ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ሰ ፡ ፳፩ኛ ፊደል በግእዝ ፊደል እልፍ ቤተ (በአበገደ) ። በፊደልነት ስሙ "ሳት" ሲሆን፣ በአኃዝ (ቁጥር) ደግሞ ሰ=፫፻ (300) ይባላል።
ሰ፡ የዘ, የከ, የጸ ተለዋጭ (ምትክ) ነው። በግእዝ "አመዝገነ" የሚለው በአማርኛ "አመሰገነ", "ምዝጋና" > "ምስጋና", "መከነ" > "መሰነ", "መካን" > "መሲና", "ጸልመ" > "ሰለመ", "ጸለለ" > "ሰለለ", "ጸጥ" > "ሰጥ" እንዲሁም "በተከ", "ቀተረ", "ወዘወዘ" የሚሉት በቅደም ተከተል "በሰከ", "ቀሰረ", "ወሰወሰ" መሆኑን ያሳያል። ፪ኛውን "ሰለመ" እና ፫ኛውን "ስለለ" ተመልከት።
ሰሓጢ (ሰሐጠ)፡ በትግሬ ክፍል ያለ በረሓ (ትርጓሜው ቈንጣጭ ማለት ነው - ትንኙን ያሳያል) ።
ሰለ፡ በለዘ፡ ነጭና፡ ጥቍር፡ ኾነ ።
ሰለሔ መለሔ፡ "ሰለሔ" እንዳለፈው "መለሔን" እይ።
ሰለሔ፡ ገንፎ በቅቤ።
ሰለለ (ትግ. ሰለለ/ኰበለለ)፡ መነመነ፡ ቀጠነ (ከውፋሬ ራቀ - ያካል/የቃል - መሳ. ፫፡ ፲፭፡ ማቴ. ፲፪፡ ፲፡ ዕብ. ፲፪፡ ፲፪) ። የጌዜና ኀላፊ ትንቢቱ "ይሰል/ይሰላል" ይላል።
ሰለለ (ጸለለ/ተንኳፈፈ)፡ ጠለለ።
ሰለለ፡ ሰው ኹሉ የሚናገረውን ሰማ፡ ወሬ ጠበቀ። ከጦርነት በፊት የጠላትን አገር እየ አስተዋለ ተመለከተ/ገመተ (ብዛትን/ኀይልን/የሰዉን ሐሳብ/ያገሩን መውጫ/መውረጃ/መግቢያ መረመረ/አጠና/በክፉ ጐበኘ) ።
ሰለለ፡ ወጣ/ወረደ (ኢያ. ፪፡ ፪) ። "መሰላል" ማለት ከዚህ የወጣ ነው። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱ "ይሰልል/ይሰልላል" ይላል።
ሰለል ብሎ ገባ፡ እንደ ሰላይ/እንደ ውሃ ሳይታይ/ሳይታወቅ ማለት ነው።
ሰለል አለ፡ ስተት አለ።
ሰለልታ፡ ጠለልታ (ጠላ ከተመላ በኋላ በላይ የሚታየው ውሃና ዐሠር) ። ዳግመኛም ዐሠር ውሃ ይባላል።
ሰለልኩላ፡ በላስታ ውስጥ ያለ አገር (የቅዳሴ ዜማ መምህራን የሚገኙበት - ሰለልኩላ ባንኮበርም አለ) ።
ሰለመ (ሰለም/ሰለመ)፡ ማተቡን በጠሰ፡ እስላም ኾነ፡ ኦሪትን/ወንጌልን ወይም ሌላውን ሃይማኖት ተወ/ካደ፡ የእስላምን እምነት ተቀበለ፡ ዳነ።
ሰለመ (ጸልመ)፡ ጨለመ።
ሰለመ፡ አፈቀረ፡ አመሰገነ፡ አሳረፈ፡ አ...ሰላሚ የሚል።
ሰለመጠ (ሰለጠ)፡ ሳያኝክ ዋጠ/ሰለቀጠ ።
ሰለመጠ/ሰለቀ፡
ሰለሰለ (ትግ. ሰንሰነ/ከሳ)፡ ቀጠነ፡ ስለተ፡ መነመነ፡ ኰሰሰ (ኢዮ. ፴፫፡ ፳፩) ። ሥሩ "ሰለለ" ነው። (ተገብሮ) ።
ሰለሰለ፡ ሸነሸነ፡ ነጠለ፡ ሠነጠቀ (ሰሌንን/ግራምጣን - ገቢር) ። "ስነሰነን" እይ።
ሰለሰል/ሰልሳላ፡ የሰለሰለ (መንማና) ።
ሰለቀ (ሠለቀ)፡ ጕርሃን/ጤፍን ፈ... አደቀቀ/ደቈሰ/አላመ/አለሀበ።
ሰለቀ፡ በጣም ዐመመ/መታ/አደከመ ሰውነትን ።
ሰለቀጠ፡ ሳያኝክ ዋጠ። "ሰለመጠን" እይ።
ሰለበ (ሰሊብ/ሰለበ - ገፈፈ/ዐለገ)፡ የወንድን ብልት ቈረጠ/ጐመደ/ደደ እስከ ዕንብርት፡ ገሸለጠ፡ ጃንደረባ አደረገ።
ሰለበ፡ ምትሀት/ባስማት በሚዛን የሰውን ምርት/ቡሖ/ቅቤ/ጥጥ ሳበ/ወሰደ (የሌላውን ጥቅም አሳነሰ/ኣጐደለ፡ የራሱን መላ አበዛ) ።
ሰለባ፡ ማንኛውም የተቀማና/የተገፈፈ/የተሰረቀ ዕቃ። "ሌባ ከነሰለባው ተያዘ" እንዲሉ።
ሰለባ፡ ቈረጣ።
ሰለባ፡ የተቈረጠ ቍላ (የግዳይ/የድል ምልክት - ፩ሳሙ. ፲፰፡ ፳፭) ። (ተረት)፡ "ምርት ከገለባ፡ ግዳይ ከሰለባ።"
ሰለተ (ሰልቶ/ሰለተ/ዘበተ)፡ ሰንበሌጥን ዘቀዘቀ (እንደ ዘበት በቀላል ከደነ ክዳንን አሣሣ) ።
ሰለተ፡ ለተተ፡ ደከመ፡ ከሳ፡ ቀኑ መነመነ፡ ፍሬ አልባ ቀረ፡ ደረቀ (ተገብሮ) ።
ሰለተ፡ ከፈለ/ለየ (ገቢር) ።
ሰለታ፡ ሥሥ ክዳን ዝቅዝቅ።
ሰለቸ፡ ታከተ፡ ደከመ።
ሰለቸ፡ ጠበ፡ ጠላ፡ ነቀፈ፡ ተሠቀቀ፡ ተንገፈገፈ (ዘፀ. ፯፡ ፲፯፡ ዘኍ. ፳፩ - ፳፡ ኢዮ. ፲፡ ፩፡ ሕዝ. ፮፡ ፱) ። (ግጥም)፡ "ፀል፵ መረቁ ወጡ፡ ሰለቸን ምኒልክ ተነሥቶ ሽሮ ባበላን።" "ብዙ ቢተቹ ይሰለቹ" እንዲሉ። "እንጃን" እይ።
ሰለንዳ (ሰነዳ)፡ ዝግጅት/መቀናበር።
ሰለንዳ ቢስ፡ ዝግጅተ መጥፎ።
ሰለከ፡ ቀጠነ፡ ቀጥ አለ፡ ወደ ውስጥ ኼደ (ሰልቶ ገባ) ። "ሾለከን" እይ።
ሰለከከ፡ አማረ፡ ተዋበ፡ ሸገነ (ካለማማር) ።
ሰለክላካ/ስልክልክ፡ የተስለከለከ/ፍልክልክ/ሹልክልክ።
ሰለጀጅ/ሰልጃጃ፡ የተንስለጀጀ/የሚንሰለጀጅ (እንስልጅ ፈዛዛ) ።
ሰለጠ (ሰልጦ/ሰለጠ)፡ ቀና ኾነ፡ በጀ፡ ተከወነ፡ ተጨረሰ/ቀለጠፈ። ፪ኛውን "ሰላ" ተመልከት።
ሰለፈ (ዐረ)፡ አበደረ በዱቤ ሰጠ።
ሰለፈ፡ ቀረበ፡ ቸኰለ፡ አቈተመ (ለምግብ/ለወሬ) ።
ሰለፈ፡ ተጠረረ፡ ተዘጋጀ ለውጊያ (ተገብሮ) ።
ሰለፈ፡ ደከረ፡ ደቀነ ጸብትን (ገቢር) ።
ሰላ (ተስሕለ)፡ ስለታም ኾነ፡ ተባሾለ፡ ሾለከ።
ሰላ (ትግ. ሰልሐ፡ ዐረ. ጸለሐ፡ ግእዝ. ተሠርሐ)፡ በጀ፡ አማረ፡ ሰመረ፡ ቀና፡ ቀለጠፈ፡ ተከወነ (፪ዜና. ፳፡ ፳፡ ሉቃ. ፰፡ ፲). "ወሰላ ወሰልሰላ ዐንገቱ በምን ሰላ? ነጭ ጤፍ እየበላ" እንዲሉ አባትና እናት ልጃቸውን።
ሰላ ገደድ፡ ቅን፡ ጠማማ ወይም ቀና ጠመመ። "እከሌ ሰላ ገደድ ያውቃል" እንዲሉ።
ሰላላ፡ መላላ (ትክክል ያልኾነ ፈትል - ቅጥነትና ጥቂት የቀጥታ ውፍረት ባንድነት ያለው - የዝንብ አንዠት/የሰዶ ጕልበት የመሰለ) ።
ሰላላ፡ የሰለለ/የመነመነ።
ሰላሌ (ኦሮ)፡ የነገድና ያገር ስም።
ሰላሌ፡ አቅኒው ነው።
ሰላመ ገብርኢል፡ ቅዱስ ገብርኤል ለመቤታችን ያቀረበው ምስጋና (ከአቡነ ዘበሰማያት ጋራ የሚጸለይ) ።
ሰላማ፡ ብርሃነ አዜብ (ንኡስ ሰላማ) በ፲፻ ዓ.ም. የነበረ የሐበሻ ጳጳስ (ያገር ተወላጅ) ።
ሰላማ፡ አንደኛው መዠመሪያው የኢትዮጵያ ጳጳስ (ከሣቴ ብርሃን ፍሬምናጦስ በ፬፻ ፱ዓ.ም. የነበረ - ማ... ያገሪቱ ዝዝ... ነው) ።
ሰላማዊ፡ የሰላም/ባለሰላም ሰው (ደንሲ፡ ራም፡ ከብት፡ እንስሳ) ። "ሰላማዊ" የግእዝ ነው፡ በአማርኛ "ሰላመኛ" ሊባል ይኵላል።
ሰላም ላንተ፡ ምስጋና/ደኅንነት ላንተ ይኹን/ይደረግ ።
ሰላም፡ አጭር፡ ደጭና ደኅንነት፡ ጤና፡ ሤራ፡ ዕረፍት፡ ጸጥታ፡ ፍቅር፡ አንድነት፡ ምስጥና።
ሰላም፡ የዜማ ስም (የቁም ዜማና የማሕሌት ክረም) ።
ሰላምተኛ፡ ባለሰላምታ ሰው (ጠያቂ) ። "ሰላምታ ሰጠ" (ጠየቀ፡ "እንዴት ነኸ?") ።
ሰላምታ፡ በሰባቱ ጊዜያት የሚጸለይ የአባ ጊዮርጊስ ድርሰት አለ።
ሰላምታ፡ የፍቅር ምስጋና ደብዳቤ (የተላከ ከይድረስ ለካለ በኋላ "እንዴት ሰንብተኻል?" ከመኻል ብሎ የሚዠምር) ።
ሰላምታ፡ ጤና ይስጥልኝ ማለት፡ እጅ መንሣት፡ ከበሬታ መስጠት (ሉቃ. ፲፩፡ ፵፫) ።
ሰላሰለ፡ ሸናሸነ/ነጣጠለ ።
ሰላቂ፡ የሰለቀ/የሚሰልቅ (አላሚ/አለዛቢ ደቋሽ) ።
ሰላቢ (ዎች)፡ የሰለበ/የሚሰልብ (በንቋይ ምትሀተኛ ጝርተኛ) ።
ሰላቢነት፡ ሰላቢ መኾን።
ሰላች (ቾች)፡ የሰለተ/የሚሰልት።
ሰላኪ፡ የሰለከ/የሚሰልክ (ዐልቅት) ።
ሰላይ (ዮች)፡ የሰለለ/የሚሰልል (ጕበኛ/ተመልካች/ነገር ጠባቂ/"አገር ምን ይላል" ባይ - ኢያ. ፪፡ ፩፡ ፪ነገ. ፱፡ ፲፯, ፲፰፡ ፰፡ ሉቃ. ፳፡ ፳).
ሰላይ፡ ከሰንጠረዥ መጫወቻ አንዱ።
ሰላይነት፡ ሰላይ መኾን (ጕበኛነት) ።
ሰላጢን፡ ጦር፡ ሠለጠ።
ሰላጣ፡ የጐመን ዐይነት ቅጠል (ሳይቀቀል የሚበላ) ።
ሰላጤ፡ ሕፅን፡ ሠለጠ።
ሰላፋ፡ ብድር ልቆ ዱቤ ።
ሰላፋ/ሰላፍ፡ የሰለፈ/የሚሰልፍ (ችኵል እቈታሚ) ።
ሰሌን (ኖች)፡ የዘንባባ ሙሽራ (ሸለም - ከዚሁ የተሠራ ምንጣፍ - ኢሳ. ፲፱፡ ፲፭) ።
ሰሌዳ፡ ሉሕ (ያልተቀጻ ብራና/ወረቀት፡ ዝርግ/ጠፍጣፋ ሥራ፡ ጡብ፡ ብረት፡ እብነ በረድ፡ ደንጊያ፡ ንሓስ፡ የዝኆን ጥርስ - በላዩ ጽፈት የሌለበት) ። ሲበዛ "ሰሌዳዎች/ሰሌዶች" ይላል።
ሰል፡ ገመድና ጕንጕን የሚኾን ዋና የመስክ ሣር።
ሰልሳይ፡ የሚሰለስል (ሸንሻኝ መንማኝ) ።
ሰልቀጥ/ስልቅጥ አደረገ፡ ዋጥ አደረገ ።
ሰልቃጭ፡ የሰለቀጠ/የሚሰለቅጥ (ዋጭ) ።
ሰልቶ፡ ስል ኹኖ፡ ሾሎ/ሾልኮ። "ሰልቶ ገባ" "ሾልኮ ገባ"።
ሰልቷል፡ ቀና ብሏል፡ በጅቷል፡ ዕምሯል፡ ስል ኹኗል፡ ሾልኳል (ስበቱ/መጥረቢያው ፈሰሱ) ።
ሰልቺ፡ የሰለቸ/የሚሰለች ።
ሰልካካ/ስልክክ፡ መልከቀና/አፍንጫ ስንደዶ። "ፊተ ሰልካካ" እንዲሉ።
ሰልፈኛ (ኞች)፡ ሰልፍ የሚያሳይ/ባለሰልፍ ወታደር/ጭፍራ።
ሰልፈኛነት፡ ሰልፈኛ መኾን።
ሰልፍ፡ የጦርነት ዝግጅት (የደመራ ለትና በዘመቻ ጊዜ የሚደረግ ከነጦር መሣሪያው የሰራዊት መታየት) ።
ሰልፍ፡ ጦርነት/ውጊያ (፩ሳሙ. ፲፯፡ ፵፯, ፵፰፡ ፳፯፡ ፲፡ ፴፩፡ ፫) ። በግእዝ "ጸብእ/ቀትል" ይባላል።
ሰልፎ፡ የሚጤ መውጊያ ሹል ዘንግ።
ሰሎሞን፡ የሰው ስም (የዳዊት ልጅ የእስራኤል ንጉሥ - ብልኀ/ዐዋቂ/ፈላስፋ - ምሳሌን/መክብብን/ጥበብን/መሓልይን የደረሰ) ። ትርጓሜው ፍቅርን/ሰላምን ያሳያል።
ሰመለ፡ ዠለጠ/አለፋ/አለሰለሰ ቈዳን፡ ላገ/ፋቀ ዕንወትን ።
ሰመለለ፡ ጠጣ/ዥው አደረገ፡ ሰመጠጠ።
ሰመመ (ዘመመ)፡ አሸለበ/አንቀላፋ።
ሰመመናም፡ ባለሰመመን ።
ሰመመን፡ ሽልብታ/እንቅልፍ ።
ሰመሰመ (ትግ. ሸምሸመ)፡ ቶሎ ቶሎ ቃመ/በላ (በሬው) ።
ሰመረ (ሰምረ)፡ በጀ/አማረ/ማለፊያ ኾነ (ያዝመራ/የሥራ) ። "ዲያቆኑ መሥዋዕት ይሰምርለታል"።
ሰመረ (ፀመረ)፡ ቸነከረ/ጨመረ/እገባ ።
ሰመራ)፡ ሰኔ ።
ሰመራ)፡ አሰመራ/አሰማራ (ረዐየ/አውፈረ)፡ ነዳ/ወሰደ/እዱር አገባ/አሠራጨ (ኤር. ፴፩፡ ፲፡ ሕዝ. ፴፬፡ ፲፬) ።
ሰመሬታ፡ የገብስ ስም (ቶሎ የሚደርስ) ።
ሰመነ (ሰምኖ ሰመነ)፡ ስምንት አደረገ፡ በስምንት ከፈለ።
ሰመነ፡ ሰመረ።
ሰመነ፡ ከበደ/ተጫነ።
ሰመነ ዥረት፡ ዳር ዳሩን ሰመግ የሚበቅልበት ዠማ አዳባይ (የዱሮ ሰዎች በየሳምንቱ ቅዳሜ ጦርነት የሚያደርጉበት የጦር ተማሪ ቤት) ። "ሰመጎ ዥረት ያለሽ ዕዳሪ መች ትቀሪያለሽ ሳትሞከሪ፡ ሰመዕ ዥረት ያለሽ አሞራ ሥጋውን በልተሽ ለምዱን ዐደራ እንዳለ ወያኔ።"
ሰመከ፡ ተጠጋ (ግእዝ) ።
ሰመግ፡ በቈላ የሚበቅል ዐረግ (ፍሬውን ሴቶች በክር እየሰኩ በእግራቸውና በእጃቸው ባንገታቸው ላይ ያስሩታል - ያጌ ጡታል። ሲበዛ "ሰመጎች" ይላል) ።
ሰመግ ዐይን፡ ዐይነ ትንሽሽ ሰው።
ሰመግ፡ የሰመግ ፍሬ (ስንድድ ዐንገት የዦሮና የእጅ ጌጥ) ። "ስመግ ዐንገት" መባሉ ውስጠ ክፍትና ያንገት ጌጥ በመኾኑ ነው። "ክሣድን" ተመልከት ።
ሰመግማ፡ ጠጕሩ እንደ ሰመግ ፍሬ ጥቍረትና ንጣት ያለው በሬ/ፍየል/ፈረስ (ጠቃጠቆ) ። ዳግመኛም ስሙ ሰመግ ይባላል።
ሰመጎ፡ ቃለ አጋኖ፡ ወይም አክብሮና ኣንክሮ ።
ሰመጠ፡ ሰጠመ ።
ሰመጠጠ (መጠጠ)፡ ሸመጠጠ/ጠጣ/ዥው አደረገ/ጨለጠ።
ሰሚ (ሰማዒ)፡ የሰማ/የሚሰማ (አድማጭ - ያዕ. ፩፡ ፳፭) ።
ሰሚ፡ በቶሎ ስለት የሚያደርስ ታቦት ወይ ብላ።
ሰሚ፡ አንተ እየተባለ ቅኔና ምስጋና የሚነገርለት የቅርብ ወንድ ።
ሰሚ፡ የተማሪን ቅኔ ሰምቶ የሚያርም የቅኔ ምር...
ሰሚነት፡ ሰሚ መኾን።
ሰሚዎች፡ ሰሞች የሚሰሙ አድማጮች (ያዕ. ፩፡ ፳፫) ።
ሰማ (ሰምዐ)፡ አደመጠ ነገርን ተቀበለ (፪ሳሙ. ፲፱፡ ፲፱) ። (ተረት)፡ "ያልሰማ ዦሮ ከጎረቤት ያጣላል።" "ሲያውቅ የተኛ ቢጠሩት አይሰማ።" (አልሰሜ)፡ "ኣልን" ተመልከት።
ሰማ፡ ጋለ/ሰማ ።
ሰማማ፡ አደማመጠ።
ሰማርያ፡ በእስያ ውስጥ በፍልስጥኤም ክፍል ያለ አገር (ቀድሞ ያሥሩ ነገደ እስራኤል መንግሥት የነበረበት) ።
ሰማኒያ (፹)፡ የቍጥር ስም (በሰባና በዘጠና መካከል ያለ ያሥር ቤት አኃዝ - ስምንት ዐሥር) ።
ሰማኒያ አወረደ፡ ሚስቱን ፈታ ለቀቀ በዳኛ ፊት ተፈጥሞ ።
ሰማኒያ ከነዳ፡ ተፈጥሞ ስለ ቀረ ፲፭ ብር ከፈለ።
ሰማኒያ፡ የሳምንት ቀጠሮ ፈጠም ።
ሰማኒያ፡ የች ኹለት አርባ።
ሰማኒያ፡ የውል የጋብቻ ቃል ማሰሪያ (እንደ ፊርማ ያለ ፊርማን የመሰለ - ይኸውም ንጉሥ ይሙት ማለት ነው) ። (ተረት)፡ "ሰማኒያ ለማገጃ ስለት ለማረጃ።"
ሰማዕት (ሰዐም)፡ ስለ ሃይማኖት የሞተ የሃይማኖት ምስክር። ሲበዛ "ሰማዕታት" ያሠኛል።
ሰማዕትነት፡ ሰማዕት መኾን (በሰይፍ/በእሳት/በክፉ ሥቃይ መሞት) ።
ሰማየ ሰማያት፡ ላይኛ መጨረሻ ከሰማዮች በላይ ያለ ሰማይ (መዝ. ፻፲፭፡ ፲፮፡ ፻፵፰፡ ፲፬) ። "ኣርያምን" እይ።
ሰማዩ ቀላ)፡ ደመነ ።
ሰማያም፡ ባለሰማይ (የሰማይ ጌታ) ።
ሰማያዊ፡ ሰማይማ ሰማይ የሚመስል (ኒል ቀለም/ጥለት ልብስ/ካባ) ።
ሰማያዊ፡ የሰማይ/በሰማይ ያለ/የተቀመጠ (እግዜር/መልአክ) ።
ሰማያይ፡ ዝኒ ከማሁ።
ሰማይ (ሰመየ)፡ ከምድር በላይ ያለ የውሃ ባጥ ጣራ (ያለባላ/ያለምሰሶ/ያላንዳች ድጋፍ በፈጣሪ ትእዛዝ የተሰቀለ ጠፈር - የሌሊት/የቀን መብራቶች ጨረቃ/ኮከብ/ፀሓይ በበታቹ የሚታዩ) ። "ሰማይ ያለባላ ምድር ያለካስማ" እንዲሉ። ሲበዛ በግእዝ "ሰማያት" በአማርኛ "ሰማዮች" ያሠኛል፡ እነዚሁም ሰባት ናቸው (ኢሳ. ፵፰፡ ፲፫፡ ማቴ. ፫፡ ፲፮) ።
ሰማይ፡ በሰማይ የሚኖር አምላክ ፈጣሪ ("የሰማይ ቍጣ" እንዲሉ) ።
ሰማይ ቤት (የሰማይ ቤት)፡ በሰማይ ያለ ቤት (ገነት/መንግሥተ ሰማይ) ።
ሰማይ ዳሱ፡ ረዥም ሰው/ደመና ገፊ (ሔኖ. ፯፡ ፪, ፬፡ ዘዳ. ፪፡ ፳, ፳፬) ።
ሰማይ ጠቀስ፡ ዐይቦ የሚባል የነጭ በሬ ቀንድ ("ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ጅራው ምድር አበስ" እንዲሉ) ። የዚህም ምስጢር የጌታችንን አምላክነትና ሰውነት ያስረዳል ።
ሰማይና ምድር፡ የተለያየ/የተራራቀ ነገር (አንድነት የሌለው) ።
ሰሜን፡ የማእዘን ስም (ካራቱ የዓለም ማእዘኖች ሦስተኛው የምድር ጎፍ ራስጌ በስተግራ ያለ) ።
ሰምሳሚ፡ የሰመሰመ/የሚሰመስም (ቃሚ) ።
ሰምዛ፡ ሰንሰል (ዮሐ. ፲፱፡ ፳፱) ። በግእዝ ግን "ስማዝ/ሸንበቆ/ጐሽ/መቃ" ተብሎ ይተረጐማል።
ሰሞነኛ (ኞች)፡ ከእሑድ እስከ እሑድ በቤተ መቅደስ የሚያገለግል ቀዳሽ ሠላሽ ቄስ/ዲያቆን። ("ፈራ" - ፈረየ ብለኸ ፍሬን እይ) ።
ሰሞነኛነት፡ ሰሞነኛ መኾን።
ሰሞን (ሰሙን)፡ የስምንት ቀን ስም፡ ዳግመኛም ሰውን በግእዝ ያንድ ዕለት ቅጽል ይኾናል፡ ትርጓሜውም ስምንተኛ ይባላል።
ሰሰ፡ ላሰሰ/ነቀለ/ጠረገ።
ሰሰለ (ሰስሎ...ራቀ) ።
ሰሰለ፡ ተወገደ/ራቀ ።
ሰሳ፡ የዛፍ ስም (የጦሚት ዐይነት ዕንጨት) ።
ሰስ፡ በቁሙ ሠሥ ።
ሰረም፡ ሰረቀ ።
ሰረም፡ ቈለቈል።
ሰረሰረ (ሰረረ)፡ ሰነፈጠ፡ በጥንቃቄ በሳ ነደለ ውስጥ ለውስጥ ኼደ ። (ተረት)፡ "ጣዝማ ይሰረስራል ዳኛ ይመረምራል።"
ሰረሰር፡ ያከርካሪ መትረብ ከማዥራት እስከ ወገብ በታች ያለ...ደል ።
ሰረረ (ሰሪር/ሰረረ)፡ ከፍ አለ፡ ወጣ/በላይ ኾነ፡ ጠቃ/መታ/ወነገ። "ቀኝም ሰረሩ ግራም ሰረሩ መገናኛው ኰሩ ወጣ"። (ተረት)፡ "ፍየል በግርግር እናቱን ይሰር"።
ሰረረ፡ ሰረሰረ ።
ሰረሪን፡ የተክል ስም (ሥሩ መቅመቆ ቅጠሉ ቀረሻሽንቦ የሚመስል ተክ) ።
ሰረቀ (ሰሪቅ/ሰረቀ)፡ ሳይታይ የሰው ገንዘብ አነሣ ወሰደ ሞጨለፈ (ቤትን ቈፍሮ ሰርስሮ ነድሎ ኪስን በርብሮ) ።
ሰረቀ፡ አከሳ። "ሰውነቱን ይሰርቀዋል።"
ሰረቀ፡ ጠቀሰ።
"በይኑ ይሰርቃል።"
ሰረበ፡ ማገሠረበ ።
ሰረበ፡ ፈሰሰ/ተንሿሿ (ግእዝ) ።
ሰረተተ) አንሰረተተ፡ አረዘመ/ጐተተ (ልብስን) ።
ሰረተት/ሰርታታ፡ የተንሰረተተ/የሚንሰረተት (ጐታታ) ።
ሰረነቀ (ሰረቀ)፡ ወደ ስናቅ ወደ ሰርን ወጣ ዐፈነ፡ ሰነፈጠ ትን አለ፡ ዐነዘዘ ።
ሰረየ (ሰርይ/ሰረየ)፡ እቀለለ/ተወ/ይቅር አለ (ኀጢኣትን በደልን) ።
ሰረየ፡ መድኀኒት አደረገ፡ ሠ...
ሰረጀ (ሰረገ - ዐረ ሰረጀ ለጐመ)፡ ጠለፈ/ጠልፎ ጣለ/አሰናከለ/አወደቀ። ባማርኛው "ጀን" ባረብኛው "ረን" አጥብቅ ።
ሰረገ (ሰሪግ/ሰረገ)፡ አደራጀ/ደገሰ ። ሰረገ፡ ልጅን አስጌጠ/ኳላ ዳረ ። ሰራጊ (ዎች)፡ የሰረገ/የሚሰርግ (ደጋሽ ዳሪ) ።
ሰረገ፡ ወደ ውስጥ ገባ፡ ሠ...ረገ ።
ሰረገላ፡ የመንኰራኵር ጋድም፤—ሀ...
ሰረጠ፡ ወጣ ሠረጠ ።
ሰረፈ (ሰሪፍ/ሰረፈ በሳ)፡ ሸረፈ/መነዘረ ። "ሰረፈ የካህናት፡ ሸረፈ የሕዝብ አማርኛ ነው"።
ሰረፋ) አንሰራፋ፡ አሰፋ/ኣንጋለለ/ዘረጋ ።
ሰሩር፡ የዐይን ግርማ ።
ሰሪ (ዎች/ሰራሒ)፡ የሰራ/የሚሰራ (ዐራሽ ቈፋሪ) ።
ሠሪታ፡ የሠራች (ዐሻሚ ቈናኝ) ።
ሰሪቴ ሻጠ፡ "ሰሪቴ በራሱ ላይ አሰረ አደረገ ሲያውቅ አበደ"።
ሰሪቴ፡ የንጨት ስም (ኹለተኛም ቀስተኒቻ ይባላል) ።
ሰራ (ሰርሐ/ደከመ)፡ ዐረሰ/ቈፈረ/ገበረ/አዘመረ/ዐጨደ/ከመረ/ወቃ ።
ሰራረቀ፡ አነሣሣ/ወሳሰደ ።
ሰራሪ፡ የሰረረ/የሚሰር (ጠቂ አውራ አለሌ) ።
ሰራራ፡ ዐራረሰ/ቈፋፈረ ።
ሰራቂ (ቆች)፡ የሰረቀ/የሚሰርቅ (ሌባ ሙጥልቅ እጀኛ) ።
ሰራን፡ ነጭና ጥቍር ፈረስ ዝንጕርጕር ጠቃጠቆ (ዘካ. ፮፡ ፫) ። በግእዝ "ኰሰኰስ" ይባላል ። ዘሩ "ሶራ" ነው፡ "ወሰራን" እይ ። "ሠራና" "ሰራን" ባማርኛ ይገጥማሉ ። (አዝማሪ)፡ "የሐመር ጌታ የዱሪ ኵሩ ነው አሉ ተከባሪ፡ እኛስ ሲገድል ያየነው የሰራን ጌታ ነው"።
ሰራኖች፡ ዝንጕርጕሮች ፈረሶች (ዘካ. ፮፡ ፮) ።
ሰራዊት፡ ዘጠኙ የስም ምትኮች እነዚሁም ርሱ/ርሷ/አንተ/አንቺ/እኔ/ርስዎ/ርሳቸው/እናንተ/እኛ ናቸው ።
ሰራዊት፡ የጭፍራ ስም (የዠግና የሐርበኛ የጦረኛ ማኅበር በያለቃውና በያበጋዙ የሚታዘዝ ብዙ ወታደር) ። ባማርኛ ደንብ ሲበዛ "ሰራዊቶች" ያሠኛል፡ በግእዝ ግን "ሰርዌ" ያንድ "ሰራዊት" የብዙ ነው። ባ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ የዘመተው
ሰራዪ፡ የሰረየ/የሚሰርይ (ቄስ) ።
ሰራዪት፡ በባላገር ይነገራል፡ "ሰራዊትናሰራዪት" ውስጠ ብዙ ነው። "አራዊትን" ተመልከት። "ሠራዊት" ተብሎ ቢጻፍ ግን ትርጓሜው ሌላ ነው ። "ሠርዌን" አስተውል ።
ሰራዪት፡ ጭፍራ፡ ሰርዌ ።
ሰራዬ፡ ያገር ስም ሠራዬ ሶርያ (በእስያ ክፍል ያለ ታችኛውና ላይኛው የአሶር የአራም አገር) ።
ሰራፊ (ፎች)፡ የሰረፈ/የሚሰርፍ (መንዛሪ - ማቴ. ፳፩፡ ፲፪፡ ፳፭፡ ፳፯) ።
ሰር፡ የሞፈር ቂጥ ድግርና ቅትርት የተዋደዱበት ።
ሰር፡ የተጠመደ በሬን ቁም ማለት ።
ሰርመዲ፡ ራስ መሸፈኛ ሠር...መዲ ።
ሰርሳሪ (ዎች)፡ የሰረሰረ/የሚሰረስር...
ሰርብ፡ ፈሳሽ ሿሿቴ ።
ሰርተት ሰርተት አለ፡ ጐተት ጐተት አለ (ሥራ ፈታ) ። (ግጥም)፡ "እንደ ተዳላት ሴት ባሏ እንደ ሞተላት ቀሚሴን አጥልቄ ልበል ሰርተት ሰርተት"።
ሰርተት፡ ጐተት፡ ሥራ ኣልባነት። "አንድ ዓመት ሰርተት አንድ ዓመት ከርተት" እንዲሉ።
ሰርናም፡ ሰርነ ረዥም ሰው ።
ሰርናቂ፡ የሰረነቀ/የሚሰረንቅ (ሰንፋጭ) ።
ሰርን (ኖች)፡ ያፍንጫ ተረተር ።
ሰርካማ፡ ያገር ስም ።
ሰርክ ምሽት፡ ዘወትር፡ ሠ...ርክ ።
ሰርዌ (ሰረወ አሸነፈ)፡ የጦር አበጋዝ (ግእዝ) ።
ሰርዲታ፡ አንዲት ሽሩባ። "ተረረ ብለኸ ተሬን" እይ ።
ሰርዶ (ዎች)፡ የሣር ስም የታወቀ ማር አንጓ ያለው። "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" አለች አህያ። "ያገሩን ሰርዶ ባገሩ ገበሬ"።
ሰርገኛ (ኞች)፡ ባለሰርግ (የወንድ ሙሽራ ተከታይ) ። (ተረት) "ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ"። "ሰርገኞች መጡ ብቅል ኣስጡ"። "ዐደመ ብለኸ ዕድመኛን" እይ።
ሰርገኛ፡ ነጭና አቦልሴ ጢፍ (ተፈጥሮው ቅይጥ ውጥንቅጥ የኾነ) ። "ሰርገኛ" መባሉ ነጩ የሙሽራውንና የሚዜዎቹን አቦልሴው የተከታዮቹን ልብስ ያሳያል ።
ሰርግ (ጎች)፡ የጋብቻ ድግስ (የሙሽራውና የሙሽራዪቱ አባትና እናት የሚደግሱት መብልና መጠጥ - ዮሐ. ፪፡ ፩, ፪፡ ራእ. ፲፱፡ ፯, ፱) ። (ተረት) "ያይጥ ሞት የድመት ሰርግ ነው"። "ሠረፃ እሠረፃ" ብለኽ "አሥርግን" ተመልከት።
ሰርግና ምላሽ፡ በጦም ምክንያት ተከታትሎ የሚደረግ ሰርግና ቤት ማያ ።
ሰርግና ምላሽ፡ ባለቤት ሳይኖር እንደ ልብ መብላት መጠጣት በሰው መሰናዶ መደሰት ።
ሰርግና፡ በመራቤቱ ክፍል ያለ አገር።
ሰርጓይ (በዓለ ሰርጕ)፡ በ፪፻ ዓ.ም የነበረ የሐበሻ ንጉሥ (ትርጓሜው "ባለ ሽልማት" ማለት ነው) ።
ሰርፍ (ዘርፍ)፡ ጌጠኛ የንጉሥ ምንጣፍ ሰፊ ባለዘርፍ ቀጪን ያልጋ ልብስ፡ በሬሳ አጐበር ላይ የሚደረግ የሐር መጐናጸፊያ ዐይነ ርግብ መሳይ (ምሳ. ፯፡ ፲፯) ።
ሰቀለ፡ ሰራ ።
ሰቀላ፡ ስቅሎሽ (የማንጠልጠል ሥራ) ።
ሰቀላ ቤት፡ አንደ ሰቀላ የተሠራ ቤት። (ተረት)፡ "የልጅ ክፉ ዲቃላ የእኸል ክፉ ባቄላ የልብስ ክፉ ነጠላ የቤት ክፉ ሰቀላ"።
ሰቀላ፡ የበላይ። "የሰቀላ ዳኛ" እንዲሉ።
ሰቀላ፡ ዳስ ግድግዳውና ጣራው ቅጠል የለበሰ የተሸፈነ (ሰርግ ማኅበር ተዝካር ማንኛውም ድግስ በውስጡ የሚበላበት) ።
ሰቀላ ድንኳን፡ በሰቀላ አምሳል የተሰፋ ድንኳን ።
ሰቀል (ሎች)፡ ዝኒ ከማሁ። "በገዳም ውስጥ ከሚኖረው መነኵሴ የሚበዛው ዶማ ሰቀል ነው"።
ሰቀልት፡ በጋይንት ክፍል ያለ አገር (ትርጓሜው "ሰቃዮች" ማለት ነው) ።
ሰቀልኛ፡ ሞላልኛ/ወገርኛ (የዳስ ዐይነት ሕንጻ ወይም ሌላ) ።
ሰቂለ ኅሊና፡ ዐሳብን ሰማያዊ ማድረግ።
ሰቂለ አዕይንት፡ በጸሎት ጊዜ ሰማይን ትክ ብሎ ማየት።
ሰቂል፡ መስቀል።
ሰቃቀለ፡ መላልሶ ሰቀለ።
ሰቃይ (ዮች)፡ የሰቀለ/የሚሰቅል (አንጠልጣይ) ። "በቀለ ብለኸ ብቅልን" እይ ።
ሰቈረ (ሰቊር/ሰቈረ)፡ በሳ/ሸነ...ቈረ ።
ሰቈቃወ ኤርምያስ፡ ስለ ኢየሩሳሌም መጥፋት የኤርምያስ ሙሾ (የመጽሐፍ ስም) ።
ሰቈቃወ ድንግል፡ የግጥም ድርሰት ዐምስት ቤት ያለው (እመቤታችን በስደቷ ጊዜ የተናገረችውን ሙሾ ያለቀሰችውን ለቅሶ አምልቶ አስፍቶ በግእዝ ቋንቋ የሚናገር) ። መሠረቱ ነገረ ማርያም ነው።
ሰቋር፡ የተበሳ/የተሸነቈረ (የዋልድባ ተራራ የከዳነ ምሕረት ገዳም) ።
ሰበሰበ፡ ለቀመ፡ አጠራቀመ፡ አከበ፡ አከማቸ፡ አንድ ላይ አደረገ፡ ከተተ (ዘፀ. ፴፭፡ ፩፡ ፪ዜና. ፴፫፡ ፯) ። "ወሰበ"ን እይ (የዚህ ሥር ነው) ።
ሰበሰበ፡ ጌታ መለሰ፡ ዐጠፈ፡ ኰረተመ፡ አሳጠረ (አኅጸረ)፡ ሰቀጠጠ፡ ሸነቀረ፡ አሳረፈ (እጅን፣ እግርን፣ ልብስን) ። (ተረት)፡ "ሰርቆ ከማሰብ እጅን መሰብሰብ" (ማሳረፍ) ።
ሰበሰብ/ስብሳብ (ቦች)፡ በቤት ዙሪያና በራፍ በኩል ብቻ ከጣራ በታች ያለ ስፍራ (እንግዳ ወይም ዕቃ ተሰብስቦ የሚቀመጥበት)፡ በአኹኑ ዘመን "በረንዳ" ይባላል (ይኸውም የህንድ ቋንቋ ነው ይላሉ) ።
ሰበረ፡ (ሰቢር፡ ሰበረ) (ዮሐ. ፲፱፡ ፴፩-፴፫)፡ አነቀሽ፡ አነከተ፡ ቀለጠመ፡ ሸረፈ፡ አደቀቀ፡ ሠነጠቀ፡ ለበጠ። (ተረት)፡ "ዘመን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል"። "ጠገበ"ን እይ።
ሰበረ፡ ላጠ፡ ለወጠ፡ ገለበጠ፡ ሻረ፡ ፍርድን።
ሰበረ፡ ሰበሰበ።
ሰበረ፡ ነደለ፡ ጣሰ፡ አፈረሰ (ዦርን) ።
ሰበረ፡ ዐጨደ፡ ቈረጠ።
ሰበረ፡ ደፋ፡ አቀረቀረ (ዐንገትን - ዘኍ. ፲፭፡ ፴፩) ።
ሰበራ፡ ቈረጣ፡ ዐዳ። "ባቄላ ሰበራ" እንዲሉ።
ሰበር (ሮች)፡ የበላይ ዳኛ በታች የተፈረደውን ፍርድ የሚለውጥ/የሚገለብጥ። "ሰበር ዳኛ" እንዲሉ። (ደኅና ሰበር)፡ መጥፎ ሰው። "ቀነበረ" ብለህ "ቀንበር"ን ተመልከት።
ሰበር፡ የስንዴና የገብስ የጤፍ አገዳ ገለባ (ባኺዶ ጊዜ የከብት እግር የሰበረው) ።
ሰበቀ ፣ (ሰቢቅ፡ ሰበቀ)፡ ወዘወዘ፡ ነቀነቀ (ጦርን) ። ጐንደሮች ግን "ጦር ሰበቀ" ሲሉ አደራ ይላሉ።
ሰበቀ፡ በጠበጠ፡ አማሰለ፡ አምታታ (የጤፍ ዶቄትንና ሊጥን በመዳፍ መታ ብዙ ጊዜ) ።
ሰበቀ፡ ነከረ፡ ዐለለ።
ሰበቀ፡ ነገር ሠራ፡ አሳጣ፡ አጣላ። "ሰበከ"ን ተመልከት።
ሰበቀ፡ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እመላለሰ እስቴን (እርጐን) ።
ሰበቀ፡ ጣለ፡ አስተኛ፡ አጋደመ፡ አያያዘ።
ሰበቀለ፡ (በቀለ)፡ ተከወነ፡ ቀለጠፈ፡ ጣፈጠ (አንደበቱ)፡ ተባበረታ።
ሰበቀለ፡ ሰበረ።
ሰበቀለ፡ ዐጪር ኾነ (ነገሩ) ።
ሰበበ፡ (ሰቢብ፡ ሰበ)፡ ምክንያት አመጣ፡ ፈጠረ፡ አመካኘ።
ሰበበኛ (ኞች)፡ የሰበብ (ባለሰበብ) ሰው፡ ሰበብ ወዳድ፡ ምክንያተኛ - ለቍጣ፣ ለስካር፣ ለጥል፣ ለመውደቅ፣ ለመታመም ጥቂት የሚበቃው።
ሰበባም፡ ሰበብ ያለው።
ሰበብ፡ ሳቢያ፡ ምክንያት።
ሰበቦች፡ ምክንያቶች።
ሰበተ (ሰብዐ)፡ ሰባት አደረገ።
ሰበተ (ትግ)፡ ረገጠ፡ እሰረ።
ሰበተ፡ ሳገ።
ሰበተ፡ አብስሎ፡ ዐረሰ፡ ገለገለ።
ሰበከ (ሰቢክ፡ ሰበከ)፡ ነገረ፡ አወራ፡ አሰማ፡ አስተማረ።
ሰበከ (ሰብሐ፡ ተሰብሐ)፡ ወገግ አለ፡ ነጋ፡ በራ፡ ወጣ፡ ታየ። "ፀሓይ ሲሰብክ ትኼዳለኽ?"
ሰበከ (ትግ)፡ በንጉሥ አለ፡ እማጠነ።
ሰበከ፡ ሰበቀ፡ አሳበቀ፡ ዋሸ። "ሰበከን ሰበቀ ማለት ከ 'ና' 'ቀ' ተወራራሽ ስለ ኾኑ ነው፡ ውስጠ ምስጢሩም ስብኮን ያሳያል።"
ሰበከም፡ ባለሰበከት፡ ሻካራ። "ሰበከተ ሰበከት ባለው ጅራፍ ገረፈ።"
ሰበከተ፡ ጠጣ፡ ዥው አደረገ።
ሰበከት፡ ሰበቀ።
ሰበከት፡ ነገረች፡ አስተማረች (ግእዝ) ።
ሰበከት፡ የቍርበት፣ የንጀራ፣ የቅጠል፣ ያውሬ ሻካራ ዠርባ (ኢዮ. ፵፩፡ ፯) ። "ሰበከት" ማለት ግልጥነትን ያሳያል። ወዝን፣ እንቧይን እይ።
ሰበካ፡ የታቦት ወይም የአቡን ግዛት (አጥቢያ ሀገረ ስብከት) ።
ሰበዘ፡ ሻጠ፡ ሸጐጠ፡ ጨመረ፡ አገባ።
ሰበዝ (ዞች)፡ ስንደዶ፡ ግራምጣ፡ የስፌት ዙር ማብዣ፡ ማሳደጊያ።
ሰበድዓት፡ እባብ ጕበና (ግእዝ) ።
ሰበድዓት፡ የጣዖት ስም፡ ታኲ (ፈረስ ጭራው እባብ፣ ላዩ ባለመርዝ ቀስት የሆነ የደግ ሰው ምስል)፡ ይኸንንም ቅዱስ ገላውዴዎስ ገደለው (አጠፋው) ይላሉ።
ሰበገናም፡ ከሲታ ደረቅ ሰው - ሰበገኑ የሚታይ።
ሰበገን፡ የጐን ዐንጥት (በግራና በቀኝ ያለ) ።
ሰበጢራ፡ ያገዳ ቅርጫት (ሠበጠር) ።
ሰባ፡ (ሰብሐ)፡ ገለጠ፡ አስረዳ።
ሰባ፡ (ሰብዐ)፡ የቁጥር ስም፡ ፸ (70) ። ሰባት ዐሥር (7 x 10) ወይም ዐሥር ጊዜ ሰባት፡ በስሳና በሰማንያ መካከል ያለ የአሥር ቤት አኃዝ። ተራ ቁጥር ሲሆን "ሰባኛ", "ሰባኛው" ይላል። ሰባትን አስተውል።
ሰባ ሊቃናት፡ ለግብጽ ንጉሥ ቶለሚ (በጥሊሞስ) ብሉያትን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የተረጎሙ ሰባ ሊቃውንት፡ ከእነሱም አንዱ ሽማግሌው ስምዖን ነበረ (ሉቃስ ፪፡ ፳፭-፴፭) ።
ሰባ አንድ፡ (፸፩)፡ ስባና አንድ። "ሰባ አንደኛ" የማዕርግ ወይም ተራ ቁጥር።
ሰባ፡ ጮማ ሆነ፡ ሠባ።
ሰባሰበ፡ ለቃቀመ፡ አግበሰበሰ።
ሰባሰገል ፣ (ሰብአ፡ ሰገል)፡ የጥንቈላ፣ የውቀት፣ የፍልስፍና ሰዎች፡ ኮከብ ቈጣሪዎች።
ሰባሪ (ሮች)፡ የሰበረ፡ የሚሰብር (ሚክ. ፪፡ ፲፫) ።
ሰባሪ (ትግ. ሰበረ)፡ ጓያ (ወገብን፣ ቋንዣን የሚያሽመደምድ) ። "ጓያ ሰባሪ" እንዲሉ።
ሰባራ ዘንግ፡ ሐሰተኛ ነገር፡ ሙግት ሰባራ ሥንጥር፡ መናኛ የቤት ዕቃ።
ሰባራ፡ የተሰበረ ዕቃ ወይም ሌላ። "ዐንተ ሰባራ!" እንዲሉ።
ሰባራነት፡ ሰባራ መሆን።
ሰባቂ፡ የሰበቀ፡ የሚሰብቅ (ነገረኛ፡ አሳሳች) ።
ሰባበረ፡ አነካከተ፡ አደቃቀቀ (፩ነገ. ፲፱፡ ፲፩፡ ፪ዜና. ፴፬፡ ፯፡ ዳን. ፮፡ ፳፬) ።
ሰባተኚት፡ ሰባተኛዪቱ ክፍል።
ሰባተኛ ቀን፡ ቅዳሜ (ዘፍ. ፪፡ ፪-፫) ።
ሰባተኛ፡ የማዕርግ ቁጥር። ሲዘረዝር "ሰባተኛው" ይላል።
ሰባቱ ቀለማት፡ ጥቍር፣ ቀይ፣ ብጫ፣ አረንጓዴ፣ ሰማያዊ፣ ነድ፣ ወርቅ ቀለሞች።
ሰባቱ ዕለታት፡ ከእሑድ እስከ ቅዳሜ ያሉ ቀኖች።
ሰባቱ ከዋክብት፡ ከፀሓይ ብርሃን የሚነሡ ኮከቦች።
ሰባቱ ፊደላት፡ ከግእዝ እስከ ሳብዕ ያሉ ፊደሎች። (ከዋክብት፣ ዕለታት፣ ፊደላት የግእዝ፡ ኮከቦች፣ ቀኖች፣ ፊደላት የአማርኛ መኾናቸውን አስተውል) ።
ሰባት (ሰብዐት)፡ የቁጥር ስም (፯) ። በስድስትና በስምንት መካከል ያለ አኃዝ።
ሰባት ቀንዶ በረሓ እንስሳ፡ ቀንድ።
ሰባት በረት፡ የከብት አንዠት።
ሰባት አደረገ (ሰብዐ)፡ እስከ ሰባት ቈጠረ፡ በሰባት ከፈለ። ሰባት ከስም አስቀድሞ እየተነገረ ቅጽል ሲኾን፡
ሰባትያ፡ ሰባት መቶ ድር።
ሰባትያ፡ ከሰባት አንድ።
ሰባትዮ፡ ሰባትነት ያለው (ውስጠ) ።
ሰባትዮሽ፡ ከሰባት አንድ የኾነ ገመድ/ፍትል ወይም ሌላ ነገር።
ሰባቶ፡ ሰባቶች። (ች ስለ ተጐረደ ሰባቶ እየተባለ ይነገራል - ብዙ) ።
ሰባኪ (ኮች)፡ የሰበከ፡ የሚሰብክ (እገር ላገር እየዞረ ባደባባይ ቆሞ የሚነግር፣ የሚያስተምር)፡ ሐዋርያ፡ መምህር፡ ነጋሪ፡ አስተማሪ (መክ. ፩፡ ፲፪፡ ኤፌ. ፬፡ ፲፩) ።
ሰባኪ፡ ሰባቂ፡ አሳባቂ፡ ውሸተኛ፡ ነቢየ ሐሰት (፩ነገ. ፲፫፡ ፲፰) ። ባላገር ግን "ሰባኺ" ይላል።
ሰባዥ፡ የሰበዘ፡ የሚሰብዝ፡ ሸጓጭ፡ ጨማሪ።
ሰባጌ፡ የቀበሌ ስም (ሰብ) ።
ሰባጌ፡ የቀበሌ ስም፡ በመራቤቴ ክፍል ያለ ገጠር። "የምድር ሰው" ወይም "የሰው ምድር"፡ ፸ ምድር ማለት ነው።
ሰብ፡ (ሰብእ)፡ ሰው፡ ባለግዕዛን። "አገረ ሰብ" (የሰው ሀገር), "እጅ ሰብ" (የሰው እጅ), "ቤተ ሰብ" (የሰው ቤት) እንዲሉ።
ሰብለ ወንጌል፡ ያጢ ልብነ ድንግልና የጻድቁ ዮሐንስ ሚስቶች ስም፡ "ይተጌ ሰብለ ወንጌል" እንዲል (ታሪ. ነገ) ። ትርጓሜውም የወንጌል እሸት ማለት ነው።
ሰብሌ (ሰብልየ)፡ የኔ ሰብል፡ እሸቴ።
ሰብሌ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ነው።
ሰብል (ሰብለ)፡ እህል፡ ዛላ (ዘለላ)፡ እሸት (የማንኛውም) ።
ሰብሳቢ (ቦች)፡ የሰበሰበ፡ የሚሰበስብ (ለቃሚ፡ አጠራቃሚ) ። "ዘመድ ሰብሳቢ" እንዲሉ።
ሰብሳቢነት፡ ለቃሚነት፡ አካቢነት።
ሰብሳቤ፡ የሰው ስም (የዘመድ/የወገን ሰብሳቢ ማለት ነው) ።
ሰብሳብ፡ ግቢ ጋብቻ (ግእዝ) ።
ሰብስብ፡ የሪያ ጥርስ ዕባጭ መተኰሻ።
ሰብስብ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ (አንቀጽ) ።
ሰብራዳ፡ ከጭቅና ጋራ ያለ ኹለት የበሬ ጐድን።
ሰብር፡ የሽቱ ስም (ውድ ከሬት የተዘጋጀ)፡ በግእዝ "ዐልው" ይባላል (ዮሐ. ፲፱፡ ፴፱) ።
ሰብቀኛ (ኞች)፡ ሰብቃም፡ ሰባቂ፡ ሰብቅ ወዳድ፡ ባለሰብቅ፡ አሾክሹኪ፡ ዦሮ ጠቢ።
ሰብቀኛነት፡ ሰብቀኛ መሆን።
ሰብቃላ፡ ዝኒ ከማሁ ለስብቅል።
ሰብቅ፡ ክፉ ነገር፡ ሹክሹክታ፡ ሐሜት (ሰውን ከሰው የሚለይ) ። "ሸውክ"ን እይ።
ሰቦች፡ ሰዎች።
ሰተረ (ሰቲር/ሰተረ)፡ ዘረጋ/እሰጣ ለፀሓይ ሰጠ ።
ሰተተ (ሰቲት/ሰተ)፡ ለጥ ቀጥ አለ፡ ሰፊ ኾነ ተዘረጋ ።
ሰተታ፡ (ትግ)፡ ሰፌድ ።
ሰተት አለ፡ ቀጥታ ኾነ ሜዳው ።
ሰተት አለ፡ ዘው አለ ገባ (ንገሩልኝ ሳይል ከልካይ አዋኪ ሳይኖርበት) ።
ሰተት አለ፡ ዟ ዝርግት አለ (ሞተ) ።
ሰተቶ፡ ድርቄ ሰገባ ።
ሰተፈ (ሳትፎ/ሳተፈ)፡ ላተ ኳስን ጥንግን ሳይቀልብ ሳይመታ ቀረ፡ ቸኰለ ተጣደፈ (ጐዣም) ።
ሰቲት፡ ያገር ስም (በትግሬ ውስጥ በሐባብ አጠገብ ያለ ቈላ በረሓ ሜዳነት ያለው) ። በሺዋም በብዙ ስፍራ ይገኛል ።
ሰታሪ (ሮች)፡ የሰተረ/የሚሰትር (ዘርጊ አስጪ) ።
ሰታታ፡ ዝቅታ ከፍታ የሌለው እውላላ ሜዳ መለሎ ዕንጨት ።
ሰታቴ፡ ውስጡ እንደ ሰፌድ ዝርግ የኾነ ትልቅና ሰፊ ድስት በግ ፈጅ ። ዳግ...
ሰታቴ፡ የሰታታ ዐይነት ወገን ማለት ነው ።
ሰት፡ ቀጤማ (ግእዝ) ። መስቴ (ዎች)፡ ታናሽ ጥዋ እንደ ቅል ዐንገት ያላት የመጠጥ ማስቀመጫና መ፵ ። "ቻችንና ቡዪትን" ተመልከት ።
ሰቸ (ሰትየ)፡ ጠጣ/ዥው አደረገ ። "ሰቸ ካማራ ይልቅ በጕራጌ ይነገራል"።
ሰች (ሰታዪ)፡ የጠጣ/የሚጠጣ (ጠጪ - ደመ ሰች እንዲሉ) ።
ሰነመኪ፡ የታናሽ ዕንወት ስም (ቅጠሉ የሽቱ ቅመም ይኾናል፡ በጠጡትም ጊዜ ያስቀምጣል - ዘፀ. ፳፡ ፳፬፡ ሕዝ. ፳፯፡ ፲፱) ። ሰነኘ (ሰኒን/ሰነ)፡ ገጠመ/ደረደረ፡ ቤት መታ።
ሰነሰለ (ሰንሰለ)፡ አጠጋጋ/አያያዘ/አቀጣጠለ/አቈራኘ/አጠላለፈ ።
ሰነሰነ (ሰነነ)፡ ሰለሰለ/ሸነሸነ/ተነ...ተነ/ነጠለ/አበዛ ።
ሰነቀረ (ደነቀረ)፡ ሻጠ/ሰካ/ወጋ/ጋረጠ/አገባ ። "ሸነቀረን" እይ።
ሰነቀረ፡ አንድ ነገር ነገረ አሰማ።
ሰነቃ (ሰንቀወ)፡ ጠረበ/ዐነጠ/ላገ/አለዘበ (ሳንቃን) ።
ሰነቃ፡ መታ/ከረከረ/ገረፈ (ማሲንቆን) ።
ሰነበ (ትግ.)፡ ቀረቀረ/ወረወረ/ሸጐረ ።
ሰነበረ፡ ሰንበር ኾነ/ተጋደመ (በገላ/በቈዳ/በብራና ላይ) ።
ሰነበተ (ሰንበተ - በዓል ኾነ/ከበረ)፡ ባንድ ስፍራ ሰባት ቀን ተቀመጠ ቈየ ።
ሰነበተ፡ ሰነገ ።
ሰነበተ፡ ብዙ ዘመን ኖረ/ነበረ (አረጀ/አፈጀ/ዕድሜው በዛ/ፈደፈደ - መዝ. ፺፡ ፲፬ ሺ ፩፻፰ ሳምንት ከረመ) ። (ተረት)፡ "ከሰነበቱ ቍላን እንቅፋት ይመታዋል"።
ሰነበተ፡ አለ/ኾነ። "እንዴት ሰነበትክ" "ደኅና ሰንብት" እንዲሉ።
ሰነበገ (ሰነገ)፡ በኀይል ገረፈ/ሰበከተ ።
ሰነበጠ፡ ሠነጠረ—ሠነበጠ ።
ሰነባ፡ ሳንባ መሰለ ።
ሰነባበተ፡ ፩ ሰንበት ፪ ሰንበት ቈያየ ።
ሰነተረ፡ በጣ፡ ሠነተረ ።
ሰነከለ (ሰከለ)፡ እግርን መታ/ጐዳ፡ የበሬን ስንድድ ቈረጠ፡ የባሪያን ሥር በጠሰ።
ሰነኰረ፡ ዘነኰረ ።
ሰነዘረ (ሰዚር/ሰዘረ)፡ በስንዝር ለካ/መጠነ ።
ሰነዘረ፡ ሠነተረ/ሠነጠቀ/በጣ (የታረደ ከብትን) ።
ሰነዘረ፡ በትርን ወደ ሰው ቃጣ (ሳይንጠራራ በቅርብ ማለት ነው - "ነዘረን" ተመልከት) ።
ሰነደቀ፡ አጓዘ/ኣቋፈ።
ሰነደቀ፡ ከበበ ክብ አደረገ፡ ኳስ/ሎሚ ኣስመሰለ ከላይ።
ሰነደበ (ሰደበ)፡ መታ ።
ሰነደደ፡ ሰካ/ደረደረ ("ሰመግን ጨሌን" የስንደዶ ጌጥ አበጀ) ።
ሰነደደ፡ ሥራን አቀና/አቅንቶ ሠራ።
ሰነዳ) (ትግ. ሰንደወ - ወረወረ)፡ ተሰናዳ፡ ተዘጋጀ/ተደራጀ (፩ሳሙ. ፲፯፡ ፪) ።
ሰነድ (ዶች)፡ ስለ ገንዘብና ስለ ውል ስለ ጠመንዣ ስለ ማንኛውም ዕቃ የማን መኾኑን የሚመሰክር ጽፈት ሰንጠረዥ ።
ሰነገ (ሰነጐ)፡ በሳ ነደለ/ሸነቈረ አፍንጫን፡ አገባ/ሻጠ/ቀረቀረ ላባን/ሽቦን።
ሰነገ፡ አስጨነቀ/አስጠበበ።
ሰነገ፡ ጠመጠመ/አጥብቆ አሰረ።
ሰነገለ (ዐረ. ሰሕገለ)፡ ፈገፈገ/ወለወለ/ጠረገ/አጠራ/አብለጨለጨ/ሳለ/አሰላ (ጦርን/ሰይፍን - ኤር. ፵፮፡ ፬) ።
ሰነገለ፡ ሰነደደ ።
ሰነገጩ፡ ነቀነቀ/ዘከዘከ/አደናቀፈ።
ሰነጋ (ትግ. ሰንገወ)፡ አኰላሸ/ኣወጣ/ጐነደለ (የፈረስ/የበቅሎ/የዶሮ ቍላን)፡ ወቀጠ/ቀጠቀጠ/አስሮ ገደለ (የወይፈንን)፡ ሠነጠቀ/ኣፈሰሰ (የበርበሬ ፍሬን)፡ የሰው ሲኾን ዐሸ/ሰለበ ያሰኛል ።
ሰነጋ፡ ሰነገ ።
ሰነጠ (ሰነጸ)፡ አሳመረ/አስጌጠ/መልክ ሰጠ/ነቀሰ/ፋቀ/አለዘበ።
ሰነጠ፡ ሰነከለ ።
ሰነጠረ፡ ሠነበጠ፡ ሠነጠረ።
ሰነጠቀ፡ ከፈለ ሠነጠቀ።
ሰነፈ፡ ሰነቃ ።
ሰነፈ፡ ሥራን ተወ ወይም ጠላ/ከተ/ደከመ (ሐሞቱ ዳውላ አከለ፡ ቦዘነ) ።
ሰነፈ፡ ሥራን ተወ ወይም ጠላ/ከተ/ደከመ (ሐሞቱ ዳውላ አከለ፡ ቦዘነ) ።
ሰነፈጠ፡ ሰረነቀ/ሰረሰረ/ፈጀ/ለበለበ/አቃጠለ (አፍንጫን) ።
ሰነፍ (ፎች)፡ የሰነፈ/የሚሰንፍ (ሥራ ል...ሰው ተቀምጦ የሚውል) ። "ሰነፍ ባል ያበዛል" እንዲሉ። "ሰነፍ ለባለአእምሮ ይገዛል" (ምሳ. ፲፩፡ ፳፱፡ ፳፮፡ ፯, ፲፱) ።
ሰነፍ ምርት፡ ላይዳ ያልተባለ።
ሰነፍ ሴት፡ ረኸጥ ።
ሰነፍ ቈሎ፡ ሲቈሉት በቶሎ የሚፈካ ለጥርስ የሚገራ ገብስ ።
ሰነፍ ዕርቅ፡ እንዳይፈርስ ማሰሪያ ውል ማገጃ ያልተበጀለት ዕርቅ (የጊዜ) ።
ሰናሰነ፡ ተናተነ/ነጣጠለ። (ግጥም)፡ "አቶ ይነሡልኸ በሰላ መጥረቢያ በዚያች በጥልቆ ቢሰናስኑት አነስ አነስ ያለው በወጣው ስምንት። ያንተን ቂጥ የሚያኸል በነበረኝ ምድር እጅጋየኹ ትሙት፡ አለጠጅ አላድር" (ቍንጪ) ትግሬ ግን "ሰንሰነ" ብሎ ከሳ ይላል፡ ከሰለሰለ ጋራ አንድ ነው።
ሰናድር (ሮች)፡ የነፍጥ ስም (ባጤ ዮሐንስ ጊዜ የነበረ ጠመንዣ) ። በጀርመንኛ "ሽናይደር" ይባላል ።
ሰናድር ያዥ፡ ሰናድር የሚይዝ/የሚሸከም ጭፍራ ወታደር ።
ሰናጊ፡ የሰነገ/የሚሰንግ (በሺ ቀርቃሪ) ።
ሰናጋ፡ በልጥ የታሰረ ሰባራ አሞሌ።
ሰናጭ፡ የሰነጠ/የሚሰንጥ (አሳማሪ) ።
ሰናፊ፡ የሚሰንፍ (ታካች) ።
ሰናፊል (ሎች)፡ የዱሮ ዘመን ሱሪ ቦላሌ ተነፋነፍ (ዘሌ. ፯፡ ፲፡ ሕዝ. ፵፬፡ ፲፰) ።
ሰናፍጭ (ስናፔ)፡ የቅመም ስም (አፍንጫን የሚለበልብ ጕረሮን የሚያቃጥል ቅመም) ። (ተረት)፡ "የፌጦ መስሎሽ ሰናፍጭ ትቀምሽ"። ስንፈጣ/ስርነቃ/ስርሰራ/ልብለባ ።
ሰኔ፡ የወር ስም—ሠኔ ።
ሰን (መቅለድ)፡ ኵስኵስት ማንቈርቈሪያ (ከንሓስ ከመዳብ የተሠራ - ጸናኒ ማለት ነው) ።
ሰን...፡ ጠባብ የገደል ውስጥ መንገድ (እንደ ንቃቃት ያለ ቀባ እጅ የማያስገባ) ።
ሰንሰለት (ቶች)፡ የተቀጣጠለ ብዙ የብረት ቀለበት ሞላላ። ጫፍና ፵ፉ ፍንጅ አለበት፡ ይኸውም ያመፀኛ ማሰሪያ ማቈራኛ ነው (ማር. ፭፡ ፬፡ ግብ. ሐዋ. ፲፪፡ ፯) ።
ሰንሰል (ሎች)፡ ብዙ ኹኖ ተያይዞ የሚበቅል ዕንጨት ስምዛ ።
ሰንቃሪ፡ የሰነቀረ/የሚሰንቅር (ሻጭ ጋራጭ) ።
ሰንቃራ/ስንቅር፡ የተሰነቀረ/የተሻጠ/የተጋረጠ (ሥንባጭ) ።
ሰንበሌጥ (ጦች)፡ ለቤት ክዳን የሚኾን ሣር ።
ሰንበራም፡ ሰንበር ያለበት (ባለሰንበር ከብት/ሰው/ልብስ) ።
ሰንበር፡ በትር ያረፈበት ያካላት መሥ...መር ።
ሰንበር፡ የሥጋ ስም (ጠንካራ ሥጋ የጨጓራ መጋጠሚያ - "ሰንበርና ምላስ" እንዲሉ) ።
ሰንበር፡ የዋንጫ/የጠንፍ/የሕንጻ/የጋን መሥመር (ትጥቅ መሳይ ጊጥ - ፬ነገ. ፯፡ ፳፰) ። ሲበዛ "ሰንበሮች" ይላል (፩ነገ. ፯፡ ፳፱) ።
ሰንበተ አይሁድ፡ ያይሁድ ሰንበት (ቅዳሜ) ።
ሰንበተ ክርስቲያን፡ የክርስቲያን ሰንበት (እሑድ) ።
ሰንበቴ፡ የሰንበት ሰንበታዊ (በየሳምንቱ እሑድ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ የሚበላ የድኾች ምሳ) ።
ሰንበት፡ ፩ኛ ቀን አሑድ (ይኸውም ሰንበት መባሉ ሰኞን አንድ ብሎ ነው) ። በወር ውስጥ አራት ቀን ሥራ አይሠራበትም፡ ቅዳሜ ወይም እሑድ የወር መባቻ ሲኾን ግን ዐምስት ጊዜ ይከብራል። የሰንበትም ምስጢር ዕረፍትና በዓል ነው ።
ሰንበት፡ ፯ኛ ቀን ቅዳሜ (ትርጓሜው ሰባት) ።
ሰንበት አምኜ፡ የድጓ ስም (በሰንበትና በአመት በዓል የሚባል ዜማ የተጻፈበት ቅድ. ድጓ) ።
ሰንበቶች (ሰናብት)፡ በየወሩ ፬ አንዳንዴም ፩ ጊዜ የሚከብሩ የቅዳሜ ቀኖች (ዘፀ. ፴፩፡ ፲፫) ።
ሰንቡላ መሬት፡ ጠንቋይ ለአንዳንድ ሰው "ኮከብኸ ሰንቡላ መሬት ነው" ይለዋል።
ሰንቡላ፡ የኮከብ ስም (የነሐሴ ኮከብ - ሽቷም ባለሽቱ ማለት ነው) ። ሥዕሉ ሽቶ ረብራቢ ነስናሽ ይመስላል ።
ሰንባች፡ የሚሰነብት/የሚቈይ ።
ሰንተል፡ ,ሰፋ ።
ሰንተል ነጋሪት፡ ከማዕድን የተሠራ ሳንቲም፡ የብር ፪ኛ ።
ሰንተል፡ የብረት ሥራ።
ሰንና ብርት፡ ሰን የላይኛው ብርት የታችኛው (የኹለቱም ስም ዳታን ይባላል) ።
ሰንከልካላ/ስንክልክል፡ የተሰነካከለ (ወጣ ገባ ደንጐላጕል ሥርጓጕጥ) ።
ሰንካላ/ስንክል፡ የተሰነከለ (እግሩ የተመታ እንደ ልቡ መኼድ መራመድ የማይች) ።
ሰንካይ፡ የሰነከለ/የሚሰነከል (መቺ) ።
ሰንኬት፡ ታናሽ የእጅ ጣት (ዐምስተኛዪቱ) ።
ሰንኬቶ፡ የታናሽ ጣት ቀለበት (በግእዝ ገመስ ትባላለች) ። "ዲዋኒን" እይ ።
ሰንኰፋም፡ ባለሰንኰፍ ቍስል።
ሰንኰፍ፡ የዕባጭ/የብጕንጅ ጥርስ።
ሰንኳራ፡ ሰንኰርቱ ነገረ ብላሽ ዘንኳራ ።
ሰንኳራ፡ ሰንኰርቱ ነገረ ብላሽ ዘንኳራ ።
ሰንዛሪ፡ የሰነዘረ/የሚሰነዝር (ለኪ ሠንታሪ) ።
ሰንደል፡ ሰነዘረ ።
ሰንደል፡ ሣጥን (ከሰንደል የተሠራ ሣጥን ባለመዐዛ) ።
ሰንደል፡ ታቹ መርገጫው የሰንደል ሉሕ የኾነ መጫሚያ።
ሰንደል፡ የህንድ አገር ዛፍ ስም (ክልካዩ - ፍርፋሪው - በውድ የሚሼጥ የጪስ ዕንጨት) ።
ሰንደል፡ የሽቱ ስም (ቅጥነቱ እንደ ሰንበሌጥ ያለ - ሰንደልን የተቀባ ዕፅ ሲያጨሱት የሚሸት) ። "ዑድን" አስተውል ።
ሰንደቅ (ቆች)፡ ከቀንድ/ከዝኆን ጥርስ/ከብር/ከዞጲ/ከልምጭ/ከቀረጥ የተቀረጸ (በላይ ክብ እንክብል በታች ጕረሮ ያለው መቋሚያ - ፪ዜና. ፲፯፡ ፲፫) ።
ሰንደቅ፡ ...ጓዝ ።
ሰንደቅ ዐላማ (መዝ. ፳፡ ፭)፡ በሰንደቅ ላይ የተሰቀለ/የተንጠለጠለ ባለአረንጓዴና ብጫ ቀይ ቀለም የመንግሥት ምልክት ባንዲራ፡ በመካከሉ ጽሑፍና ያንበሳ ሥዕል ከዘውድ ጋራ ይታይበታል፡ አንበሳውም ሰንደቅ ዐላማ ይዟል ።
ሰንደቅ ዘንጉ/መቋሚያው፡ ከነ እንክብሉ፡ ዐላማ ሐሩ ። ርግጠኛው አጻጻፍ ግን (ዐላማ ሰንደቅ) የሰንደቅ ዐላማ ነው።
ሰንደቅ፡ የጭራ/የመንሳንስ ዕን...ወት ።
ሰንዳቂ፡ የሰነደቀ/የሚሰነድቅ (አጓዥ) ።
ሰንዳቢ፡ የሰነደበ/የሚሰነድብ (መቺ) ።
ሰንዳዳ፡ ቀጥ ያለ አፍንጫ።
ሰንዳጅ፡ የሰነደደ/የሚሰነድድ (ሰኪ ደርዳሪ) ።
ሰንዳፋ፡ በአዲስ አበባ ምሥራቅ በቅርብ ያለ ቀበሌ (ስሙን ከሣሩ ወስዳል) ። ሰንዳፋ በግእዝ መጽሐፍም ይገኛል (ታም. ማር) ። ሰነደቀ (ሰደቀ)፡ አሰረ ነዶን ። "ጠየትን" እይ።
ሰንዳፋ፡ የሣር ስም (እንደ ሰርዶ አንጓ ያለው የሜዳ ሣር ወፍራም፡ በረግረግ ወይም በውሃ ውስጥና ዳር ይበቅላል) ።
ሰንድሮስ፡ ነጭ ዕጣን (ግእዝ) ።
ሰንገጮ፡ የተሰነገጨ (ደንቃፋ ዘክዛካ) ።
ሰንጊ፡ የሰነጋ/የሚስነጋ (አኰላሺ/ጐንዳይ/ወቃጭ/ቀጥቃጭ) ።
ሰንጋ (ጎች)፡ የተስነጋ/የተኰላሸ/የተጐነደለ/የተቀጠቀጠ (ኵልሽ ጕንድል ቅጥ ቅጥ) ።
ሰንጋ ምት፡ ና ቼ ቼ ቼ የሚል የሰንጋ ፈረስ ዘፈን አዝማች።
ሰንጋ ሰንጋ፡ የሰንጋ (ሰንጋ ጮሌ ፈረስ) ። ደጊሙ ቃልም ይኾናል።
ሰንጋ ቦካ፡ በቡልጋ አፋፍ ያለ ቀበሌ ።
ሰንጋ ቦካ፡ ወፈረ/ሠባ/ደለበ (መኼድ አቃተው) ።
ሰንጋ፡ አዝማሪ "ሰንጋ ሰንጋ" እያለ ሐርበኛን የሚያመሰግንበት የማሲንቆ ምት ።
ሰንጋ፡ የተቀለበ በሬ (ድልብ ገች ፍሪዳ) ።
ሰንጋ፡ የኦሮ ባላባት ግዛት ("ዳማ ከለለኝ አባ ሰንጋ" እንዲሉ) ። "አባን ዳማን" ተመልከት።
ሰንጋ ፈረስ፡ ታፍኖ በቤት የሚውል ኦሮቢ ፈረስ (ድንጕላ ያይዶለ) ።
ሰንጋይ (ዮች)፡ የስነገለ/የሚሰነግል (ሳይ - ሕዝ. ፳፩፡ ፲፩) ።
ሰንጌ፡ የቍልምጫ ቃል ("የኔ ሰንጋ" እንደ ማለት) ።
ሰንጎ መገን፡ ሰንጎ ፈረስ መገን ጋሻ ነው። "ሰንጎ መገን ተው ሰንጎ መገን" ከፈረሰኞች የምናውቃቸው በሻኸ አቦዬ ኀይሌ አንዳርጋቸው እንዳለ አዝማሪ።
ሰንጎ፡ አስጨንቆ/አስጠብቦ።
ሰንጎ/ሰንግዮ፡ ቃለ አጋኖ ("ሰንጋ ሆይ" ማለት ነው) ።
ሰንጠረዥ (ዦች)፡ የመጫወቻ ስም (ስድስት ዐይነት ምስል ያለው መጫወቻ ምስሉም ንጉሥ/ንግሥት/ፊታውራሪ/ፈረስ/ግንብ/አሽከር ይባላል) ። ነጭና ጥቍር መደብ አለው፡ ጨዋታው የጦርነት ምሳሌ ነው ። ያወጡትም ፋርሶች ናቸው ይላሉ ።
ሰንጠረዥ፡ የቍጥር መደብ (አግድምና ቍልቍል የተሠመረ መሥመር በውስጡ አኃዝ ያለበት - ክብ ሲኾን ዐውድ ይባላል) ። ሳንኳ፡ ሰኰና/ቍርጭምጭሚት/ስን...ድድ ።
ሰንጢ (ዎች)፡ የታናሽ ቢላዋና የምላጭ ዐይነት ታጣፊ መሣሪያ ባለኹለት አፍ (ትልቁ ሥጋ መብሊያ ራስ መላ...) ።
ሰንጣ፡ አሳምሮ እንደ ልብ (፩ሳሙ. ፲፬፡ ፴) ።
ሰንጣ፡ ወለል ያለ ሜዳ የሚያምር።
ሰንፋጣ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሰንፋጭ፡ የሰነፈጠ/የሚሰነፍጥ (ሰናፍጭ/በርበሬ/ዝንጅብል የመሰለው ኹሉ) ።
ሰኘ (ሰነየ)፡ ኾለተ (ኹለት አደረገ) ።
ሰኘ)፡ አሰኘ፡ አሻ ። (ሠኘ)፡ አሠኘ ።
ሰኞ (ሰኑይ)፡ ኹለተኛ ቀን (የእሑድ ማግስት) ። "ማግሰኞን" እይ።
ሰኞን ኾነ፡ አደጋ ደረሰበት ሞተ ። ሲና፡ የተራራ ስም (ሙሴ ፲ቱን ቃላትን ከፈጣሪ የተቀበለበት ተራራ) ።
ሰአልናከ፡ የተረፈ መሥዋዕት፡ የኦኰቴት ምክትል፡ "ጠዲቅ ዳቦ" ትርጓሜው "ለንኸ" ማለት ነው። "ሰአልናከ" መባልን ከጸሎቱ ወስዷል፡ ባላገር ግን "ሳሊነክ" ይለዋል።
ሰዐወ)፡ የጊዜ ስም ።
ሰዓ፡ ሰዓት ።
ሰዓተ ሌሊት፡ ከማታ እስከ ጧት ያለ ጊዜ (፲፪ ሰዓት) ። ካህናት በቤተ ክርስቲያን እያደሩ በሰባቱ ጊዜያት የሚጸልዩት የፍታት ጸሎት፡ "ሰዓተ ሌሊት" ያሠኘው የሚዠመረው በመንፈቀ ሌሊት ስለ ኾነ ነው። "መላን" አስተውል።
ሰዓተ መዓልት፡ ከጧት እስከ ማታ ያለ ጊዜ (፲፪ ሰዓት) ። "ተሲያትን ሳትንና ሳታትን" ተመልከት ።
ሰዓቱን ሞላ)፡ ዘወረ፡ ጠመዘዘ፡ እንዲንቀሳቀስ/እንዲዞር አስተካከለ (ገቢር) ።
ሰዓት ሲበዛ ቀን፡ ቀን ሲበዛ ወር፡ ወር ሲበዛ ዓመት/ዘመን ይኾናል። "ደግ ሰዓት ክፉ ሰዓት" እንዲሉ።
ሰዓት አደረሰ፡ በ፯ቱ ጊዜያት ጸለየ፡ አቍጣሮ ያዘ አደረገ።
ሰዓት፡ የሰዓት መሣሪያ (ክብ መኪና ባለ፳፬ ክፍል - በላዩ ያለው መርፌ የላይኛው በቀን ፳፬ የታችኛው ፪ ጊዜ ይዞራል፡ የደቂቃው ቍጥር አንድ ሺ አራት መቶ አርባ፡ የካልኢቱ - ሰጏንዱ - ሰማኒያ ስድስት ሺ ካራት መቶ ነው) ።
ሰዓቶች (ሰዓታት)፡ ጊዜዎች/ዘመኖች፡ የሰዓት መሣሪያዎች።
ሰከለ፡ ዐንገትንና የኋላ እግርን ወይም የፊት እግርንና የኋላ እግርን አሰረ/ቈረኘ። ምስጢሩም የተክል ፍሬ ዐጽቅን መዝኖ ከግንድ፡ ቅርንጫፍን ከዐጽቅ እንዲያገናኝ ማለት ነው።
ሰከላ፡ በጐዣም አውራጃ ያለ አገር (አባይ የሚፈልቅበት) ።
ሰከመ፡ ተሸከመ (ግእዝ) ። "ወስከምት" ማለት ከዚህ የወጣ ነው።
ሰከም ሰከም አለ፡ ሲኼድ እንደ ተሸካሚ ፈጠን ፈጠን አለ።
ሰከሰከ (ሰገሰገ)፡ ሰረረ።
ሰከረ (ሰኪር/ሰክረ)፡ ጠነበዘ፡ አበደ፡ ራሱ ዞረ፡ ቃዠ፡ ጮኸ፡ ለፈለፈ፡ ዘለለ፡ ተንገደገደ፡ ወደቀ፡ አንዱ ኹለት ኾነበት (ከመጠጥ ብዛት የተነሣ) ።
ሰከረ)፡ ዘከረ (መሰከረን አስተውል - የዚህ መስም ግስ ነው) ።
ሰከቴ፡ የተደቀነ፡ ሠከተ።
ሰከነ (ሰኪን/ሰከነ)፡ ወደ ታች ወረደ፡ ዘቀጠ፡ ረጋ (የቡናው አተላ ሰከነ) ።
ሰከነ፡ ሱካር።
ሰከነ፡ ተዋረደ፡ ዐጣ፡ ነጣ፡ ደኸየ።
ሰከከ፡ ቀናሰገገ።
ሰኪ (ሰካዒ)፡ የሰካ/የሚሰካ (ሻጭ) ።
ሰካ (ሰክዐ)፡ ሻጠ፡ ሳገ፡ አገባ፡ ወጋ፡ በተራ አቆመ፡ ደረደረ (ጦርን፡ ዕንጨትን፡ ዶቃን፡ ዐልቦን፡ ወሌን፡ ሰመግን በክር/በሢር/በሽቦ ላይ) ።
ሰካላ፡ ገመድ/ጠፍር።
ሰካሪ/ሰካር፡ የሰከረ/የሚሰክር/የጠነበዘ (ምሳ. ፳፮፡ ፱፡ ፩ቆሮ. ፮፡ ፲፩).
ሰካሪዎች/ሰካሮች፡ የሰከሩ/የሚሰክሩ (ጠንባዞች - ኢሳ. ፳፰፡ ፩, ፫).
ሰካራም፡ ሰካር ያለበት/የሚያድርበት መሸታ ቤት።
ሰካይ (ዮች)፡ የሰከለ/የሚሰክል (አሳሪ) ።
ሰክ አለ፡ ተደቀነ፡ ሠከተ።
ሰኰና (ግእዝ)፡ የሰው ጫማ ውስጥ እግር፡ ኰቴ (የከብት ጥፍር)፡ መርገ፵/መኼጃ። "ገለገለ" ብለኸ "ግልገልን" እይ።
ሰኳ/ሰኵዐ)፡ "መሰኳ"ን አስተውል (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰወለለ)፡ ተንሰዋለለ፡ ተንቀዋለለ፡ ተንከዋረረ፡ ተንሰለጀጀ።
ሰወለል/ሰውላላ፡ ቀወለል/ቀውላላ - ሰልጃጃ።
ሰወረ (ሰውሮ/ሰወረ)፡ ሸፈነ፡ ጋረደ፡ ከለለ፡ ዐወረ (ዐይንን ነሣ)፡ አሳበደ (ልብን) ። ወባ ሸሸጉ፡ ደበቀ፡ ገለበጠ (የሚታየውን እንዳይታይ በስተውስጥ አደረገ) ። "ሱረትን" እይ (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰወረ፡ አረቀቀ።
ሰዋ፡ ዐረደ፡ ሠዋ።
ሰዋም፡ ሰው ያለበት/የበዛበት (ባለ ሰው ስፍራ) ።
ሰዋስው (ሶሰወ)፡ የመሰላል ስም።
ሰዋስው፡ ነጠላ ግስ ከነርባው፡ ሀርና ነባር ወይም ስምና ግብር።
ሰዋስው፡ የነገር/የቃል/የቋንቋ እገባብ ሥርዐት/ደንብ። የግእዝን ምስጢር ካለማወቅ ወደ ማወቅ መወጣ፵ ማለት ነው።
ሰዋስው ጨዋታ፡ የግእዝ ንግግር።
ሰዋስውኛ፡ የሰዋስው ጭውውት/ዘይቤ (ነገረ ደብተራ) ። "በተነ" ብለኽ "ብትንን" እይ፡ "ጥሬን" ተመልከት።
ሰዋሪ፡ የሰወረ/የሚሰውር (ሸፋኝ ከላይ ደባቂ) ።
ሰዋራ፡ ደባቃ ስፍራ።
ሰዋወረ፡ ደባበተ።
ሰዋውሮ፡ ደባብቆ።
ሰው (ሶሰወ)፡ ኣዳም (ያዳም ልጅ)፡ የፈጣሪ ምሳሌ (ነባቢ፡ ለባዊ፡ ሕያው)፡ በሥጋው ከእንስሳት በነፍሱ ከመላእክት አንድነት ያለው ፍጥረት (ባለግዕዛን) ። "ምናልባት ሰው ለመኾን ቢያበቃኝ ውለታኽን እከፍላለኹ።" ሰው ማለት በሔዋን ኣንጻር ለሴትም ይነገራል። "አንቺ ሰው!" እንዲል ባላገር። (ተረት)፡ "ለሰው ሞት ኣነሰው።"
ሰው፡ ሌላ/ባዕድ። "ይህ ገንዘብ የሰው ነው፡ የኔ አይዶለም።" "ዳረን"ና "ቃጣን" እይ።
ሰው መሳይ፡ ሰውን የሚመስል (ዝንጀሮ፡ ጦጣ፡ ጕሬዛ፡ ዓሣ - ስሬን) ።
ሰው መሳይ በሸንጎ፡ ወስላታ/ምንቴ ነውረኛ።
ሰው ሠራሽ፡ ግብር እምግብር (ሰው የሠራው ሥራ የእግዚአብሔር አይዶለም) ።
ሰው ሰውኛውን ኖረ፡ እንደ ሰው ከሰው ጋራ ፍጹም ሰው ኹኖ (እየበላ፡ እየጠጣ ማለት ነው) ።
ሰው በላ፡ ሰውን የሚበላ ጭራቅ/አውሬ።
ሰው በሩቁ፡ የውሻ ስም።
ሰው ኾነ (ተሰብአ)፡ ነፍስና ሥጋ ያለው ኾነ፡ ተዋሐደ፡ የሰውን ባሕርይ ነሣ።
ሰው የመታ)፡ ለዳኛ የሚከፍለው/የምትከፍለው ገንዘብ ። ዱሮ አንድ አሞሌ ነበር፡ ከ1934 ዓ. ም. ወዲህ ግን ዐምስት ብር ነው ።
ሰው፡ ጌታ፡ ጨዋ፡ ባላባት፡ ክቡር፡ ባለማዕርግ (መዝ. ፵፱፡ ፳). "ጊዜ ነው እንጂ ቁም ነገራም የሰው ልጅነት አያኰራም" - (አዝማሪ) ።
ሰው ጤፉ፡ ሰውን የሚንቅ/የሚያኰስስ (ከጤፍ የሚቈጥር) ።
ሰውማ፡ ሰው መሳይ።
ሰውር (ተውር/ሶር)፡ በሬ።
ሰውር መሬት፡ ጠንቋይ (ለአንዳንድ አስጠንቋይ "ኮከብኽ ሰውር መሬት ነው" ይለዋል።)
ሰውር፡ የኮከብ ስም (በሬ የሚመስል - የማዚያ ኮከብ) ።
ሰውነተ ቢስ፡ የነገሩትን የሚረሳ ዝንጉ።
ሰውነቱን፡ ለወጠ)፡ ዐመሉን፡ አከፋ፡ ፊቱን፡ አጠቈረ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፬ ።ኤር. ፶፪፡ ፴፫") ።
ሰውነት፡ ሰው መኾን፡ የነፍስ ባሕርይ፡ አካል/ገላ (ሉቃ. ፲፪፡ ፲፱). "ዛሬ በመንገድ ውዬ ሰውነቴ ልትት ብሏል።" በዘመናችን ግን የውሻው/የፈረሱ/የመኪናው ሰውነት እየተባለ በስሕተት ይጻፋል።
ሰውኛ፡ የሰው ጠባይ/ባሕርይ።
ሰውየው፡ በሰውዬ አንጻር የርሱ ሰው ማለት ነው።
ሰውዬ፡ የኔ ሰው።
ሰውዮ (ኦ ብእሲ)፡ ሰው ሆይ! ("ዮ" በጥሪ ጊዜ ማግነንንና ማክበርን ያሳያል) ።
ሰዉ፡ ዋቢ፡ ኀላፊ። "ሰጪኽን አምጣ" እንዲሉ።
ሰየ፡ ጐመዠ፤፡ ሠየ።
ሰየመ (ሰመየ)፡ ስም ለሌለው ስም አወጣ (ስለ ልጅ የተወለደና ክርስትና የተነሣ ለት) ። "ሠየመን" እይ።
ሰየፈ (ሰይፎ/ሰየፈ)፡ በሰይፍ መታ፡ ቀላ፡ ቀነጠሰ፡ ቈረጠ፡ ጐመደ፡ ጐረደ፡ ከለለ፡ ገደለ።
ሰያሚ፡ የሰየመ/የሚሰይም (የሰየመች/የምትሰይም)፡ ስም አውጪ (አባትና እናት፡ ቄስ፡ ሴት ዐማት) ።
ሰያሚነት፡ ሰያሚ መሆን።
ሰያፊ፡ የሰየፈ/የሚሰይፍ (ቈራጭ ባለ ወግ) ።
ሰያፍ፡ ዝኒ ከማሁ።
ሰይጣናም (ሞች)፡ ሰይጣን ያለበት/ያደረበት (ባለሰይጣን፡ ክፉ ሰው፡ እባብ) ።
ሰይጣን/ሴጣን፡ ዲያብሎስ (ክፉ መንፈስ፡ ጋኔን፡ የእግዚአብሔርና የአዳም መዠመሪያና መፍረሻ ጠላት/ባለጋራ) ። ሲበዛ "ሰይጣኖች/ሴጣኖች" ይላል። "ጋንጩርን" አስተውል።
ሰይጣንነት፡ ሰይጣን መሆን (ክፉነት/ስይጣኔ/ዝኒ ከማሁ/ተንኰለኛነት) ።
ሰይፈ ሥላሴ፡ የመጽሐፍ ስም (ምስጢር ያላገመረ ካህን በግእዝ ቋንቋ የደረሰው ነው) ። ይኸንንም የመሰለ ከወንጌል የማይ ሰማማ ፈጠራ ድርሰት አርድእት ነው። (ተረት)፡ "የልጅ ጥፉ በስም ይደግፉ።"
ሰይፈ ነበልባል፡ ከነበልባል የተዘጋጀ የመልአክ ሰይፍ።
ሰይፈ አርዓድ (አርዓዴ ሰይፍ)፡ በ፲፱፻ ዓ.ም. የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ (በሰይፍ አንቀጥቃጭ ማለት ነው) ።
ሰይፈ ዣግሬ (ዣግሬ ሰይፍ)፡ የንጉሥ/የመስፍን/የመኰንን ሰይፍ ያዥ/ተሸካሚ (፩ሳሙ. ፴፩፡ ፬) ። ዳግመኛም "ዣግሬ" (ዘእግር ዘአጋር) ማለት ነው። ሦስተኛም አግሬን ያሳያል። አራተኛም ሰይፍንና ዘገርንም ያስተርጕማል። "ጋሻን"ና "ዣግሬን" እይ።
ሰይፈ ዣግሬዎች፡ ብዙዎች (ሰይፍ ተሸካሞች/የሰይፈ ዣግሬ ጭፍሮች) ።
ሰይፈኛ (ኞች)፡ ሰይፍ ታጣቂ (ሰይፍ መዛዥ) ።
ሰይፉ/ሴፉ፡ የሰው ስም።
ሰይፋም፡ ባለሰይፍ ማለት ነው።
ሰይፋይ፡ በዘመነ ብለይ የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ።
ሰይፍ፡ ፬ ጣት በሽቻ መቀስ የሚረዝም።
ሰይፍ/ሴፍ፡ የጦር መሣሪያ ስም (ይኸውም በ፪ ወገን ስለት ያለው፡ በወገብ የሚታሰር፡ በትከሻ የሚንጠለጠል ነው) ። "ጐራዴን"ና "ሾተልን" "ሐኔን" "ዱቢትን" አስተውል። (የራስጌ ሰይፍ)፡ ዐልጋ ላይ በከዳ ውስጥ የሚቀመጥ። በግእዝ "መተርእስት" ይባላል።
ሰደሰ፡ ስድስት አደረገ (ግእዝ) ።
ሰደረ (ትግ. ሰነዘረ)፡ ወለደ፡ ደረደረ፡ ረደፈ፡ መደደ፡ ኰሰኰለ፡ በተራ አስቀመጠ፡ አቆመ።
ሰደረ, ደረደረ፡ ተራ ሰጠ - ሰደረ, ደረደረ፡ ተራ አመጣ። ረደፈ (ዐረ), ደረበ - ረደፈ (ዐረብኛ), ደረደረ።
ሰደቀ፡ አብዝቶ ቀባ፡ ደለሰ፡ እፊማለቀ (ዐማርኛ) ። "ሰነደቀ"ን እይ (የዚህ ጣልቃ ነው) ።
ሰደቀ፡ ገበታ ዘረጋ (ግእዝ) ።
ሰደቃ እግሪ ረዥም፡ ስፌት (የንጀራ ማቅረቢያና መብሊያ) ። በአረብኛ ግን "ጸደቃ" ለድኆች የሚያበሉት፡ "ጠዲቅ" ስለ ጽድቅ የሚሰጡት ገንዘብ ወይም ሌላ ምጽዋት ተብሎ ይተረጐማል።
ሰደቃ፡ ከሳንቃ የተበጀ ገበታ (ዘፀ. ፳፭፡ ፳፫፡ ዮሐ. ፪፡ ፲፭).
ሰደበ፡
(ትግ. ሰደበ - ወሰነ/ደነገገ)፡ ወረፈ፡ ነቀፈ፡ ዘለፈ፡ አዋረደ፡ አሳነሰ፡ አቃለለ፡ አኰሰሰ፡ አረከሰ፡ ክፉ ስም ሰጠ። (ተረት)፡ "አባቱን የጠላ የሰው አባት ይሰድባል።"
ሰደደ፡ ሱዳ/ሱድ (ዐረ. አስወድ)፡ ጥቍር። "ኣበ ሱዳ" እንዲሉ። ሲበዛ "ሱዳን" ይላል።
ሰደደ)፡ ወሰወሰ/ሸከሸከ ።
ሰደድ፡ ቋያ (የዱር/የበረሓ ሣር) ። "የሰደድ እሳት" እንዲሉ። ዳግመኛም ዕንጨት ለዕንጨት ተፋጭቶ የሰደደው እሳት ማለትን ያሳያል።
ሰደፍ፡ የባሕር እንስሳ (ዕንቍን/ሎልን የምትወልድ - ግእዝ) ። ሲበዛ "ሰደፎች" ይላል። "ብርጋና"ን ተመልከት።
ሰደፍ፡ የጠመንጃ ላት። "ሰደፍ ዕንቀንን በሆዷ እንደምታቅፍ ይህም ጠመንጃን በስተታች በኩል በውስጡ መያዙን ያሳያል።"
ሰዱቃዊ፡ የሳዶቅ ወገን፡ ተመጻዳቂ፡ አፈ ጻድቅ።
ሰዱቃውያን፡ ተመጻዳቆች።
ሰዳ፡ ባዶ።
ሰዳ፡ ዐጥር/ቅጥር የሌለበት ባዶ ስፍራ።
ሰዳሪ፡ የሰደረ/የሚሰድር (ደርዳሪ፡ ኰልኳይ) ።
ሰዳሽ፡ የሰደሰ/የሚሰድስ።
ሰዳቢ፡ የሰደበ/የሚሰድብ (አዋራጅ) ።
ሰዳቢዎች/ሰዳቦች፡ የሰደቡ/የሚሰድቡ (፩ጢሞ. ፫፡ ፲፩).
ሰዳዳ፡ ራሰ በራ (ጠጕሩ ከፊቱ ወደ ኋላው የተሰደደ) ።
ሰዳጅ (ጆች)፡ የሰደደ/የሚሰድ (ላኪ፡ ፈቺ፡ ለቃቂ፡ አንከባላይ) ።
ሰዴቻ (ኦሮ)፡ መንቀጥቀጥ፡ መንዘፍዘፍ።
ሰዴቻ መታው፡ አንቀጠቀጠው፡ አንዘፈዘፈው ።
ሰድቦ ለሰዳቢ ሰጠ፡ መተረቻ አደረገ።
ሰድቦ፡ ነቅፎ፡ ዘልፎ።
ሰዶም (ሎጣዊ/ሰዶማዊ)፡ ግብረሰዶም የሚያደርግ የሎጥ አገር ሰው።
ሰዶም፡ በእስያ ውስጥ በዮርዳኖስ ማዶ ያለ አገር (የገሞራ ጎረቤት) ። "ሰዶምና ገሞራ" እንዲሉ። ትርጓሜውም (ሲድ) ኖራ የሚወጣበት ማለት ነው ይላሉ (ኪ. ወ. ክ).
ሰገለ ቢስ፡ ሰግላባ፡ ነገሌ።
ሰገለ ቢስ፡ ዕውቀተ መጥፎ ፀባይ ጠንቋይ።
ሰገለበ (ሰበ)፡ ቸኰለ፡ ተስገበገበ፡ ተንገበገበ፡ ሰለፈ (በምግብ ጊዜ) ።
ሰገሌ፡ የቀበሌ ስም (ካንጎለላ በላይ ያለ ሜዳ)፡ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. የርስ በርስ ጦርነት የተደረገበት።
ሰገል፡ ጥንቈላ፡ ዕውቀት (ግእዝ) ።
ሰገሰገ፡ ሰበሰበ፡ አጠጋጋ፡ አቀራረበ፡ አጠበበ (ጥለትን ማግን፡ ቍቲትን ለመቋጨት) ።
ሰገሰገ፡ ጠቀጠቀ፡ አብዝቶ በላ (እሆድ አገባ/ዐጨቀ) ።
ሰገረ ስናርኛ ኼደ፡ ሠገረ።
ሰገበ፡ (ዘገበ)፡ ሰገባ አበጀ፡ ሰፋ (ገቢር) ።
ሰገበ፡ ሰለፈ፡ ተደቀነ (ተገብሮ) ። "ገበገበ"ን እይ።
ሰገባ (ቦች)፡ የሰይፍ ቤት፡ የጐራዴ መክተቻ። "አፎት"ንና "ድርቅ"ን ተመልከት።
ሰገብጋባ/ስግብግብ (ቦች)፡ የተስገበገበ፡ ችኵል፡ ጥዱፍ፡ ቀቀበታም፡ ሰላፍ።
ሰገነት፡ ሰማይ፡ ገነት (በቁሙ የቤት ላይ ቤት/ደርብ)፡ ዕንቍላል ግንብ (ዘዳ. ፳፪፡ ፰፡ ዳን. ፬፡ ፳፱) ። ገነት ያረገንና ያበ ባን መኖር ያስረዳል።
ሰገደ፡ (ሰጊድ፡ ሰገደ)፡ አጐነበሰ፡ ተንበረከከ (በኹለት ጕልበቱና በኹለት እጁ ምድርን ተመረኰዘ)፡ ተደፋ (በግንባሩ መሬት ነካ)፡ ወደቀ፡ ተነሣ።
ሰገደደ፡ መለሰ፡ ሰበሰበ፡ ደበቀ፡ ከለለ፡ ሰወረ። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱንም "ይሰግድድ/ይሰገድዳል" ይላል።
ሰገዳ/ስግዶሽ፡ የመስገድ ኹኔታ።
ሰገድ (ዶች)፡ የዕንጨት ስም (የታወቀ ዛፍ) ። "ወይራና ሰገድ" እንዲሉ።
ሰገድ፡ በወግዳ ክፍል ያለ አገር (ሰገድ የበቀለበት/ያለበት ማለት ነው) ። "ሰገድ ያኸላል፡ ረዥም ነው።"
ሰገድ፡ ዝኒ ከማሁ። (አጽናፍ ሰገድ)፡ የአጤ ገላውዴዎስና የአጤ ዘድንግል ስመ መንግሥት፡ ዳሮች/ዳርቾች የሰገዱለት ማለት ነው። በዘመን ብዛት ግን በሕዝብ አነጋገር፡
ሰገገ (ትግ)፡ ፊት ነሣ፡ አበረረ፡ ኣባረረ (፩ሳሙ. ፳፭፡ ፲፬).
ሰገገ፡ ቀና፡ ተንጋጠጠ፡ ረዘመ፡ በረረ (የግመልና የቀጪኔ/የሰጐን ዐንገት መሰለ - ሆሴ. ፯፡ ፰)
ሰገጠ፡ የቅልን ግፍና ለጠበ ባክርማ በስንደዶ ገመድ ሰፋ/ተመተመ። (ፊቱን ሰገጠ)፡ አከፋ (መጥፎ አስተያየት እየ) ። ካባን በክር ዘመዘመ።
ሰገጥ፡ የቅል/የካባ ስፌት፡ ቅምቅማት፡ ዝምዝማት።
ሰጕድ፡ የንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ ፈረስ ስም። "አባ ሰጕድ ወልዴ" እንዳለ አዝማሪ።
ሰጊድ፡ መስገድ (ግእዝ) ።
ሰጋ፡ ባባ፡ ሠጋ።
ሰጋለብ/ሰግላባ፡ ችኩል፡ ጥዱፍ፡ ስግብግብ፡ ሰላፍ።
ሰጋጅ (ሰጋዲ)፡ የሰገደ/የሚሰግድ።
ሰጋገደ፡ መላልሶ ሰገደ።
ሰጋጊ፡ የሰገገ/የሚሰግ (ዐንገቱን አቅንቶ የሚሠግር) ። "ሰጋጊ በቅሎ" እንዲሉ።
ሰጋጭ፡ የሰገጠ/የሚሰግጥ (ሰፊ፡ ቀምቃሚ፡ ዘምዛሚ) ።
ሰግ፡ ሰጐጥ።
ሰግሳጊ፡ የሰገሰገ/የሚሰገስግ (ሰብሳቢ፡ አቀራራቢ፡ አጥባቢ፡ ዐጝቂ) ።
ሰግደድ አለ፡ ተሰገደደ። "ከታዳጊ ጌታ ሰግደድ ያለ ቦታ" እንዲሉ።
ሰግደድ አደረገ፡ ሰገደደ።
ሰግዳዳ/ስግድድ፡ የተሰገደደ፡ ሰዋራ፡ ድብቅ ስፍራ፡ ገለልታ።
ሰግዳጅ፡ የሰገደደ/የሚሰገድድ (መለሽ፡ ሰብሳቢ፡ ደባቂ) ።
ሰጐኑ፡ ያ ሰጐን፡ የርሱ ሰጐን።
ሰጐን (ሰገኖ)፡ ዐንገቱና ቅልጥሙ የረዘመ ኣሞራ። ክንፎቹን ዘርግቶ በእግሮቹ ይሽከረከራል እንጂ እንደ ሌላው በአየር አይበርም፡ ተመሥጦ የለውም። ሲበዛ ሰጐኖች ያሠኛል። ተባቱንና እንስቱን ለመለየት፡
ሰጎንድ፡ ካልኢት ፷ ቅጽበት።
ሰጐኗ (ሰጐኒቱ)፡ ያች ሰጐን።
ሰጐኗ፡ የርሷ ሰጐን።
ሰጐደ (ትግ)፡ ዕመቀ፡ ጠቀጠቀ።
ሰጐደ (ደጐጸ)፡ ዐጠፈ፡ ቀነፈ፡ አጐደጐደ፡ ጋሻ አበጀ፡ ደጐሰ፡ ጐበጐበ፡ ሸለመ፡ አስጊጠ። "ሠረጐደ"ን እይ። (ደጐሰ ከቀኝ ወደ ግራ ሲነበብ ሰጐዴ ይኾናል) ።
ሰጐደ፡ ሰገለበ።
ሰጐደ፡ በሉ መታ።
ሰጐጥ (ጦች)፡ ሰግ (በመሬት ላይ ተተክሎ የማይነቃነቅ ደንጊያ)፡ የምድር ስገጥ።
ሰጓጅ (ጆች)፡ የሰጐደ/የሚሰጕድ (ዐጣፊ፡ ቀናፊ፡ አጐድጓጅ፡ ጐብጓቢ፡ ደጓሽ፡ ሸላሚ) ። "ጋሻ ሰጓጅ" እንዲሉ።
ሰጠ (ሰጠወ) (ሉቃ. ፯፡ ፳፩)፡ አቀበለ፡ አስረከበ፡ ዐደለ፡ ቸረ፡ ለገሰ። (ተረት)፡ "የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሣ፡ ካልሰጡ ኣይዕደቡም።" "፩ ወንድ ለዘጠኝ ያውም እግዜር ሰጠኝ።"
ሰጠመ (ሰጥመ)፡ ገባ፡ ጠለቀ፡ ጠለመ፡ ዘቀጠ፡ ጠፋ። "ሰመጠን" ተመልከት (ከዚሀ ጋራ አንድ ነው) ። መጽሐፍ ግን በሰጠመ ፈንታ "ተሰጠመ" ይላል፡ ስሕተት ነው (ዕብ. ፲፩፡ ፳፱).
ሰጠሰጠ (ጠሰጠሰ)፡ ደበደበ/ገረፈ/መታ።
ሰጠረ፡ አረቀቀ፡ ሰወረ። "ምስጢርን" እይ (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰጠጠ፡ ቀደደ፡ ሠጠጠ።
ሰጣ፡ መዘርጊያ።
ሰጣ/ሰጥሐ)፡ አሰጣ (ኣስጥሐ)፡ ዘረጋ፡ ዘረረ፡ ሰተረ፡ በተነ (ለፀሓይ ሰጠ) ። (ተረት)፡ "ሰርገኞች መጡ ብቅልእስጡ።" (ድዱን አሰጣ)፡ ሣቀ፡ ገለፈጠ (ኣድራጊ) ።
ሰጣሚ፡ የሚሰጥም (ጠላቂ) ።
ሰጥ ለመጥ አለ፡ ርግት ለጥ እለተ ለመጠ ተኛ ዠርባውን ኣስመቸ።
ሰጥ አለ፡ ጸጥ አለ፡ ረጋ፡ ተገዛ።
ሰጥ፡ ጸጥ።
ሰጥር፡ ቀጪን የጐድን ዐጥንት —ሠጥር።
ሰጥቶ፡ ዕንካ ብሎ አስረክቦ።
ሰጥቶ ይለምን፡ ቸር/ደግ የዋህ ሰው (ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ - ዮሐ. ፬፡ ፯, ፲).
ሰጪ/ጭ (ዎች)፡ የሰጠ/የሚሰጥ (ቸር፡ ሊጋስ) ።
ሰጪታ፡ የምትሰጥ (ዘራፍ ሴት) ።
ሰፈሰፈ (ሰፈፈ)፡ ቀረበ/ተሰለፈ ።
ሰፈረ (ሰፊር/ሰፈረ)፡ (ገቢር)፡ ለካ/መጠነ (ምድርን/አኸልን/ውሃን/ቅቤን/ማርን ማንኛውንም ነገር ኹሉ - ሕዝ. ፵፡ ፳, ፳፫) ።
ሰፈረ (ተገብሮ)፡ ዐረፈ/ተቀመጠ (ጭፍራው/ንቡ)፡ ተሰቀለ (ዶሮው/ወፉ - ፪ዜና. ፴፪፡ ፩፡ ማቴ. ፲፫፡ ፴፪) ።
ሰፈረ፡ ሰፈሰፈ ።
ሰፈረተኛ (ኞች)፡ ሰፈር ያለው ባለሰፈር በሰፈር ያለ የተቀመጠ የሰፈር ሰው ።
ሰፈራ/ስፍሮሽ፡ የመስፈር ሥራ ምጠና ።
ሰፈር (ሮች)፡ የጦር ሰራዊት ድንኳን ተክሎ ዳስ ጥሎ የሚያድርበትና የሚ...
ሰፈርጃል (ዐረ)፡ የተክል ስም (ፍሬው ላዩ ብጫ ውስጡ ብርንዶ የሚመስል ተክል) ።
ሰፈነ (ሰፊን/ሰፈነ)፡ ተሾመ/ገዛ/ሠለጠነ (የበላይ ኾነ) ።
ሰፈፈ (ሰፊፍ/ሰፈፈ)፡ በላይ ኾነ/ተዘረጋ/ረበበ (ዘፍ. ፩፡ ፪) ። ተንካፈፈ/ተንኳፈፈ/ዋኘ (አሞራው መርከቡ) ። "ጠለለን" እይ።
ሰፈፍ አለ፡ ሰፈፈ (፪ነገ. ፮፡ ፮) ።
ሰፈፍ የለሽ፡ የሴት ስም ("እንከን ነውር ነቀፋ እድፍ ጕድፍ የለሽ" ማለት ነው) ።
ሰፈፍ፡ የጠጅ ገፈት ወይም ግፋፊደረቅ የማር እንጀራ ድቃቂ ከሠም የተደባለቀ፡ ዐዲስ ሸክላ ማማሻ። "ፋጕሎን" አስተውል ።
ሰፊ (ሰፋዪ)፡ የሰፋ ፥ የሚሰፋ፡ ጠቃሚ/ዘምዛሚ ። "ልብስ በርኖስ መጝሚያ ጠፍር መኪና ሰፊ" እንዲሉ። ሲበዛ "ሰፊዎች" ይላል።
ሰፊ (ስፉሕ)፡ የሰፋ/የተንቦረቀቀ (ቦርቃቃ ቦላሌ) ። "ሰፊ ቤት ሰፊ ሱሪ ሰፊ መንገድ" እንዲሉ። "እጅን ገበረ ብለኸ ግብርን ሆድን ልብን" እይ።
ሰፊ ሜዳ፡ በባቢሎን አገር በሰናዖር ምድር የሚገኝ ሜዳ የተንጣለለ (ዘፍ. ፲፩፡ ፪) ። "ወገደ ብለኸ ወግዳን" አስተውል ።
ሰፊ ሰፈር፡ የድንኳን/የልብስ/የኮርቻ ሰፊ ቦታ ።
ሰፊ ኾነ፡ ሰፋ አልጠበበም።
ሰፊታ (ሰፋዪት)፡ የመሶብንና የሌላውንም ስፌት የምታውቅ የምታፈጥን በቶሎ የምትቈርጥ ሴት ።
ሰፊነት፡ ሰፊ መኾን (ጠቃሚነት) ።
ሰፊዋ/ሰፊዪቱ፡ የሰፋች ከጥበት የራቀች (ዘፀ. ፫፡ ፰) ።
ሰፋ (ሰፈየ)፡ ጠቀመ/ዘመዘመ/ደረዘ/ደረተ/ደበደበ/ወሰወሰ/ሸደሸደ/ሸከሸከ/ሸለለ። (ተረት)፡ "ለስ መጥሪያ ቍና ስፋች"።
ሰፋ (ሰፊሕ)፡ መስፋት።
ሰፋ (ሰፍሐ)፡ ተዘረጋ/ፋገ/ተንቦረቀቀ (ከጥበት ራቀ፡ ረዘመ በጐን በወርድ) ።
ሰፋ (ዐረ ጸፋ)፡ ጠራ/ጥሩ ኾነ ።
ሰፋ፡ ሴፍ ።
ሰፋ፡ በዛ እየጨመረ ኼደ።
ሰፋ አለ፡ ሰፊ ኾነ።
ሰፋ፡ የታናሽ ዛፍ ስም (ዘንግና ሶማያ የሚኾን ዕንወት ቀጥታ መለልታ ያለው ፪ኛ ስሙ ጠዬ ይባላል፡ ይኸውም ተባትና እንስት ነው፡ ወንዴ ሰፋ ሴቴ ሰፋ እንዲሉ) ። ጐዣሞች ግን ሱማያ ይሉታል፡ ሶማያ ከማለት ጋራ ይሰማማል። "ሰፋ ማለፊያ ጥሩ ማለት ነው፡ ፋ እይነሣም"።
ሰፋሪ፡ የሰፈረ/የሚሰፍር/የሚለካ (ተቀማጭ) ። "ዓሥራት ሰፋሪ ቀለብ ሰፋሪ መኻል ሰፋሪ" እንዲሉ።
ሰፋሪዎች፡ የሚሰፍሩ ተቀማጮች ።
ሰፋፊ፡ ብዙ ሰፊ (የኮባን የንሰትን የሙዝን ቅጠል ቈርበትን የመሰለ ነገር) ። (ግጥም)፡ "ይወለድና ቂጠ ሰፋፊ፡ ያባቱን ምድር ወሰን አስገፊ"።
ሰፋፊ፡ የሰፈፈ/የሚሰፍ።
ሰፋፋ፡ ጠቃቀመ ።
ሰፌድ (ዶች)፡ (ሰፋ/ሰፈየ)፡ ሰታታ ዝርግ ስፌት እኸል ማበጠሪያ ከምጣድ ላይ ትኩስ እንጀራ ማውጫ ። በትግሪኛ "ሰተታ" ይባላል ።
ሰፌድ እግር፡ እግሩ ለማጣ ጠፍጣፋ የኾነ ሰው ።
ሰፌዶ፡ መርከብ የሚገለብጥ የባሕር...
ሰፌዶ፡ ሰፌድን የመሰለ እንደ ሰፌድ ያለ ነገር።
ሰፌዶ፡ ዝርግ ጋሻ ።
ሰፌዶ፡ የዓሣ ስም (ጠፍጣፋ ዓሣ) ።
ሰፍነግ፡ እንደ ኳስ ክብ ኹኖ በባሕር ውስጥ የሚበቅል ብቋያ (ኹለንተናው ዐይን ውሃ መጣ የባሕር እንጕዳይ ዐይነ በጎ መሳይ) ።
ሱላይ፡ የዠማ ስም (በወግዳና በተጕለት መካከል ያለ ወንዝ) ።
ሱሌማ፡ ከድንጊያ የሚገኝ ማዕድን (ሌሎችን ማዕድኖች የሚያሰማማ/የሚያጠራ) ።
ሱሎ፡ የብ... ነጭ ፈረስ።
ሱማሌ (ዎች)፡ የነገድ ስም (በሐረርጌ አውራጃ በውጋዴና በኢሳ የሚኖር ዘላን ሕዝብ፡ በምሥራቅ አፍሪቃም አለ) ። "ሱማሌ ወገን" ቅጽል ይኾናል ።
ሱማል/ሶማል፡ ላም ዕለብ። ሱማል ዐረብኛ፡ ሶማል ሱማልኛ ነው።
ሱማልኛ፡ የሱማሌ ቋንቋ (የሱማሌ አፍ) ።
ሱማልያ፡ የሱማሌ አገር።
ሱማራ (ውሳጤ ባሕር)፡ የባሕር ውስጥ ለውስጥ የጦር መሣሪያ (መርከብን እየሸነቈረ የሚያሰጥም መኪና) ። በ፲፰፻ ዓ.ም መጨረሻ አሻሽለው ያበጁት የፈረንሳይና የጣሊያን የሆላንድ ሊቃውንት ናቸው ይባላል።
ሱሳ (ዕብ ሱስ ፈረስ)፡ የቀበሌ ስም (ነቢዩ ሕዝቅኤል በባቢሎን ራእይ ያየበት ስፍራ) ።
ሱሳ፡ በወይናደጋ የሚበቅል ዛፍ ቅጠለ ብዙ ዕንጨት ።
ሱሳን፡ በቀድሞ ዘመን በቤተ መንግሥት የሚሣል ባላበባ ሐረግ ።
ሱስ፡ ልማድ ሡሥ ።
ሱሪ (ዐረ ሱርዋል)፡ ታችኛ ልብስ (ወንድ በ፪ እግሩ አጥልቆ በወገቡ ላይ የሚታጠቀው - ሰፊ/ጠባብ/ቦላሌ/ተነፋነፍ ሱሪ፥ ኢያሱ ሱሪ ተፈሪ ሱሪ ቍምጣ ሱሪ እንዲሉ) ። ሲበዛ "ሱሪዎች" ያሠኛል ።
ሱሪ፡ ምስጢረኛ ውስጥ ዐዋቂ ሰው ። "ሱሪ ታጠቀ" (ወንድ ወጣው ሞያ...) ።
ሱሪ፡ ሰረገ ።
ሱራፌል፡ የነገድ ስም (የግዜርን መንበር የሚያጥኑ መላእክት ካህናተ ሰማይ ፮ ፮ ክንፍ ያላቸው) ። አንዱ "ሱራፊ" ይባላል፡ ትርጓሜው "ዐጣኝ" ማለት ነው ።
ሱርስት፡ የታችኛውና የላይኛው ሶርያ የአሶር የአራም ቋንቋ። "ሶርያን" እይ ።
ሱባዔ (ሰብዐ)፡ አንድ ወይም ኹለት ሰባት (ከሰው ተለይቶ በበኣት ተከቶ የሚደረግ ጾምና ጸሎት) ። የሱባዔ ትርጕም ሰባት ሰባትነት ማለት ነው።
ሱባዔ ገባ፡ ከሰው ተለየ፡ ዘጋ፡ ብቻውን ተቀመጠ።
ሱቲ፡ መናኛ ግምጃ ሐርነት የሌለው ። ሳተ (ስሕተ)፡ ወርውሮ ተኩሶ እጁን ዘርግቶ ሳይወጋ ሳይመታ ሳይዝ ቀረ (ዘንጉ ጥይቱ ጊጤውን ይላማውን ዐለፈ ዘለለ) ።
ሱት (ስሑት)፡ የሳተ/የሳተች (ደካማ - "ሴት ሱት" እንዲል ባላገር) ። "ሔዋንን" ያሳያል ።
ሱካ፡ ኀፍረተ ብእሲ። "ሹካን" እይ።
ሱካረ ነቢያት፡ ቀይ ሱካር። በግእዝ "ሶከረ ነቢያት" ይባላል (የመቤታችን ምሳሌ ነው) ።
ሱካር (ሶከር)፡ የሸንኰራገዳ እንቀት (ክርትፍ)፡ በያይነቱ ክብ/እንክብል/ድብልብል/አራት ማእዘን ኹኖ የተዘጋጀ ከሻይና ከቡና ጋራ የሚጠጣ ምግብ (ጣፋጭ) ። "ሸንኲርን" እይ። ሱካር (ሸንኰር - ዐማርኛ፡ ሶከር - ግእዝኛ) ።
ሱካር፡ የበሽታ ስም (ከሱካር የሚመጣ ሕመም - ብዙ ውሃ ያስጠጣል፡ በሰው ገላ ላይ ቍስል ያበዛል) ።
ሱካርና ወተት፡ የመጽሐፍ ስም (ብላቴን ጌታ ኅሩይ ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ የተረጐሙት ታናሽ የተረት መጽሐፍ) ።
ሱክሱክ አለ፡ ተንሶከሶክ ውሽኛ ኼደ።
ሱዳኔ (ሱዳናዊ)፡ የሱዳን ሰው/የሱዳን ተወላጅ።
ሱዳን (ኖች)፡ ያገር/የነገድ ስም (ሱዳን በአረብኛ ጥቍሮች ማለት ነው፡ በግእዝ ግን አገሩ ኖባ ይባላል) ። በ፲፬፻ ዓ.ም. ጊዮርጊስ ንጉሠ ኖባ የሚባል ክርስቲያናዊ ንጉሥ ነበራቸው።
ሱፋላ (ሱፍ)፡ ከበግ ጠጕር የተሠራ ጸዐዳ ካባ። ሱፍና ሱፋላ ባማርኛ ይተባበራሉ ። (ግጥም)፡ "ቅባኑጉ ወጥቶ ሲተርፈው ለይፋት ሱፋላጣኹ እኔ ያሰናጂ ጥፋት"። "ሱፍ አላጣኹ ሱፋላ ዐጣኹ" ማለት ነው።
ሱፋላ፡ የበርባሬ ብጫ ጥለት የሱፍ ኣበባ መሳይ።
ሱፋላ፡ የነጭ በግ ጠጕር እንደ ሱፍ ንጣት ነጭነት ያለው። "ሎፊሳን" አስተውል።
ሱፋጭ (ሰፈጠ)፡ ስለት ያለው ጥቍር ደንጊያ (ተሰብሮና ተፈንክቶ ሻፎ የኾነ አለት) ።
ሱፍ (ዐረ ጹፍ)፡ ጠጕር ። ጥብቆና ሱሪ ቀሚስ የሚኾን ከጠጕር የተሠራ ልብስ እንደ በርኖስ ያለ በርኖስን የመሰለ። "ሱፋላን" ተመልከት።
ሱፍ (ፎች)፡ የቅመም ስም (ዘይት የሚወጣው ነጭ ቅመም ባላገዳ) ።
ሲ፡ "በለው ሲሲ በለው" - ነገርን አስተውል።
ሲ፡ ዐቢይ (ዋና) አገባብ፡ በትንቢት ውስጥ ገብቶ አንቀጽ እያስቀረ በቁሙ ቀሪነቱን (ያለፈውን ሁኔታ) ያሳያል። (ማስረጃ)፡ "መብራት ሲበራ ጨለማ ይጠፋል፡ ነገር ሲያመልጥ ራስ ሲመለጥ አይታወቅም። ሲያውቅ የተኛን ሲሰማ ቅበረው።" "ሰን" ሲያስኘው የትንቢት መነሻ "ይ" ነው። "አ" ሲከተለው "ሳ" ይሆናል፡ "ዓለም ሳይፈጠር ፈጣሪ ነበር። ሰነፍ ሳይከብር ይሞታል"። "እኔ", "አንተ", "እናንተ", "እሷ" በነዚህ በአራቱ ሰዋሰዋዊ ግሶች በትንቢት ውስጥ ገብቶ "ስ" ሲሆን "ስጥፍ" (አንተ, እሷ), "ስትጥፉ" (እናንተ) ይላል። በግእዝ መሠረቱ "እንዘ" ነው።
ሲ፡ የስም ባዕድ መነሻ፡ ከሚያስደራጊ (ተሳቢ) አንቀጽ የሚወጣ። (ምሳሌ)፡ "አስካካ" > "ሲካካ"
ሲሉ (እንዘ ይብሉ)፡ ፈረንጆች "እጨረቃ ላይ እንወጣለን" ሲሉ ይወድቃሉ።
ሲላ (ሰላ)፡ (ዘዳ. ፲፬፡ ፲፱)፡ ያሞራ ስም (ፀረ እንቄ፡ ዐይነተ ጭልፊት፡ ቁመተ ዐርአሞራ፡ ጥፍሩ የሾለ/የሰላ የወፍ/የዶሮ ጠላት ነው) ። ሌሎቹ አሞሮች የያዙትን ይቀማቸዋል፡ ስለዚህ ጐበዝ ሰው "ሲላ" ይባላል። "ሾተልን" እይ።
ሲላ በዳሳ፡ የሰው ስም (ዐጤ ቴዎድሮስ በጦርነት ጊዜ ይዘው የሰቀሉት የንጉሥ ሣህለ ሥላሴ አሽከር ሐርበኛ ጐበዝ) ። በዳሳ በጋልኛ "ቸር" ማለት ነው።
ሲላዮ፡ ታናሽ መስፈሪያ (ርቦ) ።
ሲል (እንዘ ይብል)፡ ሲ ከሰ፡ ል ከኣለ፡ ትንቢት ይል መጥቶ "ሲል" ተብሏል። ሙሴ "ዐመሌ ዐመሌ" ሲል በደብረ ሲና ያየው እሳት በልቶት ይኾናል።
ሲል፡ ሳለ።
ሲል አለ፡ ታንቆ ሞተ። ይህ ዐማርኛ ከሲላ በዳሳ ተሰቅሎ መሞት የመጣ ነው።
ሲሎንዲስ፡ ቀድሞ ዘመን ዕፀ ሕይወትን ያገኘ ፈላስፋ (ቅዳ. ማር) ።
ሲመሽ፡ የሰው ስም (አባት ካረጀ በኋላ የወለደውን ልጅ "ሲመሽ" ይለዋል) ።
ሲሳያም፡ ሲሳየ ብዙ አገር ምግባም ።
ሲሳይ፡ ምግብ/መብል/ቀለብ/ጕርሥ/እንጀራ/የለት እራት ።
ሲራራ፡ ጭነት ቀርቃባ አጋሰስ ዠርባ ላይ የሚወጣ ።
ሲር ሲር አለ፡ ጮኸ ፥ ተንሰረሰረ ።
ሲር፡ የልብ ጩኸት፡ ሰረሰረ ።
ሲር፡ የተጣደ ማሰሮና የልብ ጩኸት ።
ሲሻኝ ሲያምረኝ ሲፈልገኝ ። (ተረት)፡ "እንባ ሲሻኝ ዐይኔን ስ...ወጋኝ"።
ሲሻው ሲያምረው ።
ሲቀር ይቀራል)፡ የሞተ ሰው ከቀባሪዎች ተለይቶ በመቃብር ሲቀር ሀብቱ እንዳልነበረ ይኾናል፡ በቤት ይቀራል ("(መዝ. ፵፱፥ ፲፯)") ።ቀረ ከ ሊ ሲ መነሻ እየኾኑት ሲነገር፡ "ከቀረ ሊቀር ሲቀር"፡ ባሉታም "ካልቀረ ላይቀር ሳይቀር" ይላል ።
ሲበሉ፡ የላኩት)፡ ችኩል፡ ጥዱፍ።ላኪ፡ (ዎች)፡ ለኣኪ) የላከ፡ የ ሚልክ፡ ሰዳጅ።
ሲባጎ (ዎች)፡ ቀጪንና ወፍራም የፈረንጅ ክር ወይም ገመድ።
ሲቶ (ብእሲቶ)፡ ቃለ አክብሮ ።
ሲቷ (እኅት)፡ እት፡ መነኵሴው፡ (እኅው)፡ ወንድም ይባላሉ ።በብዙም ለመናገር ("አኀው/አኃት") ወንድሞች፡ እቶች፡ ያሠኛል። ይቶት፡ አለስም፡ ብቻውን፡ ሲነገር፡ እንዳለፈው፡ በቂ፡
ሲነኳት የምትለበልብ ዐረግ ("በግእዝ አብላሊት ትባላለች ብል ለብላባ ለፍላፊ ልብለባ ትኰሳ ሽንገላ መለብለብ መተኰስ መፍጀት ማቃ ፯፻፫ መለብለቢያ ገለባ ጭራሮ ግባስ መተኰሻ መለብለቢያ ቀጪን የመቀነቻ ጠፍር መጥለፊያ ማሰሪያ ስትጠብቅ የፈረስን የበቅሎን ሆድ እንደ እሳት ለብልባ መላጧን ያሳያል ረፈ ለባለበ ተኳኰሰ አስለበለበ አስተኰሰ አስፈጀ - አስገ አስለብላቢ ያስለበለበ የሚያስለበልብ ማስለብለብ ማስፈጀት ማስገረፍ ተለበለበ ተተኰሰ ተቃጠለ ቅርፊትቅርፊቱ ቈዳ ቈዳው ተለብላቢ የሚለበለብ ዕርፍ ሞፈር ቀንበር ሽመልመሌ ልብልብ የተለበለበ ርጥብ ዕንወትሥጋ ቅልጥም ልብልባት ቀላል ቃጠሎ የእሳት ግርፋት ትኵሳት ልብላቢ የበርበሬ ፍሬ መገኛ መቀ መጫ ቋሚው መካከሉ ድልኸ ሲያደርጉት የሚለበልብ ክንክናን እይ ") ።
ሲኒማ፡ በመብራት (በኤሌትሪክ) ኀይል በተዘጋ ቤት ጐልቶ የሚታይ የማንኛውም ፍጥረት ሥዕል ጥላ (የማይናገርና የሚናገር) ። ይህን ጥበብ ያወጡ የዘር ስማቸው ሉሜር የሚባል ወንድማማቾች ፈረንሳዮች ናቸው ይባላል፡ ጊዜውም ፲፱፻ ዓ.ም ነው ።
ሲኒማ፡ በመብራት (በኤሌትሪክ) ኀይል በተዘጋ ቤት ጐልቶ የሚታይ የማንኛውም ፍጥረት ሥዕል ጥላ (የማይናገርና የሚናገር) ። ይህን ጥበብ ያወጡ የዘር ስማቸው ሉሜር የሚባል ወንድማማቾች ፈረንሳዮች ናቸው ይባላል፡ ጊዜውም ፲፱፻ ዓ.ም ነው ።
ሲኒጋል (ሎች)፡ ያገር/የነገድ ስም (በምዕራብ አፍሪቃ ውስጥ የሚኖር ሻንቅላ የሱዳን ቍራጭ የፈረንሳይ ቅኝ የነበረ፡ የሚገኘውም በአትላንቲክ ውቅያኖስ አጠገብ ነው) ።
ሲናር (ሮች)፡ ከገብስ ጋራ የሚበቅል የገረማ ዐይነት (ፍሬው ለፈረስ ቀለብ ይኾናል) ።
ሲኖዶስ፡ የካህናት ጉባኤ/ሸንጎ/ኣደባባይ/ዐውድ ። የጉባኤ መጽሐፍ በየጊዜው የተጻፈ ። ሲኖዶስ የጽርእ ቋንቋ ነው ።
ሲኦል፡ የቅጣትና የንስሓ ስፍራ፡ እስከ ፍርድ ቀን ኃጥኣን የሚኖሩበት ታችኛ ጐድጓዳ (የጨለማ ቦታ)፡ የዘብጥያ ምሳሌ።
ሲካ፡ ርጎ (ጐንደር) ። "ሲካ መስበቂያውን ያያል"።
ሲካካ፡ ቄብ ዶሮ።
ሲው፡ ሰዋስው።
ሲው/ጭው፡ የወፍ/የጫጩት/የከይሲ ጩኸት። "ሲውሲዋን" ተመልከት።
ሲውሲዋ፡ ሰጠ።
ሲውሲዋ፡ ከዘረምቦና ከሻሻቴ ከፍ ያለ ዶሮ።
ሲያክ (በኪክ በከ በክ)፡ በክት ሙቶ ያደረ፡ ከንቱ ብላሽ ዋዛ ፈዛዛ ። ንኡስ አገባብ ነው ።
ሲደልል፡ ዝኒ ከማሁ ("ሲያሞኝ ሲሸ ነግል መግደሉ ላይቀር ገል") ።
ሲዳማ፡ በሲዳሞ ውስጥ ያለ አገር (በጋልኛ ዐማራ/ሐበሻ ማለት ነው) ። ይኸውም ስም ዐማራ አስቀድሞ በዚህ ክፍል መኖሩን ያስረዳል ።
ሲዳሞ፡ በኃላ ቤት ያለ አገር።
ሲጥ፡ መጮኸ፡ ሠጠጠ።
ሲፈራ ሲቸር)፡ ላድርግ አላድርግ ልስጥ አልስጥ እያለ ሲያመነታ ። "ዶረሰን ዐፈረን" አስተውል ።
ሳ ፣ (ስ)፡ ዝኒከማሁ ንኡስ (ትንሽ) ኣገባብ። "ደግ ሳንሠራ ሞት ቢመጣሳ እንዴት እንሆናለን?"
ሳ፡ እንደ "ን" በመጨረሻ እየገባ የጥያቄ ወይም የቃለ አጋኖ ስሜት ይሰጣል፡ እሱንም "ማ" ያጎላዋል። (ጥያቄ)፡ "ሳኦል ሺ ገደለ፡ ዳዊትሳ?" (መልስ)፡ "ዳዊትማ እልፍ ገደለ። ኢዮአብ ከዘመቻ ደኅና ገባ፡ ኦርዮሳ?"
"ኦርዮማ ሙቶ ቀረ" በማለት የመሰለውን ሁሉ ያሳያል። በግእዝ መሠረቶቹ "ሰ",
"ኬ",
"ና" ናቸው።
ሳሕን (ዐረ. ጻሕን)፡ ጻሕል፡ ወጭት፡ ጣባ ደቅ (ከሽክላ/ከማዕድን የተሠራ - ትንሹም ትልቁም) ።
ሳለ (ሰሐለ)፡ ሞረደ፡ ፈገፈገ፡ ስነገለ፡ አሰላ፡ ለመጠ (መዝ. ፻፵፡ ፫) ። "በሳልከው ተመተር" እንዲሉ። "ሰላ"ና "ሳለ" ከ"ሰሐለ" መውጣታቸውን ልብ አድርግ።
ሳለ፡ (ሰአለ) ።
ሳለ (ሰአለ)፡ ለመነ፡ ጠየቀ።
ሳለ (ሰዐለ)፡ ኡሁ ኡሁ አለ፡ ጐበሰተ።
ሳለ (እንዘ ሀሎ)፡ ሳይሞት/ሳያልፍ። (ተረት)፡ "አባት ሳለ አጌጥ፡ ጀንበር ሳለ ሩጥ።"
ሳለ አይሰጥ፡ ሰረሰር ደንደስ (ቢቈርጡት/ቢግጡት ሥጋው የማይጠቅም) ። መዠመሪያውን "አለ" እይ።
ሳላ፡ መልኩ ወደ ጥቍረት የሚያደላ ወፍራም ስንዴ። "ሳላ ያሠኘው ምርቁ ይኾናል"።
ሳላ፡ ቀንዱ የሾለ/የሰላ የበረሓ እንስሳ (በግእዝ "ብዕዛ" ይባላል) ።
ሳላም፡ ሳል የያዘው/ያለበት/ያደረበት (ባለሳል) ።
ሳላይሽ፡ በወግዳና በተጕለት ክፍል ያለ ቀበሌ።
ሳላይሽ፡ የቀሰሌ ስም ። የፈረንጅ ፈረስ ።
ሳላይሽ፡ የፈትል ስም (የፈረንጅ ማግ) ።
ሳሌ፡ ካዋሽ የሚያንስ ጋን ዝንግሪር። "ቻልን" አስተውል (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሳሌ፡ የበሬ ስም።
ሳሌም፡ ሰላም። "ኢየሩሳሌምን" እይ።
ሳል (ሰዓል)፡ ከነፋስ/ከብርድ/ከክፉ ሽታ/ከጕንፋን/ ከመጠጥ የሚመጣ ጥዳቂ የሳንባ በሽታ (ትክትክ አክታ ያለው) ።
ሳመ (ሰዐመ)፡ ጨመጨመ/ተሳለሙ (ሉቃ. ፳፪፡ ፵፯) ። "እግር ሳመ/እጅ ሳመ/ምድር ሳመ/መስቀል ሳመ" እንዲሉ።
ሳሙና፡ ኮስቲክ ሶዳ ከሚባል የምድር ጨው ጋራ ተቀላቅሎ የተበጀ ቅባት (ዘይት ሞራ)፡ በእንዶድ ፈንታ ልብስ ማጠቢያ እድፍ ማስለቀቂያ (ሚል. ፫፡ ፪) ። ኮስቲክ ሶዳም ነጥሮን ሳይኾን አይቀርም ። "ሳሙና" በአረብኛ "ሳቡን" ይባላል ።
ሳሙና፡ ፈገግ ያለ የበቅሎ መልክ ("ገላ ሳሙና" - የገላ መታጠቢያ ባለሽቱ ሳሙና) ።
ሳሚ (ዎች)፡ የሳመ/የሚስም (ተሳላሚ/ጨምጫሚ) ። "ቤተ ክርስቲያን ሳሚ" ("ዐላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል" እንዲሉ) ።
ሳሚነት፡ ሳሚ መኾን።
ሳማ (ሞች)፡ የቅጠል ስም (ረቂቅ የኾነ እሾኹ እንደ እሳት የሚለበልብ/የሚያቃጥል/የሚያንገበግብ ቅጠል - ኢዮ. ፬፡ ኢሳ. ፴፬፡ ፲፫) ። በጦም ቀን እየተቀቀለ ይበላል፡ በጋልኛም "ዶቢ" ይባላል ።
ሳማ (ሰማ)፡
ሳማ (ሰዐምአ)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ እንቀጽና ቃለ መልእክት። "በበዓል ቀን ተቀምጠሽ ከመዋል ቤተ ክርስቲያን ሳማ"።
ሳማ (እንዘአሐሚ)፡ ጠላቴን ሳማ እኔ እጐዳለኹ እንጂ እሱ አይጐዳም።
ሳማ ሰንበት (ሰምዐ ሰንበት)፡ በምንጃር አውራጃ የተተከለ የሰንበት ታቦት (ትርጓሜው ሰንበት ሰማ ይመስላል) ።
ሳማ ቅቤ፡ ሰባት ዓመት የኖረ ቅቤ (ሖምጣጣ ጥቂቱ የሚበቃ የሆድ መድኀኒት) ።
ሳም (ስዒም)፡ መሳም።
ሳም ሳም አደረገ፡ ሳሳመ (ጭም ጭም አደረገ) ።
ሳም አደረገ፡ አጥብቆ ሳመ።
ሳምራውያን፡ የሰማርያ ሰዎች።
ሳምር፡ አገር—ሰማርያ ።
ሳምር፡ ዝኒ ከማሁ።
ሳምንት፡ ስምንት ቀን (በግእዝ ግን ያንዲት ሴት ተራ ቍጥር ነው - ትርጓሜውም ስምንተኛዪቱ/ስምንተኛዋ ያሠኛል) ።
ሳምንት፡ አንድ ወር ሠላሳ ቀን። "ማነኸ ባለሳምንት" እንዲል ሙሴ። የዚህም ምስጢር ሰንበቴን ያሳያል።
ሳሳለ፡ ሞራረደ፡ ለማመጠ። አሳለ (ኣስሐለ)፡ አስሞረደ፡ አስፈገፈገ፡ አሰነገለ፡ አስለመጠ።
ሳሳመ፡ መላልሶ ሳመ።
ሳራ፡ የሴት ስም (ያብርሃም ሚስት - እመቤት ማለት ነው) ።
ሳበ ፣ (ሰሐበ)፡ ጐተተ፡ መዘዘ፡ እረዘመ፡ (ተረት)፡ "በሬ ወዳገሩ ይስባል" (ይጐትታል) ። ሳበ፡ ጠራ፡ አወጣ፡ አመጣ፡ አቀረበ (ጋኔንን) ።
ሳበ፡ ወጠረ፡ ገተረ፡ ለጠጠ (ቈዳን፣ ድንኳንን) ።
ሳበ ይፋት፡ የሴት ስም፤
ሳበው፡ ጠመንጃ፡ በአፉ ባሩድ ከተመላበት በኋላ መጣቀሻው በቋድ ተስቦ የሚተኰስ የዱሮ ነፍጥ።
ሳቢ፡ (ዎች)፡ የሳበ፡ የሚስብ፡ ጐታች፡ አምጪ፡ አቅራቢ (በሬ፣ ፈረስ፣ ግመል፣ ባቡር) ። "ሳቢውን ግረፈው" እንዲሉ። (ጋኔን ሳቢ)፡ ጋኔን ጠሪ፡ አነጋጋሪ።
ሳቢ ዘር፡ ሳቢ ርጥበት፡ "ዘር መርጠብ"። የርጥበት ትርጓሜ መርጠብ መሆኑን ያሳያል። ፪ኛው የአማርኛ "ሳቢ ዘር" - "አስተራረስ", "አጐራረሥ" ይላል። (ግጥም)፡ "በኔ አስተራረስ ባንቺ አጐራረሥ እንኳን እሠኔ እማዚያም አንደርስ።"
ሳቢ ግመል፡ የቀድሞ አቡ (አባት), ጀዲ (ቅድመ አያት) ምልክት።
ሳቢሳ (ዎች)፡ ነጭ አሞራ (በዠማ ዳር በዝቶ የሚገኝ) ። በበሬ ዠርባ ተቀምጦ ወንዝ ይሻገራል፡ ከከብት ጋራ ይሰማራል። "ጫት"ን እይ።
ሳቢና ተሳቢ፡ ጐታችና ተጐታች፡ አንቀጽና ጥራ። "ሳቢ ጎደለ፡ ተሳቢ ሰውን።"
ሳቢያ፡ ሰበብ፡ ምክንያት።
ሳቢያ፡ ቀጥታ ሞፈር።
ሳቢያ፡ ኹለተኛ ዐረቄ፡ መናኛ ተወራጅ።
ሳባ፡ ሰበከ።
ሳባ፡ የሰው ስም፡ የኵሽ ልጅ፡ የትግሮች አባትና አገር (ዘፍ. ፲፡ ፯) ። "ሳባ ኖባ" እንዲሉ።
ሳባ፡ የየመኑ (የሳባ) ።
ሳቤላ፡ የሴት ስም፡ ብቃት ያላት የጽርዕ ፈላስፋ (በጣዖት ምኵራብ የምትቀመጥ) ። በአንድ ሌሊት የታየ የፈላስፎችን ሁሉ ራእይ ከመተርጐም በላይ እመቤታችን በፀሓይ አምሳል ወንድ ልጅ እንደ ታቀፈች በራእይ አይታ ተናግራለች። የነበረችውም በታላቁ እስክንድር ዘመን ነው። የትንቢት መጽሐፉም በግእዝ ይገኛል፡ አባቷ ህልቃስ ይባላል።
ሳቤላ፡ ጐበዝ በሬ፡ ብርቱ፡ ፈጣን፡ ሳቢ (ዐማርኛ) ።
ሳቤቅ፡ ያረገ ሬሳ (በመሬት ላይ የተጋደመ) ። "ዕፅ"ን ተመልከት።
ሳብ፡ (ስሒብ)፡ መሳብ።
ሳብ ረገብ አለ፡ ተገተረ፡ ላላ።
ሳብ አለ፡ ተሳበ።
ሳብ አደረገ፡ ጐተት አደረገ።
ሳብዕ፡ ሰባተኛ ፊደል። "ኦ ሳብዕ ቦ ሳብዕ" እንዲል ፊደል ቈጣሪ።
ሳብዕነት፡ ሰባተኛነት።
ሳተ፡ ሕግን ትእዛዝን አፈረሰ፡ ሃይማኖትን ካደ፡ ኀጢአት አደረገ የማይገባ ሥራ ሠራ (ዘሌ. ፭፡ ፲፰፡ ኢሳ. ፳፰፡ ፯፡ ሕዝ. ፵፭፡ ፳) ። ሳተ፡ ቅዘኑን ዘሩን ለቀቀ አፈሰሰ ። ሳተ፡ ዐጣ። "እባብ ጕድጓዱን አይስትም" እንዲሉ።
ሳተ፡ ዘነጋ/ገደፈ/አጠፋ የሚያውቀውን ።
ሳተነ (ሰይጠነ)፡ በረታ/ሮጠ/ፈጠነ/ቀለጠፈ (ኢዮ. ፩፡ ፯፡ ፪፡ ፪) ።
ሳተና/ሳታና (ሳጥና)፡ የሳተነ/የሚሳትን (ብርቱ ሯጭ ፈጣን ቀልጣፋ) ።
ሳተናው፡ የክራር መቺ ዘፈን ኣዝ...
ሳተናው፡ ያ ሳተና (ፈጣኑ ቀልጣፋው) ።
ሳታርፍ፡ በዱላ፡ ቀልቦ፡ መዠመሪያ፡ ቀላ፡ መታ፡ አጠነጋ ።ለግዐ፡ ጥንታዊ፡ ዐማርኛም፡ ሲባል፡ ይቻላል ።
ሳታት (ሰዓታት)
ሳታት፡ ሻ, ሻየ፤
ሳታት ቆመ)፡ ከመንፈቀ ሌሊት እስከ ጧት በዜማ ፈጣሪን ሲያመሰግን እመቤታችንን መላእክትን ጻድቃንን ሲለምን ዐደረ ።
ሳታት ቋሚ (ቀዋሜ ሰዓታት)፡ ሌሊት በቤተ ክሲያን ውስጥ ቆሞ ሳታት የሚያደርስ አወዳሽ ። "መዓል ብለኸ መዓል ሳታትን" ተመልከት ።
ሳታት ቋሚ)፡ አወዳሽ ደብተራ ።
ሳት (ስሒት)፡ መሳት ።
ሳት፡ ሰዓት ጊዜ ። "ሰዓትን" ተመልከት ።
ሳት አለው፡ ነገር አመለጠው ።
ሳት፡ የፊደል ስም "ሰ"። "ሳቱ ሰ" እንዲሉ። "ሳታትን" እይ፡ የዚህ ብዢ ነው።
ሳቻ (ስሕተት)፡ ኀጢአት ክሕደት ነውር ።
ሳች፡ የሚስት...
ሳነ) (ስእነ)፡ ተሳነ፡ አቃተ/አወከ/ቸገረ/ታከተ/ደከመ (፪ቆሮ. ፫፡ ፯) ።
ሳንሳ (ምዝላል)፡ የጋራ ሸክም (መሸከሚያውም አጣና መሎጊያ ይባላል) ። "የሳንሳ ያዘ የሳንሳ ተሸከመ" እንዲሉ።
ሳንቃ፡ ተጠርቦና ተልጎ የተቀመጠ የንጨት ሉሕ (፩ነገ. ፯፡ ፱) ።
ሳንቃ፡ ከዕንቍና ከወርቅ ከብር ከንሓስ የተሠራ የለምድ መጋጠሚያ በስተደረት ያለ።
ሳንቃ፡ የበር መዝጊያ መግጠሚያ።
ሳንቆች፡ መዝጊያዎች (ዘፀ. ፳፮፡ ፳፯, ፳፱) ።
ሳንባ (ሰንቡዕ)፡ በፍጥረት ሆድ ውስጥ ከልብ ጋራ የሚገኝ ሥጋዊ ወናፍ (እሳት መልክ ባፍንጫ ውዥሞነት አየርን የሚያመላልስ መዝገበ ትንፋሽ) ።
ሳንባ ቀለም፡ ሳንባ የሚመስል ቀለም (እሳትማ) ።
ሳንባ ዐቃፊ፡ ሳንባ ወደ ባር ሆድ እንዳይወርድ ዐቅፎ ደግፎ የሚይዝ የሚሸከም የደረት ውስጥ ሥጋዊ ቋት ።
ሳንባ ድድ፡ ችካም።
ሳንባ ጠለፍ፡ ዐልፎ ዐልፎ ቍጥራት ያለው ጅራፍ (ግርፋቱ ለልብ የሚሰማ ትንፋሽ የሚከለክል) ።
ሳንቲ፡ የሜትር ፪ኛ (አንዲት ጭረት) ።
ሳንቲ፡ የዋሽንት ዐይነት የዘፈን መሣሪያ ።
ሳንቲም (ሞች)፡ የብር ፻ኛ (የም...ትርጓሜ ኛ ነው) ።
ሳንከኛ (ኞች)፡ ሰበበኛ/ሁከተኛ። ሳንኮች፡ ቅባቶች (በዘፋኝ ዳዊት ጊዜ ለተዋሕዶዎች ሳንክ የኾኑ በቅባት ሃይማኖት የሚያምኑ ሰዎች) ።
ሳንክ፡ ጕትቻ፡ ሰበብ/ሁከት/ክፉ ሐሳብ ።
ሳንጃ፡ በጠመንዣ ጫፍ የሚሰካ የጦር መሣሪያ (ሽፋፉ ብረት መጠኑ የጩቤ ሲኾን ጫፉ ሹል ነው፡ የጨበጣ ውጊያ ይደረግበታል) ።
ሳንጃ ተርብ፡ የተርብ መርዝ፡ ወይም ሳንጃ የሚባል ተርብ (ተቈናጣጭ ዝንብ) ።
ሳንፊል፡ የነፋስ ስልክ (አለሽቦ ድምፅ የሚሰጥና የሚቀበል መኪና - ራዲዮ) ። ማርኮኒ የሚባል ጣሊያን ያወጣው፡ ሳንፊል ፈረንሳይኛ ራዲዮ ጣሊያንኛ ነው።
ሳዕስዐ)፡ ተንሻሻ በዛ ተን...“የተንቀሳቃሽ የዶሮ” ።
ሳኦል፡ ክፉ፡ አት፡ ሞተ ።
ሳኦል፡ የሰው ስም፡ በእስራኤል ላይ መጀመሪያ የነገሠ ንጉሥ።
ሳካ (ስሕከ/ሳሕክ)፡ እንከን (የገላ ነውር፡ ቋቍቻ፡ ዕከክ) ።
ሳካም የለሽ፡ የሴት ስም ("እንከንም የለሽ" ማለት ነው) ።
ሳክላ፡ በሺዋ ክፍል ያለ አገር።
ሳይ (ሰሓሊ)፡ የሳለ/የሚስል (ሞራጅ ሰንጋይ) ።
ሳይ (እንዘ እሬኢ)፡ እኔ ሳስተውል/ስመለከት ። "አየን" እይ።
ሳይንት፡ ያገር ስም።
ሳይዳ፡ እመቤት። "ሴዱን" እይ (ከዚህ ጋራ ዘሩ አንድ ነው) ።
ሳደረ፡ ሰው።
ሳደረ፡ አመረቀዘ (ቍስሉ)፡ ተበላሸ፡ ጠመመ (መቃብሩ/ነገሩ/የቀንበሩ ብስ) ።
ሳደፍ፡ መበከል ማኵለፍለፍ ማበሽጥቀ ።
ሳዱላ (ኦሮ)፡ ሴት ልጅ፡ ልጃገረድ።
ሳዱላ፡ በብር/በመዳፍ ልክ የተቦቀረ ያናት ቡቅራት (ባል ባላገባች ልጃገረድ መኻል ራስ/ቍንጮ ላይ የሚታይ ክብ ልጭታት) ።
ሳድስ ቅጽል) ንግር ።
ሳድስ፡ የፊደል ስም (ስድስተኛ ፊደል) ። "እ ሳድስ፡ ብ ሳድስ" እንዲል ፊደል ቈጣሪ። "ትጽል"ን ተመልከት።
ሳድስነት፡ ስድስተኛነት።
ሳዶቅ፡ የሰው ስም (ጻድቅ ማለት ነው) ።
ሳገ፡ ሳጋ (ሰሐገ)፡ ሻጠ፡ ሰካ፡ ጨመረ፡ አገባ። ላፃ የካህናት፡ ሳጋ የባላገር። "መሰገን" እይ (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሳገ፡ የሳገ/የሚስግ (ሻጭ) ።
ሳጋ፡ ባንድ በኩል እየሾለ እባጥ/እግድግዳ የሚገባ ጠርብ/ሽብልቅ።
ሳጠራ፡ አቴና ሣጠራ።
ሳጥናኤል (ሰይጣነ ኤል)፡ ሰይጣን (ጠላት) + ኤል (አምላክ) = በተገናኘ ፀረ አምላክ/ያምላክ ጠላት/ባለጋራ ማለት ነው።
ሳጨ (ትግ. ሳጸየ - መነመነ)፡ በጠጠር ዐጠበ፡ ፈገፈገ።
ሳጻ) ነጻ (ነጻሒ/ሐራ/ግዑዝ)፡ ጌታው የለቀቀው (ባርነት የቀረለት በራሱ ሐሳብ ዐዳሪ) ።
ሳፈረ (ዐረ)፡ ወደ ውጭ እግር ኼደ።
ሳፍ (ዐረ ጻፊ)፡ ጥሩ የጠራ ።
ሳፍ፡ ሹል ዐጥንት፡ ሰፋ (ሰፈየ) ።
ሳፍ፡ ያካንዱራ መውጊያ ሹል ዐጥንት ወይም ዕንጨት ።
ሳፍራ፡ የነፋስ ባሕርይ (ግእዝ) ።
ሳፍራን፡ አበባው ዐደይ መሳይ የሽቱ ቅጠል። በግእዝ "መጽርይ" ይባላል (ማሕ. ፩፡ ፲፬) ።
ሳፍወርቃ፡ የሴት ስም ("ጥሩ ወርቅ" ማለት ነው) ። ይህችውም በመርሐ ቤቴ የግርጌት ባላባት ነች።
ሳፍጅ፡ በጠራ ውስጥ ያለ ቀበሌ።
ሴላ፡ ድንቅ ማለት ነው።
ሴሎ፡ በእስያ ክፍል ያለ አገር።
ሴም፡ የሰው ስም (ከኖኅ ልጆች አንዱ በኵሩ - የርሱም ዕጣ ክፍል እስያ ነው) ።
ሴሰነ (ሰስኖ/ሰሰነ)፡ ኣመነዘረ/ቀነዘረ/ሸረሞጠ (ካንዲት ሴት ዐለፈ ተረፈ) ።
ሴሰን፡ ምንዝር/ቅንዝር/ሽርሙጥና ።
ሴሰኛ (ኞች)፡ የሴሰን ባለሴሰን (እመንዝራ ቅንዝረኛ ኻያጅ) ።
ሴሰኛነት፡ ቅንዝረኛነት ።
ሴሰኝነት፡ ዝኒ ከማሁ (ሮሜ ፲፫፡ ፲፫) ።
ሴራ፡ ዐድማ (ሠየረ፡ ሤረ) ።
ሴታውል (ሴት አውል)፡ ላም ዐንገት የሴት እረኛ ከሴት ጋራ የሚውል ወንድ (ደካማ ዐቅመ ቢስ ፈሪ) ።
ሴቴ ሰፋ፡ ጕጥ አልባ ጠዬ ።
ሴቴ ሬት፡ ጥርስ የሌለው የቍስል መድኀኒት ።
ሴቴ ቍልቋል፡ ለስላሳ መላላ ቀጥተኛ ቍልቋል ።
ሴቴ ብር፡ የሴት ሥዕል ያለባት ብር ("ብረ ሰብስብ") ።
ሴቴ ብርጕድ፡ ያልተመጠነ ያልተቀላቀለ ብርጕድ ።
ሴቴ ዐፈር፡ ቀይ መሬት ሸክላ ያፈር ወይዘሮ ።
ሴቴ፡ ወገን ቅጽል (የሴት ሲታዊ ሴትማ ሴት ዐይነት እንስታዊ) ።
ሴት (ብእሲት/ብእሰ)፡ ሚስት (የወንድ ጣምራ ኹለተኛ ባልተቤት የቤት አሳዳሪ - ፩ቆሮ. ፯፡ ፪, ፫, ፬) ። በሐባብ "እሲት" ትባላለች ።
ሴት ተወ፡ አበከረ ።
ሴት አኵሪ፡ የስንዴ ስም (ዳቦው የሚያምር ስንዴ) ።
ሴት አኵሪ፡ የቅጠል ስም (የዥብ ሽንኩርት የሚመስል ቅጠል ጠቈር ያለ) ። (ግጥም)፡ "የምናየው ቅጠል ካበቦች መካከል ሰፋ ሰፋ ያለው ለካ ሴት አኵሪ ነው"።
ሴት ወይዘሮ፡ የባለጠጋ ሚስት እመቤት ። "ወይዘሮ" ለሴት ቅጽል ነው ።
ሴትነት፡ ሴት መኾን (የሴት ያ - "ሴትነቱ ጣጣ ነው" እንዲሉ) ።
ሴትኛ ዐዳሪ፡ መበለት (ባል አልባ ብቻዋን የምታድር የምትኖር) ።
ሴትዮ (ኦ ብእሲቶ)፡ ቃለ አጋኖ ወይም አራኅርኆ (አንክሮና አክብሮም ከዚሁ ይገባሉ - "ሴት ሆይ" ማለት ነው) ።
ሴቶ፡ ቅጥ ዐጣሽ (የወፍ ጩኸት) ።
ሴቶች፡ ሚስቶች (ባልተቤቶች) ። ሴት፡ የሰው ስም (ያዳም ፫ኛ ልጅ ምትክ ማለት ነው ይላሉ) ።
ሴቷ/ሴቲቱ፡ ያች ሴት (ራእ. ፲፪፡ ፬, ፮, ፲፬, ፲፭, ፲፮, ፲፯) ።
ሴክል፡ ያመት ዘለላ (፻ ዓመት) ።
ሴዋ፡ ጌሾ (ገድ ተክ) ።
ሴደር፡ ቀይና ነጭ የበሬ መልክ (ቅላትና ንጣት እንደ መቀነት እየኾነ ገላውን የከበበው) ። ነጭና ጥቍር ሲኾን ጕሬዝ ይባላል።
ሴደርማ፡ የሴደር ወን... (ባካሉ ላይ ሴደር ያለበት ከብት) ።
ሴደርያ (ዐረ. ጸደይሪያህ)፡ የደረት ጥብቆ ባለጌጥ።
ሴዱ፡ የሰው ስም (ጌታ ማለት ነው) ። "ሳይዳን" ተመልከት።
ሴጣን፡ ጋኔን።
ሴፍ፡ ሰይፍ፡ ሰየፈ ።
ስ፡ በስም መጨረሻ እየገባ አፍራሽ (የማስተባበያ) ይሆናል። "አቤል ኀጢአት ሠርቷልን?" (ወይ) "ቃየል ኀጢአት ሠራ እንጂ፡ አቤልስ ኀጢአት አልሠራም። ይሁዳ ንስሓ ገብቷልን?" (ወይ) "ጴጥሮስ ንስሓ ገባ እንጂ፡ ይሁዳስ ንስሓ አልገባም።" በግእዝ መሠረቱ "ስ" ነው፡ "ግን"ን ተመልከት። ዳግመኛም በጥያቄና በስም በኀላፊ አንቀጽ ጫፍ እየተጨመረ እንደ "ም" ወይም "ዋዊ" ይሆናል። "እመቤታችንን ያበሠራት ሚካኤል ነውን ወይስ ሩፋኤል?" "ገብርኤል ነው እንጂ ሚካኤልና ሩፋኤል አይደሉም።"
ስ፡ የቅጽል ባዕድ መነሻ፡ ከተደራጊ አንቀጽ የሚወጣ፡ "ከረከረ" >
"ተስከረከረ" >
"ስክርክር"። "ስ" + ሴ፡ ምእላድ። "አንድ" -
"አንድስ",
"ማን" -
"ማንትስ",
"ማንትሴ",
"ምን" -
"ምንትስ",
"ምንትሴ",
"ቅባጥር" -
"ቅባጥርሴ"። የሁሉንም ፍቺ በየስፍራው እይ።
ስሓ (ሳካ)፡ እንከን። በግእዝ ዘሩ "ሴሐ" ነው።
ስሓ (ትግ)፡ ዕከክ።
ስሃ፡ እንከን፡ ስሓ።
ስኂን (ሰኀነ)፡ የጪስ ዕንጨት፡ ምጥን ልባንጃ፡ ዕጣን (ጥሩ ሽታ ያለው) ።
ስሒን፡ ልባንጃ።
ስለ (ሰአለ)፡ ዐቢይ እገባብ። "ዠግና ስሙን ማስጠራት ስለ ወደደ ዝኆን ዐደን ኼደ።"
ስለ ኀደለች ጉደኛዋ ጉደኚት እንደ ማለት እሳቶ ጉዲት ተብላለች ።
ስለ ሺ (ስለሺ)፡ የሰው ስም ("በሺ ፈንታ አንተ ትበቃለኸ" ማለት ነው) ። ስለ ከተናባቢ ሳድስ ቅጽል ሲገኝ "ታቦት ዘፋኝ" ይላል።
ስለ፡ እንደ። "ጥቍሬታ ስለ ጤፍ ነው።" "ስለ ምን?" (በምን ምክንያት/በምን ሰበብ?)
ስለ ደቂቅ እገባብ፡ የልመና ቃል ("ስላቦ/ስለግዜር/ስለ ጊዮርጊስ/ስለ ማሪያም/ስለ ነፍስ" እንዲል ለማኝ) ። "ብለኸ" ማለትንና አማላጅነትን ያሳያል።
ስለ ጠላት ፍራቻ ቤታቸውን በተራራ ላይ ይሠሩ ስለ ነበረ ነው ።
ስለ ፍቅር፡ በስመ አብ ይቅር (የሰይጣን ነገር) ።
ስለላ፡ የመሰለል ሥራ።
ስለቃ፡ ድቈሳ።
ስለታ፡ የመሰለት ሥራ።
ስለታም፡ ስለት ያለው/ባለስለት (ብረት ወይም ሰው - ፪ሳሙ. ፪፡ ፲፮).
ስለት (ስሕለት)፡ ስልነት (ሹለት) ። (ተረት) "እምብዛም ብልኀት ያደርሳል ከሞት፡ እምብዛም ስለት ይቀዳል እፎት።"
ስለት (ስእለት)፡ መለመን/ልመና (ማታ፡ ብፅዐት፡ ተሳይ የሚሰጠው ወርቅ/ብር/ግምጃ/መጽሐፍ/ከብት ወይም ሌላ ስጦታ - ዘፍ. ፳፰፡ ፳፡ ግብ. ሐዋ. ፳፩፡ ፳፫) ።
ስለት፡ ልመና ("ሳለ" - ሰአለ) ።
ስለት፡ ማረጃ።
ስለት፡ ማረጃ ("ሳለ" - ሰሐለ) ።
ስለት፡ ማረጃ (ካራ፡ ቢላዋ፡ ኣፋ፡ ጩቤ፡ ዱቢት፡ ሾተል፡ ሰይፍ፡ ጐራዴ፡ ሐኔ፡ ፈንዜ፡ ዋልሴ፡ ወንበርቲ - ፪ዜና. ፳፫፡ ፯, ፲) ። "ስለት አወጣ" "አሰላ"።
ስለት ድጕሱን፡ ደባ ራሱን ይቀዳል፡ ይጐዳል።
ስለቸ፡ ሰማ።
ስለፋ፡ ችኰላ/ቍተማ።
ስላች፡ ከብት የማይኼድበት ጠባብ የዱር መንገድ (አሳቻ እጐዳና የሚያደርስ) ።
ስላች፡ የነገር ጭላንጭል (አንድ ሰው በሌላ ሰው ጕዳይ የሚገባበት ሰበብ/ምክንያት) ።
ስላንቲያ፡ የመልሱ መጨረሻ ስድብ የኾነ የልጆች ጥያቄ። "ስላንተ ዘለፋ" ማለትን ያሳያል። "ዕንካ ስላንቲያሽ?" "በምንንቲያኸ?" "በወንፊት ምን አለኸ?" "በወንፊት ከልጆቹ ኹሉ አንተ ነኸ ምድር ፊት" እንዲል እረኛ (ዕንካ ስላንቲያ)፡ ጭቅጭቅ/ንዝንዝ/እሽኰለሌ ።
ስላዳም ብለኸ በሸንጎ ከለሜዳ ለብሰሽ ደምኸ የተነዛ ።"
ስሌት፡ ሒሳብ፡ ቍጥጥር።
ስል (ስሑል)፡ የሰላ።
ስል (ሥሩሕ)፡ የቀና ማረሻ (ግትር ያይዶለ ስበት) ። በትግሪኛ "ስሉሕ" ይባላል። "ስል የሰላሳለ"።
ስል (እንዘ እብል)፡ "ደግ መሥራቴ እጸድቅ ስል ነው።"
ስል፡ ስለታም መሣሪያ ("ስል መጥረቢያ" "ስል ምላጭ" "ስል ሰንጢ" እንዲሉ) ።
ስል፡ የሰለለ/ሰላላ።
ስል፡ የበጀ/የሰላሰላ/ሳለ።
ስልል፡ ማስረጃ/ነገር። "እከሌ ስልል አይገባውም" እንዲሉ።
ስልል አለ፡ ምንምን አለ።
ስልል፡ የተሰለለ አገር/መንግሥት።
ስልም (ጽሉም)፡ የጨለመ ።
ስልም አለ፡ ጭልም አለ ዐይኑ፡ ዛለ/ደከመ ሰውነቱ።
ስልምልም አለ፡ ተስለመለመ።
ስልምልም፡ የተስለመለመ (ዝልፍልፍ ጭልምልም) ።
ስልምልምታ፡ ጭልምልምታ፡ ዝልፍልፍታ ።
ስልምጥ አደረገ፡ ሰለመጠ።
ስልምጥ፡ የተሰለመጠ (ስልቅጥ) ።
ስልሰላ፡ ምንመና/ንጠላ/ሽንሸና/ሥንጠቃ።
ስልስል (ዕዉስ)፡ ዝኒ ከማሁ ልምሾ።
ስልስል አለ፡ ምንምን አለ ።
ስልቃት፡ ስለቃ።
ስልቅ፡ ሰለተ።
ስልቅ አደረገ፡ ድቅቅ አደረገ/ጐዳ (በሽታ ድጅኖ ሰውን) ።
ስልቅ፡ የተስለቀ (ድቍስልም ልዝብ) ።
ስልቅ፡ ያገር ስም ሥልቅ።
ስልቅጥ፡ የተሰለቀጠ/የተዋጠ (ውጥ) ።
ስልባቦታም፡ ስልባቦት ያለው/ባለስልባቦት።
ስልባቦት፡ በፈላ ወተት ላይ የሰፈፈ ቅቤ (በትግሪኛ "ላሕመት" ይባላል፡ ፈረንጆች "ክሬም" ይሉታል) ። ምስጢሩ ከወተት ላይ ተገፎ መነሣት ነው።
ስልብ (ቦች)፡ የተሰለበ/የተቈረጠ (ጕምድ፡ ጃንደረባ፡ ጠባቂ) ።
ስልቦሽ፡ ዝኒ ከማሁ።
ስልቦት፡ ጋዣ።
ስልት፡ ቀጠና/ጠኔ።
ስልት አለ፡ ልትት ድክም አለ፡ አሳለተ/አካደነ።
ስልት፡ ክፍል/ወገን። (የነገር ስልት)፡ ዐቅድ/መልስ። (የዜማ ስልት)፡ ዐይነት (ግእዝ/ዕዝል/አራራይ) ። (በስልት/በስልቱ)፡ በክፍል/በክፍሉ፡ በወገን/በወገኑ፡ ባይነት/ባይነቱ (ስም) ።
ስልቸታ፡ ጥጋብ/ጥላቻ ።
ስልቹ፡ የሰለቸ/የተሰለቸ (ታካች) ።
ስልቻ (ቾች)፡ የበግና የፍየል ቀልቀሎ/አቍማዳ/ዳውላ/ቀርበታ (ትንሹም ትልቁም የወይፈን ሲኾን ጭልጊ/ዐይበት ይባላል) ። ሥሩ "ዕለተ" ይመስላል።
ስልችት አለ፡ ተሰለቸ ።
ስልከኛ (ኞች)፡ ስልክ ጠባቂ ("ሳለስልክ ሰውን በስልክ 'አሎ' እያለ የሚጠራና የሚያነጋግር") ።
ስልከኛነት፡ ስልከኛ መኾን (የስልክ ሥራ መያዝ) ። ስልክን መዠመሪያ በ፲፰፻፸፮ ዓ.ም. ያወጣው እስክንድር ግራሐምበል የሚባል አሜሪካዊ ነው ይላሉ። ፈረንጆች "ቴሌፎን" ይሉታል።
ስልክ (ኮች)፡ የብረት/የመዳብ/የናስ ቀጥተኛ ሽቦ (የቃል/የኤሌትሪክ መኼጃ/መመላለሻ) ።
ስልክልክ አለ፡ ተስለከለከ።
ስልክክ አለ፡ ስልክ መሰለ፡ ቈነዠ ።
ስልጆ፡ ከባቄላና ከሰናፍጭ የተዘጋጀ የጦም ወጥ (ምግብ - ነጭ ሽንኵርትም አለበት) ።
ስሎሽ፡ ሙረዳ፡ ፍግፈጋ፡ ስንገላ።
ስመ መንግሥት፡ አንድ ንጉሥ የሚጠራበት ስም (ወናግ ሰገድን የመሰለ) ። በዘመናችን የፈረስ ስም ይባላል።
ስመ ስርጋዌ፡ አፈ በረከት/አፈ ወርቅ።
ስመ ርስት፡ የርስት ስም (የገባር የ...ግንደ በል) ።
ስመ ተጸውዖ፡ የመጠራት ስም (በስመ አብ የጸሎት መዠመሪያ) ። (ተረት)፡ "በእንተ ፍቅር በስመ አብ ይቅር ከበ ስመ አብ ተቀንሶለት።"
ስመ አምላክ፡ ያምላክ ስም (በቅዱስ መጽሐፍ ተጽፎ የሚገኝ - ይሖባ/አዶናይ/ኤሎሄ/አህያ ሸራህያ/አልፋ ወዖ/እግዚኣ ብሔር የመሰለው ኹሉ) ።
ስመ አምላክ፡ ጠንቋዮች እንደ ሐሳባቸው ጽፈው የሚሼጡት መጽሐፍ ።
ስመ ክርስትና፡ የክርስትና ስም (ገብረ ክርስቶስ/ተክለ ማርያም) ።
ስመ ክፉ፡ ስሙ በክፉ የሚነሣ ኀጢአተኛ/ግፈኛ ሰው።
ስመ ጥር (ሩ)፡ በዠግንነት/በደግ ሥራ/በውቀት ስሙ የተጠራና የታወቀ ባለዝና (በግእዝ "ስሙይ" ይባላል) ።
ስመ ፈጣሪ፡ ክፉ ስም ሰጪ ሐሜተኛ።
ስመ ፈጣሪ፡ የፈጣሪ ስም።
ስመኛ (ኞች)፡ ስም አክራ (የስም ባለስም ተብሎም ይተረጐማል) ። ስም ከአንቀጽ በፊት ተነግሮ በተሳቢነት፡ ከቅጽል ተናቦ በዘርፍነት፡ ከጥሬ ተናቦ በባለዘርፍነት ይነገራል።
ስመኝ፡ የወንድና የሴት ስም።
ስመጥ፡ ሰመመ ።
ስመጥ፡ የዠርባ ወንዝ (ሽንጥ - ግእዝ) ።
ስሙር፡ የሰመረ (የበጀ ማለፊያ - ኵስትር) ። "ስሙር እረኛ" እንዲሉ።
ስሙኒ፡ ሩብ ፳፭ ሳንቲም (ከጣሊያን ወዲህ የተለመደ ቋንቋ ነው - የተሙን ተሙናዊ ማለት ነው - ባ፩ ተሙን ፪ ይመነዘር ነበር) ።
ስሙን ለሰው አወረሰው፡ የራሱን ነውር በሌላ ላከከው።
ስሚ፡ መስማት (ወሬ ጭምጭምታ) ።
ስማ (ስማዕ/መስክር)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ፲ አድምጥ።
ስማ ምስክር፡ ዕወቅልኙን ስማ ("ያየኸውን/የሰማኸውን መስክር" ማለት ነው) ።
ስማ ስማ፡ መሰማሚያ ይንሣው (ያድባርን ያውጋርን ጠላት እንዲል ዐዋጅ ነጋሪ) ።
ስማ ስማ፡ ያዋጅ ቃል መዠመሪያ።
ስማ በለው፡ ተርጕመኸ ንገረው።
ስማ በለው፡ አስተርጓሚ።
ስማርድ (ስመ አርድ)፡ ነብርን ያሳያል ።
ስማርድ (ዶች)፡ የነብር ወጥመድ (ላዩ በብረት የተጠረቀ ውፍረቱ እንደ ቀንበር የኾነ ውስጠ ክፍት ዕንጨት - በውጭ የዝንጀሮ ጠጕር ገመድ ያለበት) ።
ስማንፋር (ዐረ. ሱም እልፋር)፡ ያይጥ መርዝ (ዐይጥን የሚገድል የቈለቈል ዐይነት መድኀኒት) ።
ስሜት፡ መገረን (በውስጥ ያለ ደዌ በስተው ሲሰማ ስሜት ይባላል - ትርጓሜውም መሰማት ነው) ።
ስሜነኛ (ኞች)፡ የስሜን ተወላጅ (የስሜን አገር ሰው) ።
ስሜን (ስምየ)፡ የኔን ስም ስምና ስሜን በገቢር ጊዜ ይገጥማሉ። "ስሜን ስሜን እነግርኻለኹ" (ዐጤ ቴዎ) ።
ስሜን፡ በጐንደር ሰሜን ያለ አገር። "ስሜን" የተባለው በቧሒት (የያሬድ ተራራ) ምክንያት ይመስላል ።
ስም ።
ስም (ሰመየ)፡ የቦታና የአካል መጠሪያ (ማንኛውም የሚታይና የማይታይ ነገር ኹሉ የሚጠራበትና የሚታወቅበት ስም ይባላል) ። የሚታይ (ሰማይ/ፀሓይ/ጨረቃ/ኮከብ/ደመና/ዝናም/ምድር/ውሃ/እሳት/እንስሳ/አውሬ/ወፍ/ሰው) ። የማይታይ (እግዜር/ወልአክ/ነፍስ/ነፋስ/ሐሳብ/ድምፅ የመሰለው ኹሉ) ። ከዚህም በቀር የተቀብዖ/የመጽሐፍ/ክርስትና/የባሕርይ/የግብር/የወል/የመጠን/የመልክ/የቄሳቍስ ስም (ነባር ስም/ጥሬ ስም የሚባል አለና ኹሉንም ባገባብ ተመልከት) ።
ስም፡ ሰመጠ።
ስም ሰጠ፡ ቀኛዝማች/ግራዝማች አለ።
ስም ቀቢ፡ በሰው ስም ላይ ነውርን የሚቀባ/የሚላክክ ።
ስም ዐበር፡ ሞክሼ ።
ስም አወጣ፡ የማዕርግ ስም ሰጠ፡ ወይም ተቀበለ/ተሾመ።
ስም አውጪ፡ ለሰው ክፉ ወይም ደግ ስም የሚያወጣ።
ስም አጠራር፡ የሰውን ስም ሲኾን በደግ ሳይኾን በክፉ ማንሣት ።
ስም አጥፊ፡ ስምን የሚያጠፋ/የሚያበላሽ ።
ስም እኩይ፡ የሐሜት ስም።
ስም ጠራ፡ እከሌ አለ።
ስምል፡ የተሰመለ (ልፍ ልዝብ) ።
ስምም፡ የተስማማ (ወዳጅ) ። "እከሌና እከሌ ስምም ናቸው" እንዲሉ።
ስምም፡ ፍቅር/ሰላም (ዓሞ. ፫፡ ፫) ።
ስምምነት፡ ስምም መኾን (ወዳጅነት) ።
ስምሪት፡ ወደ ዱር መኼድ፡ የዱር ሥራ (ዕንጨት ቈረጣ/እኸልና ሣር ዐዳ/ዕርሻ) ።
ስምና ግብር፡ ነባርና አባት ዘር።
ስምን (ስሙን)፡ የተሰመነ።
ስምን መልአክ ያወጣዋል፡ ይሰጠዋል/ይስይመዋል (ማቴ. ፩፡ ፳፩) ።
ስምንምን አለ፡ ተስመነመነ።
ስምንምን አደረገ፡ አስመነመነ።
ስምንምን፡ የተስመነመነ (ድቅስቅስ) ።
ስምንተኚት፡ ስምንተኛዪቱ ክፍል።
ስምንተኛ (፰ኛ)፡ የተራ ወይም የማዕርግ ቊጥር የስምንት ወገን።
ስምንተኛዋ፡ ስምንተኛዪቱ (ያች ስምንተኛ) ።
ስምንተኛው ሺ፡ የዘመን ስም (ሽንገላና ተንኰል ክሕደት ክፋት ጥመት የበዛበት ጊዜ) ። "ካጤ ምኒልክ አሽከሮች አንዱ መኰንን ስምንተኛው ሺ ብለው ሲጠሩ አገልጋያቸው ሰው አበላሺ ይል ነበር" ይባላል (አርእስተ መዝ. ፲፩) ።
ስምንተኛው፡ ያ ስምንተኛ (የርሱ ስምንተኛ) ።
ስምንቲያ፡ ከስምንት አንድ።
ስምንት (፰)፡ የቍጥር ስም (በሰባትና በዘጠኝ መካከል ያለ መድበል ወይም ጅምላ ቍጥር ያንድ ቤት) ።
ስምንቶ/ስምንትዮ፡ ስምንትነት ያለው ውስጠ ብዙ...
ስምዖን፡ የሰው ስም (የያዕቆብ ልጅ ካ፲፪ቱ ነገደ እስራኤል አንዱ) ። በዕብራይስጥ "ሺምዖን" ይባላል።
ስምጥ አለ፡ ስጥም አለ።
ስምጥ፡ የሰመጠ/የሰጠመ። "ዕጥ የኾነ ስምጥ ታጣ" እንዲሉ።
ስሞሽ (ስዕመት)፡ መሳም። "ራስ ስሞሽ" እንዲሉ።
ስሞተኛ፡ ስሞታ ወዳድ (ነጋሪ) ።
ስሞታ፡ እከሌ እንዲህ ሠራኝ እንዲህ ኣደረገኝ ብሎ ለዋ... የሚያሰሙት ወቀሣ።
ስሞታ፡ ወቀሣ—ሰማ ።
ስሞች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ መጠሪያዎች።
ስሳ ስድስት ዐሥር፡ , ሰደሰ ። ሴሰየ (ሴስዮ/ሴሰየ)፡ አጐረሠ/አስታረበ/ኣበላ/መገበ/ቀለበ ።
ስረጌ፡ የማንም ከብት መዋያ ሥ...
ስሪያ፡ ያውሬ የንስሳ ያሞራ ሩካቤ እሮጥ...ግንኝት ።
ስራ (ስራሕ)፡ ዕርሻ/ቍፋሮ/ዐዳ ። "ስራ መስራት የማይወድ አይብላ" (፪ተሰ. ፫፡ ፲) ።
ስራና፡ የሽንብራ ኩፍታ (ትግ) ።
ስርሰራ፡ ስንፈጣ ነደላ ።
ስርስራ፡ የሣር ስም (ቀጪን ሰንበሌጥ - ጐዣም) ።
ስርስር፡ የተሰረሰረ/የተበሳ (ብስ/ነዳላ/ሰባራ ሸክላ ብረት ግንብ ቅል) ።
ስርቂያ/ስርቆሽ/ስርቆት፡ መስረቅ/ሌብነት (ምሳ. ፱፡ ፲፯) ።
ስርቅ (ስሩቅ)፡ የተሰረቀ ከባለቤቱ...
ስርቅ አለው፡ ሆዱን ጐሰመው/ሸቀበው ።
ስርቅ፡ የሆድ ጕስምት። በግእዝ ግን "ስርቆት" ማለት ነው ።
ስርቅታ፡ ስርቅ ማለት (ፋቅ ሕቅታ) ።
ስርቆሽ በር፡ በፊት በር አንጻር ካዳራሽ ከልፍኝ በስተኋላ ያለ በር (ነገሥታት መኳንንት ለሕዝብ ሳይታዩ የሚወጡበት) ።
ስርነቃ፡ ስንፈጣ ትንታዞ ።
ስርንቅ አደረገ፡ ሰረነቀ ።
ስርንቅ፡ የተሰረነቀ (ዕፍን) ።
ስርዋጽ (ሰርወጸ)፡ ሽብልቅ ውሻል ስባሪ ጣልቃ ገብ ሥንጣሪ ለቃልም ይነገራል ።
ስርየት/ስሬት፡ የኀጢአት ይቅርታ ።
ስርጀታ፡ ጠለፋ ።
ስርግ (ስርግው)፡ የተስረገ/የተጌጠ/የተዳረ ።
ስርጓጕጥ፡ ወጣ ገባ፡ ሥርጓጕጥ ሠረጐደ ።
ስሻሽ፡ የሴት ስም ("ስፈልግሽ") ።
ስሻኸ፡ የሰው ስም ("ስፈልግኸ" ማለት ነው) ።
ስቅለት፡ ሰቀላ/መስቀል/መሰቀል (ግእዝ) ።
ስቅለት፡ የታላቅ በዓል ስም (ጌታችን ዓለምን ለማዳን በመስቀል ላይ የተሰቀለበት መጋቢት ፳፯ ቀን) ።
ስቅላት፡ ዝኒ ከማሁ (ለስቅለት - አማርኛ) ።
ስቅል (ስቁል)፡ የተሰቀለ/የተንጠለጠለ (እንጥልጥል ዝልዝል ሥጋ ርጥብ ልብስ) ። ባላገር ግን ሥዕልን "ስቅል" ይለዋል።
ስቅል አለ፡ ተሰቀለ ።
ስበብ፡ ሰበብ። "በስበቡ መምሬ ተሳቡ" እንዲሉ።
ስበት (ስሕበት)፡ እየተረገጠ በጥፍር አንድነት የታሰረ/የተቈራኘ ማረሻ (ድግር፣ ሞፈር፣ ቅትርት፣ ዕርፍ)፡ መርገጥ ወገል ሰባትነት ያለው።
ስበዛ፡ ሽጐጣ፡ ጭመራ።
ስባሪ፡ የሸክላ፣ የብርጭቆ ሽራፊ፡ ድቃቂ (ኢሳ. ፴፡ ፲፬፡ ፴፩፡ ፬፡ ግብ. ሐዋ. ፳፯፡ ፵፬) ።
ስባሪ፡ የቈሎ ክርታሽ፡ ፍንካች፡ ልብጥ።
ስባቅ፡ ቀለም (ባንድነት የታሸ ዕይር) ።
ስብሐተ ነግህ፡ የጧት ምስጋና (ቅዱስ ያሬድ በዜማ የደረሰው) ።
ስብሐተ ፍቁር፡ ሦስተኛ የሰዓታት ክፍል (ባለ ፫ ስንኝ)፡ የወዳጅ ምስጋና ማለት ነው።
ስብሐት (ሰብሐ)፡ ምስጋና፡ ማመስገን። "ስብሐት ለእግዚአብሔር" - ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል፡ "ለ" ማለት "ይገባል" ማለትን ያመጣል። ስብሐት ለአብ፡ ከማዕድ በኋላ የሚባል ጸሎት።
ስብሐት ለአብ፡ የሰው ስም (በኢያሱ አድያም ሰገድ ጊዜ መልከአ ሥላሴን የደረሱ ፍጹም ሊቅ) ።
ስብሰባ፡ ለቀማ፡ እከባ።
ስብሰባ፡ ጉባይ፡ ጉባኤ።
ስብሰባዎች፡ ጉባኤዎች፡ ጉባዮች።
ስብስባት/ስብስብነት፡
ስብስብ አለ፡ ተሰበሰበ።
ስብስብ፡ የተሰበሰበ፡ ጥርቅም፡ እክብ፡ ክምቹ።
ስብራት፡ መሰበር፡ ሰባራነት (ኢሳ. ፴፡ ፳፮፡ ኤር. ፶፩፡ ፻፬) ።
ስብራት፡ ዕጥፋት፡ ቅንፋት (የልብስ፣ የቈዳ) ።
ስብር (ስቡር)፡ የተሰበረ፡ ሥንጥቅ።
ስብር አለ፡ እንክት፡ ቅልጥም አለ።
ስብርባሪ፡ ስብርብር፡ የተሰባበረ፡ እንክትካች፡ ቅልጥምጥም ።
ስብርብር አለ፡ እንክትክት አለ።
ስብቀላ፡ ቅልጠፋ።
ስብቀት፡ ስብቅ፡ ማሳበቅ።
ስብቅ፡ ዱቄቱ የተሰበቀ (የታሸ) ጤፍ እንጀራ።
ስብቅል (ሎች)፡ የሰበቀለ፡ ጣፋጭ፡ ቀልጣፋ ቃል/ሰው።
ስብቅል አለ፡ ሰበቀለ።
ስብቅልቅል፡ ቅልጥፍጥፍ፡ የተሰበቃቀለ፡ የተመሰቃቀለ።
ስብቅልቅል አለ፡ ቅልጥፍጥፍ ምስቅልቅል አለ።
ስብቅልነት፡ ቀልጣፋነት፡ ጣፋጭነት።
ስብቆ/ስብቆሽ፡ ታሽቶ ተሰብቆ የፈላ የጥቍር ስንዴ ሙቅ እንትክትክ፡ ያጃ አጥሚት።
ስብት፡ የተሰበተ፡ የታረሰ፡ የተገለገለ፡ ግልግል ።
ስብከተ ገና ጾም፡ የነቢያት ጾም፡ የልደት የስብከት እሑድ (ከታኅሣሥ ፯ እስከ ፲፫ ያለ) ።
ስብከት፡ ቃል፡ ነገር፡ ትምህርት (ከሰባኪ አንደበት የሚወጣ) ።
ስብዛት፡ የሰበዝ አገባብ ኹኔታ።
ስብዝ፡ የተሰበዘ፡ የተሻጠ፡ የተሸጐጠ።
ስቦሽ፡ ጐተታ።
ስቱፋን፡ የሳቱ ያልመቱ ። "ልጆችም አንዱን ልጅ ስቱፋን ይሉታል"።
ስቱፍ፡ የሳተ ያልቀለበ ያልመታ ፉርሽ (ችኩል ጥዱፍ) ።
ስትል (አንተ/እሷ)፡ ስትሉ፡ ስትዪ፡ ስል፡ ስንል እያለ በ፰ ሰራዊት ይዘረዝራል ። "ሰን" ተመልከት።
ስትር (ስቱር)፡ የተሰተረ (ዝርግ ስጥ) ።
ስነጋ፡ ነደላ/ቅርቀራ።
ስነጣ፡ የመሰነጥ ሥራ።
ስኒ (ሺናዊ)፡ የሽን አገር ሥራ ታናሽ ሸክላ (የቡና መጠጫ በጥዋ አምሳል የተሠራ) ። "ፍንጃልን" አስተውል ። ሺን በግእዝ ሲን ይባላልና ስኒ ሲናዊ (ዘሲን ማለት ነው) ።
ስኒ ካፓ፡ የማዕርግ ልብስ (እንደ ስኒ ነጭ የኾነ ካፓ፡ ወይም ከነጭ ሐር የተሠራ ሺናዊ የሽን ካባ ማለት ይኾናል - ማር. ይሥ. ፫) ።
ስናም፡ ነፈሊያም አፍንጫ ነፍናፋ ።
ስናር፡ በሰሜን አፍሪቃ በሱዳን ክፍል ያለ አገር።
ስናር በቅሎ፡ ስናር አህያ ከእንስት ፈረስ የዴቀለው (ሲኼድ እንደ እንዝ የሚሾር የሚሽከረከር) ።
ስናር አህያ፡ ቁመቱ ፈረስ የሚያኸል ረዥም የስናር አህያ ።
ስናቅ/ስናግ/ትናግ፡ አፍንጫ ወይም ውሳጣዊ ያፍንጫ ቀዳዳ። "ሕፃኑ የጠባው ወደ ስናቁ ወጣና ትን አለ"።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር ።
ስናን፡ የሕፃን በሽታ (ተውሳክ ግግን የመሰለ) ።
ስናን፡ ያንድ ክፍል ጭፍራ ስም (በዱሮ ዘመን) ።
ስናጋ/ስናግ፡ ንፎ (የከብት አፍንጫ ቀለበት - በግእዝ ዝማም ይባላል - ፪ነገ. ፲፱፡ ፳፰፡ ኢዮ. ፵፡ ፳፮) ።
ስናግ (ትናግ)፡ ከላንቃ በስተኋላ ያለ ቀዳዳ ወዳፍንጫ የሚደርስ። "ስናቅን" እይ።
ስናግ፡ እዶሮ አፍንጫ የገባ ላባ።
ስናግ፡ የመጋረጃ ዘንግ (ከብረት ዋ የተሠራ - በግእዝ ሰንጐጕ ይባላል) ።
ስናግ፡ ያፍንጫ መካከለኛ ጫፍ (በግእዝ ሕልበት ይባላል) ።
ስናጭ፡ ለገድ ነፈል (ያፍንጫ ትንፋሽ በቀጥታ እንዳይወጣ የሚከለክል ሥጋ) ።
ስናፍቅሽ፡ የሴት ስም።
ስናፍቅኽ፡ የወንድ መጠሪያ ስም ("ስሻኸ ስፈልግሽ አገኘኹኸ" ማለት ነው) ።
ስናፒክ፡ የተክል ስም (የባሕር አገር) ።
ስንቀራ፡ የመሰንቀር ኹናቴ።
ስንቀን፡ ሱረት ሠነቀ ።
ስንቅር አለ፡ ተሰነቀረ ።
ስንቅር አደረገ፡ ሰነቀረ ።
ስንበባም፡ ቃታም (ባለቃታቍና ቍና የሚተነፍስ) ።
ስንበብ/ስንባብ፡ ቃታ የትንፋሽ ...ጥነት ።
ስንቡል፡ ሽቱ (ሽቶ በግእዝ ሰንበልት ይባላል) ።
ስንብር፡ የሰነበረ (መንታነት ያለው ድጕስ - በማኅደርና በዝናር ላይ ይታያል) ።
ስንብት/ስንብቻ፡ ወደ ሌላ ስፍራ ለመኼድ ለመዛወር ከጌታ/ካለቃ/ካሳዳሪ የሚቀበሉት ፈቃድ (የጥቂት ወይም የብዙ ሳምንት - መክ. ፰፡ ፰) ።
ስንተኛ (ኞች)፡ የተራ ቍጥርን መጠን ለማወቅ የሚነገር ጥያቄ። ሲጫፈር ስንትና ስንት ይላል፡ ብዛትንም ያመለክታል ።
ስንተኛው (ስንተኛቸው)፡ የጊዜና የማንኛውም ነገር ዐጸፋና በቂ ።
ስንታየኹ፡ የወንድና የሴት ስም።
ስንት (ስፍን)፡ የቍጥርን ልክ ለመጠየቅ የሚነገር ንኡስ አገባብ (ምን ያኸል) ። "ይሁዳ ጌታችንን ለስንት ብር ሼጠው፡ ጴጥሮስ ስንት ጊዜ ካደው፡ አይሁድ ስንት ጊዜ ገረፉት፡ ጌታችን ስንት ተኣምራት አደረገ"።
ስንቶች (እስፍንቱ)፡ ምንያኽሎች ።
ስንቾ፡ የሚጥሚጣ ስም (ሚጥሚጣ) ።
ስንን (ኖች)፡ ፪ኛው "ን" ይጠብቃል፡ ቅንቅን ገዳይ ቅጠል።
ስንኝ (ኞች)፡ የመልክ/የሰላምታ/የዐርኬ/የዘፈን ቤት ግጥም።
ስንከላ፡ የእግር ላይ ምት።
ስንኩል፡ ዝኒ ከማሁ (ጐደሎ) ። "ሀብተ ስንኩል መብሉ እኩል ሥራው ስንኩል" እንዲሉ።
ስንክልክል አለ፡ ተስነካከለ ።
ስንክሳር፡ የመጽሐፍ ስም (የመላእክትን ማዕርግና ሹመት የሚያስረዳ የነቢያትንና የሐዋርያትን የጻድቃንንና የሰማዕታትን የደናግልንና የመነኮሳትን ምግባር መከራና ዕረፍት ከዕለት እስካመት የሚነግር መጽሐፍ - የቤተ ክርስቲያን ታሪክ) ። የመቤታችንን ዜና የልጇንም በጎ ሥራ ኹሉ በሰፊው ይናገራል። ትርጓሜውም በጽርእ "የተሰበሰበ ስብስብ" ማለት ነው ።
ስንክሳሮች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ መጽሐፎች።
ስንኳ፡ ንኡስ አገባብ (የማማረጥ ቃል - ስንኳን/እንኳ - ዘፀ. ፲፬፡ ፳፰፡ ዘዳ. ፪፡ ፭፡ መዝ. ፻፴፱፡ ፲፮፡ ኢሳ. ፴፫፡ ፳፫፡ ፴፭፡ ፰፡ ሕዝ. ፳፬፡ ፲፪) ።
ስንኳን (ጥቀ. ጓ)፡ ንኡስ አገባብ ።
ስንኳን፡ ሰነፈ ።
ስንዘራ፡ የመሰንዘር ኹኔታ።
ስንዛሪ፡ የተሰነዘረ/የተሠነተረ።
ስንዝር (ስዝር)፡ ካውራ ጣት ጫፍ እስከ መካከለኛ ጣት መጨረሻ ያለ ልክ መጠን። "ስንዝር ተጋት" እንዲሉ (ስም) ።
ስንዝር አለ፡ ዕልፍ አለ ።
ስንዝር፡ የተለካ/የተመጠነ (ሥንትር ሥንጥቅ - ቅጽል) ።
ስንደቃ፡ አሰራ ።
ስንደዶ፡ ስፌትና ገመድ የሚኾን ሣር። (የውሻ ስንደዶ)፡ ስንደዶ የሚመስል ዋና የመስክ ሣር ሰል።
ስንዱ፡ የሴት ስም ።
ስንዱ፡ የተሰናዳ/የተዘጋጀ (ዝግጁ) ።
ስንዱነት፡ ዝግጁነት/ድርጁነት።
ስንዴ (ስንዳሌ)፡ የእኸል ስም (ዳቦና እንጀራ የሚኾን የብር እኸል - አምኜ/አቶሳል/ጐዣሜ/ጣይ/ሶራ/ዐዛዜ/መንዜ/ሸመጥ/ተኸሬ፡ ከዚህም በቀር ብዙ ዐይነት ስንዴ አለ) ። (ተረት)፡ "ስንዴ በጭንቅ ባለጌ በጥብቅ"።
ስንዴ ማና፡ የነጭ ገብስ ስም (እንጀራው የስንዴ መና የሚመስል) ።
ስንድቅ፡ የተሰነደቀ/የታሰረ ነዶ።
ስንድድ አለ፡ ቀጥታ ኾነ፡ አማረ አፍንጫው።
ስንድድ፡ ከተረከዝ ተያይዞ በስተላይ ያለ ሥር።
ስንድድ፡ የስንደዶ ቀለበት (የዦሮ ደግፍ መድኀኒት) ።
ስንድድ፡ የተሰነደደ ሰመግ።
ስንድድ፡ ጨሌ (የሴት እጅና እግር ጌጥ፡ መጋረጃና የመሶብ ቀሚስም ይኾናል) ።
ስንገላ፡ ፍግፈጋ/ውልወላ።
ስንጋት፡ ስነጋ (የመሰነግ ሥራ) ።
ስንግ፡ የተሰነገ (አፍንጫው ዋ በስናግ የተያዘ በሬ/ዶሮ) ።
ስንግ፡ የንግዴ ልጅ (የሴትን ማሕፀን በወሊድ ጊዜ ሰንጎ የሚያስንቅ) ።
ስንግል፡ የተሳለ/የተሰነገለ (ውልውል ጥሩ ብልጭልጭ ባለስለት መሣሪያ) ።
ስንጥ፡ የተሰነጠ/ያማረ (ልዝብ) ።
ስንፍ፡ ስንፍና/ስንፈት (ሥራ መፍታት/ሰነፍነት - ምሳ. ፳፮፡ ፬, ፭፡ ማር. ፯፡ ፳፪፡ ፩ቆሮ. ፩፡ ፳, ፳፩, ፳፫, ፳፭) ። "ስንፍ የዶባ ላም የጋለሞታ" እንዲሉ።
ስንፍ አለ፡ ሰነፈ ።
ስንፍ ገባው፡ ስንፍና ዐደረበት ተጠቃ ።
ስኣ፡ የኢፍ ፫ኛ (ሦስተኛ) ።
ስከላ፡ አሰራ (የመሰከል ሥራ) ።
ስካራም፡ ዘወትር ሰክሮ የሚታይ (ሳይስክር የማያውል ሰው/ቅዠታም) ። "ሰካራም" ማለት ግን ያልታረመ ዐማርኛ ነው።
ስካር ልብ አያሳጣም፡ ቍርሾን ያናግራል፡ ቂምን ይገልጣል ።
ስካር፡ የመጠጥ እብደት/ቅዠት። "ስካር ሰውን ከእንስሳ በታች ያደርጋል፡ የሚሰክርም ሰው በቁሙ የሞተ ነው"።
ስክ (ስኩዕ)፡ የተሰካ/የተሻጠ። "ስክ መዝጊያ" እንዲሉ።
ስክል (ሎች)፡ የተሰከለ - የታሰረ (ፈረስ፡ በቅሎ፡ ግመል፡ አህያ) ።
ስክረት፡ መስከር፡ ሰካርነት።
ስክር (ስኩር)፡ ስካሪ/የሰከረ።
ስክር አለ፡ ጥንብዝ አለ።
ስክርክር፡ የውሃ ዝቃጭ ከረከረ።
ስክተት (ሰክተተ)፡ ዝርግ/ጠፍጣፋ ሉሕ (የወጋግራ መቆሚያ) ። "ክባስን" እይ።
ስወራ (ስዋሬ)፡ ሽፈና፡ ክለላ፡ ድበቃ።
ስዊስ፡ በፈረንሳይና በጀርመን በጣሊያን መካከል ያለ አገር (ሰዓት የሚሠራበት) ። ሕዝቡ በ፫ ኣንጻር ፈረንሳይኛ፡ ጀርመንኛ፡ ጣሊያንኛ ይናገራል።
ስውር (ሮች - ስዉር)፡ የተሰወረ (የማይታይ፡ ድብቅ - ፈጣሪ፡ መልአክ፡ ሰይጣን፡ ነፍስ - መዝ. ፲፩፡ ፪፡ ማቴ. ፯፡ ፬, ፯) ። ረቂቅ ነገር (ምስ ዚር የለበስ/የጋቢ/የኩታ ስፌት) ። "ዐይን"ን ተመልከት።
ስውር ቦታ፡ ድብቅና ሽሽግ ስፍራ።
ስውር አለ፡ ድብቅ አለ፡ ዕቡ ኾነ።
ስየማ/ስያሜ፡ ስም አጠራር።
ስያፍ፡ ቀጥታ ያይዶለ (ከታች ሰፊ ከላይ ቀጪን ሾጣጣ፡ ወይም ጐደሎ የኾነ ዕቃ/ልብስ) ። "መቅንን" ተመልከት።
ስይም (ስሙይ)፡ የተሰየመ ("እከሌ" የተባለ) ።
ስይም፡ ልብም።
ስይፍ፡ የተሰየፈ (ዐንገቱ የተቈረጠ) ።
ስደራ፡ ድርደራ፡ ኵልኵላ።
ስደተኛ (ኞች)፡ (ዘፍ. ፳፰፡ ፩፡ ዘፀ. ፳፫፡ ፱)፡ በስደት ያለ/የኖረ (ላገሩ እንግዳ፡ ለሰው ባዳ፡ ባይተዋር፡ መጻተኛ) ። (ተረት)፡ "ሐሰተኛ በቃሉ፡ ስደተኛ በቅሉ (ይታወቃል) ።"
ስደት፡ መሰደድ። "ስደት ለወሬ ይመቻል" እንዲሉ።
ስዱብ፡ የተሰደበ፡ ውርፍ፡ ንቁፍ።
ስዱኝ፡ ስደዱኝ።
ስዱኝ አለ፡ ሰውን ለመጣላት/ለመምታት "ተውኝ/ልቀቁኝ" አለ።
ስዱዳም፡ የስዱድ ወገን (ስዱድ ያለበት) ።
ስዱዳን፡ ስደተኞች።
ስዱድ፡ የተሰደደ (ካገሩ ወጥቶ የኼደ - ፈላሻ) ።
ስዳጅ፡ መረን፡ የመከር መካተቻ፡ የካቲት።
ስድ፡ ልቅ፡ አግድሞ፡ አደግ፡ ባለጌ።
ስድሳ/ስሳ (፷)፡ የቁጥር ስም (ባምሳና በሰባ መካከል ያለ ያሥር ቤት አኃዝ - ስድስት ጊዜ ዐሥር ወይም ዐሥር ጊዜ ስድስት) ።
ስድስ፡ የተሰደሰ።
ስድስተኚት፡ ስድስተኛዪቱ ክፍል
ስድስት (፮)፡ ባምስትና በሰባት መካከል ያለ ቁጥር (ያንድ ቤት) ። ስድስተኛ/ስድስተኛው እያለ ተራ ቁጥር ይኾናል።
ስድስት አደረገ፡ እስከ ስድስት ቈጠረ/በስድስት ከፈለ።
ስድስትነት፡ ስድስት መኾን።
ስድስትያ፡ ስድስት መቶ ድር።
ስድስትያ፡ ከስድስት አንድ።
ስድስቶ ች፡ ባንድነት ጅብ ብለው የሚታዩ ኮከቦች (ስድስትነት ያላቸው) ።
ስድራ (ትግ)፡ ባል፡ ሚስት፡ ልጆች (ቤተ ሰብ) ።
ስድራት፡ ድርድራት።
ስድር፡ የተሰደረ ድርድር/ክልል።
ስድብ፡ ዘለፋ፡ ነቀፋ (ሕዝ. ፳፪፡ ፬፡ ማር. ፯፡ ፳፪) ። (በሌባ ቤተ ሰብ ላይ የተነገረ ስድብ) ። "የሚስቱ ባልትና ኺዱ ምን አለና፡ የማጭዱ ስም ተው፡ ቈያ ይጨልም፡ የልጆቹ አልተኙም ሰዎቹ።"
ስጃራ (ዐረ)፡ በወረቀት ተጠቅልሎ ፊሱ የሚጠጣደረቅ ትንባኾ። (የገለሞታ ግጥም)፡ "ስጃራ እማይጠጣ ትንሽ ልጅ ወድጄ በምን አመካኝቶ ይደርሳል እደጄ?" በፈረንጅኛ "ሲጋሬት" ይባላል።
ስጃጃ (ስጋጃ)፡ የፉቅራ/የቃልቻ መቀመጫ ምንጣፍ።
ስጃጃ፡ ሰደረ።
ስጕድ፡ የተሰጐደ (ቅንፍ፡ ጐድጓዳ፡ ዐቃፋ፡ ጕብጕብ፡ ሽልም) ።
ስጋጃ (ጆች) (ዐረ. ሱጋጃ)፡ ከጠጕር/ከቃጫ የተዘጋጀ ምንጣፍ (መስገጃ/መቀመጫ)፡ ግብረ መርፌ (የፋርስ ሥራ - ምሳ. ፴፩፡ ፳፪) ። "ስጋጃና ወላንሳ" እንዲሉ።
ስግ፡ የሰጋ፡ ሠጋ።
ስግ፡ የተሳገ ዕንጨት።
ስግሰጋ፡ የመሰግሰግ ሥራ (ስብሰባ ዕቃ) ።
ስግስጋት፡ መጠጋጋት።
ስግስግ አለ፡ ጥቅጥቅ አለ።
ስግስግ፡ የተሰገሰገ፡ የተቀራረበ።
ስግብግብ አለ፡ ተስገበገበ።
ስግደት፡ መስገድ፡ ሰገዳ፡ መውደቅና መነሣት።
ስግደዳ፡ ምለሳ፡ ስብሰባ፡ ድበቃ፡ ስውራ።
ስግድድ አለ፡ ድብቅ አለ (እንደ ዔሊ) ።
ስግጥ፡ የተሰገጠ/የተሰፋ ስፍ... ቅምቅም ዝምዝም።
ስጥ (ስጡሕ)፡ የተሰጣ (ዝርግ፡ ስትር፡ ለፀሓይ የተሰጠ፡ ቅይጥ) ።
ስጥ፡ አቀብል፡ ሰጠ።
ስጥ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (አቀብል፡ አስረክብ) ።
ስጥ፡ የተሰጣ (ሰጣ) ።
ስጥም (ስጡም)፡ የሰጠመ/የዘቀጠ (ጥልም) ።
ስጥም አለ፡ ስጠሙ።
ስጦታ/ስጥወታ፡ መስጠት፡ ችሮታ፡ ልገሳ (ዘፀ. ፴፭፡ ፭፡ ምሳ. ፳፭፡ ፲፬፡ ሮሜ. ፭፡ ፲፭, ፲፯) ። በሴት ለመናገር፡ ብትፈልግ "ስጦታዋ/ስጥወታዪቱ ያች ስጥወታ" በል። (ሮሜ. ፭፡ ፲፮).
ስጦታዋ፡ የርሷ ስጦታ። "ቀረ" ብለኽ "ይቅርታን" እይ።
ስፋት፡ ሰፊነት/ጐን።
ስፌት (ቶች/ስፍየት)፡ መስፋት። "እከሊት ስፌት ታውቃለች"።
ስፌት፡ ካክርማ/ከስንደዶ/ካለላ/ከግራምጣ የተሰፋ (ሰፌድ/ቍና/ጕርዝኝ/እንቅብ/መሶብ/ሌማት/ሙዳይ/አገልግል/ጮጮ/ጕብ የመሰለው ኹሉ) ።
ስፌት፡ የሸማ/የሱሪ/የበርኖስ/የዐጽፍ የማንኛውም ልብስ መጋጠሚያ። "ደርዝ ተኵስ ውስውስ ስፌት" እንዲሉ።
ስፌት፡ ጥልፍ ዝምዝማት ("ማሪያምን" አስተውል) ።
ስፍ (ስፉይ)፡ የተሰፋ (ድርዝ ዝም...) ።
ስፍ (ስፍይት)፡ የሐረርጌ ኦሮሞና የሱማሌ ልጃገረድ የተሰፋች ።
ስፍሕ፡ ድር ዝሓ (ግእዝ) ። ምስጢሩ ስፋትና ዝርግነት ነው።
ስፍረ ሰዓት፡ ሰው ጥላውን በማው...እየሰፈረ የሚያውቀው የሰዓት ቍጥር።
ስፍራ (ዎች)፡ ቦታ ቀበሌ (መዝ. ፻፴፭፡ ፪) ።
ስፍር (ስፉር)፡ የተሰፈረ/የተለካ (ቅጽል) ።
ስፍር፡ ልክ መጠን። "ስፍር የሌለው ስፍር ቍጥር" እንዲሉ (ስም) ።
ሶለላ (ጸለለ/ጋረደ)፡ አግሬ (፩ዜና. ፲፪፡ ፲, ፴፬፡ ፪ዜና. ፲፩፡ ፲፪).
ሶለላ፡ ወሰራ (ጐም) ።
ሶለሶለ) አንሶለሶለ፡ እዞረ/እንቀዠቀዠ/አንቀለቀለ። "ዘለዘለን" እይ።
ሶለሶል/ሶልሷላ/ሶልሶልቱ፡ የተንሶለሶለ/የሚነሶለሶል (ዘዋሪ) ።
ሶለግ (ጎች)፡ (ሰለከ)፡ ከግንዶሽ በላይ ከቍግ በታች ያለ የጅራፍ ክፍል (ከታች ወደ ላይ እየቀጠነ ይኼዳል) ። "ሾለቅን" ተመልከት።
ሶለግ ውሻ፡
ሶለግ፡ ውሻ ቀጪን ረዥም የፈረንጅ ውሻ (ሽንጣም ዐዳኝ) ። "ሶለግ" የውሻ ቅጽል ነው።
ሶል፡ ፀሓይ/ጀንበር (ሮማይስጥ) ።
ሶል)፡ ፀሓይ (ጧት በምሥራቅ፡ ቀትር ሲኾን በሰማይ መካከል፡ ማታ በምዕራብ እንድትታይ - ይህም እንደዚያ ማለት ነው) ።
ሶልዲ፡ ገንዘብ (ጣሊያንኛ) ።
ሶመሶመ)፡ አሶመሶመ፡ አረጠረጠ/አረተረተ/አኰተኰተ ለመጋለብ ። "እሶምሱምና ይዘኸልኝ ና" እንዲል ሰርገኛ።
ሶማያ (ሰው ማያ)፡ በላይ ጦር በታች ጀንፎ የተዋደደበት ዘንግ ጠዬ፡ ወይም ሌላ ዕንጨት። በጐዣምም ብዬ (ሰፋ) ሱማያ ይባላል።
ሶምሳ፡ ከጅኁር አፋፍ በታች ያለ አገር (በቡልጋም ይገኛል) ።
ሶምሶማ፡ ርትረታ (ከደንገላሳ የሚቀ ድም የሰንጋ ፈረስ ሩጫ) ።
ሶምሶን፡ የሰው ስም (በዕብራይስጥ "ሺምሾን" በአረብኛ "ሸምሽ" ይባላል - ፀሓይ ማለት ነው) ።
ሶስና፡ የሴት ስም ("አበቡት" ማለት - ኪ.ወ.ወ.ክ) ።
ሶረኔ/ሶረናዊ፡ የሶረን (ፍጹም ቅላት ያላት የቈላ ቆቅ) ።
ሶረን (ሶራ)፡ ቀይ በሬና ላም።
ሶሪት ቀይ ወፍ፡ , ሶራ ።
ሶሪት፡ የእንስት በግ ስም (ተባቱ ዳንግሌ ይባላል) ።
ሶሪት/ሶራዊት፡ ሶራ የምትመስል እንደ ጣዎስ የምታምር ቀይ ወፍ (አብረቅራቂ ጥቍረትና ንጣት ያላት ዞሬት ዞሪቴ) ። ባረብኛ "ዙራ" በጋልኛ "ጆሮ" ትባላለች ። "ሰራ ንን ሶረንን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው።
ሶራ (ሱርትዮን)፡ ቀይ ግምጃ የጣዎስ ሥዕል በላዩ ያለበት ። (ግጥም)፡ "ሶራ ሶራ ልበስ የጊዮርጊስ ፈረስ"። ሶራ ባረብኛ "ጹራ" በዕብራይስጥ "ጹራት" ይባላል (ኪ.ወ.ክ) ።
ሶሮሮ፡ ነጭ ጤፍ ።
ሶብይ፡ ጐበዝ፡ ጕልማሳ፡ ወጣት (ሦታ) ።
ሶታ፡ ሰተተ ።
ሶታ፡ ወጣት ሦታ ።
ሶከሶከ)፡ አሶከሶከ፡ በዝግታና በሩጫ መካከል ያለ ኣካኼድ ኼደ ውሻው።
ሶክሷካ፡ የተንሶከሶከ/የሚንሶከሶክ።
ሶዳ፡ የመጠጥ ስም (ጠርሙሱን ሲከፍቱት የሚጨስ/የሚፈላ ቀላል የባሕር አገር መጠጥ) ።
ሶፍያ፡ ሕልመ ዝሙት ተጻብኦ (በሴት አምሳል የሚታይ ምትሀት ፍትወታዊ የሰይጣን ጥበብ) ። "ሶፍያ መታችኝ" እንዲል ተማሪ አራተኛውን ጠባ እይ ።
ሶፍያ፡ የሴት ስም (የጽርእ ሰማዕት) ። ሶፍያ ጥበብ ማለት ነው።
ሰ፡ የዘ, የከ, የጸ ተለዋጭ (ምትክ) ነው። በግእዝ "አመዝገነ" የሚለው በአማርኛ "አመሰገነ", "ምዝጋና" > "ምስጋና", "መከነ" > "መሰነ", "መካን" > "መሲና", "ጸልመ" > "ሰለመ", "ጸለለ" > "ሰለለ", "ጸጥ" > "ሰጥ" እንዲሁም "በተከ", "ቀተረ", "ወዘወዘ" የሚሉት በቅደም ተከተል "በሰከ", "ቀሰረ", "ወሰወሰ" መሆኑን ያሳያል። ፪ኛውን "ሰለመ" እና ፫ኛውን "ስለለ" ተመልከት።
ሰሓጢ (ሰሐጠ)፡ በትግሬ ክፍል ያለ በረሓ (ትርጓሜው ቈንጣጭ ማለት ነው - ትንኙን ያሳያል) ።
ሰለ፡ በለዘ፡ ነጭና፡ ጥቍር፡ ኾነ ።
ሰለሔ መለሔ፡ "ሰለሔ" እንዳለፈው "መለሔን" እይ።
ሰለሔ፡ ገንፎ በቅቤ።
ሰለለ (ትግ. ሰለለ/ኰበለለ)፡ መነመነ፡ ቀጠነ (ከውፋሬ ራቀ - ያካል/የቃል - መሳ. ፫፡ ፲፭፡ ማቴ. ፲፪፡ ፲፡ ዕብ. ፲፪፡ ፲፪) ። የጌዜና ኀላፊ ትንቢቱ "ይሰል/ይሰላል" ይላል።
ሰለለ (ጸለለ/ተንኳፈፈ)፡ ጠለለ።
ሰለለ፡ ሰው ኹሉ የሚናገረውን ሰማ፡ ወሬ ጠበቀ። ከጦርነት በፊት የጠላትን አገር እየ አስተዋለ ተመለከተ/ገመተ (ብዛትን/ኀይልን/የሰዉን ሐሳብ/ያገሩን መውጫ/መውረጃ/መግቢያ መረመረ/አጠና/በክፉ ጐበኘ) ።
ሰለለ፡ ወጣ/ወረደ (ኢያ. ፪፡ ፪) ። "መሰላል" ማለት ከዚህ የወጣ ነው። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱ "ይሰልል/ይሰልላል" ይላል።
ሰለል ብሎ ገባ፡ እንደ ሰላይ/እንደ ውሃ ሳይታይ/ሳይታወቅ ማለት ነው።
ሰለል አለ፡ ስተት አለ።
ሰለልታ፡ ጠለልታ (ጠላ ከተመላ በኋላ በላይ የሚታየው ውሃና ዐሠር) ። ዳግመኛም ዐሠር ውሃ ይባላል።
ሰለልኩላ፡ በላስታ ውስጥ ያለ አገር (የቅዳሴ ዜማ መምህራን የሚገኙበት - ሰለልኩላ ባንኮበርም አለ) ።
ሰለመ (ሰለም/ሰለመ)፡ ማተቡን በጠሰ፡ እስላም ኾነ፡ ኦሪትን/ወንጌልን ወይም ሌላውን ሃይማኖት ተወ/ካደ፡ የእስላምን እምነት ተቀበለ፡ ዳነ።
ሰለመ (ጸልመ)፡ ጨለመ።
ሰለመ፡ አፈቀረ፡ አመሰገነ፡ አሳረፈ፡ አ...ሰላሚ የሚል።
ሰለመጠ (ሰለጠ)፡ ሳያኝክ ዋጠ/ሰለቀጠ ።
ሰለመጠ/ሰለቀ፡
ሰለሰለ (ትግ. ሰንሰነ/ከሳ)፡ ቀጠነ፡ ስለተ፡ መነመነ፡ ኰሰሰ (ኢዮ. ፴፫፡ ፳፩) ። ሥሩ "ሰለለ" ነው። (ተገብሮ) ።
ሰለሰለ፡ ሸነሸነ፡ ነጠለ፡ ሠነጠቀ (ሰሌንን/ግራምጣን - ገቢር) ። "ስነሰነን" እይ።
ሰለሰል/ሰልሳላ፡ የሰለሰለ (መንማና) ።
ሰለቀ (ሠለቀ)፡ ጕርሃን/ጤፍን ፈ... አደቀቀ/ደቈሰ/አላመ/አለሀበ።
ሰለቀ፡ በጣም ዐመመ/መታ/አደከመ ሰውነትን ።
ሰለቀጠ፡ ሳያኝክ ዋጠ። "ሰለመጠን" እይ።
ሰለበ (ሰሊብ/ሰለበ - ገፈፈ/ዐለገ)፡ የወንድን ብልት ቈረጠ/ጐመደ/ደደ እስከ ዕንብርት፡ ገሸለጠ፡ ጃንደረባ አደረገ።
ሰለበ፡ ምትሀት/ባስማት በሚዛን የሰውን ምርት/ቡሖ/ቅቤ/ጥጥ ሳበ/ወሰደ (የሌላውን ጥቅም አሳነሰ/ኣጐደለ፡ የራሱን መላ አበዛ) ።
ሰለባ፡ ማንኛውም የተቀማና/የተገፈፈ/የተሰረቀ ዕቃ። "ሌባ ከነሰለባው ተያዘ" እንዲሉ።
ሰለባ፡ ቈረጣ።
ሰለባ፡ የተቈረጠ ቍላ (የግዳይ/የድል ምልክት - ፩ሳሙ. ፲፰፡ ፳፭) ። (ተረት)፡ "ምርት ከገለባ፡ ግዳይ ከሰለባ።"
ሰለተ፡ ለተተ፡ ደከመ፡ ከሳ፡ ቀኑ መነመነ፡ ፍሬ አልባ ቀረ፡ ደረቀ (ተገብሮ) ።
ሰለተ፡ ከፈለ/ለየ (ገቢር) ።
ሰለታ፡ ሥሥ ክዳን ዝቅዝቅ።
ሰለቸ፡ ታከተ፡ ደከመ።
ሰለቸ፡ ጠበ፡ ጠላ፡ ነቀፈ፡ ተሠቀቀ፡ ተንገፈገፈ (ዘፀ. ፯፡ ፲፯፡ ዘኍ. ፳፩ - ፳፡ ኢዮ. ፲፡ ፩፡ ሕዝ. ፮፡ ፱) ። (ግጥም)፡ "ፀል፵ መረቁ ወጡ፡ ሰለቸን ምኒልክ ተነሥቶ ሽሮ ባበላን።" "ብዙ ቢተቹ ይሰለቹ" እንዲሉ። "እንጃን" እይ።
ሰለንዳ (ሰነዳ)፡ ዝግጅት/መቀናበር።
ሰለንዳ ቢስ፡ ዝግጅተ መጥፎ።
ሰለከ፡ ቀጠነ፡ ቀጥ አለ፡ ወደ ውስጥ ኼደ (ሰልቶ ገባ) ። "ሾለከን" እይ።
ሰለከከ፡ አማረ፡ ተዋበ፡ ሸገነ (ካለማማር) ።
ሰለክላካ/ስልክልክ፡ የተስለከለከ/ፍልክልክ/ሹልክልክ።
ሰለጀጅ/ሰልጃጃ፡ የተንስለጀጀ/የሚንሰለጀጅ (እንስልጅ ፈዛዛ) ።
ሰለጠ (ሰልጦ/ሰለጠ)፡ ቀና ኾነ፡ በጀ፡ ተከወነ፡ ተጨረሰ/ቀለጠፈ። ፪ኛውን "ሰላ" ተመልከት።
ሰለፈ (ዐረ)፡ አበደረ በዱቤ ሰጠ።
ሰለፈ፡ ቀረበ፡ ቸኰለ፡ አቈተመ (ለምግብ/ለወሬ) ።
ሰለፈ፡ ተጠረረ፡ ተዘጋጀ ለውጊያ (ተገብሮ) ።
ሰለፈ፡ ደከረ፡ ደቀነ ጸብትን (ገቢር) ።
ሰላ (ተስሕለ)፡ ስለታም ኾነ፡ ተባሾለ፡ ሾለከ።
ሰላ (ትግ. ሰልሐ፡ ዐረ. ጸለሐ፡ ግእዝ. ተሠርሐ)፡ በጀ፡ አማረ፡ ሰመረ፡ ቀና፡ ቀለጠፈ፡ ተከወነ (፪ዜና. ፳፡ ፳፡ ሉቃ. ፰፡ ፲). "ወሰላ ወሰልሰላ ዐንገቱ በምን ሰላ? ነጭ ጤፍ እየበላ" እንዲሉ አባትና እናት ልጃቸውን።
ሰላ ገደድ፡ ቅን፡ ጠማማ ወይም ቀና ጠመመ። "እከሌ ሰላ ገደድ ያውቃል" እንዲሉ።
ሰላላ፡ መላላ (ትክክል ያልኾነ ፈትል - ቅጥነትና ጥቂት የቀጥታ ውፍረት ባንድነት ያለው - የዝንብ አንዠት/የሰዶ ጕልበት የመሰለ) ።
ሰላላ፡ የሰለለ/የመነመነ።
ሰላሌ (ኦሮ)፡ የነገድና ያገር ስም።
ሰላሌ፡ አቅኒው ነው።
ሰላመ ገብርኢል፡ ቅዱስ ገብርኤል ለመቤታችን ያቀረበው ምስጋና (ከአቡነ ዘበሰማያት ጋራ የሚጸለይ) ።
ሰላማ፡ ብርሃነ አዜብ (ንኡስ ሰላማ) በ፲፻ ዓ.ም. የነበረ የሐበሻ ጳጳስ (ያገር ተወላጅ) ።
ሰላማ፡ አንደኛው መዠመሪያው የኢትዮጵያ ጳጳስ (ከሣቴ ብርሃን ፍሬምናጦስ በ፬፻ ፱ዓ.ም. የነበረ - ማ... ያገሪቱ ዝዝ... ነው) ።
ሰላማዊ፡ የሰላም/ባለሰላም ሰው (ደንሲ፡ ራም፡ ከብት፡ እንስሳ) ። "ሰላማዊ" የግእዝ ነው፡ በአማርኛ "ሰላመኛ" ሊባል ይኵላል።
ሰላም ላንተ፡ ምስጋና/ደኅንነት ላንተ ይኹን/ይደረግ ።
ሰላም፡ አጭር፡ ደጭና ደኅንነት፡ ጤና፡ ሤራ፡ ዕረፍት፡ ጸጥታ፡ ፍቅር፡ አንድነት፡ ምስጥና።
ሰላም፡ የዜማ ስም (የቁም ዜማና የማሕሌት ክረም) ።
ሰላምተኛ፡ ባለሰላምታ ሰው (ጠያቂ) ። "ሰላምታ ሰጠ" (ጠየቀ፡ "እንዴት ነኸ?") ።
ሰላምታ፡ በሰባቱ ጊዜያት የሚጸለይ የአባ ጊዮርጊስ ድርሰት አለ።
ሰላምታ፡ የፍቅር ምስጋና ደብዳቤ (የተላከ ከይድረስ ለካለ በኋላ "እንዴት ሰንብተኻል?" ከመኻል ብሎ የሚዠምር) ።
ሰላምታ፡ ጤና ይስጥልኝ ማለት፡ እጅ መንሣት፡ ከበሬታ መስጠት (ሉቃ. ፲፩፡ ፵፫) ።
ሰላሰለ፡ ሸናሸነ/ነጣጠለ ።
ሰላቂ፡ የሰለቀ/የሚሰልቅ (አላሚ/አለዛቢ ደቋሽ) ።
ሰላቢ (ዎች)፡ የሰለበ/የሚሰልብ (በንቋይ ምትሀተኛ ጝርተኛ) ።
ሰላቢነት፡ ሰላቢ መኾን።
ሰላች (ቾች)፡ የሰለተ/የሚሰልት።
ሰላኪ፡ የሰለከ/የሚሰልክ (ዐልቅት) ።
ሰላይ (ዮች)፡ የሰለለ/የሚሰልል (ጕበኛ/ተመልካች/ነገር ጠባቂ/"አገር ምን ይላል" ባይ - ኢያ. ፪፡ ፩፡ ፪ነገ. ፱፡ ፲፯, ፲፰፡ ፰፡ ሉቃ. ፳፡ ፳).
ሰላይነት፡ ሰላይ መኾን (ጕበኛነት) ።
ሰላጢን፡ ጦር፡ ሠለጠ።
ሰላጣ፡ የጐመን ዐይነት ቅጠል (ሳይቀቀል የሚበላ) ።
ሰላጤ፡ ሕፅን፡ ሠለጠ።
ሰላፋ፡ ብድር ልቆ ዱቤ ።
ሰላፋ/ሰላፍ፡ የሰለፈ/የሚሰልፍ (ችኵል እቈታሚ) ።
ሰሌን (ኖች)፡ የዘንባባ ሙሽራ (ሸለም - ከዚሁ የተሠራ ምንጣፍ - ኢሳ. ፲፱፡ ፲፭) ።
ሰሌዳ፡ ሉሕ (ያልተቀጻ ብራና/ወረቀት፡ ዝርግ/ጠፍጣፋ ሥራ፡ ጡብ፡ ብረት፡ እብነ በረድ፡ ደንጊያ፡ ንሓስ፡ የዝኆን ጥርስ - በላዩ ጽፈት የሌለበት) ። ሲበዛ "ሰሌዳዎች/ሰሌዶች" ይላል።
ሰል፡ ገመድና ጕንጕን የሚኾን ዋና የመስክ ሣር።
ሰልሳይ፡ የሚሰለስል (ሸንሻኝ መንማኝ) ።
ሰልቀጥ/ስልቅጥ አደረገ፡ ዋጥ አደረገ ።
ሰልቃጭ፡ የሰለቀጠ/የሚሰለቅጥ (ዋጭ) ።
ሰልቶ፡ ስል ኹኖ፡ ሾሎ/ሾልኮ። "ሰልቶ ገባ" "ሾልኮ ገባ"።
ሰልቷል፡ ቀና ብሏል፡ በጅቷል፡ ዕምሯል፡ ስል ኹኗል፡ ሾልኳል (ስበቱ/መጥረቢያው ፈሰሱ) ።
ሰልቺ፡ የሰለቸ/የሚሰለች ።
ሰልካካ/ስልክክ፡ መልከቀና/አፍንጫ ስንደዶ። "ፊተ ሰልካካ" እንዲሉ።
ሰልፈኛ (ኞች)፡ ሰልፍ የሚያሳይ/ባለሰልፍ ወታደር/ጭፍራ።
ሰልፈኛነት፡ ሰልፈኛ መኾን።
ሰልፍ፡ የጦርነት ዝግጅት (የደመራ ለትና በዘመቻ ጊዜ የሚደረግ ከነጦር መሣሪያው የሰራዊት መታየት) ።
ሰልፍ፡ ጦርነት/ውጊያ (፩ሳሙ. ፲፯፡ ፵፯, ፵፰፡ ፳፯፡ ፲፡ ፴፩፡ ፫) ። በግእዝ "ጸብእ/ቀትል" ይባላል።
ሰልፎ፡ የሚጤ መውጊያ ሹል ዘንግ።
ሰሎሞን፡ የሰው ስም (የዳዊት ልጅ የእስራኤል ንጉሥ - ብልኀ/ዐዋቂ/ፈላስፋ - ምሳሌን/መክብብን/ጥበብን/መሓልይን የደረሰ) ። ትርጓሜው ፍቅርን/ሰላምን ያሳያል።
ሰመለ፡ ዠለጠ/አለፋ/አለሰለሰ ቈዳን፡ ላገ/ፋቀ ዕንወትን ።
ሰመለለ፡ ጠጣ/ዥው አደረገ፡ ሰመጠጠ።
ሰመመ (ዘመመ)፡ አሸለበ/አንቀላፋ።
ሰመመናም፡ ባለሰመመን ።
ሰመመን፡ ሽልብታ/እንቅልፍ ።
ሰመሰመ (ትግ. ሸምሸመ)፡ ቶሎ ቶሎ ቃመ/በላ (በሬው) ።
ሰመረ (ሰምረ)፡ በጀ/አማረ/ማለፊያ ኾነ (ያዝመራ/የሥራ) ። "ዲያቆኑ መሥዋዕት ይሰምርለታል"።
ሰመረ (ፀመረ)፡ ቸነከረ/ጨመረ/እገባ ።
ሰመራ)፡ ሰኔ ።
ሰመራ)፡ አሰመራ/አሰማራ (ረዐየ/አውፈረ)፡ ነዳ/ወሰደ/እዱር አገባ/አሠራጨ (ኤር. ፴፩፡ ፲፡ ሕዝ. ፴፬፡ ፲፬) ።
ሰመሬታ፡ የገብስ ስም (ቶሎ የሚደርስ) ።
ሰመነ (ሰምኖ ሰመነ)፡ ስምንት አደረገ፡ በስምንት ከፈለ።
ሰመነ፡ ሰመረ።
ሰመነ፡ ከበደ/ተጫነ።
ሰመነ ዥረት፡ ዳር ዳሩን ሰመግ የሚበቅልበት ዠማ አዳባይ (የዱሮ ሰዎች በየሳምንቱ ቅዳሜ ጦርነት የሚያደርጉበት የጦር ተማሪ ቤት) ። "ሰመጎ ዥረት ያለሽ ዕዳሪ መች ትቀሪያለሽ ሳትሞከሪ፡ ሰመዕ ዥረት ያለሽ አሞራ ሥጋውን በልተሽ ለምዱን ዐደራ እንዳለ ወያኔ።"
ሰመግ፡ በቈላ የሚበቅል ዐረግ (ፍሬውን ሴቶች በክር እየሰኩ በእግራቸውና በእጃቸው ባንገታቸው ላይ ያስሩታል - ያጌ ጡታል። ሲበዛ "ሰመጎች" ይላል) ።
ሰመግ ዐይን፡ ዐይነ ትንሽሽ ሰው።
ሰመግ፡ የሰመግ ፍሬ (ስንድድ ዐንገት የዦሮና የእጅ ጌጥ) ። "ስመግ ዐንገት" መባሉ ውስጠ ክፍትና ያንገት ጌጥ በመኾኑ ነው። "ክሣድን" ተመልከት ።
ሰመግማ፡ ጠጕሩ እንደ ሰመግ ፍሬ ጥቍረትና ንጣት ያለው በሬ/ፍየል/ፈረስ (ጠቃጠቆ) ። ዳግመኛም ስሙ ሰመግ ይባላል።
ሰመጎ፡ ቃለ አጋኖ፡ ወይም አክብሮና ኣንክሮ ።
ሰመጠ፡ ሰጠመ ።
ሰመጠጠ (መጠጠ)፡ ሸመጠጠ/ጠጣ/ዥው አደረገ/ጨለጠ።
ሰሚ (ሰማዒ)፡ የሰማ/የሚሰማ (አድማጭ - ያዕ. ፩፡ ፳፭) ።
ሰሚ፡ በቶሎ ስለት የሚያደርስ ታቦት ወይ ብላ።
ሰሚ፡ አንተ እየተባለ ቅኔና ምስጋና የሚነገርለት የቅርብ ወንድ ።
ሰሚ፡ የተማሪን ቅኔ ሰምቶ የሚያርም የቅኔ ምር...
ሰሚዎች፡ ሰሞች የሚሰሙ አድማጮች (ያዕ. ፩፡ ፳፫) ።
ሰማ (ሰምዐ)፡ አደመጠ ነገርን ተቀበለ (፪ሳሙ. ፲፱፡ ፲፱) ። (ተረት)፡ "ያልሰማ ዦሮ ከጎረቤት ያጣላል።" "ሲያውቅ የተኛ ቢጠሩት አይሰማ።" (አልሰሜ)፡ "ኣልን" ተመልከት።
ሰማ፡ ጋለ/ሰማ ።
ሰማማ፡ አደማመጠ።
ሰማርያ፡ በእስያ ውስጥ በፍልስጥኤም ክፍል ያለ አገር (ቀድሞ ያሥሩ ነገደ እስራኤል መንግሥት የነበረበት) ።
ሰማኒያ (፹)፡ የቍጥር ስም (በሰባና በዘጠና መካከል ያለ ያሥር ቤት አኃዝ - ስምንት ዐሥር) ።
ሰማኒያ አወረደ፡ ሚስቱን ፈታ ለቀቀ በዳኛ ፊት ተፈጥሞ ።
ሰማኒያ ከነዳ፡ ተፈጥሞ ስለ ቀረ ፲፭ ብር ከፈለ።
ሰማኒያ፡ የሳምንት ቀጠሮ ፈጠም ።
ሰማኒያ፡ የች ኹለት አርባ።
ሰማኒያ፡ የውል የጋብቻ ቃል ማሰሪያ (እንደ ፊርማ ያለ ፊርማን የመሰለ - ይኸውም ንጉሥ ይሙት ማለት ነው) ። (ተረት)፡ "ሰማኒያ ለማገጃ ስለት ለማረጃ።"
ሰማዕትነት፡ ሰማዕት መኾን (በሰይፍ/በእሳት/በክፉ ሥቃይ መሞት) ።
ሰማየ ሰማያት፡ ላይኛ መጨረሻ ከሰማዮች በላይ ያለ ሰማይ (መዝ. ፻፲፭፡ ፲፮፡ ፻፵፰፡ ፲፬) ። "ኣርያምን" እይ።
ሰማዩ ቀላ)፡ ደመነ ።
ሰማያም፡ ባለሰማይ (የሰማይ ጌታ) ።
ሰማያዊ፡ ሰማይማ ሰማይ የሚመስል (ኒል ቀለም/ጥለት ልብስ/ካባ) ።
ሰማያዊ፡ የሰማይ/በሰማይ ያለ/የተቀመጠ (እግዜር/መልአክ) ።
ሰማያይ፡ ዝኒ ከማሁ።
ሰማይ (ሰመየ)፡ ከምድር በላይ ያለ የውሃ ባጥ ጣራ (ያለባላ/ያለምሰሶ/ያላንዳች ድጋፍ በፈጣሪ ትእዛዝ የተሰቀለ ጠፈር - የሌሊት/የቀን መብራቶች ጨረቃ/ኮከብ/ፀሓይ በበታቹ የሚታዩ) ። "ሰማይ ያለባላ ምድር ያለካስማ" እንዲሉ። ሲበዛ በግእዝ "ሰማያት" በአማርኛ "ሰማዮች" ያሠኛል፡ እነዚሁም ሰባት ናቸው (ኢሳ. ፵፰፡ ፲፫፡ ማቴ. ፫፡ ፲፮) ።
ሰማይ፡ በሰማይ የሚኖር አምላክ ፈጣሪ ("የሰማይ ቍጣ" እንዲሉ) ።
ሰማይ ቤት (የሰማይ ቤት)፡ በሰማይ ያለ ቤት (ገነት/መንግሥተ ሰማይ) ።
ሰማይ ዳሱ፡ ረዥም ሰው/ደመና ገፊ (ሔኖ. ፯፡ ፪, ፬፡ ዘዳ. ፪፡ ፳, ፳፬) ።
ሰማይ ጠቀስ፡ ዐይቦ የሚባል የነጭ በሬ ቀንድ ("ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ጅራው ምድር አበስ" እንዲሉ) ። የዚህም ምስጢር የጌታችንን አምላክነትና ሰውነት ያስረዳል ።
ሰማይና ምድር፡ የተለያየ/የተራራቀ ነገር (አንድነት የሌለው) ።
ሰሜን፡ የማእዘን ስም (ካራቱ የዓለም ማእዘኖች ሦስተኛው የምድር ጎፍ ራስጌ በስተግራ ያለ) ።
ሰምሳሚ፡ የሰመሰመ/የሚሰመስም (ቃሚ) ።
ሰምዛ፡ ሰንሰል (ዮሐ. ፲፱፡ ፳፱) ። በግእዝ ግን "ስማዝ/ሸንበቆ/ጐሽ/መቃ" ተብሎ ይተረጐማል።
ሰሞነኛ (ኞች)፡ ከእሑድ እስከ እሑድ በቤተ መቅደስ የሚያገለግል ቀዳሽ ሠላሽ ቄስ/ዲያቆን። ("ፈራ" - ፈረየ ብለኸ ፍሬን እይ) ።
ሰሞነኛነት፡ ሰሞነኛ መኾን።
ሰሞን (ሰሙን)፡ የስምንት ቀን ስም፡ ዳግመኛም ሰውን በግእዝ ያንድ ዕለት ቅጽል ይኾናል፡ ትርጓሜውም ስምንተኛ ይባላል።
ሰሰ፡ ላሰሰ/ነቀለ/ጠረገ።
ሰሰለ (ሰስሎ...ራቀ) ።
ሰሰለ፡ ተወገደ/ራቀ ።
ሰሳ፡ የዛፍ ስም (የጦሚት ዐይነት ዕንጨት) ።
ሰስ፡ በቁሙ ሠሥ ።
ሰረም፡ ሰረቀ ።
ሰረም፡ ቈለቈል።
ሰረሰረ (ሰረረ)፡ ሰነፈጠ፡ በጥንቃቄ በሳ ነደለ ውስጥ ለውስጥ ኼደ ። (ተረት)፡ "ጣዝማ ይሰረስራል ዳኛ ይመረምራል።"
ሰረረ (ሰሪር/ሰረረ)፡ ከፍ አለ፡ ወጣ/በላይ ኾነ፡ ጠቃ/መታ/ወነገ። "ቀኝም ሰረሩ ግራም ሰረሩ መገናኛው ኰሩ ወጣ"። (ተረት)፡ "ፍየል በግርግር እናቱን ይሰር"።
ሰረረ፡ ሰረሰረ ።
ሰረሪን፡ የተክል ስም (ሥሩ መቅመቆ ቅጠሉ ቀረሻሽንቦ የሚመስል ተክ) ።
ሰረቀ (ሰሪቅ/ሰረቀ)፡ ሳይታይ የሰው ገንዘብ አነሣ ወሰደ ሞጨለፈ (ቤትን ቈፍሮ ሰርስሮ ነድሎ ኪስን በርብሮ) ።
ሰረቀ፡ አከሳ። "ሰውነቱን ይሰርቀዋል።"
ሰረበ፡ ፈሰሰ/ተንሿሿ (ግእዝ) ።
ሰረተተ) አንሰረተተ፡ አረዘመ/ጐተተ (ልብስን) ።
ሰረተት/ሰርታታ፡ የተንሰረተተ/የሚንሰረተት (ጐታታ) ።
ሰረነቀ (ሰረቀ)፡ ወደ ስናቅ ወደ ሰርን ወጣ ዐፈነ፡ ሰነፈጠ ትን አለ፡ ዐነዘዘ ።
ሰረየ (ሰርይ/ሰረየ)፡ እቀለለ/ተወ/ይቅር አለ (ኀጢኣትን በደልን) ።
ሰረየ፡ መድኀኒት አደረገ፡ ሠ...
ሰረገ (ሰሪግ/ሰረገ)፡ አደራጀ/ደገሰ ። ሰረገ፡ ልጅን አስጌጠ/ኳላ ዳረ ። ሰራጊ (ዎች)፡ የሰረገ/የሚሰርግ (ደጋሽ ዳሪ) ።
ሰረገ፡ ወደ ውስጥ ገባ፡ ሠ...ረገ ።
ሰረገላ፡ የመንኰራኵር ጋድም፤—ሀ...
ሰረፈ (ሰሪፍ/ሰረፈ በሳ)፡ ሸረፈ/መነዘረ ። "ሰረፈ የካህናት፡ ሸረፈ የሕዝብ አማርኛ ነው"።
ሰረፋ) አንሰራፋ፡ አሰፋ/ኣንጋለለ/ዘረጋ ።
ሰሩር፡ የዐይን ግርማ ።
ሰሪ (ዎች/ሰራሒ)፡ የሰራ/የሚሰራ (ዐራሽ ቈፋሪ) ።
ሠሪታ፡ የሠራች (ዐሻሚ ቈናኝ) ።
ሰሪቴ ሻጠ፡ "ሰሪቴ በራሱ ላይ አሰረ አደረገ ሲያውቅ አበደ"።
ሰሪቴ፡ የንጨት ስም (ኹለተኛም ቀስተኒቻ ይባላል) ።
ሰራ (ሰርሐ/ደከመ)፡ ዐረሰ/ቈፈረ/ገበረ/አዘመረ/ዐጨደ/ከመረ/ወቃ ።
ሰራረቀ፡ አነሣሣ/ወሳሰደ ።
ሰራሪ፡ የሰረረ/የሚሰር (ጠቂ አውራ አለሌ) ።
ሰራራ፡ ዐራረሰ/ቈፋፈረ ።
ሰራቂ (ቆች)፡ የሰረቀ/የሚሰርቅ (ሌባ ሙጥልቅ እጀኛ) ።
ሰራን፡ ነጭና ጥቍር ፈረስ ዝንጕርጕር ጠቃጠቆ (ዘካ. ፮፡ ፫) ። በግእዝ "ኰሰኰስ" ይባላል ። ዘሩ "ሶራ" ነው፡ "ወሰራን" እይ ። "ሠራና" "ሰራን" ባማርኛ ይገጥማሉ ። (አዝማሪ)፡ "የሐመር ጌታ የዱሪ ኵሩ ነው አሉ ተከባሪ፡ እኛስ ሲገድል ያየነው የሰራን ጌታ ነው"።
ሰራኖች፡ ዝንጕርጕሮች ፈረሶች (ዘካ. ፮፡ ፮) ።
ሰራዊት፡ ዘጠኙ የስም ምትኮች እነዚሁም ርሱ/ርሷ/አንተ/አንቺ/እኔ/ርስዎ/ርሳቸው/እናንተ/እኛ ናቸው ።
ሰራዊት፡ የጭፍራ ስም (የዠግና የሐርበኛ የጦረኛ ማኅበር በያለቃውና በያበጋዙ የሚታዘዝ ብዙ ወታደር) ። ባማርኛ ደንብ ሲበዛ "ሰራዊቶች" ያሠኛል፡ በግእዝ ግን "ሰርዌ" ያንድ "ሰራዊት" የብዙ ነው። ባ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ የዘመተው
ሰራዪ፡ የሰረየ/የሚሰርይ (ቄስ) ።
ሰራዪት፡ በባላገር ይነገራል፡ "ሰራዊትናሰራዪት" ውስጠ ብዙ ነው። "አራዊትን" ተመልከት። "ሠራዊት" ተብሎ ቢጻፍ ግን ትርጓሜው ሌላ ነው ። "ሠርዌን" አስተውል ።
ሰራዪት፡ ጭፍራ፡ ሰርዌ ።
ሰራዬ፡ ያገር ስም ሠራዬ ሶርያ (በእስያ ክፍል ያለ ታችኛውና ላይኛው የአሶር የአራም አገር) ።
ሰራፊ (ፎች)፡ የሰረፈ/የሚሰርፍ (መንዛሪ - ማቴ. ፳፩፡ ፲፪፡ ፳፭፡ ፳፯) ።
ሰር፡ የሞፈር ቂጥ ድግርና ቅትርት የተዋደዱበት ።
ሰር፡ የተጠመደ በሬን ቁም ማለት ።
ሰርመዲ፡ ራስ መሸፈኛ ሠር...መዲ ።
ሰርሳሪ (ዎች)፡ የሰረሰረ/የሚሰረስር...
ሰርተት ሰርተት አለ፡ ጐተት ጐተት አለ (ሥራ ፈታ) ። (ግጥም)፡ "እንደ ተዳላት ሴት ባሏ እንደ ሞተላት ቀሚሴን አጥልቄ ልበል ሰርተት ሰርተት"።
ሰርተት፡ ጐተት፡ ሥራ ኣልባነት። "አንድ ዓመት ሰርተት አንድ ዓመት ከርተት" እንዲሉ።
ሰርናም፡ ሰርነ ረዥም ሰው ።
ሰርናቂ፡ የሰረነቀ/የሚሰረንቅ (ሰንፋጭ) ።
ሰርን (ኖች)፡ ያፍንጫ ተረተር ።
ሰርካማ፡ ያገር ስም ።
ሰርክ ምሽት፡ ዘወትር፡ ሠ...ርክ ።
ሰርዌ (ሰረወ አሸነፈ)፡ የጦር አበጋዝ (ግእዝ) ።
ሰርዲታ፡ አንዲት ሽሩባ። "ተረረ ብለኸ ተሬን" እይ ።
ሰርዶ (ዎች)፡ የሣር ስም የታወቀ ማር አንጓ ያለው። "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" አለች አህያ። "ያገሩን ሰርዶ ባገሩ ገበሬ"።
ሰርገኛ (ኞች)፡ ባለሰርግ (የወንድ ሙሽራ ተከታይ) ። (ተረት) "ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ"። "ሰርገኞች መጡ ብቅል ኣስጡ"። "ዐደመ ብለኸ ዕድመኛን" እይ።
ሰርገኛ፡ ነጭና አቦልሴ ጢፍ (ተፈጥሮው ቅይጥ ውጥንቅጥ የኾነ) ። "ሰርገኛ" መባሉ ነጩ የሙሽራውንና የሚዜዎቹን አቦልሴው የተከታዮቹን ልብስ ያሳያል ።
ሰርግ (ጎች)፡ የጋብቻ ድግስ (የሙሽራውና የሙሽራዪቱ አባትና እናት የሚደግሱት መብልና መጠጥ - ዮሐ. ፪፡ ፩, ፪፡ ራእ. ፲፱፡ ፯, ፱) ። (ተረት) "ያይጥ ሞት የድመት ሰርግ ነው"። "ሠረፃ እሠረፃ" ብለኽ "አሥርግን" ተመልከት።
ሰርግና ምላሽ፡ በጦም ምክንያት ተከታትሎ የሚደረግ ሰርግና ቤት ማያ ።
ሰርግና ምላሽ፡ ባለቤት ሳይኖር እንደ ልብ መብላት መጠጣት በሰው መሰናዶ መደሰት ።
ሰርግና፡ በመራቤቱ ክፍል ያለ አገር።
ሰርጓይ (በዓለ ሰርጕ)፡ በ፪፻ ዓ.ም የነበረ የሐበሻ ንጉሥ (ትርጓሜው "ባለ ሽልማት" ማለት ነው) ።
ሰርፍ (ዘርፍ)፡ ጌጠኛ የንጉሥ ምንጣፍ ሰፊ ባለዘርፍ ቀጪን ያልጋ ልብስ፡ በሬሳ አጐበር ላይ የሚደረግ የሐር መጐናጸፊያ ዐይነ ርግብ መሳይ (ምሳ. ፯፡ ፲፯) ።
ሰቀለ፡ ሰራ ።
ሰቀላ፡ ስቅሎሽ (የማንጠልጠል ሥራ) ።
ሰቀላ ቤት፡ አንደ ሰቀላ የተሠራ ቤት። (ተረት)፡ "የልጅ ክፉ ዲቃላ የእኸል ክፉ ባቄላ የልብስ ክፉ ነጠላ የቤት ክፉ ሰቀላ"።
ሰቀላ፡ የበላይ። "የሰቀላ ዳኛ" እንዲሉ።
ሰቀላ፡ ዳስ ግድግዳውና ጣራው ቅጠል የለበሰ የተሸፈነ (ሰርግ ማኅበር ተዝካር ማንኛውም ድግስ በውስጡ የሚበላበት) ።
ሰቀላ ድንኳን፡ በሰቀላ አምሳል የተሰፋ ድንኳን ።
ሰቀል (ሎች)፡ ዝኒ ከማሁ። "በገዳም ውስጥ ከሚኖረው መነኵሴ የሚበዛው ዶማ ሰቀል ነው"።
ሰቀልት፡ በጋይንት ክፍል ያለ አገር (ትርጓሜው "ሰቃዮች" ማለት ነው) ።
ሰቀልኛ፡ ሞላልኛ/ወገርኛ (የዳስ ዐይነት ሕንጻ ወይም ሌላ) ።
ሰቂለ ኅሊና፡ ዐሳብን ሰማያዊ ማድረግ።
ሰቂለ አዕይንት፡ በጸሎት ጊዜ ሰማይን ትክ ብሎ ማየት።
ሰቂል፡ መስቀል።
ሰቃቀለ፡ መላልሶ ሰቀለ።
ሰቃይ (ዮች)፡ የሰቀለ/የሚሰቅል (አንጠልጣይ) ። "በቀለ ብለኸ ብቅልን" እይ ።
ሰቈረ (ሰቊር/ሰቈረ)፡ በሳ/ሸነ...ቈረ ።
ሰቈቃወ ኤርምያስ፡ ስለ ኢየሩሳሌም መጥፋት የኤርምያስ ሙሾ (የመጽሐፍ ስም) ።
ሰቈቃወ ድንግል፡ የግጥም ድርሰት ዐምስት ቤት ያለው (እመቤታችን በስደቷ ጊዜ የተናገረችውን ሙሾ ያለቀሰችውን ለቅሶ አምልቶ አስፍቶ በግእዝ ቋንቋ የሚናገር) ። መሠረቱ ነገረ ማርያም ነው።
ሰቋር፡ የተበሳ/የተሸነቈረ (የዋልድባ ተራራ የከዳነ ምሕረት ገዳም) ።
ሰበሰበ፡ ለቀመ፡ አጠራቀመ፡ አከበ፡ አከማቸ፡ አንድ ላይ አደረገ፡ ከተተ (ዘፀ. ፴፭፡ ፩፡ ፪ዜና. ፴፫፡ ፯) ። "ወሰበ"ን እይ (የዚህ ሥር ነው) ።
ሰበሰበ፡ ጌታ መለሰ፡ ዐጠፈ፡ ኰረተመ፡ አሳጠረ (አኅጸረ)፡ ሰቀጠጠ፡ ሸነቀረ፡ አሳረፈ (እጅን፣ እግርን፣ ልብስን) ። (ተረት)፡ "ሰርቆ ከማሰብ እጅን መሰብሰብ" (ማሳረፍ) ።
ሰበሰብ/ስብሳብ (ቦች)፡ በቤት ዙሪያና በራፍ በኩል ብቻ ከጣራ በታች ያለ ስፍራ (እንግዳ ወይም ዕቃ ተሰብስቦ የሚቀመጥበት)፡ በአኹኑ ዘመን "በረንዳ" ይባላል (ይኸውም የህንድ ቋንቋ ነው ይላሉ) ።
ሰበረ፡ (ሰቢር፡ ሰበረ) (ዮሐ. ፲፱፡ ፴፩-፴፫)፡ አነቀሽ፡ አነከተ፡ ቀለጠመ፡ ሸረፈ፡ አደቀቀ፡ ሠነጠቀ፡ ለበጠ። (ተረት)፡ "ዘመን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል"። "ጠገበ"ን እይ።
ሰበረ፡ ላጠ፡ ለወጠ፡ ገለበጠ፡ ሻረ፡ ፍርድን።
ሰበረ፡ ሰበሰበ።
ሰበረ፡ ነደለ፡ ጣሰ፡ አፈረሰ (ዦርን) ።
ሰበረ፡ ዐጨደ፡ ቈረጠ።
ሰበረ፡ ደፋ፡ አቀረቀረ (ዐንገትን - ዘኍ. ፲፭፡ ፴፩) ።
ሰበራ፡ ቈረጣ፡ ዐዳ። "ባቄላ ሰበራ" እንዲሉ።
ሰበር (ሮች)፡ የበላይ ዳኛ በታች የተፈረደውን ፍርድ የሚለውጥ/የሚገለብጥ። "ሰበር ዳኛ" እንዲሉ። (ደኅና ሰበር)፡ መጥፎ ሰው። "ቀነበረ" ብለህ "ቀንበር"ን ተመልከት።
ሰበር፡ የስንዴና የገብስ የጤፍ አገዳ ገለባ (ባኺዶ ጊዜ የከብት እግር የሰበረው) ።
ሰበቀ ፣ (ሰቢቅ፡ ሰበቀ)፡ ወዘወዘ፡ ነቀነቀ (ጦርን) ። ጐንደሮች ግን "ጦር ሰበቀ" ሲሉ አደራ ይላሉ።
ሰበቀ፡ በጠበጠ፡ አማሰለ፡ አምታታ (የጤፍ ዶቄትንና ሊጥን በመዳፍ መታ ብዙ ጊዜ) ።
ሰበቀ፡ ነከረ፡ ዐለለ።
ሰበቀ፡ ነገር ሠራ፡ አሳጣ፡ አጣላ። "ሰበከ"ን ተመልከት።
ሰበቀ፡ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እመላለሰ እስቴን (እርጐን) ።
ሰበቀ፡ ጣለ፡ አስተኛ፡ አጋደመ፡ አያያዘ።
ሰበቀለ፡ (በቀለ)፡ ተከወነ፡ ቀለጠፈ፡ ጣፈጠ (አንደበቱ)፡ ተባበረታ።
ሰበቀለ፡ ሰበረ።
ሰበቀለ፡ ዐጪር ኾነ (ነገሩ) ።
ሰበበ፡ (ሰቢብ፡ ሰበ)፡ ምክንያት አመጣ፡ ፈጠረ፡ አመካኘ።
ሰበበኛ (ኞች)፡ የሰበብ (ባለሰበብ) ሰው፡ ሰበብ ወዳድ፡ ምክንያተኛ - ለቍጣ፣ ለስካር፣ ለጥል፣ ለመውደቅ፣ ለመታመም ጥቂት የሚበቃው።
ሰበባም፡ ሰበብ ያለው።
ሰበብ፡ ሳቢያ፡ ምክንያት።
ሰበቦች፡ ምክንያቶች።
ሰበተ (ሰብዐ)፡ ሰባት አደረገ።
ሰበተ (ትግ)፡ ረገጠ፡ እሰረ።
ሰበተ፡ ሳገ።
ሰበተ፡ አብስሎ፡ ዐረሰ፡ ገለገለ።
ሰበከ (ሰቢክ፡ ሰበከ)፡ ነገረ፡ አወራ፡ አሰማ፡ አስተማረ።
ሰበከ (ሰብሐ፡ ተሰብሐ)፡ ወገግ አለ፡ ነጋ፡ በራ፡ ወጣ፡ ታየ። "ፀሓይ ሲሰብክ ትኼዳለኽ?"
ሰበከ፡ ሰበቀ፡ አሳበቀ፡ ዋሸ። "ሰበከን ሰበቀ ማለት ከ 'ና' 'ቀ' ተወራራሽ ስለ ኾኑ ነው፡ ውስጠ ምስጢሩም ስብኮን ያሳያል።"
ሰበከት፡ ሰበቀ።
ሰበከት፡ ነገረች፡ አስተማረች (ግእዝ) ።
ሰበከት፡ የቍርበት፣ የንጀራ፣ የቅጠል፣ ያውሬ ሻካራ ዠርባ (ኢዮ. ፵፩፡ ፯) ። "ሰበከት" ማለት ግልጥነትን ያሳያል። ወዝን፣ እንቧይን እይ።
ሰበካ፡ የታቦት ወይም የአቡን ግዛት (አጥቢያ ሀገረ ስብከት) ።
ሰበዘ፡ ሻጠ፡ ሸጐጠ፡ ጨመረ፡ አገባ።
ሰበዝ (ዞች)፡ ስንደዶ፡ ግራምጣ፡ የስፌት ዙር ማብዣ፡ ማሳደጊያ።
ሰበድዓት፡ እባብ ጕበና (ግእዝ) ።
ሰበድዓት፡ የጣዖት ስም፡ ታኲ (ፈረስ ጭራው እባብ፣ ላዩ ባለመርዝ ቀስት የሆነ የደግ ሰው ምስል)፡ ይኸንንም ቅዱስ ገላውዴዎስ ገደለው (አጠፋው) ይላሉ።
ሰበገናም፡ ከሲታ ደረቅ ሰው - ሰበገኑ የሚታይ።
ሰበገን፡ የጐን ዐንጥት (በግራና በቀኝ ያለ) ።
ሰበጢራ፡ ያገዳ ቅርጫት (ሠበጠር) ።
ሰባ፡ (ሰብሐ)፡ ገለጠ፡ አስረዳ።
ሰባ፡ (ሰብዐ)፡ የቁጥር ስም፡ ፸ (70) ። ሰባት ዐሥር (7 x 10) ወይም ዐሥር ጊዜ ሰባት፡ በስሳና በሰማንያ መካከል ያለ የአሥር ቤት አኃዝ። ተራ ቁጥር ሲሆን "ሰባኛ", "ሰባኛው" ይላል። ሰባትን አስተውል።
ሰባ ሊቃናት፡ ለግብጽ ንጉሥ ቶለሚ (በጥሊሞስ) ብሉያትን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የተረጎሙ ሰባ ሊቃውንት፡ ከእነሱም አንዱ ሽማግሌው ስምዖን ነበረ (ሉቃስ ፪፡ ፳፭-፴፭) ።
ሰባ አንድ፡ (፸፩)፡ ስባና አንድ። "ሰባ አንደኛ" የማዕርግ ወይም ተራ ቁጥር።
ሰባ፡ ጮማ ሆነ፡ ሠባ።
ሰባሰበ፡ ለቃቀመ፡ አግበሰበሰ።
ሰባሰገል ፣ (ሰብአ፡ ሰገል)፡ የጥንቈላ፣ የውቀት፣ የፍልስፍና ሰዎች፡ ኮከብ ቈጣሪዎች።
ሰባሪ (ሮች)፡ የሰበረ፡ የሚሰብር (ሚክ. ፪፡ ፲፫) ።
ሰባሪ (ትግ. ሰበረ)፡ ጓያ (ወገብን፣ ቋንዣን የሚያሽመደምድ) ። "ጓያ ሰባሪ" እንዲሉ።
ሰባራ ዘንግ፡ ሐሰተኛ ነገር፡ ሙግት ሰባራ ሥንጥር፡ መናኛ የቤት ዕቃ።
ሰባራ፡ የተሰበረ ዕቃ ወይም ሌላ። "ዐንተ ሰባራ!" እንዲሉ።
ሰባራነት፡ ሰባራ መሆን።
ሰባቂ፡ የሰበቀ፡ የሚሰብቅ (ነገረኛ፡ አሳሳች) ።
ሰባበረ፡ አነካከተ፡ አደቃቀቀ (፩ነገ. ፲፱፡ ፲፩፡ ፪ዜና. ፴፬፡ ፯፡ ዳን. ፮፡ ፳፬) ።
ሰባተኚት፡ ሰባተኛዪቱ ክፍል።
ሰባተኛ ቀን፡ ቅዳሜ (ዘፍ. ፪፡ ፪-፫) ።
ሰባተኛ፡ የማዕርግ ቁጥር። ሲዘረዝር "ሰባተኛው" ይላል።
ሰባቱ ቀለማት፡ ጥቍር፣ ቀይ፣ ብጫ፣ አረንጓዴ፣ ሰማያዊ፣ ነድ፣ ወርቅ ቀለሞች።
ሰባቱ ዕለታት፡ ከእሑድ እስከ ቅዳሜ ያሉ ቀኖች።
ሰባቱ ከዋክብት፡ ከፀሓይ ብርሃን የሚነሡ ኮከቦች።
ሰባቱ ፊደላት፡ ከግእዝ እስከ ሳብዕ ያሉ ፊደሎች። (ከዋክብት፣ ዕለታት፣ ፊደላት የግእዝ፡ ኮከቦች፣ ቀኖች፣ ፊደላት የአማርኛ መኾናቸውን አስተውል) ።
ሰባት (ሰብዐት)፡ የቁጥር ስም (፯) ። በስድስትና በስምንት መካከል ያለ አኃዝ።
ሰባት ቀንዶ በረሓ እንስሳ፡ ቀንድ።
ሰባት በረት፡ የከብት አንዠት።
ሰባት አደረገ (ሰብዐ)፡ እስከ ሰባት ቈጠረ፡ በሰባት ከፈለ። ሰባት ከስም አስቀድሞ እየተነገረ ቅጽል ሲኾን፡
ሰባትያ፡ ሰባት መቶ ድር።
ሰባትያ፡ ከሰባት አንድ።
ሰባትዮ፡ ሰባትነት ያለው (ውስጠ) ።
ሰባትዮሽ፡ ከሰባት አንድ የኾነ ገመድ/ፍትል ወይም ሌላ ነገር።
ሰባቶ፡ ሰባቶች። (ች ስለ ተጐረደ ሰባቶ እየተባለ ይነገራል - ብዙ) ።
ሰባኪ (ኮች)፡ የሰበከ፡ የሚሰብክ (እገር ላገር እየዞረ ባደባባይ ቆሞ የሚነግር፣ የሚያስተምር)፡ ሐዋርያ፡ መምህር፡ ነጋሪ፡ አስተማሪ (መክ. ፩፡ ፲፪፡ ኤፌ. ፬፡ ፲፩) ።
ሰባኪ፡ ሰባቂ፡ አሳባቂ፡ ውሸተኛ፡ ነቢየ ሐሰት (፩ነገ. ፲፫፡ ፲፰) ። ባላገር ግን "ሰባኺ" ይላል።
ሰባዥ፡ የሰበዘ፡ የሚሰብዝ፡ ሸጓጭ፡ ጨማሪ።
ሰባጌ፡ የቀበሌ ስም (ሰብ) ።
ሰባጌ፡ የቀበሌ ስም፡ በመራቤቴ ክፍል ያለ ገጠር። "የምድር ሰው" ወይም "የሰው ምድር"፡ ፸ ምድር ማለት ነው።
ሰብ፡ (ሰብእ)፡ ሰው፡ ባለግዕዛን። "አገረ ሰብ" (የሰው ሀገር), "እጅ ሰብ" (የሰው እጅ), "ቤተ ሰብ" (የሰው ቤት) እንዲሉ።
ሰብለ ወንጌል፡ ያጢ ልብነ ድንግልና የጻድቁ ዮሐንስ ሚስቶች ስም፡ "ይተጌ ሰብለ ወንጌል" እንዲል (ታሪ. ነገ) ። ትርጓሜውም የወንጌል እሸት ማለት ነው።
ሰብሌ (ሰብልየ)፡ የኔ ሰብል፡ እሸቴ።
ሰብሌ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ነው።
ሰብል (ሰብለ)፡ እህል፡ ዛላ (ዘለላ)፡ እሸት (የማንኛውም) ።
ሰብሳቢ (ቦች)፡ የሰበሰበ፡ የሚሰበስብ (ለቃሚ፡ አጠራቃሚ) ። "ዘመድ ሰብሳቢ" እንዲሉ።
ሰብሳቢነት፡ ለቃሚነት፡ አካቢነት።
ሰብሳቤ፡ የሰው ስም (የዘመድ/የወገን ሰብሳቢ ማለት ነው) ።
ሰብሳብ፡ ግቢ ጋብቻ (ግእዝ) ።
ሰብስብ፡ የሪያ ጥርስ ዕባጭ መተኰሻ።
ሰብስብ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ (አንቀጽ) ።
ሰብራዳ፡ ከጭቅና ጋራ ያለ ኹለት የበሬ ጐድን።
ሰብር፡ የሽቱ ስም (ውድ ከሬት የተዘጋጀ)፡ በግእዝ "ዐልው" ይባላል (ዮሐ. ፲፱፡ ፴፱) ።
ሰብቀኛ (ኞች)፡ ሰብቃም፡ ሰባቂ፡ ሰብቅ ወዳድ፡ ባለሰብቅ፡ አሾክሹኪ፡ ዦሮ ጠቢ።
ሰብቀኛነት፡ ሰብቀኛ መሆን።
ሰብቃላ፡ ዝኒ ከማሁ ለስብቅል።
ሰብቅ፡ ክፉ ነገር፡ ሹክሹክታ፡ ሐሜት (ሰውን ከሰው የሚለይ) ። "ሸውክ"ን እይ።
ሰቦች፡ ሰዎች።
ሰተረ (ሰቲር/ሰተረ)፡ ዘረጋ/እሰጣ ለፀሓይ ሰጠ ።
ሰተተ (ሰቲት/ሰተ)፡ ለጥ ቀጥ አለ፡ ሰፊ ኾነ ተዘረጋ ።
ሰተታ፡ (ትግ)፡ ሰፌድ ።
ሰተት አለ፡ ቀጥታ ኾነ ሜዳው ።
ሰተት አለ፡ ዘው አለ ገባ (ንገሩልኝ ሳይል ከልካይ አዋኪ ሳይኖርበት) ።
ሰተት አለ፡ ዟ ዝርግት አለ (ሞተ) ።
ሰተቶ፡ ድርቄ ሰገባ ።
ሰተፈ (ሳትፎ/ሳተፈ)፡ ላተ ኳስን ጥንግን ሳይቀልብ ሳይመታ ቀረ፡ ቸኰለ ተጣደፈ (ጐዣም) ።
ሰቲት፡ ያገር ስም (በትግሬ ውስጥ በሐባብ አጠገብ ያለ ቈላ በረሓ ሜዳነት ያለው) ። በሺዋም በብዙ ስፍራ ይገኛል ።
ሰታሪ (ሮች)፡ የሰተረ/የሚሰትር (ዘርጊ አስጪ) ።
ሰታታ፡ ዝቅታ ከፍታ የሌለው እውላላ ሜዳ መለሎ ዕንጨት ።
ሰታቴ፡ ውስጡ እንደ ሰፌድ ዝርግ የኾነ ትልቅና ሰፊ ድስት በግ ፈጅ ። ዳግ...
ሰት፡ ቀጤማ (ግእዝ) ። መስቴ (ዎች)፡ ታናሽ ጥዋ እንደ ቅል ዐንገት ያላት የመጠጥ ማስቀመጫና መ፵ ። "ቻችንና ቡዪትን" ተመልከት ።
ሰቸ (ሰትየ)፡ ጠጣ/ዥው አደረገ ። "ሰቸ ካማራ ይልቅ በጕራጌ ይነገራል"።
ሰች (ሰታዪ)፡ የጠጣ/የሚጠጣ (ጠጪ - ደመ ሰች እንዲሉ) ።
ሰነመኪ፡ የታናሽ ዕንወት ስም (ቅጠሉ የሽቱ ቅመም ይኾናል፡ በጠጡትም ጊዜ ያስቀምጣል - ዘፀ. ፳፡ ፳፬፡ ሕዝ. ፳፯፡ ፲፱) ። ሰነኘ (ሰኒን/ሰነ)፡ ገጠመ/ደረደረ፡ ቤት መታ።
ሰነሰለ (ሰንሰለ)፡ አጠጋጋ/አያያዘ/አቀጣጠለ/አቈራኘ/አጠላለፈ ።
ሰነሰነ (ሰነነ)፡ ሰለሰለ/ሸነሸነ/ተነ...ተነ/ነጠለ/አበዛ ።
ሰነቀረ (ደነቀረ)፡ ሻጠ/ሰካ/ወጋ/ጋረጠ/አገባ ። "ሸነቀረን" እይ።
ሰነቀረ፡ አንድ ነገር ነገረ አሰማ።
ሰነቃ (ሰንቀወ)፡ ጠረበ/ዐነጠ/ላገ/አለዘበ (ሳንቃን) ።
ሰነቃ፡ መታ/ከረከረ/ገረፈ (ማሲንቆን) ።
ሰነበ (ትግ.)፡ ቀረቀረ/ወረወረ/ሸጐረ ።
ሰነበረ፡ ሰንበር ኾነ/ተጋደመ (በገላ/በቈዳ/በብራና ላይ) ።
ሰነበተ (ሰንበተ - በዓል ኾነ/ከበረ)፡ ባንድ ስፍራ ሰባት ቀን ተቀመጠ ቈየ ።
ሰነበተ፡ ሰነገ ።
ሰነበተ፡ ብዙ ዘመን ኖረ/ነበረ (አረጀ/አፈጀ/ዕድሜው በዛ/ፈደፈደ - መዝ. ፺፡ ፲፬ ሺ ፩፻፰ ሳምንት ከረመ) ። (ተረት)፡ "ከሰነበቱ ቍላን እንቅፋት ይመታዋል"።
ሰነበተ፡ አለ/ኾነ። "እንዴት ሰነበትክ" "ደኅና ሰንብት" እንዲሉ።
ሰነበገ (ሰነገ)፡ በኀይል ገረፈ/ሰበከተ ።
ሰነበጠ፡ ሠነጠረ—ሠነበጠ ።
ሰነባ፡ ሳንባ መሰለ ።
ሰነባበተ፡ ፩ ሰንበት ፪ ሰንበት ቈያየ ።
ሰነተረ፡ በጣ፡ ሠነተረ ።
ሰነከለ (ሰከለ)፡ እግርን መታ/ጐዳ፡ የበሬን ስንድድ ቈረጠ፡ የባሪያን ሥር በጠሰ።
ሰነኰረ፡ ዘነኰረ ።
ሰነዘረ (ሰዚር/ሰዘረ)፡ በስንዝር ለካ/መጠነ ።
ሰነዘረ፡ ሠነተረ/ሠነጠቀ/በጣ (የታረደ ከብትን) ።
ሰነዘረ፡ በትርን ወደ ሰው ቃጣ (ሳይንጠራራ በቅርብ ማለት ነው - "ነዘረን" ተመልከት) ።
ሰነደቀ፡ አጓዘ/ኣቋፈ።
ሰነደቀ፡ ከበበ ክብ አደረገ፡ ኳስ/ሎሚ ኣስመሰለ ከላይ።
ሰነደበ (ሰደበ)፡ መታ ።
ሰነደደ፡ ሰካ/ደረደረ ("ሰመግን ጨሌን" የስንደዶ ጌጥ አበጀ) ።
ሰነደደ፡ ሥራን አቀና/አቅንቶ ሠራ።
ሰነዳ) (ትግ. ሰንደወ - ወረወረ)፡ ተሰናዳ፡ ተዘጋጀ/ተደራጀ (፩ሳሙ. ፲፯፡ ፪) ።
ሰነድ (ዶች)፡ ስለ ገንዘብና ስለ ውል ስለ ጠመንዣ ስለ ማንኛውም ዕቃ የማን መኾኑን የሚመሰክር ጽፈት ሰንጠረዥ ።
ሰነገ (ሰነጐ)፡ በሳ ነደለ/ሸነቈረ አፍንጫን፡ አገባ/ሻጠ/ቀረቀረ ላባን/ሽቦን።
ሰነገ፡ አስጨነቀ/አስጠበበ።
ሰነገ፡ ጠመጠመ/አጥብቆ አሰረ።
ሰነገለ (ዐረ. ሰሕገለ)፡ ፈገፈገ/ወለወለ/ጠረገ/አጠራ/አብለጨለጨ/ሳለ/አሰላ (ጦርን/ሰይፍን - ኤር. ፵፮፡ ፬) ።
ሰነገለ፡ ሰነደደ ።
ሰነገጩ፡ ነቀነቀ/ዘከዘከ/አደናቀፈ።
ሰነጋ (ትግ. ሰንገወ)፡ አኰላሸ/ኣወጣ/ጐነደለ (የፈረስ/የበቅሎ/የዶሮ ቍላን)፡ ወቀጠ/ቀጠቀጠ/አስሮ ገደለ (የወይፈንን)፡ ሠነጠቀ/ኣፈሰሰ (የበርበሬ ፍሬን)፡ የሰው ሲኾን ዐሸ/ሰለበ ያሰኛል ።
ሰነጋ፡ ሰነገ ።
ሰነጠ (ሰነጸ)፡ አሳመረ/አስጌጠ/መልክ ሰጠ/ነቀሰ/ፋቀ/አለዘበ።
ሰነጠ፡ ሰነከለ ።
ሰነጠረ፡ ሠነበጠ፡ ሠነጠረ።
ሰነጠቀ፡ ከፈለ ሠነጠቀ።
ሰነፈ፡ ሰነቃ ።
ሰነፈ፡ ሥራን ተወ ወይም ጠላ/ከተ/ደከመ (ሐሞቱ ዳውላ አከለ፡ ቦዘነ) ።
ሰነፈ፡ ሥራን ተወ ወይም ጠላ/ከተ/ደከመ (ሐሞቱ ዳውላ አከለ፡ ቦዘነ) ።
ሰነፈጠ፡ ሰረነቀ/ሰረሰረ/ፈጀ/ለበለበ/አቃጠለ (አፍንጫን) ።
ሰነፍ (ፎች)፡ የሰነፈ/የሚሰንፍ (ሥራ ል...ሰው ተቀምጦ የሚውል) ። "ሰነፍ ባል ያበዛል" እንዲሉ። "ሰነፍ ለባለአእምሮ ይገዛል" (ምሳ. ፲፩፡ ፳፱፡ ፳፮፡ ፯, ፲፱) ።
ሰነፍ ምርት፡ ላይዳ ያልተባለ።
ሰነፍ ሴት፡ ረኸጥ ።
ሰነፍ ቈሎ፡ ሲቈሉት በቶሎ የሚፈካ ለጥርስ የሚገራ ገብስ ።
ሰነፍ ዕርቅ፡ እንዳይፈርስ ማሰሪያ ውል ማገጃ ያልተበጀለት ዕርቅ (የጊዜ) ።
ሰናሰነ፡ ተናተነ/ነጣጠለ። (ግጥም)፡ "አቶ ይነሡልኸ በሰላ መጥረቢያ በዚያች በጥልቆ ቢሰናስኑት አነስ አነስ ያለው በወጣው ስምንት። ያንተን ቂጥ የሚያኸል በነበረኝ ምድር እጅጋየኹ ትሙት፡ አለጠጅ አላድር" (ቍንጪ) ትግሬ ግን "ሰንሰነ" ብሎ ከሳ ይላል፡ ከሰለሰለ ጋራ አንድ ነው።
ሰናድር (ሮች)፡ የነፍጥ ስም (ባጤ ዮሐንስ ጊዜ የነበረ ጠመንዣ) ። በጀርመንኛ "ሽናይደር" ይባላል ።
ሰናድር ያዥ፡ ሰናድር የሚይዝ/የሚሸከም ጭፍራ ወታደር ።
ሰናጊ፡ የሰነገ/የሚሰንግ (በሺ ቀርቃሪ) ።
ሰናጋ፡ በልጥ የታሰረ ሰባራ አሞሌ።
ሰናጭ፡ የሰነጠ/የሚሰንጥ (አሳማሪ) ።
ሰናፊ፡ የሚሰንፍ (ታካች) ።
ሰናፊል (ሎች)፡ የዱሮ ዘመን ሱሪ ቦላሌ ተነፋነፍ (ዘሌ. ፯፡ ፲፡ ሕዝ. ፵፬፡ ፲፰) ።
ሰናፍጭ (ስናፔ)፡ የቅመም ስም (አፍንጫን የሚለበልብ ጕረሮን የሚያቃጥል ቅመም) ። (ተረት)፡ "የፌጦ መስሎሽ ሰናፍጭ ትቀምሽ"። ስንፈጣ/ስርነቃ/ስርሰራ/ልብለባ ።
ሰኔ፡ የወር ስም—ሠኔ ።
ሰን (መቅለድ)፡ ኵስኵስት ማንቈርቈሪያ (ከንሓስ ከመዳብ የተሠራ - ጸናኒ ማለት ነው) ።
ሰን...፡ ጠባብ የገደል ውስጥ መንገድ (እንደ ንቃቃት ያለ ቀባ እጅ የማያስገባ) ።
ሰንሰለት (ቶች)፡ የተቀጣጠለ ብዙ የብረት ቀለበት ሞላላ። ጫፍና ፵ፉ ፍንጅ አለበት፡ ይኸውም ያመፀኛ ማሰሪያ ማቈራኛ ነው (ማር. ፭፡ ፬፡ ግብ. ሐዋ. ፲፪፡ ፯) ።
ሰንሰል (ሎች)፡ ብዙ ኹኖ ተያይዞ የሚበቅል ዕንጨት ስምዛ ።
ሰንቃሪ፡ የሰነቀረ/የሚሰንቅር (ሻጭ ጋራጭ) ።
ሰንቃራ/ስንቅር፡ የተሰነቀረ/የተሻጠ/የተጋረጠ (ሥንባጭ) ።
ሰንበሌጥ (ጦች)፡ ለቤት ክዳን የሚኾን ሣር ።
ሰንበራም፡ ሰንበር ያለበት (ባለሰንበር ከብት/ሰው/ልብስ) ።
ሰንበር፡ በትር ያረፈበት ያካላት መሥ...መር ።
ሰንበር፡ የሥጋ ስም (ጠንካራ ሥጋ የጨጓራ መጋጠሚያ - "ሰንበርና ምላስ" እንዲሉ) ።
ሰንበር፡ የዋንጫ/የጠንፍ/የሕንጻ/የጋን መሥመር (ትጥቅ መሳይ ጊጥ - ፬ነገ. ፯፡ ፳፰) ። ሲበዛ "ሰንበሮች" ይላል (፩ነገ. ፯፡ ፳፱) ።
ሰንበተ አይሁድ፡ ያይሁድ ሰንበት (ቅዳሜ) ።
ሰንበተ ክርስቲያን፡ የክርስቲያን ሰንበት (እሑድ) ።
ሰንበቴ፡ የሰንበት ሰንበታዊ (በየሳምንቱ እሑድ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ የሚበላ የድኾች ምሳ) ።
ሰንበት፡ ፩ኛ ቀን አሑድ (ይኸውም ሰንበት መባሉ ሰኞን አንድ ብሎ ነው) ። በወር ውስጥ አራት ቀን ሥራ አይሠራበትም፡ ቅዳሜ ወይም እሑድ የወር መባቻ ሲኾን ግን ዐምስት ጊዜ ይከብራል። የሰንበትም ምስጢር ዕረፍትና በዓል ነው ።
ሰንበት፡ ፯ኛ ቀን ቅዳሜ (ትርጓሜው ሰባት) ።
ሰንበት አምኜ፡ የድጓ ስም (በሰንበትና በአመት በዓል የሚባል ዜማ የተጻፈበት ቅድ. ድጓ) ።
ሰንበቶች (ሰናብት)፡ በየወሩ ፬ አንዳንዴም ፩ ጊዜ የሚከብሩ የቅዳሜ ቀኖች (ዘፀ. ፴፩፡ ፲፫) ።
ሰንቡላ መሬት፡ ጠንቋይ ለአንዳንድ ሰው "ኮከብኸ ሰንቡላ መሬት ነው" ይለዋል።
ሰንቡላ፡ የኮከብ ስም (የነሐሴ ኮከብ - ሽቷም ባለሽቱ ማለት ነው) ። ሥዕሉ ሽቶ ረብራቢ ነስናሽ ይመስላል ።
ሰንባች፡ የሚሰነብት/የሚቈይ ።
ሰንተል፡ ,ሰፋ ።
ሰንተል ነጋሪት፡ ከማዕድን የተሠራ ሳንቲም፡ የብር ፪ኛ ።
ሰንተል፡ የብረት ሥራ።
ሰንና ብርት፡ ሰን የላይኛው ብርት የታችኛው (የኹለቱም ስም ዳታን ይባላል) ።
ሰንከልካላ/ስንክልክል፡ የተሰነካከለ (ወጣ ገባ ደንጐላጕል ሥርጓጕጥ) ።
ሰንካላ/ስንክል፡ የተሰነከለ (እግሩ የተመታ እንደ ልቡ መኼድ መራመድ የማይች) ።
ሰንካይ፡ የሰነከለ/የሚሰነከል (መቺ) ።
ሰንኬት፡ ታናሽ የእጅ ጣት (ዐምስተኛዪቱ) ።
ሰንኬቶ፡ የታናሽ ጣት ቀለበት (በግእዝ ገመስ ትባላለች) ። "ዲዋኒን" እይ ።
ሰንኰፋም፡ ባለሰንኰፍ ቍስል።
ሰንኰፍ፡ የዕባጭ/የብጕንጅ ጥርስ።
ሰንኳራ፡ ሰንኰርቱ ነገረ ብላሽ ዘንኳራ ።
ሰንኳራ፡ ሰንኰርቱ ነገረ ብላሽ ዘንኳራ ።
ሰንዛሪ፡ የሰነዘረ/የሚሰነዝር (ለኪ ሠንታሪ) ።
ሰንደል፡ ሰነዘረ ።
ሰንደል፡ ሣጥን (ከሰንደል የተሠራ ሣጥን ባለመዐዛ) ።
ሰንደል፡ ታቹ መርገጫው የሰንደል ሉሕ የኾነ መጫሚያ።
ሰንደል፡ የህንድ አገር ዛፍ ስም (ክልካዩ - ፍርፋሪው - በውድ የሚሼጥ የጪስ ዕንጨት) ።
ሰንደል፡ የሽቱ ስም (ቅጥነቱ እንደ ሰንበሌጥ ያለ - ሰንደልን የተቀባ ዕፅ ሲያጨሱት የሚሸት) ። "ዑድን" አስተውል ።
ሰንደቅ (ቆች)፡ ከቀንድ/ከዝኆን ጥርስ/ከብር/ከዞጲ/ከልምጭ/ከቀረጥ የተቀረጸ (በላይ ክብ እንክብል በታች ጕረሮ ያለው መቋሚያ - ፪ዜና. ፲፯፡ ፲፫) ።
ሰንደቅ፡ ...ጓዝ ።
ሰንደቅ ዐላማ (መዝ. ፳፡ ፭)፡ በሰንደቅ ላይ የተሰቀለ/የተንጠለጠለ ባለአረንጓዴና ብጫ ቀይ ቀለም የመንግሥት ምልክት ባንዲራ፡ በመካከሉ ጽሑፍና ያንበሳ ሥዕል ከዘውድ ጋራ ይታይበታል፡ አንበሳውም ሰንደቅ ዐላማ ይዟል ።
ሰንደቅ ዘንጉ/መቋሚያው፡ ከነ እንክብሉ፡ ዐላማ ሐሩ ። ርግጠኛው አጻጻፍ ግን (ዐላማ ሰንደቅ) የሰንደቅ ዐላማ ነው።
ሰንደቅ፡ የጭራ/የመንሳንስ ዕን...ወት ።
ሰንዳቂ፡ የሰነደቀ/የሚሰነድቅ (አጓዥ) ።
ሰንዳቢ፡ የሰነደበ/የሚሰነድብ (መቺ) ።
ሰንዳዳ፡ ቀጥ ያለ አፍንጫ።
ሰንዳጅ፡ የሰነደደ/የሚሰነድድ (ሰኪ ደርዳሪ) ።
ሰንዳፋ፡ በአዲስ አበባ ምሥራቅ በቅርብ ያለ ቀበሌ (ስሙን ከሣሩ ወስዳል) ። ሰንዳፋ በግእዝ መጽሐፍም ይገኛል (ታም. ማር) ። ሰነደቀ (ሰደቀ)፡ አሰረ ነዶን ። "ጠየትን" እይ።
ሰንዳፋ፡ የሣር ስም (እንደ ሰርዶ አንጓ ያለው የሜዳ ሣር ወፍራም፡ በረግረግ ወይም በውሃ ውስጥና ዳር ይበቅላል) ።
ሰንድሮስ፡ ነጭ ዕጣን (ግእዝ) ።
ሰንገጮ፡ የተሰነገጨ (ደንቃፋ ዘክዛካ) ።
ሰንጊ፡ የሰነጋ/የሚስነጋ (አኰላሺ/ጐንዳይ/ወቃጭ/ቀጥቃጭ) ።
ሰንጋ (ጎች)፡ የተስነጋ/የተኰላሸ/የተጐነደለ/የተቀጠቀጠ (ኵልሽ ጕንድል ቅጥ ቅጥ) ።
ሰንጋ ምት፡ ና ቼ ቼ ቼ የሚል የሰንጋ ፈረስ ዘፈን አዝማች።
ሰንጋ ሰንጋ፡ የሰንጋ (ሰንጋ ጮሌ ፈረስ) ። ደጊሙ ቃልም ይኾናል።
ሰንጋ ቦካ፡ በቡልጋ አፋፍ ያለ ቀበሌ ።
ሰንጋ ቦካ፡ ወፈረ/ሠባ/ደለበ (መኼድ አቃተው) ።
ሰንጋ፡ አዝማሪ "ሰንጋ ሰንጋ" እያለ ሐርበኛን የሚያመሰግንበት የማሲንቆ ምት ።
ሰንጋ፡ የተቀለበ በሬ (ድልብ ገች ፍሪዳ) ።
ሰንጋ፡ የኦሮ ባላባት ግዛት ("ዳማ ከለለኝ አባ ሰንጋ" እንዲሉ) ። "አባን ዳማን" ተመልከት።
ሰንጋ ፈረስ፡ ታፍኖ በቤት የሚውል ኦሮቢ ፈረስ (ድንጕላ ያይዶለ) ።
ሰንጋይ (ዮች)፡ የስነገለ/የሚሰነግል (ሳይ - ሕዝ. ፳፩፡ ፲፩) ።
ሰንጌ፡ የቍልምጫ ቃል ("የኔ ሰንጋ" እንደ ማለት) ።
ሰንጎ መገን፡ ሰንጎ ፈረስ መገን ጋሻ ነው። "ሰንጎ መገን ተው ሰንጎ መገን" ከፈረሰኞች የምናውቃቸው በሻኸ አቦዬ ኀይሌ አንዳርጋቸው እንዳለ አዝማሪ።
ሰንጎ፡ አስጨንቆ/አስጠብቦ።
ሰንጎ/ሰንግዮ፡ ቃለ አጋኖ ("ሰንጋ ሆይ" ማለት ነው) ።
ሰንጠረዥ (ዦች)፡ የመጫወቻ ስም (ስድስት ዐይነት ምስል ያለው መጫወቻ ምስሉም ንጉሥ/ንግሥት/ፊታውራሪ/ፈረስ/ግንብ/አሽከር ይባላል) ። ነጭና ጥቍር መደብ አለው፡ ጨዋታው የጦርነት ምሳሌ ነው ። ያወጡትም ፋርሶች ናቸው ይላሉ ።
ሰንጠረዥ፡ የቍጥር መደብ (አግድምና ቍልቍል የተሠመረ መሥመር በውስጡ አኃዝ ያለበት - ክብ ሲኾን ዐውድ ይባላል) ። ሳንኳ፡ ሰኰና/ቍርጭምጭሚት/ስን...ድድ ።
ሰንጢ (ዎች)፡ የታናሽ ቢላዋና የምላጭ ዐይነት ታጣፊ መሣሪያ ባለኹለት አፍ (ትልቁ ሥጋ መብሊያ ራስ መላ...) ።
ሰንጣ፡ አሳምሮ እንደ ልብ (፩ሳሙ. ፲፬፡ ፴) ።
ሰንጣ፡ ወለል ያለ ሜዳ የሚያምር።
ሰንፋጣ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሰንፋጭ፡ የሰነፈጠ/የሚሰነፍጥ (ሰናፍጭ/በርበሬ/ዝንጅብል የመሰለው ኹሉ) ።
ሰኘ (ሰነየ)፡ ኾለተ (ኹለት አደረገ) ።
ሰኘ)፡ አሰኘ፡ አሻ ። (ሠኘ)፡ አሠኘ ።
ሰኞ (ሰኑይ)፡ ኹለተኛ ቀን (የእሑድ ማግስት) ። "ማግሰኞን" እይ።
ሰኞን ኾነ፡ አደጋ ደረሰበት ሞተ ። ሲና፡ የተራራ ስም (ሙሴ ፲ቱን ቃላትን ከፈጣሪ የተቀበለበት ተራራ) ።
ሰአልናከ፡ የተረፈ መሥዋዕት፡ የኦኰቴት ምክትል፡ "ጠዲቅ ዳቦ" ትርጓሜው "ለንኸ" ማለት ነው። "ሰአልናከ" መባልን ከጸሎቱ ወስዷል፡ ባላገር ግን "ሳሊነክ" ይለዋል።
ሰዐወ)፡ የጊዜ ስም ።
ሰዓ፡ ሰዓት ።
ሰዓተ ሌሊት፡ ከማታ እስከ ጧት ያለ ጊዜ (፲፪ ሰዓት) ። ካህናት በቤተ ክርስቲያን እያደሩ በሰባቱ ጊዜያት የሚጸልዩት የፍታት ጸሎት፡ "ሰዓተ ሌሊት" ያሠኘው የሚዠመረው በመንፈቀ ሌሊት ስለ ኾነ ነው። "መላን" አስተውል።
ሰዓተ መዓልት፡ ከጧት እስከ ማታ ያለ ጊዜ (፲፪ ሰዓት) ። "ተሲያትን ሳትንና ሳታትን" ተመልከት ።
ሰዓቱን ሞላ)፡ ዘወረ፡ ጠመዘዘ፡ እንዲንቀሳቀስ/እንዲዞር አስተካከለ (ገቢር) ።
ሰዓት ሲበዛ ቀን፡ ቀን ሲበዛ ወር፡ ወር ሲበዛ ዓመት/ዘመን ይኾናል። "ደግ ሰዓት ክፉ ሰዓት" እንዲሉ።
ሰዓት አደረሰ፡ በ፯ቱ ጊዜያት ጸለየ፡ አቍጣሮ ያዘ አደረገ።
ሰዓት፡ የሰዓት መሣሪያ (ክብ መኪና ባለ፳፬ ክፍል - በላዩ ያለው መርፌ የላይኛው በቀን ፳፬ የታችኛው ፪ ጊዜ ይዞራል፡ የደቂቃው ቍጥር አንድ ሺ አራት መቶ አርባ፡ የካልኢቱ - ሰጏንዱ - ሰማኒያ ስድስት ሺ ካራት መቶ ነው) ።
ሰዓቶች (ሰዓታት)፡ ጊዜዎች/ዘመኖች፡ የሰዓት መሣሪያዎች።
ሰከለ፡ ዐንገትንና የኋላ እግርን ወይም የፊት እግርንና የኋላ እግርን አሰረ/ቈረኘ። ምስጢሩም የተክል ፍሬ ዐጽቅን መዝኖ ከግንድ፡ ቅርንጫፍን ከዐጽቅ እንዲያገናኝ ማለት ነው።
ሰከላ፡ በጐዣም አውራጃ ያለ አገር (አባይ የሚፈልቅበት) ።
ሰከመ፡ ተሸከመ (ግእዝ) ። "ወስከምት" ማለት ከዚህ የወጣ ነው።
ሰከም ሰከም አለ፡ ሲኼድ እንደ ተሸካሚ ፈጠን ፈጠን አለ።
ሰከሰከ (ሰገሰገ)፡ ሰረረ።
ሰከረ (ሰኪር/ሰክረ)፡ ጠነበዘ፡ አበደ፡ ራሱ ዞረ፡ ቃዠ፡ ጮኸ፡ ለፈለፈ፡ ዘለለ፡ ተንገደገደ፡ ወደቀ፡ አንዱ ኹለት ኾነበት (ከመጠጥ ብዛት የተነሣ) ።
ሰከረ)፡ ዘከረ (መሰከረን አስተውል - የዚህ መስም ግስ ነው) ።
ሰከቴ፡ የተደቀነ፡ ሠከተ።
ሰከነ (ሰኪን/ሰከነ)፡ ወደ ታች ወረደ፡ ዘቀጠ፡ ረጋ (የቡናው አተላ ሰከነ) ።
ሰከነ፡ ሱካር።
ሰከነ፡ ተዋረደ፡ ዐጣ፡ ነጣ፡ ደኸየ።
ሰከከ፡ ቀናሰገገ።
ሰኪ (ሰካዒ)፡ የሰካ/የሚሰካ (ሻጭ) ።
ሰካ (ሰክዐ)፡ ሻጠ፡ ሳገ፡ አገባ፡ ወጋ፡ በተራ አቆመ፡ ደረደረ (ጦርን፡ ዕንጨትን፡ ዶቃን፡ ዐልቦን፡ ወሌን፡ ሰመግን በክር/በሢር/በሽቦ ላይ) ።
ሰካላ፡ ገመድ/ጠፍር።
ሰካሪ/ሰካር፡ የሰከረ/የሚሰክር/የጠነበዘ (ምሳ. ፳፮፡ ፱፡ ፩ቆሮ. ፮፡ ፲፩).
ሰካይ (ዮች)፡ የሰከለ/የሚሰክል (አሳሪ) ።
ሰክ አለ፡ ተደቀነ፡ ሠከተ።
ሰኰና (ግእዝ)፡ የሰው ጫማ ውስጥ እግር፡ ኰቴ (የከብት ጥፍር)፡ መርገ፵/መኼጃ። "ገለገለ" ብለኸ "ግልገልን" እይ።
ሰኳ/ሰኵዐ)፡ "መሰኳ"ን አስተውል (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰወለለ)፡ ተንሰዋለለ፡ ተንቀዋለለ፡ ተንከዋረረ፡ ተንሰለጀጀ።
ሰወለል/ሰውላላ፡ ቀወለል/ቀውላላ - ሰልጃጃ።
ሰወረ (ሰውሮ/ሰወረ)፡ ሸፈነ፡ ጋረደ፡ ከለለ፡ ዐወረ (ዐይንን ነሣ)፡ አሳበደ (ልብን) ። ወባ ሸሸጉ፡ ደበቀ፡ ገለበጠ (የሚታየውን እንዳይታይ በስተውስጥ አደረገ) ። "ሱረትን" እይ (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰወረ፡ አረቀቀ።
ሰዋ፡ ዐረደ፡ ሠዋ።
ሰዋም፡ ሰው ያለበት/የበዛበት (ባለ ሰው ስፍራ) ።
ሰዋስው (ሶሰወ)፡ የመሰላል ስም።
ሰዋስው፡ ነጠላ ግስ ከነርባው፡ ሀርና ነባር ወይም ስምና ግብር።
ሰዋስው፡ የነገር/የቃል/የቋንቋ እገባብ ሥርዐት/ደንብ። የግእዝን ምስጢር ካለማወቅ ወደ ማወቅ መወጣ፵ ማለት ነው።
ሰዋስው ጨዋታ፡ የግእዝ ንግግር።
ሰዋስውኛ፡ የሰዋስው ጭውውት/ዘይቤ (ነገረ ደብተራ) ። "በተነ" ብለኽ "ብትንን" እይ፡ "ጥሬን" ተመልከት።
ሰዋሪ፡ የሰወረ/የሚሰውር (ሸፋኝ ከላይ ደባቂ) ።
ሰዋራ፡ ደባቃ ስፍራ።
ሰዋወረ፡ ደባበተ።
ሰዋውሮ፡ ደባብቆ።
ሰው (ሶሰወ)፡ ኣዳም (ያዳም ልጅ)፡ የፈጣሪ ምሳሌ (ነባቢ፡ ለባዊ፡ ሕያው)፡ በሥጋው ከእንስሳት በነፍሱ ከመላእክት አንድነት ያለው ፍጥረት (ባለግዕዛን) ። "ምናልባት ሰው ለመኾን ቢያበቃኝ ውለታኽን እከፍላለኹ።" ሰው ማለት በሔዋን ኣንጻር ለሴትም ይነገራል። "አንቺ ሰው!" እንዲል ባላገር። (ተረት)፡ "ለሰው ሞት ኣነሰው።"
ሰው መሳይ፡ ሰውን የሚመስል (ዝንጀሮ፡ ጦጣ፡ ጕሬዛ፡ ዓሣ - ስሬን) ።
ሰው መሳይ በሸንጎ፡ ወስላታ/ምንቴ ነውረኛ።
ሰው ሠራሽ፡ ግብር እምግብር (ሰው የሠራው ሥራ የእግዚአብሔር አይዶለም) ።
ሰው ሰውኛውን ኖረ፡ እንደ ሰው ከሰው ጋራ ፍጹም ሰው ኹኖ (እየበላ፡ እየጠጣ ማለት ነው) ።
ሰው በላ፡ ሰውን የሚበላ ጭራቅ/አውሬ።
ሰው በሩቁ፡ የውሻ ስም።
ሰው ኾነ (ተሰብአ)፡ ነፍስና ሥጋ ያለው ኾነ፡ ተዋሐደ፡ የሰውን ባሕርይ ነሣ።
ሰው የመታ)፡ ለዳኛ የሚከፍለው/የምትከፍለው ገንዘብ ። ዱሮ አንድ አሞሌ ነበር፡ ከ1934 ዓ. ም. ወዲህ ግን ዐምስት ብር ነው ።
ሰው፡ ጌታ፡ ጨዋ፡ ባላባት፡ ክቡር፡ ባለማዕርግ (መዝ. ፵፱፡ ፳). "ጊዜ ነው እንጂ ቁም ነገራም የሰው ልጅነት አያኰራም" - (አዝማሪ) ።
ሰው ጤፉ፡ ሰውን የሚንቅ/የሚያኰስስ (ከጤፍ የሚቈጥር) ።
ሰውማ፡ ሰው መሳይ።
ሰውር (ተውር/ሶር)፡ በሬ።
ሰውር መሬት፡ ጠንቋይ (ለአንዳንድ አስጠንቋይ "ኮከብኽ ሰውር መሬት ነው" ይለዋል።)
ሰውነተ ቢስ፡ የነገሩትን የሚረሳ ዝንጉ።
ሰውነቱን፡ ለወጠ)፡ ዐመሉን፡ አከፋ፡ ፊቱን፡ አጠቈረ፡ ("፩ነገ. ፳፪፡ ፬ ።ኤር. ፶፪፡ ፴፫") ።
ሰውነት፡ ሰው መኾን፡ የነፍስ ባሕርይ፡ አካል/ገላ (ሉቃ. ፲፪፡ ፲፱). "ዛሬ በመንገድ ውዬ ሰውነቴ ልትት ብሏል።" በዘመናችን ግን የውሻው/የፈረሱ/የመኪናው ሰውነት እየተባለ በስሕተት ይጻፋል።
ሰውኛ፡ የሰው ጠባይ/ባሕርይ።
ሰውየው፡ በሰውዬ አንጻር የርሱ ሰው ማለት ነው።
ሰውዬ፡ የኔ ሰው።
ሰውዮ (ኦ ብእሲ)፡ ሰው ሆይ! ("ዮ" በጥሪ ጊዜ ማግነንንና ማክበርን ያሳያል) ።
ሰዉ፡ ዋቢ፡ ኀላፊ። "ሰጪኽን አምጣ" እንዲሉ።
ሰየ፡ ጐመዠ፤፡ ሠየ።
ሰየመ (ሰመየ)፡ ስም ለሌለው ስም አወጣ (ስለ ልጅ የተወለደና ክርስትና የተነሣ ለት) ። "ሠየመን" እይ።
ሰየፈ (ሰይፎ/ሰየፈ)፡ በሰይፍ መታ፡ ቀላ፡ ቀነጠሰ፡ ቈረጠ፡ ጐመደ፡ ጐረደ፡ ከለለ፡ ገደለ።
ሰያሚ፡ የሰየመ/የሚሰይም (የሰየመች/የምትሰይም)፡ ስም አውጪ (አባትና እናት፡ ቄስ፡ ሴት ዐማት) ።
ሰያሚነት፡ ሰያሚ መሆን።
ሰያፊ፡ የሰየፈ/የሚሰይፍ (ቈራጭ ባለ ወግ) ።
ሰያፍ፡ ዝኒ ከማሁ።
ሰይጣናም (ሞች)፡ ሰይጣን ያለበት/ያደረበት (ባለሰይጣን፡ ክፉ ሰው፡ እባብ) ።
ሰይጣን/ሴጣን፡ ዲያብሎስ (ክፉ መንፈስ፡ ጋኔን፡ የእግዚአብሔርና የአዳም መዠመሪያና መፍረሻ ጠላት/ባለጋራ) ። ሲበዛ "ሰይጣኖች/ሴጣኖች" ይላል። "ጋንጩርን" አስተውል።
ሰይጣንነት፡ ሰይጣን መሆን (ክፉነት/ስይጣኔ/ዝኒ ከማሁ/ተንኰለኛነት) ።
ሰይፈ ሥላሴ፡ የመጽሐፍ ስም (ምስጢር ያላገመረ ካህን በግእዝ ቋንቋ የደረሰው ነው) ። ይኸንንም የመሰለ ከወንጌል የማይ ሰማማ ፈጠራ ድርሰት አርድእት ነው። (ተረት)፡ "የልጅ ጥፉ በስም ይደግፉ።"
ሰይፈ አርዓድ (አርዓዴ ሰይፍ)፡ በ፲፱፻ ዓ.ም. የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ (በሰይፍ አንቀጥቃጭ ማለት ነው) ።
ሰይፈ ዣግሬ (ዣግሬ ሰይፍ)፡ የንጉሥ/የመስፍን/የመኰንን ሰይፍ ያዥ/ተሸካሚ (፩ሳሙ. ፴፩፡ ፬) ። ዳግመኛም "ዣግሬ" (ዘእግር ዘአጋር) ማለት ነው። ሦስተኛም አግሬን ያሳያል። አራተኛም ሰይፍንና ዘገርንም ያስተርጕማል። "ጋሻን"ና "ዣግሬን" እይ።
ሰይፈ ዣግሬዎች፡ ብዙዎች (ሰይፍ ተሸካሞች/የሰይፈ ዣግሬ ጭፍሮች) ።
ሰይፈኛ (ኞች)፡ ሰይፍ ታጣቂ (ሰይፍ መዛዥ) ።
ሰይፉ/ሴፉ፡ የሰው ስም።
ሰይፋም፡ ባለሰይፍ ማለት ነው።
ሰይፋይ፡ በዘመነ ብለይ የነበረ የኢትዮጵያ ንጉሥ።
ሰይፍ፡ ፬ ጣት በሽቻ መቀስ የሚረዝም።
ሰይፍ/ሴፍ፡ የጦር መሣሪያ ስም (ይኸውም በ፪ ወገን ስለት ያለው፡ በወገብ የሚታሰር፡ በትከሻ የሚንጠለጠል ነው) ። "ጐራዴን"ና "ሾተልን" "ሐኔን" "ዱቢትን" አስተውል። (የራስጌ ሰይፍ)፡ ዐልጋ ላይ በከዳ ውስጥ የሚቀመጥ። በግእዝ "መተርእስት" ይባላል።
ሰደሰ፡ ስድስት አደረገ (ግእዝ) ።
ሰደረ (ትግ. ሰነዘረ)፡ ወለደ፡ ደረደረ፡ ረደፈ፡ መደደ፡ ኰሰኰለ፡ በተራ አስቀመጠ፡ አቆመ።
ሰደረ, ደረደረ፡ ተራ ሰጠ - ሰደረ, ደረደረ፡ ተራ አመጣ። ረደፈ (ዐረ), ደረበ - ረደፈ (ዐረብኛ), ደረደረ።
ሰደቀ፡ አብዝቶ ቀባ፡ ደለሰ፡ እፊማለቀ (ዐማርኛ) ። "ሰነደቀ"ን እይ (የዚህ ጣልቃ ነው) ።
ሰደቀ፡ ገበታ ዘረጋ (ግእዝ) ።
ሰደቃ እግሪ ረዥም፡ ስፌት (የንጀራ ማቅረቢያና መብሊያ) ። በአረብኛ ግን "ጸደቃ" ለድኆች የሚያበሉት፡ "ጠዲቅ" ስለ ጽድቅ የሚሰጡት ገንዘብ ወይም ሌላ ምጽዋት ተብሎ ይተረጐማል።
ሰደቃ፡ ከሳንቃ የተበጀ ገበታ (ዘፀ. ፳፭፡ ፳፫፡ ዮሐ. ፪፡ ፲፭).
ሰደደ)፡ ወሰወሰ/ሸከሸከ ።
ሰደድ፡ ቋያ (የዱር/የበረሓ ሣር) ። "የሰደድ እሳት" እንዲሉ። ዳግመኛም ዕንጨት ለዕንጨት ተፋጭቶ የሰደደው እሳት ማለትን ያሳያል።
ሰደፍ፡ የባሕር እንስሳ (ዕንቍን/ሎልን የምትወልድ - ግእዝ) ። ሲበዛ "ሰደፎች" ይላል። "ብርጋና"ን ተመልከት።
ሰደፍ፡ የጠመንጃ ላት። "ሰደፍ ዕንቀንን በሆዷ እንደምታቅፍ ይህም ጠመንጃን በስተታች በኩል በውስጡ መያዙን ያሳያል።"
ሰዱቃውያን፡ ተመጻዳቆች።
ሰዳ፡ ባዶ።
ሰዳ፡ ዐጥር/ቅጥር የሌለበት ባዶ ስፍራ።
ሰዳሪ፡ የሰደረ/የሚሰድር (ደርዳሪ፡ ኰልኳይ) ።
ሰዳሽ፡ የሰደሰ/የሚሰድስ።
ሰዳቢ፡ የሰደበ/የሚሰድብ (አዋራጅ) ።
ሰዳቢዎች/ሰዳቦች፡ የሰደቡ/የሚሰድቡ (፩ጢሞ. ፫፡ ፲፩).
ሰዳጅ (ጆች)፡ የሰደደ/የሚሰድ (ላኪ፡ ፈቺ፡ ለቃቂ፡ አንከባላይ) ።
ሰዴቻ (ኦሮ)፡ መንቀጥቀጥ፡ መንዘፍዘፍ።
ሰዴቻ መታው፡ አንቀጠቀጠው፡ አንዘፈዘፈው ።
ሰድቦ ለሰዳቢ ሰጠ፡ መተረቻ አደረገ።
ሰድቦ፡ ነቅፎ፡ ዘልፎ።
ሰዶም (ሎጣዊ/ሰዶማዊ)፡ ግብረሰዶም የሚያደርግ የሎጥ አገር ሰው።
ሰዶም፡ በእስያ ውስጥ በዮርዳኖስ ማዶ ያለ አገር (የገሞራ ጎረቤት) ። "ሰዶምና ገሞራ" እንዲሉ። ትርጓሜውም (ሲድ) ኖራ የሚወጣበት ማለት ነው ይላሉ (ኪ. ወ. ክ).
ሰገለ ቢስ፡ ዕውቀተ መጥፎ ፀባይ ጠንቋይ።
ሰገለበ (ሰበ)፡ ቸኰለ፡ ተስገበገበ፡ ተንገበገበ፡ ሰለፈ (በምግብ ጊዜ) ።
ሰገሌ፡ የቀበሌ ስም (ካንጎለላ በላይ ያለ ሜዳ)፡ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. የርስ በርስ ጦርነት የተደረገበት።
ሰገል፡ ጥንቈላ፡ ዕውቀት (ግእዝ) ።
ሰገሰገ፡ ሰበሰበ፡ አጠጋጋ፡ አቀራረበ፡ አጠበበ (ጥለትን ማግን፡ ቍቲትን ለመቋጨት) ።
ሰገሰገ፡ ጠቀጠቀ፡ አብዝቶ በላ (እሆድ አገባ/ዐጨቀ) ።
ሰገረ ስናርኛ ኼደ፡ ሠገረ።
ሰገበ፡ (ዘገበ)፡ ሰገባ አበጀ፡ ሰፋ (ገቢር) ።
ሰገበ፡ ሰለፈ፡ ተደቀነ (ተገብሮ) ። "ገበገበ"ን እይ።
ሰገባ (ቦች)፡ የሰይፍ ቤት፡ የጐራዴ መክተቻ። "አፎት"ንና "ድርቅ"ን ተመልከት።
ሰገብጋባ/ስግብግብ (ቦች)፡ የተስገበገበ፡ ችኵል፡ ጥዱፍ፡ ቀቀበታም፡ ሰላፍ።
ሰገነት፡ ሰማይ፡ ገነት (በቁሙ የቤት ላይ ቤት/ደርብ)፡ ዕንቍላል ግንብ (ዘዳ. ፳፪፡ ፰፡ ዳን. ፬፡ ፳፱) ። ገነት ያረገንና ያበ ባን መኖር ያስረዳል።
ሰገደ፡ (ሰጊድ፡ ሰገደ)፡ አጐነበሰ፡ ተንበረከከ (በኹለት ጕልበቱና በኹለት እጁ ምድርን ተመረኰዘ)፡ ተደፋ (በግንባሩ መሬት ነካ)፡ ወደቀ፡ ተነሣ።
ሰገደደ፡ መለሰ፡ ሰበሰበ፡ ደበቀ፡ ከለለ፡ ሰወረ። የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱንም "ይሰግድድ/ይሰገድዳል" ይላል።
ሰገዳ/ስግዶሽ፡ የመስገድ ኹኔታ።
ሰገድ (ዶች)፡ የዕንጨት ስም (የታወቀ ዛፍ) ። "ወይራና ሰገድ" እንዲሉ።
ሰገድ፡ በወግዳ ክፍል ያለ አገር (ሰገድ የበቀለበት/ያለበት ማለት ነው) ። "ሰገድ ያኸላል፡ ረዥም ነው።"
ሰገገ (ትግ)፡ ፊት ነሣ፡ አበረረ፡ ኣባረረ (፩ሳሙ. ፳፭፡ ፲፬).
ሰገጥ፡ የቅል/የካባ ስፌት፡ ቅምቅማት፡ ዝምዝማት።
ሰጕድ፡ የንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ ፈረስ ስም። "አባ ሰጕድ ወልዴ" እንዳለ አዝማሪ።
ሰጊድ፡ መስገድ (ግእዝ) ።
ሰጋ፡ ባባ፡ ሠጋ።
ሰጋለብ/ሰግላባ፡ ችኩል፡ ጥዱፍ፡ ስግብግብ፡ ሰላፍ።
ሰጋጅ (ሰጋዲ)፡ የሰገደ/የሚሰግድ።
ሰጋገደ፡ መላልሶ ሰገደ።
ሰጋጊ፡ የሰገገ/የሚሰግ (ዐንገቱን አቅንቶ የሚሠግር) ። "ሰጋጊ በቅሎ" እንዲሉ።
ሰጋጭ፡ የሰገጠ/የሚሰግጥ (ሰፊ፡ ቀምቃሚ፡ ዘምዛሚ) ።
ሰግ፡ ሰጐጥ።
ሰግሳጊ፡ የሰገሰገ/የሚሰገስግ (ሰብሳቢ፡ አቀራራቢ፡ አጥባቢ፡ ዐጝቂ) ።
ሰግደድ አለ፡ ተሰገደደ። "ከታዳጊ ጌታ ሰግደድ ያለ ቦታ" እንዲሉ።
ሰግደድ አደረገ፡ ሰገደደ።
ሰግዳዳ/ስግድድ፡ የተሰገደደ፡ ሰዋራ፡ ድብቅ ስፍራ፡ ገለልታ።
ሰግዳጅ፡ የሰገደደ/የሚሰገድድ (መለሽ፡ ሰብሳቢ፡ ደባቂ) ።
ሰጐኑ፡ ያ ሰጐን፡ የርሱ ሰጐን።
ሰጐን (ሰገኖ)፡ ዐንገቱና ቅልጥሙ የረዘመ ኣሞራ። ክንፎቹን ዘርግቶ በእግሮቹ ይሽከረከራል እንጂ እንደ ሌላው በአየር አይበርም፡ ተመሥጦ የለውም። ሲበዛ ሰጐኖች ያሠኛል። ተባቱንና እንስቱን ለመለየት፡
ሰጎንድ፡ ካልኢት ፷ ቅጽበት።
ሰጐኗ (ሰጐኒቱ)፡ ያች ሰጐን።
ሰጐኗ፡ የርሷ ሰጐን።
ሰጐደ (ትግ)፡ ዕመቀ፡ ጠቀጠቀ።
ሰጐደ (ደጐጸ)፡ ዐጠፈ፡ ቀነፈ፡ አጐደጐደ፡ ጋሻ አበጀ፡ ደጐሰ፡ ጐበጐበ፡ ሸለመ፡ አስጊጠ። "ሠረጐደ"ን እይ። (ደጐሰ ከቀኝ ወደ ግራ ሲነበብ ሰጐዴ ይኾናል) ።
ሰጐደ፡ ሰገለበ።
ሰጐደ፡ በሉ መታ።
ሰጐጥ (ጦች)፡ ሰግ (በመሬት ላይ ተተክሎ የማይነቃነቅ ደንጊያ)፡ የምድር ስገጥ።
ሰጓጅ (ጆች)፡ የሰጐደ/የሚሰጕድ (ዐጣፊ፡ ቀናፊ፡ አጐድጓጅ፡ ጐብጓቢ፡ ደጓሽ፡ ሸላሚ) ። "ጋሻ ሰጓጅ" እንዲሉ።
ሰጠ (ሰጠወ) (ሉቃ. ፯፡ ፳፩)፡ አቀበለ፡ አስረከበ፡ ዐደለ፡ ቸረ፡ ለገሰ። (ተረት)፡ "የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሣ፡ ካልሰጡ ኣይዕደቡም።" "፩ ወንድ ለዘጠኝ ያውም እግዜር ሰጠኝ።"
ሰጠረ፡ አረቀቀ፡ ሰወረ። "ምስጢርን" እይ (የዚህ ዘር ነው) ።
ሰጠጠ፡ ቀደደ፡ ሠጠጠ።
ሰጣ፡ መዘርጊያ።
ሰጣ/ሰጥሐ)፡ አሰጣ (ኣስጥሐ)፡ ዘረጋ፡ ዘረረ፡ ሰተረ፡ በተነ (ለፀሓይ ሰጠ) ። (ተረት)፡ "ሰርገኞች መጡ ብቅልእስጡ።" (ድዱን አሰጣ)፡ ሣቀ፡ ገለፈጠ (ኣድራጊ) ።
ሰጣሚ፡ የሚሰጥም (ጠላቂ) ።
ሰጥ ለመጥ አለ፡ ርግት ለጥ እለተ ለመጠ ተኛ ዠርባውን ኣስመቸ።
ሰጥ አለ፡ ጸጥ አለ፡ ረጋ፡ ተገዛ።
ሰጥ፡ ጸጥ።
ሰጥር፡ ቀጪን የጐድን ዐጥንት —ሠጥር።
ሰጥቶ፡ ዕንካ ብሎ አስረክቦ።
ሰጥቶ ይለምን፡ ቸር/ደግ የዋህ ሰው (ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ - ዮሐ. ፬፡ ፯, ፲).
ሰጪታ፡ የምትሰጥ (ዘራፍ ሴት) ።
ሰፈሰፈ (ሰፈፈ)፡ ቀረበ/ተሰለፈ ።
ሰፈረ (ሰፊር/ሰፈረ)፡ (ገቢር)፡ ለካ/መጠነ (ምድርን/አኸልን/ውሃን/ቅቤን/ማርን ማንኛውንም ነገር ኹሉ - ሕዝ. ፵፡ ፳, ፳፫) ።
ሰፈረ (ተገብሮ)፡ ዐረፈ/ተቀመጠ (ጭፍራው/ንቡ)፡ ተሰቀለ (ዶሮው/ወፉ - ፪ዜና. ፴፪፡ ፩፡ ማቴ. ፲፫፡ ፴፪) ።
ሰፈረ፡ ሰፈሰፈ ።
ሰፈረተኛ (ኞች)፡ ሰፈር ያለው ባለሰፈር በሰፈር ያለ የተቀመጠ የሰፈር ሰው ።
ሰፈራ/ስፍሮሽ፡ የመስፈር ሥራ ምጠና ።
ሰፈር (ሮች)፡ የጦር ሰራዊት ድንኳን ተክሎ ዳስ ጥሎ የሚያድርበትና የሚ...
ሰፈነ (ሰፊን/ሰፈነ)፡ ተሾመ/ገዛ/ሠለጠነ (የበላይ ኾነ) ።
ሰፈፈ (ሰፊፍ/ሰፈፈ)፡ በላይ ኾነ/ተዘረጋ/ረበበ (ዘፍ. ፩፡ ፪) ። ተንካፈፈ/ተንኳፈፈ/ዋኘ (አሞራው መርከቡ) ። "ጠለለን" እይ።
ሰፈፍ አለ፡ ሰፈፈ (፪ነገ. ፮፡ ፮) ።
ሰፈፍ የለሽ፡ የሴት ስም ("እንከን ነውር ነቀፋ እድፍ ጕድፍ የለሽ" ማለት ነው) ።
ሰፈፍ፡ የጠጅ ገፈት ወይም ግፋፊደረቅ የማር እንጀራ ድቃቂ ከሠም የተደባለቀ፡ ዐዲስ ሸክላ ማማሻ። "ፋጕሎን" አስተውል ።
ሰፊ (ሰፋዪ)፡ የሰፋ ፥ የሚሰፋ፡ ጠቃሚ/ዘምዛሚ ። "ልብስ በርኖስ መጝሚያ ጠፍር መኪና ሰፊ" እንዲሉ። ሲበዛ "ሰፊዎች" ይላል።
ሰፊ (ስፉሕ)፡ የሰፋ/የተንቦረቀቀ (ቦርቃቃ ቦላሌ) ። "ሰፊ ቤት ሰፊ ሱሪ ሰፊ መንገድ" እንዲሉ። "እጅን ገበረ ብለኸ ግብርን ሆድን ልብን" እይ።
ሰፊ ሜዳ፡ በባቢሎን አገር በሰናዖር ምድር የሚገኝ ሜዳ የተንጣለለ (ዘፍ. ፲፩፡ ፪) ። "ወገደ ብለኸ ወግዳን" አስተውል ።
ሰፊ ሰፈር፡ የድንኳን/የልብስ/የኮርቻ ሰፊ ቦታ ።
ሰፊ ኾነ፡ ሰፋ አልጠበበም።
ሰፊታ (ሰፋዪት)፡ የመሶብንና የሌላውንም ስፌት የምታውቅ የምታፈጥን በቶሎ የምትቈርጥ ሴት ።
ሰፊነት፡ ሰፊ መኾን (ጠቃሚነት) ።
ሰፊዋ/ሰፊዪቱ፡ የሰፋች ከጥበት የራቀች (ዘፀ. ፫፡ ፰) ።
ሰፋ (ሰፈየ)፡ ጠቀመ/ዘመዘመ/ደረዘ/ደረተ/ደበደበ/ወሰወሰ/ሸደሸደ/ሸከሸከ/ሸለለ። (ተረት)፡ "ለስ መጥሪያ ቍና ስፋች"።
ሰፋ (ሰፊሕ)፡ መስፋት።
ሰፋ (ሰፍሐ)፡ ተዘረጋ/ፋገ/ተንቦረቀቀ (ከጥበት ራቀ፡ ረዘመ በጐን በወርድ) ።
ሰፋ (ዐረ ጸፋ)፡ ጠራ/ጥሩ ኾነ ።
ሰፋ፡ ሴፍ ።
ሰፋ፡ በዛ እየጨመረ ኼደ።
ሰፋ አለ፡ ሰፊ ኾነ።
ሰፋ፡ የታናሽ ዛፍ ስም (ዘንግና ሶማያ የሚኾን ዕንወት ቀጥታ መለልታ ያለው ፪ኛ ስሙ ጠዬ ይባላል፡ ይኸውም ተባትና እንስት ነው፡ ወንዴ ሰፋ ሴቴ ሰፋ እንዲሉ) ። ጐዣሞች ግን ሱማያ ይሉታል፡ ሶማያ ከማለት ጋራ ይሰማማል። "ሰፋ ማለፊያ ጥሩ ማለት ነው፡ ፋ እይነሣም"።
ሰፋሪ፡ የሰፈረ/የሚሰፍር/የሚለካ (ተቀማጭ) ። "ዓሥራት ሰፋሪ ቀለብ ሰፋሪ መኻል ሰፋሪ" እንዲሉ።
ሰፋሪዎች፡ የሚሰፍሩ ተቀማጮች ።
ሰፋፊ፡ ብዙ ሰፊ (የኮባን የንሰትን የሙዝን ቅጠል ቈርበትን የመሰለ ነገር) ። (ግጥም)፡ "ይወለድና ቂጠ ሰፋፊ፡ ያባቱን ምድር ወሰን አስገፊ"።
ሰፋፊ፡ የሰፈፈ/የሚሰፍ።
ሰፋፋ፡ ጠቃቀመ ።
ሰፌድ (ዶች)፡ (ሰፋ/ሰፈየ)፡ ሰታታ ዝርግ ስፌት እኸል ማበጠሪያ ከምጣድ ላይ ትኩስ እንጀራ ማውጫ ። በትግሪኛ "ሰተታ" ይባላል ።
ሰፌድ እግር፡ እግሩ ለማጣ ጠፍጣፋ የኾነ ሰው ።
ሰፌዶ፡ መርከብ የሚገለብጥ የባሕር...
ሰፌዶ፡ ዝርግ ጋሻ ።
ሰፌዶ፡ የዓሣ ስም (ጠፍጣፋ ዓሣ) ።
ሰፍነግ፡ እንደ ኳስ ክብ ኹኖ በባሕር ውስጥ የሚበቅል ብቋያ (ኹለንተናው ዐይን ውሃ መጣ የባሕር እንጕዳይ ዐይነ በጎ መሳይ) ።
ሱላይ፡ የዠማ ስም (በወግዳና በተጕለት መካከል ያለ ወንዝ) ።
ሱሌማ፡ ከድንጊያ የሚገኝ ማዕድን (ሌሎችን ማዕድኖች የሚያሰማማ/የሚያጠራ) ።
ሱሎ፡ የብ... ነጭ ፈረስ።
ሱማሌ (ዎች)፡ የነገድ ስም (በሐረርጌ አውራጃ በውጋዴና በኢሳ የሚኖር ዘላን ሕዝብ፡ በምሥራቅ አፍሪቃም አለ) ። "ሱማሌ ወገን" ቅጽል ይኾናል ።
ሱማል/ሶማል፡ ላም ዕለብ። ሱማል ዐረብኛ፡ ሶማል ሱማልኛ ነው።
ሱማልኛ፡ የሱማሌ ቋንቋ (የሱማሌ አፍ) ።
ሱማልያ፡ የሱማሌ አገር።
ሱማራ (ውሳጤ ባሕር)፡ የባሕር ውስጥ ለውስጥ የጦር መሣሪያ (መርከብን እየሸነቈረ የሚያሰጥም መኪና) ። በ፲፰፻ ዓ.ም መጨረሻ አሻሽለው ያበጁት የፈረንሳይና የጣሊያን የሆላንድ ሊቃውንት ናቸው ይባላል።
ሱሳ (ዕብ ሱስ ፈረስ)፡ የቀበሌ ስም (ነቢዩ ሕዝቅኤል በባቢሎን ራእይ ያየበት ስፍራ) ።
ሱሳ፡ በወይናደጋ የሚበቅል ዛፍ ቅጠለ ብዙ ዕንጨት ።
ሱሳን፡ በቀድሞ ዘመን በቤተ መንግሥት የሚሣል ባላበባ ሐረግ ።
ሱስ፡ ልማድ ሡሥ ።
ሱሪ (ዐረ ሱርዋል)፡ ታችኛ ልብስ (ወንድ በ፪ እግሩ አጥልቆ በወገቡ ላይ የሚታጠቀው - ሰፊ/ጠባብ/ቦላሌ/ተነፋነፍ ሱሪ፥ ኢያሱ ሱሪ ተፈሪ ሱሪ ቍምጣ ሱሪ እንዲሉ) ። ሲበዛ "ሱሪዎች" ያሠኛል ።
ሱሪ፡ ምስጢረኛ ውስጥ ዐዋቂ ሰው ። "ሱሪ ታጠቀ" (ወንድ ወጣው ሞያ...) ።
ሱሪ፡ ሰረገ ።
ሱራፌል፡ የነገድ ስም (የግዜርን መንበር የሚያጥኑ መላእክት ካህናተ ሰማይ ፮ ፮ ክንፍ ያላቸው) ። አንዱ "ሱራፊ" ይባላል፡ ትርጓሜው "ዐጣኝ" ማለት ነው ።
ሱርስት፡ የታችኛውና የላይኛው ሶርያ የአሶር የአራም ቋንቋ። "ሶርያን" እይ ።
ሱባዔ (ሰብዐ)፡ አንድ ወይም ኹለት ሰባት (ከሰው ተለይቶ በበኣት ተከቶ የሚደረግ ጾምና ጸሎት) ። የሱባዔ ትርጕም ሰባት ሰባትነት ማለት ነው።
ሱባዔ ገባ፡ ከሰው ተለየ፡ ዘጋ፡ ብቻውን ተቀመጠ።
ሱቲ፡ መናኛ ግምጃ ሐርነት የሌለው ። ሳተ (ስሕተ)፡ ወርውሮ ተኩሶ እጁን ዘርግቶ ሳይወጋ ሳይመታ ሳይዝ ቀረ (ዘንጉ ጥይቱ ጊጤውን ይላማውን ዐለፈ ዘለለ) ።
ሱት (ስሑት)፡ የሳተ/የሳተች (ደካማ - "ሴት ሱት" እንዲል ባላገር) ። "ሔዋንን" ያሳያል ።
ሱካ፡ ኀፍረተ ብእሲ። "ሹካን" እይ።
ሱካረ ነቢያት፡ ቀይ ሱካር። በግእዝ "ሶከረ ነቢያት" ይባላል (የመቤታችን ምሳሌ ነው) ።
ሱካር (ሶከር)፡ የሸንኰራገዳ እንቀት (ክርትፍ)፡ በያይነቱ ክብ/እንክብል/ድብልብል/አራት ማእዘን ኹኖ የተዘጋጀ ከሻይና ከቡና ጋራ የሚጠጣ ምግብ (ጣፋጭ) ። "ሸንኲርን" እይ። ሱካር (ሸንኰር - ዐማርኛ፡ ሶከር - ግእዝኛ) ።
ሱካር፡ የበሽታ ስም (ከሱካር የሚመጣ ሕመም - ብዙ ውሃ ያስጠጣል፡ በሰው ገላ ላይ ቍስል ያበዛል) ።
ሱካርና ወተት፡ የመጽሐፍ ስም (ብላቴን ጌታ ኅሩይ ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ የተረጐሙት ታናሽ የተረት መጽሐፍ) ።
ሱክሱክ አለ፡ ተንሶከሶክ ውሽኛ ኼደ።
ሱዳኔ (ሱዳናዊ)፡ የሱዳን ሰው/የሱዳን ተወላጅ።
ሱዳን (ኖች)፡ ያገር/የነገድ ስም (ሱዳን በአረብኛ ጥቍሮች ማለት ነው፡ በግእዝ ግን አገሩ ኖባ ይባላል) ። በ፲፬፻ ዓ.ም. ጊዮርጊስ ንጉሠ ኖባ የሚባል ክርስቲያናዊ ንጉሥ ነበራቸው።
ሱፋላ (ሱፍ)፡ ከበግ ጠጕር የተሠራ ጸዐዳ ካባ። ሱፍና ሱፋላ ባማርኛ ይተባበራሉ ። (ግጥም)፡ "ቅባኑጉ ወጥቶ ሲተርፈው ለይፋት ሱፋላጣኹ እኔ ያሰናጂ ጥፋት"። "ሱፍ አላጣኹ ሱፋላ ዐጣኹ" ማለት ነው።
ሱፋላ፡ የበርባሬ ብጫ ጥለት የሱፍ ኣበባ መሳይ።
ሱፋላ፡ የነጭ በግ ጠጕር እንደ ሱፍ ንጣት ነጭነት ያለው። "ሎፊሳን" አስተውል።
ሱፋጭ (ሰፈጠ)፡ ስለት ያለው ጥቍር ደንጊያ (ተሰብሮና ተፈንክቶ ሻፎ የኾነ አለት) ።
ሱፍ (ዐረ ጹፍ)፡ ጠጕር ። ጥብቆና ሱሪ ቀሚስ የሚኾን ከጠጕር የተሠራ ልብስ እንደ በርኖስ ያለ በርኖስን የመሰለ። "ሱፋላን" ተመልከት።
ሱፍ (ፎች)፡ የቅመም ስም (ዘይት የሚወጣው ነጭ ቅመም ባላገዳ) ።
ሲ፡ "በለው ሲሲ በለው" - ነገርን አስተውል።
ሲ፡ ዐቢይ (ዋና) አገባብ፡ በትንቢት ውስጥ ገብቶ አንቀጽ እያስቀረ በቁሙ ቀሪነቱን (ያለፈውን ሁኔታ) ያሳያል። (ማስረጃ)፡ "መብራት ሲበራ ጨለማ ይጠፋል፡ ነገር ሲያመልጥ ራስ ሲመለጥ አይታወቅም። ሲያውቅ የተኛን ሲሰማ ቅበረው።" "ሰን" ሲያስኘው የትንቢት መነሻ "ይ" ነው። "አ" ሲከተለው "ሳ" ይሆናል፡ "ዓለም ሳይፈጠር ፈጣሪ ነበር። ሰነፍ ሳይከብር ይሞታል"። "እኔ", "አንተ", "እናንተ", "እሷ" በነዚህ በአራቱ ሰዋሰዋዊ ግሶች በትንቢት ውስጥ ገብቶ "ስ" ሲሆን "ስጥፍ" (አንተ, እሷ), "ስትጥፉ" (እናንተ) ይላል። በግእዝ መሠረቱ "እንዘ" ነው።
ሲ፡ የስም ባዕድ መነሻ፡ ከሚያስደራጊ (ተሳቢ) አንቀጽ የሚወጣ። (ምሳሌ)፡ "አስካካ" > "ሲካካ"
ሲላ (ሰላ)፡ (ዘዳ. ፲፬፡ ፲፱)፡ ያሞራ ስም (ፀረ እንቄ፡ ዐይነተ ጭልፊት፡ ቁመተ ዐርአሞራ፡ ጥፍሩ የሾለ/የሰላ የወፍ/የዶሮ ጠላት ነው) ። ሌሎቹ አሞሮች የያዙትን ይቀማቸዋል፡ ስለዚህ ጐበዝ ሰው "ሲላ" ይባላል። "ሾተልን" እይ።
ሲላ በዳሳ፡ የሰው ስም (ዐጤ ቴዎድሮስ በጦርነት ጊዜ ይዘው የሰቀሉት የንጉሥ ሣህለ ሥላሴ አሽከር ሐርበኛ ጐበዝ) ። በዳሳ በጋልኛ "ቸር" ማለት ነው።
ሲላዮ፡ ታናሽ መስፈሪያ (ርቦ) ።
ሲል (እንዘ ይብል)፡ ሲ ከሰ፡ ል ከኣለ፡ ትንቢት ይል መጥቶ "ሲል" ተብሏል። ሙሴ "ዐመሌ ዐመሌ" ሲል በደብረ ሲና ያየው እሳት በልቶት ይኾናል።
ሲል፡ ሳለ።
ሲል አለ፡ ታንቆ ሞተ። ይህ ዐማርኛ ከሲላ በዳሳ ተሰቅሎ መሞት የመጣ ነው።
ሲሎንዲስ፡ ቀድሞ ዘመን ዕፀ ሕይወትን ያገኘ ፈላስፋ (ቅዳ. ማር) ።
ሲመሽ፡ የሰው ስም (አባት ካረጀ በኋላ የወለደውን ልጅ "ሲመሽ" ይለዋል) ።
ሲሳያም፡ ሲሳየ ብዙ አገር ምግባም ።
ሲሳይ፡ ምግብ/መብል/ቀለብ/ጕርሥ/እንጀራ/የለት እራት ።
ሲራራ፡ ጭነት ቀርቃባ አጋሰስ ዠርባ ላይ የሚወጣ ።
ሲር ሲር አለ፡ ጮኸ ፥ ተንሰረሰረ ።
ሲር፡ የልብ ጩኸት፡ ሰረሰረ ።
ሲር፡ የተጣደ ማሰሮና የልብ ጩኸት ።
ሲሻኝ ሲያምረኝ ሲፈልገኝ ። (ተረት)፡ "እንባ ሲሻኝ ዐይኔን ስ...ወጋኝ"።
ሲሻው ሲያምረው ።
ሲቀር ይቀራል)፡ የሞተ ሰው ከቀባሪዎች ተለይቶ በመቃብር ሲቀር ሀብቱ እንዳልነበረ ይኾናል፡ በቤት ይቀራል ("(መዝ. ፵፱፥ ፲፯)") ።ቀረ ከ ሊ ሲ መነሻ እየኾኑት ሲነገር፡ "ከቀረ ሊቀር ሲቀር"፡ ባሉታም "ካልቀረ ላይቀር ሳይቀር" ይላል ።
ሲበሉ፡ የላኩት)፡ ችኩል፡ ጥዱፍ።ላኪ፡ (ዎች)፡ ለኣኪ) የላከ፡ የ ሚልክ፡ ሰዳጅ።
ሲባጎ (ዎች)፡ ቀጪንና ወፍራም የፈረንጅ ክር ወይም ገመድ።
ሲቶ (ብእሲቶ)፡ ቃለ አክብሮ ።
ሲቷ (እኅት)፡ እት፡ መነኵሴው፡ (እኅው)፡ ወንድም ይባላሉ ።በብዙም ለመናገር ("አኀው/አኃት") ወንድሞች፡ እቶች፡ ያሠኛል። ይቶት፡ አለስም፡ ብቻውን፡ ሲነገር፡ እንዳለፈው፡ በቂ፡
ሲነኳት የምትለበልብ ዐረግ ("በግእዝ አብላሊት ትባላለች ብል ለብላባ ለፍላፊ ልብለባ ትኰሳ ሽንገላ መለብለብ መተኰስ መፍጀት ማቃ ፯፻፫ መለብለቢያ ገለባ ጭራሮ ግባስ መተኰሻ መለብለቢያ ቀጪን የመቀነቻ ጠፍር መጥለፊያ ማሰሪያ ስትጠብቅ የፈረስን የበቅሎን ሆድ እንደ እሳት ለብልባ መላጧን ያሳያል ረፈ ለባለበ ተኳኰሰ አስለበለበ አስተኰሰ አስፈጀ - አስገ አስለብላቢ ያስለበለበ የሚያስለበልብ ማስለብለብ ማስፈጀት ማስገረፍ ተለበለበ ተተኰሰ ተቃጠለ ቅርፊትቅርፊቱ ቈዳ ቈዳው ተለብላቢ የሚለበለብ ዕርፍ ሞፈር ቀንበር ሽመልመሌ ልብልብ የተለበለበ ርጥብ ዕንወትሥጋ ቅልጥም ልብልባት ቀላል ቃጠሎ የእሳት ግርፋት ትኵሳት ልብላቢ የበርበሬ ፍሬ መገኛ መቀ መጫ ቋሚው መካከሉ ድልኸ ሲያደርጉት የሚለበልብ ክንክናን እይ ") ።
ሲኒማ፡ በመብራት (በኤሌትሪክ) ኀይል በተዘጋ ቤት ጐልቶ የሚታይ የማንኛውም ፍጥረት ሥዕል ጥላ (የማይናገርና የሚናገር) ። ይህን ጥበብ ያወጡ የዘር ስማቸው ሉሜር የሚባል ወንድማማቾች ፈረንሳዮች ናቸው ይባላል፡ ጊዜውም ፲፱፻ ዓ.ም ነው ።
ሲኒማ፡ በመብራት (በኤሌትሪክ) ኀይል በተዘጋ ቤት ጐልቶ የሚታይ የማንኛውም ፍጥረት ሥዕል ጥላ (የማይናገርና የሚናገር) ። ይህን ጥበብ ያወጡ የዘር ስማቸው ሉሜር የሚባል ወንድማማቾች ፈረንሳዮች ናቸው ይባላል፡ ጊዜውም ፲፱፻ ዓ.ም ነው ።
ሲኒጋል (ሎች)፡ ያገር/የነገድ ስም (በምዕራብ አፍሪቃ ውስጥ የሚኖር ሻንቅላ የሱዳን ቍራጭ የፈረንሳይ ቅኝ የነበረ፡ የሚገኘውም በአትላንቲክ ውቅያኖስ አጠገብ ነው) ።
ሲናር (ሮች)፡ ከገብስ ጋራ የሚበቅል የገረማ ዐይነት (ፍሬው ለፈረስ ቀለብ ይኾናል) ።
ሲኖዶስ፡ የካህናት ጉባኤ/ሸንጎ/ኣደባባይ/ዐውድ ። የጉባኤ መጽሐፍ በየጊዜው የተጻፈ ። ሲኖዶስ የጽርእ ቋንቋ ነው ።
ሲኦል፡ የቅጣትና የንስሓ ስፍራ፡ እስከ ፍርድ ቀን ኃጥኣን የሚኖሩበት ታችኛ ጐድጓዳ (የጨለማ ቦታ)፡ የዘብጥያ ምሳሌ።
ሲካ፡ ርጎ (ጐንደር) ። "ሲካ መስበቂያውን ያያል"።
ሲካካ፡ ቄብ ዶሮ።
ሲው፡ ሰዋስው።
ሲው/ጭው፡ የወፍ/የጫጩት/የከይሲ ጩኸት። "ሲውሲዋን" ተመልከት።
ሲውሲዋ፡ ሰጠ።
ሲውሲዋ፡ ከዘረምቦና ከሻሻቴ ከፍ ያለ ዶሮ።
ሲያክ (በኪክ በከ በክ)፡ በክት ሙቶ ያደረ፡ ከንቱ ብላሽ ዋዛ ፈዛዛ ። ንኡስ አገባብ ነው ።
ሲደልል፡ ዝኒ ከማሁ ("ሲያሞኝ ሲሸ ነግል መግደሉ ላይቀር ገል") ።
ሲዳማ፡ በሲዳሞ ውስጥ ያለ አገር (በጋልኛ ዐማራ/ሐበሻ ማለት ነው) ። ይኸውም ስም ዐማራ አስቀድሞ በዚህ ክፍል መኖሩን ያስረዳል ።
ሲዳሞ፡ በኃላ ቤት ያለ አገር።
ሲጥ፡ መጮኸ፡ ሠጠጠ።
ሲፈራ ሲቸር)፡ ላድርግ አላድርግ ልስጥ አልስጥ እያለ ሲያመነታ ። "ዶረሰን ዐፈረን" አስተውል ።
ሳ ፣ (ስ)፡ ዝኒከማሁ ንኡስ (ትንሽ) ኣገባብ። "ደግ ሳንሠራ ሞት ቢመጣሳ እንዴት እንሆናለን?"
ሳሕን (ዐረ. ጻሕን)፡ ጻሕል፡ ወጭት፡ ጣባ ደቅ (ከሽክላ/ከማዕድን የተሠራ - ትንሹም ትልቁም) ።
ሳለ (ሰሐለ)፡ ሞረደ፡ ፈገፈገ፡ ስነገለ፡ አሰላ፡ ለመጠ (መዝ. ፻፵፡ ፫) ። "በሳልከው ተመተር" እንዲሉ። "ሰላ"ና "ሳለ" ከ"ሰሐለ" መውጣታቸውን ልብ አድርግ።
ሳለ፡ (ሰአለ) ።
ሳለ (ሰአለ)፡ ለመነ፡ ጠየቀ።
ሳለ (ሰዐለ)፡ ኡሁ ኡሁ አለ፡ ጐበሰተ።
ሳለ (እንዘ ሀሎ)፡ ሳይሞት/ሳያልፍ። (ተረት)፡ "አባት ሳለ አጌጥ፡ ጀንበር ሳለ ሩጥ።"
ሳላ፡ መልኩ ወደ ጥቍረት የሚያደላ ወፍራም ስንዴ። "ሳላ ያሠኘው ምርቁ ይኾናል"።
ሳላ፡ ቀንዱ የሾለ/የሰላ የበረሓ እንስሳ (በግእዝ "ብዕዛ" ይባላል) ።
ሳላም፡ ሳል የያዘው/ያለበት/ያደረበት (ባለሳል) ።
ሳላይሽ፡ በወግዳና በተጕለት ክፍል ያለ ቀበሌ።
ሳላይሽ፡ የቀሰሌ ስም ። የፈረንጅ ፈረስ ።
ሳላይሽ፡ የፈትል ስም (የፈረንጅ ማግ) ።
ሳሌ፡ ካዋሽ የሚያንስ ጋን ዝንግሪር። "ቻልን" አስተውል (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሳሌ፡ የበሬ ስም።
ሳሌም፡ ሰላም። "ኢየሩሳሌምን" እይ።
ሳል (ሰዓል)፡ ከነፋስ/ከብርድ/ከክፉ ሽታ/ከጕንፋን/ ከመጠጥ የሚመጣ ጥዳቂ የሳንባ በሽታ (ትክትክ አክታ ያለው) ።
ሳመ (ሰዐመ)፡ ጨመጨመ/ተሳለሙ (ሉቃ. ፳፪፡ ፵፯) ። "እግር ሳመ/እጅ ሳመ/ምድር ሳመ/መስቀል ሳመ" እንዲሉ።
ሳሙና፡ ኮስቲክ ሶዳ ከሚባል የምድር ጨው ጋራ ተቀላቅሎ የተበጀ ቅባት (ዘይት ሞራ)፡ በእንዶድ ፈንታ ልብስ ማጠቢያ እድፍ ማስለቀቂያ (ሚል. ፫፡ ፪) ። ኮስቲክ ሶዳም ነጥሮን ሳይኾን አይቀርም ። "ሳሙና" በአረብኛ "ሳቡን" ይባላል ።
ሳሙና፡ ፈገግ ያለ የበቅሎ መልክ ("ገላ ሳሙና" - የገላ መታጠቢያ ባለሽቱ ሳሙና) ።
ሳሚ (ዎች)፡ የሳመ/የሚስም (ተሳላሚ/ጨምጫሚ) ። "ቤተ ክርስቲያን ሳሚ" ("ዐላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል" እንዲሉ) ።
ሳሚነት፡ ሳሚ መኾን።
ሳማ (ሞች)፡ የቅጠል ስም (ረቂቅ የኾነ እሾኹ እንደ እሳት የሚለበልብ/የሚያቃጥል/የሚያንገበግብ ቅጠል - ኢዮ. ፬፡ ኢሳ. ፴፬፡ ፲፫) ። በጦም ቀን እየተቀቀለ ይበላል፡ በጋልኛም "ዶቢ" ይባላል ።
ሳማ (ሰማ)፡
ሳማ (ሰዐምአ)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ እንቀጽና ቃለ መልእክት። "በበዓል ቀን ተቀምጠሽ ከመዋል ቤተ ክርስቲያን ሳማ"።
ሳማ (እንዘአሐሚ)፡ ጠላቴን ሳማ እኔ እጐዳለኹ እንጂ እሱ አይጐዳም።
ሳማ ሰንበት (ሰምዐ ሰንበት)፡ በምንጃር አውራጃ የተተከለ የሰንበት ታቦት (ትርጓሜው ሰንበት ሰማ ይመስላል) ።
ሳማ ቅቤ፡ ሰባት ዓመት የኖረ ቅቤ (ሖምጣጣ ጥቂቱ የሚበቃ የሆድ መድኀኒት) ።
ሳም (ስዒም)፡ መሳም።
ሳም ሳም አደረገ፡ ሳሳመ (ጭም ጭም አደረገ) ።
ሳም አደረገ፡ አጥብቆ ሳመ።
ሳምራውያን፡ የሰማርያ ሰዎች።
ሳምር፡ አገር—ሰማርያ ።
ሳምር፡ ዝኒ ከማሁ።
ሳምንት፡ ስምንት ቀን (በግእዝ ግን ያንዲት ሴት ተራ ቍጥር ነው - ትርጓሜውም ስምንተኛዪቱ/ስምንተኛዋ ያሠኛል) ።
ሳምንት፡ አንድ ወር ሠላሳ ቀን። "ማነኸ ባለሳምንት" እንዲል ሙሴ። የዚህም ምስጢር ሰንበቴን ያሳያል።
ሳሳለ፡ ሞራረደ፡ ለማመጠ። አሳለ (ኣስሐለ)፡ አስሞረደ፡ አስፈገፈገ፡ አሰነገለ፡ አስለመጠ።
ሳሳመ፡ መላልሶ ሳመ።
ሳራ፡ የሴት ስም (ያብርሃም ሚስት - እመቤት ማለት ነው) ።
ሳበ ፣ (ሰሐበ)፡ ጐተተ፡ መዘዘ፡ እረዘመ፡ (ተረት)፡ "በሬ ወዳገሩ ይስባል" (ይጐትታል) ። ሳበ፡ ጠራ፡ አወጣ፡ አመጣ፡ አቀረበ (ጋኔንን) ።
ሳበ፡ ወጠረ፡ ገተረ፡ ለጠጠ (ቈዳን፣ ድንኳንን) ።
ሳበ ይፋት፡ የሴት ስም፤
ሳበው፡ ጠመንጃ፡ በአፉ ባሩድ ከተመላበት በኋላ መጣቀሻው በቋድ ተስቦ የሚተኰስ የዱሮ ነፍጥ።
ሳቢ፡ (ዎች)፡ የሳበ፡ የሚስብ፡ ጐታች፡ አምጪ፡ አቅራቢ (በሬ፣ ፈረስ፣ ግመል፣ ባቡር) ። "ሳቢውን ግረፈው" እንዲሉ። (ጋኔን ሳቢ)፡ ጋኔን ጠሪ፡ አነጋጋሪ።
ሳቢ ዘር፡ ሳቢ ርጥበት፡ "ዘር መርጠብ"። የርጥበት ትርጓሜ መርጠብ መሆኑን ያሳያል። ፪ኛው የአማርኛ "ሳቢ ዘር" - "አስተራረስ", "አጐራረሥ" ይላል። (ግጥም)፡ "በኔ አስተራረስ ባንቺ አጐራረሥ እንኳን እሠኔ እማዚያም አንደርስ።"
ሳቢሳ (ዎች)፡ ነጭ አሞራ (በዠማ ዳር በዝቶ የሚገኝ) ። በበሬ ዠርባ ተቀምጦ ወንዝ ይሻገራል፡ ከከብት ጋራ ይሰማራል። "ጫት"ን እይ።
ሳቢና ተሳቢ፡ ጐታችና ተጐታች፡ አንቀጽና ጥራ። "ሳቢ ጎደለ፡ ተሳቢ ሰውን።"
ሳቢያ፡ ቀጥታ ሞፈር።
ሳቢያ፡ ኹለተኛ ዐረቄ፡ መናኛ ተወራጅ።
ሳባ፡ ሰበከ።
ሳባ፡ የሰው ስም፡ የኵሽ ልጅ፡ የትግሮች አባትና አገር (ዘፍ. ፲፡ ፯) ። "ሳባ ኖባ" እንዲሉ።
ሳባ፡ የየመኑ (የሳባ) ።
ሳቤላ፡ የሴት ስም፡ ብቃት ያላት የጽርዕ ፈላስፋ (በጣዖት ምኵራብ የምትቀመጥ) ። በአንድ ሌሊት የታየ የፈላስፎችን ሁሉ ራእይ ከመተርጐም በላይ እመቤታችን በፀሓይ አምሳል ወንድ ልጅ እንደ ታቀፈች በራእይ አይታ ተናግራለች። የነበረችውም በታላቁ እስክንድር ዘመን ነው። የትንቢት መጽሐፉም በግእዝ ይገኛል፡ አባቷ ህልቃስ ይባላል።
ሳቤላ፡ ጐበዝ በሬ፡ ብርቱ፡ ፈጣን፡ ሳቢ (ዐማርኛ) ።
ሳቤቅ፡ ያረገ ሬሳ (በመሬት ላይ የተጋደመ) ። "ዕፅ"ን ተመልከት።
ሳብ፡ (ስሒብ)፡ መሳብ።
ሳብ ረገብ አለ፡ ተገተረ፡ ላላ።
ሳብ አለ፡ ተሳበ።
ሳብ አደረገ፡ ጐተት አደረገ።
ሳብዕ፡ ሰባተኛ ፊደል። "ኦ ሳብዕ ቦ ሳብዕ" እንዲል ፊደል ቈጣሪ።
ሳብዕነት፡ ሰባተኛነት።
ሳተ፡ ሕግን ትእዛዝን አፈረሰ፡ ሃይማኖትን ካደ፡ ኀጢአት አደረገ የማይገባ ሥራ ሠራ (ዘሌ. ፭፡ ፲፰፡ ኢሳ. ፳፰፡ ፯፡ ሕዝ. ፵፭፡ ፳) ። ሳተ፡ ቅዘኑን ዘሩን ለቀቀ አፈሰሰ ። ሳተ፡ ዐጣ። "እባብ ጕድጓዱን አይስትም" እንዲሉ።
ሳተ፡ ዘነጋ/ገደፈ/አጠፋ የሚያውቀውን ።
ሳተነ (ሰይጠነ)፡ በረታ/ሮጠ/ፈጠነ/ቀለጠፈ (ኢዮ. ፩፡ ፯፡ ፪፡ ፪) ።
ሳተና/ሳታና (ሳጥና)፡ የሳተነ/የሚሳትን (ብርቱ ሯጭ ፈጣን ቀልጣፋ) ።
ሳተናው፡ የክራር መቺ ዘፈን ኣዝ...
ሳታርፍ፡ በዱላ፡ ቀልቦ፡ መዠመሪያ፡ ቀላ፡ መታ፡ አጠነጋ ።ለግዐ፡ ጥንታዊ፡ ዐማርኛም፡ ሲባል፡ ይቻላል ።
ሳታት (ሰዓታት)
ሳታት ቆመ)፡ ከመንፈቀ ሌሊት እስከ ጧት በዜማ ፈጣሪን ሲያመሰግን እመቤታችንን መላእክትን ጻድቃንን ሲለምን ዐደረ ።
ሳታት ቋሚ (ቀዋሜ ሰዓታት)፡ ሌሊት በቤተ ክሲያን ውስጥ ቆሞ ሳታት የሚያደርስ አወዳሽ ። "መዓል ብለኸ መዓል ሳታትን" ተመልከት ።
ሳታት ቋሚ)፡ አወዳሽ ደብተራ ።
ሳት (ስሒት)፡ መሳት ።
ሳት፡ ሰዓት ጊዜ ። "ሰዓትን" ተመልከት ።
ሳት አለው፡ ነገር አመለጠው ።
ሳት፡ የፊደል ስም "ሰ"። "ሳቱ ሰ" እንዲሉ። "ሳታትን" እይ፡ የዚህ ብዢ ነው።
ሳቻ (ስሕተት)፡ ኀጢአት ክሕደት ነውር ።
ሳች፡ የሚስት...
ሳንሳ (ምዝላል)፡ የጋራ ሸክም (መሸከሚያውም አጣና መሎጊያ ይባላል) ። "የሳንሳ ያዘ የሳንሳ ተሸከመ" እንዲሉ።
ሳንቃ፡ ተጠርቦና ተልጎ የተቀመጠ የንጨት ሉሕ (፩ነገ. ፯፡ ፱) ።
ሳንቃ፡ ከዕንቍና ከወርቅ ከብር ከንሓስ የተሠራ የለምድ መጋጠሚያ በስተደረት ያለ።
ሳንቃ፡ የበር መዝጊያ መግጠሚያ።
ሳንቆች፡ መዝጊያዎች (ዘፀ. ፳፮፡ ፳፯, ፳፱) ።
ሳንባ (ሰንቡዕ)፡ በፍጥረት ሆድ ውስጥ ከልብ ጋራ የሚገኝ ሥጋዊ ወናፍ (እሳት መልክ ባፍንጫ ውዥሞነት አየርን የሚያመላልስ መዝገበ ትንፋሽ) ።
ሳንባ ቀለም፡ ሳንባ የሚመስል ቀለም (እሳትማ) ።
ሳንባ ዐቃፊ፡ ሳንባ ወደ ባር ሆድ እንዳይወርድ ዐቅፎ ደግፎ የሚይዝ የሚሸከም የደረት ውስጥ ሥጋዊ ቋት ።
ሳንባ ድድ፡ ችካም።
ሳንባ ጠለፍ፡ ዐልፎ ዐልፎ ቍጥራት ያለው ጅራፍ (ግርፋቱ ለልብ የሚሰማ ትንፋሽ የሚከለክል) ።
ሳንቲ፡ የሜትር ፪ኛ (አንዲት ጭረት) ።
ሳንቲ፡ የዋሽንት ዐይነት የዘፈን መሣሪያ ።
ሳንቲም (ሞች)፡ የብር ፻ኛ (የም...ትርጓሜ ኛ ነው) ።
ሳንከኛ (ኞች)፡ ሰበበኛ/ሁከተኛ። ሳንኮች፡ ቅባቶች (በዘፋኝ ዳዊት ጊዜ ለተዋሕዶዎች ሳንክ የኾኑ በቅባት ሃይማኖት የሚያምኑ ሰዎች) ።
ሳንክ፡ ጕትቻ፡ ሰበብ/ሁከት/ክፉ ሐሳብ ።
ሳንጃ፡ በጠመንዣ ጫፍ የሚሰካ የጦር መሣሪያ (ሽፋፉ ብረት መጠኑ የጩቤ ሲኾን ጫፉ ሹል ነው፡ የጨበጣ ውጊያ ይደረግበታል) ።
ሳንጃ ተርብ፡ የተርብ መርዝ፡ ወይም ሳንጃ የሚባል ተርብ (ተቈናጣጭ ዝንብ) ።
ሳንፊል፡ የነፋስ ስልክ (አለሽቦ ድምፅ የሚሰጥና የሚቀበል መኪና - ራዲዮ) ። ማርኮኒ የሚባል ጣሊያን ያወጣው፡ ሳንፊል ፈረንሳይኛ ራዲዮ ጣሊያንኛ ነው።
ሳዕስዐ)፡ ተንሻሻ በዛ ተን...“የተንቀሳቃሽ የዶሮ” ።
ሳኦል፡ ክፉ፡ አት፡ ሞተ ።
ሳኦል፡ የሰው ስም፡ በእስራኤል ላይ መጀመሪያ የነገሠ ንጉሥ።
ሳካ (ስሕከ/ሳሕክ)፡ እንከን (የገላ ነውር፡ ቋቍቻ፡ ዕከክ) ።
ሳካም የለሽ፡ የሴት ስም ("እንከንም የለሽ" ማለት ነው) ።
ሳክላ፡ በሺዋ ክፍል ያለ አገር።
ሳይ (ሰሓሊ)፡ የሳለ/የሚስል (ሞራጅ ሰንጋይ) ።
ሳይ (እንዘ እሬኢ)፡ እኔ ሳስተውል/ስመለከት ። "አየን" እይ።
ሳይንት፡ ያገር ስም።
ሳይዳ፡ እመቤት። "ሴዱን" እይ (ከዚህ ጋራ ዘሩ አንድ ነው) ።
ሳደረ፡ ሰው።
ሳደረ፡ አመረቀዘ (ቍስሉ)፡ ተበላሸ፡ ጠመመ (መቃብሩ/ነገሩ/የቀንበሩ ብስ) ።
ሳደፍ፡ መበከል ማኵለፍለፍ ማበሽጥቀ ።
ሳዱላ (ኦሮ)፡ ሴት ልጅ፡ ልጃገረድ።
ሳዱላ፡ በብር/በመዳፍ ልክ የተቦቀረ ያናት ቡቅራት (ባል ባላገባች ልጃገረድ መኻል ራስ/ቍንጮ ላይ የሚታይ ክብ ልጭታት) ።
ሳድስ ቅጽል) ንግር ።
ሳድስ፡ የፊደል ስም (ስድስተኛ ፊደል) ። "እ ሳድስ፡ ብ ሳድስ" እንዲል ፊደል ቈጣሪ። "ትጽል"ን ተመልከት።
ሳድስነት፡ ስድስተኛነት።
ሳዶቅ፡ የሰው ስም (ጻድቅ ማለት ነው) ።
ሳገ፡ ሳጋ (ሰሐገ)፡ ሻጠ፡ ሰካ፡ ጨመረ፡ አገባ። ላፃ የካህናት፡ ሳጋ የባላገር። "መሰገን" እይ (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሳገ፡ የሳገ/የሚስግ (ሻጭ) ።
ሳጋ፡ ባንድ በኩል እየሾለ እባጥ/እግድግዳ የሚገባ ጠርብ/ሽብልቅ።
ሳጠራ፡ አቴና ሣጠራ።
ሳጥናኤል (ሰይጣነ ኤል)፡ ሰይጣን (ጠላት) + ኤል (አምላክ) = በተገናኘ ፀረ አምላክ/ያምላክ ጠላት/ባለጋራ ማለት ነው።
ሳጨ (ትግ. ሳጸየ - መነመነ)፡ በጠጠር ዐጠበ፡ ፈገፈገ።
ሳጻ) ነጻ (ነጻሒ/ሐራ/ግዑዝ)፡ ጌታው የለቀቀው (ባርነት የቀረለት በራሱ ሐሳብ ዐዳሪ) ።
ሳፈረ (ዐረ)፡ ወደ ውጭ እግር ኼደ።
ሳፍ (ዐረ ጻፊ)፡ ጥሩ የጠራ ።
ሳፍ፡ ሹል ዐጥንት፡ ሰፋ (ሰፈየ) ።
ሳፍ፡ ያካንዱራ መውጊያ ሹል ዐጥንት ወይም ዕንጨት ።
ሳፍራ፡ የነፋስ ባሕርይ (ግእዝ) ።
ሳፍራን፡ አበባው ዐደይ መሳይ የሽቱ ቅጠል። በግእዝ "መጽርይ" ይባላል (ማሕ. ፩፡ ፲፬) ።
ሳፍወርቃ፡ የሴት ስም ("ጥሩ ወርቅ" ማለት ነው) ። ይህችውም በመርሐ ቤቴ የግርጌት ባላባት ነች።
ሳፍጅ፡ በጠራ ውስጥ ያለ ቀበሌ።
ሴላ፡ ድንቅ ማለት ነው።
ሴሎ፡ በእስያ ክፍል ያለ አገር።
ሴም፡ የሰው ስም (ከኖኅ ልጆች አንዱ በኵሩ - የርሱም ዕጣ ክፍል እስያ ነው) ።
ሴሰነ (ሰስኖ/ሰሰነ)፡ ኣመነዘረ/ቀነዘረ/ሸረሞጠ (ካንዲት ሴት ዐለፈ ተረፈ) ።
ሴሰን፡ ምንዝር/ቅንዝር/ሽርሙጥና ።
ሴሰኛ (ኞች)፡ የሴሰን ባለሴሰን (እመንዝራ ቅንዝረኛ ኻያጅ) ።
ሴሰኛነት፡ ቅንዝረኛነት ።
ሴሰኝነት፡ ዝኒ ከማሁ (ሮሜ ፲፫፡ ፲፫) ።
ሴራ፡ ዐድማ (ሠየረ፡ ሤረ) ።
ሴታውል (ሴት አውል)፡ ላም ዐንገት የሴት እረኛ ከሴት ጋራ የሚውል ወንድ (ደካማ ዐቅመ ቢስ ፈሪ) ።
ሴቴ ሰፋ፡ ጕጥ አልባ ጠዬ ።
ሴቴ ሬት፡ ጥርስ የሌለው የቍስል መድኀኒት ።
ሴቴ ቍልቋል፡ ለስላሳ መላላ ቀጥተኛ ቍልቋል ።
ሴቴ ብር፡ የሴት ሥዕል ያለባት ብር ("ብረ ሰብስብ") ።
ሴቴ ብርጕድ፡ ያልተመጠነ ያልተቀላቀለ ብርጕድ ።
ሴቴ ዐፈር፡ ቀይ መሬት ሸክላ ያፈር ወይዘሮ ።
ሴቴ፡ ወገን ቅጽል (የሴት ሲታዊ ሴትማ ሴት ዐይነት እንስታዊ) ።
ሴት (ብእሲት/ብእሰ)፡ ሚስት (የወንድ ጣምራ ኹለተኛ ባልተቤት የቤት አሳዳሪ - ፩ቆሮ. ፯፡ ፪, ፫, ፬) ። በሐባብ "እሲት" ትባላለች ።
ሴት ተወ፡ አበከረ ።
ሴት አኵሪ፡ የስንዴ ስም (ዳቦው የሚያምር ስንዴ) ።
ሴት አኵሪ፡ የቅጠል ስም (የዥብ ሽንኩርት የሚመስል ቅጠል ጠቈር ያለ) ። (ግጥም)፡ "የምናየው ቅጠል ካበቦች መካከል ሰፋ ሰፋ ያለው ለካ ሴት አኵሪ ነው"።
ሴት ወይዘሮ፡ የባለጠጋ ሚስት እመቤት ። "ወይዘሮ" ለሴት ቅጽል ነው ።
ሴትነት፡ ሴት መኾን (የሴት ያ - "ሴትነቱ ጣጣ ነው" እንዲሉ) ።
ሴትኛ ዐዳሪ፡ መበለት (ባል አልባ ብቻዋን የምታድር የምትኖር) ።
ሴትዮ (ኦ ብእሲቶ)፡ ቃለ አጋኖ ወይም አራኅርኆ (አንክሮና አክብሮም ከዚሁ ይገባሉ - "ሴት ሆይ" ማለት ነው) ።
ሴቶ፡ ቅጥ ዐጣሽ (የወፍ ጩኸት) ።
ሴቶች፡ ሚስቶች (ባልተቤቶች) ። ሴት፡ የሰው ስም (ያዳም ፫ኛ ልጅ ምትክ ማለት ነው ይላሉ) ።
ሴቷ/ሴቲቱ፡ ያች ሴት (ራእ. ፲፪፡ ፬, ፮, ፲፬, ፲፭, ፲፮, ፲፯) ።
ሴክል፡ ያመት ዘለላ (፻ ዓመት) ።
ሴዋ፡ ጌሾ (ገድ ተክ) ።
ሴደር፡ ቀይና ነጭ የበሬ መልክ (ቅላትና ንጣት እንደ መቀነት እየኾነ ገላውን የከበበው) ። ነጭና ጥቍር ሲኾን ጕሬዝ ይባላል።
ሴደርማ፡ የሴደር ወን... (ባካሉ ላይ ሴደር ያለበት ከብት) ።
ሴደርያ (ዐረ. ጸደይሪያህ)፡ የደረት ጥብቆ ባለጌጥ።
ሴዱ፡ የሰው ስም (ጌታ ማለት ነው) ። "ሳይዳን" ተመልከት።
ሴጣን፡ ጋኔን።
ሴፍ፡ ሰይፍ፡ ሰየፈ ።
ስ፡ በስም መጨረሻ እየገባ አፍራሽ (የማስተባበያ) ይሆናል። "አቤል ኀጢአት ሠርቷልን?" (ወይ) "ቃየል ኀጢአት ሠራ እንጂ፡ አቤልስ ኀጢአት አልሠራም። ይሁዳ ንስሓ ገብቷልን?" (ወይ) "ጴጥሮስ ንስሓ ገባ እንጂ፡ ይሁዳስ ንስሓ አልገባም።" በግእዝ መሠረቱ "ስ" ነው፡ "ግን"ን ተመልከት። ዳግመኛም በጥያቄና በስም በኀላፊ አንቀጽ ጫፍ እየተጨመረ እንደ "ም" ወይም "ዋዊ" ይሆናል። "እመቤታችንን ያበሠራት ሚካኤል ነውን ወይስ ሩፋኤል?" "ገብርኤል ነው እንጂ ሚካኤልና ሩፋኤል አይደሉም።"
ስሓ (ሳካ)፡ እንከን። በግእዝ ዘሩ "ሴሐ" ነው።
ስሓ (ትግ)፡ ዕከክ።
ስሃ፡ እንከን፡ ስሓ።
ስኂን (ሰኀነ)፡ የጪስ ዕንጨት፡ ምጥን ልባንጃ፡ ዕጣን (ጥሩ ሽታ ያለው) ።
ስሒን፡ ልባንጃ።
ስለ (ሰአለ)፡ ዐቢይ እገባብ። "ዠግና ስሙን ማስጠራት ስለ ወደደ ዝኆን ዐደን ኼደ።"
ስለ ሺ (ስለሺ)፡ የሰው ስም ("በሺ ፈንታ አንተ ትበቃለኸ" ማለት ነው) ። ስለ ከተናባቢ ሳድስ ቅጽል ሲገኝ "ታቦት ዘፋኝ" ይላል።
ስለ፡ እንደ። "ጥቍሬታ ስለ ጤፍ ነው።" "ስለ ምን?" (በምን ምክንያት/በምን ሰበብ?)
ስለ ጠላት ፍራቻ ቤታቸውን በተራራ ላይ ይሠሩ ስለ ነበረ ነው ።
ስለ ፍቅር፡ በስመ አብ ይቅር (የሰይጣን ነገር) ።
ስለላ፡ የመሰለል ሥራ።
ስለቃ፡ ድቈሳ።
ስለታ፡ የመሰለት ሥራ።
ስለታም፡ ስለት ያለው/ባለስለት (ብረት ወይም ሰው - ፪ሳሙ. ፪፡ ፲፮).
ስለት፡ ልመና ("ሳለ" - ሰአለ) ።
ስለት፡ ማረጃ።
ስለት፡ ማረጃ ("ሳለ" - ሰሐለ) ።
ስለት፡ ማረጃ (ካራ፡ ቢላዋ፡ ኣፋ፡ ጩቤ፡ ዱቢት፡ ሾተል፡ ሰይፍ፡ ጐራዴ፡ ሐኔ፡ ፈንዜ፡ ዋልሴ፡ ወንበርቲ - ፪ዜና. ፳፫፡ ፯, ፲) ። "ስለት አወጣ" "አሰላ"።
ስለት ድጕሱን፡ ደባ ራሱን ይቀዳል፡ ይጐዳል።
ስለቸ፡ ሰማ።
ስለፋ፡ ችኰላ/ቍተማ።
ስላች፡ ከብት የማይኼድበት ጠባብ የዱር መንገድ (አሳቻ እጐዳና የሚያደርስ) ።
ስላች፡ የነገር ጭላንጭል (አንድ ሰው በሌላ ሰው ጕዳይ የሚገባበት ሰበብ/ምክንያት) ።
ስላንቲያ፡ የመልሱ መጨረሻ ስድብ የኾነ የልጆች ጥያቄ። "ስላንተ ዘለፋ" ማለትን ያሳያል። "ዕንካ ስላንቲያሽ?" "በምንንቲያኸ?" "በወንፊት ምን አለኸ?" "በወንፊት ከልጆቹ ኹሉ አንተ ነኸ ምድር ፊት" እንዲል እረኛ (ዕንካ ስላንቲያ)፡ ጭቅጭቅ/ንዝንዝ/እሽኰለሌ ።
ስላዳም ብለኸ በሸንጎ ከለሜዳ ለብሰሽ ደምኸ የተነዛ ።"
ስል (ስሑል)፡ የሰላ።
ስል (ሥሩሕ)፡ የቀና ማረሻ (ግትር ያይዶለ ስበት) ። በትግሪኛ "ስሉሕ" ይባላል። "ስል የሰላሳለ"።
ስል (እንዘ እብል)፡ "ደግ መሥራቴ እጸድቅ ስል ነው።"
ስል፡ የሰለለ/ሰላላ።
ስል፡ የበጀ/የሰላሰላ/ሳለ።
ስልል፡ ማስረጃ/ነገር። "እከሌ ስልል አይገባውም" እንዲሉ።
ስልል አለ፡ ምንምን አለ።
ስልል፡ የተሰለለ አገር/መንግሥት።
ስልም (ጽሉም)፡ የጨለመ ።
ስልም አለ፡ ጭልም አለ ዐይኑ፡ ዛለ/ደከመ ሰውነቱ።
ስልምልም አለ፡ ተስለመለመ።
ስልምልም፡ የተስለመለመ (ዝልፍልፍ ጭልምልም) ።
ስልምልምታ፡ ጭልምልምታ፡ ዝልፍልፍታ ።
ስልምጥ አደረገ፡ ሰለመጠ።
ስልምጥ፡ የተሰለመጠ (ስልቅጥ) ።
ስልሰላ፡ ምንመና/ንጠላ/ሽንሸና/ሥንጠቃ።
ስልስል (ዕዉስ)፡ ዝኒ ከማሁ ልምሾ።
ስልስል አለ፡ ምንምን አለ ።
ስልቃት፡ ስለቃ።
ስልቅ፡ ሰለተ።
ስልቅ አደረገ፡ ድቅቅ አደረገ/ጐዳ (በሽታ ድጅኖ ሰውን) ።
ስልቅ፡ የተስለቀ (ድቍስልም ልዝብ) ።
ስልቅ፡ ያገር ስም ሥልቅ።
ስልቅጥ፡ የተሰለቀጠ/የተዋጠ (ውጥ) ።
ስልባቦታም፡ ስልባቦት ያለው/ባለስልባቦት።
ስልባቦት፡ በፈላ ወተት ላይ የሰፈፈ ቅቤ (በትግሪኛ "ላሕመት" ይባላል፡ ፈረንጆች "ክሬም" ይሉታል) ። ምስጢሩ ከወተት ላይ ተገፎ መነሣት ነው።
ስልብ (ቦች)፡ የተሰለበ/የተቈረጠ (ጕምድ፡ ጃንደረባ፡ ጠባቂ) ።
ስልቦሽ፡ ዝኒ ከማሁ።
ስልቦት፡ ጋዣ።
ስልት፡ ቀጠና/ጠኔ።
ስልት አለ፡ ልትት ድክም አለ፡ አሳለተ/አካደነ።
ስልት፡ ክፍል/ወገን። (የነገር ስልት)፡ ዐቅድ/መልስ። (የዜማ ስልት)፡ ዐይነት (ግእዝ/ዕዝል/አራራይ) ። (በስልት/በስልቱ)፡ በክፍል/በክፍሉ፡ በወገን/በወገኑ፡ ባይነት/ባይነቱ (ስም) ።
ስልቸታ፡ ጥጋብ/ጥላቻ ።
ስልቹ፡ የሰለቸ/የተሰለቸ (ታካች) ።
ስልቻ (ቾች)፡ የበግና የፍየል ቀልቀሎ/አቍማዳ/ዳውላ/ቀርበታ (ትንሹም ትልቁም የወይፈን ሲኾን ጭልጊ/ዐይበት ይባላል) ። ሥሩ "ዕለተ" ይመስላል።
ስልችት አለ፡ ተሰለቸ ።
ስልከኛ (ኞች)፡ ስልክ ጠባቂ ("ሳለስልክ ሰውን በስልክ 'አሎ' እያለ የሚጠራና የሚያነጋግር") ።
ስልከኛነት፡ ስልከኛ መኾን (የስልክ ሥራ መያዝ) ። ስልክን መዠመሪያ በ፲፰፻፸፮ ዓ.ም. ያወጣው እስክንድር ግራሐምበል የሚባል አሜሪካዊ ነው ይላሉ። ፈረንጆች "ቴሌፎን" ይሉታል።
ስልክ (ኮች)፡ የብረት/የመዳብ/የናስ ቀጥተኛ ሽቦ (የቃል/የኤሌትሪክ መኼጃ/መመላለሻ) ።
ስልክልክ አለ፡ ተስለከለከ።
ስልክክ አለ፡ ስልክ መሰለ፡ ቈነዠ ።
ስልጆ፡ ከባቄላና ከሰናፍጭ የተዘጋጀ የጦም ወጥ (ምግብ - ነጭ ሽንኵርትም አለበት) ።
ስሎሽ፡ ሙረዳ፡ ፍግፈጋ፡ ስንገላ።
ስመ መንግሥት፡ አንድ ንጉሥ የሚጠራበት ስም (ወናግ ሰገድን የመሰለ) ። በዘመናችን የፈረስ ስም ይባላል።
ስመ ስርጋዌ፡ አፈ በረከት/አፈ ወርቅ።
ስመ ርስት፡ የርስት ስም (የገባር የ...ግንደ በል) ።
ስመ ተጸውዖ፡ የመጠራት ስም (በስመ አብ የጸሎት መዠመሪያ) ። (ተረት)፡ "በእንተ ፍቅር በስመ አብ ይቅር ከበ ስመ አብ ተቀንሶለት።"
ስመ አምላክ፡ ጠንቋዮች እንደ ሐሳባቸው ጽፈው የሚሼጡት መጽሐፍ ።
ስመ ክርስትና፡ የክርስትና ስም (ገብረ ክርስቶስ/ተክለ ማርያም) ።
ስመ ክፉ፡ ስሙ በክፉ የሚነሣ ኀጢአተኛ/ግፈኛ ሰው።
ስመ ጥር (ሩ)፡ በዠግንነት/በደግ ሥራ/በውቀት ስሙ የተጠራና የታወቀ ባለዝና (በግእዝ "ስሙይ" ይባላል) ።
ስመ ፈጣሪ፡ ክፉ ስም ሰጪ ሐሜተኛ።
ስመ ፈጣሪ፡ የፈጣሪ ስም።
ስመኛ (ኞች)፡ ስም አክራ (የስም ባለስም ተብሎም ይተረጐማል) ። ስም ከአንቀጽ በፊት ተነግሮ በተሳቢነት፡ ከቅጽል ተናቦ በዘርፍነት፡ ከጥሬ ተናቦ በባለዘርፍነት ይነገራል።
ስመኝ፡ የወንድና የሴት ስም።
ስመጥ፡ ሰመመ ።
ስመጥ፡ የዠርባ ወንዝ (ሽንጥ - ግእዝ) ።
ስሙር፡ የሰመረ (የበጀ ማለፊያ - ኵስትር) ። "ስሙር እረኛ" እንዲሉ።
ስሙኒ፡ ሩብ ፳፭ ሳንቲም (ከጣሊያን ወዲህ የተለመደ ቋንቋ ነው - የተሙን ተሙናዊ ማለት ነው - ባ፩ ተሙን ፪ ይመነዘር ነበር) ።
ስሙን ለሰው አወረሰው፡ የራሱን ነውር በሌላ ላከከው።
ስሚ፡ መስማት (ወሬ ጭምጭምታ) ።
ስማ (ስማዕ/መስክር)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ፲ አድምጥ።
ስማ ምስክር፡ ዕወቅልኙን ስማ ("ያየኸውን/የሰማኸውን መስክር" ማለት ነው) ።
ስማ ስማ፡ መሰማሚያ ይንሣው (ያድባርን ያውጋርን ጠላት እንዲል ዐዋጅ ነጋሪ) ።
ስማ ስማ፡ ያዋጅ ቃል መዠመሪያ።
ስማ በለው፡ ተርጕመኸ ንገረው።
ስማ በለው፡ አስተርጓሚ።
ስማርድ (ስመ አርድ)፡ ነብርን ያሳያል ።
ስማርድ (ዶች)፡ የነብር ወጥመድ (ላዩ በብረት የተጠረቀ ውፍረቱ እንደ ቀንበር የኾነ ውስጠ ክፍት ዕንጨት - በውጭ የዝንጀሮ ጠጕር ገመድ ያለበት) ።
ስማንፋር (ዐረ. ሱም እልፋር)፡ ያይጥ መርዝ (ዐይጥን የሚገድል የቈለቈል ዐይነት መድኀኒት) ።
ስሜት፡ መገረን (በውስጥ ያለ ደዌ በስተው ሲሰማ ስሜት ይባላል - ትርጓሜውም መሰማት ነው) ።
ስሜነኛ (ኞች)፡ የስሜን ተወላጅ (የስሜን አገር ሰው) ።
ስሜን (ስምየ)፡ የኔን ስም ስምና ስሜን በገቢር ጊዜ ይገጥማሉ። "ስሜን ስሜን እነግርኻለኹ" (ዐጤ ቴዎ) ።
ስሜን፡ በጐንደር ሰሜን ያለ አገር። "ስሜን" የተባለው በቧሒት (የያሬድ ተራራ) ምክንያት ይመስላል ።
ስም ።
ስም (ሰመየ)፡ የቦታና የአካል መጠሪያ (ማንኛውም የሚታይና የማይታይ ነገር ኹሉ የሚጠራበትና የሚታወቅበት ስም ይባላል) ። የሚታይ (ሰማይ/ፀሓይ/ጨረቃ/ኮከብ/ደመና/ዝናም/ምድር/ውሃ/እሳት/እንስሳ/አውሬ/ወፍ/ሰው) ። የማይታይ (እግዜር/ወልአክ/ነፍስ/ነፋስ/ሐሳብ/ድምፅ የመሰለው ኹሉ) ። ከዚህም በቀር የተቀብዖ/የመጽሐፍ/ክርስትና/የባሕርይ/የግብር/የወል/የመጠን/የመልክ/የቄሳቍስ ስም (ነባር ስም/ጥሬ ስም የሚባል አለና ኹሉንም ባገባብ ተመልከት) ።
ስም፡ ሰመጠ።
ስም ሰጠ፡ ቀኛዝማች/ግራዝማች አለ።
ስም ቀቢ፡ በሰው ስም ላይ ነውርን የሚቀባ/የሚላክክ ።
ስም ዐበር፡ ሞክሼ ።
ስም አወጣ፡ የማዕርግ ስም ሰጠ፡ ወይም ተቀበለ/ተሾመ።
ስም አውጪ፡ ለሰው ክፉ ወይም ደግ ስም የሚያወጣ።
ስም አጠራር፡ የሰውን ስም ሲኾን በደግ ሳይኾን በክፉ ማንሣት ።
ስም አጥፊ፡ ስምን የሚያጠፋ/የሚያበላሽ ።
ስም እኩይ፡ የሐሜት ስም።
ስም ጠራ፡ እከሌ አለ።
ስምል፡ የተሰመለ (ልፍ ልዝብ) ።
ስምም፡ የተስማማ (ወዳጅ) ። "እከሌና እከሌ ስምም ናቸው" እንዲሉ።
ስምም፡ ፍቅር/ሰላም (ዓሞ. ፫፡ ፫) ።
ስምምነት፡ ስምም መኾን (ወዳጅነት) ።
ስምሪት፡ ወደ ዱር መኼድ፡ የዱር ሥራ (ዕንጨት ቈረጣ/እኸልና ሣር ዐዳ/ዕርሻ) ።
ስምና ግብር፡ ነባርና አባት ዘር።
ስምን (ስሙን)፡ የተሰመነ።
ስምን መልአክ ያወጣዋል፡ ይሰጠዋል/ይስይመዋል (ማቴ. ፩፡ ፳፩) ።
ስምንምን አለ፡ ተስመነመነ።
ስምንምን አደረገ፡ አስመነመነ።
ስምንምን፡ የተስመነመነ (ድቅስቅስ) ።
ስምንተኚት፡ ስምንተኛዪቱ ክፍል።
ስምንተኛ (፰ኛ)፡ የተራ ወይም የማዕርግ ቊጥር የስምንት ወገን።
ስምንተኛዋ፡ ስምንተኛዪቱ (ያች ስምንተኛ) ።
ስምንተኛው ሺ፡ የዘመን ስም (ሽንገላና ተንኰል ክሕደት ክፋት ጥመት የበዛበት ጊዜ) ። "ካጤ ምኒልክ አሽከሮች አንዱ መኰንን ስምንተኛው ሺ ብለው ሲጠሩ አገልጋያቸው ሰው አበላሺ ይል ነበር" ይባላል (አርእስተ መዝ. ፲፩) ።
ስምንተኛው፡ ያ ስምንተኛ (የርሱ ስምንተኛ) ።
ስምንቲያ፡ ከስምንት አንድ።
ስምንት (፰)፡ የቍጥር ስም (በሰባትና በዘጠኝ መካከል ያለ መድበል ወይም ጅምላ ቍጥር ያንድ ቤት) ።
ስምንቶ/ስምንትዮ፡ ስምንትነት ያለው ውስጠ ብዙ...
ስምጥ አለ፡ ስጥም አለ።
ስምጥ፡ የሰመጠ/የሰጠመ። "ዕጥ የኾነ ስምጥ ታጣ" እንዲሉ።
ስሞሽ (ስዕመት)፡ መሳም። "ራስ ስሞሽ" እንዲሉ።
ስሞተኛ፡ ስሞታ ወዳድ (ነጋሪ) ።
ስሞታ፡ እከሌ እንዲህ ሠራኝ እንዲህ ኣደረገኝ ብሎ ለዋ... የሚያሰሙት ወቀሣ።
ስሞታ፡ ወቀሣ—ሰማ ።
ስሞች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ መጠሪያዎች።
ስሳ ስድስት ዐሥር፡ , ሰደሰ ። ሴሰየ (ሴስዮ/ሴሰየ)፡ አጐረሠ/አስታረበ/ኣበላ/መገበ/ቀለበ ።
ስረጌ፡ የማንም ከብት መዋያ ሥ...
ስራ (ስራሕ)፡ ዕርሻ/ቍፋሮ/ዐዳ ። "ስራ መስራት የማይወድ አይብላ" (፪ተሰ. ፫፡ ፲) ።
ስራና፡ የሽንብራ ኩፍታ (ትግ) ።
ስርሰራ፡ ስንፈጣ ነደላ ።
ስርስራ፡ የሣር ስም (ቀጪን ሰንበሌጥ - ጐዣም) ።
ስርስር፡ የተሰረሰረ/የተበሳ (ብስ/ነዳላ/ሰባራ ሸክላ ብረት ግንብ ቅል) ።
ስርቂያ/ስርቆሽ/ስርቆት፡ መስረቅ/ሌብነት (ምሳ. ፱፡ ፲፯) ።
ስርቅ (ስሩቅ)፡ የተሰረቀ ከባለቤቱ...
ስርቅ፡ የሆድ ጕስምት። በግእዝ ግን "ስርቆት" ማለት ነው ።
ስርቅታ፡ ስርቅ ማለት (ፋቅ ሕቅታ) ።
ስርቆሽ በር፡ በፊት በር አንጻር ካዳራሽ ከልፍኝ በስተኋላ ያለ በር (ነገሥታት መኳንንት ለሕዝብ ሳይታዩ የሚወጡበት) ።
ስርነቃ፡ ስንፈጣ ትንታዞ ።
ስርንቅ አደረገ፡ ሰረነቀ ።
ስርንቅ፡ የተሰረነቀ (ዕፍን) ።
ስርዋጽ (ሰርወጸ)፡ ሽብልቅ ውሻል ስባሪ ጣልቃ ገብ ሥንጣሪ ለቃልም ይነገራል ።
ስርየት/ስሬት፡ የኀጢአት ይቅርታ ።
ስርጀታ፡ ጠለፋ ።
ስርግ (ስርግው)፡ የተስረገ/የተጌጠ/የተዳረ ።
ስርጓጕጥ፡ ወጣ ገባ፡ ሥርጓጕጥ ሠረጐደ ።
ስሻሽ፡ የሴት ስም ("ስፈልግሽ") ።
ስሻኸ፡ የሰው ስም ("ስፈልግኸ" ማለት ነው) ።
ስቅለት፡ ሰቀላ/መስቀል/መሰቀል (ግእዝ) ።
ስቅለት፡ የታላቅ በዓል ስም (ጌታችን ዓለምን ለማዳን በመስቀል ላይ የተሰቀለበት መጋቢት ፳፯ ቀን) ።
ስቅላት፡ ዝኒ ከማሁ (ለስቅለት - አማርኛ) ።
ስቅል (ስቁል)፡ የተሰቀለ/የተንጠለጠለ (እንጥልጥል ዝልዝል ሥጋ ርጥብ ልብስ) ። ባላገር ግን ሥዕልን "ስቅል" ይለዋል።
ስቅል አለ፡ ተሰቀለ ።
ስበብ፡ ሰበብ። "በስበቡ መምሬ ተሳቡ" እንዲሉ።
ስበት (ስሕበት)፡ እየተረገጠ በጥፍር አንድነት የታሰረ/የተቈራኘ ማረሻ (ድግር፣ ሞፈር፣ ቅትርት፣ ዕርፍ)፡ መርገጥ ወገል ሰባትነት ያለው።
ስበዛ፡ ሽጐጣ፡ ጭመራ።
ስባሪ፡ የሸክላ፣ የብርጭቆ ሽራፊ፡ ድቃቂ (ኢሳ. ፴፡ ፲፬፡ ፴፩፡ ፬፡ ግብ. ሐዋ. ፳፯፡ ፵፬) ።
ስባሪ፡ የቈሎ ክርታሽ፡ ፍንካች፡ ልብጥ።
ስባቅ፡ ቀለም (ባንድነት የታሸ ዕይር) ።
ስብሐተ ነግህ፡ የጧት ምስጋና (ቅዱስ ያሬድ በዜማ የደረሰው) ።
ስብሐተ ፍቁር፡ ሦስተኛ የሰዓታት ክፍል (ባለ ፫ ስንኝ)፡ የወዳጅ ምስጋና ማለት ነው።
ስብሐት (ሰብሐ)፡ ምስጋና፡ ማመስገን። "ስብሐት ለእግዚአብሔር" - ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል፡ "ለ" ማለት "ይገባል" ማለትን ያመጣል። ስብሐት ለአብ፡ ከማዕድ በኋላ የሚባል ጸሎት።
ስብሐት ለአብ፡ የሰው ስም (በኢያሱ አድያም ሰገድ ጊዜ መልከአ ሥላሴን የደረሱ ፍጹም ሊቅ) ።
ስብሰባ፡ ለቀማ፡ እከባ።
ስብሰባ፡ ጉባይ፡ ጉባኤ።
ስብሰባዎች፡ ጉባኤዎች፡ ጉባዮች።
ስብስባት/ስብስብነት፡
ስብስብ አለ፡ ተሰበሰበ።
ስብስብ፡ የተሰበሰበ፡ ጥርቅም፡ እክብ፡ ክምቹ።
ስብራት፡ መሰበር፡ ሰባራነት (ኢሳ. ፴፡ ፳፮፡ ኤር. ፶፩፡ ፻፬) ።
ስብራት፡ ዕጥፋት፡ ቅንፋት (የልብስ፣ የቈዳ) ።
ስብር (ስቡር)፡ የተሰበረ፡ ሥንጥቅ።
ስብር አለ፡ እንክት፡ ቅልጥም አለ።
ስብርባሪ፡ ስብርብር፡ የተሰባበረ፡ እንክትካች፡ ቅልጥምጥም ።
ስብርብር አለ፡ እንክትክት አለ።
ስብቀላ፡ ቅልጠፋ።
ስብቀት፡ ስብቅ፡ ማሳበቅ።
ስብቅ፡ ዱቄቱ የተሰበቀ (የታሸ) ጤፍ እንጀራ።
ስብቅል (ሎች)፡ የሰበቀለ፡ ጣፋጭ፡ ቀልጣፋ ቃል/ሰው።
ስብቅል አለ፡ ሰበቀለ።
ስብቅልቅል፡ ቅልጥፍጥፍ፡ የተሰበቃቀለ፡ የተመሰቃቀለ።
ስብቅልቅል አለ፡ ቅልጥፍጥፍ ምስቅልቅል አለ።
ስብቅልነት፡ ቀልጣፋነት፡ ጣፋጭነት።
ስብቆ/ስብቆሽ፡ ታሽቶ ተሰብቆ የፈላ የጥቍር ስንዴ ሙቅ እንትክትክ፡ ያጃ አጥሚት።
ስብት፡ የተሰበተ፡ የታረሰ፡ የተገለገለ፡ ግልግል ።
ስብከተ ገና ጾም፡ የነቢያት ጾም፡ የልደት የስብከት እሑድ (ከታኅሣሥ ፯ እስከ ፲፫ ያለ) ።
ስብከት፡ ቃል፡ ነገር፡ ትምህርት (ከሰባኪ አንደበት የሚወጣ) ።
ስብዛት፡ የሰበዝ አገባብ ኹኔታ።
ስብዝ፡ የተሰበዘ፡ የተሻጠ፡ የተሸጐጠ።
ስቦሽ፡ ጐተታ።
ስቱፋን፡ የሳቱ ያልመቱ ። "ልጆችም አንዱን ልጅ ስቱፋን ይሉታል"።
ስቱፍ፡ የሳተ ያልቀለበ ያልመታ ፉርሽ (ችኩል ጥዱፍ) ።
ስትል (አንተ/እሷ)፡ ስትሉ፡ ስትዪ፡ ስል፡ ስንል እያለ በ፰ ሰራዊት ይዘረዝራል ። "ሰን" ተመልከት።
ስትር (ስቱር)፡ የተሰተረ (ዝርግ ስጥ) ።
ስነጋ፡ ነደላ/ቅርቀራ።
ስነጣ፡ የመሰነጥ ሥራ።
ስኒ (ሺናዊ)፡ የሽን አገር ሥራ ታናሽ ሸክላ (የቡና መጠጫ በጥዋ አምሳል የተሠራ) ። "ፍንጃልን" አስተውል ። ሺን በግእዝ ሲን ይባላልና ስኒ ሲናዊ (ዘሲን ማለት ነው) ።
ስኒ ካፓ፡ የማዕርግ ልብስ (እንደ ስኒ ነጭ የኾነ ካፓ፡ ወይም ከነጭ ሐር የተሠራ ሺናዊ የሽን ካባ ማለት ይኾናል - ማር. ይሥ. ፫) ።
ስናም፡ ነፈሊያም አፍንጫ ነፍናፋ ።
ስናር፡ በሰሜን አፍሪቃ በሱዳን ክፍል ያለ አገር።
ስናር በቅሎ፡ ስናር አህያ ከእንስት ፈረስ የዴቀለው (ሲኼድ እንደ እንዝ የሚሾር የሚሽከረከር) ።
ስናር አህያ፡ ቁመቱ ፈረስ የሚያኸል ረዥም የስናር አህያ ።
ስናቅ/ስናግ/ትናግ፡ አፍንጫ ወይም ውሳጣዊ ያፍንጫ ቀዳዳ። "ሕፃኑ የጠባው ወደ ስናቁ ወጣና ትን አለ"።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር።
ስናን፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር ።
ስናን፡ የሕፃን በሽታ (ተውሳክ ግግን የመሰለ) ።
ስናን፡ ያንድ ክፍል ጭፍራ ስም (በዱሮ ዘመን) ።
ስናጋ/ስናግ፡ ንፎ (የከብት አፍንጫ ቀለበት - በግእዝ ዝማም ይባላል - ፪ነገ. ፲፱፡ ፳፰፡ ኢዮ. ፵፡ ፳፮) ።
ስናግ (ትናግ)፡ ከላንቃ በስተኋላ ያለ ቀዳዳ ወዳፍንጫ የሚደርስ። "ስናቅን" እይ።
ስናግ፡ እዶሮ አፍንጫ የገባ ላባ።
ስናግ፡ የመጋረጃ ዘንግ (ከብረት ዋ የተሠራ - በግእዝ ሰንጐጕ ይባላል) ።
ስናግ፡ ያፍንጫ መካከለኛ ጫፍ (በግእዝ ሕልበት ይባላል) ።
ስናጭ፡ ለገድ ነፈል (ያፍንጫ ትንፋሽ በቀጥታ እንዳይወጣ የሚከለክል ሥጋ) ።
ስናፍቅሽ፡ የሴት ስም።
ስናፍቅኽ፡ የወንድ መጠሪያ ስም ("ስሻኸ ስፈልግሽ አገኘኹኸ" ማለት ነው) ።
ስናፒክ፡ የተክል ስም (የባሕር አገር) ።
ስንቀራ፡ የመሰንቀር ኹናቴ።
ስንቀን፡ ሱረት ሠነቀ ።
ስንቅር አለ፡ ተሰነቀረ ።
ስንቅር አደረገ፡ ሰነቀረ ።
ስንበባም፡ ቃታም (ባለቃታቍና ቍና የሚተነፍስ) ።
ስንበብ/ስንባብ፡ ቃታ የትንፋሽ ...ጥነት ።
ስንቡል፡ ሽቱ (ሽቶ በግእዝ ሰንበልት ይባላል) ።
ስንብር፡ የሰነበረ (መንታነት ያለው ድጕስ - በማኅደርና በዝናር ላይ ይታያል) ።
ስንብት/ስንብቻ፡ ወደ ሌላ ስፍራ ለመኼድ ለመዛወር ከጌታ/ካለቃ/ካሳዳሪ የሚቀበሉት ፈቃድ (የጥቂት ወይም የብዙ ሳምንት - መክ. ፰፡ ፰) ።
ስንተኛ (ኞች)፡ የተራ ቍጥርን መጠን ለማወቅ የሚነገር ጥያቄ። ሲጫፈር ስንትና ስንት ይላል፡ ብዛትንም ያመለክታል ።
ስንተኛው (ስንተኛቸው)፡ የጊዜና የማንኛውም ነገር ዐጸፋና በቂ ።
ስንታየኹ፡ የወንድና የሴት ስም።
ስንት (ስፍን)፡ የቍጥርን ልክ ለመጠየቅ የሚነገር ንኡስ አገባብ (ምን ያኸል) ። "ይሁዳ ጌታችንን ለስንት ብር ሼጠው፡ ጴጥሮስ ስንት ጊዜ ካደው፡ አይሁድ ስንት ጊዜ ገረፉት፡ ጌታችን ስንት ተኣምራት አደረገ"።
ስንቶች (እስፍንቱ)፡ ምንያኽሎች ።
ስንቾ፡ የሚጥሚጣ ስም (ሚጥሚጣ) ።
ስንን (ኖች)፡ ፪ኛው "ን" ይጠብቃል፡ ቅንቅን ገዳይ ቅጠል።
ስንኝ (ኞች)፡ የመልክ/የሰላምታ/የዐርኬ/የዘፈን ቤት ግጥም።
ስንከላ፡ የእግር ላይ ምት።
ስንኩል፡ ዝኒ ከማሁ (ጐደሎ) ። "ሀብተ ስንኩል መብሉ እኩል ሥራው ስንኩል" እንዲሉ።
ስንክልክል አለ፡ ተስነካከለ ።
ስንክሳር፡ የመጽሐፍ ስም (የመላእክትን ማዕርግና ሹመት የሚያስረዳ የነቢያትንና የሐዋርያትን የጻድቃንንና የሰማዕታትን የደናግልንና የመነኮሳትን ምግባር መከራና ዕረፍት ከዕለት እስካመት የሚነግር መጽሐፍ - የቤተ ክርስቲያን ታሪክ) ። የመቤታችንን ዜና የልጇንም በጎ ሥራ ኹሉ በሰፊው ይናገራል። ትርጓሜውም በጽርእ "የተሰበሰበ ስብስብ" ማለት ነው ።
ስንክሳሮች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ መጽሐፎች።
ስንኳ፡ ንኡስ አገባብ (የማማረጥ ቃል - ስንኳን/እንኳ - ዘፀ. ፲፬፡ ፳፰፡ ዘዳ. ፪፡ ፭፡ መዝ. ፻፴፱፡ ፲፮፡ ኢሳ. ፴፫፡ ፳፫፡ ፴፭፡ ፰፡ ሕዝ. ፳፬፡ ፲፪) ።
ስንኳን (ጥቀ. ጓ)፡ ንኡስ አገባብ ።
ስንኳን፡ ሰነፈ ።
ስንዘራ፡ የመሰንዘር ኹኔታ።
ስንዛሪ፡ የተሰነዘረ/የተሠነተረ።
ስንዝር (ስዝር)፡ ካውራ ጣት ጫፍ እስከ መካከለኛ ጣት መጨረሻ ያለ ልክ መጠን። "ስንዝር ተጋት" እንዲሉ (ስም) ።
ስንዝር አለ፡ ዕልፍ አለ ።
ስንዝር፡ የተለካ/የተመጠነ (ሥንትር ሥንጥቅ - ቅጽል) ።
ስንደቃ፡ አሰራ ።
ስንደዶ፡ ስፌትና ገመድ የሚኾን ሣር። (የውሻ ስንደዶ)፡ ስንደዶ የሚመስል ዋና የመስክ ሣር ሰል።
ስንዱ፡ የሴት ስም ።
ስንዱ፡ የተሰናዳ/የተዘጋጀ (ዝግጁ) ።
ስንዱነት፡ ዝግጁነት/ድርጁነት።
ስንዴ (ስንዳሌ)፡ የእኸል ስም (ዳቦና እንጀራ የሚኾን የብር እኸል - አምኜ/አቶሳል/ጐዣሜ/ጣይ/ሶራ/ዐዛዜ/መንዜ/ሸመጥ/ተኸሬ፡ ከዚህም በቀር ብዙ ዐይነት ስንዴ አለ) ። (ተረት)፡ "ስንዴ በጭንቅ ባለጌ በጥብቅ"።
ስንዴ ማና፡ የነጭ ገብስ ስም (እንጀራው የስንዴ መና የሚመስል) ።
ስንድቅ፡ የተሰነደቀ/የታሰረ ነዶ።
ስንድድ አለ፡ ቀጥታ ኾነ፡ አማረ አፍንጫው።
ስንድድ፡ ከተረከዝ ተያይዞ በስተላይ ያለ ሥር።
ስንድድ፡ የስንደዶ ቀለበት (የዦሮ ደግፍ መድኀኒት) ።
ስንድድ፡ የተሰነደደ ሰመግ።
ስንድድ፡ ጨሌ (የሴት እጅና እግር ጌጥ፡ መጋረጃና የመሶብ ቀሚስም ይኾናል) ።
ስንገላ፡ ፍግፈጋ/ውልወላ።
ስንጋት፡ ስነጋ (የመሰነግ ሥራ) ።
ስንግ፡ የተሰነገ (አፍንጫው ዋ በስናግ የተያዘ በሬ/ዶሮ) ።
ስንግ፡ የንግዴ ልጅ (የሴትን ማሕፀን በወሊድ ጊዜ ሰንጎ የሚያስንቅ) ።
ስንግል፡ የተሳለ/የተሰነገለ (ውልውል ጥሩ ብልጭልጭ ባለስለት መሣሪያ) ።
ስንጥ፡ የተሰነጠ/ያማረ (ልዝብ) ።
ስንፍ፡ ስንፍና/ስንፈት (ሥራ መፍታት/ሰነፍነት - ምሳ. ፳፮፡ ፬, ፭፡ ማር. ፯፡ ፳፪፡ ፩ቆሮ. ፩፡ ፳, ፳፩, ፳፫, ፳፭) ። "ስንፍ የዶባ ላም የጋለሞታ" እንዲሉ።
ስንፍ አለ፡ ሰነፈ ።
ስንፍ ገባው፡ ስንፍና ዐደረበት ተጠቃ ።
ስኣ፡ የኢፍ ፫ኛ (ሦስተኛ) ።
ስከላ፡ አሰራ (የመሰከል ሥራ) ።
ስካራም፡ ዘወትር ሰክሮ የሚታይ (ሳይስክር የማያውል ሰው/ቅዠታም) ። "ሰካራም" ማለት ግን ያልታረመ ዐማርኛ ነው።
ስካር ልብ አያሳጣም፡ ቍርሾን ያናግራል፡ ቂምን ይገልጣል ።
ስካር፡ የመጠጥ እብደት/ቅዠት። "ስካር ሰውን ከእንስሳ በታች ያደርጋል፡ የሚሰክርም ሰው በቁሙ የሞተ ነው"።
ስክ (ስኩዕ)፡ የተሰካ/የተሻጠ። "ስክ መዝጊያ" እንዲሉ።
ስክል (ሎች)፡ የተሰከለ - የታሰረ (ፈረስ፡ በቅሎ፡ ግመል፡ አህያ) ።
ስክረት፡ መስከር፡ ሰካርነት።
ስክር (ስኩር)፡ ስካሪ/የሰከረ።
ስክር አለ፡ ጥንብዝ አለ።
ስክርክር፡ የውሃ ዝቃጭ ከረከረ።
ስክተት (ሰክተተ)፡ ዝርግ/ጠፍጣፋ ሉሕ (የወጋግራ መቆሚያ) ። "ክባስን" እይ።
ስወራ (ስዋሬ)፡ ሽፈና፡ ክለላ፡ ድበቃ።
ስዊስ፡ በፈረንሳይና በጀርመን በጣሊያን መካከል ያለ አገር (ሰዓት የሚሠራበት) ። ሕዝቡ በ፫ ኣንጻር ፈረንሳይኛ፡ ጀርመንኛ፡ ጣሊያንኛ ይናገራል።
ስውር (ሮች - ስዉር)፡ የተሰወረ (የማይታይ፡ ድብቅ - ፈጣሪ፡ መልአክ፡ ሰይጣን፡ ነፍስ - መዝ. ፲፩፡ ፪፡ ማቴ. ፯፡ ፬, ፯) ። ረቂቅ ነገር (ምስ ዚር የለበስ/የጋቢ/የኩታ ስፌት) ። "ዐይን"ን ተመልከት።
ስውር ቦታ፡ ድብቅና ሽሽግ ስፍራ።
ስውር አለ፡ ድብቅ አለ፡ ዕቡ ኾነ።
ስየማ/ስያሜ፡ ስም አጠራር።
ስያፍ፡ ቀጥታ ያይዶለ (ከታች ሰፊ ከላይ ቀጪን ሾጣጣ፡ ወይም ጐደሎ የኾነ ዕቃ/ልብስ) ። "መቅንን" ተመልከት።
ስይም (ስሙይ)፡ የተሰየመ ("እከሌ" የተባለ) ።
ስይም፡ ልብም።
ስይፍ፡ የተሰየፈ (ዐንገቱ የተቈረጠ) ።
ስደራ፡ ድርደራ፡ ኵልኵላ።
ስደተኛ (ኞች)፡ (ዘፍ. ፳፰፡ ፩፡ ዘፀ. ፳፫፡ ፱)፡ በስደት ያለ/የኖረ (ላገሩ እንግዳ፡ ለሰው ባዳ፡ ባይተዋር፡ መጻተኛ) ። (ተረት)፡ "ሐሰተኛ በቃሉ፡ ስደተኛ በቅሉ (ይታወቃል) ።"
ስዱብ፡ የተሰደበ፡ ውርፍ፡ ንቁፍ።
ስዱኝ፡ ስደዱኝ።
ስዱኝ አለ፡ ሰውን ለመጣላት/ለመምታት "ተውኝ/ልቀቁኝ" አለ።
ስዱዳም፡ የስዱድ ወገን (ስዱድ ያለበት) ።
ስዱዳን፡ ስደተኞች።
ስዱድ፡ የተሰደደ (ካገሩ ወጥቶ የኼደ - ፈላሻ) ።
ስዳጅ፡ መረን፡ የመከር መካተቻ፡ የካቲት።
ስድ፡ ልቅ፡ አግድሞ፡ አደግ፡ ባለጌ።
ስድሳ/ስሳ (፷)፡ የቁጥር ስም (ባምሳና በሰባ መካከል ያለ ያሥር ቤት አኃዝ - ስድስት ጊዜ ዐሥር ወይም ዐሥር ጊዜ ስድስት) ።
ስድስ፡ የተሰደሰ።
ስድስተኚት፡ ስድስተኛዪቱ ክፍል
ስድስት (፮)፡ ባምስትና በሰባት መካከል ያለ ቁጥር (ያንድ ቤት) ። ስድስተኛ/ስድስተኛው እያለ ተራ ቁጥር ይኾናል።
ስድስት አደረገ፡ እስከ ስድስት ቈጠረ/በስድስት ከፈለ።
ስድስትነት፡ ስድስት መኾን።
ስድስትያ፡ ስድስት መቶ ድር።
ስድስትያ፡ ከስድስት አንድ።
ስድስቶ ች፡ ባንድነት ጅብ ብለው የሚታዩ ኮከቦች (ስድስትነት ያላቸው) ።
ስድራ (ትግ)፡ ባል፡ ሚስት፡ ልጆች (ቤተ ሰብ) ።
ስድራት፡ ድርድራት።
ስድር፡ የተሰደረ ድርድር/ክልል።
ስድብ፡ ዘለፋ፡ ነቀፋ (ሕዝ. ፳፪፡ ፬፡ ማር. ፯፡ ፳፪) ። (በሌባ ቤተ ሰብ ላይ የተነገረ ስድብ) ። "የሚስቱ ባልትና ኺዱ ምን አለና፡ የማጭዱ ስም ተው፡ ቈያ ይጨልም፡ የልጆቹ አልተኙም ሰዎቹ።"
ስጃጃ (ስጋጃ)፡ የፉቅራ/የቃልቻ መቀመጫ ምንጣፍ።
ስጃጃ፡ ሰደረ።
ስጕድ፡ የተሰጐደ (ቅንፍ፡ ጐድጓዳ፡ ዐቃፋ፡ ጕብጕብ፡ ሽልም) ።
ስጋጃ (ጆች) (ዐረ. ሱጋጃ)፡ ከጠጕር/ከቃጫ የተዘጋጀ ምንጣፍ (መስገጃ/መቀመጫ)፡ ግብረ መርፌ (የፋርስ ሥራ - ምሳ. ፴፩፡ ፳፪) ። "ስጋጃና ወላንሳ" እንዲሉ።
ስግ፡ የሰጋ፡ ሠጋ።
ስግ፡ የተሳገ ዕንጨት።
ስግሰጋ፡ የመሰግሰግ ሥራ (ስብሰባ ዕቃ) ።
ስግስጋት፡ መጠጋጋት።
ስግስግ አለ፡ ጥቅጥቅ አለ።
ስግስግ፡ የተሰገሰገ፡ የተቀራረበ።
ስግብግብ አለ፡ ተስገበገበ።
ስግደት፡ መስገድ፡ ሰገዳ፡ መውደቅና መነሣት።
ስግደዳ፡ ምለሳ፡ ስብሰባ፡ ድበቃ፡ ስውራ።
ስግድድ አለ፡ ድብቅ አለ (እንደ ዔሊ) ።
ስግጥ፡ የተሰገጠ/የተሰፋ ስፍ... ቅምቅም ዝምዝም።
ስጥ (ስጡሕ)፡ የተሰጣ (ዝርግ፡ ስትር፡ ለፀሓይ የተሰጠ፡ ቅይጥ) ።
ስጥ፡ አቀብል፡ ሰጠ።
ስጥ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ (አቀብል፡ አስረክብ) ።
ስጥ፡ የተሰጣ (ሰጣ) ።
ስጥም (ስጡም)፡ የሰጠመ/የዘቀጠ (ጥልም) ።
ስጥም አለ፡ ስጠሙ።
ስጦታ/ስጥወታ፡ መስጠት፡ ችሮታ፡ ልገሳ (ዘፀ. ፴፭፡ ፭፡ ምሳ. ፳፭፡ ፲፬፡ ሮሜ. ፭፡ ፲፭, ፲፯) ። በሴት ለመናገር፡ ብትፈልግ "ስጦታዋ/ስጥወታዪቱ ያች ስጥወታ" በል። (ሮሜ. ፭፡ ፲፮).
ስፋት፡ ሰፊነት/ጐን።
ስፌት (ቶች/ስፍየት)፡ መስፋት። "እከሊት ስፌት ታውቃለች"።
ስፌት፡ ካክርማ/ከስንደዶ/ካለላ/ከግራምጣ የተሰፋ (ሰፌድ/ቍና/ጕርዝኝ/እንቅብ/መሶብ/ሌማት/ሙዳይ/አገልግል/ጮጮ/ጕብ የመሰለው ኹሉ) ።
ስፌት፡ የሸማ/የሱሪ/የበርኖስ/የዐጽፍ የማንኛውም ልብስ መጋጠሚያ። "ደርዝ ተኵስ ውስውስ ስፌት" እንዲሉ።
ስፌት፡ ጥልፍ ዝምዝማት ("ማሪያምን" አስተውል) ።
ስፍ (ስፉይ)፡ የተሰፋ (ድርዝ ዝም...) ።
ስፍ (ስፍይት)፡ የሐረርጌ ኦሮሞና የሱማሌ ልጃገረድ የተሰፋች ።
ስፍሕ፡ ድር ዝሓ (ግእዝ) ። ምስጢሩ ስፋትና ዝርግነት ነው።
ስፍረ ሰዓት፡ ሰው ጥላውን በማው...እየሰፈረ የሚያውቀው የሰዓት ቍጥር።
ስፍራ (ዎች)፡ ቦታ ቀበሌ (መዝ. ፻፴፭፡ ፪) ።
ስፍር (ስፉር)፡ የተሰፈረ/የተለካ (ቅጽል) ።
ስፍር፡ ልክ መጠን። "ስፍር የሌለው ስፍር ቍጥር" እንዲሉ (ስም) ።
ሶለላ (ጸለለ/ጋረደ)፡ አግሬ (፩ዜና. ፲፪፡ ፲, ፴፬፡ ፪ዜና. ፲፩፡ ፲፪).
ሶለሶለ) አንሶለሶለ፡ እዞረ/እንቀዠቀዠ/አንቀለቀለ። "ዘለዘለን" እይ።
ሶለሶል/ሶልሷላ/ሶልሶልቱ፡ የተንሶለሶለ/የሚነሶለሶል (ዘዋሪ) ።
ሶለግ (ጎች)፡ (ሰለከ)፡ ከግንዶሽ በላይ ከቍግ በታች ያለ የጅራፍ ክፍል (ከታች ወደ ላይ እየቀጠነ ይኼዳል) ። "ሾለቅን" ተመልከት።
ሶለግ ውሻ፡
ሶለግ፡ ውሻ ቀጪን ረዥም የፈረንጅ ውሻ (ሽንጣም ዐዳኝ) ። "ሶለግ" የውሻ ቅጽል ነው።
ሶል፡ ፀሓይ/ጀንበር (ሮማይስጥ) ።
ሶል)፡ ፀሓይ (ጧት በምሥራቅ፡ ቀትር ሲኾን በሰማይ መካከል፡ ማታ በምዕራብ እንድትታይ - ይህም እንደዚያ ማለት ነው) ።
ሶልዲ፡ ገንዘብ (ጣሊያንኛ) ።
ሶመሶመ)፡ አሶመሶመ፡ አረጠረጠ/አረተረተ/አኰተኰተ ለመጋለብ ። "እሶምሱምና ይዘኸልኝ ና" እንዲል ሰርገኛ።
ሶማያ (ሰው ማያ)፡ በላይ ጦር በታች ጀንፎ የተዋደደበት ዘንግ ጠዬ፡ ወይም ሌላ ዕንጨት። በጐዣምም ብዬ (ሰፋ) ሱማያ ይባላል።
ሶምሳ፡ ከጅኁር አፋፍ በታች ያለ አገር (በቡልጋም ይገኛል) ።
ሶምሶማ፡ ርትረታ (ከደንገላሳ የሚቀ ድም የሰንጋ ፈረስ ሩጫ) ።
ሶምሶን፡ የሰው ስም (በዕብራይስጥ "ሺምሾን" በአረብኛ "ሸምሽ" ይባላል - ፀሓይ ማለት ነው) ።
ሶስና፡ የሴት ስም ("አበቡት" ማለት - ኪ.ወ.ወ.ክ) ።
ሶረኔ/ሶረናዊ፡ የሶረን (ፍጹም ቅላት ያላት የቈላ ቆቅ) ።
ሶረን (ሶራ)፡ ቀይ በሬና ላም።
ሶሪት ቀይ ወፍ፡ , ሶራ ።
ሶሪት፡ የእንስት በግ ስም (ተባቱ ዳንግሌ ይባላል) ።
ሶሪት/ሶራዊት፡ ሶራ የምትመስል እንደ ጣዎስ የምታምር ቀይ ወፍ (አብረቅራቂ ጥቍረትና ንጣት ያላት ዞሬት ዞሪቴ) ። ባረብኛ "ዙራ" በጋልኛ "ጆሮ" ትባላለች ። "ሰራ ንን ሶረንን" እይ፡ የዚህ ዘር ነው።
ሶራ (ሱርትዮን)፡ ቀይ ግምጃ የጣዎስ ሥዕል በላዩ ያለበት ። (ግጥም)፡ "ሶራ ሶራ ልበስ የጊዮርጊስ ፈረስ"። ሶራ ባረብኛ "ጹራ" በዕብራይስጥ "ጹራት" ይባላል (ኪ.ወ.ክ) ።
ሶሮሮ፡ ነጭ ጤፍ ።
ሶብይ፡ ጐበዝ፡ ጕልማሳ፡ ወጣት (ሦታ) ።
ሶታ፡ ሰተተ ።
ሶታ፡ ወጣት ሦታ ።
ሶከሶከ)፡ አሶከሶከ፡ በዝግታና በሩጫ መካከል ያለ ኣካኼድ ኼደ ውሻው።
ሶክሷካ፡ የተንሶከሶከ/የሚንሶከሶክ።
ሶዳ፡ የመጠጥ ስም (ጠርሙሱን ሲከፍቱት የሚጨስ/የሚፈላ ቀላል የባሕር አገር መጠጥ) ።
ሶፍያ፡ ሕልመ ዝሙት ተጻብኦ (በሴት አምሳል የሚታይ ምትሀት ፍትወታዊ የሰይጣን ጥበብ) ። "ሶፍያ መታችኝ" እንዲል ተማሪ አራተኛውን ጠባ እይ ።
ሶፍያ፡ የሴት ስም (የጽርእ ሰማዕት) ። ሶፍያ ጥበብ ማለት ነው።
No comments:
Post a Comment