለ ሻካራ ሰው

ገንትቶ፡ ጩኾ አሰምቶ ተቈጥቶ "ገንትቶ ተናገረ ቃሉን ከፍ አድርጎ አሰማ።"

ገንቺ፡ የገነታ/የሚገነታ (ጯኺ)

ገንዘባም፡ ባለገንዘብ/ሀብታም

ገንዘብ (ቦች) ዕንቍ/አልማዝ/ወርቅ/ብር/አሞሌ

ገንዘብ አደረገ፡ ወረሰ/ያዘ/ረዘዘ/ገዛ/ነዳ

ገንዘብ ካለ፡ በሰማይ መንገድ አለ (በጥያራ መብረር ይቻላል በምጿት ገነት መንግሥተ ሰማይ ይገኛል)

ገንዘብ፡ በገንዘብ የተገዛ በድካም የተገኘ ከብት ዕቃ ማንኛውም ለሰው ጠቃሚ የሚኾን ነገር ኹሉ

ገንዘብ፡ ዐቢይ ኣገባብ (ከኣንቀጽ ጋራ እየቀደመው ማሰሪያ ሲያስቀር እከሌ እከሌን ባዋረደ ገንዘብ ተዋረደ ይላል ምስጢሩም ስላዋረደ እንዳዋረደ ያዋረደ ያኸል ማለት ነው በግእዝ መሠረቱ በዘ)

ገንደስ ገንደስ አለ፡ ግንድኛ ኼደ/ተራመደ (የወፍራም ሰው)

ገንደስ፡ ዘንበል/ጋደም

ገንዳ፡ ከግንድ ተፈልፍሎ የተበጀ ሞላላ የቤት ዕቃ (ማቡኪያና ጠጅ ማሳረፊያ) "ገንዳ መካከሉን ጠርበው አጐድጕደው ለከብት ውሃ የሚያጠጡባት ብሓ ደንጊያ። በግእዝ ገብላ ይባላል።"

ገንዳሳ፡ ጋድሚያ/ውድቃን/እንቅልፋም ዐዞ

ገንዳሽ፡ የገነደሰ/የሚገነድስ (ሰባሪ)

ገንዴት፡ ምርቀ ትንሽ ዐጪር ገብስ

ገንዶር፡ የእግር ማሰሪያ ግንድ (ግእዝ) "ገንዶራሂ '' ዋዊ ነው የእግሯ ማሰሪያም ያሠኛል ባለቅኔዎች ግን ነጋሪት መቺ ይሉታል።"

ገንጃሪ፡ የገነጀረ/የሚገነጅር (ዐራጅ በጋማች)

ገንገበት፡ ቀቀበታም/ገብጋባ/ሥሥታም (ግርግራ) "ዘሩ ገበገበ ነው።"

ገንጋና፡ ዝኒ ከማሁ

ገንጋኝ (ኞች) የገነገነ/የሚገነግን (ፈሪ ጠርጣሪ ታዛቢ ሥጉ)

ገንጣላ፡ የተገነጠለ (ሰባራ)

ገንጣይ (ዮች) የገነጠለ/የሚገነጥል (የሚያበላሽ)

ገንጥል፡ የሚለይ (ሰባሪ) "ዛቢያ ገንጥል" እንዲሉ "ገንጥል ትእዛዝ ሲኾን በቅጽልነት መፈታቱን አስተውል።"

ገንፋይ፡ የሚገነፍል/የሚፈላ

ገንፎ፡ ከፍና ከገብስ ከዐጃ ዱቄት የተዘጋጀ (ቅቤና ዐዋዜ የገባበት የላመ የጣመ ለስላሳ ምግብ)

ገኛ

ገወለል/ገውላላ፡ የተንገዋለለ/የዞረ

ገወራ፡ በጐዣም ውስጥ ያለ አገር ትርጓሜው ጉርብትና ማለት ነው

ገውዝ (ዐረ. እልጀውዛ) ሥዕሉ ባልና ሚስት ወንድና ሴት የሚመስል የግንቦት ኮከብ (ዕጥፍ/ጥንድ/መንታ ማለት ነው) "ገውዝ ነፋስ" እንዲል ጠንቋይ "ወሩን ኮከቡ ስለ ያዘው ሽማግሎች በግንቦት መጋባት አይገባም ይላሉ።"

ገውዝ (ዞች) የተክል ዛፍ ስም (ፍሬው የሚበላ መንታነት ያለው "ገውዝ ለውዝ" እንዲሉ)

ገውዝ ነፋስ፡ የነፋስ ገውዝ (በግንቦት ኀይለኛ ነፋስ መንፈሱን ያሳያል)

ገውጋዋ (መንጎግው) ዘዋሪ/ቀውላላ (ሞኝ) "ኦሮ 'ጥዋ' የሚለው ከዚህ ጋራ አንድ ነው" (ተመልከት፡ ቀውቃዋን)

ገውጡ፡ መረንዐገገ

ገዎች ቻ፡ ገለብ/ቋጥኝ (ታላቅ የደንጊያ)

ገዎች ዐምባ፡ ቋጥኝ ያለበት መንደር ወይም ቀበሌ/ተራራ

ገዘመ (ገዚም/ገመ) ቈረጠ/ከፈለ/አመመ

ገዘመ፡ ናቀ/ነቀፈ/አሸነፈ/አዋረደ/ገረዘዘ

ገዘረ (ገር/ገዘረ) ገረዘ/ቈረጠ/ቀነጠበ "ገዘረ የግእዝ ገረዘ ያማርኛ ነው።"

ገዘራ፡ መግረዝ/ቈረጣ

ገዘተ (ወጊዝ/ወገዘ) በቃል/በመንፈሳዊ ሥልጣን ያዘ/አሰረ "ክፉ ነገር እንዳይሠራ እውነተኛ ሃይማኖት እንዳይካድ አገደ ከለከለ። ሠርቶ ክዶ ቢገኝ ከሕዝብ ከማኀበር ለየ እወገዘ ቄሱ ጳጳሱ።" "በረከተ የባረከ ጥሬ ግስ እንደ ኾነ 'ገዘተም' የወገዘ ጥሬ ግስ ነው።"

ገዘት፡ ስም በመንዝ ውስጥ ያለ ቀበሌ

ገዘዘ (ገዚዝ/ገዘ/ገዘዘ) ጀጐለ/ዐጥር ዐጠረ/ቀጠረ/ጋረደ/ከለለ/መከተ (ተመልከት፡ ሃዘ ገዘን የዚህ ደጊም ነው)

ገዘገዘ (ገዚዝ/ገዘ/ገዘዘ/ገዝዐ ወሠረ) ከረከረ/መዝከረከመ/ከመመ

ገዘገዘ፡ አደከመ/አሰለተ "እከሌን በሽታ ገዝግዞታል "

ገዘገዘ፡ ከበደ/አረጀ "ሰውነቱ ገዝግዟል "

ገዘገዝ/ገዝጋዛ፡ ለዝጋዛ ገትጋታ ነገር የማይቈርጥ

ገዘፈ (ገዚፍ/ገዝፈ) አጐራ/አጓራ/አጋፈተ "ሂያ ሂያ አለ" (የዛር) "አካል ገዛ ዳጐሰ ደነደነ ወፈረ ጐላ ዛርም ቢኾን በሰው ዐድሮ ሥጋ ለብሶ ማለት ነው።"

ገዘፋ፡ ድንደና/ውፈራ።

ገዛ (ገዚእ/ገዝአ) ማንኛውንም ነገር በገንዘብ በየ እቀና እኸልን ሸመተ እስረኛን ዋጀ

ገዛ፡ ርስ/ራስ "የስም ዘርፍ እየኾነ ይነገራል በመነሻውም '' ያስቀድማል።"

ገዛ፡ አገርን በጦር ኀይል ያዘ/ኣስገበረ/ጌተየ/ጌታ ኾነ/ሠለጠነ/አዘዘ

ገዛሚ፡ የገመ/የሚገዝም/የሚያመም/የሚገረዝዝ (አማሚ/ገርዛዥ/አሸናፊ እንቅልፍ ሰው)

ገዛሪ፡ የገዘረ/የሚዝር (ገራዥ)

ገዛች፡ የገዘተ/የሚዝት/የሚያስር/የሚለይ/የሚያወግዝ (አውጋዥ) "ገዛቾች አውጋዦች ቄሶች ጳጳሶች።"

ገዛዛ፡ የገዛ ድርብ መላልሶ ገዛ/ገበያየ ሸማመተ

ገዛፊ (ፎች) የሚገዝፍ/የሚያጐራ/የሚያጓራ ቃልቻ

ገዛፍ፡ ዝኒ ከማሁ (ደጓሳ/ወፍራም)

ገዝሙ፡ የሰው ስም/የሴት ስም

ገዝም፡ እመም/ቃዳ/ተለላ/ፈፋ/መዛሪያ/ትልም "በትግሪኛ ግን 'ገዝሚ' መዳሪያ ማለት ነው ርስቱ ገንዘቡ ተከፍሎ መሰጠቱን ያሳያል።"

ገዝት፡ ዝኒ ከማሁ ለገዛች "ወፈ ገዝት" እንዲሉ።

ገዝጋዥ (ዦች) (ገዛዚ/ገዛዒ/ወሣሪ) የገዘገዘ/የሚዝግዝ/የሚመግዝ (መጋዥ ከርካሪ/ከርካሚ)

ገዠሞ (ዎች) (ገዛሚ/መግዝም/ጕድብ) ባለቒ ጫፍ መሣሪያ (ዶማ ባ፩ ወገን ሹለት በኛው በኩል ስለት ያለው መቂፈሪያና መቍረጫ)

ገዢ (/ዦች) (ገዛኢ) የሚገዛ (ጌታ/ሹም/መኰንን) (ዘዳ. ፩፡ ፲፭፡ ምሳ. ፮፡ ) "አገረ ገዢ" እንዲሉ።

ገዢነት፡ ገዢ መኾን/ጌትነት።

ገደ

ገደ ቢስ፡ ዕድለቢስ/ሀብተ ቢስ (ዕድሉ ማጣት የኾነ)

ገደለ

ገደለ (ገዲል/ገደለ/ቀቲል/ቀተለ) ዐደነ/መታ/ደበደበ/ወጋ/እቈሰለ

ገደለ፡ ወደ ገደል ጣለ/ኣሽቀነጠረ።

ገደሉ ገደልገባ፡ ፈረሰ/ተናደ/ወረደ።

ገደላም፡ ገደል ያለበት/የበዛበት ስፍራ።

ገደላገደል፡ የገደል ገደል።

ገደል (ሎች) የተራራና የኰረብታ ደረት፡ የደጋና የቈላ የላይና የታች መካከል የሚያዝ/የሚጨበጥ ነገር የሌለበት የመጥፎ ነገር መጣያ (ሕዝ. ፮፡ ) (ተረት) "እባብ ግደል ከነበትሩ ገደል።" (ተመልከት፡ ማሞን)

ገደል ሰደደ፡ አንከባለለ።

ገደል ገባ (ጸድፈ) ተንከባለለ/ወደቀ።

ገደልጌ፡ በይፋት ያለ ቀበሌ

ገደመ (ገዲም/ገደመ) ገዳም አደረገ፡ ለገዳም ሰጠ፡ ጐለተ/ከለለ፡ መስቀል አዞረ "ዳሩ እሳት መኻሉ ገነት" እለ (ዘፍ. ፫፡ ፳፬)

ገደማ፡ ዘንዳ/ዘንድ/ቀበሌ/ኣጠገብ

ገደማ፡ ያገር ስም (በታችኛው ወግዳ ወረዳ ያለ አገር) "ገደማ ጊዮርጊስ" እንዲሉ።

ገደማ፡ ጊዜ/ሰዓት "ወደ ማታ ገደማ እመጣለኹ።"

ገደም አለ፡ ወደ ጐን ኼደ።

ገደረ (ዕብ. ጋዳር ዐጠረ/ቀጠረ/ከተረ ዐረ ቀደረ ቻለ) አስቸገረ/አሳጣ (በችግር/በዕጦት ከበበ)  

ገደረ፡ ቻለ/ቀጠለ (ተመልከት፡ ቄደረን)

ገደረ፡ አሽማጠጠ/አላገጠ።

ገደራ፡ ያገር ስም (በሺዋ ክፍል ያለ አገር)

ገደበ (ጐዲብ/ጐደበ) ከተረ ገደ/ወሰነ/ከለከለ/ወደበ/ደለደለ/ዦር ሠራ/አበጀ

ገደበ፡ ዕድር ዐደረ።

ገደበ፡ ደገፈ/ሀጎዘ/ረዳ።

ገደብ፡ ዕድር/ማገጃ/ውሳኔ/ዕርቅ አፍራሽ የሚከፍለው ዕዳ። "የተጣሉት ሰዎች በገደብ ታረቁ።" (ተረት) "ዐጢን መደብ ይተ ጌን ገደብ።"

ገደብ፡ ወሰን/ወደብ/ዐቃባ/ደገፍ (ኢዮ. ፳፰፡ ፲፩)

ገደደ (ገዲድ/ገደ) ግድ/ግዴታ ኾነ፡ ጠመመ/ተጠመዘዘ

ገደደ፡ ቸገረ/ጠፋ/ታጣ/ተሳነ (ሉቃ. ፳፪፡ ፴፭)

ገደገደ (ገድገደ) ተከለ/አቆመ/እወከ/ገረገረ (አላናግር/ኣላስኬድ አለ) "ርጥብ ቈዳን በካስማ ወጠረ ገተረ።" (ተመልከት፡ መደመደን)

ገደፈ (ገዲፍ/ገደፈ) ጊዜ ሳይደርስ በላ ጦምን ተወ/ሻረ/ፈሰከ

ገደፈ፡ ቃል/ትምርትን ዘነጋ/ረሳ/ጣለ/ሳተ/ዘለለ/ዘለጐሰ/አጐደለ (ሲጥፍና ሲያነብ እጠፋ)

ገደፋ፡ ግድፈት/ርሳታ/ዝንጋታ/መግደፍ (መክ. ፲፡ ) "ለቦም ግድፈት ለበዓል ሽረት" እንዲሉ።

ገደፍ ዐቃባ ደገፈ/ደገፍ

ገዲ (ዶች) (አንቄ) አሞራ/ጭላት (የዶሮና የወፍ ጠላት፡ መልኳ በስተኋላ )

ገዳሚ፡ የገደመ/የሚገድም (ገዳም የሚያደርግ)

ገዳሜ/ገዳሜ ገደምዳማዬ፡ የዘፈን አዝማች

ገዳም ኾነ፡ በብዙ ዘበኛ ታጀበ/ተከበበ

ገዳም ገባ፡ ዓለምን ናቀ/ተወ/መነነ/ከዓለም ተለየ

ገዳም፡ ታላቅ ደብር (የከተማ ቤተ ክሲያን በዙሪያው መስቀል የዞረበት መደወያ መማጠኛ)

ገዳም፡ የመናኞች/ባሕታውያንና መነኮሳት መኖሪያ (ዓለማዊ የሌለበት ስፍራ ዋልድባንና ደብረ ሊባኖስን የመሰለ ዱር በረሓ ደን) "የፈላሾች ቦታ የጠይብ ገዳም" እንዲሉ። "ገዳም መባሉ ጠይቦቹ መነኮሳት ስላሏቸው ነው።"

ገዳም፡ የቤት አሽከር/የንጉሥ ዘበኛ።

ገዳምጌ፡ በታች ወግዳ ያለ አገር (የገዳም ምድር ማለት ነው)

ገዳሞች (ገዳማት) ዱሮች/መናኞች/መነኵሴዎች/ጠይቦች

ገዳሞች፡ መሸሻዎች/መደወያዎች/መማጠኞች ስፍራዎች (ዘኍ. ፴፡ , )

ገዳቢ፡ የገደበ/የሚገድብ/የሚያግድ (እጋጅ/ዐጋዥ/ረዳት/ደጀን የኋላ ጦር)

ገዳዎ፡ ጉዳይ ሆይ። (ተመልከት፡ ዐሻን)

ገዳይ (ገዳሊ/ቀታሊ) የሚመታ/የሚገድል (ዐዳኝ/ነፍስ አጥፊ) (ዘዳ. ፬፡ ፵፪፡ ማቴ. ፳፪፡ ፯፡ ሉቃ. ፲፫፡ ፴፪) "ነፍሰ ገዳይ ሰው ገዳይ" እንዲሉ። (ተረት) "እኸል ከበዩ ሰው ከገዳዩ።" (ተመልከት፡ ጓሮን)

ገዳይ፡ የጉደለ/የገደለች። "ሴትን ከወንድ ለመለየት 'ገዳዪት' ይሏል።"

ገዳይ፡ የፉከራ ቃል "እዚህ ገዳይ" እንዲል ፎካሪ። "ተደጋግሞ ሲነገር 'ገዳይ ጉዳይ' ይባላል።"

ገዳይነት (ቅትለት) ዐዳኝነት/ገዳይ ሙኾን

ገዳዮች፡ የገደሉ/የሚገድሉ (ወንዶችና ሴቶች)

ገዳደለ፡ የገደለ ድርብ መላልሶ ፈጽሞ ደባደበ/ገደለ

ገዳዳ (ዶች) የገደደ (ጠማማ/ጠምዛዛ/ወልጋዳ/ዘዋራ)

ገዳጅ፡ የሚገድ (ጠማሚ/ቸጋሪ)

ገዳፊ፡ የገደፈ/የሚገድፍ (ጦምን የሚተው አለሰዓቱ የሚበላ ገዳፊ)

ገዳፋ፡ ዝኒ ከማሁ

ገዳፍ ቃል፡ የሚገድፍ/የሚጥል መጽሐፍ/ሰው።

ገድ በለኝ፡ በጧት የኔን ዕቃ ግዛ።

ገድ፡ ዕድል/ክፍል/ሀብት/በረከት (ሥሩ "ገደደ" ይመስላል)

ገድለኛ፡ ገድል ያለው/ባለገድል (ሰማዕት/ጻድቅ)

ገድል (ሎች) የሰማዕታትንና የጻድቃንን መጋደል የሚነግር መጽሐፍ። "ገድለ ጊዮርጊስ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ያቦ ገድል" እንዲሉ።

ገድል፡ ሰማዕታት ስለ ክርስቶስ እጅ እግራቸውን ለስለት ዐይናቸውን ለፍላት ሰጥተው በሰውነታቸው የፈጸሙት መንፈሳዊ ትግልና ግድያ። "ጻድቃን የመዓልት ሐሩር የሌሊት ቍር ታግሠው ዳዋ ለብሰው ደንጊያ ተንተርሰው ጤዛ ልሰው ያደረጉት ስግደት ጾም ጸሎት ትሩፋት መልካም ሥራ ኹሉ።"

ገድገድ/ገድጋዳ፡ ወዝዋዛ/ነቅናቃ/ቀጥቃጣ

ገድጋጅ (ጆች) የገደገደ/የሚገደግድ/የሚተክል (ተካይ/ወጣሪ) (ተረት) "ያባት ወዳጅ የድንጋይ ገድጋጅ።"

ገድፎ ትቶ፡ (ተረት) "በዓል ሽሮ የከበረ ጦም ገድፎ የወፈረ የለም።"

ገጀለ (ገደለ/ተገደለ) ልበ ሙት ኾነ/ቄለ

ገጀለ፡ ግጅል

ገጀሞ መቍረጫ፡ ገዠሞ

ገገመ፡ ከጕዳት/ከክሳት/ከመገርጣት ጥቂት ዳነ/አሸለተ፡ ደሙ ተመለሰ/ተሻለው።

ገገም አለ፡ ገገመ፡ በረታ፡ ዐቅም አገኘ። (ተመልከት፡ ዘገመንና ሸለተን)

ገገምተኛ (ኞች) ያገገመ/ያሸለተ/የተሻለው

ገገምተኛነት፡ ገገምተኛ መኾን።

ገገምታ፡ ጤና/ድኅነት

ገገረ

ገገረ፡ አፈጠጠ (ዐይኑን አፍጦ አየ/ጀጀረ) አጐረጠ።

ገገጭ፡ ገጭጋ ሚል የሚጮኸ ቀጭ

ገጋ፡ (ኦሮ ወለላ የሌላት የንብ ደረቅ ቀለሕ ሰፈፍ)

ገጠ

ገጠ ቢስ፡ ፊተ መጥፎ/ግንባረ ፈጣጣ/አፍንጫ ደፍጣጣ መልኩ የማያምርና ደስ የማያሠኝ ሰው

ገጠመ፡ በመንገድ አገኘ

ገጠመ፡ አንድ ኾነ/ዐበረ "የባልና የሚስቱ ኮከባቸው ገጥማል።"

ገጠመ፡ ዘጋ/ዐተመ/ልክክ አደረገ (ማር. ፲፭፡ ፲፮) (ተመልከት፡ ሰካንና ወደደን)

ገጠመ፡ ዘፈነ (የዘፈንን ጫፍ አንድ ዐይነት ፊደል አደረገ ቤት መታ) (፪ዜና. ፴፭፡ ፳፭)

ገጠመ፡ ዠመረ/ያዘ "ውጊያ ሙግት ጦርነት ገጠመ" እንዲሉ።

ገጠም፡ የገጠሙ "ኩታ ገጠም" እንዲሉ።

ገጠረ፡ ዋንጫ ኾነ "ይህ መሬት ገጥሯል።"

ገጠረ፡ ፈረሰ/ወደቀ/ተፈታ/ጠፋ (ያገር/የከተማ)

ገጠር (ሮች) ባላገር (የባላገር ቤተ ክሲያን አጥቢያና ሰበካ ቀበሌ ጭንጫ)

ገጠበ

ገጠበ (ትግ. ገጸበ/ተገጠበ) ነካ/አቈሰለ/መለጠ/ላጠ/ላፈ/ጋጠ ገላን በጭነት ባለንጋ ሣርን በጥርስ በማጭድ

ገጠገጠ (ቀጥቀጠ) ቀጠቀጠ/መደበደበ (የክትክታ/የፍየለፈጅ)

ገጠገጠ፡ ብዙ ቤት ሠራ/ፀያድንኳን ተከለ

ገጠጠ፡ ባይን ቂጥ በክፉ ገጽ እየተኰረ ፊት ነሣ አጐጠጠ (ገቢር) (ተመልከት፡ ገመጠጠን)

ገጠጠ፡ ገጣጣ ኾነ/ፈነገጠ/ፈነረ ወደ ገጽ (ግንባር) ቀና አለ (ተገብሮ)

ገጡ ለጣይ፡ ጥርሱን የማይከድን

ገጣለ፡ ገጥ አለ (ገጸወ) ፊት ለፊት ተገለጠ/ታየ/መጣ/ከተፍ አለ

ገጣሚ (ሞች) የሚገጥም (ዐናጢ/ዘፋኝ/ግጥም ዐዋቂ)

ገጣቢ፡ የግጠበ/የሚገጥብ (ኦቍሳይ)

ገጣቢት፡ የተገጠበች (ተረት) "ወደሽን ገጣበት ንጉሥ ትመርቂ።"

ገጣባ (ቦች) የተነካ/የተገጠበ (የጋማ ከብት/የጭነት አጋሰስ/ወቀሬ/ግመል) "ገጣባ አህያ" እንዲሉ።

ገጣባ፡ ቢጋማ ከብት ዠርባ ላይ ያለ ቍስል

ገጣጠመ፡ መላልሶ ብዙ ጊዜ ገጠመ ዘጋ/ደጋጋ/ዘፋፈነ

ገጣጣ (ጦች) የገጠጠ (ጥርሰ ረዥም ጣረ ሞት ፍልፈል ዕሪያ) (ተረት) "ገጣጣ ሲሞት የሣቀ ይመስላል።"

ገጣጣሚ፡ የገጣጠመ/የሚገጣጥም ዕቃን/ግጥምን

ገጣጭ፡ የሚገጥ (አጐጣጭ)

ገጥ (ገጽ) ግንባር/ፊት (ከግንባር እስከ አገጭ ያለ የፊት መልክ) #

ገጥ፡ በፈረስና በበቅሎ ግንባር ላይ የሚውል መካከለኛ የልባብ ጠፍር

ገጥ፡ የፊት ጥርስ

ገጥም

ገጥታ (ገጽ) ገጥ ፊት አርኣያ ምስል ወረራ መልክ "ይህ ሰው ገጥታው አያምርም።" (ተመልከት፡ ገጠጠንና ጐጠጠን)

ገጥታ (ግጻዌ) የፊት/የግንባር መገለጥ/መታየት

ገጥጋጭ፡ የገጠገጠ/የሚጋግጥ ቃጭ

ገጨ (ጐጠየ) መታ/ኰረኰመ/ለተመ/ተመተመ ገጽን (ተመልከት፡ ገገን የዚህ ደጊም ነው)

ገጨረ፡ ደነሰረ/ጐበለ

ገጨገጯ (ቀጯቀል) መላልሶ ገጯገጯ ጮኸ ድምጡ ጩኸቱ ተሰማ ከመጋጨት የተነሣ (የደንጊያ/የብረት/የንጨት የደረቅ ነገር ኹሉ።)

ገጭ አደረገ፡ ገጨ መታ

ገጭ፡ መግጨት

ገጭገጭ አለ፡ ተንገጫገጩ

ገጭገጭ አደረገ፡ አንገጫገጩ

ገጯ፡ የሚገጭ (ለታሚ)

ገጸ ላሕም፡ ፊቱ በሬ የሚመስል መልአክ

ገጸ ሰብእ፡ ፊቱ ሰው የሚመስል መልአክ "እነዚህ ኹሉ የግዜርን መንበር ተሸካሞች ናቸው ነገዳቸውም ኪሩብ ይባላል" (ሕዝ. ፩፡ ፲፡ ራእ. ፬፡ )

ገጸ በረከት (በረከተ ገጽ) እጅ መንሻ መተያያ (ለጳጳስ ለንጉሥ ለባለማዕርግ ኹሉ የሚሰጥ ገንዘብና ማንኛውም ስጦታ ጥቂቱ እንደ ብዙ ኹኖ በተቀባዩ ፊት ስለሚቀርብ በረከተ ገጽ ተባለ)

ገጸ ንስር፡ ፊቱ አሞራ የሚመስል መልአክ

ገጸ አንበሳ፡ ግንባሩ ፊቱ አንበሳ የሚመስል መልአክ (ፊተ አንበሳ)

ገጸ ከልብ፡ ውሻ ፊት (ውሻ መሳይ ሰው የቅዱስ መርቆሬዎስ ጋሻ ዣግሬ) (ተመልከት፡ እንድሪስን እይ)

ገጽ፡ በአርእስት የተጻፈ አኃዝ የገጽን ብዛት የሚነግር

ገጽ፡ ከአርእስት እስከ ኅዳግ ከምስማክ እስከ ግልየት የሚታይ የመጽሐፍ መልክ

ገጽ፡ ግንባር/ፊት (ተመልከት፡ ገጥን እይ)

ገጾች፡ ግንባሮች/ፊቶች

ገፈል (ዐረ. ጀፈል) የቡና ገለባ "ገፈል ትግሪኛ ነው።"

ገፈረ፡ ቸፈረ/ቃመ/ቻመ/በላ

ገፈረ፡ ገፈራ ከፈለ/ገበረ

ገፈራ፡ ቃሚያ/ቅሞሽ "የገፈራ እኸል" እንዲሉ

ገፈራ፡ የሹም የመንግሥት ፈረስ በቅሎ የሚገፍረው የሚበላው ገብስ "ይህንንም ባላገር ይሰፍራል።"

ገፈተ፡ ኣቅለሸለሸ (ልውጣ ልውጣ አለ ፈጀ አቃጠለ ዐመመ "ይህ ኮሶ (እንቆቆ) ልብ ይገፍታል")

ገፈተ፡ ፈትን ገፈፈ (ቀመሰ ጠጣ ዠመረ "ዘኮንኪን ገፍትልኝ" እንዲል ተማሪ ዠምርልኝ ሲል)

ገፈተረ (ገፈተ/ፈተረ) በኅይል ገፋ

ገፈታ፡ ዝኒ ከማሁ (እስኩታ)

ገፈት፡ ያሻሮ የብቅል ገለባ (በጠላ ላይ የሚሰፍ ዐሠር)

ገፈን (ትግ) ፈፋ/ፈረፈር

ገፈገፈ (ገፈፈ) (ትግ. ገፍገፈ) ሥራን ኹሉ ብቻውን ሠራ/ገፋ

ገፈገፈ፡ ላጠ/ላጯ! ዐጨደ/ጠረገ/ቀረደደ/ሰበሰበ

ገፈገፈ፡ በላ/ጨረሰ

ገፈገፈ፡ ብዙ ዕዳ ከፈለ

ገፈገፍ፡ በመንዝ ውስጥ ያለ አገር "ምስጢሩ የካፊያን ብዛትና ደጋነትን ያሳያል።"

ገፈጠ (ትግ) ለቀመ/ሰበሰበ/አከማቸ

ገፈጠጥ/ገፍጣጣ (እንግፍጥ) የተንገፈጠጠ (ጠረዘዝ ቀበዴድ ጠርዛዛ ቀብዳዳ ዘርጣጣ)

ገፈጥ (ትግ) ግባስ ማገዶ

ገፈፈ (ቀፈፈ) ቈዳን ከሥጋ ዐይነ ልቡናን ከዐይን ልብስን ከገላ ክዳንን ከጣራ ገፈትን ከጠላ ላይ ሰነዘረ/ሸለቀቀ/ለየ/አስገለለ/ነጠቀ/ቀማ/ሞሸለቀ/አራቈተ/አነሣ (ጠጕርን ላጩ ዛፍን ላጠ) (ዘፀ. ፲፪፡ ፴፮፡ ሚክ. ፫፡ ፫፡ ማቴ. ፳፯፡ ፳፰፡ ፩ቆሮ. ፲፩፡ ፰፡ ቈላ. ፪፡ ፲፭)

ገፈፋ (ትግ. ሐባ) ምርኮ/ምርኮኛ

ገፈፋ፡ የመግፈፍ ሥራ/ቅሚያ

ገፊ (ዎች) (ገፋዒ) የገፋ/የሚገፋ (በዳይ ጉዳይ አጥፊ) (ተመልከት፡ ወስንን ዐፈርን እይ)

ገፊ፡ አሻራው በግንባሩ የኾነ ልጅ (አባት እናቱ የሞቱበት ዘመዶቹ ያለቁበት)

ገፋ (ገፊዕ/ገፍዐ) ማንኛውንም ነገር ካለበት ስፍራ ዕልፍ አደረገ/አገለለ

ገፋ ቢል፡ ቢያክል/ቢጨምር/ቢበዛ

ገፋ አደረገ፡ ዕልፍ አደረገ

ገፋ ገፋ አደረገ፡ ዕልፍ ዕልፍ ገለል ገለል አደረገ (ገፋፋ)

ገፋ፡ ናጠ/ወዘወዘ (ወተትን)

ገፋ፡ ዐመፀ/በደለ

ገፋ፡ ዐበጠ/አደገ/ሰፋ/በዛ/በረከተ (የሆድ የቀን) "አድራጊና ተደራጊ መኾኑን አስተውል "

ገፋሪ፡ የገፈረ/የሚገፍር (ቃሚ ምስንጅር)

ገፋች (ቾች) የገፈተ/የሚገፍት (ገፈት ጠጪ ዐቃቢ)

ገፋፊ (ዎች) የገፈፈ/የሚገፍ (የማለይ ቀማኛ ወንበዴ ያፈ መምር አሽከር የማች ልብስ ወሳጅ) "ልብስ ገፋፊ" እንዲሉ

ገፋፋ፡ የገፋ ድርብ (መላልሶ ገፋ "አድርግ አድርግ በል በል አትፍራ አለ አስደፈረ" (ኢሳ. ፫፡ ))

ገፍ፡ ከጳጕሜ መጨረሻ ያለፈ ዝናም "የዘንድሮ ክረምት ካምና ይልቅ ገፍ ነው ምስጢሩ ብዛትንና መግፋትን ያሳያል።"

ገፍ፡ የስጦታ ብዛት ልክ የሌለው "እከሌ ቸር ነው በገፍ ይሰጣል።"

ገፍታሪ፡ የገፈተረ/የሚገፈትር (ገፊ! ነፋስ ውሃ ሰው)

ገፍጋፊ፡ የገፈገፈ/የሚገፈግፍ (ገፊ ዐጅ ቀርዳጅ)

ጕ፡ የማር መስፈሪያ ("ብዙውን ጕንዶ አንድ የሚያደርግ ማድጋ")

ጕለላ፡ የመጐለል ሥራ (ከደና)

ጉለሌ፡ የቀበሌ ስም (ባዲስ አበባና በሰላሌ ይገኛል ጉለሌ አቅኒው ነው)

ጕለማ፡ የመክፈል ሥራ (ቈረጣ ልየታ)

ጕለሻ (ሾች) ደካማ ዐቅመ ቢስ

ጕለሻ ደካማ፡ ጐለሰሰ

ጕለንታ፡ በርሻ ዳር ያለ የቦይ ዐፈር ጓል ድድቅ

ጕለንታ፡ ጥምጥም ጠጕር

ጕሊት፡ የሠባች ወፍራሚቱ መሬት

ጕላላ፡ የግንድና የደንጊያ ክምር (የውሃ መገደቢያ)

ጕላስ፡ ዐሸን ብዙ ጕንዳን ሰራዊት ምድርን የሚያለብስ የሚሸፍን

ጕላንጆ፡ ያልሠባ/ያልጮመየ ጕፋያ

ጕል፡ ዝኒ ከማሁ

ጕልሕ (ሖች) (ጐሊሕ/ጐልሐ) የጐላ ግዙፍ ወፍራም ቁም ጥፈት (ወይም ረቂቅ ያይዶለ ሌላ ነገር)

ጕልላት (ቶች) (ጐላት) በዘውድና በአክሊል ምሳሌ የተሠራ ሸክላ የቤት ቆብ (ኳስ የሚመስል ክብ እንክብል በድንኳን ጫፍ የሚሰካ ፪ና ዕንጨት) (ኢሳ. ፶፬፡ ፲፪፡ ዘፀ. ፴፮፡ ፴፰) (ተመልከት፡ ማዘንትን)

ጕልል፡ ተከድኖ ያለቀ (የተጐለለ)

ጕልመሳ፡ ጕልማሳ መኾን

ጕልማ (ሞች) ላሽከር/ለሎሌ/ለዘመድ/ለወዳጅ ተከፍሎ የተሰጠ ማሳ "ይህ ዕርሻ የጕልማዬ ነው።"

ጕልማ፡ የወንድና የሴት ስም

ጕልማሳ፡ የጐለመሰ (ለጋ ጐበዝ ወጣት ሶባ ሥታ ለማልሞ ዐፍለኛ ጐረምሳ ሠላሳ ዓመት የመላው መናዎ)

ጕልማስነት፡ ዝኒ ከማሁ

ጕልማሶች፡ ዐፍለኞች (ዘዳ. ፴፩፡ ፲፰)

ጕልም፡ የተጐለመ (ጕልማ የኾነ)

ጕልምስና፡ ጕልማሳነት/ጕርምስና/ጕብዝና ዐፍላ

ጕልስስ አለ፡ ተጐለሰሰ

ጕልስስ አደረገ፡ ጐለሰሰ

ጕልስስ፡ ዝኒ ከማሁ

ጕልሻ ከለላ፡ ጐለሰሰ

ጕልሻ፡ የኀፍረት የብልት ከለላ ጨሌ

ጕልበተኛ፡ ዝኒ ከማሁ (ሐርበኛ)

ጕልበቱን አፈሰሰ፡ ወዙን ማለት ነው (ሥራ ሠራ)

ጕልበቱን ኰርምቶ ያደረውን ወንድ ባለጌዎች የኰርምት ክፈል ' ይሉታል

ጕልበታም፡ ኀይለኛ/ጐበዝ/ብርቱ/ጠንካራ

ጕልበት (ቶች) (ብርክ/አብራክ) በጭንና በቅልጥም መካከል ያለ የእግር አንጓ ዐጥቅ (ሎሚታ ታጥፎ የሚዘረጋ ተዘርግቶ የሚታጠፍ)

ጕልበት አወጣ፡ ኅይል አገኘ/ጐለበተ

ጕልበት፡ ኀይል/ብርታት/ጥንካሬ "ድኻ በጕልበቱ ባለጠጋ በሀብቱ ከብዙ ጕልበት ጥቂት ብልኀት" እንዲሉ።

ጕልባን፡ የባቄላ ክክና የፍትግ ስንዴ ንፍሮ በጸሎተ ኀሙስ የሚበላ የዕዝን "ጕልባን የጐለበና የቀለበ ዘር ነው።"

ጕልቴ፡ የሰው ስም "የኔ ጕልት ማለት ነው።"

ጕልቴና ሰሎሞን፡ በሣህለ ሥላሴ ጊዜ የነበሩ ሊቃውንት (በማታለልና በመታለል የታወቁ አንዱ ያስፈራኻል ኹለተኛው ተጠንቀቅ እያሉ ሌላውን የሚያታልሉ ርስ በርሳቸውም የሚታለሉ ቀልደኞች የንጉሥ ባለማሎች አጫዋቾች)

ጕልት ቀለም፡ ፊደል "በግእዝ እግዚኡ እዴሁ እያለ ገቢር ተገብሮ የሚከት።"

ጕልት አለ፡ ተጐለተ (ተመልከት፡ ገደመ ብለኸ ግድም አለን)

ጕልት አደረገ፡ ጐለተ

ጕልት፡ የወሰን ደንጊያ ባራት ወገን የተተከለ

ጕልቻ (ቾች) ከሸክላና ከብሓ ደንጊያ ከብረት የተበጀ የድስት የምጣድ የማሰሮ የጋን መጣጃ ባለ፫ ቍጥር

ጕልቻ፡ ሹለትና ክንፍ ያለው የመርከብ ማቆሚያ መልሕቅ

ጕልድማ (ሞች) ጫፈ ድብልብል የማውድ ዐጥንት "ፈረንጆች 'ፌሙር' ይሉታል።"

ጕልድማ፡ ቍርጭምጭሚት/ኵርማ/ጕልበት አንጓ መለያያ

ጕልድም፡ የተጐለደመ/የተናጋ/የተለየ (ንግ ልዩ)

ጕልድፍ አለ፡ ድንዝ አለ/ዶለዶመ

ጕልድፍድፍ፡ ፍጹም ዱልዱም (አፈ)

ጕልጕል፡ የተጐለጐለ/የተበላሸ ልቃቂት

ጕልጐላ/ጕልጓሎ፡ ቍንጫቶ/ለቀማ (የመጐልጐል ሥራ)

ጕልጓይ፡ ንፍጣም/መንጐላም (ወይም ንፍጥ የተናደ ፈትል)

ጕልጥምት (ቶች) በመሬት ውስጥ ያለ ደረቅ የንጨት ቅሬታ

ጕሎ በቁሙ፡ ጐላ

ጕሎ (ዎች) (ትግ. ጕልዕ) የዛፍ ስም (ብጫዊ ፍሬው ቅባትና ዘይት የሚኾን ዕንወት) "ፍሬውም ጕሎ ይባላል መጠኑ ከእኸል ቅንጣት መብለጡን ያሳያል።"

ጕሎ (ጥሎ) ጕሎ፡ ብጫ መልክ ፈረስ "የራስ ዐሊ ፈረስ ስም (አባ ጕሎ)" (ተመልከት፡ ቦራን)

ጕመላ፡ እንደ ግመል መውጋት የማይችል ጐዳ በሬ (በጭራሽ ቀንድ ያላበቀለ በጋልኛ ሞግሎ ይባላል)

ጕመራ፡ መጐመር

ጉመር፡ የጕራጌ አገርና ነገድ (ከ፯ቱ ወንድማማቾች አንዱ)

ጉመሮ፡ የቀንጠፋ ዐይነት ዕንጨት

ጕመይ፡ የቀበሮ ዐይነት አውሬ

ጉማ (ጉማዕ) ሙዳ ሥጋ ቍራጭ (፩ነገ. ፲፮፡ ) (ተመልከት፡ ጐመተን)

ጉማ፡ የነፍስ ዋጋ፡(ተመልከት፡ ገመገመ)

ጉማ፡ የነፍስ ዋጋ/ገንዘብ ወይም ቁም ከብት "ጉማ ጋልኛ ነው በግእዝ ግን ታላቅ ጩኸት ማለት ነው።" "ጋልኛውም ቢኾን በቀንበር ተጠምዶ የሚደረገውን እግዚኦታ ያሳያል።"

ጉማ፡ የኦሮ ባላባት ነው

ጉማም፡ ጉም የሸፈነው ተራራ/ደን (ጉም የማይለየው ባለጉም)

ጕማራ፡ የወንዝና የቀበሌ ስም (በበጌምድር ውስጥ ያለ ዠማ)

ጕማሬ (ሮች) ወፍራም/ደንዳና/ታላቅ የባሕር እንስሳ (በዟይና በጣና የሚገኝ)

ጕማሬ፡ በበላበት የሚያራ አፍ ቂጡ (ዘፈንና ጨዋታ ነጋሪት ወዳድ የጕምር ዐይነት ክምር መሳይ)

ጕማሬ፡ ከጕማሬ ቈዳ ተጠርቦና ተሸልቶ የተበጀ ዐለንጋና አኰርባጅ (ተመልከት፡ ርኰትን)

ጕማርዮስ፡ የዛር አዛዥ (ብር ዐለንጋን ያስተርጕማል)

ጕማርዮስ፡ የጅን በሬ እንደ ጕማሬ በባሕር የሚኖር

ጕማጅ፡ ጕራጅ/ቍራጭ

ጉሜ (ጉማዊ) በብርና በወርቅ የተጌጠ ያንበሳ አንፋሮ (የነጭ ፍየል ሎፊሳ) "በጋልኛ ግን 'አንባር' ማለት ነው።"

ጉሜ፡ ሚስት ቤተ ሰብ "እልል በይ ጉሜ" እንዲሉ።

ጉሜ፡ አንፋሮ፡(ተመልከት፡ ጎመ)

ጉም (ጊሜ) ምድርን የሚያፍን የሚሸፍን ንድፍ መሳይ ነጭ ደመና (ከምድርና ከባሕር ላይ ወዳየር ወደ ሰማይ እየበነነ (እየተነነ) የሚወጣ)

ጉም ለበስ፡ ዝኒ ከማሁ (ጉም የለበሰ)

ጉም አለ፡ ለብቻው ተቀመጠ (ጉማ መሰለ ኰራ)

ጉም አስጎምጉም፡ ጉም ልጁ "አስጎምጉም አባቱ።" (ተመልከት፡ ጎመጎመን)

ጉም፡ ነጭ ደመና፡(ተመልከት፡ ጎመ)

ጉም፡ የሰው ስም (በ፰፻ ዓመተ ምሕረት የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ)

ጉምሩክ (ዐረ. ጅምሩክ) በዋና ከተማና በያገረ ገዢው መኖሪያ የተሠራ ቤት (የነጋዴና ያጣሪ የቸርቻሪ የመሸተኛ የሸቃጭ ግብርና ቀረጥ መቀበያ በግእዝ ምጽባሕ ይባላል)

ጕለታ፡ ተከላ/ጥምዘዛ (የጕልቻ)

ጕምር፡ የተጐመረ (ንፍ ኵሩ ኵራተኛ)

ጉምብራ፡ ዕንብርት፡(ተመልከት፡ ጕንብራ)

ጕምዘዛ/ጕምዛዜ፡ ምረት/ኩምጣጤ

ጕምዝዝ አለ፡ ጐመዘዘ

ጕምዠታ፡ ዝኒ ከማሁ

ጕምዡ፡ የጐመዥ ቋማጭ

ጕምዣን (ፍትወተ መብልዕ) ሥየታ ምኞት "ባገኘኹት ማለት።" (ተመልከት፡ ጕረሮን)

ጕምድ አለ፡ ቍርጥ አለ (ተጐመደ)

ጕምድ፡ የተጐመደ (ጕርድ ቍርጥ ዱሽ)

ጕምድማጅ፡ ዝኒከማሁ (የተጐማመደ)

ጕምድምድ አለ፡ ብጥስጥስ አለ

ጕምድምድ፡ ቍርጥርጥ/ጕርድርድ/ብጥስጥስ

ጕምጕም አለ፡ ጥቂት በጥቂት ቀስታ ተናገረ ስለ ቅርታ

ጕምጕምታ፡ ጒምጕም ማለት

ጕስማት፡ የጐን ላይ ምት

ጕስማዬ፡ ዘመን አመጣሽ ዘፈን ("የኔ ጒስም ማለት ነው።") "ጕስማዬ እንዳለ ሙዚቃ።"

ጕስም፡ የተጐሰመ/የተመታ ነጋሪት

ጕስምታም፡ ጕስምት ያለበት የበዛ በት ሰው

ጕስምት፡ እውክታ/ስርቅታ (የሆድ ዕቃ በትር)

ጕስር፡ እብቅ የመላበት የጥጃ ስልቻ (ጐፍላ እንበጣ)

ጕስቈላ፡ ክሳት/ጥቍረት

ጕስጕስ፡ የተጐሰጐሰ/የገባ/የተከተተ ጥቅጥቅ "የሜዳ ንስንስ የቤት ጕስጕስ" እን ዲሉ

ጕስጕሻ፡ የጭቃ የአበት ድብኝት (ዶቄት ማኖሪያ ወታቦ ቅጥልጥሉ ደልገን ይባላል)

ጕስጐሳ፡ ጐረሣ/ጥቅጠቃ/ጕትጐታ

ጕረሮ (ጕርዔ) በስተፊት በኩል ባንገት ውስጥ ያለ የመብልና የመጠጥ አሸ ንዳ (ሰፊ የሥጋ ቀሠም ምግብን ኹሉ ከአፍ ተቀብሎ ወደ ሆድ የሚያወርድ የነገር/የቃል/የድምፅ መውጫ ማለት ነው) (ተመልከት፡ መነዠኸ ብለኸ ምንዣኸን፡ ዐረዶ ብለኸ ታራጅን እይ)

ጕረሮኸን ይክፈትልኸ፡ ሰው ወደ ግብዣ ሲኼድ የሚነገር ቃል (በፈረን ጅኛ "ቦን አፐቲ" ይባላል)

ጕረንጆ፡ ያገዳ ስም (ጥቍሬታ ራሰ ብትን ተቀምጨ)

ጕረኖ የግልገል ቤት ጐራ

ጕረኖ (ዎች) በጭቃና በደንጊያ የተሠራ የግልገሎች የቡችሎች ቤት መከማቻቸው (ተመልከት፡ ጐረተን እይ የጐራ ዘር ነው)

ጕረኛ (ኞች) ባለጕራ/ጕራ ተና ጋሪ ፎካሪ (ይስሙልኝ ባይ ጕራ ወዳድ አንጀ በኛ አንቧታሪ አንፋሻሪ) "ጐረረና ቀረረ የገ ረረ ዘሮች ናቸው።"

ጕራ፡ ያልተፈጸመ ፉከራ/ዛቻ "ይህ ድብርቅ ዐይን እኔ ልጆቼን ከቈጥ እባጥ እያልኹ አሳደግኹና ለሱ መገበር ኾነን ቈይ ብቻ (አቶ ዐይጦ ድመትን)"

ጕራ፡ ፉከራ —(ተመልከት፡ ጐረረ)

ጕራማይሌ ወፍ ገረመ

ጕራማይሌ (ዎች) የወፍ ስም (ሰማያዊነትና አረንጓዴነት ያላት ሐር የምት መስል ወፍ የምታብረቀርቅ "ድንቃዊት ድንቅ ላቲ ማለት ነው።")

ጕራማይሌ፡ አንድ ዐለፍ የጥርስ ንቅሳት

ጕራሽ፡ አፍ የሚመጥነው ዳቦ እን

ጕራች (ኦሮ) ጥቍር ጠቋራ ፈረስ ሰው ወይም ሌላ ነገር

ጕራንጕር የጕር ጕር ጐራ

ጕራንጕር፡ የጕር ጕር (ዐባጣ ጐበጣ ወጣ ገባ ሥርጓጕጥ ደንጊያማ ስፍራ) " ስሯጽ ነው።"

ጕራዕ፡ በትግሬ ውስጥ በሐማሴን ክፍል ያለ አገር ("ጕር ከማለት ይሰማማል።") (ተመልከት፡ ጕራጌን ተመልከት)

ጕራጅ

ጕራጅ፡ ቍራጭ/ጕማጅ

ጕራጌ ( ጕራዕ) ምድረ ጕራዕ (ድንጋያም ምድር) "በትግሬ አውራጃ ያለ የጕራዕ አገር።"

ጕራጌ (ጎች) ከትግሬ ወረዳ ከጕራዕ መጥቶ በሺዋ የተቀመጠ ነገድ ( ወንድማማች) ባለብዙ ቋንቋ

ጕራጌ፡ ፯ቱ ክፍል የጕራጌ አገር " ቤት ጕራጌ" እንዲሉ "በዝርዝር ሲቈጥሩት ግን ነገዱና አገሩ እስከ ፳፭ ይደርሳል።"

ጕሬዛ (ዎች) ነጭና ጥቍር የዛፍ ላይ አውሬ (የጦጣና የዝንጀሮ ወገን ጠጕረ ረዥም ቈዳው በቤት ውስጥ በግድግዳ ላይ ይለጠፋል በወንበር ላይ ይነጠፋል) "ጥቍረቱን ንጣት ንጣቱን ጥቍረት የገረዘው (የቈረጠው) ማለት ነው።"

ጕሬዛዎች

ጕሬዝ (ዞች) የበሬ መጥሪያ ስም

ጕሬዝማ (ጕሬዛዊ) የጕሬዛ ዐይነት ወገን (መልኩ ጠጕሩ ጕሬዛ የሚመስል በሬ ፍየል በግ ወፈ ያሬድ)

ጕር (ሮች) የደንጊያ ክምር (ክምቹ ኣረንዛ ስብስብ ቍልል) "በግእዝ ጕርዕ = ይባላል" (ገድ. ተክ) (ተመልከት፡ ጕራጌን ዘንዶን ተመልከት)

ጕር በቁሙ፡ (ተመልከት፡ ጐራ)

ጕር ዐምባ፡ የጕር ዐምባ (መዠመሪያ ዐጢ ቴዎድሮስ የሸፈቱበት ቀበሌ ጕራም)

ጕር፡ ያገር ስም (ጕር ያለበት አገር ጕር ሥላሴ እንዲሉ)

ጕርማጅ፡ የዳቦ ቍራጭ (ታናሽ ፍል ለሰው የሚሰጥ የሚታደል ቍራሽ)

ጕርምስና፡ ጕልምስና

ጕርምርሜ፡ የጕርምርም ወገን (የኔ ጕርምርም)

ጕርምርም፡ ድምፀ ወፍራም ሰው

ጕርምርምታ (ነጐርጓር) የድምፅ ውፋሬ (ክፉ ነገር) (ኢዮ. ፴፯፡ )

ጕርሥ (ፋእም/ላእፍ) ቀለብ ምግብ መብል "ልብስ ጕርሥ" እንዲሉ

ጕርሥ አደረገ፡ ብልት አደረገ

ጕርሥ፡ የተጐረሠ አፍ ውስጥ የገባ እንጀራ ትንባኾ

ጕርሥ፡ የትምትም ኹለተኛ ስም

ጕርሦ፡ ከርትፍ/ሽምሽም (ያልደቀቀ ዶቄት)

ጕርሻ፡ የመብልና የገንዘብ ታናሽ ስጦታ (አፍ ሙሉ ቍራሽ ዳረጎት ማግ ዐረር)

ጕርብ (ቍቁዕ) የጐረበ/የረገበ (ቋጣራ ፈትል ቍርብጭ እጅ ያልደቀቀ የገብስ ፍትግ ንድፍና ኣኺዶ)

ጉርብትና፡ ዝኒ ከማሁ (ጎረቤት መኾን)

ጕርብጥ፡ የተጐረበጠ

ጕርብጥብጥ፡ የጕርብጥ ጕርብጥ

ጕርት፡ የተጐረተ (ጕር የደንጊያ ልል) (ተመልከት፡ ኰረተን ተመልከት የዚህ ዘር ነው)

ጕርና (ጕርን/ዐውድማ) የወተት ዕቃ መግፊያ መናጫ

ጕርናታም፡ ቅርናታም (የማይጣፍጥ ላሽ ወጥ)

ጕርናት፡ ቅርናት (መጥፎ ሽታና ዕም)

ጕርዝኝ (ኞች) የስፌት ስም (በንቅ ብና በቍና መካከል ያለ ስፌት አንዱን እንቅብ ኹለት ዐምስቱን ቍና አንድ የሚያደርግ መስፈሪያ)

ጕርደማ፡ ቍርጠማ

ጕርዳ በሺ፡ ማሕፀን ዳባሽ ወጌሻ (ጕርዳን የሚጠርግና የሚያስወግድ ሐኪም) "ጕርዳ ጋልኛ ነው ባማርኛም ይነገራል።"

ጕርዳ፡ ማርገዝና መውለድ የሚከለ ክል የሚያቈርጥ ማሕፀን ደፋኝኛ ዘጊ ውፋሬ

ጕርድ፡ ዐጪር ጠመንዣ

ጕርድ፡ ከወገብ በታች የተለበሰ ሴት ጥብቆ

ጕርድ፡ የተጐረደ ዛፍ ወይም ሌላ ነገር "ቀሪና ኻያጅ የደረሰኝ ወረቀት ከመካ ከሉ የተቈረጠ።"

ጕርድርድ አለ፡ ቍርጥርጥ አለ (ተጐ ራረደ)

ጕርድርድ፡ ቍርጥርጥ/ብጥስጥስ

ጕርዶ፡ የተፈተገ ስንዴ እንቅጥቃጥ (ዘፀ. ፳፱፡ ፪፡ ፪ነገ. ፯፡ , ፲፯) "ጕርዶ ግርድ ንም ያስተረጕማል።"

ጕርጅ (ጆች) የቤት ውስጥ ቅይድ ጓዳ ክፍል (በያይነቱ ዕቃ የሚቀመጥበት) (ዘፍ. ፮፡ ፲፬) "የንጉሥ ጐተራ እኸል ቤት ባለመከታ።"

ጕርጕራ፡ የነገድ ስም (በሐረርጌ አውራጃ ኢሳ በሚባለው ሱማሌ አጠገብ የሚገኝ የኦሮ ጐሣ አገሩም ጕርጕራ ይባላል)

ጕርጕጭ አደረገ (ሐዘዘ/ሠረበ) ማገ/ጠጣ (አጠጣጡ የሕፃን የበሽተኛ ነው)

ጕርጕጭ፡ ማማግ (ወደ ማንቍርት ማግባት አንድ ጊዜ ማጠጣት) "ጕር (ጕርዔ) ጕጭ ጕጡ ጕብሩ) ማለት ይመስላል ጕርዔ በግእዝ ጕረሮ ማለት ነው።"

ጕርጐራ/ጕርጓሮ፡ ብርበራ/ፍለጋ (የመጐርጐር ሥራ)

ጕርጥ (ጓጕንቸር) ዐይነ ትልቅና ከፍተኛ እንቍራሪት (ታናናሽ ዓሣና ያይጥ ዓሣ የሚውጥ የሚሰለቅጥ ድምፀ ወፍራም)

ጕርጥ ዐይን፡ ዐይነ ፈጣጣ ሰው

ጕርፍርፍ፡ የተጕረፈረፈ (ዝርክርክ ርፍርፍ)

ጕርፎ፡ ካመድ ጋራ የታሸ ሱረት (ሥንቀን ጠጪው በሞተ ጊዜ ካፍንጫው ሚጐርፍ)

ጕሸማ፡ ድሰቃ/ድሰማ

ጕሽ (ጻዕፍ) ድፍርስ (አተላውና አንቡላው ያልተለየ ጥሩ ያይዶለ ብጥብጥ ዝልል መጠጥ) (ግብ. ሐዋ. ፪፡ ) "ጕሽ ጠላ ጕሽ ጠጅ" እንዲሉ "ጕሽ የጌሾ ምስጢር አለበት።"

ጕሽም፡ የተጉሸመ (ጕጕም) "ጕሽም የጡ የቡጢ ምት በትር በጕሽም መታው" እንዲሉ

ጕበት፡ በሆድ ዕቃ መካከል ለብቻው ጕብ ብሎ የሚገኝ ለምለም ደማዊ ሥጋ (ዘሩ ጐባ ነው) (ስቈ. ፪፡ ፲፩)

ጕበትን አየ፡ በጕበት አረተ/ጠነቈለ (ሕዝ. ፳፩፡ ፳፩)

ጕበን (ኖች) በደንፍ/አንጸር በመቃን ላይ ያለ ከመቃን የተዋደደ አራት ማእዘን ዕንጨት። "መቃንና ጕበን" እንዲሉ።

ጕበኛ (ኞች) (ሰብአ ዐይን) ሰላይ/መርማሪ (ዘፍ. ፵፪፡ , ፲፩, ፲፮)

ጕባ ጐበበ

ጉባ (ኦሮ) ያገሰስ ዠርባ፡ መተኰሻ፡ ጐባጣ ብረት።

ጕባ (ዎች) / ቍባ፡ በምድር ላይ ያለ የመሬት ዕንብርት፡ ቍልልታ።

ጕባ፡ ከተስዐቱ ቅዱሳን አንዱ።

ጉባኤ (ገብአ) መስብሰብ፣ ስብሰባ፣ አሰባሰብ።

ጉባኤ ሐዋርያት፡ ቤተ ክርስቲያን።

ጉባኤ መላእክት፡ የመላእክት አንድነት።

ጉባኤ ቃና፡ የቅኔ ስም፡ መዠመሪያ ቅኔ፡ ባለ ሁለት ቤት፡ በቡልጋ ቃና በሚባል ቀበሌ የተወሰነ። ወይም (ቃና ጉባኤ) ጣዕም ያለው ቅኔ፡ የጉባኤ ጣዕም ኅብሮን ተመልከት።

ጉባኤ ነቢያት፡ የነቢያት ማኅበር።

ጉባኤ ነገረ ትርጓሜ አስተማረ

ጉባኤ ነጋሪ፡ ሊቅ፡ ታላቅ መምህር፡ ሰባኪ፡ አስተማሪ።

ጉባኤ፡ ሰርገኛ፣ ዱለተኛ፣ ገበያተኛ፣ ለቅሶኛ፡ ብዙ ሕዝብ፡ ሰራዊት (ዘፀ. ፲፯፡ )

ጉባኤ፡ የትርጓሜ ክፍል፡ ማንሻና ማረፊያ።

ጉባኤ፡ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበው የሚማሩት የብሉይ፣ የሐዲስ፣ የሊቃውንት የመጽሐፈ መነኮሳት ትርጓሜ። "አራቱ ጉባኤ" እንዲሉ።

ጉባኤ፡ ጉባይ፡ ዐውድ፡ አደባባይ፡ ሺንጎ፡ ታላቅ ተማሪ ቤት።

ጉባይ (ጉባኤ) እንደ ገበያ ብዙ ሕዝብ የሚሰበሰብበት ሸንጎ/ዐውድ/አደባባይ (ኢሳ. ፬፡ )

ጉባይ / ጐበኘ

ጉባይ፡ ስብሰባ፡ ክምችት

ጉባይ፡ የወንድና የሴት ስም።

ጉባዮች፡ ስብሰባዎች፡ ሸንጎች፡ አደባባዮች (ዘሌ. ፳፫፡ ፴፯፡ መክ. ፲፪፡ ፲፩)

ጕብ (ቦች) ግብ፡ ታላቅ የሸማ ጮጮ ከግራምጣ የተሰፋ እንደ ጕድጓድ ያለ።

ጕብ አለ፡ ተጐበለ፡ ቍጭ አለ፡ ተቀመጠ፡ እንደ ጕብ።

ጕብሰታም፡ የሚጐበስት (ሳላም/ጕንፋናም)

ጕብሰት፡ ክፉና ደረቅ ሳል (ከምች/ከነፋስ/ከብርድ/ኮፀሓይ የሚነሣ አክታ ቢስ)

ጕብታ፡ ቍጭ ማለት፡ መጐበል፣ መቀመጥ።

ጕብታ፡ ጕባ። "እጕብታው ላይ ተቀመጥ" እንዲሉ።

ጕብንጭር (ሮች) የሸማ መጠቅለያ የሚሰካበት በቀኝ የተተከለ ፈጣጣ/ሹል ዕንጨት፡ ወንዳወንዴ።

ጕብኘታ (ሕዋጼ) ጥየቃ፡ ስለላ (የመሳሰለ ሥራ)

ጕብኙ፡ የተጐበኘ፡ የተሰለለ።

ጕብዝና፡ ዝኒ ከማሁ፡ ጥናት/ብርታት/ጥንካሬ (ኢዮ. ፴፫፡ ፳፭፡ ምሳ. ፭፡ ፲፰)

ጕብጕባ፡ የስሚንቶ ዐይነት፡ ዐፈርየምድር ስሚንቶ፡ በሰንበሌጥ ፈንታ በአፈር ቤት (በእድሞ) ላይ የሚፈስ/የሚነሰነስ/የሚከዶን።

ጕብጕባት፡ ሽልማ፡ የጕብጕብ ሥራጌጥ/ሽልማት።

ጕብጕብ (ቦች) በጋሻና በለምድ ሳንቃ ወይም በዙሪያው ላይ ያለ ጌጥ፡ የጥንብራና የመጣብር ዐይነት።

ጕብጕብ፡ የተጐበጐበ አብሲት፡ የጉባባት ሊጥ/ቡሖ።

ጕብጓቢ፡ ዝኒ ከማሁ (ይህም እንደዚያው) ያብሲት ጭማቂ።

ጕብጠት፡ ጐባጣነት።

ጕብጥብጥ፡ ዝኒ ከማሁ፡ ሥርጓጕጥ/ዐባጣ ጐባጣ ድንጕርጕር

ጕብጭ፡ ፍላጻ በጐባጣ ቀስት የሚወረወር/የሚነደፍ

ጕቦ (ሕልያን) ፍርድን ለማጥመምና ሓሰትን እውነት ለማስመስል ሐሰተኛ ለዳኛ የሚሰጠው መማለጃ።

ጕቦ፡ መስጠት።

ጕቦኛ (ኞች) ጕቦ ሰጪና ተቀባይ፡ ጕሶ ወዳጅ።

ጕተታ፡ ስቦሽ

ጕተና፡ ያደገ የረዘሙ ጐፈሬ (፩ቆሮ. ፲፩፡ ፲፬)

ጕተና፡ ጐሚት (የብላጊ አበባ እጅግ የሚያምር ቀይ ደማቅ የሬት ዐይነት) "ጕተና አበባ" እንዲሉ

ጕተናማ፡ ጕተናም (ባለረዥም ጕተና)

ጕታ፡ ቍግ፡ ጐተነ

ጕታ፡ ከና ከቃጫ ከጥፍራንዶ ክርማ ከስንደዶ ከሳማ ከንሰት ከማንኛውም ጭረት የተበጀ ቍግ (የጅራፍ ውልብል ቢት ነፋስን በመጥለፍ የሚጮኸ ጕተና መሳይ)

ጕት ቅኔ ጐተተ

ጕትት፡ የተጐተተ (አዝጋሚ ዝግ ብሎ ኻያጅ የእባብ የዘንዶ ያዞ የዔሊ ዐይነት)

ጕትቻ፡ ከወርቅና ከብር ከንሓስ ከሌላም ማዕድን የተሠራ የዦሮ ያፍን ጌጥ

ጕትቻ፡ የነገር ሳቢያ ንዝንዝ ውዝ ግብ

ጕትን፡ ብጥር ምይድ ጠጕር

ጕትዬ ቍንጯም ወፍ፡ ተነ

ጕትዬ፡ ቍንጪም ወፍ እንድርማ ሚት (ጕተናም አሞራ)

ጕትጐታ፡ ንቅነቃ/ውትወታ

ጕቶ

ጕቶ የግንድ ቅሬታ ገታ

ጕቶ፡ የተቈረጠ ግንድ (በምድር ላይ የቆመ የንጨት ጕራጅ "ማዶጉን መቈረጥ የጌታው።")

ጕቺ (ኦሮ) ሰጐን በሩቅ ሲያይዋት ጕቾ መሳይ

ጕች አለ፡ ቍጭ አለ (ተቀመጠ)

ጕች፡ ቍጭ መቀመጥ

ጕቾ፡ የተጐቸ (ክምር ዘመመን ልል የእኸል የሣር)

ጕነት፡ ንሮሽ፡(ተመልከት፡ ጓነ)

ጕነጣ፡ የመጐነጥ ሥራ (ንቅነቃ)

ጕነፋ፡ ዐጠባ/ዕጀላ/ጠረባ/ድጐሳ

ጕኒና፡ ከጠጕር ከፈትል ከሣር ከሰሌን የተበጀ የተቈነነ ቍንን ቆብ

ጕናጕኒት፡ በደብረ ብርሃን እቅራቢያ ያለች አገር (ኮባ ያለባት ጕናጕናሚት መስኗሚት ማለት ነው)

ጕናጕና፡ ቅጠለ ድርብርብ ንብብር ኮባ (ጭረቱ (ቃጫው) የሚጐነጐን)

ጕንም፡ ጕንጪ ትልቅ ሰው

ጕንቍል፡ የጐነቈለ (የበቀለ በቈልት የተነከረ ዐተር ባቄላ ሽንብራ)

ጕንብስ፡ ቅጽልና ጥሬ

ጕንብራ፡ ዕንብርት፡ (ተመልከት፡ ጐበረ)

ጕንዳን (ኖች) (ጐነደ) ጥሬ እኽል ለቀለቡ ባፉ እየያዘ ወደ ጕድጓድ የሚያገባ/የሚከት/የሚጐደጕድ ጥቍር ተንቀሳቃሽ (እንዳይነቅዝበት እየከካ በውጭ በፀሓይ ላይ የሚያሰጣ አግዝ (ገብረ ጕንዳን)) "በግእዝ ቃሕም ይባላል።"

ጕንዳን፡ መልከ ቀይ ማረ በላ ፈጣን "የስሙ ምስጢር ጐናዴነት ነው።" "ከነዚህም አግዝ ደገኛና ቈለኛ ተናካሽ ደገኛ ሻሻቴና ማረ በላ ቈለኞች ናቸው።"

ጕንዳን፡ ተናካሽ/ተቈናጣጭ (ሥጋና ቅባት ወዳድ)

ጕንዳን፡ ዘማች/ሻሻቴ/ችስችሳ/ምሥጠ በል

ጕንዳጕንዲት (ትግ. ጐዳጕዲ) ዐጤ ዮሐንስ ቱርክን ድል ያደረጉባት ጐድጓዳ ስፍራ

ጕንድል (ሎች) የተጐነደለ (ቍላው የወጣ ኵልሽ ስልብ ዶሮ እያስካካ እንደ እንስቷ ከነፋስ ዕንቍላል የሚወልድ የሚጥል)

ጕንድሽ (ጐነደ) እጁ ካንባር ያው የተቈረጠ ሰው (ማቴ. ፲፰፡ )

ጕንድሾች፡ እጀ ቍርጦች (ሉቃ. ፲፬፡ ፲፫, ፳፩) (ተመልከት፡ ኰነተሽ ብለኸ ኵንትሽን እይ)

ጕንዶ (ዎች) (ግንዶ) ከግንድና ከቀንድ የተበጀ ጥንታዊ የማር መስፈሪያ (ቀንዶ) "ጕንዶ ማር እሰጥ" እንዲል ተጋች

ጕንጕናት፡ የጕንጕን ሥራ

ጕንጕን፡ ሽሩባ (መሳ. ፲፮፡ ፲፫, ፲፱)

ጕንጕን፡ የተደራረበ/የተነባበረ (ኢዮ. ፵፡ )

ጕንጕን፡ የተጐነጐነ/የተወሰበ (ጠፍር ገመድ ሽቦ ፈትል ጠጕር ዥማት ሢር ሰርዶ ሰሌን ትት ቍንን)

ጕንጕን፡ ድፍድፍ

ጕንጕኖች፡ የተጐነጐኑ ገመዶች ጌጦች (፩ነገ. ፯፡ ፵፩, ፵፪)

ጕንጐና፡ ጠለፋ/ቋጠራ/ድፍደፋ

ጕንጥ፡ የተጐነጠ/የተነካ

ጕንጨ፡ የሰው ስም "ጕንግም" "ጕንጨ የኔ ጕንጭ።"

ጕንጨፋ፡ ሽምጠጣ/ዥምገጋ

ጕንጩን ወጠረ፡ ነፋ (በውሃ በትንፋሽ)

ጕንጪት፡ ጕንጫሚት

ጕንጭ (መልታሕት) ያፍ ጓዳ (የምግብ የመጠጥ መያዣ ቋት) (ኢሳ. ፶፡ ፮፡ ሰቈ. ፩፡ )

ጕንጭ አለ፡ ካፍ ወደ ጕንጭ ከጕንጭ ወደ ጕረሮ አገባ ውሃን

ጕንጭና ጕንጭ፡ ባፍ ግራና ቀኝ ያሉ ኹለቱ (ማሕ. ፬፡ ፫፡ ፭፡ , ፲፫)

ጕንጮች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ (ዘዳ. ፲፰፡ )

ጕንፋት፡ ዕጥበት/ዕጅላት (ሕንጻ ቅርጽ! ድጕሰት ድጕሳት)

ጕንፋን (ትግ. ጕንፋዕ) የበሽታ ስም (በክፉ ሽታና በብርድ የሚነሣ የሚያስል የሚያስነጥስ ትኵሳታም ንፍጣም ሕመም እስከ ቀን ከጭንቅላት ንፍጥን የሚያወርድ ባፍንጫ የሚያንቈረቍር ከዚያ በኋላ የሚበስል)

ጕንፍ፡ የተጐነፈ (ሸክላ የዘንጋዳ ጠቈርት ጥርብ የመጣና ገበታ ድጕስ)

ጕኝር፡ የተጐኘረ (በስልቻ የተመላ ዘኬ)

ጕዉ፡ ጕብሯ (የርሷ ጕጥ)

ጕዛ፡ ያሞራ ስም (ቀደ)

ጕዝጕዝ አለ፡ ተጐዘጐዘ/ንስንስ አለ

ጕዝጕዝ፡ የተጐዘጐዘ/የተነሰነሰ ንስንስ (የተሿሚ ማረፊያ ቤት)

ጕዝጐዛ፡ ብተና/ምንዘራ/ንስነሳ።

ጕዝጓዝ (ዞች) (ጐዘጐዝ) ደረቅና ርጥብ ሣር

ጕዞ ፍታት፡ የጕዞ ፍታት ባለ፯ ማረፊያ

ጕዞ፡ የግሥገሣ ተቃራኒ (ዘገምታ/ቀስታ ቀስ ዝግ ብሎ መኼድ) "ነገሥታትና መኳንንት ጧት ከ፪ ሰዓት እስከ ሰዓት የሚያደርጉት ርምጃ።"

ጕያ፡ የጭንና የጭን ውስጥ መካከል። "እናት ጕያ" እንዲሉ። "ጕያ በግእዝ ሽሽት ማለት ስለ ኾነ የሕፃን መሸሻና መደበቂያ መኾኑን ያስረዳል። አንተ ልጅ ዛሬ እናትኸ ጕያ ብትገባም አታመልጠኝም" እንዲል ባላገር (ተረት) "ወዳጅ ይመጣል ከራያ ጠላት ይወጣል ከጕያ" (፪ሳሙ. ፲፭፡ ፲፪)

ጕያ፡ ያገር ስም (በተጕለት ውስጥ በታችኛው ወግዳ ባሻገር ያለ አገር) "ሽሽ ሩጥ ማለት ነው።"

ጕይ ማጋ (ጕይማጋ) ማጋ

ጕይ፡ ወደ ማጋ ሽሽ "አቀማመጡ የማግ ልታቂት የሚመስል ባናቱ የጊዮርጊስ ታቦት ያለበት ረዥምና ሾጣጣ ዐምባ የጕይ ተራራ ወደ ሰማይ የተንጠራራ።" "ጕይ ማጋ ጊዮርጊስ" እንዲሉ። (ተመልከት፡ አንጕይንና እንጕይን ሚጋን)

ጕደል

ጕደሪ፡ የመከር ዐውሎ ነፋስ (ክረምት ውጭ ከሰሚን የሚነፍስ) "ሥሩ 'ጐደራ' ስለ ኾነ ጩኸቱን ያሳያል።"

ጕደፈደፈ፡ የጐደፈ ድርብ ተኵለፈለፈ

ጉዲት (ጕዲት/ይሁዲት/ዮዲት) በ፰፺ . የኢትዮጵያን መንግሥት በተንኰሏ ነጥቃ ዓመት ስለ ነገሠችና ከርሷ በፊት የነበረውን እውነተኛውን የሳባ የግእዝ ታሪከ ነገሥት እያቃጠለች ባላባቶቹን

ጕዳሌ፡ አእምሮ የሚያጐድል በሽታ ወይም ጋኔን። "እሱ ራሱም ከመላእክት ማዕርግና ቍጥር መጕደሉን ያሳያል። ደስክ ወጕዳሌ" እንዲል ዐይነ ጥላ

ጉዳም (ጕደኛ) (ኞች) ድንቀኛ/ታምረኛ/ጉድ አድራጊ/ባለጉድ ነውረኛ

ጕዳተኛ (ኞች) ራብተኛ/ችጋረኛ/ከሲታ/ዕርዝተኛ።

ጕዳት (ጕድዐት) ችጋር/ራብ/ክሳት/ንጣት (ኢሳ. ፶፱፡ )

ጕዳይ (ዮች) የጐደለ። "ለ፯ ሰዓት ሩብ ጕዳይ እመጣለኹ።"

ጕዳይ ፈጻሚ፡ ነገር ጨራሽ።

ጕዳይ፡ መላ/ረባ/ጠቀመ/ፈየደ።

ጕዳይ፡ ቁም ነገር (፪ዜና. ፱፡ )

ጕዳይ፡ ተፈላጊ ሥራና ነገር። "አንተ ዘንድ ጕዳይ አለኝ" እንዲል ወዳጅ ለወዳጁ።

ጉዳጉድ፡ የጉድ ጉድ (ፈናፍንት)

ጉዴላ/ጕዴላ፡ በዳር አገር በከንባታ ወረዳ ያለ የነገድና ያገር ስም (ተመልከት፡ ዘነበን)

ጉድ (ዶች) ተኣምር/ግሩም/ዕጡብ/ድንቅ (ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ ዐዲስ ነገርና ሥራ)

ጉድ አወጣ፡ የሰውን ነውር ገለጠ። (ተመልከት፡ ጐመደን)

ጉድ አደረገ፡ ሰረቀ/ኣታለለ

ጕድ ፈላ) ወጣ ተገለጠ

ጉድ፡ ኀላፊ ወሬ። (ግጥም) "እቴ ብንጋባ ምነው፡ ጉድ አንድ ሰሞን ነው።"

ጉድ፡ ነውር/መጥፎ ነገር (ከሰውና ከእንስሳ ሆድ የሚወጣ/የሚወሰድ ወሬውን ሊሰሙት ኹናቴውን ሊያዩት የማይገባ) "ጉድ ኾነ! ጉድ ፈላ/ጉድ ተወለደ/ጉድ ታየ፡ እከሌ በገድ ወጣ" እንዲሉ። "በቃለ አጋኖ ሲነገር 'ወይ ጉድ! ወይ ጉዴ! ላግባሽ አለኝ ነጋዴ!' ይላል።"

ጕድለት፡ ጐደሎነት/ሕጸጽ (የጠባይ ስሕተት)

ጕድል (ጐዲል) እንስ/ቅምጥል

ጕድል አለ፡ እንስ አለ፡ ቅምጥል አለ፡ ጐደለ/ተቀመጠለ።

ጕድሩ፡ ያገር ስም (በወለጋ ክፍል የሚገኝ አገር) "ጕድሩ ቢጋልኛ ቍንጮ ማለት ነው።"

ጕድባ (ቦች) ዕርድ/ፈፋ (ሰው/ብይም/ውሃ ያረያው/ያጐደጐደው)

ጕድብ፡ ስለትና ሹለት ያለው ዶማ (ግእዝ)

ጕድኝ (ኞች) የቅጠል ስም (በወንዝ ዳር የሚበቅል የደጋ ቅጠል ከብት ሲበላው የሚገድል) "በቍስል ላይ ቢያስሩት አለልክ ጠዝጥዞ ነዝንዞ ልብ ይነሣልና ስለ ዚህ ጕድኝ ጕደኛ ማለት ይመስላል።"

ጕድጕድ አለ፡ በጓዳ ሮጠ/ተንጐዳ

ጕድጕድ አለ፡ ጐደጐደ/ተሠረጐደ።

ጕድጕድ፡ ሥርጕድ።

ጕድጕድ፡ ሮጥ ሮጥ።

ጕድጓድ (ዶች) የተማሰ/የተቈፈረ/የተጐደበ (ያውሬ/የእህል/የሬሳ ቤት) ውሃ የሚቀዳበት ዐዘቅት፡ ሸማኔ ሸማ የሚሠራበት።

ጕድፈራ፡ ቍፈራ/ምንቀራ/ብተና።

ጕድፋም፡ ጕድፍ ያለበት/የገባበት እድፋም

ጕድፍ (ፎች) (ሐሠር) የሣር/የገለባ/የንጨት/የቅጠል/የደንጊያ/ያፈር ድቃቂ ግባስ (፩ቆሮ. ፬፡ ፲፫) "ዝንብ ትንኝ በምግብና በመጠጥ ውስጥ ገብቶ የሚገኝ ማንኛውም ነገር።"

ጕድፍ መጣያ፡ ቍሻሻ ማኖሪያ ስፍራ (ኤር. ፳፭፡ ፴፫)

ጕድፍ፡ ፍግ/ፋንድያ/በጠጥ/ዐመድ/የቤት ጥራጊ የፈሰሰበት ደጅ ቀዬ አረዳባዶ "እልፍ የመምሬን ጠላት አንጠልጥሎ ወደ ጕድፍ እንዳይመለስ በብረት ቍልፍ" እንዲል ተማሪ

ጕዶ፡ አፋ ጩቤ/ማረጃና መጕጃ ማለት ነው።

ጕጆ፡ የዛፍ ስም (የግራዋ ዐይነት ዕንጨት)

ጕጉ (ጕጉእ) የጓጓ/የከጀለ/ጕምዡ።

ጕጕ()

ጕጕ() (ቶች) (ጕጕእት/”/ጕጋ) ስትጮኽ የምትቸኵል የሌሊት አሞራ (ድመት መሳይ) "ሌሊት ቀኑ ቀን ሌሊቱ በጩኸቷ ጐትት የምትል ስለዚህ ባላገሮች 'ሰው ይሞታል' ይላሉ" (መዝ. ፻፪፡ )

ጕጕለት፡ የደም መርጋት/ጓጓላነት

ጕጕማት፡ ቀላል ውግታት/አወጋግ

ጕጕም፡ የተጐጐመ/የተወጋ (ልትም ውግ)

ጕጕት (ጕጓኤ) ክጀላ/ሥየታ/ጕምዠታ/ፍላጎት።

ጕጕት፡ አሞራ፡ ጓጓ

ጉጉግ፡ ኣሞራ (ያሞራ ስም) (ዘሌ. ፲፩፡ ፲፮)

ጉግሳ፡ የሰው ስም (የጁዬ ጉግስ ዐዋቂ/ባለጉግስ/የጉግስ ጌታ ማለት ይመስላል) "ጉግሳ ኣርኣያ" እንዲሉ።

ጉግስ (ጎግ) የጨዋታ ስም (የፈረሰኞች ጨዋታ የጦርነት ምሳሌ - ማሸነፍና መሸነፍ/ማሳደድና መሻሽ በዘንግ በሸንቦዬ መውጋትና መወጋት ያለበት)

ጕጐማ፡ ልተማ

ጕጠታፍ (ጕጠት አፍ) ሹላፍ ነገረኛ በነገሩ ሰውን የሚነካና የሚጐዳ ክፉ ሰው

ጕጠት (ቶች) (ጐጠየ) በእሳት የጋለ ብረት መያዣ መቈንጠ በስተፉ በምስማር የታጋጠመ መንታ ብረት

ጕጠት፡ (መውፅኤ ዐይን መጐሥሠ ስነን)

ጕጠት፡ ችንካር መንቀያ ፈቸል

ጕጣ (ቍጥ) ዕላቂ ማረሻ

ጕጣ፡ ንአስ እስኪት

ጕጣ፡ ዕላቆ ማረሻ፡ ጐጠጐጠ

ጉጣ፡ ዕላቆ/ማረሻ

ጕጣም፡ ጕጥ ያለው ዕንጨት እጅ ባለጕጥ

ጕጣጕጥ፡ የጕጥ ጕጥ

ጉጥ ጕብር፡ ጐጠጐጠ ጕጥ

ጕጥ፡ የንጨት ዐይን፡ ጐጠጐጠ

ጕጥ፡ ጕብር የንጨት ዐይን "በስተውስጥ ዐብጦ የደረቀ የውስጥ እጅ ሥጋ የድር ቋር።"

ጕጥር፡ የተጐጠረ (ጕስር/ጕኝር)

ጕጥጐጣ፡ መዘዛ/ነቀላ።

ጕጦች፡ ጕብሮች/ቋሮች

ጕጭ፡ ማንቍርት

ጕጭ፡ ማንቍርት፡ ጐጠጐጠ

ጕጭማ (ሞች) የጕጭ/የዶማ ዕላቂ ብረት

ጕጮ፡ ዐጪር ሣር/ጠጕርጤፍ

ጉፋ፡ የደጋ አባሎ (ፍሬውን አሳርሮ ከቅቤ ጋራ ቢቀቡት ቅጠሉን ዘፍዝፎ ብልትን እንዳይነካ ተጠንቅቆ ቢታጠቡበት ለዕከክ መድኀኒት ይኾናል)

ጕፋያ (ዮች) (ዕብ. ጉፍ ሥጋ) ያልሠባ/ያልጮመየ ቀይ ሥጋ ወይም በሬ

ጉፍታ፡ የስላም ሴት ራስ ማሰሪያ ቀለም የገባ ወይም ቅቤ ጠገብ ጨርቅ የጠጕር መሸፈኛ (ተመልከት፡ ኩፌትን እይ)

ጕፍጥጥ አለ፡ ጭብጥ አለ

ጕፍጥጥ፡ ዝኒ ከማሁ

ጊሆን፡ የደጋ አባሎ (ጉፋ)

ጊሚራ፡ በከፋ ክፍል ያለ የሻንቅላ ነገድና አገር (ተመልከት፡ ሺዋን)

ጊሚሮች፡ የጊሚራ ሰዎች

ጊኒ (ዐረ. ጀኒህ) የወርቅና የወረቀት ገንዘብ (በምንዛሪ ያንዱ ዋጋ ካሥር ብር ይወጣል ይወርዳል) "የምስር የንግሊዝ የቱርክ ጊኒ" እንዲሉ።

ጊኒ፡ ያገር ስም (አሳግርት አጠገብ ያለ ወረዳ) "ጊኒ አገር" እንዲሉ

ጊንር፡ በባሌ ክፍል ያለ ተራራ

ጊንጥ፡ በዥራቱ የሚነድፍ ባፉ የሚነክስ ባለ፯ ክርክር መርዛም ተንቀሳቃሽ የምድር አውሬ (ዘሩ ጐነጠ ነው) (ዘዳ. ፰፡ ፲፭) "ሴትና ጊንጥ በቂጥ" እንዲሉ

ጊንጦች፡ ተናዳፎች/መርዘኞች (የክፉዎች ሰዎችና ያጋንንት ምሳሌዎች) (ሕዝ. ፪፡ )

ጊዜ

ጊዜ

ጊዜ

ጊዜ

ጊዜ (... ጊዜ) ዐቢይና ደቂቅ አጋባብ "በን ከአንቀጽ ጋራ አስቀድሞ ይነገራል።" (ማስረጃ) "ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ፀሓይ ጨለመ።" ደቂቅነቱንም "በኖኅ ጊዜ በአብርሃም ጊዜ" እያለ ያሳያል። (ተመልከት፡ ባልን)

ጊዜ (ዎች) ዘመን/ዓመት/ወር/ቀን/ሰዓት/አፍታ

ጊዜ አለው ለሰው፡ ዕድሜ ካላነሰው (የባሪያ ስምና መልስ ይሾማል ያገኛል ይከብራል ማለት ነው)

ጊዜ አለጊዜ፡ ጨለማ ሌሊት ውድቅት ዐጕል ሰዓት

ጊዜ አደረሰ፡ አቍጣሮ አደረገ/ጸለየ

ጊዜ፡ ፀሓይ ሳለ ሳይመሽ ሳይጨልም "እንግዳ በጊዜ መጣ።" ቅጽል እየቀደመው ሲነገር "ያን ጊዜ ሌላ ጊዜ እንደግዜ ኹለግዜ" ይላል "ጊዜው ጊዜዋ" እያለ እስከ ይዘረዝራል።

ጊዜዋ ዕፅ፡ ግጃዋ

ጊዜዋ (ጊዜሃ) ያች ጊዜ/የርሷ ግዜ/የርሷ ዘመን

ጊዜው (ጊዜሁ) ጊዜ/የርሱ ጊዜ

ጊያ ቍልልታ (ተመልከት፡ ጐትን የዚህ ዘር ነው)

ጊዮርጊስ፡ የሰው ስም (የጽርእ ሰው በልዳ የተወለደ ሰማዕት ባለዐምባላይ ፈረስ የሰማዕታት አለቃ ቢሩታይትን ከደራጎን አፍ ያዳነ) "ትርጓሜው ዐራሽ ገበሬ ማለት ነው ይላሉ።" (ተመልከት፡ አባ)

ጊዮርጊሶች (ጊዮርጊሳውያን) የጊዮርጊስ መቅደስ አወዳሾች ካህናት

ጊደራች፡ በይፋት ውስጥ ያለ አገር።

ጊደር (ሮች) አውራ ለመሸከምና ለመጠቃት ዘር ለመቀበል የምትችል ድርስ ከብት (፩ሳሙ. ፲፬፡ ፴፪) "በጕራጌ 'ጐበዝ' ትባላለች።"

ጊድረኛ፡ ተንኰለኛ/ጥመመኛ።

ጊድራ (ኦሮ) ተንኰል/ክፋት/ጥመት

ጊጋር፡ የሰው ስም (ሰማዕት፡ እመቤታችን በተሰደደች ጊዜ ሥንቅ ሰጥቶ የሸኛት የሶርያ መስፍን)

ጊጋር፡ ያንጥረኛ ወረንጦ መቈንጠጫ

ጊጤ (ዎች) (ጐጠየ/ጋየጸ) በሹል ዘንግ የሚወጋ (ቍልቋልና የእንዶድ ወይም የሬት ሥር) "ጊጤ በግእዝ 'ቃፍ መጠራ' ይባላል።" "እንደ ይላማ የጦር አወራወርና አወጋግ ልጆች ይማሩበታል "

እነት አንድጋ

ጋለ ("ተኰሰ ተቃ ጠለ አለ ሉባ ማለፊያ ብርቱ ልጅ ፈጣንና ቀልጣፋ ማለትንም ያሳያል ሉባ ") ("ኦሮ")

ጋለ (ጕሒል/ጐሐለ) (ዕብ. ጋሓል) ጋመ/ሞቀ/ሠማ/ተኰሰ እሳት መሰለ (ተመልከት፡ ጋየን ከዚህ ጋራ አንድ ነው)

ጋለ፡ ከበረ/ገነነ "ያቶ እከሌ ቤቱ ግሏል።"

ጋለበ/ጓለበ፡ ሸሸ/በረረ/ሮጠ/ፈረጠጠ/ወነበደ/ሸመጠጠ (በፈረስ/በበቅሎ ተቀምጦ ቂጡን ገልቦ ሰው ዥራቱን ጭራውን ለብሶ ከብቱ)

ጋለባ፡ ሶምሶማ/ሽምጥ (ተረት) "ልባልማ ታጥቆ ዐዛባ ሱሪ አውልቆ ፈረስ ጋለባ።"

ጋሊት፡ ብረት፡(ኦሮ)

ጋል (ግሒል) መጋል

ጋል ጋል አለ፡ ባለማቋረጥ ኀይለ ቃል ተናገረ

ጋል፡ መኻል እጅ ውስጥ እጅ (ገላ ጠፍጣፋ ማለት ነው) (ተመልከት፡ ገለለን)

ጋልማ፡ ውስጥ እጅ፡(ተመልከት፡ ጋል)

ጋልማ፡ ዝኒ ከማሁ (የጋል) "ፈረንጆች 'ጋሌ' ይሉታል።"

ጋመ (ግሒም/ግሕመ) ፋመ/ጋለ/ሞቀ/ተኰሰ/ተቃጠለ "ትግሬ ግን 'ገሐመን ጠፋ' ይለዋል መክሰልን መጥለስን ያሳያል።" (ተመልከት፡ ሠማን)

ጋመረ፡ አደገ፡(ተመልከት፡ ገበረ)

ጋመረ፡ አደገ/ጐለመሰ/ጠና

ጋመረች፡ ዘር ለመቀበልና ለማርገዝ ደረሰች/ጠናች (ልጅነቷ ዐለቀ ተፈጸመ) "ጋመረች አሳጣች ከማለት ይሰማማል።"

ጋመን (ጋበን) ግመት ሐሩር ሙቀት ወበቅ

ጋመኛ፡ የሜዳ ስም (ባንኮበር ክፍል ያለ ስፍራ)

ጋሙዳ፡ ራብተኛ ችጋራም (በገ ፈጅ ቍና ፈጅ)

ጋሙድ፡ ራብ አንዠት የሚገምድ የሚያጥመለምል

ጋሚ፡ የሚግም/የሚፍም ዕንጨት ኵበት ከሰል

ጋሚቶ፡ የማሽላ በሶ (ኑግና በርበሬ ያለበት ሻሜት የፈረሳቤት መዳኒት)

ጋማ (ሞች) የግመል/የፈረስ/ያህያ/የበቅሎ ማዥራት ጠጕር ወይም ጭራ

ጋማ ከብት፡ (የጋማ ከብት) ፈረስን አህያን የመሰለ የቤትና የዱር እንስሳ (ኣውሬ) "ያውሬው ከብትነት ተይዞ ለማዳ ሲኾን ነው።"

ጋማ፡ የገብስ ስም "ጋማ የሚመስል ገብስ።"

ጋማ፡ የፊደል ስም "ገ።" (ተመልከት፡ ገመለ ብለኸ ገምልን)

ጋማ፡ ግመል (የቤት እንስሳ) "አልፋ ጋማ" እንዲል ጽርኣዊ ፊደል።

ጋማማ/ጋማም፡ ብዙ ጋማ ያለው ባለጋማ "አንበሳ ጋማማ" እንዲል መስተዤርት

ጋማዊ፡ የወንድና የሴት ልጅ ጠጕር

ጋሜ (ትግ. ጋማ) ገርዳሳ (ተመልከት፡ ጉሜን እይ ጎመ)

ጋሜ (ዎች) መካከሉ ተላጭቶ በራስ ዙሪያ ያለ እንደ ጋማ የቆመ

ጋሜ፡ የዛፍ ስም (ደጋን የሚኾን ዕንጨት ጋሜ ያሠኘው መጕበጡ ነው)

ጋሜ፡ ጋሜ ያለው ባለጋሜ ታናሽ ልጅ አሽከር

ጋምጨ፡ ጅር የሌለው ዝንጀሮ (ስጥ የሚቀማ ቢይዙት የሚገምጥ ቦለዴ)

ጋሰሰ፡ ነቀለ/ጋፈፈ/ደፈረ

ጋረ (ግዒር/ገዐረ) ተጨነቀ (የጭንቅ ጩኸት ጮኸ ጣረ አለቀሰ) (ተመልከት፡ ገረረን ተመልከት)

ጋረኛ፡ የተጨነቀ/ጣረኛ

ጋረኛነት/ጋረኝነት፡ ጣረኝነት

ጋረደ (ገልዶ/ገለዶ) ከለለ/ጠለለ/ሸፈነ/ሰወረ (መከተ ዘረጋ) (ተመልከት፡ ቀየደን እይ)

ጋረዴ፡ ጋረደው (የሰው ስም "ክልሌ ከለለው ሰወረው ማለት ነው።")

ጋረድ፡ ዝኒ ከማሁ

ጋረጠ (ጐረጸ) ወጋ/ሰካ/ሻጠ/ተከለ/ቀደደ/ፈቃ/በጣ/ቈራ

ጋሪ (ዎች) በመንኰራኵር የሚኼድ (በቅሎ ፈረስ ግመል ባቡር የሚስበው የሚጐትተው የሰው መቀመ፵ የዕቃ መጫኛ ከብረት ከሳንቃ ባጐበርና በቤት አምሳል የተሠራ ሠረገላ ፪ና - ከዚህም በላይ እግር ያለው) "ዘሩ ገረረ ነው።"

ጋሪ (ገዓሪ) የጋረ/የሚግር (ጯኺ)

ጋሪባልዲ፡ የምድርን መዞር የፀሓይን አለመዞር የተናገረ የጣሊያን ፈላስፋ (እንደ ፈረንጅ አቈጣጠር በ፲፰፻፯ .. ተወለደ እስካ፲፰፻፹፪ .. ነበረ)

ጋሪያታሞ፡ ባለጋሪያት (ጯኺ ቍጡ)

ጋሪያት ቍጣ፡ ጋረ

ጋሪያት፡ ቍጣ/ብስጭት

ጋራ (ምስለ) አንድነት = ማኅበር ሱታፌ ጭምር (ዘዳ. ፳፡ , ፫፡ ማቴ. ፭፡ ፳፬) " በማድረጊያነት በቅጽልነት በመነሻነት ቀድመው እየገቡ ይሰማሙታል"

ጋራ አንድነት፡ (ተመልከት፡ ገራ (ገርዐ))

ጋራጅ (ጆች) የጋረደ/የሚጋርድ አሽከር (ከላይ ሰዋሪ "አንጣፊ ጋራጅ" እንዲሉ)

ጋራጭ፡ የጋረጠ/የሚጋርጥ (ወጊ በጪ)

ጋሬ (ዎች) (ገዓራዊ) የዘንጋዳና የገብስ ቅይጥ መናኛ እንጀራ (በመያዣ ሥር አስቀድሞ የሚጣል የገበታ ጕዝጓዝ ጥሮ ግሮ የሚበላ ማለት ነው)

ጋሬ (ገዓርየ) ጩኸቴ (የኔ ጩኸት ጋሬ የወፍጮውንም ድካምና እምምታ ያሳያል)

ጋሬዳ (ግዝእ) ጐዶ/ውርርድ (የዋዛ ፈዛዛ መብል መጠጥ ዳስ ተጥሎ ቅጠል ተጋርዶ "ነገ ባንዱ ቤት ተነግ ወዲያ በሌላው ቤት የሚበላ ድኻ አይቀምስሽ ምግብ ርኩስ ማኅበር" (ዘዳ. ፳፩፡ ))

ጋሬጣ፡ ሥንጥር/ሥንጣቂ (የግራጭ (ዣርት) ወስፌ እሾኸ እግርን ልብስን የሚ ቀድ የሚሸረክት)

ጋሬጣ፡ አፈኛ/ነገረኛ/ክፉ ሰው

ጋር (ገዓር) ጭንቅ ጩኸት ጣር (የመከራ ድምፅ)

ጋርኖ፡ በበጌምድር ውስጥ ያለ ተራራ ("አርኖ ጋርኖ" እንዲሉ)

ጋርዱላ፡ ያገር ስም (በኦሮ ቤት በገሙ ክፍል ያለ አገር)

ጋርዱሎች፡ የጋርዱላ ተወላጆች

ጋሸበ፡ አደገ/ረዘመ/ወደቀ/ተኛ "ከዚህ የተነሣ ፍሬ ዐጣ ፍሬ ቢስ ኾነ።"

ጋሸኛ (ኞች) ጋሻም ባለጋሻ ኀይለኛ ጦረኛ ስመ ጥር "በግእዝ ያርብሓዊ ጋራዊ ይባላል።"

ጋሸኛነት፡ ዠግንነት/ሐርበኝነት

ጋሻ (ሾች ወልታ ሐገፋ) (ዮሐ. ፲፰፡ ) ከጐሽና ከጕማሬ ካውራሪ ከዝኆን ቈዳ የተበጀ የዠግና መከታ "ትልቁ አግሬ ይባላል።" "ጋሻ (ገያሣ) ገሥጋሽ ከማለት የወጣ ነው ትግሬ አንግዳ ሲል ጋሻ ይላልና።" (ተመልከት፡ ጣፋን ሻንቆን እይ)

ጋሻ ለበሰ፡ ጋሻን በላይ ሰውነቱን በታች አደረገ

ጋሻ ዣግሬ (ዣግሬ ጋሻ) የንጉሥ የሻለቃ ጋሻ ተሸካሚ ጐበዝ "ጋሻ አግሬ ቢል አግሬ የሚሳል ወይም ዣግር ጋሻና ዘገር ያዥ" (፩ነገ. ፴፩፡ -) (ተመልከት፡ አግሬን ዣግሬን ተመልከት)

ጋሻ ዣግሬዎች፡ ብዙዎች ጋሻ ሸካሞች (የጋሻ ዣግሬ ጭፍሮች)

ጋሻ፡ ኀይል ጕብዝና ወኒ "እከሌ እከሌን ጋሻ አነሣ (ወረሰ)"

ጋሻ፡ በገመድ ተለክቶ ለዘማች ተሰጠ ቀላድ መሬት "ዘመቻው ዘገር ነጥቆ ጋሻ አንግቦ ስለ ኾነ መሬቱ ጋሻ ተባለ ቀላድን ተመልከት።"

ጋሻ፡ በጦርነት ጊዜ የጋሻ መካች ምድር

ጋሻ፡ እንጕዳይ ("የረኛ ጋሻ" እንዲሉ) በትግሪኛም ("ዋልታ ምድሪ") የምድር ጋሻ ይባላል

ጋሻ፡ ዘማች ወታደር ነፍጠኛ ( ስት ልጅ ቤተ ሰብ ያሉት ጠልጠሌ ወንደ ላጤ ያይዶለ) "ጓዝ ተጋሻ" እንዲሉ

ጋሻ፡ የደረሰ አሽከር ልጅ እግር "ማር ተጋሻ" እንዲሉ "ማር መብላቱንና ጋሻ መሸከሙን ያሳያል።"

ጋሻ፡ የጦር ዠብዱ "እከሌ ከሌን በጋሻ ይበልጠዋል።" "ወይ ጋሻ ዱሮ ቀረሻ።"

ጋሼ፡ የታላቅ ወንድም መጠሪያ ስም "ጋሻዬ የኔ ጋሻ ማለት ነው።"

ጋሾ ዐምባ፡ ያገር ስም (በይፋት ወረዳ ያለ አገር ጋሼ የሚባል ሰው ዐምባ (መንደር) የነበረበት)

ጋሾጥ (ጋሾ ጥግ) ያገር ስም (በላይኛው ወግዳ በገደል ሥር ያለ ቀበሌ ጥንት ጋሼ የሚባል ሰው የነበረበት) "ጋሾጥ ማሪያም" እንዲሉ

ጋበን (ጋመን) ሐሩር/ሙቀት/ወበቅ

ጋበን / ገበረ

ጋበን፡ ዕሩር። "በና ተወራራሾች ስለ ኾኑ በጋበን ፈንታ ጋመን ይላል።" (ተመልከት፡ ገመነን)

ጋበዘ

ጋቢ (—የልብስ ስምገባ)

ጋቢ ወፍራም ሸማ፡ የሌሊትና የቀን ተገቢ ልብስ፡ ጥለት የሌለው ረዥም ኩትኛ ወይም ዝቅዝቅ

ጋባዤ፡ ዝኒ ከማሁ "የኔ ጋባዥ"

ጋባዥ (ዦች) የጋበዘ/የሚጋብዝ፡ የሚያመሳስል፡ አስታራቂ፡ አብሊ/አጠጪ/አስተናጋጅ፡ ከልካይ "ተው ባይ"

ጋባዥ፡ የሰው ስም።

ጋባዥነት፡ አብሊ/አጠጪነት።

ጋብ (ጋብኦ) መመለስ መተው ለሳ

ጋብ አለ ተመለሰ ተወ ቆመ፡ ቍጣው በረደ

ጋብር (ትግ) ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቦ

ጋብቻ፡ በቁሙ፡ ገባ

ጋብቻ፡ በቁሙ፡ ገባ

ጋብቻ ተክሊል ሩካቤ ዕምረት ሙሽራው እሙሽራዋ ሙሽራዪቱ አሙሽራው ቤት መግባታቸውንም ያሳያል

ጋተ (ገዐተ) ለሕፃን ለበሽተኛ ጥጃ ውሃን/ወተትን በጋት በቅል ዐንገት ግዴታ ጭምር አጠጣ/አስጐነጩ (፩ቆሮ. ፫፡ )

ጋተ፡ በጥፊ መታ ("የጋት ምስጢር አለበት።")

ጋተለ፡ ተሰበሰበ/ታከበ/ተያዘ

ጋተሎ/ግትል፡ ስብስብ (ታላቅ )

ጋተው፡ የፈረስ ስም (ተመልከት፡ አባን እይ)

ጋቴራ፡ ጣፋ/ጋሻ (ቁመት ሙሉ ሾጣጣ አግሬ ከጕማሬ ቈዳ የተበጀ ሲሰጐድ የተወጠረ ወይም ተሸላሚው ይዞት የሚቆም)

ጋት (ጋዕት) ውስጥ እጅ መዳፍ ጥርኝ (የክንድ ፮ኛ ልክ) (ዘፀ. ፳፭፡ ፳፭)

ጋች (ገዓቲ) የጋተ/የሚግት ( ጠጪ)

ጋነ ገብ፡ የመንግሥት ምስለኔዎች ግዛት (ዐላባው ኹሉ በወር ተራ ወደ ንጉሥ ማድ ቤት የሚገባ) "ጋነ ግብ ያሠኘው ማሩ ጌሾው ዐሻሮው ነው።"

ጋኔል፡ ጋኔን (ተመልከት፡ ገነነ)

ጋኔናም፡ ጋኔን ያደረበት

ጋኔን (ኖች) ክፉ መንፈስ ጅን (ይህን ዓለም በጨለማ የሚገዛ በክፋት የገነነ የግዜርና የሰው መዠመሪያና መጨረሻ ጠላት በላይ በታች የሚገኝ (ያየር ጋኔን) ባየር የሚኖር (የጕድፍ ጋኔን) ልክስክስ በጕድፍ የሚውል ሰይጣን) "በን ፈንታ ባላገር ጋኔል ይላል።"

ጋኔን ሳቢ፡ ጋኔን ጐታች

ጋኔን ዐደረበት፡ ገባበት/ተዋሓደው

ጋኔን ጐታች፡ አስማተኛ/ጠንቋይ "እሰግድ ለግልፎ ብሎ ማተቡን በጥሶ ዕራቍቱን ኹኖ ጋኔን የሚስብ ሳቢ ኣነጋጋሪ።"

ጋኔን ጣለው፡ ሰውየውን ጋኔኑ ከመሬት አወደቀው/መታው/አንደባለለው/አንከባለለው/ቈበር አስደፈቀው/አስጮኸው/አስለፈለፈው

ጋኔን፡ ክፉ ሰው

ጋን (ኖች) (ገንዕ) የጠላ መጥመቂያ/የጠጅ መጣያ/የቡሖ ማቡኪያ/የሸማ መክተቻ ታላቅ የሸክላ ዕቃ (ማድጋ ሳሌ ዝንግሪር ገች ዐዋሽ) "የማስ አቍማዳም ጋን ይባላል።" "የሰካር አፉ ጋን ጋን ይላል።" "እየጠጡ ዝም የጋን ወንድም " "ጋን የገነነ ዘር ነው።" "ደንጊያም ጋን ይኾናል" (ዮሐ. ፪፡ , )

ጋን ሆይ፡ (ተመልከት፡ ገናና ሆይ) ጃን

ጋን ሰበር፡ የገብስ ስም (ጠላው ጋን የሰበረ ጥቍር ገብስ)

ጋን ታረደ፡ ሙክት ተዘነበለ (ገላቢጦሽ ነገር)

ጋን፡ ከታችኛው ወግዳ በስተቀኝ በተጕለት ክፍል ያለ አገር

ጋንዣ፡ ያንገት መትን ዥማት (ራስን ከትከሻና ከደረት ጋራ የሚያያይዝ)

ጋንድያ (ዮች) ወፍራም አህያና የበቅሎ አጋሰስ ምስንጅር ግንድ የሚጭን የሚደበለል

ጋንድያ፡ ምስንጅር፡ (ተመልከት፡ ግንድ)

ጋንገኛ፡ ኀይለኛ/ዶሰኛ (ብዙ ሰው የሚመታ) "በፈረንጅኛ ጋንግስተር ይባላል።"

ጋንጋት፡ ጋጋኖ ድምፀ ጋንገኛ (የሚንጋጋ ብዙ ማለት ይመስላል)

ጋንግ (ትግ. ሐባ. ጊንግ፡ ግንድ) ኀይል/ብርታት "ግእዝ 'ጋጋ' ከሚለው የወጣ ነው።" (ተመልከት፡ ቀንበርን)

ጋንጢጥ (ጋጠጥ) ደፋር "ይሉኝ አይልም።"

ጋንጩር፡ ሰይጣናም ሰው

ጋንጩር፡ ጋኔን/ሰይጣን

ጋንፉር (ሮች) እንደ መጅ ያለ ጨው

ጋኖች፡ ትልልቆች ሰዎች ዋኖች ጨዎች ጐምቱዎች አባቶች ዐዛውንቶች

ጋዛ፡ ያገር ስም (የይሁዳ ክፍል ካ፭ቱ የኢሎፍሊ - አገሮች አንዲቱ)

ጋዜጠኛ (ኞች) ባለጋዜጣ/ጋዜጣ ጻፊ/ጋዜጣ ወዳድ አንባቢ

ጋዜጣ (ጦች) የቀን/የሳምንት/የወር/ያመት ወሬ ጽሑፍ ዕትም ወይም ወሬው የተጻፈበትና የታተመበት ወረቀት/መጻፍ "የኢትዮጵያ ጋዜጦች እነዚህ ናቸው፦ ፩ኛ አእምሮ ፪ኛ ብርሃንና ሰላም ፫ኛ በጣለ ያን ጊዜ ተሐደሰት ኢትዮጵያ ፬ኛ የሮማ ብርሃን ከጣሊያን ወዲህ ፭ኛ ሰንደቅ ዐላማችን ፮ኛ ዐዲስ ዘመን ፯ኛ የኤርትራ ድምፅ ፰ኛ ነጋሪት ጋዜጣ ፱ኛ ተክለ ሃይማኖት ፲ኛ ዜና ቤተ ክርስቲያን ፲፩ኛ የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ፲፪ኛ የኢትዮጵያ ድምፅ ፲፫ኛ መነን ፲፬ኛ ኅብረት ፲፭ኛ ወታደርና ዐላማው ፲፮ኛ ወታደርና ጊዜው ፲፯ኛ ፖሊስና ርምጃው ፲፰ኛ ፈለገ ብርሃን ፲፱ኛ ኑሮ በዘዴ" !

ጋዝ (ዐረ. ቃዝ) ላምባ()/መብራት የሚኾን የምድር ዘይት ወይም ቅባት (በግእዝ ነፍጥ ይባላል)

ጋዝ (ጋእዝ) ጠብ/ክርክር/ንዝንዝ/ውዝግብ/ጭቅጭቅ/ጦርነት "አበ ጋዝ" እንዲሉ።

ጋዝ (ግዕዘ/ጋዕዝ) ዕቃ/ጓዝ/ጭነት/ሲራራ "ወደል ጋዝ" እንዲሉ።

ጋዠ (ቃዠ) አረጀ/አፈጀ/ረሳ/ዘነጋ/ኣእምሮ ዐጣ/ዣዠ ከፋ/ተበላሸ/መጥፎ ኾነ (ዐመሉ/ጠባዩ)

ጋዣ፡ የሣር ስም (ማለፊያ ሣር የፈረስ መኖ ቅልጥሙን ሲመጡት ማር ማር የሚል "የጋዣ ማር" እንዲሉ)

ጋየ፡ ጋለ/ፋመ/ነደደ/ተቃጠለ/ቀላ ሸክላ መሰለ

ጋይ (ዮች) የጋየ/የጋለ (ያፈር/የመሬት ፍም ጣረት) "የጋይ መሬት" እንዲሉ።

ጋይ፡ የጋለ/የሚግል ብረት

ጋይንቴ፡ የጋይንት ተወላጅ/የጋይንት አገር ሰው

ጋይንት (ቶች) በበጌምድር ክፍል ያለ የነገድና ያገር ስም ትርጓሜው ትልቅ

ጋደ (ገሀደ) ተገለጠ/ታየ።

ጋደለ፡ ዘነበለ (ወዳንድ ፊት ኣለ/መዘነ)

ጋደል አለ፡ ዘንበል አለ/ጋደለ።

ጋደል፡ ዘንበል።

ጋዱ

ጋዱ (ዎች) ዝኒ ከማሁ (የሚከለክል/አዋኪ/ሽፍታ) "ላምን ጋድቶ ወተቷን እንደ ማለብ ሰውን ይዞ የፊጥኝ አስሮ ገንዘቡን የሚቀማ። ጋዱ በጋልኛም ይነገራል።"

ጋዲ፡ ባንድ በኩል ቍጥር ያላት ዐጪር ጠፍር (የላም እግሮች ማሰሪያ) (ተመልከት፡ አከለ ብለህ አኮሌን አስተውል)

ጋዲሎ፡ ያገር ስም (ዐጤ ምኒልክና)

ጋዳ

ጋዳ ለጦሙ (ጾመ ገሃድ) በጦም ቀን የሚነገር ቃል። "ጋዳ ለጦ ለጦ (ዳነት) ግልጥነት ይግባውና ትላንትና ዐሙስ ጮማ በላን።"

ጋዳ/ጋድ (ገሃድ) የወንዶች ገና (የጥምቀት ከተራ) "የገና የጥምቀት ዋዜማ እንዳርብ ሮብና እንደ ፍልሰታ እንደ ሑዳዴ የሚጦም። ትርጓሜው የሚገለጥ/ተገላጭ/ግልጥ ማለት ነው። ጌታችን እንደ ሰውነቱ ባጪር ቁመት ዐጠባብ ደረት ተወስኖ መታየቱን ያስረዳል "

ጋዳ፡ አሰረ/ወደረ/አዋሰዐ (እንደ ባላ/ድር ጠለፈ) ከለከለ/አገደ (እንዳይኼድ አደረገ) "ጋዳ ከአገደ የወጣ ነው።"

ጋዳይ፡ የሚጋድል (ዘንባይ)

ጋድ (ገደወ) የሰው ስም (የያዕቆብ ልጅ ትርጓሜው እጅ መንሻ)

ጋድርኤል፡ የጋኔን ስም (ሔዋንን ያሳተ ሰይጣን) (ሔኖ. ፲፱፡ ፲፱)

ጋጂ፡ የጋዳ/የሚጋዳ (ላም ዐላቢ)

ጋገረ፡ ሊጥን በምጣድ ላይ ኣዞረ፡ አሰረረ/አሰፋ/ደፋ/አበሰለ (የንጀራ/የቂጣ/የዳቤ/የድፎ ዳቦ/የጥረሾ/የብርኩታ/የማር) (ተመልከት፡ ለጠለጠን)

ጋገራ፡ የመጋገር/የማብሰል ሥራ (መጋገር/ማዞር/ማስረር/ማስፋት/መድፋት/ማብሰል)

ጋጊ

ጋጋ (ገህግሀ/ጎገወ) ገረፈ፡ በጥፊ መታ/አጮለ

ጋጋ፡ ለየ/ከላ/ከለከለ (ከዝሪት) (ተመልከት፡ ጋጋኖን)

ጋጋ፡ ግርግር አደረገ፡ አራቀ/አስገለለ (ከቤት)

ጋጋሪ (ሮች) የጋገረ/የሚጋግር (አብሳይ/ዐበዛ)

ጋጋታ (ተዋክቶ) ጃጃታ/ግርግርታ

ጋጋታ፡ ግርግርታ፡ ጋጋ

ጋጋኖ (ዎች) (ጓጓ) ርኩምና የወንዝ አመቴ መሳይ፡ ያሞራ መንጋ በምድር በሰማይ የሚንጋጋ፡ ጯኺ ድምጠ ረዥም (የነቢያት ምሳሌ)

ጋግርታም (ሞች) የጋግርት ወገን (ባለጋግርት/አፍጣጭ/አጕራጭ)

ጋግርት (ቶች) የጐረጥ የሚያይ (የደጋ ቆቅ ሲነሣ ግር የሚል)

ጋግርት፡ የደጋ ቆቅ

ጋጠ (ትግ. ገሐጸ) በጥርስ ላጠ/መለጠ/ገጠበ (ነጩ በላ ሰበረ ያጥንት/የሣር/የጨው/የብክካ)

ጋጠ፡ ሰውን ዐማ

ጋጠመ፡ ጭፍንፍን እንባው የማይቆም ("ዐይነ ጨምጭማ እንዲሉ መጨመጯን እይ")

ጋጠረ፡ ለፋ/ደከመ (በገጠር)

ጋጠረ፡ የገረ ዘር ነው "ገጠረ የስፍራን መበላሸት 'ጠረ' የሰውነትን መጐዳት ያሳያል።"

ጋጠወጥ ባለጌ፡ ጋጠ

ጋጠወጥ፡ የጋጠውን ወጥ የሚያስነካ (ግጦ ከወጥ ባለጌ መረን አግድሞ አደግ) (ተመልከት፡ ገመጠን)

ጋጠጠ፡ ሥጋን ካጥንት ላይ ቈረጠ/ገፈፈ ጥቂት ሳያስቀር ጨርሶ ጠረገ ደደ ጠጠ (ተመልከት፡ ጋጠን)

ጋጠጥ፡ የጋጠጠ/የሚጋጥጥ (ባለጌ ደድ)

ጋጣ/ጋጥ (ጋሕጽ) የፈረስ/የበቅሎ/የአህያ/የበግ/የፍየል ጓዳ መጠጊያና ማደሪያ "ሲርባቸው ግድግዳውን መሬቱን የሚግጡ ስለ ኾኑ ጋጣ ተባለ" (ኢሳ. ፩፡ ) "ጋጣ ከብት ግጦ ያበጀው ዋሻ።"

ጋጤ፡ የተጋ/የተመለጠ።

ጋጥ፡ ትእዛዝ አንቀጽ ላጥ ምለጥ ንጭ ብላ "ጋጣ ጋጥ ግእዝ ዕጋዕ ምፅንጋዕ ካለው ይሰማማል።"

ጋጯ፡ የጋጠ/የሚግጥ/የሚልጥ/የሚነጭ/የሚበላ (ሰው/አውሬ/ከብት/በረሮ)

ጋፈ (ግሒፍ/ገሐፈ) ዐፈሠ/ጠረገ (ከምጣድ አወጣ እንደ በሬ አብዝቶ ጠጣ) (ተመልከት፡ ጋፈፈን እይ)

ጋፈፈ (ገፈረ) ዐወደ/ጠረገ/ሰበሰበ/ወሰደ (የደረቅ ሣር ያሣ)

ጋፈፈ፡ አብዝቶ በላ/ጨረሰ

ጋፈፎ፡ ዐጨዳ/ጠረጋ/ስብሰባ (ውሃ ሲመላ በሸማ ዓሣ መያዝ)

ጋፊ (ዎች) የጋፈ/የሚግፍ (ጠራጊ)

ጋፊኛ፡ በቀጥታ ቀንበርን አለመሳብ (ወደ ጐን የበሬ ጫንቃ ግፊያ)

ጋፊኛ፡ የበሬ ግፊያ፡ (ተመልከት፡ ገፋ)

ጋፋት፡ የነገድና ያገር ስም (በጐዣም አጠገብ በዳሞት ውስጥ ያለ አገር)

ጋፋቶች፡ የጋፋት ሰዎች (ነገደ ጋፋት)

ጋፋፊ፡ የጋፈፈ/የሚጋፍፍ (ዐጫጅ ሰብሳቢ ዓሣ ያዥ ዘኬ ተሸካሚ)

ጋፍ (ገሐፍ) ዕፈሥ/ጥረግ

ጋፍ (ጋሕፍ) የባሕር ዔሊ (ግእዝ)

ጋፍ፡ ሞኝ/ቂል/ግትቻ

ከፊለ ስም፡ ባለጌ ማለት ነው (ትርጓሜ መቅድመ ወንጌል)

እንደ በቃል መጨረሻ እየገባ ምድር ቦታ ስፍራ ተብሎ ይተረጐማል (ማስረጃ) እጅጌ ባለጌ ገደልጌ ገዳምጌ ጕራጌ ግርጌ ደረስጌ ወገብጌ ዋንዛጌ ሐረርጌ ይተጌ

ጌስ ጐሽ

ጌሥ (ጊሥ) የገበጣ ጨዋታ "የያዝኸውን ይዘኸ ኺድ ገሥግሥ ባትመለስ ማለት ነው።"

ጌሥ፡ በመንዝ ውስጥ ያለ አገር

ጌስ፡ ያገር ስም፡ ጌሥ

ጌሦች፡ የጌሥ ሰዎች/የጌሥ ተወላጆች (መንዞች)

ጌራ፡ የሰው ስም (ከመንዝ ባላባቶች አንዱ አገሩም ጌራ ይባላል)

ጌራ፡ የራስ ወርቅ (የራስ ቍር የብረት ቆብ) (ግእዝ)

ጌራ፡ የገንዘብ ስም (ታናሽ ገንዘብ) (ተመልከት፡ ሐዲሱን መጽሐፈ ግስ ገጽ ፫፻፲፬ እይ)

ጌራ፡ ያገር ስም (የሻንቅላ አገር "የጌራ ንግሥት" እንዲሉ)

ጌርጊስ፡ የመናፍቅ ስም (ያባ ተክሌ ጠላት እመንገድ ላይ ተቀምጦ ወደ ዜጋ መል የሚኼዱትን ጠበለተኞች ኹሉ "ባገራችኹ ቤተ ክሲያንና ውሃ የለምን?" እያለ የሚያውክ መቃብሩ በደብረ ሊባኖስ ባሻገር ካቢ ሰሚባል አገር ይገኛል መሬንዝ በቅሎ በታል በዚያ የሚያልፍ መንገደኛ ምን ጊዜም ቢኾን ደንጊያ ይጥልበታል ስለ ርሱ ሌላም ብዙ አፈ ታሪክ ይነገራል እውነት መኾኑን እንጃ)

ጌርጌሴኖን፡ ያገር ስም (በምድረ ፍል ስጥኤም ያለ አገር)

ጌሾ (ትግ. ጌሦ) የታወቀ ተክል ስም (ከጥንስስ ዠምሮ ቅጠሉና ዐጥንቱ እየተ ወቀጠ ጠላ ዐጥንቱ ተልጦ ሳይወቀጥ ጠጅ የሚኾን በርሱ ምክንያት ጠላውና ጠጁ አብ ዝቶ ሲጠጡት የሚያሰክር ራስ የሚያዞር)

ጌተየ (ገይተየ) ከበረ/በለጠገ/ ሾመ/ተሸለመ/ገዛ/ነዳ/ገነነ

ጌታ በቁሙ ጌተየ

ጌታ (ቶች) (እግዚእ) ባለጠጋ ሀብታም ገንዘባም ከበርቴ ባለእዱኛ (ሹም መስፍን መኰንን አለቃ አሳዳሪ ባለማረግ ዳኛ ገዢ እግዜር) "ዘርፍ ይዞ ሲነገር ብላቴን ጌታ ግራ ጌታ ቀኝ ጌታ የኔታ ቅጽል ሲቀድመው መሪ ጌታ ይላል።"

ጌታ (ኢያ ) መለከ ብለኸ መልከ ጼዴቅን እይ

ጌታ ሆይ ( እግዚኦ) አምላክ ፈጣሪ ሆይ

ጌታ መሳይ፡ ተግደርዳሪ ራሱን የማ ይጥል ሰው

ጌታ፡ ባለቤት "የዚህ ጌታ" እንዲሉ (ተመልከት፡ አባን እይ)

ጌታ፡ ከ፯ቱ የጕራጌ ወንድማማቾች ንዱ ነገዱም አገሩም ጌታ ይባላል

ጌታችን (እግዚእነ) የኛ ጌታ ጣሪያችን መምራችን ኢየሱስ ክርስቶስ

ጌታው (እግዚኡ) የሀብት የእዱኛ ባለቤቱ (የሰማይ የምድር የዓለም ፈጣሪው) "ጌታው ጌታ የርሱ ጌታ ጌታዋ የርሷ ጌታ"

ጌታዬ (እግዚእየ) የኔ ጌታ አሳ ዳሪዬ አዛዤ

ጌት፡ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ በፍልስጥ ኤም ውስጥ ያለ አገር

ጌትነት (እግዚእና) ጌታ መኾን ባለጠግነት ሹምነት ንጉሥነት ኣምላክነት (ኢሳ. ፴፫፡ ፲፯፡ ይሁ. ) (ተመልከት፡ የኔታን እይ)

ጌትኛ፡ የጌታ ኹኔታ አነጋገር አስተ

ጌትዬ፡ የሰው ስም (አስቀድሞ የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ኋላም ያጢ ምኒልክ ሸላይ የነበረ ትርጓሜው ጌታዬ ማለት ነው)

ጌቶ (እግዚኦ) አቤቱ/አቤቶ

ጌቶች፡ በባላገር ከንጉሥ ዠምሮ ስላ ንድ ባለሥልጣን ይነገራል

ጌኔ፡ የጎፋ ባላባትና ንግሥት "ጎፋ ጌኔ" እንዲሉ "ከገን ጋራ አንድ ነው።"

ጌንጭ፡ እንደ ጤፍ ዳልጋ ያለው ሣር (ዐረም)

ጌጠኛ (ኞች) ያጌጠ/የተጌጠ/የተሸለመ (ሽልም ባለጌጥ ጌጣም ጌጥ ያለው ጌጥ ወዳድ)

ጌጣት፡ ጌጦች (በተጕለት ፵ፍ ያለ ቀበሌ) "የጣት ምድር ተብሎም ይተረጐማል በእጅ ዐደር ማለት ነው።"

ጌጣጌጥ፡ የጌጥ ጌጥ ብዙ ዐይነት

ጌጥ

ጌጥ ገጠገጠ

ጌጥ (በቁሙ) (ገየጠ)

ጌጥ (ጌጽ) የሚያምር ልብስ (ሓርዕ/ንቍ/ፈርጥ/ወርቅ/ብር/ቀለበት/አንባር/ጕትቻ/ግርጃ/ድኰት/ሽልማት/ጥልፍ/ሻት/ዝምዝም የመሰለው ኹሉ።)

ጌጦች፡ ማዕድኖች/ጥልፎች

ጌጽ፡ በቁሙ ሽልማት (ተመልከት፡ (ገየጠ ጌጠ) ብለኸ ጌጥን ተመልከት)

ግሃ፡ በሽተኛ ፈርካሳ ጥርስ "ግሃ ጥርስ" እንዲሉ።

ግሑሣን፡ መናኞች/ባሕታዊዎች ከሰው የማይገናኙ

ግሑሥ (ግሒሥ/ገሐሠ) የተወገደ ውግድ (ከሰው ተለይቶ በበኣት (ዋሻ) ተከቶ የሚኖር መናኝ ባሕታዊ)

ግለት፡ ግመት/ሙቀት/ትኵሳት

ግላሎ፡ ከርሻ ከዝሪት ውስጥ ተነቅሎ የሚወገድ ዐረም

ግላስ (ሶች) ከተንቤን ከነት ከጀንዲ ከሐር ከግምጃ የተበጀ በኮርቻ ላይ የሚደረግ መቀመጫ

ግላጭ፡ ብቻ (ሌላ ሰው ሳይኖር) "ነጋዴው በግላጭ ብዙ ትርፍ አገኘ።"

ግላጭ፡ ወበቅ (የፀሓይ ሙቀት) "የደመና ግላጭ" እንዲሉ።

ግላጭ፡ የተገፈፈ (ግፋፊ) "እግር ግላጭ" እንዲሉ።

ግል የተገለለ፡ ገለለ

ግል() ምቢጥ (ግፍትዒት) ግልብጮ "የዥብ ገበሬ ያህያ በሬ የጦጣ ዘር አቀባይ የዝንጀሮ ጐልጓይ ኹሉም እንብላ ባይ።" ስሯጽ ነው

ግል፡ ልዩ ገንዘብ/ከብት (ባል ለሚስቱ ያልቈጠረው ያላገባው) "የግሉ ነው የግሏ ነው" እንዲሉ።

ግል፡ የመለየት ሥራ (ብቻ ቈይታ) "እከሌና እከሌ ስለ ተጣሉ ሽማግሎች ግል ይዘዋቸዋል።"

ግል፡ የተገለለ/የተለየ/የራቀ (ሩቅ)

ግልሙትና፡ ፈትነት/ብቻነት/ምንዝር (የምንዝር ሥራ ብልግና ባል አልባነት) (ዘፍ. ፴፰፡ ፳፬፡ ኢሳ. ፳፫፡ ፲፯)

ግልም፡ ትኰራ/ቍጣ/ፍጥጫ/ግርማ

ግልምቢጥ፡ ግልብጮ፡(ተመልከት፡ ገለበጠ)

ግልምት አለ፡ ፈጽሞ ገለማ

ግልምት፡ መገልማት (እክክ ማለት)

ግልስልስ አለ፡ ቅልስልስ አለ (ተኛ ተመሳቀለ)

ግልበጣ፡ ልወጣ/ቅየራ/ትርጐማ/ምልሳ/ክንበላ

ግልቢያ, ፍርጠጣ, ሽምጠጣ ("(፩ቆሮ፲ ፱፡ ፳፬)") - ሩጫ, ፍጥነት ("(1ቆሮ. 9 24)"). (የልም ሩጫ) ሳይሮጡ መሮጥ - (የምናብ ሩጫ) ሳይሮጡ መሮጥ።

ግልቢያ፡ ሽሽት/ሩጫ/ፍርጠጣ

ግልባጭ፡ ዝኒ ከማሁ (ተመልከት፡ ነገረ ብለኸ ነገርን)

ግልባጭ፡ የተቀዳ/የተተረጐመ (ቅድ ትርጒም ፪ኛ ጥፈት)

ግልብጥ፡ የተገለበጠ (በላይ ወይም በውስጥ የኾነ ልውጥ ቅይር) (ተረት) "ተወኝ ተወኝ ዐዲስ ግልብጥ ነኝ።"

ግልብጦሽ፡ በአጅና በእጅ መካከል ወደ ኋላ እየተገለበጡ ወጣቶች የሚጫወቱት የጢሎሽ ጨዋታ "ፈረንጆች 'ባር ፓራሌል' ከሚሉትጋራ ይገጥማል።"

ግልብጮ፡ ደቂቅ ኣገባብ (ግርምቢጥ የኋሊት) (ተረት) "ዶሮ ከጋጥ በሬ ከቈጥ ቍርባን ውጪ ክርስትና።"

ግልየት፡ የመጽሐፍ መግለጫ በጥፈት ዳርና ዳር በስተጠርዝ በኩል ያለ "('ገለየ' 'ግልየት' ግእዝኛ ናቸው።)"

ግልድመኛ፡ ዝኒ ከማሁ

ግልድማም፡ ባለግልድም እስላም በረኛ

ግልድም/ግልድሞሽ (ገልድ) ትጥቅ ሽርጥ

ግልድሞች፡ ሽርጦች

ግልድው አለ፡ ወደቀ/ተጋደመ

ግልድው፡ መውደቅ/መጋደም

ግልገላ/ግልጋሎ፡ መሳ (የበጋ ዕርሻ)

ግልገል (ሎች) የበግ/የፍየል/የፈረስ ልጅ (የዥብ ግልግል) ቡችላ

ግልገል መሪ፡ ያማጭ ምክትል

ግልገል ሙሴ፡ ምክትል ሙሴ (፪ኛ የማኅበረተኛ ሹም አዛዥ አለቃ አሳዳሪ)

ግልገል ሚዜ፡ ፪ኛ ሚዜ (የዋና ሚዜ ተወራጅ ዝቅተኛ)

ግልገል ሞራ፡ ከወተት አንዠት ጋራ የሚገኝ

ግልገል ሰኰና፡ ከወደ ኋላ ከሰኰና በላይ ያለ የከብት ጥፍር

ግልገል በቅሎ፡ አህያ ከፈረስ የወለደው

ግልገል አህያ፡ ውርንጭላ (ዘፍ. ፴፪፡ ፲፭፡ ሉቃ. ፲፱፡ ፴፫, ፴፭)

ግልገል አንሣ፡

ግልገል አንሣ፡ የሎስ ታላቅ አሞራ/ንስር ጐሢ ግልገል አንሥቶ የሚወስድ

ግልገል፡ ከጐርዝ የሚበልጥ ከግንቡል የሚያንስ ዓሣ

ግልገል፡ የግብግብ ጥብቆ (ሕዕንግልገል የሙቀጫ ልጅ ዘነዘና)

ግልገል፡ የጐሽ እንቦሳ ጥጃ "የጐሽ ግልገል የመሰለ ልጅ" እንዲሉ።

ግልግል (ሎች) ከመደቡ ተነቅሎ በሌላ ስፍራ የተተከለ የጌሾ የበርበሬ የዛፍ የማንኛውም ተክል ችግኝ

ግልግል፡ ዕርቅ/ስምም (ተመልከት፡ ነካ ብለኸ ተነካን)

ግልጥ (ጦች) የተገለጠ/የታወቀ/የጐላ/የተረዳ (ክሡት)

ግልጥ ነገር፡ ያልተሰወረና ምስጢር ያይዶለ ወሬ ወይም ሌላ

ግልጥ አለ፡ ተገለጠ

ግልጥ አደረገ፡ ገለጠ

ግልጥ ኾነ፡ ጐላ/ታወቀ (ከመሰወር ከመርቀቅ ራቀ)

ግልጥልጥ፡ የተገላለጠ (ክፍትፍት)

ግልጥነት፡ ግልጥ መኾን (አለመሰወር አለመታባት)

ግልጸ

ግልጽ፡ ግልጥ/ክሡት

ግልፊያም፡ የግልፍ ወገን ባለግልፍ

ግልፋጭ፡ የተገለፈጠ (ግልፋፊ)

ግልፋፊ፡ የብራና ፍቄት

ግልፌ፡ በድንገት የምትመላ (ባዲስ አበባ ያለች የሥላሴ አጥቢያ ፈፋ ዳግመኛም ግንፍሌ ትባላለች)

ግልፍ አለኝ፡ ፪ኛ የግልፌ ስም

ግልፍ አለኝ፡ ተቈጣኹ (ቍጣ ገጠመኝ)

ግልፍ አለው፡ ቍጡ ኾነ (ቍጣ አገኘው)

ግልፍ፡ የተቈጣ ቍጡ

ግልፍተኛ (ኞች) በጥቂት ነገር የሚቈጣ ወፈፍተኛ አምራሪ

ግልፍተኛነት፡ ቍጡነት ወፈፍተኛነት

ግልፍታ/ግልፍት፡ ቍጣ ወፈፍታ

ግልፍጥ፡ ዝኒ ከማሁ (ግልፍፍ)

ግልፍፍ፡ የተገለፈፈ/የተላጠ/የተላፈ

ግሎብ (ሮማይ፡ ግሎቡስ) ክብ እንክብል (የዓለም ሥዕል በብረት ላይ የተሣለ) "የመጋለብና የመዞር ምስጢር አለበት።" (ተመልከት፡ ከበለለ እንክብልን)

ግመለኛ (ገመላዊ) ግመል ጫኝ/ግመል ሳቢ

ግመላም፡ ባለግመል/ጠባሳም (በገላው የብጫ ነጠብጣብ ያለበት)

ግመል (ሎች) (ገመል) የጋማ ከብት (እንደ ፈረስ ጋማ እንደ በሬ ሻኛ ያለው የሚያመሰኳ ቁመቱና ዐንገቱ ረዥም ታዛዥ ተንበርክኮ የሚንበረከክ በቅሎ ጭነት የሚያነሣ በረሓ ደፋር ውሃ ጥም ቻይ የቤት እንስሳ) (ዘፍ. ፳፬፡ ፲፩, ፴፩፴፬)

ግመል አወጣ፡ ጠባሳ አበጀ/አደረገ

ግመል ዠርባ፡ መፃጕዕ

ግመል፡ የጭን/የቅልጥም ብዊ ጠባሳ

ግመት፡ ግለት/ሙቀት/ቃጠሎ

ግመኒ/ጥን በኒ፡ " እንደ ኛና እንደ መኖርንና ባለቤትነትን ያሳያል።"

ግማታም (ሞች) ጥንባታም/ክርፋታም/ቅርናታም

ግማት፡ ጥንባት/ክርፋት/ቅርናት (ክፉ ሽታ) (ኢሳ. ፫፡ ፳፬)

ግማድ/ጕማጅ፡ (ግእዝ) "ግማደ መስቀል ዐጤ ዳዊት ከኢየሩሳሌም ያስመጡት የጌታችን መስቀል ቍራጥ።"

ግማጭ፡ ከጥርስ የተረፈ ቍራሽ (የዳቦ የንጀራ ቅሬታ)

ግም

ግም (ሞች) (ግሙእ) የገማ/የጠነባ (ጥንብ የተበላሸ ውዳቂ) "ግም ለግም ዐብረኸ አዝግም።" "ላፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል "

ግም አለ፡ አስተጋባ፡(ተመልከት፡ ገመገመ)

ግም አለ፡ ድም ኣለ/ጮኸ (ድምፅ ሰጠ አስተጋባ የሳንቃ የነጋሪት የሰማይ)

ግም፡ መጥፎ ሰው/ሥራ

ግም፡ የመንቀፍና የማዋረድ ቃል።

ግምላም፡ ልብልባታም/ጠባሳም

ግምል፡ የተገመላ/የተለበለበ (ልብልብ ቅርፊቱ የሚወድቅ ለጠላ የሚኾን የማሽላ አብሲት ቂጣ)

ግምሳት፡ የመግመስ/የመፈንከት ሥራ ወይም ፍንክት

ግምስ፡ የተገመሰ/የታረሰ (ትልም)

ግምት (ቶች) ሒሳብ/ግምጋሚ/ስሌት (ያንድ ነገር ዋጋ - ጥሬ)

ግምት አለ፡ ፈጽሞ ገማ

ግምት የለሽ፡ የሴት ስም

ግምት የለኸ፡ የሰው ስም "ላንተ ዋጋ የሚኾን የለም ማለት ነው።"

ግምት፡ መግማት

ግምት፡ የተገመተ የተገመገመ (ቅጽል)

ግምነት፡ ንዴት ቅጥለት

ግምን (ግሙን) የገመነ ያረረ

ግምን አለ፡ ንድድ ቅጥል ዕርር ክስል እለ

ግምንምን አለ፡ የግምን አለ

ግምንምን፡ የተግመነመነ

ግምደላ፡ ቈረሳ/ገመሳ

ግምድ፡ የእግር ቍርጥማት (እግርን እንደ ገመድ የሚያደርግ በግእዝ ግን ቍራጭ ዕራፊ ማለት ነው)

ግምድል አለ፡ ቍርስ አለ (ተገመ)

ግምዶ፡ ያራስ ጥሪ

ግምጃ ሱሪ፡ ከግምጃ የተዘጋጀ ሱሪ

ግምጃ ቀሚስ፡ ከግምጃ የተሰፋ ቀሚስ እጀ ጠባብ ዐብደላ ካኒ

ግምጃ ቤት፡ በጐንደር ግንብ ውስጥ ያለ የማሪያም አጥቢያ

ግምጃ ቤት፡ የግምጃ ቤት ሹም በዥሮንድ

ግምጃ ቤት፡ የግምጃ የገንዘብ ቤት

ግምጃ ኰደኰደ (ጐደጐደ) ገረን የኋላ እግርንና የፊት እግርን ወይም እግንና እጅን ባንድነት ገጥሞ እየረገጠ በኀይል አሰረ ("ጠፈረ ገርኚ አሰራ ")

ግምጃ፡ ከጥጥ ከሐር ተፈትሎ የተሠራ በያይነቱ ባለቀለም ልብስ የሚያስጐመዥ (ዘፀ. ፳፯፡ ) (ተመልከት፡ ሶራን ሱቲን)

ግምገማ፡ ገመታ/ስሌት

ግምጋሚ፡ ግምት/ሸለግ/ሒሳብ (ዘፀ. ፭፡ ፲፰፡ ፩ነገ. ፳፡ ፴፱፡ ኢሳ. ፯፡ ፳፫)

ግምግም አለ፡ ድምድም አለ (መላልሶ ጮኸ)

ግምግም፡ ዝኒ ከማሁ "፪ኛውን '' አጥብቅ።"

ግምግም፡ የተገመገመ/የተገመተ "የላይኛው ጥሬ የታችኛው ቅጽል መኾኑን አስተውል።"

ግምግምታ፡ ግምግም ማለት (ጩኸት)

ግምጥ አደረገ፡ ገመጠ

ግምጥ፡ ዝኒ ከማሁ

ግምጥምጥ፡ የተገማመጠ (ስብርብር ሽርፍርፍ)

ግሠጻ (ግሣጼ) ቍጣ/ዘለፋ

ግሣት (ጕሥዐት) ካፍ የሚወጣ ክፉና መልካም ሽታ

ግሴት (ግሰት) የሚያዝና የሚዳሰስ የቤት ቈሳቍስ "ዕቃ ግሴት" እንዲሉ

ግሴት የቤት ዕቃ ገሰሰ

ግስ፡ የሩቅ ወንድ አንቀጽ (ዐወቀ ነበረ አለ ነው እያለ የሚገሰስና የሚነገር ኹሉ ይኸውም ነጠላ ግስ ይባላል) "የግእዝ ኣገባብም የግስን ዐይነት ከተማ ግስ መን ደር ግስ ተራ ግስ ይለዋል።" (ተመልከት፡ መስምን ተመ ልከት)

ግስ፡ የቋንቋ መጻፍ (በፊደል ተራ ማንኛውም ቃልና ነገር በጠቅላላው ዘርና ነባር (ስምና ግብር) ከእልፍ እስከ ታው ተጽፎ የሚገኝበት መዝገበ ቃላት)

ግስ፡ ያንዱን ላንዱ በማወራረስ የሚ ባል የወረብና የቅኔ ጥቅስ

ግስ፡ ጓዝ እክት "ሰማይ ከነግሱ ምድር ከነልብሱ" እንዲሉ

ግስላ (ሎች) እጅግ ቍጡ አውሬ የነብር ዐይነት እልከኛ

ግስላ፡ የጐበዝ ጐበዝ ጨካኝ ሰው

ግስንግሳም፡ ኮተታም (ባለብዙ ኮተት)

ግስንግስ ኮተት ገሰሰ

ግስንግስ፡ ብዙ ዐይነት ዕቃ ጥርቃሞ በራፍ የመለሰው ማጀት የጐረሠው

ግሥገሣ/ግሥጋሤ (ጊሠት) ውሎ ሳያደርጉ ሲነጋ ዕለት ዕለት ለጦርነት ፈጥኖ መኼድ/መራመድ (ሩጫ ጥድፊያ ችኰላ)

ግሥገሣ፡ ዐጤ ምኒልክ ራስ መንገሻ ዮሐንስን ለመያዝ ያደረጉት ዘመቻ

ግሥግሥ፡ የገሠገሠ "ተሳቢና ባለቤት ከቅጽል ሲቀድም ግሥግሥ ይባላል ይኸውም የግእዝ አገባብ ነው።"

ግሶች፡ አንቀጾች የቋንቋ መጻፎች

ግረት (ግዕረት) ጭንቀት/ጩኸት

ግረግ

ግሩማን፡ የተፈሩ/የሚፈሩ "ግሩማን አራዊት ግሩማን መላእክት" እንዲሉ

ግሩም አንተ፡ ቃለ አንክሮ ወይም

ግሩም እምግሩማን፡ ከተፈሩ ይልቅ የተፈራ

ግሩም፡ በቁሙ ድንቅ/ዐጀብ/ዕጹብ (መዝ. ፻፯፡ ፳፪) "ልዩ የተፈራ ገናና ታላቅ እግዜር ሳይወጋ የሚገድል ሳይታገል የሚጥል።" "መልኣክ ድምፅ አንድ ነገር።"

ግሪ/ግሪያ (ርያፄ) ቅጣት (የሥግሪያ ርምጃ ትምርት ልማድ)

ግሪሳ መቄ ገረገረ

ግሪሳ፡ መቄ/ነጐዴ (ብዙ ወፍ ወይም ዝንብ ግር ብሎ የሚነሣ)

ግሪን ማግሰኞንና፡ ማግስትን፡ ተመልከት

ግሪክ (ኮች) የነገድ ስም (የጽርእ አገር ሰው የያፌት ዘር የያዋን ተወላጅ)

ግሪዶ፡ ዝኒ ከማሁ

ግራ (ፅግም) በግራ በኩል ያለ ስፍራ

ግራ ቢስ፡ ሥራ የለሽ/ዕውቀት የለሽ/ከርታታ/ችግረኛ

ግራ አገባ፡ አስቸገረ/አወከ (ዕረፍት ነሣ)

ግራ አግቢ፡ አስቸጋሪ/አዋኪ

ግራ እጅ፡ በስተግራ ያለ ፪ኛ እጅ (ደካማ ሰነፍ ከቀኝ እየተጋራ የሚሠራ) (ተመልከት፡ ፫ኛውን ገራ እይ ዘሩ እሱ ነው)

ግራ ገባው፡ ተቸገረ (የሚያደርገውን ዐጣ ታወከ ተጨነቀ)

ግራ ጌታ (የግራ ጌታ) በካህናት አለቃ ግራ የሚቀመጥ የደብተሮች ሹም የቅዱስ ገብርኤል ምሳሌ

ግራ ጐንደር፡ ዳር አገር

ግራ፡ ደካማ/ጐደሎ (ከቀኝ የሚያንስ) ጸጥተኛ

ግራም፡ የሚዛን ስም (ታናሽ ክፍል የኪሎ ሺሕኛ)

ግራምጣ፡ ማእዘን ያለው ጠንካራ ሣር (እንደ ገሣ በረግረግ ውስጥ የሚበቅል ሴቶች እየሠነጠቁ ጕብና ጮጮ ይሰፉታል የትግሬም ልጃገረዶች እሱን እያሸረጡ ባው ዳመት ይጨፍራሉ)

ግራሞች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች

ግራር

ግራር (ሮች) የዛፍ ስም (የታወቀ ዕንጨት እሾኻም ፍልጡ ሲማግዱት እን ኵሮ ምጣድ የሚያጎር የሚያግል ወይም ለዕቃ መጥረቢያ የሚገር (የሚገዛ) በድግር ነት ከሞፈር ጋራ የሚሳብ የሚጐተት ማለት ነው) (ዘፀ. ፳፭፡ ) (ተመልከት፡ ሀሎን እይ)

ግራርያ (ግራራዊ) ያገር ስም (በበጌምድር ያለ አገር ግራራም ባለግራር ብዙ ግራር የበቀለበት ያለበት ማለት ነው ይህ ስም በግእዝ መጻሕፍት ይገኛል በሺ ዋም (ሰላሌ) ግራር ወንዝ ነው) (ተመልከት፡ ገድለ ፊልጶስ ተመልከት)

ግራት፡ ገርነት/መግራት

ግራናማ፡ የቀንድ መብቀያ

ግራንጃ ክፉ ቃል ግራ

ግራንጃ፡ ክፉ ቃል (የሸፍጥ ንግግር የአንጃ መልስ) "አንጃ የቀኝ አሉታ ግራንጃ የግራ አሉታ እንጃ አላውቅም አላውቅም መባባል" (ተመልከት፡ አንጃን ተመልከት)

ግራኝ (ኞች) (ፀጋማይ) " ከቀኝ መጥቶ ተደርቧል" (በግራው የሚሠራና የሚበላ ሰው ግራ ቀኙ) (ተመልከት፡ አባን እይ)

ግራኝ፡ የሰው ስም (በሐረርጌ አውራጃ የተወለደ መሓመድ ገራድ ኢትዮጵያን ባፄ ልብነ ድንግል ጊዜ ፲፭ ዓመት በጦርነት ያስጨነቀ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ አቃጣይ የስላም መሪ)

ግራዋ (ዎች) የዛፍ ስም (ባዲስ አበባ እንደ ሰንሰል በዝቶ የሚገኝ የጕጆ ዐይነት ዕንጨት ጣዕሙ መራራ ኹኖ አፍ ስለሚያዋዋ ወይዛዝሮች ቅጠሉን ቀጥቅጠው ከአጓት ጋራ ይጠጡታል)

ግራዝማች (የግራ አዝማች) በንጉሥ ግራ ጭፍራውን የሚያዘምት የጦር አለቃ

ግራዬ ሆይ፡ የገና ስድብ ዘፈን አዝማች

ግራጫ፡ የበቅሎ መልክ (ግራጭ (ዣርት) የሚመስል በቅሎ እያደር የሚነጣ) "ዳግመኛም ግራ በቅሎን ሲጠሩ ግራጭ ይላሉ።"

ግራጭ (ጮች) ዣርት (የዣርት ስምና መልክ የገላው ጠጕር (እሾኸ) ንጣት ከጥቍረት ያለው አውሬ ጠጕረ ወስፌ የእኸ ልና ያትክልት ጠላት ቁመቱ ዐጪር ስለ ኾነ በማሳ እኸል ላይ እየተንደባለለ ፍሬውን ይበላል)

ግራፍ፡ ጅራፍ

ግሬራ፡ አኮሌ ጮጮ የግልገል አቍ ማዳ "የላም ጡት እየጐተቱ ማለቢያ ስለ ኾነ ግሬራ ተባለ።"

ግሬት፡ በመራቤቴ ውስጥ ያለ አብር

ግር (ርዩፅ/ግሩህ) የተገራ/የተለመደ

ግር ሲል እወፍጮ ሥር፡ ፈሪ ሴታውል

ግር ሲል ገዳይ፡ ጐበዝ የወንዶች ባል

ግር ሲል፡ ሲነሣሣ ሲታወክ ሲተራመስ ሲደበላለቅ

ግር አለ፡ በብዛት ተነሣ (ግው አለ የሕዝብ የባለክንፍ ኹሉ)

ግር አለ፡ ተነሣ ገረገረ

ግር አለ፡ ገረበደ

ግር አለው፡ ቅር አለው (አልገባውም አልተረዳውም) (ተመልከት፡ ቀረን እይ)

ግር()ግሪት፡ ኋሊት/ፊጥኝ "የግርንግሪት ታሰረ ወደቀ" እንዲሉ

ግርመማ፡ ግልምጫ

ግርመት፡ መግረም/ድንቅነት

ግርማ መለኮት፡ የመለኮት ግርማ

ግርማ መንግሥት፡ የመንግሥት

ግርማ ሞገስ (ሞገሰ ግርማ) ወደጃ ባለል መኾኛ መኳንንት በደረታ ቸውና በክንዳቸው የሚያንጠለጥሉት በንጉሥ ዘንድ መወደድን በሕዝብ በኩል መፈራትን የሚሰጥ ያስማት ክታብ "እውነት መኾኑን እንጃ።"

ግርማ፡ መፈራት/አስፈሪነት (የንጉሥ የሞት የምጽአት)

ግርማም (ግርማዊ) ግርማ ያለው (ባለግርማ ተፈሪ አስፈሪ)

ግርማዊ/ግርማዊት፡ የንጉሥና የን ግሥት የስም ቅጽል

ግርማዊነትዎ/ግርማዊትነትዎ፡ አስ ፈሪነትዎ/መፈረትዎ

ግርምቡድ (ጐረመደ) የግንድ ቍራጭ መቀመጫ በርጩማ

ግርምቢጥ ግልብጦ ገለበጠ

ግርስስ አለ፡ ፍልስ አለ (ተገረሰሰ)

ግርስስ፡ የተገረሰሰ (ንቅል ፍልስ )

ግርር (ገሪር) መግረር

ግርር አለ፡ አለልክ ሠማ/ጋለ (ጥብርር አለ)

ግርሻ፡ ኹለተኛ ዕመም

ግርሻ፡ የራስ ዳርጌ ፈረስ ስም (ተመልከት፡ አባን ተመልከት)

ግርሽ (ዐረ.) የገንዘብ ስም (አንድ መሐለቅ) (ተመልከት፡ ቅርስን አስተውል)

ግርሽጥ (ጦች) የቅጠል ስም (ሴቶች ሥሩን ቀቅለው በእንፋሎቱ እግራቸውን የሚያቀሉበት የወይናደጋ ቅጠል) (ተመልከት፡ እንሶስላን ሒናን ተመልከት)

ግርባብ (ትግ. ፈርጅ) ኰረጃ አቍፋዳ (አፈ ከፋታ መኾኑን ያሳያል)

ግርንቡድ በርጩማ

ግርንድስ፡ ወፍራም ግንድ ዐይነት

ግርንግሪት፡ የኋሊት፡ ገረገረ

ግርንግያ፡ ያልጋ ጠፍር

ግርኘታ፡ አሰራ/ኵድኰዳ

ግርዛት (ግዝረት) ዝዘራ/መግዘር/መገዘር

ግርዝ (ግዙር) የተገረዘ (ይሁዲ ፈላሻ ዐማራ ዐረብ ሽፍን ያይዶለ ማንኛ ውም ነገድ)

ግርድ፡ በማጦያ ከምርት የተለየ መናኛ እኽል (ገለባና ሰበር ያለበት የምርት ምክትል "ሚስትና ምርት ገረድና ግርድ በምስጢር አንዳንድ ወገን ናቸው።") (ተመልከት፡ እንቡርቧይን እንችፍን እይ)

ግርድ፡ የጥርስ በሽታ (ጥሮሶችን ራርፎ የሚጨርስ)

ግርድም፡ የተገረደመ ስብር

ግርድፍ፡ የተገረደፈ (ክርትፍ እንቀት ሽርክት ሽርንክት ጕርሦ)

ግርዶ፡ ግርዶሽ/መጋረጃ

ግርጃ፡ የእግር አንባር (እግርን በጌጥነቱ የሚጋርድ)

ግርገራ፡ ቅርቀራ/ግድግዳ/ድርደራ/ተከላ (የመገርገር የመደርደር (ጥገ) የማገር ሥራ)

ግርጌ፡ የእግር ስፍራ፡ (ተመልከት፡ እግር)

ግርግም (ሞች) ከብቶች ሣርና ገለባ እኸል የሚበሉበት የሚቅሙበት (በግ ንብ ወይም በግድግዳ የተሠራ ሞላላ የበረት የጋጣ ቋት)

ግርግም፡ ጫፍ ጫፉ የተሸረፈ (ሸራፋ ሰባራ ግርግም ጥርስ እንዲሉ)

ግርግራ፡ ጭንጫ መሬት ማረሻን የሚገረግር (ገበሬ አዋኪ)

ግርግራት (ስያሕ) ሴቶች ጪስ የሚሞቁበት እግራም ሸክላ ወይም ከንሓስ የተበጀ እንደ ጥዋና እንደ ጥና ያለ ዕቃ

ግርግራት፡ የደረቅ ኵበት ጥፍጥፍ አቋቋም በምድጃ

ግርግር (ሮች) በካብ ላይ የቆመ ዕንጨት (ያልተማገረ ቢማገርም ያልተሸመጠጠ ዐጥር)

ግርግር አለ፡ ሊሸበር ቀረበ (ታወከ ተነሣሣ ተተራመሰ ዕረፍትና ጸጥታ ዐጣ)

ግርግር/ግርግርታ (ወክሕ) ሁከት/ውካታ/ትርምስ "የገበያ ግርግርታ ለሌባ ተመቸው።"

ግርግር፡ በሜዳ ተደጋግፎ የቆመ ጥፍጥፍ

ግርግር፡ እብድ አስተኔ ወፈፌ "እከሌ ግርግር ነው" እንዲሉ

ግርጣት፡ ንጣት/ነጭነት

ግርፋት፡ መግረፍ/መገረፍ/ጥብጥባት (የጅራፍ ቅጣት) (ዘሌ. ፲፱፡ ፳፡ ዘዳ. ፳፭፡ ፫፡ ፪ቆሮ. ፲፩፡ ፳፬)

ግርፋት፡ የጨረር ምች ትኵሳት (ሽፍ ያለ ዕከክ ጅራፍ ያቈሰለው ያሰነበረው ገላ)

ግርፍ (ግሩፍ) የተገረፈ/የተመታ/የተቀጣ (ቍንድድ/ልቍጥጥ/ትኵስ (የተተኰሰ) ወይፈን አሽከር ማደጎ ድፎ ጠባሳ) "ግርፍ አደረገ ገረፈ።"

ግሼ (ግሼቅ ገድ ተክ) ያገር ስም (የመንዝ መዠመሪያ አገር "ግሼ ያው ሳቤ ልጅ" እንዲል ዘር ቈጣሪ) "አንቀጹ ገሣ ሲኾን ትርጓሜው ምንጭ ይባላል።"

ግሼ አባይ፡ በሰከላ ዳሞት ያለ የአ ባይ መፍለቂያ (ተመልከት፡ ግሼንን እይ)

ግሼን (ግሼ) ያገር ስም (ዐጤ ዳዊት ግማደ መስቀል ያኖሩበት (የቀበሩበት) ዐምባ ተራራ "ግሼን ማሪያም" እንዲሉ) "ግሼን ያሠኘው በላዬ ያለው ኩሬ ነው።" "አገሩ የሚገኝበት አውራጃ ዐምባሰል (ዐምባ ዐሰል)" (ተመልከት፡ ዐጢን ተመልከት፡ ሞኝን እይ)

ግሼኖች (ግሼናውያን) የግሼን ዎች የግሼን ተወላጆች

ግሽልጥ አደረገ፡ ግፍፍ አደረገ ( ብስን ቀማ)

ግሽልጥ፡ የተገሸለጠ/የተላጠ/የተመ ለጠ/የተገፈፈ (መለመላ ዕራቍት)

ግሽር (ሮች) የተገሸረ (ቅምጥ)

ግሽር፡ የጋን የማድጋ ውሃ

ግቡ (ግቡእ) ዝኒ ከማሁ ደምን ተመልከት

ግቡ (ግብኡ) ትእዛዝ አንቀጽ ሰዎች አቤት ግቡ

ግቡ ገቢ ተገቢ (ዕዝ ፲፫)

ግቢ (ዐጸድ) ውስጥ፡ ባጥር በቅጥር የተከበበ ቦታ ዐጥር ግቢ እንዲሉ

ግቢ (ግብኢ) በቁሙ የዜማ ምል ክት

ግቢ ነፍስ (ግብኢ ነፍስ) ነፍስ ወደ ሥጋሽ ግቢ ተመለሺ፡ ወይም ሥጋ ወደ መሬትነትሽ ተመለሺ

ግቢ ነፍስ ውጪ ነፍስ በጣረ ሞት ጊዜ ይባላል

ግቢ የጋብቻ ሥርዐት፡ ወይም ጋብቻ (ግጥም) እንቢልታ መለከት የሚነፋው የት ነው፡ አንድም በስርቆሽ በር አንድም በግቢ ነው

ግባ በገመዴ እኔ በምቀጣበት ቅጣት ተቀጣ (ኣስቴ )

ግባ ተመሬት እመሬት ግባ ተቀበር (ግጥም) በተማረው ድጓ በጣፈው ግን ዘት፡ ድረስ ድረስ አሉት፡ ግባ ተመሬት

ግባሳም፡ ግባስ ተሸካሚ/ባለግባስ።

ግባስ/ግባሶ፡ ድቃቂ ሣር/ገለባ/ቈሻሻ/ጭራንፎ።

ግባተ መሬት (ግብአተ መሬት) ሬሳ ወደ መቃብር ሲገባ የሚደረግ ፍታት፡ ትርጓሜው ወደ መሬት መግባት (ግጥም) ግባተ መሬቱን አትድገሙ እናንተ፡ ታዞ ኺዷል እንጂ ልጄ መቼ ሞተ

ግባት (ግብአት) የንጉሥ ግብር መብል መጠጥ (ጐንደር) ደምን እይ

ግባት ሚዛን፡ ኹለት አሞሌ መሣ

ግባት ብዙ የጠመንዣ ተኵስ ሳያቋርጥ እየተመላለሰ የሚተኰስ

ግባት ክተት ሰራዊት

ግቤ ከመኻል የኦሮ አገር የሚነሣ ዠማ፡ ብዙ ፈሳሽ የሚገባበት እሱም ጅማንና ጕራጌን የሚያዋስን ታላቅ ወንዝ ነው

ግቤ የኔ ግብ

ግቤ የዛፍ ስም፡ ዓሣ ማስከሪያ የበረሓ ዕንጨት

ግብ (ግቡእ) የገባ፡ በውስጥ የኾነ

ግብ መጨረሻ መዳረሻ ልክ ነገርከ ግቡ ጋሻ ከንግቡ እንዲሉ

ግብ የነገር መልስ፡ አመጣጥ

ግብ የኳስና የሩር ማረፊያ፡ ኳስና ዕሩር የሚገቡበት ስፍራ፡ የሜዳ ግፍ ዳር ድንበር፡ ወይም ምልክትና የጥንግ አስተራ ረፍ

ግብስብስ፡ የተግበሰበሰ፡ ብዙ ግባስ/ገለባ፡ ጕትት/ክብስብስ ሰው

ግብረ ሐዋርያ፡ የመጽሐፍ ስም፡ ሐዋርያት የሠሩትን ሥራና ያስተማሩትን ትምህርት የሚናገር መጽሐፍ።

ግብረ መርፌ፡ ወፍራምና ጠጕራም ባለዘርፍ ስጋጃ ምንጣፍ፡ ለሱ በሚኾን ወፍራም መርፌ ስለ ተሠራና ስለ ተታታ (ግብረ መርፌ) የመርፌ ሥራ ተባለ።

ግብረ መርፌ፡ ደባደቦ ጨርቅ ወይም የድሪቶ ምንጣፍ።

ግብረ ሥጋ፡ የሥጋ ግብር፡ ወንድና ሴት የሚሠሩት ዕምረት/ሩካቤ

ግብረ በላ፡ በንጉሥ/በመኳንንት ቤት መብል የሚበላ ዘወትር የሚመገብ ካህን/ወታደር (ማንኛውም ሰው ኹሉ።)

ግብረ ገብ፡ ፍጹም፡ ምግባረ መልካም፡ ምግባሩ የቀና ሃይማኖቱ የጠና እውነተኛ ደግ (ጻድቅ) ሰው፡ ሕግ ፈጻሚ ትሑት ነባይ።

ግብረ ጠል፡ በርስቱ ለመንግሥት ያልገበረ፡ ግብርን ጠልቶ የኼደ

ግብራ፡ የዛፍ ስምበጣና ዳር የሚ በቅል ዕንጨት

ግብር መጣጃ፡ ሰዓት

ግብር አቀለጠ፡ ሳይከፍል ቀረ።

ግብር እስከ መቃብር፡ "ሙቶ አስኪቀበሩ ድረስ ግብር አይቀርም፡ አይታጐልም።"

ግብር ውሃ፡ ሴቶች ማታ ማታ ይዘውት የሚወጡ መታጠቢያ

ግብር ገባ፡ በላ/ጠጣ (ሰራዊቱ)

ግብር ገባ፡ ከሰው ተለየ፡ በዋሻ ተከተተ/ተዘጋ፡ ሱባዔ ያዘ

ግብር፡ ዐሥራት/ቀረጥ (ማቴ. ፲፯፡ ፳፬) "ግብር በግእዝ ጸባሕት ይባላል።"

ግብር፡ የማይቀር ግዴታ/ሥራ/ቅዳሴ/የአባት ዕዳ፡ ለባሕርይ የሚስማማ መብልና መጠጥ። "ለተራበ በግብር ለተበደለ በነገር ተገኘ" እንዲሉ።

ግብርና፡ ገበሬነት፡ ማረስ/መቈፈር (የገበሬ ሥራ) (በግእዝም "ግብርናት" ባርነት ማለት ነው)

ግብት አለ ፈጥኖ ገባ፡ ጥልቅ አለ ዘው አለ

ግብት መግባት በውስጥ መኾን

ግብዝ (ተምያን) ድልዝ፡ ውስጠ ሰባራ ብይድ/ቅልቅል ቂራጥ፡ ጥኑ/ጠንካራ/ጥሩ ያይዶለ፡ የተንኰል/የማታለል ሥራ ወይም ነገር። "ግብዝ ወርቅ ግብዝ ፍርድ" እንዲሉ።

ግብዝ (ዞች) መደልው (ፈሪሳዊ) ሰነፍ፡ ይሉኝታ ቢስ፡ ዋሾ፡ ለራሱ የሚያደላ፡ ናዝራዊ/ባሕታዊ (ላየ ደኅና ውስጠ ቀጣፊ) ወይም ላዩ ዳባ ውስጡ ደባ (ማቴ. ፯፡ ፭፡ ኢሳ. ፴፫፡ ፲፬፡ ማቴ. ፮፡ -)

ግብዝ አደረገ።

ግብዝ ኾነ፡ ተገበዘ፡ ተደለዘ፡ ተቀላቀለ፡ "አፈ ጻድቅ ልበ ኃጥእ ኣድላዊ ኾነ"

ግብዝነት፡ ዋሾነት፡ አታላይነት፡ ቀጣፊነት፡ ቅልቅልነት (ሉቃ. ፲፪፡ ፩፡ ሮሜ. ፲፪፡ ፬፡ ፩ጢሞ. ፩፡ )

ግብዣ፡ ጥሪ፡ መብል/መጠጥ/ምግብ።

ግብየታ፡ ግዥ፡ ሸመታ።

ግብድ (ዶች) ወፍራምና ሰፊ ፍልጥ፡ ያልቀጠነ፡ ያልተሠነጠረ፡ ያልተሸነሸነ።

ግብግብ

ግብግብ አለ፡ ትግል ገጠመ ዠመረ።

ግብግብ፡ ሠመር ገብቶ ደረት ለደረት ተጋጥሞ የሚተናነቁት ትንንቅ።

ግብጣ (ጦች) ታናናሽ የጐድን ዐጥንት ከኩላሊት ጋራ።

ግብጣ፡ ሕፅን፡ ሾለቅ፡ ሠላጤ፡ ቅድ፡ ወሽመጥ።

ግብጥ ገበየ

ግብጥ (ግብጽ/ቅብጥ) የነገድና ያገር ስም፡ የካም ዕጣ፡ የእስያና የአፍሪቃ ወሰን/ደንበር።

ግብጥ ምስር፡ ሻሞች/ዐደስ ምስሪ የሚሉት ከግብጥ የመጣ የግብጥ ምስር ወጥ፡ "ብርስነ ግብጽ" ማለት ነው።

ግብጦ (ተርሙስ) የደንጐሎ ዐይነት መራራ እኸል፡ "ግብጣዊ" ማለት ነው።

ግብጦ፡ ጠጠር ጣዮች በግብጦ የሚቈጥሩት የግብጦ ቍጥር ጥንቈላና መላ።

ግብጦች (ግብጻውያን) የግብጥ ሰዎች/ቅብጦች

ግቦ እየጣፈጠ ወደ ሆድ የሚገባ የመኳንንት ምግብ

ግተም፡ የንጨት ስም (ሎል የሚመ ስል ዛፍ ፍሬውን ጦጦና ዝንጀሮ የሚገት መው ቅጠሉ ሰበከተ ነጭ ወዙ አረንጓዴ)

ግተት (አብድ) ከርፋፋ/ሞኝ/ቂል

ግታም፡ ግተ (ትልቅ ላም ፍየል )

ግት በቁሙ ጋተ

ግት (ግቱዕ) የተገታ/የታገደ ( ግድ ውስን ክልክል)

ግት (ግዕት) በጡት ውስጥ የታ ቈረ/የተቋጠረ ወተት (ያራስ የንቦሳ የግልገል የውርንጭላ ምግብ)

ግትልትላም፡ ቅጥልጥላም ቍጥርጥ

ግትልትል፡ የተግተለተለ/የተያያዘ ( ጥልጥል)

ግትም አደረገ፡ ጨርሶ ቃመ (ተመልከት፡ ፬ኛውን እይ)

ግትም፡ የተገተመ/የተቃመ

ግትር አለ፡ ውጥር አለ/ቅስር አለ (ተገተረ)

ግትር ግትር አለ፡ ውጥር ውጥር ውትር ውጥር አለ (ተገታተረ ተላሳበ ተወጣጠረ)

ግትር፡ "ይስበረኝ ይሠንጥረኝ የማይል ፊት ለፊት እውነቱን እቅጩን ተናጋሪ ሰው ነገረ ጠንካራ።"

ግትር፡ ልጥጥ ውጥር ቅስር ድክር

ግትር፡ ስል ያይዶለ ዕርፍ ማረሻ ወይም ስበት

ግትርትር አለ፡ ውጥርጥር ውትርትር አለ

ግትቻ (ግተት) የማንኛውም ስፌት ዕላቂ (ዐመድና ጥራጊ ፍግ ማውጫ ኣሮጌ የኾነ) "ግተት ግእዝ ግትቻ ዐማርኛ ነው"

ግትን፡ የተገተነ (ቡጭቅ ዝንትር)

ግትግት፡ የተገተገተ (ንክስ ዕኝክ)

ግቻ (ግጫ) የስንደዶና ያክርማ ሌላውም ሣር ቅሬታ (የማጭድ የከብት ራፊ)

ግቻ የሣር ቅሬታ ገታ

ግነዛ (ግንዘት) ጥቅለላ/አሰራ (የመገነዝ ሥራ)

ግናዝ/ግንዛት፡ እስራት/ቍጥራት

ግንቡል (ሎች) (ግንጱል) ወፍራም/ደንዳና ዓሣ የተጋደመ ጋድሚያ .... "የስብስቴ ግንቡል ጊዮርጊስ ደብተራ እንዳለ ታቦት ዘፋኝ ዞረ።"

ግንባረ ቦቃ፡ ፊተ ነጭ ከብት

ግንባረ ደረቅ፡ ዕፍረተ ቢስ "ይሉኝ አይልም።"

ግንባራም፡ ግንባረ ፈጣጣ

ግንባራም፡ ጠላት የማይቆምለት ዕድላም ድል አድራጊ አሸናፊ

ግንባር (ሮች) ገጽ (ከሰርንና ከሽፋል በላይ ያለ ገላ ፊት ስፍራ) (የጐሽ ግንባር) የስንዴ ስም (ነጭ ስንዴ ዐጪር) "ግንባርን ገጽ ማለት በከፊል ነው።"

ግንባር ለግንባር፡ ፊት ለፊት

ግንባር ቀደም፡ በኵር/አለቃ/ዋና/አንጋፋ

ግንባር ጸያፍ፡ ወርቅ ቀድሞ ከሠም ሲናበብ ግንባር ጸያፍ ይባላል

ግንባር፡ ዕድል/ሀብት/ገድ

ግንብል ግንብል አለ፡ ግልብጥ ግልብጥ አለ

ግንብል፡ የተገነበለ (ግልብጥ)

ግንብብ፡ የዝነበበ (ባዶ አገዳ ጣራ እንደሌለው ግንብ የተገተረ)

ግንብጥ፡ ከድብድብነት ያለፈ (ያገዳ የበቈሎ የብር እኸል ፍሬ ብቅ ያለ)

ግንብጥ፡ የገነበጠ (የጐን (የገቦ) ቅጥይ ፍሬያዊ)

ግንቦት፡ የወር ስም፡(ተመልከት፡ ገነባ)

ግንትር፡ የነተረ ሥጋ ጭብጥ ያለ (ገርዳዳ ዐኞ)

ግንኙ (ዎች) የተገናኘ/የተጋጠመ/የተያያዘ (ድርብርብ ንብብር ቅልቅል)

ግንኙ፡ የተጋጠመ፡ (ተመልከት፡ (ገኘ፡ ገነኘ))

ግንኙነት፡ መገናኘት/ተገናኝ

ግንኝ/ግንኙ፡ ግጥም

ግንኝት፡ ዝኒ ከማሁ

ግንኝነት፡ ግንኙነት

ግንዘት (ቶች) የመጽሐፍ ስም (ለሞቱ ሰዎች ስለ ፍታት የሚደገም የሚጸለይ ጣፍ ከቅዱስ አትናቴዎስ የተደረሰና የተጣፈ ባለ፯ ምዕራፍ)

ግንዝ (ግኑዝ) የተገነዘ (ጥቅልል ሽፍን እስር ክፍን)

ግንደ ቈርቍር፡ ግንድ ቈርቍሮ የሚበሳ የቅንቡርስ ዐይነት ቡልማ ትል "ደንቈር የሚባልም ወፍ ትሉን ለመብላት ግንድ ይቈረቍራል "

ግንደ በል፡ የዘመቻ መሬት ያለው ጭፍራ (በጦርነት ጊዜ ሥንቅና ድንኳን ጝኝ ተራዳ ተሸካሚ) (ተመልከት፡ ግደ በል "በግድ ጭኖ የሚበላ።")

ግንደ በረት፡ ከሙገር በስተግራ ያለ አገር

ግንዲላ፡ ያልተጠረበ ዕንጨት ግንድነት ያለው

ግንድ (ዶች) (ጕንድ) በሥርና በዐጽቅ መካከል ያለ ያልተቈረጠ ወፍራም ዕንጨት (ርጥብ)

ግንድ ዐመድ፡ (የግንድ ዐመድ) የሰራዊት ብዛት ብዙነት

ግንድ፡ መደብ/ሥር/መብቀያ "ዦሮ ግንድ" እንዲሉ

ግንድ፡ ተቈርጦ ሥራ ያሊያዘና የያዘ ደረቅ ዕንጨት (ደንዳና የእግር ማሰሪያ የፊት ግንድ ዐጋዥ ግንድ) "በወደቀ ግንድ መጥረቢያ ይበዛበታል" እንዲሉ

ግንድ፡ የትውልድ መዠመሪያ አባት

ግንድስ፡ ዝኒ ከማሁ (የተገነደሰ ስብር ሥንጥቅ)

ግንዶሽ በቁሙ ግንድ

ግንዶሽ፡ የጅራፍ የዥራት ግንድ

ግንጃር (ሮች) በሱዳን ቈላ ያለ ሻንቅላ

ግንገና፡ ፍራት/ጥርጠራ/ጥርጣሪ/ሥጋት

ግንጠላ፡ ቈረጣ/ሰበራ (የመገንጠል ሥራ)

ግንጣር፡ ቅንጣር

ግንጣይ፡ ዝኒ ከማሁ

ግንጥል (ሎች) ከቃታው አጠገብ የሚገነጠል ባለ፪ አፍ ማደኛ ጠመንዣ

ግንጥል አለ፡ ተገነጠለ (ወደ ጐን ወረደ)

ግንጥል ጌጥ፡ የማያምር ልዩ ጌጥ (ለሰውነት የማይስማማ)

ግንጥል፡ የባላ ዛቢያ ሲቈፍሩበት "ግንጥል" የሚል (ተመልከት፡ ወደደን)

ግንጥልጥል አለ፡ ተገነጣጠለ

ግንጥልጥል፡ የተገነጣጠለ (ብጥስጥስ)

ግንጭል (መንሰክ) ልዩነት ያለው ታችኛ መንጋጋ ማላመ አገጭ

ግንፈላ፡ ፍላት/ፍልቅ ማለት

ግንፊጥ (ጦች) ታዛ/ታዛይ (የሰበሰብ ቅይድ ልጥፍ ቤት) "ዘሩ ገነበጠ ነው።"

ግንፍሌ፡ የገነፈለች (ግልፌ)

ግንፍል አለ፡ ፍልቅ አለ/ፍስስ አለ

ግንፍል ግንፍል አለ፡ ፍልቅ ፍልቅ ፍስስ ፍስስ አለ (መላልሶ ፈላ ጠላው ጠጁ በናው ውሃው)

ግንፍል፡ የገነፈለ (የባቄላ በቈልት ሙዳ ሥጋ ወይም እንፊሎ)

ግዕዘ ብሔር፡ ያገር ልማድ

ግዕዛን፡ ነጻነት/ሐርነት "ግዕዛን የሌለው እንስሳ" እንዲሉ

ግእዛዊ ተረት) "ኣነ አእምር ግብሮሙ ለቈራብትየ" "ቈራብትን ሥራ እኔ ዐውቃለኹ" አለ ዥብ ።ቈራብት ቈራቢዎች ተብሎ ቢተረጐም ግን ሰሞነኞች ለሳታት ለተልእኮ ሌሊት መኼዳ ቸውን ያስረዳል።

ግእዜ (ገዝአ ግዝእ) ጐዶ ሬዳ ድግስ መሰናዶ ፍሪዳ ያለበት የመብል የመጠጥ የምሳ በዓል (ኢዮ ) ግዝኡ ባለ በቀና ነበር

ግእዜ ገባ

ግእዝ "ሰፈርጐል" ይለዋል

ግእዝ (ግኢዝ ግእዘ ገአዘ) የቋንቋ ስም፡ ሴማዊ አዳማዊ ልሳን፡ ከሱርስትና ከዕብራይስጥ ከዐረብ የሚገጥም ዘይ ቤው አንድ መዠመሪያ፡ ምስጢሩ ጥንታዊ አዳማዊ ማለት ነው ግእዝ አንድ መባሉ በአ ምክንያት መኾኑን አስተውል

ግእዝ ገደልከ ያለው ገደልኸ በመባል -- ንታ ገደልክ ተብሎ ይጻፋል። ኸን፡ እይ። አለ፡ ድምጥ/ሰጠ፡ ("ኳኳኩቤ") ክንፍ አልባ ፌንጣ ("ኰበኰበ")

ግዕዝ፡ ባህል/ልማድ

ግእዝ የንባብ ስም፡ ከወርድ ንባብ የሚቀድም፡ ሕፃናት የፊደልን ቍጥር እጅ እግሩን ከለዩ በኋላ ከነቍጥ እስከ ነቍጥ የሚያግዙት ማጋዝ

ግእዝ የዜማ ስም፡ አንደኛ ስልት፡ መዠመሪያ ዜማ የአብ ምሳሌ

ግእዝ የፊደል ስም፡ አንድ ወጣት አንድ ቅንጣት ዕዝል ቅጥል ነቍጣ ምክትል (ዋየል) የሌለው ቀንጃ ነጠላ ፊደል ከአ እስከ ያለ፡ አንድ አንደኛ መዠመሪያ ማለት ነው ግእዝ ግእዝ ግእዝ እንዲሉ የአን አፈታት እይ

ግእዝኛ (ግእዛዊ) ዝኒ ከማሁ፡ ፊተኛና ኋለኛ ፊተኛው ነገሠ ረመሐየ ኋለኛው ንጉሥ ረምሓይ እያለ በአኵስም መሐ ልቅና ሐውልት ላይ ተቀርጾ የሚታይ

ግው (ጎግዎ/ጎገወ) ግር/ግም/ብው

ግው አለ፡ ግር አለ/ግም አለ/ብው አለ "የኹሉንም ፍች በየስፍራው ተመልከት ገረገረ ገመገመ።"

ግዘታ፡ ውግዣ/ውግዘት/ልየታ/ክልከላ

ግዙ/ግዝ (ግዙእ) የተገዛ/ተገዥ (ባሪያ/መግዞ)

ግዙር፡ የተገዘረ (ግርዝ)

ግዙርነት/ግርዝነት፡ ይሁዲነት/ፈላሻነት

ግዙፍ፡ የገዘፈ/የደነደነ/ደንዳና

ግዛ (ትግ. ግዛዕ) አንዳች ምናምን

ግዛ ምዛ (ትግ. ግዛዕ/ምዛዕ) ምናምን ነገር/ጣጣ/ሰበብ/ምክንያት "ይህ ሰው ግዛ ምዛ ያበዛል።" (ተመልከት፡ ምዛን)

ግዛት (ቶች) (ግዝአት) ወረዳ/አውራጃ/ቀበሌ/ይዘታ/ርስት/ጕልት/መንግሥት (መክ. ፮፡ ፪፡ ሕዝ. ፳፱፡ ፲፰) (ተመልከት፡ አገርን)

ግዜ፡ ዝኒ ከማሁ

ግዝረት፡ መግዘር/መገዘር/ገዘራ

ግዝረት፡ በጥር ቀን የሚውል የጌታችን የኢየሱስ በዓል።

ግዝራት/ግርዛት፡

ግዝት (ውጉዝ) የተገዘተ/የተወገዘ/የተለየ/የተከለከለ (ክልክ) "አንተ ይህን እንዳታደርግ ግዝት ነኸ።"

ግዝት (ግዘት) መገዘት/መገዘት/ማላ/ክልከላ/ውግዣ/ርግማን "እከሌ ግዝት አፍራሽ ነው" እንዲሉ።

ግዝገዛ፡ ክርከራ/ምገዛ/ክርከማ።

ግዝግዝ (ግዙዝ/ግዙዕ/ውሡር) የተገዘገዘ/የተመዝዘ (ክርክር/ምግዝ/ክርክም)

ግዝፈት፡ ውፍረት/ድንዳኔ።

ግዝፊያ፡ ዝኒ ከማሁ/መግዘፍ።

ግዞተኛ (ኞች) የተጋዘ/የተሻረ/የታሰረ (ሽር እስረኛ)

ግዞተኛነት ሽር መኾን/እስረኛነት

ግዞት (ግእዘት) ሽረት/እስራት/ቅጣት/ውርደት/ወህኒ (ዘፍ. ፴፱፡ , ፳፪, ፳፫፡ ኢሳ. ፵፪፡ ፯፡ ማቴ. ፭፡ ፳፭)

ግዡ፡ የጋዥ/የከፋ/ክፉ/የተበላሸ/ብልሹ/መጥፎ ዥዡ

ግዥ፡ ግብየታ/ሸመታ።

ግዥል፡ ውዳቂ

ግዥልዥል፡ ረዥም ጕትት ውዥምጎም

ግዮን፡ ነጭ አባይ (ግእዝ)

ግዱፍ፡ የተገደፈ/የተጣለ ዝልጕስ

ግዳም፡ ግድ ያለው/ባለግድ (ወፍራም/ቦርም)

ግዳይ (ግዱል/ቅቱል) የተገደለ/የሞተ (ሬሳ/በድን የማይሰማ/የማይለማ ሰለባ) (ሕዝ. ፳፩፡ )

ግዳይ ጣለ፡ ሰላባ አሳየ/ፎከረ።

ግዳይ፡ መግደል። "ነፍሰ ግዳይ" እንዲሉ።

ግዳዮች፡ ሬሶች/በድኖች (ኤር. ፳፭፡ ፴፫)

ግዳጅ (ትክቶ) የሴቶች አበባ በወር በወር የሚፈስ ደም። "ባላገሮች ግን በኦሪት ሕግ አደፍ፡ ካህናትም መርገም ይሉታል።"

ግዳጅ፡ ችግር/መፍቅድ (በግድ የሚፈለግ ነገር/ጕዳይ) "ግዳጅ አለኝና አንተ ዘንድ እመጣለኹ።"

ግዴታ (ዎች) ማስገደድ/መገደድ (ግድ/ግድነት) "በግእዝ 'ግደት' ይባላል።"

ግድ አለ (አገበረ) በግድ አዘዘ/አስቸገረ/ወጥሮ ያዘ

ግድ አሠኘ፡ አስባለ/አናገረ በግድ

ግድ የለሽ፡ ዐሳብ የለሽ "ምን ቸረኝ ባይ።"

ግድ፡ "እንደ '' '' ሲሰማማው 'የግድ' ይላል።"

ግድ፡ ሥብ (የማዥራት ሥጋ እንደ ዕርከን ኹኖ የሚታይ መተንፈስና መኼድ የሚከለክል) (ተመልከት፡ ቅርድን ቀረደደ)

ግድ፡ ውድና ፈቃድ የሌለበት ሥራ/ነገር/ግብር (፩ሳሙ. ፳፡ ፳፰) (ግጥም) "ግድ የለም ግድ የለም ሰው እንዳይኾን የለም።"

ግድ፡ የተጋዳ/የተጠለፈ።

ግድል አደረገ፡ አደበነ።

ግድመት፡ ዝኒ ከማሁ ለግድም (ኢሳ. ፲፭፡ )

ግድም አለ፡ ረብ አለ/ጐኑ ምድር ነካ።

ግድም፡ ገደማ ዘንዳ። በመንዝ ውስጥ ያለ አገር። "ግድምና ኤፍራታ" እንዲሉ።

ግድርድር፡ የተግደረደረ (ኵሩ/ግብዝ ሲበዛ ግድርድሮች ያሠኛል)

ግድብ፡ የተገደበ/የተከተረ (ክትር/ድልድል/የታገደ እግድ) "መሬትንና ውሃን ባንድነት ያሳያል።"

ግድቦች፡ ክትሮች/ዦሮች።

ግድነት፡ ግድ መኾን

ግድንግዲ ያሞራ ስም፡ ግድ

ግድንግድ (ዶች) በሜዳ ላይ

ግድያ (ቀትል) ሰልፍ/ውጊያ/ውጊት/ጦርነት/ትግል/ትንንቅ

ግድገዳ፡ ተከላ/ውጠራ።

ግድግዲ/ግድንግዲ፡ ታላቅ እሞራ ነጣቂ ግልገል አንሣ (የሎስ ጐሢ) "እንደ ግድንግድ በምድር ቍሞ ተገትሮ የሚታይ" (ዘሌ. ፲፩፡ ፲፱)

ግድግዳ (ዶች) (ገድገድ) ቦግንብ ፈንታ ቍሞ የተማገረ ጣራ ተሸካሚ ብዙ ዕንጨት (ዘፀ. ፴፯፡ ፳፯)

ግድግዳ፡ መዠመሪያ ስንኝ (ተመልከት፡ ዘለሰ ብለህ ዘለሰኛን እይ)

ግድግድ፡ የተገደገደ/የተተከለ/የቆመ ውጥር

ግድፈተ ጸሓፊ፡ የጻፊ ቃልን መዝለል

ግድፍት፡ ፍስክ/ፋሲካ ብሎት ገናና ጥምቀት ጦም የቀረበት ሥጋ የሚበላበት ማንኛውም ቀን። "በግእዝ ግን 'የተገደፈች/የተጣለች' ማለት ነው።"

ግጃዋ (ጊዜዋ) የንጨት ስም (ጠላ እንዳይበላሽ ሴቶች እጥንስስ የሚያገቡት ዕንጨት)

ግጅል (ግዱል) አእምሮ ቢስ/ሞኝ/ቂል/ውዳቂ።

ግጋም፡ ግጉ የሚነቀል/የሚመነገል ልጅ ወይም ዘር/ነገድ። "መንቀያውም ታናሽ ቈላፋ ብረት ናት።"

ግግ፡ ጋጋኖ

ግግ፡ መዠመሪያ ድድን ሠንጥቆ በላይና በታች የሚወጣ የልጆች ጣጣ የሚያስቀምጣቸው/የሚያስቀዝናቸው የወተት ጥርስ (ካደገ በኋላ ክራንቻ ይባላል) "ግግ የመነገገና የሞገገ ዘር ነው።"

ግግር አለ፡ ተጋገረ፡ ልክክ ኣለ፡ ተሰጣ

ግግር፡ ዝምተኛ ሰው።

ግግር፡ የተጋገረ/የረጋ/የጠና (ሠም/ሞራ/ደም/ቅባት የመሰለው ኹሉ።) (ተረት) "ንግርና ግግር ሳይደርስ አይቀር።"

ግጣም (ሞች) ለጠብ መግጠሚያ

ግጣቢ፡ ቅንነት የሌለው ሲጠሩት ወይ የማይል ክፉና አልምጥ ልጅ ለዛ ቢስ መታዘዝና ትሕትና አልባ

ግጥ) ዕግዝ (ሕጉዝ) የታገዘ የተረዳ ያረፈ

ግጥሚያ፡ መግጠም/አገጣጠም ( ነኛ ተሰማሚ ውድ ግንኝነት ቀረቤታ)

ግጥም (ሞች) የተገጠመ/የተዘጋ/የታተመ/የታሸገ (ዝግ እሽግ የዘፈን ስንኝ) (፪ዜና. ፴፭፡ ፳፭)

ግጥም አለ፡ ልክክ አለ/ሞተ/ዐይኑ ተከደነ/አፉ ተዘጋ "እከሌ ሳይታመም ድንገት ግጥም አለ ሞላ ሙሉ ኾነ።"

ግጥም አለ፡ ጨለመ "ስዓቱ ግጥም ቢል ይህን ነገር አላደርገውም።"

ግጥም አደረገ፡ በጥፊ መታ/አጥብቆ አሰረ/ጨልጦ ጠጣ "መላ ምሉዕ አደረገ።"

ግጥም ገጣሞች አረኾዎች ድምፀ ረዣዥሞች ወንዶችና ሴቶች

ግጥም) "ነፍሴ ለሥጋ ስትሣሺ ፍሪዳ መጣልሽ፡ እኔ በመሣሌ ምነው መሣቅሽ፡ ዘው ዲቱ ምኒልክ ፍሪዳ አለብሽ" ("(አገኘኹ እን ግዳ)")

ግጥም) "እሱ ጥቍር ጐራዴው ሽቅርቅር፡ ምጣ ወይ ይቅር"

ግጥም) "ያውና እዚያ ማዶ ፍሪዳ ተጥሏል፡ ቢላዋው ደንዞ ልብ አልቈ ርጥ ብሏል"

ግጥም) ያውና እዚያ ማዶ (ያውና እዚያ ላይ - የናጅራች አገር የነሰው ገዳይ - ለወንዶ ችም ይነገራል ")

ግጥም "እንደነራስ ወሌ ነጋሪት የለኽ በቶሎ አትኬድም ወይ ንጉሥ ሲጠሩኸ")

ግጥም "የከንፈሯ ለዛ የጕንጯ ሙስና ዐርብ ሮብ ያስክዳል እንዃን ዐሙስና")

ግጥም፡ ምሉዕ ዕቃ ርስ በርሱ የሚ

ግጥምጥም አለ፡ ተገጣጠመ/ተሳካ

ግጥምጥም፡ የተገጣጠመ

ግጥብ አለ፡ ተገጠበ

ግጥብ አደረገ፡ ምልጥ አደረገ

ግጥብ፡ የተገጠበ/የተመለጠ (ሣር/ቅጠል የሌለበት መሬት ንክ የስና የከብት ዠርባ)

ግጥብጣቢ/ግጥብጥብ፡ የተገጣጠበ (በብዙ ስፍራ ተገጥቦ የቈሰለ ምልጥልጥ)

ግጥብጥብ አለ፡ ተገጣጠበ

ግጥገጣ፡ ቅጥቀጣ ምት

ግጥግጥ፡ የተገጠገጠ (ቅጥቅጥ የመብራት ዕንጨት ክትክታ ፍየለፈጅ)

ግጦ፡ በቡልጋ ክፍል ያለ ቀበሌ "ግጠኸ ውጣ በጭንቅ በችግር ሠርተኸ ወርስ።"

ግጦ፡ ግጦሽ/ለቀም (ሣር/ደንጊያ)

ግጫ (ግቻ) ከብት የነጨው/የጋጠው በመሬት ላይ ያለ ያጪር ሣር ቅሬታ

ግጫ/እንግጫ (ጮች) የንቍጣጣሽ ሣር/እንቍጣጣሽ (ኢሳ. ፲፱፡ ፲፭)

ግጭ፡ ትእዛዝ አንቀጽ ምታ ለትም ኰርኵም

ግጭ፡ አገጭ (በታችኛ ከንፈር ሥር ያለ ሾጣጣ ገላ) "የመንጋጋውን መጋጨትና መፋጨት እንደ መጅና እንደ ወፍጮ መኾኑን ያሳያል።" (ተመልከት፡ ለገን ግንጭልን መንገጭሊን)

ግጭት (ቶች) (ድድቅ) መግጨት

ግፈኛ (ኞች) ዐመፀኛ/በደለኛ/ክፉ አድራጊ/ቀማኛ (መዝ. ፻፴፱፡ , ፲፩፡ ምሳ. ፫፡ ፴፩፡ ሉቃ. ፲፮፡ ፲፡ ሮሜ. ፫፡ )

ግፈኛነት፡ ዐመፀኛነት/በደለኛነት

ግፈኝነት፡ ዝኒ ከማሁ (ሮሜ. ፪፡ )

ግፉዓን፡ የተገፉ ሰዎች (የደብረ ሊባኖስ ጠበል) "ግፉዕና ግፉዓን ግእዝኛ ነው ግፉዓን ጠበለተኞች ናቸው ሲጠመቁ ይገፋሉና።"

ግፉዕ፡ የተገፋ/የተበደለ

ግፊ/ግፊያ፡ የመግፋት ሥራ

ግፋ ወሰን፡ የሰው ስም

ግፋን፡ የቍርጥና የመት የፍጥነት የቀጥታ መንገድ ሳያመነቱ ግራ ቀኝ ሳይሉ መኼድ (ርምጃ መቀጠል)

ግፍ (ግፍዕ) በቁሙ በደል/ዐመፅ/ክፉ ሥራ (ሉቃ. ፲፮፡ )

ግፍ ሠራ፡ ነፍስ አጠፋ/ገደለ

ግፍ ተዋለበት፡ ተሠራበት/ተደረገበት

ግፍ፡ ቅርፊት፡ (ተመልከት፡ ገፈፈ)

ግፍልፍል፡ ተጫዋች ሰው

ግፍልፍል፡ የተግፈለፈለ (የድርቆሽ)

ግፍት አገር፡ ገፈተ

ግፍት፡ ያገር ስም (በታችኛው ወግዳና በተጕለት ውስጥ ያለ አገር) "ግፍት ከወይና ሲናበብ የንጨት ስም ይኾናልና ወይናን እይ የግፍት ትርጓሜ ማቃጠልንና መግፈፍን ያሳያል።"

ግፍንት፡ ገልቱ ዕውቀተ ቢስ ሴት

ግፍገፋ፡ ዐጨዳ/ጠረጋ/ቅርደዳ

ግፍጥፍጥ፡ የተግፈጠፈጠ (በምድጃ እየጨሰ የሚነድ ግንድና ኵበት)

ጎሐ ጽባሕ፡ የመጻፍ ስም (ብላቴን ጌታ ኅሩይ ጽፈው ያሳተሙት መጻፍ) "ማተሚያ ቤቱም 'ጎሐ ጽባሕ' ይባል ነበር።"

ጎሐ ጽባሕ፡ የንጋት ውጋገን

ጎሐ ጽዮን፡ ያገር ስም (በሰላሌ አውራጃ ያለ አገርና መቅደስ) "የጽዮን ጎሕ ማለት ነው።"

ጎሕ (ገዊሕ/ጎሐ) ከንጋት በፊት ደም መስሎ የሚታይ ብርሃን (የመንጋት ምልክት)

ጎሕ ሲቀድ፡ ጎሕ ሲያበራ/ሲያሳይ "መንገደኛው ጎሕ ሲቀድ ተነሥቶ ኼደ።"

ጎሕ ቀደደ፡ አየሩን የሌሊቱን ጨለማ ከፈለ/ሠነጠቀ/ኣበራ/አሳየ

ጐለለ (ቈለለ) ጕልላት ሠራ/አበጀ (በቤት ቍንጮ ላይ አኖረ ክዳን ጨረሰ)

ጐለለ፡ ቀለም አበዛ ሲጽፍ

ጎለልታ፡ ገለል ማለት

ጐለመ፡ ከፈለ/ለየ/ቈረጠ/ሰጠ መሬትን "በትግሪኛም 'ገመጠ' ማለት ነው 'ፈለ' ካለው ይገባል።"

ጐለመሰ፡ አሞላ/አካለ መጠን አደረሰ/ጐረመሰ/ጐበዘ/ሪዝ አወጣ/አቀመቀመ/ጸና/በረታ

ጐለሰ፡ በዛ/ፈደፈደ

ጐለሰሰ፡ ፈጥኖ አሸነፈ/አደከመ/ጣለ/ተጫነ/ጨቈነ/ጐለፈጠ/ጐለፈፈ/ረፈቀ/ኣሳፈረ

ጐለሰስ/ጐልሳሳ፡ የተጐለሰሰ (ሽንፍ ጭቍን ደካማ አሮጌ)

ጐለበ (ገለወ) በቈዳ ለጐመ/ለበደ/ሸፈነ/ጠፈረ (የከበሮ/የሌላም ነገር) "ትግሬ ግን 'ጐለበን' ተቀለሰ ጐበጠ ይለዋል።"

ጐለበተ፡ በረታ/ጠና/ጠነከረ/ዐየለ

ጐለተ (ጐልቶ/ጐለተ) ጕልቻን ተከለ/ጠመዘዘ/አቆመ (ለካህናት ለመኳንንት ለወይዛዝር ጕልትን ከለላ ሰጠ ሰውን አስቀመጠ ረፈቀ)

ጐለት፡ ጭጐት

ጐለንዳ፡ እባብ ከይሲ

ጐለንዳ፡ ወምበርቲ

ጐለደመ፡ አናጋ/ለየ/ዐጠፈ/ኰረተመ/አወጣ

ጐለደፈ (ለደፈ) ፈጽሞ ደነዘ/ላሸ/ስለትና ሹለት ጥፍር ትባት ዐጣ/ለንባዳ ኾነ (፩ሳሙ. ፲፫፡ ፳፩፡ መክ. ፲፡ )

ጐለደፍ/ጐልዳፋ/ጕልድፍ፡ ደነዝ (ዕውር ጣት ለንባዳ አንደበት)

ጐለጐለ፡ ቈነጨ/ነሰነሰ/ለቀመ ዐረምን ሰርዶን (ኢዮ. ፴፱፡ ፲፡ ሆሴ. ፲፡ ፲፩)

ጐለጐለ፡ ናደ/አበላሸ ልቃቂትን

ጐለጐለ፡ አፈጠጠ/አጐረጠ ዐይንን

ጐለጐለ፡ ኣወጣ ምላስን ንፍጥን አንዠትን

ጐለጐል፡ ከዋሻ የወጣ ነብር/አነር (የነብር ዲቃላ ከልብሱ ውስጥ እግሮቹንና ዐንገቱን ብቅ ያደረገ ዔሊ የልጆች ማስፈራሪያ)

ጐለጠመ፡ ሰበረ/አነከተ/ቀለጠመ

ጐለፈጠ፡ ጐለፈፈ

ጐለፈፈ፡ በርጅና ከሳ (ተገብሮ)

ጐለፈፈ፡ ጐለሰሰ (ገቢር)

ጐላ (ስም) ታላቅ የብረት ጋን ወይም ድስት ( ፍሪዳ ዳውላ እኸል የሚቀቅል)

ጐላ (ጐሊሕ) መጕላት

ጐላ (ጐሊሕ/ጐልሐ) ከመቅጠን/ከርቀት ራቀ ጕልሕ ኾነ ገዘፈ ወፈረ ከሩቅ ታየ ደመቀ (የጥፈት/የጥቃቅን ነገር)

ጐላ ሰፈር፡ በአዲስ አበባ የሚገኝ የጐላ አፃር ሰው ሰፈር

ጐላ አለ፡ ጐላ

ጐላ፡ ያገር ስም (በባሶ ወረዳ ያለ ቀበሌ)

ጐላሚ፡ የጐለመ/የሚጐልም (ምድር)

ጐላቢ፡ የጐለበ/የሚጐልብ (ለባጅ)

ጐላች (ቾች) የጐለተ/የሚጐልት (ጕልት ሰጪ ተካይ ከላይ)

ጐላዎች፡ ታላላቆች ጋኖች ድስቶች

ጐላይ (ዮች) የጐለለ/የሚጐልል (የሚጭን ከዳኝ)

ጐሌ ገለበ

ጐሌ፡ የሰው ስም (በመንዝ የአፍቀራ ባላባት) "ጕልላቴ ማለት ነው።"

ጐልማሽ፡ የሚጐለምስ

ጐልደያ፡ በኦሮ ቤት በከፋ ክፍል ያለ አገር

ጎልጎታ፡ የራስ ዐጥንት (ራስ ቅል) "ጌታ የተሰቀለበት ስፍራ የአዳም መቃብር።"

ጎልጎታ፡ የጸሎት መጽሐፍ በመቤታችን ስም የተጻፈ

ጐልጓይ (ዮች) የጐለጐለ/የሚጐለጕል (የሚቈነጭ ለቃሚ አውጪ)

ጐልፋጣ/ጐልፋፋ፡

ጐልፋፋ/ጐልሳሳ፡ ከሲታ

ጎመ (ገዪም/ጌመ) ጉም ኾነ (ዐፈነ ሸፈነ ጠቀጠቀ) "ዐጕልና ገቢር መኾኑን አስተውል።"

ጐመ፡ ዐለቀ/አነሰ//ጕጣ መሰለ/ኣከለ

ጐመለለ፡ አንበስኛ ዝንጀርኛ ኼደ (ተመልከት፡ ጐደደንና ጀነነን እይ)

ጐመረ፡ ነፋ/አሳበጠ/አኰራ

ጐመራ (ጻዕደወ) በሰለ/ነጣ/ገረጣ (የሰብል)

ጐመርታ፡ ሽበት የወረረው ያርባና ያምሳ ዓመት ሐርበኛ (ብስል ሰው የጦር ገበሬ)

ጐመተ፡ ርጥብ ሥጋን ሙዳ እያደረገ ጭብጦ ያካክል ጐመደ/ቈረጠ/ከፈለ " የደ ለውጥ መኾኑን አስተውል።"

ጐመተ፡ ትልቅ አደረገ

ጐመን (ኖች) የተክል ስም (ተክል ተቀቅሎ የሚበላ ቅጠል ፍሬው ማሠሻ ሲያደርጉት የሚያር የሚገምን)

ጐመን በጤና፡ በሽተኛ ኹኖ ሥጋ ከመብላት ጤንነት ካለ ጐመን ይሻላል

ጐመን ዘር፡ የጐመን ዐይነት ዘረር

ጐመን ዘር፡ የጐመን ፍሬ ዘር የሚኾን

ጐመዘዘ፡ መረረ/መረገገ/ኮመጠጠ (በምረትና በኩምጣጤ መካከል ኾነ የንጆሪ የኰሽም)

ጐመዘዝ/ጐምዛዛ፡ የጐመዘዘ (ኮምጣጣ መርጋጋ ዦሮ ግንድ የሚወጋ ጐምዛ መራራ ሴት ዐመለ መጥፎ)

ጐመዠ፡ ሺዋ (የሴት ስም)

ጐመዥ (ተመነየ/ፈተወ) ሠየ/ጓጓ/ቋመጠ/ተቃረ (አኹን አኹን አለ ማግኘትን ቍርጥ አደረገ) "ዠና ተወራራሾች ስለ ኾኑ መጽሐፍ ጐመጀ ይላል" (ዘፍ. ፴፡ ፴፰, ፵፩፡ ኤር. ፭፡ )

ጐመደ (ገምዶ/ገመደ) ቈረጠ/ጐረደ/ጐነደበ/በጠሰ/ሰለበ (ተመልከት፡ ጐመተን እይ)

ጐመደ፡ በጐመድ መታ/ደበደበ

ጐመደ፡ ዐሰለ/ዋሸ

ጐመደ፡ ገመጠ/በላ ዳቦን

ጐመደሰተ፣ መታ (ሰውን)

ጐመዳም ዱላ፡ ጐመድ የለበሰ ያጠለቀ ባለጐመድ በትር

ጐመድ፡ ከበግና ከፍየል እግር ተገፎ እንደ ቀለበትና የሚወጣ ቈዳ ማፈኛ በዱላ ላይ የሚሰካ የበትር ቤዛ ጂና

ጐመጀ፡ ሠየ፡(ተመልከት፡ ጐመዠ)

ጐመጎመ (ጎመ) ሸፋፈነ/ዐፋፈነ

ጐመጐመ (ጐጐመ) ወጣ/ብቅ አለ/በቀለ/ታየ (ተመልከት፡ ጐጐመን እይ መዠመሪያውን ጎማ ተመልከት ከዚህ የወጣ ነው)

ጐመጠ፡ ውሃን ፉት አለ (ዐጠበ አጠዳ አጠራ አፍንጫውን)

ጐመጠጠ (ትግ. ጐምጠጠ) ደን ልብስን ሳበ/ጐተተ (ሰው እሸትን ላሰሰ ሰሰ)

ጐመጭ፡ ከዳ "ዕጭ ጐመጭ" እንዲሉ።

ጐመጭ፡ የሣር ስም (አገዳው ቀጪን የኾነ ሣር ባለብዙ ዛላ ርጥቡን ከብት የሚበላው የሚያጓምጠው ዝንጀሮ የሚያኝከው የሚመገበው)

ጐሚት (ቶች) (ፍሕሶ) እጅግ የሚያምር ዕጥፍ አበባ (በበልግ ዝናም የሚለመልም ክብ የምድር ጕተና ደማቅ ቀይ)

ጐሚት (ገኘ/ገነኘ)

ጐሚት ገና፡ የእባብ ስም (ዠርባው የጐሚት ዕንጨት (ላንፋ) ሆዱ ብልጭልጭ የሚመስል ቁመቱ የጥንግና የሩር መምቻ ገና የሚያኸል ትልቅና ተልብማ አባብ ማደሪያው መደበቂያው (ጎሜእ) የሚባል ቀርክሓ ስለ ኾነ ጎሚት ገና የተባለ ይመስላል) "የገና ለት ወደ ሄሮድስ የኼደው የሰይጣን ምሳሌ።"

ጎማ፡ ድዳ የማይናገር ሰው "አፈ ጎማ" እንዲሉ።

ጎማ፡ ጕመላ (ቀንድ አልባ ጐዳ በሬ እንስት የዱር ፍየል)

ጎማ፡ ጠንካራ ላስቲክ (ተመልከት፡ ላፒስን)

ጎማመደ፡ ሸራረበ

ጐማመደ፡ ቈራረጠ/ጐራረደ/በጣጠሰ

ጐማሪ፡ የጐመረ/የሚጐምር (ነፊ አኰራ)

ጐማች፡ የጐመተ/የሚጐምት (የሚቈርጥ ጐማጅ ከፋይ)

ጐማዳ (ዶች) ስልብ አፍንጫ ዐጪር (ዘሌ. ፳፩፡ )

ጐማዴ፡ ዝኒ ከማሁ (ጃን ደረባ ጠባቂ የጐማዳ ወገን አባን ተመልከት)

ጐማጅ (ገማዲ) የጐመደ/የሚጐምድ (የሚቈርጥ የሚጐርድ ቈራጭ ጐራጅ)

ጐምላላ (መካሕ) ቈናና/ኰፍናና (ጕልማሳ አንበሳ ገመር)

ጐምር (ሮች) የበሰለ እሸት (አገዳው ብሩ የነጣ የገረጣ)

ጐምቱ (ዎች) ጨዋ/ትልቅ ሰው/ዐዛውንት

ጐምዛ፡ ክፉ ሴት፡(ተመልከት፡ ጐመዘዘ)

ጐምዢ፡ የሚጐመዥ/የሚጓጓ

ጐምዤ፡ ዘንጋዳ፡(ተመልከት፡ ጐመዘዘ)

ጐምዤ፡ የሚጐመዝዝ (ዘንጋዳ)

ጎሞር፡ አንድ መገበሪያ ዶቄት የሚይዝ የሸክላ ወይም የስፌት ዕቃ ንዋየ ቅድሳት (ልብም)

ጐሰመ (ትግ. ጐሰመ ቃመ ብስ አጣፋ) ነጋሪት መታ (ድም ድም አደረገ) (ተመልከት፡ ደለቀን እይ) "ሽቅብ ሽቅብ አለ ወከ ሆድን።"

ጐሰመ፡ ወጋ/ጓጐጠ በሬን ኣህያን

ጐሰሰ (ቈሰሰ) ኰሰሰ/ከሳ/ደከመ

ጐሰረ፡ ሰብዙ/ጨመረ/መላ ጠቀ ጠቀ/ዐመቀ/ዐጨቀ/ነፋ/ወጠረ ሆድን በመ ብል ስልቻን በእብቅ

ጐሰረት፡ ሆደ ክርብ የቦና

ጐሰቈለ (ሐርተመ) ጠፋ/ተበላሸ/ከሳ/ጠቈረ (ወራዳ ኾነ ቈሸሸ ከሰረ ከበሽ ታና ከክፉ ዐመል ከችጋር የተነሣ) (ኤር. ፲፭፡ ፱፡ ፴፩፡ ፲፱)

ጐሰጐሰ (ትግ. ጐስጐሰ በረበረ ጐተጐተ) እንደ በሬ አብዝቶ ጐረሠ/በላ/ጠቀጠቀ (የግሥገሣ አበላል ነው)

ጐሠጐሠ፡ አብዝቶ ጐረሠ

ጐሰጐሰ፡ እድብኝት ውስጥ አገባ

ጐሢ (ጐሣዒ) ያሞራ ስም (ጥቍር አሞራ ግልገል አንሣ በአየር መጥቆ የሚያገሣ) "በግእዝ ንስር ይባላል።"

ጐሣ (ኦሮ) ዘር/ትውልድ/ወገን

ጐሳሚ፡ የጐሰሙ/የሚጐስም (መቺ)

ጐሳሳ፡ ደካማ ሰው (ኰሳሳ ጥጃ)

ጐሳሪ፡ የጐሰረ/የሚጐስር (ዐቂ)

ጐሳራ/ጕስር (ሮች) የተጐሰረ (ውጥር ንፍ ጥቅጥቅ ክርብ እንቅብ ሆድ ዘርጣጣ)

ጐስቋላ (ሎች) ጕስቋይ/ጕስ ቍል (ሕርቱም) (የጐሰቈለ መጥፎ ራዳ ምናምንቴ ልክስክስ ዐመለ ውዳቂ ሰው ታናሽ) (ምሳ. ፲፱፡ ፳፯፡ ሮሜ. ፯፡ ፳፬፡ ልጵ. ፫፡ )

ጐስቋል()ነት፡ ጕስቍልና (ሕር ትምና) (ብላሽነት ምናምንቴነት ውርደት ጥፋት ጕዳት አደጋ መከራ) (ኤር. ፵፮፡ ፲፪፡ ሰቈ. ፫፡ )

ጐስቋይ፡ የሚጐሰቍል

ጐስጓሽ፡ የጐሰጐሰ/የሚጐሰጕስ (በላ ተኛ ጐትጓች)

ጎረ ገነት፡ የገነት አቅራቢያ ረዥም ተራራ

ጐረመ (ጐርጐረ/አንጐርጐረ) ወፍራም ድምፅ ሰጠ/አሰማ

ጐረመመ (ጐርመመ) የትግሬ (ፎነነ ያማራ ነው)

ጐረመመ፡ አፍን ከንፈርን ቈረጠ/ፎነነ

ጐረመሰ፡ ጐለመሰ "ለና ተወራ ራሽ መኾናቸውን አስተውል።"

ጐረመደ፡ ጐመደ/ጐረደ/ገመሰ/ተነ ተነ/ሸነሸነ/ከፈላ/ሰበረ/ቈረሰ/ቈረጠ ዳቦን

ጐረምሳ (ሶች) ጕልማሳ ("ጎረ ኅምሳ ለብእሲት")

ጐረሠ (ገረሠ) ወዳፍ አገባ/ከተተ/በላ/ተመገበ ምግብን (ትንባኾን ባፉ ያዘ)

ጐረሣ፡ የመጕረሥ ሥራ (መጕረሥ መብላት መመገብ)

ጐረረ ጋሻ

ጐረረ (ትግ. አጕረረ) ፎከረ/ዛተ/አንገራበደ/ተላገደ/ተመካ/ታጀረ/ወሬ ነዛ/አንቧተረ/አንፋሸረ (ራሱን አከበረ ሌላውን ናቀ አኰሰሰ "አንተን አንድ ነገር ሳላደርግ የቀረኹ እንደ ኾነ ሰው አትበለኝ አለ።") "ጓሮ ማለት ከዚህ የወጣ ነው።"

ጐረበ (ቈቍዐ) ረገበ/ተቋጠረ/አጐበጐበ/ቈረበጨ/ተመደደ (የውስጥ እጅ የእንግርግብ የድር) (ተመልከት፡ ቀረበን ተመልከት)

ጐረበጠ፡ ነካ/ቈረቈረ/ወጋ (አልመች አለ አስቸገረ ጐንን ሆድን)

ጎረባብት (ቶች) ዝኒ ከማሁ

ጎረቤላ፡ ያገር ስም (ካንኮበር በላይ ያለ አገር)

ጎረቤት (ጎር/ጎረ ቤት) የቤት ኣጠገብ ወይም ቤቱን በሰው ቤት ጐን የሠራ ሰው

ጎረቤትነት፡ የቤት አቅራቢያነት/አጠገብነት

ጎረቤቶች (አግዋር) የቤት አጠቦች (ዐምባቸው መንደራቸው አንድ የኾነ ሰዎች)

ጐረተ፡ ጐራ ከመረ

ጐረነነ (ጐረና) ወፈረ/ደነደነ ( ድምዕ)

ጐረና፡ ቀረና/ተበላሸ (የቅቤ የወጥ ሳይማሰል ስለ ቀረ)

ጐረንጐሬ ሽፋፍ ጐራ

ጐረንጐሬ፡ የጐሬ ጐሬ (የፍላጻ የስለት መክተቻ ማከማቻ ከቈዳ የተበጀ ኰረጆ ሽፋፍ) " ስሯጽ ነው" (ዐብድ. ፩፡ ) "በግእዝ ምጕንጳ ይባላል።"

ጐረደ (ገረዘ/ቀረፀ) ከጫፍ ከመኻል ጐመደ/ቈረጠ/መቀሰ (ጐነደበ/ዐረደ/አሳጠረ/ቀየደ/ከፈለ/ፈተገ) "ዘና በዐረብ ተብለው ስለሚነገሩ ጐረደ የገረዘና የቀረፀ ዲቃላ ነው ገና ቀም መወራረሳቸውን ባማርኛው ገበታዋሪያ መቅድም ተመልከት።"

ጐረደ፡ ፊደል ዘለለ/አስቀረ/ዋጠ

ጐረደመ፡ ቈረጠመ/ሸረደመ (በቅሎና አህያ ጥሬ ያበባ እኸልን)

ጐረደማን (ኖች) የነጋዴ ሎሌ ጫኝ "ምስጢሩ አቈርጣሚነትን ያሳያል።"

ጐረደድ (ጐርዳዳ) ቈረጠጥ/ቈር

ጐረድ ጐረድ አደረገ፡ ከላይ ከላይ መላልሶ ጐረደ (በቀላል ወቀጠ ዠብ ዠብ ኣደረገ)

ጐረድ፡ የጐረደ (ቀጣፊ ዐባይ)

ጐረዶ፡ ተዠምሮ የቀረ ያላለቀ ራና ነገር ውዝፍ

ጐረጐመ፡ ጥርስን ዐልፎ ዐልፎ አወለቀ/ነቀለ

ጐረጐማ (ሞች) ጥርሰ ወላቃ

ጐረጐሜ፡ የጐረጐማ ወገን ወይም ጥርስ ጐደሎ

ጐረጐረ (ጐርጐረ) ኰረኰረ/ፈተሸ/በረበረ/ጓጐጠ//ፈለገ (የኵክ የቅቤ የድልኸ የዓሣ የጥርስ)

ጐረጐጪ፡ አማገ/እጠጣ (ከጕንጭ ወደ ጕረሮ ሲያወርድ ገጭ ሲያደርግ ተሰማ ውሃን መጠጥን)

ጐረጠ (ጐረጸ) ወጣ/ፈጠጠ (" ይን!" (ተገብሮ))

ጐረጠ፡ ጫረ/ወረ ("(ገቢር)" ትግሬ ግን ጐረጸን በቡጢ መታ ይለዋልና የቀኝ እጅ አውራ ጣትን ጥፍር ያሳያል)

ጐረጥ (ደንቈር) ግንድ በሺ ሆደ ወይብማ ወፍ ዐይኑን አጕርጦ የሚያይ "የጐ ረጥ አየ" እንዲሉ

ጐረፈ (ጐሪፍ ጐረፈ) ወረደ/ፈሰሰ በዝቶ (ደንጊያን ዐፈርን ሣርን ቅጠልን ግንድን ግባስን ቍሻሻን ኹሉ ይዞ) (ማቴ. ፯፡ ፳፭, ፳፯)

ጐረፈ፡ መዠመሪያ ታጠበ

ጐሪ፡ የጐራ/የሚጐራ (ድንጋይ ከማሪ)

ጐራ (ጐርዐ) (ዕብ. ጋር) ደንጊያ ሰበሰበ/አከማቸ - ከመረ/ጐረተ/ቈለለ "ጐርዐ ጥንታዊ ግእዝ ነው።"

ጐራ ማለት (ግሒሥ) መንገድ ለቆ እግር መንገዱን ወደ ቤት መምጣት/መግባት "ጐራ በጋልኛ ቀጋ ማለት ነው።"

ጐራ በል፡ ገባ በል/ ግባ

ጐራ አለ (ገሐሠ) መጣ/ገባ (ተመልከት፡ (ጐደኘ) ብለኸ ተጐዳኘን እይ)

ጐራ፡ የጦር ሜዳ (የጭንቅ የመከራ ስፍራ "የጐራው ባላ እከሌ ላንድ ጐራ የሚበቃ ጐበዝ ነው" እንዲሉ)

ጐራ፡ የፊታውራሪ ገበየኹ የፈረስ ስም "የጐራው ገበየኹ" እንዲሉ

ጐራ፡ ጠባብ መንገድ (ዐንገት ዐራዳ መተላለፊያ)

ጐራ፡ ፊና/አኳያ "በጐራኸ" እንዲል ገና ተጫዋች

ጐራሥ፡ ጋን የሸማና የዕቃ መክተቻ

ጐራረደ፡ ቈራረጠ/ጐነዳደበ (ጠጕርን ሲቈርጥ አበላሸ ረዥምና ዐጪር አደረገ)

ጐራሸሽ፡ ሰን ኵስኵስት (ፊልክስ ዩስ ፻፲፪)

ጐራሽ (ሾች) የጐረሠ/የሚጐርሥ (በላተኛ)

ጐራቢ፡ የሚጐርብ/የሚቈረብጭ

ጐራዝመን፡ ርጥበትና ደረቅነት ሰው ዕንጨት (ያልታጨደ እኸል)

ጐራዝመን፡ ጥቍር አይሉት ነጭ

ጐራዳ (ዲት) ከጫፉ የተሰበረ ዕቃ (አፍንጫ ዐጪር ሰው)

ጐራዴ

ጐራዴ (ጐራጅ) የሰይፍ ዐይነት (አንድ አፍ የጦር መሣሪያ ሐኔ ዋልሴ ሾተል የጠላትን ዐንገት ዐራጅ ጐራጅ ማለት ነው)

ጐራዴ፡ በመሬት ላይ ከራሱ ዘንበል የሚል የሚዘናፈል ባለዳልጋ ጤፍ አቋቋመ ጐራዴ (ተመልከት፡ ቈንደልን እይ)

ጐራድ፡ ዐንገት የሌለው ማድጋ (መስፈሪያ)

ጐራጅ (ጆች) የሚጐርድ (ቈራጭ)

ጐራጅ፡ በመካከልና በመጨረሻ በግእዛዊ ቃል ሲገባ ራሱን ጐርዶ ሌላውን ፊደል ባማርኛ ራብዕና ሳብዕ በማድረግ የሚታጣ ፊደል (ኣዐ/ሀሐኀ//)

ጐራጅነት፡ ጐራጅ መኾን (ቈራጭነት)

ጐራጐረ፡ ኰራኰረ

ጐራጣ፡ የጐረጠ ፈጣጣ

ጐራጭ (ጐራጺ) የሚጐርጥ ( ጣጭ ጝሪ)

ጐራፊ፡ የጐረፈ/የሚጐርፍ (ፈላሽ ታጣቢ)

ጐሬ፡ በኢሉባቦር ክፍል ያለ አገር

ጐሬ፡ ጕድጓድ/ዋሻ (ያውሬ የንብ መኖሪያ ደንጊያም ቋጥኛም ማለት ነው)

ጎር (ግእዝ) ጎረቤት

ጐርማሚ፡ የጐረመመ/የሚጐረምም (ፎናኝ)

ጐርማማ፡ የተጐረመመ (ፉን)

ጐርምድ፡ የሚጐረምድ (ቈራሽ)

ጐርምጥ (ጐርምድ) ባለብዙ እግር የባሕር ተንቀሳቃሽ ጓጕንቸር (ሸርጣን መቀስ ያለው ዐረቦች ኣቡ መቀስ የሚሉት)

ጐርምጥ፡ ቈላ ቍስል እግር የሚቈርጥ የሚጐረምድ (ተመልከት፡ ጐረጠ ብለኸ መጐ ራጕርጥን እይ)

ጐርበጥባጣ፡ የጐርባጣ ጐርባጣ (ወጣ ገባ)

ጐርባጣ፡ መጥፎ መኝታ አስቸጋሪ

ጐርባጭ፡ የጐረበጠ/የሚጐረብጥ (ቈርቋሪ ነኪ)

ጐርብጥ፡ ያለፋ የበሬ ቈዳ (ቈርቍር ውጋ ማለት ነው "እንግዳ ጐርብጥ" እንዲሉ)

ጐርናና፡ ቃለ ወፍራም ጕልማሳ

ጐርዝ/ጐርዞ፡ የዓሣ ስም (ከግልገል የሚያንስ ዓሣ) "ጐርዝ ያሠኘው የሆዱና የጐኑ ንጣት የዠርባው ጥቍረት (ጠይምነት) ነው ሦርዞ ጐርዞ እንዲሉ።"

ጐርደድ ጐርደድ አለ፡ ቈርጠጥ ቈርጠጥ አለ

ጐርደድ፡ ቈርጠጥ

ጐርዳሚ፡ የጐረደሙ/የሚጐረድም (ቈርጣሚ ሸርዳሚ)

ጐርዶማ፡ ያገር ስም (ከደብረ ሊባ ኖስ በላይ ዕልፍ ብሎ ያለ አገር)

ጎርጎ (ዎች) የንጨት ስም (እሾኻም ሻካራ ዛፍ ፍሬው ቀይ ለሕፃናት ቍንጮ ጌጥ የሚኾን የኮርች ዐይነት ወይም ርሱ ራሱ ኮርች)

ጐርጐራ፡ በበጌምድር ክፍል በደንቢያ ውስጥ ያለ አገር

ጎርጎርዮስ፡ የኑሲስ ኤጲስቆጶስ ባለታ ምራት

ጎርጎርዮስ፡ የአርማንያ ሊቀ ጳጳሳት (ከውነተኞቹ ሊቃውንት አንዱ ድርሰቱና ትምርቱ ሐሰት ስሕተት የሌለበት ጥሩ እውነት የአርመንን ንጉሥ በክርስቲያን ሃይማኖት ያሳመነ እሱ ነው)

ጐርጓማ፡ የተጐረጐመ/ጐረጐማ

ጐርጓሪ (ሮች) የጐረጐረ/የሚጐረጕር (በርባሪ ፈላጊ "ዓሣ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል የሰው ፈላጊ የራሱን ያጣል")

ጐርጠብ፡ የቅጠል ስም (በመረሬ የሚበቅል ቅጠል እሱን ቀጥቅጦ በውሃ ቢጨምቁት የታመመ ዐይን ያድናል ለቍስ ልም መድኀኒት ይኾናል)

ጐርፉ/ጐርፌ፡ የሰው ስም (የዘሩን ብዛትና ኀይሉን ያሳያል) "ዳግመኛም ጐርፉ የርሱ ጐርፍ ጐርፌ የኔ ጐርፍ ተብሎ ይተረጐማል።"

ጐርፍ (ጐረፋ) ድፍርስና ብጥብጥ የክረምት የብላጊ ውሃ አንፎርሻ (ማቴ. ፯፡ ፳፭-፳፯)

ጐርፎ፡ የቀበሌ ስም (እስላምን ለማጥቃት ኦሮን ስቦ ጐትቶ ወደ መኻል ያገባ ጐርፉ "ጋራ ጐርፎ" እንዲሉ) (ተመልከት፡ ሙሎን እይ)

ጐሸ (ትግ. ጐሰየ ኰራ ናቀ) ደፈረሰ/አተለ/ተዘለለ/ተበጠበጠ/ጕሽ ኾነ/ወፈረ

ጐሸመ (ጐሰመ) ደሰቀ/ደሰመ/ጐጐመ (በጕልበት በክርን በቡጢ) "ሌባሻይ ሰውን ይጐሽማል።" "እንደ ጐሰመ ለነጋሪትም ይነገራል።"

ጐሸመጠ (ጐሸመ) በነገር ነካ/ጐነጠ/ነጠበ

ጐሹ ባዶ፡ በታላቅ ዐምባ ውስጥ የሚገኝ የጐሹ ወና

ጐሹ፡ የሰው ስም "አራት ዐይና ጐሹ" እንዲሉ

ጐሹ፡ የበሬ ስም (ጐሽ የሚመስል በሬ የጐሽ ዲቃላ)

ጐሻሚ፡ የጐሸመ/የሚጐሽም (ደሳቂ ይሳሚ ጐጓሚ)

ጐሽ (ጋሙስ) (ጐሥዐ ጐሣዒ) ያሣ የሚያገሣ አግሺ (ሰውን በምላሱ የሚ ቃወም ቈርበተ ወፍራም የዱር የበረሓ በሬ) (ኢዮ. ፴፱፡ ) "በህንድና በምስር ግን ለማዳ ነው ተባቱ ያርሳል እንስቷ ትታለባለች።"

ጐሽ መቃ (የጐሽ መቃ) ቅጠ ሉን ጐሽ የሚበላው እንደ መቃ አንጓ ያለው (ከቅጥነቱ በቀር ሽመል የሚመስል መዝጊያና መከታ የሚኾን የመቃ መስዬ ዐይነት) "ጐንደሮች ቀለም ይሉታል።"

ጐሽ ዐረስ፡ ከባለምድሩ ሳይጋዛና ሳያስፈቅድ አንድ ሌላ ሰው ያረሰው ሬት "ጉሽ ምድርን በቀንዱ በማረሱ በመፈ ለሱ ዋጋ የለሽ ስለ ኾነ አለባለቤቱ ፈቃድ የታረሰው ማሳ ጐሽ ዐረስ ተባለ ለባለርስቱ ጥሎ ከመኼድ በቀር ሌላ ጥቅም የለውምና።"

ጐሽ ውሃ፡ በላይኛው ወግዳ ያለ አገር (ጐሹ የሚሳል ሰው ያቀናው) "በቡልጋም ጐሽ ውሃ የሚባል ቀበሌ አለ።"

ጐሽ ግንባር፡ የገብስ ስም

ጐሽ ጠጕር (የጐሽ ጠጕር) ቀይ የልጅ ጠጕር (ካ፲፭ ዓመት በኋላ የሚ ጠቍር)

ጐሽ፡ የምስጋና የምርቃት ቃል " ሰው የኰርማ ወንድም ይውጣብሽ!" (ተመልከት፡ ወጣን እይ) "ጐሽ ልጄ" እንዲሉ

ጐሽመቃ ቀለም፡ ጐሽ

ጐሽማጭ፡ የጐሸመጠ/የሚጐሸምጥ (ጐናጭ)

ጐሽሜ፡ የሰው ስም (የጐሻሚ ወገን ወይም ጐሽም ማለት ነው)

ጐበለ፡ (ዕብ. ጋባል ወሰነ/ድንጋይ አቆመ) ቍጭ አደረገ፡ አስቀመጠ።

ጐበሰተ፡ ሠጠ፡ ሳለ "ኡሁ ኡሁ" አለ።

ጐበበ (ገብቦ ገበበ) ጐነበሰ፡ ተቀለሰ እንደ ቀስት፣ እንደ ደጋን ኾነ። "ጐበብ አለ" ቀለስ አለ።

ጐበና (ኦሮ) የሰው ስም፡ በሙሉ ጨረቃ የተወለደ ማለት ነው።

ጐበና ዳጪ፡ የዳጯ ልጅ ራስ ጐበና (ያጤ ምኒልክ አበ ጋዝ የታወቁ ስመጥር ዠግና፡ በባታቸው ከኦሮ በናታቸው ከአማራ ያወለዳሉ፡ የፈረስ ስማቸው አባ ጥጉ)

ጐበኘ፡ (ሐወጸ) ዐወጠ፡ አየ፡ ተኰረተ/ተመለከተ፡ ፈቀደ/ጠየቀ፡ ሰለለ/መረመረ (ክፉ ወይም በበጎ - በጠላትነት/በወዳጅነት) (ዘፍ. ፳፮፡ ፳፮፡ ዘኍ. ፲፫፡ , ፳፩፡ ኢሳ. ፴፮፡ ፲፬)

ጐበዘ

ጐበዛየኹ (ጐበዝ አየኹ) የጠመንዣ ስም (የዱሮ ነፍጥ) "ካሽከር ገበየኹ ከነፍጥ ጐበዛየኹ" እንዲሉ።

ጐበዜ፡ የሰው ስም፡ የጐበዝ ወገን ወይም "የኔ ጐበዝ"

ጐበዝ (ዞች) ጕልበታም፡ ኀይለኛ፡ ብርቱ፡ ጨካኝ፡ ጕልማሳ፡ ምሎ ሰው። "ጐበዛዝት/ጐበዞች" (ዮኤ. ፩፡ ፲፡ ዓሞ. ፪፡ ፲፩)

ጐበዝነት፡ ኀይለኛነት፡ ጠንካራነት።

ጎበደደ፡ ተሰበሰበ፡ ሊያልቅ ቀረበ፡ ጥቂት ቀረ፡ አንድ ወገን ኾነ (የሥራ ረብ) (ተመልከት፡ በሀዘን)

ጐበደደ፡ ጐበጠ፡ ጐነበሰ፡ ተንጐበረረ፡ ዘነበለ፡ ጐበበ፡ ደጋን መሰለ።

ጐበደድ (ጐብዳዳ) (ዶች) የጐበደደ፡ ጐባጣ፡ ተርካሳ፡ ፈንዳዳ።

ጐበጐበ

ጐበጐባ

ጐበጠ፡ ደነነ፡ ጸነነ፡ ጐነበሰ፡ ዘባ፡ ደጋንና ቀስት/ሙጭና/ከዘራ/አጐበር መሰለ። ተቀሰተ፡ ተደገነ፡ ተቀለሰ (መዝ. ፵፬፡ ፳፭)

ጐበጥባጣ፡ የጐባጣ ጐባጣ፡ ወጣ ገባ አስቸጋሪ መንገድ፡ ደንጐላጕል/ድንጕር።

ጐቢ የጐባ የሚጐባ የሚደግፍ፡ ጕቦ ሰዉ

ጐቢጥ፡ ያረቄ ስም፡ ኀይለኛ መጠጥ አብዝቶ ቢጠጡት የሚያጐብጥ።

ጐባ አስቀመጠ ቍልልታ አደረገ

ጐባ ደገፈ ጣራን አነሣ ወደ ላይ ገፋ

ጐባ ጕብ ሰፋ

ጐባ ጕቦ ሰጠ አስበበተ

ጐባባ፡ የጐበበ፡ ጐባጣ፡ ጐንባሳ፡ ቀላሳ።

ጐባታ፡ ዝኒ ከማሁ ለጕባ (ይህም እንደ ጕባ ማለት ነው)

ጐባን (ኖች) የሰው ሚስት ያገባ ጣውንት

ጐባን፡ የሌላዪቱን ባል ያገባች ሴት (፩ሳሙ. ፩፡ )

ጐባንነት፡ ጣውንትነት፡ የሌላ ባል ወይም ሚስት መውሰድ/ማግባት።

ጐባጣ፡ ጐባጥ፡ ቀላሳ፡ ተርከሳ፡ ደጋን ወገብ (ዘሌ. ፳፩፡ ፳፡ ) "ሲበዛ ጐባጦች ይላል" (ዮሐ. ፭፡ )

ጐባጣነት፡ ጐባጥነት፡ ቀላሳነት፡ ተርካሳነት

ጐባጤ፡ የጐባጣ/የተርካሳ ዐይነትና ወገን።

ጐባጭ፡ የሚጐብጥ፡ ዘቢ።

ጐቤ

ጐቤ፡ ግብዝ፣ ጐበጐበ።

ጐቤ፡ ግብዝ፡ አስመሳይ፡ ወሬኛ።

ጐብኚ (ዎች) (ሐዋጺ) የጐበኘ/የሚጐበኝ/የሚጠይቅ/የሚያይ፡ ፈቃጅ፡ ተመልካች

ጎብደድ አለ፡ ገበደደ፡ ተወገደ፡ ተገሰሰለ

ጐብጓቢ፡ የጐበጐበ/የሚጐበጕብ፡ ጕብጕብ ሠሪ፡ ሸላሚ፡ ደጓሽ።

ጐተራ፡ ሰፊ ኹኖ በግንብ የተሠራ የመንግሥት እኸል መክተቻ ማስቀመጫ ቤት (ባለብዙ ጕርጅ) (ሚል. ፫፡ )

ጐተራ፡ የግድግዳ ጐታ ከሪቅ የሚ በልጥ "ሲበዛ ጐተሮች ይላል" (ዮኤ. ፩፡ ፲፯)

ጐተተ፡ ሳበ/ስቦ ወሰደ/አበዛ/አረ ዘመ/ጠራ/አቀረበ (የሞፈር የሠረገላ የሰው የመረብ የነገር የጋኔን) (ምሳ. ፳፫፡ ፴፭፡ ሕዝ. ፴፪፡ ፳፡ ዮሐ. ፳፩፡ ፲፩)

ጐተተ፡ ጕትቻ ሠራ/አበጀ

ጐተታ፡ መጐተት

ጐተታ፡ ክብ ያይዶለ ሞላላ (ንብ የጋገረው የማር እንጀራ ከቀፎ ተጐትቶ የሚወጣ)

ጐተት፡ የቀበሌ ስም (በታችኛው ወግዳ ባሻገር በስተግራ ያለ ገደል) "ክፉ ልጅ ዕድሜያም አባቱን ጐትቶ ስለ ጣለበት ጐተት ተባለ ይላሉ። እሱም በፈንታው አባ ቴን ከዚህ አላሳለፍኩትምና አታሳልፈኝ አለ ይባላል። ይህ ታሪክ በሐተታ ወልደ ሕይወት ተጽፎ ይገኛል።"

ጐተነ፡ አደገ/ረዘመ/ቆመ (ፍሕሶ መሰለ ተበጠረ ተመየደ)

ጐተጐተ (ትግ. ጐስጐሰ) ነቀነቀ/አተጋ/አጣደፈ/አስቸኰለ/ዕረፍት ነሣ/ወተ ወተ/ኰረኰረ/ነዘነዘ/ዘበዘበ (በሥራ በነገር)

ጐታ

ጐታ (ለጐተ) ከክትክታና ከቀጨሞ ከመቃ ከቀርክሓ ከሌላም ዕንጨት እንደ ቅር ጫት የተታተ የእኸል መክተቻ ማስቀመጫ (ማቴ. ፫፡ ፲፪) "ሲበዛ ጐቶች ይላል" (ዮኤ. ፩፡ ፲፯) (ተመልከት፡ ደረባን እይ፡ ጐተራንና ሪቅን ተመልከት) "እጐታ ውስጥ የሚገቡ ያልባለቀ ጅና ልጃገረድ ናቸው።"

ጐታታ፡ ረዥም ቀሚስ (የታቦት ብስ መጐናጸፊያ)

ጐታች (ቾች) የጐተተ/የሚጐትት (ሳቢ በሬ ፈረስ በቅሎ ግመል ባቡር ጠን ቋይ) "ጋኔን ጐታች" እንዲሉ

ጐታጐተ፡ ኰራኰረ

ጐትት (ሳብ) የጕጕት ጩኸት ማማረቻ "ዛሬ ሌሊት ጕጕቷ ጐትት ስትል ዐደረች።"

ጐትት፡ ዝኒ ከማሁ (የምትጉትት) " ሮጊት ነገረ ጐትት" እንዲሉ

ጐትጓች፡ የጐተጐተ/የሚጐተጕት ( ጣዳፊ ኣስቸኳይ ወትዋች)

ጐቸ፡ ከመረ/ዘመመ/ቈለለ/አስቀመጠ "ገዎቻ አስመሰለ።"

ጐቺ፡ የጐቸ/የሚጐች (ከማሪ ቈላይ)

ጐነ ሰፊ፡ ዝኒ ከማሁ

ጐነቈለ፡ መብቀል ዠመረ (ወጣ ፈጠጠ)

ጐነበ (ጐነጰ) ከነበ ጐነፈ

ጐነበሰ፡ ዘነበለ/ተዘለሰ/ተቀለሰ (በእጁ ጭምር እንሰስኛ ቆመ ለመቈፈር ለማረም ለማጨድ አንድ ነገር ለማንሣት)

ጐነበጠ፡ ቦጨቀ/ነጯ

ጐነተለ፡ ባፍ ወይም በእጅ ወዳንድ ስፍራ ለማድረስ ነካ/ጐነጠ/ገፋ

ጐነተረ (ጐነተለ) ቈነጠረ

ጐነነ፡ ቈነነ/ታታ (በራስ ልክ ቆብ ሠራ) (ተመልከት፡ ጐነጐነን "ከዚህ የወጣ ነው።")

ጐነዘለ (ነዘለ) ረዘመ (በትከሻ ላይ ተኛ አማረ - የጠጕር)

ጐነዪ፡ ግንድ ቈረጠ/ጐመደ

ጐነደ (ጐኒድ/ጐነደ) ወፈረ/ደነደነ

ጐነደ፡ ካባት ከናቱ ቤት ተለየ (ጐዦ ወጣ ከግንድ ተቈርጦ እንደሚተከል ዕንጨት ለራሱ የትውልድ ግንድ (ኣባት) ለመኾን)

ጐነደለ (ቈነጸለ) ነደለ/ቀደደ/ሰለበ/አጐደለ/ሰነጋ/ኣኰላሸ (የዶሮ) "ጐነደለ የነደለና የጐደለ ዘር ስለ ኾነ ሲቀር ነደለ ሲቀር ጐደለ ይኾናል "

ጐነደበ (ጐደበ) ግንድን ከወገቡ በላይ ጐረደ/ቈረጠ/ጐመደ

ጐነጐነ (ጐነነ) ታታ/ቈነነ/ጠለፈ/ጠላለፈ (ገመድን ከገመድ ጠጕርን ከጠጕር ጋራ የቀኙን ከግራ የግራውን ከቀኝ ወሰበ ጠመረ)

ጐነጐነ፡ ነገር ሠራ/ቋጠረ (ሚክ. ፯፡ )

ጐነጐነ፡ ደፈደፈ (ጌሾን ብቅልን እንኵሮን አዋዋደ ቀላቀለ ደባለቀ)

ጐነጠ (ትግ. ጐነጸ) ደፈረ/ነካ/ገፋ/ነቀነቀ

ጐነጥ አደረገ፡ ጐነጠ (ላካፋ) ነካ/ገፋ/ነቅነቅ አደረገ

ጐነጥ፡ መጐነጥ

ጐነጨ (ለትሐ) ጕንጭ አወጣ/አማረበት

ጐነጨፈ፡ በጥቂቱ ሸመጠጠ/መገገ

ጐነጩ፡ በጕንጭ ያዘ/ጠጣ (ተመልከት፡ ማገን)

ጐነፈ (ገኒፍ/ገነፈ) ረመጥ ጨመረ (በፍል ውሃ ዐጠሰ ቅባት የነካውን ድስት)

ጐነፈ፡ ዘንጋዳን ባመድ ኹለት ቀን ዐጀሰ

ጐነፈ፡ ጠረበ/ዐነጠ/ቀረጻ/ኣለበሰ/ደጐሰ "ቀረጸ ደጐሰ የህናት ትርጓሜ ነው 'ጐነፈን አለበሰ ደጐሰ' ማለት የጐነበ ምስጢር አለበት።"

ጐነፈረ (ጐነፈ/ጐፈረ/ጐረፈ) ገነፈለ (ከመጠን ዐለፈ ተረፈ)

ጐናም፡ ወርዳም።

ጐናዴ (ዎች) ዝኒ ከማሁ (የጐናድ ወገን ዐይነት ወይም ርሱ ራሱ)

ጐናድ (ዶች) የጐነደ/የሚጐንድ (ዐዲስ ጐዦ ወጪ)

ጐናጭ (ጮች) የጐነጠ/የሚጐንጥ (ደፋር ነኪ ነቅናቂ)

ጐናፊ (ገናፊ) የጐነፈ/የሚጐንፍ (የሚቀርጽ ዐጣቢ ደጓሽ)

ጐን (ኖች) ከብብት እስከማውድ ያለ ገላ። "ንፍሮ ቀቅዬ ብላ ብለው ጕልቻ አንሥቶ ጐኔን አለው። ጐኔን ጐኔን ኵላሊቴን እናቴን ጥሩ መድኀኒቴን" እንዲሉ ልጃገረዶች

ጐን ለጐን፡ አጠገብ ላጠገብ/ቅርብ ለቅርብ

ጐን፡ በስተቀኝና በስተግራ ያለ ስፍራ

ጐን፡ ኣጠገብ/ቅርብ።

ጐን፡ ወርድ/ስፋት።

ጐንቋይ፡ የሚጐነቍል

ጐንባሲት፡ ታናሽ ጐዦ ቀላሲት (ዐጪር በር ጐንብሶ የሚገቡባት)

ጐንባሳ (ሶች) የጐነበሰ (ዘንባላ ቀላሳ)

ጐንባሳ፡ የመጐንበስ ኹኔታ "ሕፃኑ በጕንብሱ ይኼዳል "

ጐንባሽ፡ የሚጐነብስ (ዘንባይ)

ጐንታይ፡ የጐነተለ/የሚጐነትል (ገፊ)

ጐንቸል፡ አህያ ጐናጭ ዥብ

ጐንና ጐን፡ ግራናቀኝ (ኢዮ. ፴፩፡ )

ጐንአጠገብ፡ (ተመልከት፡ ጐደነ)

ጐንዛላ፡ የተመቸው/የደላው/ቈንዳላ

ጐንደራ (ትግ) የወስፋት ስም ()

ጐንደሬ (ሮች) የጐንደር ሰው (የጐንደር ተወላጅ)

ጐንደሬ፡ ለስላሳ ጥጥ ሳይነደፍ የሚ

ጐንደሬ፡ ነጭ ዐተር በሳል (መጠኑ ኢየሩሴን የሚያኸል)

ጐንደር (ጕንደ ሀገር) ዋና አገር (ያገር ግንድ ያገር ቀንድ ፋሲል የሠራው መናገሻ የበጌምድር ራስ ከተማ መዲና ባለ፵፬ ደብር) (ተመልከት፡ ግራን)

ጐንዳ (ጕንዳዊ) (ጐምዳ) ጐማዳ (ቈራጣ ቈማጣ ጣቱ የረገፈ ላሊበላ) "ኣባ ጐንዳ" እንዲሉ

ጐንዳ ፈረስ፡ ጭራው ተቈርጦ የዥራቱ ግንዶሽ የቀረ

ጐንዳቢ፡ የጐነደበ/የሚጐነድብ (ጕራጅ)

ጐንጊት ትንሿ፡ "ጐንጊት እንዲሉ ውሃ በመላ ጊዜ የምትንጓጓ ማለት ነው።"

ጐንጊት፡ በደብረ ሊባኖስ ቤተ ክርስቲያን ግራና ቀኝ ያሉ ወንዞች ስም (ትልቋ)

ጐንጊት፡ የወንዝ ስም፡(ተመልከት፡ ጓጓ)

ጐንጓኝ (ኞች) የጐነጐነ/የሚጐነጕን (ነገረ ሠሪ)

ጐንጣፋ፡ የተጐናጠፈ (ጐታታ)

ጐንጤ፡ የሰው ስም "ጐናጭ ወይም ጐንጥ ማለት ነው።"

ጐኘረ፡ መላ ዐጨቀ/ጠቀጠቀ/ጐሰረ/ነፋ (የሆድ የከረጢት)

ጐዘለ (ዘጐለ) ኣነሰ/ኰሰሰ/ተናቀ

ጐዘጐዘ (ጐዝጐዘ) ሣርና ቅጠል በተነ/መነዘረ/ነሰነሰ/አነጠፈ/ኣመቻቸ/ኣስተካከለ/አስቀመጠ "አነጠፈ የኮባ የንሰት የሙዝ የሰፋፊ ቅጠል ኹሉ። አስቀመጠ ሰው።"

ጐዛጐዘ፡ በታተነ/ነሳነሰ

ጐዝጓዥ (ዦች) የሚጐዘጕዝ (ነስናሽ/አንጣፊ)

ጐዝጓዥነት፡ ነስናሽነት/አመቻቺነት

ጐዠሬ፡ የጐዠር ዐይነት መሣሪያ ወይም ርሱ ራሱ ጐዠር

ጐዠሬ፡ ዶማ ባለ ኣፍ።

ጐዠር (ገዛሪ) መጥረቢያ/ቦለድጠገራ (የንጨት መቍረጫ)

ጐዣሜ (ጐዣማዊ) የጐዣም ሰው/የጐዣም ስንዴ "ጐዣሞች የጐዣም ተወላጆች።"

ጐዣም (ጐገና) ጐም/ዘላን/ባለጐዦ "አቅኒዎቹን ያሳያል።"

ጐዣም፡ ያገር ስም (ካማሮች አገር አንዱ ክፍ)

ጐዦ (ዎች) (ግዕዘ) በዱር/በመንደር ያለች ቅልስ ወይም ታናሽ ቤት

ጐዦ አወጣ፡ አባት ለልጁ ቤት ሠርቶ ገንዘብና ከብት ከፍሎ ሰጠ (አጐነደ) "የጐዦ ምስጢር ተነቅሎ መጓዝ ነው ይኸንንም ዘላኖች ሲያደርጉት ይኖራሉ" (ተመልከት፡ ጐዣምን እይ ደሳን)

ጐዦ ወጪ፡ ትዳር ዠማሪ "ጐዦና ጕልቻ ንብረት ትዳር።"

ጐዦ፡ ወጣት ዳር ያዘ (ጐነደ ከናት ከአባቱ ቤት ተለየ)

ጐደ

ጐደለ (ጐዲል/ጐደለ) አነሰ/ተቀነሰ/ዐጸጸ/ዐጠጠ/ዐረዘ (ሳይመላ ቀረ) (ዘፍ. ፯፡ ፩፡ ኢሳ. ፰፡ )

ጐደል፡ የጐደለ። "ዋና ጐደል" እንዲሉ።

ጐደሎ (ዎች) ባላንድዐይን/ዦሮ/እጅ/እግር (ስልብ) "ያነሰ ቍጥሩ ያልሞላ ሕጹጽ ጊዜው ወደ ሌሊት ኺዶ ሰዓቱ ፲፪ ያልኾነ ቀን አካለተ ጐደሎ ጐደሎ ቀን" እንዲሉ። "ያልተላ ኑሮ መፍቅድ" (፪ቆሮ. ፱፡ ፲፪)

ጐደሎ ቀን) ሰዓቱ ከ፲፪ ያነሰ

ጐደሎነት፡ ጐደሎ መኾን/ታናሽነት።

ጐደራ፡ ጮኸ/ቀተራ (የበሬ)

ጐደሬ፡ የድንች ዐይነት ተክል።

ጐደበ (ጐዲብ/ጐደበ) ማሰ/ተፈረ/መነቀረ/ቈረጠ/ዐረደ/አጐደጐደ "ጐደበ የግእዝ ገደበ ያማርኛ ነው።"

ጐደነ፡ መንገድ ጠረገ/አሰፋ (አድራጊ)

ጐደነ፡ ወደ ጐን ኼደ (ተደራጊ)

ጐደደ፡ ተላከከ/ተጣበቀ/ተጋገረ።

ጐደደ፡ ዝግ/ቀስ አለ

ጐደዳ፡ በጥፍጣፍ ደንጊያ ላይ የተጣበቀ እንደ እንጀራ የተጋገረ የበግና የፍየል በጠጥ/ጠቦት።

ጐደጐደ ገደደ

ጐደጐደ (ጐድጐደ) ጐድጓዳ/ጕድጓድ/ዘባጣ ኾነ (ተደራጊ)

ጐደጐደ፡ እጕድጓድ አገባ/ከተተ/ረገረገ/ቀበረ/ደፈነ (አድራጊ)

ጐደፈ (ጐዲፍ/ጐደፈ) /ጕድፍ ኾነ/አደፈ/ቈሸሸ/ወሰከ/ረከሰ

ጐደፈረ (ጐጽፈረ) ጫረ/ማሰ/ቈፈረ/መነቀረ/ዛቀ (ዐፈርን ጕድፍን በተነ ያውራ ያውሬ የሰው የበሬ)

ጐደፋ፡ በማይገባ ሥራ/ባመፅ/በቅሚያ መጕደፍ/መርከስ ወይም የግፍ ሥራ። "ባፈፋ በጐደፋ" እንዲሉ።

ጐደፍር፡ ማሽ ቈፋሪ/ጫሪ/መንቃሪ።

ጐዳ (ጕድ)

ጐዳ (ጐዲዕ/ጐድዐ) በጣም በኀይል መታ/ደሰቀ/ሰበረ/ቀጠቀጠ/አደቀቀ/አከላ

ጐዳ ኩታ፡ ጥለት የሌለው ኩታ

ጐዳ፡ በደለ/ጨቈነ/አስጨነቀ (ራእ. ፲፩፡ )

ጐዳ፡ ባዶ አደረገ/አሳጣ።

ጐዳቢ፡ የጐደበ/የሚጐድብ (ማሽ ቈፋሪ)

ጐዳና

ጐዳና (ዎች) ጥርጊያና ጐነ ሰፊ መንገድ

ጐዳና፡ የበገና ምት ስልት

ጐዳናዋ/ጐዳናዪቱ፡ ያች የርሷ ጐዳና (ጥርጊያዋ/ጥርጊያዪቱ) (ኢሳ. ፴፡ ፲፩)

ጐዳዊ፡ የጐዳ ወተንና ዐይነት።

ጐዳይ፡ የሚጐድል (አናሽ)

ጐዳዳ፡ ዝግተኛ/ቀስተኛ።

ጐዳዴ፡ የጐዳዳ ወገን ወይም "የኔ ጐዳዳ ጐዳዳዬ።" "ዐይናማው ጐዳዴ" እንዳለ ዘፋኝ።

ጐዳፊ፡ የሚጐድፍ (የፍግ/የጥራጊ ማፍሰሻ መሬት)

ጐዳፋ፡ የጐደፈ/ጕድፋም/ቈሻሻ ዐሣማ ዐይነት።

ጐዴ ድንኳን፡ ትልቅና ሞላልኛ ድንኳን (ዳርና ዳሩ ክብ ጕልላት የሌለው)

ጐዴ፡ የጐዳ

ጐድር፡ የሣር ስም (ለቤት ክዳንና ጕንጕን የሚኾን ሣር) (ጐዣም) (ተመልከት፡ ማሰልን)

ጐድን (ኖች) የጐን ዐጥንት (ቍጥሩ ፮ና ፲፪) (ዘሌ. ፫፡ , ፲፭)

ጐድን ከዳቢት፡ የስጋብልት ስም " ጐድን ከዳቢት ጋራ የብራኳ ዐጥንትና ሻኛ አንድነት ነው።"

ጐድን፡ የተጫነ አህያን ለማስተላለፍ የሚነገር ቃል "ወደ ጐን ኺድ ማለት ነው።"

ጐድጓዳ ዐቃፋ፡ ወጭት/ድስት።

ጐድጓዳ፡ የጐደጐደ/ፈፋ/ፈረፈር (በግደልና በተራራ መካከል ያለ የምድር ዋዲያት) "ጐድጓዳ ስፍራ" እንዲሉ።

ጐድጓጅ፡ የሚጐደጕድ (ከታች)

ጐድፋሪ (ጐጽፋሪ) የጐደፈረ/የሚጐደፍር

ጐዶ፡ ቸግሮ/ጠፍቶ/ታጥቶ "ምን ገዶ ምን ገዶት" እንዲሉ።

ጐዶ፡ ጐበዛዝት በዋሻ/በሰቀላ ውስጥ ሥጋ እየበሉ የሚያደርጉት ዕረፍትና በዓል (ከጕዳት/ከድካም የሚያርፉበት ትልቅነትንና ጌትነትን የሚቀምሱበት)

ጐጀሬ/ገዠሞ ጐዠሬ

ጐጀብ፡ የዠማ ስም (በከፋና በጌራ መካከል የሚወርድ ታላቅ ወንዝ)

ጐጂ (ጐዳዒ) የጐዳ/የሚጐዳ/የሚያከሳ

ጐጋ (ጕጋ) የጕጕት ወገን (ፈሪ/አንበልጋ/ቡከን)

ጎግ (ቃውቃዝ) የነገድና ያገር ስም

ጎግ (ጎገወ) የያፌት ልጅ (የመስኮቦች አባት)

ጎግ ማጎግ፡ "ጎግ ጀርመን ማጎግ መስኮብ። ምስጢሩ ብዛትንና አሕዛብነትን ያሳያል። ጎግ ሕዝብ ማጎግ አሕዛብ ማለት ነው (. . ) ባላገር ግን ጉግ ማንጉግ ይላል።"

ጐጐመ (ቀቀበ) በጦር/በቀንድ ጥቂት ለተመ/ወጋ (አላቈሰለም)

ጐጓ (ጐጕኦ/ጐጕአ) አጣደፈ/አስቸኰለ

ጐጓ፡ ቋቅ አሠኘ፡ ባለማቋረጥ አስታወከ/አስመለሰ/አቀረሸ/አስፈለቀ/አስተፋ

ጐጓሚ፡ የጐጐመ/የሚጐጕም (ወጊ)

ጐጠ፡ ጕጣ

ጐጠረ (ገየጠ/ጌጠ) ጐሰረ/ጐኘረ መላ ጠቀጠቀ ወጠረ

ጐጠጐጠ

ጐጠጐጠ ገጠጠ

ጐጠጐጠ (ቈጠቈጠ) ወጣ በቀለ/ጐመጐመ (የጐጥ/የጕጥ/የጡት)

ጐጠጐጠ (ትግ. ጐጥጐጠ) ዐይንን ወጋ/አወጣ/ቦጠቦጠ "ዐይኖቹን ጐጠጐጡት። የወንዝ ዳር ቍሮች ይጐጠጕጧታል" (፪ነገ. ፳፭፡ ፯፡ ምሳ. ፲፯)

ጐጠጐጠ (ትግ. ጐጽጐጸ/ተጕመጠመጠ) ወጣ ገባ ኾነ ከፍና ዝቅ አለ

ጐጠጐጠ፡ በጕጣ ዐረሰ

ጐጠጐጠ፡ ጥርስን መዘዘ/ነቀለ

ጐጠጠ (ቈጢጥ/ቈጠጠ) አነሰ/ኰሰሰ/ቀጠነ/ተናቀ (ተመልከት፡ ጐጠጐጠን የዚህ ደጊም ነው) #

ጐጣጕጥ (ጐጻጕጽ) ዐባጣ/ጐባጣ/ሻካራ ወጣ ገባ አስቸጋሪ ሥርጥ ሰንከልካሳ ደንጐላጕል'ሥርጓጕጥ ብዙ ጐጥ ተደራርቦ ያለበት የበዛበት ስፍራ

ጐጥ (ጦች) የምድር ጕጥ (ታናሽ ዝቅተኛ ጕባ ከፍታ) "የጐጥ አለቃ" እንዲሉ።

ጐጥ ፲ጕባ

ጐጥ፡ የሰጐጥ ከፊል ስለኾነ ታላቅ ቋጥኝ ገዎቻ ሊባልም ይቻላል

ጐጥጓጭ፡ የጐጠጐጠ/የሚጐጠጕጥ (አውጪ መዛዥ ነቃይ)

ጎጭት፡

ጐጯጯ (ቈጪጪ) ቀጨጩ ዐጠረ/ዐጪር ኾነ

ጐፈረ (ቀፈረ) ረዘመ (ጐፈሬ ኾነ ቆመ ተመየደ ተበጠረ)

ጐፈረ፡ ጨቈነ/ረፈቀ/ጫረ/ማረረ

ጐፈሪያም፡ ጐፈሬ ያለው ባለጐፈሬ

ጐፈሬ (ጐፈራዊ) የጐፈር ዐይነት (በመቀስ ጫፍ ጫፉ የሚከረከም የማያላጭ መጠነኛና ረዥም የራስ ጠጕር ጕትና ብርንጎ የጐፈር ገዳይ ወይም የሌላ)

ጐፈሬ፡ የመሬት ጥቅም ሣር እኽል

ጐፈር፡ ያንበሳ ለምድ "ወታደሩ ጐፈር ለብሷል።"

ጐፈር፡ ጠጕረ ረዥም አህያ ውሻ

ጐፈር፡ ጠጕራም አንበሳ "ዐዳኙ ጐፈር ገደለ።"

ጐፈነነ (ቈፈነነ) ቀፈፈ/መረረ (ክፉኛ አገሣ አቀመ ሰቀጠጠ የኮሶ)

ጐፈየ፡ ከላ/ማንጆ ኾነ (ሥባት ዐጣ) "ሠባ እንረደው ጐፈየ እንስደደው" እንዲሉ

ጐፈጐፍ/ጐፍጓፋ፡ የተንጐፈጐፈ

ጐፈጠጠ፡ ፈጽሞ ኣረጀ/አፈጀ/ደከመ (ሰውነቱ ተጨበጠ ጐነበሰ ጐበጠ መኼድ አቃተው)

ጐፈጠጥ/ጐፍጣጣ፡ የጐፈጠጠ (ደካማ ያረጀ ያፈጀ አሮጌ ሽማግሌ)

ጐፈጨረ፡ ገፈፈ

ጐፈፍ አለ፡ ዘገም አለ

ጎፋ ጌኔ፡ የጎፋ ንግሥት

ጎፋ፡ ያገር ስም (በኃላ ቤት ያለ ክፍል አገር)

ጐፋፋ፡ ደካማ ሽማግሌ ቈርሳሳ

ጐፍላ (ሎች) ረዥምና ብዙ የውሻ ጠጕር ወይም ጠጕራም ባለረዥም ጠጕር "ጐፍላ ውሻ" እንዲሉ

ጐፍላ፡ እንቡጣ (ከነጠጕሩ ስልቻ የወጣ ሣርና ገለባ የመላበት የተጐሰረበት ባ፬ የንጨት እግር የቆመ የጥጃ ቈዳ ላም እሱን እየላሰች ወተት ትሰጣለች) "ላም በጐፍላ ትታለባለች" እንዲሉ

ጐፍናና፡ ፊቱን ያቀጨመ/ያስቀየመ/ያከፋ

ጐፍናኝ፡ የጐፈነነ/የሚጐፈንን (መራራ ነገር)

ጐፍጐፍ አለ፡ ተንጐፈጐፈ

(ቆዕ) ጓሚያ ያልበሰለ ፍሬ፡ ጨረቋ ቃሪያ፡ በትግሪኛ ጉዕ ይባላል ጓይን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው

አለ (—ጮኸጓጓ)

እጓ አለ ( እቋ አለ) ተንጓጓ አለ ጓጓ

ጓለበ፡ ተንገዋለለ/ተመረጠ/ተለየ

ጓል (ሎች) የተድበለበለ ዐፈር በመሬት ላይ እንደ ደንጊያ ጐልቶ የሚታይ ድብልብል መከሎ

ጓመጠ፡ ታኘከ/ተበላ

ጓሚያ (ጓዕ) ያልበሰለ የተክል የእንጨት ፍሬ (ጠንካራ ቃሪያ) " ጓይ ጓሚያ ጓዕ ኹሉም ከቆዕ የወጣ ነው።"

ጓሣ፡ ሣር፡ (ተመልከት፡ ጓሳ)

ጓሳ፡ የሣር ስም (የታወቀ ሣር እንደ ጣርማበር ባለ በጉም ለበስ ተራራ ላይ ከአስታ ጋራ የሚበቅል አንጓ የለሽ ሻካራ መላላ) "ለቤት መክደኛ ገመድ ለወፍጮ መጥ ረጊያ ሙሬ ይኾናል እንቀጹ ጐሰሰ ነው"

ጓረኛ፡ ዝኒ ከማሁ

ጓሮ (ገዊር/ጎረ/ጎር) ከቤት በስተኋላ ያለ ዐጥር ግቢ (ሕዝ. ፵፡ ፲፬, ፲፯, ፲፱) "ባለቤት ጓሮ ዞረ።"

ጓሮ (ጐረረ/ጐረጐረ) ጠብ/ጥል/ክርክር "ዐምባ ጓሮ" እንዲሉ (ተመልከት፡ ዐምባን ተመልከት)

ጓሮ ቤት፡ በጓሮ ያለ ሠገራ ቤት

ጓሮ ገዳይ፡ በቅርብ በጓሮ አጠገብ የገደለ "የዝኆን ገዳይ ዘፈን አዝማች።"

ጓሮኛ (ኞች) ጠበኛ ("ጥል ያለሽ ዳቦ የሚል" ጠብ ወዳድ) "ጓሮ ጠብ ተብሎ ሲተረጐም ግእዝ ጐርጐረ አንጐርጐረ ነጐር ጓር ካለው ይወጣል።"

ጓታ፡ ጌተየ

ጓታ (ገብጥ) የሆድ በሽታ (ብስና/እሕታ የሚቈርጥ/የሚጐረብጥ)

ጓታ፡ የሆድ የመብረቅ ኸት፡ ጓጓ

ጓታ፡ የመብረቅ ጩኸት ("" ማለት)

ጓች

ጓንጕል (ትግ) ሕብረ ዕንቍ/ጨሌ/ሽልማት (ዝንጕርጕር ነገር ነጭና ቀይ በሬ ሴደር ሴደርማ)

ጓንጕል፡ የሰው ስም "ጌጤ ነኸ እንደ ማለት ነው።" "ጓንጕል ዘገየ" እንዲሉ

ጓንጓ፡ የንጨት ዋሻ (ውስጠ ክፍት ዛፍ ማጓ (ቀባ) የሚገኝበት) "ጓንጓ ትግሪኛ ነው።"

ጓዕ (ቆዕ) ጓሚያ

ጓዝ (ዞች) (ገዓዝ/ጋዕዝ ዕቃ)

ጓዝ ተጋሻ፡ አንድ ወታደር ከነቤተ ሰቡ "ጓዝ ሚስት ልጅ አሽከር ጋሻ ባለቤት ነው።"

ጓዝ ጠባቂ፡ የጓዝ ዘበኛ

ጓያ (ዮች) (ጐይይ/ጐየ) በክፉ ቀን የበሉትን ሰዎች ወገብ ሰብሮ ቋንዣቸውን ያሽመደመደ ባለሐረግ እኸል "ከዚህ የተነሣ ብዙዎች ሰዎች ፈርተው እሱን ከመብላት ይሸሻሉና ጓያ ማለት ፍራትን ሽሽትን ያሳያል። ትግሬም ነበረ ይለዋል።"

ጓይ፡ የጥጥ ጓሚያ (ጓዕ)

ጓደና፡ ዘላንነት/በዱር መቀመጥ።

ጓደኛ ባልንጀራ፡ ጓደደ

ጓደኛ (ኞች) ጓድ ወይም ጓድ ያለው/ባለጓድ "ሚስትም ለባሏ ጓደኛ ናት።"

ጓደኛ()ነት፡ ባልንጀርነት/ባልደረብነት

ጓደደ (ትግ. ጓዕደደ/ኰራ) ዐበረ/ገጠመ/ባልንጀራ ኾነ

ጓዳ (ተጨማሪ ቤት) ጐደጐደ

ጓዳ (ዎች/ዶች) የዕቃ/የምግብ መክተቻ/መጐድጐጃ (በቤት ዙሪያ ተያይዞ ወይም ተቀጥሎ የተሠራ ማጀት) "የንጀራ የጠላ የጠጅ የሥጋ ጓዳ" እንዲሉ።

ጓዳ ጐድጓዳ፡ እንደ መታደያ ያልተደለደለ የቤት ሥርቻ ውስጣውስጥ የጐድጓዳ ጓዳ።

ጓዴ፡ ባልንጀራዬ/ባልደረባዬ/ቢጤ "የኔ ጓድ።"

ጓድ (ዶች) ባልደረባ/ዐብሮ አደግ/ጭፍራ

ጓድ፡ ባልንጀራ (ጓደደ)

ጓጕንቸር

ጓጕንቸር (ሮች) ትልቅ እንቍራሪት/ጕርጥ ወይም ሸርጣን/ጐርምጥ (ዘፀ. ፯፡ ፳፰፡ ፰፡ -፯፡ ራእ. ፲፮፡ ፲፫)

ጓጕንቸር፡ መንጦው የንቍራሪቱን እግር የሚመስል ትልቅ የመዝጊያ ቍልፍ

ጓጒ፡ የሚጓጓ/ከጃይ/ሠዪ/ጐምዢ።

ጓጐለ፡ ረጋ/ተቋጠረ (የደም)

ጓጐለ፡ ተድበለበለ/ድብልብል ኾነ (የቡሖ/የሊጥ) (ተመልከት፡ ካረጠ)

ጓጐረ፡ ከመያዝ/ከመጋት/ከጭንቅ የተነሣ ጮኸ/አጓራ

ጓጐት፡ ወንዴ ቋቍቻ/ቅርፍርፍ/ሽርክርክ (ከቀይ ወደ ቀይ ከጠይም ወደ ጠይም ገላ የሚጋባ ተላላፊ ተረማማጅ የከክ ወገን ካፍለኛ በቀር ሽማግሌ የማይዝ - ቋቍቻና ጓጐት አንድ ስም ነው)

ጓጓ (ጐጕአ) ከጀለ/ተመኘ/ሠየመ/ጐመዠ (ቶሎ ለማግኘት ተስፋ አደረገ)

ጓጓ አለ፡ ተንጓጓ።

ጓጓ አደረገ፡ አንጓጓ።

ጓጓ አደረገ፡ አጓጓ።

ጓጓላ፡ የጓጐለ/ድብልብል/የረጋ/የተቋጠረ (ቋጣራ ጭን)

ጓጓላነት፡ ጓጓላ መኾን/ቋጣሪነት።

ጓጓሪ፡ የጓጐረ (በሬኛ/ጯኺ)

ጓጓራ፡ ዝኒ ከማሁ (የሚጓጕር)

ጓጓታ (ዎች) መንጓጓት/ጩኸት። "የጋሻ ጓጓታ" እንዲሉ።

ጓጓታ፡ መንጓጓት፡ ጓጓ

ጓጓይ፡ የሚጓጕል/ተድበልባይ

ጓጓጠ (ጐጽጐጸ) ወጋ/ሸቀሸቀ/ቈሰቈሰ

ጓጓጭ (ጮች) የጓጐጠ/የሚጓጕጥ/የሚሸተሽቅ (ሸቅሻቂ)

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ