Friday, June 6, 2025


: ፲፬ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ። በፊደልነት ስሙ ነሐስ፡ በአኃዝነት ነ፶ ይባላል።

: በጫፉ ዝርዝር እየጨመረ ነባር አንቀጽ ይሆናል። "ነውን" እይ።

: ዝርዝር (ከን ግስ የመጣ)

: ረና የመ ተለዋዋጭ። "አጠናቀረ" "አጠራቀመ""ንስር" "ምስር"

: የለ ተለዋጭ (ከግእዝ ወዳማርኛ) "ወልድ ወንድ"

ነሐሴ: የወር ስም፣ ናሴ፡ ፲፪ኛ ወር። ሥሩ በግእዝ ነሐሰ ነው።

ነሐስ: የፊደል ስም ነ፡ ሽቦ ማለት ነው።

ነኈረጥ፣ ነኍራጣ: የተነኋረጠ፣ የሚነኋረጥ።

ነኆለለ: ደነቈረ (ከነኾለለ ግስ የመጣ)

ነኆረጠ (ንኅረ): ነፍናፋ ሆነ፡ በአፍንጫው ተናገረ። "ሖረጠን" እይ።

ነምሳ: በአውሮፓ እጀርመን አጠገብ ያለ አገር።

ነሰረ (ነሲር፡ ነሰረ): ወረደ፡ ፈሰሰ (ደሙ)

ነሰረ: በዛ፡ ፈደፈደ፡ ተንጣለለ። "ይህ ወጥ ቅቤ ነስሮታል።

ነሰረ: ከሰማይ ቍልቍል ተወረወረ (አሞራው)

ነሠረ: ወረደ፡ ነሰረ።

ነሰረኝ: ወረደኝ፡ ፈሰሰኝ። "ዛሬ ፀሓይ መታኝና ነሰረኝ። "

ነሰበ (ዐረ፡ ነጸበ): ዐደለ፡ ዕድል ሰጠ።

ነሠበ: ዐደለ፡ ነሰበ።

ነሰተ: በቀተ፡ ነሠተ።

ነሠተ: ነዘነዘ፡ በቀተ፣ አስቸገረ።

ነሰነሰ (ነስነሰ): በቀላል በተነ፡ ዘራ፡ ጐዘጐዘ። "እከሌ ወዳጁ ስለ ሞተ ማቅ ለብሶ ዐመድ ነስንሶ ተኛ" (፩ሳሙ፡ ፩፡ ፲፪፣ ኤር፮፡ ፳፮፣ ማቴ፲፩፡ ፳፩፣ ራእ፲፰፡ ፲፱)

ነሰነሰ: ወዘወዘ፡ አንቀሳቀሰ። "ውሻ ጌታውን ባየ ጊዜ ዥራቱን ይነሰንሳል" "ቈላን" እይ።

ነሲቡ (አፈ ንጉሥ ነሲቡ): የአፄ ምኒልክ የፍርድ አንደራሴ ልጅ። አባቱን በኀጢአት ከሶ፡ በርሳቸው ዳኝነት በረታ ጊዜ "የአባት ዕዳ ለልጅ ነውና ጣለው" ብለው በተወራረደበት አርባ ጅራፍ ልጁን ገረፉ። ዳግመኛም አንድ ሰው አንዷን ሴት ለአንድ ሌሊት በአንድ አሞሌ ተዋውሎ ወሰዳትና ሚስት ኹና ዓመት ከተቀመጠች በኋላ አንድ አሞሌ ሰጥቶ ባባረራት ጊዜ ለአፈ ንጉሥ አቤት አለች። እሳቸውም ነገሩን "ሽማግሌ ይየው" ቢሉት እንቢ ስላለ፡ በወር ሒሳብ ፩፻፻፰፻ (ዐሥር ስምንት መቶ) ጨው እንዲሰጣት ፈረዱበትና ትዳሩን ለቆ ኼደ ይባላል።

ነሲቡ: የሰው ስም፡ ለአባቱ ዕድሉ ኹኖ የተሰጠው ማለት ነው።

ነሲብ: ዕድል፡ ግምት። "በነሲብ ግዛ" እንዲል እስላም።

ነሣ (ነሥአ): ከለከለ፣ ወሰደ፣ አራቀ። "እግዜር ሰጠ፡ እግዜር ነሣ። " "የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሣ። " "ሥጋ ሰጥተው ቢላዋ ነሡ። " "ለፈሪ ሜዳ አይነሡም። " (የባልቴት ግጥም): "እኒህ ሥሙ ለዝናም ጌታ ውሃ ነሡ። " "ድልን" "ኅብርን" "ፊትን" ተመልከት።

ነሣ: ቀነሰ፣ አጐደለ። (ሥጋ ነሣ): ተፀነሰ፣ ሰው ሆነ፣ ሥጋ ለበሰ።

ነሣ: ተቀበለ፣ ወሰደ። "ይህ ኅብስት ሥጋዬ ነው፡ ንሡ ብሉ" እንዳለ ጌታ በወንጌል።

ነሣ: ቻለ፡ ወሰነ (፪ዜና ፪፡ ፮)

ነሣ: ያዘ፣ ጨበጠ። በ፳፮ኛ ተራ "እጅን" አስተውል።

ነሣሣ: ወሳሰደ፣ ቀናነሰ፣ አጐዳደለ። "ነሣሣለትና አመጣው" እንዲል ተርጓሚ።

ነሳነሰ: በታተነ፡ ጐዛጐዘ።

ነስር (ዐረ፡ ነጽር): መዋኢ፡ አሸናፊ (ማር፡ ይሥ፡ መቅ)

ነስር: ከአፍን የሚወርድ የደም ፈሳሽ።

ነስናሽ (ሾች): የነሰነሰ፡ የሚነሰንስ፡ በታኝ፡ ጐዝጓዥ፡ ወዝዋዥ።

ነረተ: መታ፡ ጠሀለ፡ ደበደበ።

ነረተ: ነፋ፡ ቀበተተ (ሆድን)

ነረነረ: ነርነር አለ፡ በኀይል ተሰማ (ወፍራም ድምጥ ሰጠ - በገናው፣ ከበሮው)

ነራች: የነረተ፡ የሚነርት፡ ነፊ፡ መቺ።

ነርነርቱ: ኣደዝዳዥ፡ አነጥናጭ፡ ዐፍለኛ (ኰረዳ)

ነሸረ (ዕብ፡ ናሻር): ኣባሰ፡ አመረረ (ጥልን)፡ ነጯ፡ ፈተገ፡ መለጠ (ገላን)

ነሸቀ) ተናሸቀ (መጣላት/መቀያየም)

ነሸቀ) ተናሸቀ: በክፉ ተጋጠመ፣ ተጣላ፣ ተቀያየመ፣ ተናሸረ። "በሸቀን" ተመልከት።

ነሸጠ: አሳሰበ፡ አነሣሣ (ጠብን፣ መጥፎ ነገርን)"በል በል" አለ። "ሸፈጠን" አስተውል።

ነሸጥ: ሸፈጥ።

ነሺ: የነሣ፣ የሚነሣ፡ ከልካይ፣ ተቀባይ፣ ወሳጅ።

ነሺነት: ከልካይነት፣ ተቀባይነት።

ነሽ (ነየኪ): አንቺ ነሽ፡ አለሽ።

ነሽ: የቅርብ ሴት ነባር አንቀጽ። "ነውን" እይ።

ነቀለ (ነቂል፡ ነቀለ): መዘዘመነገለኣፈለሰአነቀለአወጣአወለቀ (የአበባ እኸልን፣ እንግጫን፣ ጥርስን፣ የእጅና የእግር ዐጥንትን፣ ማንኛውንም ነገር)

ነቀለ: ሰውን ከርስቱ፣ ከመሬቱ ላይ አራቀ፡ አስወገደ።

ነቀለ: ኣነሣ፡ ያዘ።

ነቀለ: እግሩን አነሣ፡ ስፍራ ለቀቀ።

ነቀላ: የመንቀል ሥራ፡ መዘዛ።

ነቀል ተከል: የዘላን ጐዦ።

ነቀል: "ነቃይ" ጋር ተመሳሳይ፡ ያነሣ፡ የያዘ። "ብር ነቀል፣ ጦር ነቀል" እንዲሉ።

ነቀልቃል፡ ወላፈን፡ ነበልባል፡ ነብ፡ ነድ፡ (ግእዝ)

ነቀምቴ: የነቀምት ተወላጅ፡ የነቀምት ሰው። "ነቀምቴ በጋልኛ ተከተተች" ማለት ነው።

ነቀምት: የከተማ ስም፡ በወለጋ ክፍል ያለ አገር። ዐማሮች ግን "ለቀምት" ይሉታል።

ነቀሰ: መሰከረ፡ ያየውን ተናገረ፡ ነገርን አሻሻለ፡ "ይኸ ቢኾን ይኸ ነው" አለ።

ነቀሰ: ቀነሰ፡ ዋጋ አጐደለ። "ነቀሰ ዐረብኛ፡ ቀነሰ ዐማርኛ ነው"

ነቀሰ: እሾኸን ነቀለ፡ አወጣ። "ሾኸን" እይ።

ነቀሰ: ወርቅንና ብርን፣ ዕንጨትን፣ የጌጥ ዕቃን አስጌጠ፡ ሸለመ።

ነቀሰ: ጠቀጠቀ፡ ወቀረ፡ ወጋ፡ አጠቈረ (ጥርስን፣ ገላን) (ተረት) "ያልወጋኝ ነቀሰኝ"

ነቀሰ: ጠጕርን አበጠረ፡ ጥጥን አጠራ፡ ሰውነቱን አሳመረ።

ነቀሳ: ንቅሻ፡ የመንቀስ፣ የማጥራት፣ የማበጠር ሥራ።

ነቀስ: "ነቃሽ" ጋር ተመሳሳይ።

ነቀረ) አነቀረ: ጠጠ፡ አጝጠጠ፡ ጨለጠ፡ ጨርሶ ቀዳ። "መነቀረን" እይ፡ የዚህ መስም ግስ ነው።

ነቀርሳ: የቍስል ስም፡ የሰውን ገላ የሚነድል፣ ደምን የሚያነቅር በሽታ። ኹለተኛ ስሙ "ምሽሮ" ነው።

ነቀሸ: ተሰበረ፡ ተቀለጠመ።

ነቀበ: በሳ፡ ነደለ፡ ስፌት ሰፋ።

ነቀነቀ (ትግ፡ ቀንቀነ): ቀሰቀሰ፡ ወዘወዘ፡ ናጠ፡ አናወጠ፡ አንገሸገሸ (ሰውን፣ ዐልጋን፣ ሀንገትን፣ ራስን) (ኢሳ፲፫፡ ፲፫) በግእዝ መሠረቱ "ነክነክ" ነው፡ "ነከነከን" እይ።

ነቀነቀ: ሰበቀ (ጦርን)

ነቀነቅ: ነቅናቃ: የተነቀነቀ፡ የተወዘወዘ፡ ወዝዋዛ።

ነቀዘ (ነቅዘ): ጠነጠነ፡ ዐመድ ኾነ። "ብሳና ይነቅዛልን" ቢሉ፡ "ለእንጨት ኹሉ መንቀዝን ያስተማረ ማነው?" (ተረት): "ዝም አይ ነቅዝም"

ነቀዛም: ነቀዝ ያለበት፡ ባለነቀዝ።

ነቀዝ (ዞች): ቍንቍኔ፡ ከእንጨት ባሕርይ የሚፈጠር ትል (ወይራን፣ ጥድን፣ ኮሶን፣ ዋንዛን፣ ዝግባን፣ አርዝን፣ ሀሎን የማይመስለውን ዕንጨት ኹሉ ውስጥ ውስጡን በልቶ ዐመድ ያደርጋል)፡ ዳግመኛም ጥንጣን ይባላል።

ነቀዝ (ፃፄ): ከእኸል ውስጥ የሚፈጠር ባለክንፍ ተንቀሳቃሽ፡ ከቅማል ከፍ ይላል፡ ጥሬ እኸልን ያበላሻል (ማቴ፮፡ ፳)

ነቀዝ: ሆዳም፡ በላተኛ ሰው።

ነቀደ (ደነቀ): (ትግ፡ አንቀደ) ዐሰበ፡ ተጋ (ዘየደ)፡ ድንቅ አደረገ፡ ተናገረ፡ ተረከ።

ነቀፈ (ነቂፍ፡ ነቀፈ፡ ቀረፈ): የሰውን ስምና ግብር አጥላላ፡ ሰደበ፡ ዋጋና ክብር ኣሳጣ፡ ናቀ፡ አቀለለ፡ አጸየፈ፡ አነወረ፡ ተቈጣ፡ ገሠጸ፡ ወቀሠ፡ ዘለፈ። ፫ኛውን "ዐቀፈ" እይ።

ነቀፋ: ነቀፌታንቅፊያመንቀፍስድብንቀትቍጣወቀሣ

ነቍጣ: በበግ፣ በፍየል ገላ ላይ ያለ ጥቃቅን፣ ነጠብጣብ፡ ንጣት፡ ነጭነት (ዘፍ፴፡ ፴፭)

ነቍጣ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ። ዐረብም አንዱን ጠብታ "ኑቅጣ" ይለዋል።

ነቍጥ (ጦች): የነጥብ ስም፡ የቃል፣ የንባብ መለያ (ኹለት ጠብታ ()፡ አራቱም ጦብታ ()) ነቍጥ ይባላል።

ነቂ (ነቃሂ): የሚነቃ፡ የሚተጋ።

ነቂስ: ኹሉ፡ ምሉ፡ ጠቅላላ።

ነቃ (ነቅሀ): ተቀሰቀሰ (ከእንቅልፍ)ተነሣብንን አለ (፩ነገ፡ ፫፡ ፲፭)

ነቃ (ነቅዐ። ዕብ፡ ናቃቅ): በጥቂቱ ተሠነጠቀተተረተረ (የተረከዝ፣ የንጨት፣ የግንብ) (ግጥም)"ብርሌ ከነቃ አይኾንም ዕቃ"

ነቃ በል: ጠንቀቅ በልትጋ

ነቃ ነቃ አለ: ሰውነቱን ጠበቀ (በልብስ፣ በጽዳት)

ነቃ አለ: ጠንቀቅ አለ

ነቃ: ተጋተጠነቀቀ

ነቃ: ወጣመነጨፈለቀተገኘ

ነቃላ: ንቅልንቁል፡ የተነቀለ፡ የተመዘዘ፡ የተመነገለ።

ነቃሽ (ሾች): የነቀሰ፡ የሚነቅስ። "ጠጕር ነቃሽ፣ ጥርስ ነቃሽ" እንዲሉ።

ነቃሽ: መስካሪ፡ ምስክር፡ እውነትን ከሐሰት ነቅሶ (ለይቶ፣ አጥርቶ) የሚናገር።

ነቃሽነት: ነቃሽ መኾን፡ ምስክርነት።

ነቃሾች: ምስክሮች።

ነቃቀለ: መዛዘዘ፡ መነጋገለ።

ነቃቃ: ተሠነጣጠቀ

ነቃዥ: የነቀዘ፡ የሚነቅዝ (ዕንጨት፣ እኸል፣ ሣር)

ነቃይ (ዮች): የነቀለ፡ የሚነቅል። "ዐተር፣ ሽንብራ፣ ተልባ፣ ምስር፣ ጓያ፣ ድንኳን ነቃይ" እንዲሉ።

ነቃይ ተካይ: ሰውን ከምድርና ከሥራ ላይ የሚተክልና የሚነቅል (ሹም፣ ዳኛ፣ ባለሥልጣን)

ነቃፊ (ዎች): የነቀፈ፡ የሚነቅፍ፡ ሰዳቢ።

ነቈረ (ነቊር፡ ነቈረ): ጠቅ አደረገ፡ ነከስ፡ ወጋ፡ በሳ፡ ቀደደ።

ነቈጠ (ነቍጠ): ነጠበ፡ ጠብ አለ።

ነቅ (ነቅዕ): ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ እንከን "ቄስ ነቅ የሌለበትን ኅብስት መርጦ ወደ መንበር ያቀርባል"

ነቅ: ምንጭመነሻ

ነቅናቂ (ቆች): የነቀነቀ፡ የሚነቀንቅ፡ ወዝዋዥ።

ነቅዐ ኀልዮ: ማሰብ መገኛልብ

ነቋሪ: የነቈረ፡ የሚነቍር።

ነቋራ (ነቋር): አንድ ነገር ያነቈረው፡ ኣንድ ዐይና።

ነበልባል (ሰው): ለፍላፊ፣ ተናጋሪ፣ አፈኛ ሰው።

ነበልባል (እሳት): የእሳት ላንቃ፡ ነዲዱ (ነቡ) ብርሃኑ፣ ወላፈኑ።

ነበልባል: የእሳት ላንቃ (ከበለ ግስ የመጣ)

ነበልባሎች: ወላፈኖች፣ ለፍላፊዎች።

ነበረ (ነቢር፡ ነበረ): አለ፣ ኖረ፣ ቈየ፣ ተቀመጠ። "እግዜር ከዓለም አስቀድሞ ነበረ። " "አለኝ እንጂ ነበረኝ አይጠቅምም"

ነበረ: በ፱ ሰራዊት ሲዘረዝር ይላል።

ነበረረ (ነበረ): አንዱ "" ተቀጽላ ነው፡ ፈጽሞ አረጀ፣ ከሳ፣ ደረቀ (ሰውነቱ)፡ ሰለለ (ድምፁ) (ብዙ ዘመን ከመኖር የተነሣ) "ዠበረረን" እይ።

ነበረር/ነብራራ: የነበረረ፣ የሚነበርር፡ ዠብራራ።

ነበረሽ: አለሽ፣ ኖረሽ።

ነበረን: አለን፣ ኖረን።

ነበረኝ: አለኝ፣ ኖረኝ።

ነበረኸ: አለኸ፣ ኖረኸ።

ነበረው: አለው፣ ኖረው።

ነበረዎ: አለዎ፣ ኖረዎ።

ነበራርት (ቶች): የነብር ዲቃላ፣ ነብር የሚመስል፡ ጥቍረትና ንጣት ቅላት አለው።

ነበራት: አላት፣ ኖራት።

ነበራቸው: አላቸው፣ ኖራቸው።

ነበራችሁ: "ለእናንተ ዕውቀት ነበራችሁ። "

ነበር: በትንቢትና በቦዝ መጨረሻ እየገባ የቈየ፣ የዘገየ፣ ኀላፊ ይሆናል። "ዐወቅ ነበር""ዐውቄ ነበር" "መዠመሪያውን አለ" እይ።

ነበር: ነበረ፡ ከ፣ የ፣ ሲሰማሙት ከነበር፣ ከነበር ይሻላል።

ነበርነ ባይ: ወገኛ።

ነበርና: አለና፣ ሆነና፣ ተደረገና።

ነበበ (ነቢብ፡ ነበ): ተናገረ፣ አለ።

ነበበ: ተሠነጠቀ፣ ተተረተረ (ራስ፣ ቅሉ፣ እንስራው)

ነበበ: ነደደ (እሳቱ)

ነበበ: ከበረ፣ ገነነ። "የአቶ እከሌ ቤቱ ነበበ"

ነበበ: ጮኸ፣ ተሰማ (ከበሮው)

ነበነበ (ነበበ፡ ዐረ፡ ነብነበ): ንብኛ ጮኸ፣ ባለማቋረጥ ተናገረ፣ ነዘነዘ።

ነበነብ/ነብናባ: ነዘነዝ፣ ነዝናዛ፣ ለፍላፊ።

ነበዘ (ነቢዝ፡ ነበዘ): ቀማ፣ ገፈፈ።

ነበዘ: ልብ አሳጣ፣ ለወጠ። "ነፈዘን" ተመልከት።

ነበዘ: መረዘ። "ቀለሙ ልብሱን ነበዘው። "

ነበዘ: ሰለበ፣ ቈረጠ።

ነበዘ: አከሳ፣ አገረጣ።

ነበዘው: ቀለመው፣ መረዘው።

ነበዘው: ቀማው፣ ገፈፈው።

ነበጀለ (ነበበ፡ ጀለ): ንባበ ጅል፣ ነገረ በክ ሆነ፡ ነኈረጠ፣ ቂልኛ ተናገረ። "ጀለን" እይ።

ነበጀል: ነኈረጥ።

ነቢ (ዐረ): ነቢይ። "ካላህ አልሆንኩ ከነቢ" እንዳለ እስላም።

ነቢብ: መናገር (ግእዝ) "በነቢብ በገቢር" እንዲል ቄስ።

ነቢየ ሐሰት: ያላየውን አየሁ ያልስማውን ሰማሁ የሚል የሐሰት ነቢይ።

ነቢየ ጽድቅ: የውነት ነቢይ።

ነቢዩ ሕዝቅኤል: በባቢሎን ራእይ ያየበት ስፍራ።

ነቢያት: ቀድሞ ከሔኖክ በኋላም ከሙሴ ዠምሮ እስከ ጌታችን የነበሩ ትንቢተኞች፣ ትንቢት ተናጋሮች፣ ደጋጎች ሰዎች፣ ኀላፍያትንና መጻእያትን የሚያውቁ፡ በሕዝብ አነጋገር ነቢያቶች ይባላሉ።

ነቢያት: በዳዊት መዝሙር መጨረሻ ተጽፎ የሚገኝ ፲፭ የነቢያት ጸሎት።

ነቢይ: በሴት ለመናገር ነቢዪቱ ይላል።

ነቢይ: በቁሙ፡ ያለፈውንና የሚመጣውን ዐውቆ የሚናገር ሰው፣ ብቃት ያለው።

ነባ (ነብዐ): መነጨ፣ ወረደ፣ ፈሰሰ (እንባው)

ነባሪ (ዎች): የነበረ፣ ያለ፣ የኖረ፣ የቈየ፡ የዳኛ አቀማማጭ ምስክር።

ነባሪ: የዓሣ ቅጽል (ዓሣ)

ነባሪነት: ነባሪ መሆን፡ ኗሪነት፣ ተቀማጭነት።

ነባር (ሮች): ነባሪ፣ ኗሪ። ሴትና ወንድን ያስተባብራል።

ነባር አንቀጽ: በ፱ መደብ በኀላፊ ብቻ በራሱ ዝርዝር እየጨመረ የሚረባ፣ ትንቢትና ዘንድ ትእዛዝ አንቀጽ የሌለው፡ ተቀማጭ፣ የማይንቀሳቀስ ማለት ነው። "ነውን" እይ።

ነባር: ከአንቀጽ የማይወጣ ስም፡ "ውሃን" "አሞራን" የመሰለ።

ነባቢ: የነበበ፣ የሚነብ፣ የሚናገር፡ ተናጋሪ።

ነባቢት: የተናገረች፣ የምትናገር ነፍስ።

ነባዛ: ከሲታ፣ መጣጣ። "ፊተ ነባዛ" እንዲሉ።

ነባዛ: የተነበዘ፣ የተቀማ፡ ልውጥ፣ ልበ ቢስ። በግእዝ እንቡዝ ይባላል።

ነባይ: አማርኛ፡ ነቢይ ግእዝ ነው።

ነባይ: ደግ፣ ጻድቅ፣ የግዜር ሰው።

ነቤላ: በበረሃ የሚበቅል የምድር ፍሬ፡ ግመሎች ምግብነቱን የሚወዱት።

ነብ: የእሳት ላንቃ፡ ጂ የሚል ነድ።

ነብሩ: ነብር፣ የርሱ ነብር።

ነብሩቴ: ሽልምልም፣ ባቡቴ።

ነብሪድ: እንደዚሁ፡ ትግሮች ንቡረ እድን "ነብሪድ" ይሉታል።

ነብራም: ነብር ያለበት ዱር፣ ባለነብር።

ነብር (ነምር): የአውሬ ስም፡ የታወቀ ዥጕርጕር አውሬ፣ ቍጡ፣ የፍየል ጠላት (ተባቱም፣ እንስቱም)

ነብር ሲርበው: የሞተ መስሎ በዠርባው ይተኛና እጆቹን ወደ ላይ ያንጨፈርራል፡ ጆፌ አሞራም በቀረበው ጊዜ ይዞ ይበላዋል።

ነብር ሳይዝ አይሞትም: አንድ ሰው ሳያጠፋ አይገደልም።

ነብር አጥማጅ: ነብርን በወጥመድ የሚይዝ። "ስማርድን" አስተውል።

ነብር ወለደች: በፀሓይ ዝናብ ሲጥል እረኞች "ነብር ወለደች" ይላሉ።

ነብርማ (ነምራዊ): ነብር የሚመስል፡ ፍየል፣ ጠራጠርማ።

ነብሮ: ቃለ አክብሮ፡ ነብር ሆይ ማለት ነው። "አያ ነብሮ" እንዲሉ ልጆች በተረት።

ነብሮ: የሥጋ ስም፡ ንጣትና ብርንዶነት ያለው የጡንቻ ሥጋ።

ነብሯ/ነብሩት: ያች ነብር።

ነብጃላ: ነኍራጣ።

ነተረ: ሖረጠ፡ ሖመጠጠ፡ ሸመጠረ።

ነተረ: ወጠረ፡ ነፋ።

ነተረከ (ተረከ): መነቸከ፡ አተከረ፡ ነዘነዘ፡ ጨቀጨቀ፡ በቀተ። "ከዚህ ቀደም እንዲህ ሠራኸ፣ አደረግኸ" አለ።

ነተረክ: ነትራካ: ነዘነዝ፡ ነዝናዛ፡ ጭቅጭቃ።

ነተበ (ነቲፍ፡ ነተፈ): ተጐዳ፡ ማለቅ ዠመረ (የመጫሚያ፣ የልብስ) ፈለግ አወጣ (የተረከዝ)

ነት (ነትዕ): ቀይ ቈርበት፡ ተንቤን።

ነት: ዐመለ ልስልስ ሰው።

ነትራኪ: የነተረከ፡ የሚነተርክ፡ ጨቅጫቂ።

ነትጋራ: (እነት)

ነች: ናት (ነያ): እሷ ነች፣ ናት፣ እለች።

ነች: ናት፡ የሩቅ ሴት ነባር አንቀጽ። "ነውን" እይ።

ነችሽ ነችሽ አለ: ኵርኵር አለ።

ነችሽ: የእንስት አህያ መጥሪያ። " ነዪ፣ ችሽ፣ ቲውሽ" የማለት ለውጥ ነው።

ነነ ነን: "እኛ" የሚሉ ወንዶችና ሴቶች ነባር አንቀጽ "ነውን" ተመልከት።

ነነ: ቀጠነ፣ አነሰ፡ አማረ።

ነነዌ: የ፫ ቀን ጦም (የነነዌ ሰዎች የጦሙት) ባላገር ግን "ነይነይ" ይላል።

ነነዌ: የአገር፣ የከተማ ስም፡ በእስያ ክፍል ያለች ጥንታዊት የአሶር ከተማ (ዮናስ የሰበከባት)

ነነጭ፣ ነጭናጫ: የተነጫነጨ፣ የሚነጫነጭ፡ ጨቅጫቃ፣ ብስጩ።

ነና፣ መወራረሳቸውን አስተውል።

ነን (ነነ): ነየነ፡ እኛ ነን፣ ነነ፣ አለን፣ ነ።

ነኛ (አነኬ): ቃለ አጋኖ። "አባት ልጆቹን ከናንተ ዛሬ የሚላከኝ ማነው ብሎ ሲጠይቅ፡ ፈቃደኛው እኔ ነኛ ይላል። "

ነኝ (ነየ): እኔ ነኝ፣ ኾንኹ፡ አለኹ (ዮሐ ፲፫፡ ፴፫)

ነኝ: "እኔ" የሚል፣ የምትል የወንድና የሴት ነባር አንቀጽ "ነውን" እይ።

ነአኵተከ: ሁለተኛ የዘወትር ጸሎት አባ ጊዮርጊስ የደረሱት።

ነከለ) ነቀለ: አነከለ (እግሩን) ነቀለአነሣዐነከሰ

ነከሰ (ነሲክ፡ ነሰከ): ዐኝ አለ፣ ዘነተረ፣ ዘበተረ፣ በላ፣ ቦጨቀ፣ ቦተረፈ፣ ዘከዘከ፣ ዘረከተ፣ ዘለዘለ፣ ዘተዘተ። "ዘረገፈን" ተመልከት። (ጥርሱን ነከሰ): ጨከነ ዕመምን ቻለ ታገሠ (ከንፈሩን ነከሰ): ዛተ አስፈራራ "ገመጠን" እይ።

ነከሰ: ነደፈ ጠቅ አደረገ "እባብ ነከሰው፣ ጊንጥ ነከሰው" እንዲሉ።

ነከሰ: ፈጽሞ ጠላ መረዘ

ነከሳ: መንከስ

ነከረ (ነኪር፡ ነከረ): ለየ አስገለለ (ተረት): "ምከረው ምከረው፡ ባይሰማ ንከረው (ከሕዝብ፣ ከማኅበር) ለየው። "

ነከረ (ጠምዐ): ዘፈ አራሰ ዐለለ (ማለትም አዘፈዘፈ፣ ረጠብ አደረገ)

ነከረ: አጠመቀ ዘፈቀ አጠለቀ ዘፈ

ነከረ: ጠለቀ አጠቀሰ (ዮሐ ፲፫፡ ፳፮)

ነከራ: ዝፍዘፋ

ነከርት: ሞኝ ቂል ዘርፋፋ "እቂልነት ባሕር ነክሮ ያወጣው፣ ከብልኅ የተለየ። "

ነከርት: ጥቍሬታ

ነከርቶች: ሞኞች ቂሎች ጠባየ ልዩዎች

ነከተ: ተሰበረ ደቀቀአነሰ

ነከነከ (ነክነከ): አብዝቶ በላ በግእዝ ግን ወዘወዘ ማለት ነው፡ ይኸውም መንጋጋን መነቃነቅ ያሳያል።

ነከነከ: ነዘነዘ መታ "ሌሊት ዝናሙ ሲነከንከው ዐደረ። "

ነከፈ (ትግ): ለኰስ አቃጠለ

ነከፈ: ቈለ ጀለ "ነቀፈን" ተመልከት።

ነኪ: የነካ፣ የሚነካ።

ነካ (ነከየ): ዳበሰ ዳሰሰ ደረሰ ጐነጠ ድል አለ አቈሰለ ገጠበ በደለ "አብ ሲነካ ወልድ ይነካ። " "እከሌን ጠላቶቹ ዐር የነካው ዕንጨት አደረጉት። " "ጐሸመጠን" "ጣቈሰን" ተመልከት።

ነካ (ነክይ): መንካት

ነካ ነካ አደረገ: ዳበስ ዳበስ አደረገ

ነካ አደረገ: ዳበስ አደረገ ነካ

ነካሪ: የነከረ፣ የሚነክር።

ነካሽ (ሾች): የነከሰ፣ የሚነክስ፡ ዘንታሪ "ዐዛዬን ነካሽ" እንዲሉ። (ጠፍር ነካሽ): የፈረስ፣ የበቅሎ ዕቃ ሰፊ፡ የስራ ፈቶች አማርኛ ነው።

ነካታ: የነከተ (ሰባራ)

ነካች: የሚነክት (ደቃቂ)

ነካከሰ: ዘነታተረ ቦጫጨቀ

ነካከተ: ተሰባበረ

ነካካ: ደባበሰ መላልሶ ነካ

ነክ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ። "ጎላ ነክ" "ሰንበት ነክ" እንዲሉ።

ነክናኪ: የነከነከ፣ የሚነከንክ፡ ነዝናዥ

ነኰረ (ነቈረ): አነኰረወጋ ዐረሰ አማሰለ ገለበጠ (የውስጡን በላይ፣ የላዩን በውስጥ አደረገ)

ነኰተ: እንደ እንኵቶ ሆነነከተ

ነኳታ: የነኰተ (ነካታ)

ነኸ: አንተ ለሚባል፡ የቅርብ ወንድ ነባር አንቀጽ "ነውን" እይ።

ነኽ (ነየከ): አንተ ነኸ፡ አለኸ። (ግጥም): "እንዴት ነኸ እንዴት ነሽ አንባባልም ወይ፡ ሰው ካባቱ ገዳይ ይታረቅ የለም ወይ። "

ነኾለለ (ኮለለ): ደነቈረ (አእምሮውና ንግግሩ ተበላሸ)ራሱ ዞረ

ነኾለል ነኹላላ: የነኾለለ፡ ደንቈሮ ሞኝ ቂል ነጕላ እንቆል

ነወረ (ነዊር፡ ኖረ): ኾነ፣ ተደረገ፣ ተገኘ (ነውሩ)

ነወረ: ኖረ።

ነወር አለ: ብድግ አለ፣ መቀመጫውን ለቀቀ።

ነወር: ሰው በመጣ ጊዜ ተቀማጭ ተነሥቶ የሚናገረው የከበሬታ ቃል: ትርጓሜው "ኑሮ ተቀመጥ" ማለት ነው።

ነወርታ: ነወር ማለት፡ ሰውን ማክበር።

ነወነ: ጨቀጨቀ። "ነጩን" እይ።

ነወዘ: ናወዘ (ናወተ): ዞረ፣ ባከነ፣ ዋተተ፣ ተንከራተተ።

ነወጠ (ትግ፡ ነወጸ): ነቀነቀነ፣ ናጠ፡ አወከ፣ ጸጥታ አሳጣ (አገርን፣ ሕዝብን፣ ልብን፣ ናላን)

ነዋ: ነው፡ ከስም ምትክና ከደቂቅ አገባብ ጋራ በቃለ አጋኖ ሲነገር፡ "እሱ ነዋ" "እንዲህ ነዋ" "እንዴት ነዋ" ያሠኛል (፪ሳሙ ፬፡ ፲፩) በግእዝ ግን እንሆ ማለት ነው። "ሸነን" ተመልከት።

ነዋ: "ነው" ቃል አጋኖ (ነው)

ነዋሪ (ዎች): ኗሪ።

ነዋሪነት: ነዋሪ መሆን፣ አለመጥፋት፣ አለመታጣት።

ነዋዛ: ናዋዥ፣ የናወዘ፣ የሚናውዝ፡ ዘዋሪ፣ ባካና።

ነዌ: የሰው ስም፡ ጌታችን በወንጌል የተናገረው ባለጠጋ። ንዋያም፣ ገንዘባም ማለት ነው (ኪ፡ ወ፡ ክ)

ነዌ: የኢያሱ አባት (ኢያ ፩፡ ፩)

ነው (ነዋ፡ ነዮ፡ ናሁ): በአንድ የሩቅ ወንድ ስም የሚነገር ነባር አንቀጽ። በጥያቄና በስም ሲያስር "ከሰማይ የወረደ፣ ወደ ሰማይ የወጣ፣ ዳግመኛ የሚመጣ ማነው?" ብሎ ለሚጠይቅ፡ "ክርስቶስ ነው" ተብሎ ይመለሳል። "ያይጥ ሞት የድመት ሰርግ ነው" "ሰውን ማመን ቀብሮ ነው" "እኮንና ስበው ሲያስቀሩት፡ 'ነው እኮን ነውና' ያሠኛል" "ነው" ሳይጻፍና ሳይነገር በማሰሪያነት ተመርምሮ ይገለጣል። "የፈሪ በትር ዐሥር" እንዲሉ።

ነው: አለ። "እሱ እቤት ነው" ከጥያቄ ጋራ ሲነገር "ነውን" ይላል። በ፰ ሰራዊት ተዘርዝሮ ማሰሪያ ሲሆን።

ነውረ ሥጋ: ኮሶ፣ ወስፋት፣ አደፍ።

ነውረኛ (ኞች): ጕደኛ፡ ነውር አድራጊ፣ ባለነውር (፪ጴጥ ፪፡ ፲፫)

ነውረኛነት: ነውረኛ መሆን።

ነውራም: ነውር ያለበት።

ነውር ነው: "እንኳን ሊሠሩት ሊሰሙት አይገባም"

ነውር ጌጡ: ልክስክስ፣ "ይሉኝ አይል"

ነውር: በሰው፣ በእንስሳ ገላ ላይ ያለ ዕብጠት፣ ጕድለት፡ ላይን የሚያስቀይም፡ ክፉ ግብር፣ ኀጢአት (ስካርን፣ ምንዝርን የመሰለ)

ነውጠኛ (ኞች): ነውጥ አድራጊ፣ ባለነውጥ፣ አዋኪ።

ነውጠኛነት: ነውጠኛ መሆን።

ነውጡ: የሰው ስም፡ የርሱ ነውጥ።

ነውጤ: ዝኒ ከማሁ፡ የኔ ነውጥ ማለት ነው።

ነውጥ: ሁከት፡ የመናወጥ ኹኔታ።

ነዉ (ነጻዪ): የነጩ፣ የሚነጭ፡ ነቃይ፣ ቦጫቂ።

ነዎ: ነኹ፡ "ርስዎ ነዎ ነኹ" አሉ (ግጥም) "እንዴት ነኹ አቡዬ" እንዳለ ታቦት ዘፋኝ።

ነዘለ: (ዐረ) ወረደ፣ ተቈለቈለ። "መነዘለን" እይ፡ የዚህ ባዕድ ግስ ነው።

ነዘረ (ነዚር፡ ነዘረ): ወረወረ (በትር)፡ አሳረፈ (በሰው ላይ)

ነዘረ: በመርዝ ወጋ፣ ጠቅ አደረገ፣ ነደፈ፡ ጠዘጠዘ፣ ነዘነዘ፣ ቀየ (የቍስል) ነዘረ የፍላጻ ምስጢር አለበት። "መነዘረን" እይ፡ የዚህ መስም ግስ ነው።

ነዘር፣ ነዝር: ተናዳፊ ከይሲ (እስራኤልን በበረሓ እየነደፈ የገደላቸው) "ነዝር እባብ" እንዲሉ።

ነዘነዘ (ነዘዘ): ጨቀጨቀ፣ ነተረከ፣ አተከረ (ዘፀ ፳፪፡ ፳፭፣ ምሳ ፮፡ ፫፣ ኤር ፯፡ ፲፯፣ ሉቃ ፲፸፡ ፭)

ነዘነዘ: ጠዘጠዘ፣ ቈረጠመ፡ ጤና ነሣ።

ነዘነዝ፣ ነዝናዛ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ ጨቅጫቃ (ምሳ ፲፬፡ ፳፱)

ነዘዘ (ሐዘዘ): ብን፣ ትን አለ፡ ወጣ፣ ፈሰሰ።

ነዘገ: ዐከከ፣ ፎከተ (ዘር)

ነዘፈ (ምጥዋ፡ ነዝፈ): ለበሰ። (ወነዘፈን) - አስተውል።

ነዘፈ (ዐረ፡ ነጸፈ): አጠራ፣ አጸዳ፣ ነጣ፡ ንድፍ አስመሰለ።

ነዚፋ: ጥሩ፣ የጸዳ፣ ነጭ ነጠላ፡ ጸዐዳ ልብስ። ይህ ስም በሐረርጌ ይነገራል።

ነዛ (ነዝሀ): ረጩ፣ ፈነጠቀ፡ ውሃን፣ ደምን፣ በተነ (ጥሬ እኽልን በምጣድ ላይ) "መነዠኸን" አስተውል፡ የዚህ ዘር ነው።

ነዛ: አሠራጨ (መርዝን)

ነዛ: አዘመተ፣ አደረሰ (ወሬን)

ነዛ: ዘረጋ (መረብን)

ነዛሪ: የነዘረ፣ የሚነዝር፡ ጠንቀኛ።

ነዝናዥ: የነዘነዘ፣ የሚነዘንዝ ጨቅቂ።

ነዢ: የነዛ፣ የሚነዛ፡ በታኝ።

ነየለ: ኒል ነከረ ዐለለ

ነዪ (ንዒ): የቅርብ ሴት መምጣት ትእዛዝ አንቀጽ

ነያ (ንዒአ): ቃለ መልእክት

ነይ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ነይማ (ንዒ፡ እም): እናት ነይ፡ ዳግመኛም ቃለ አጋኖ ይሆናል።

ነይነይ: ነነዌ

ነይኮ (ንዒኬ): ቃለ አጋኖ

ነይጡን: ከፀሓይ ብርሃን ከሚነሡ ኮከቦች፡ ፯ኛው ኮከብ

ነደለ (ነዲል፡ ነደለ): ፈለፈለ፣ ሸረሸረ፣ በሳ፣ ሸነቈረ፣ ቀደደ፣ አፈረሰ (ድልድልን፣ ዦርን፣ ቤትን፣ ምርጊትን፣ ሸክላን፣ ስልቻን፣ ከረጢትን፣ ምድርን) (ኢዮ ፳፬፡ ፲፯፣ ዓሞ ፱፡ ፪፣ ማቴ ፯፡ ፲፱) "ዘነጠለን" አስተውል።

ነደላ: ሽንቈራ፣ ቀደዳ፡ የመብሳት፣ የመሸንቈር ሥራ።

ነደረ (ትግ፡ አንደረ): ዘለለ፣ ፈነጨ።

ነደቀ: ገነባ፣ ናሰ (ግእዝ)

ነደየ (ነድየ): ዐጣ፣ ደኸየ።

ነደደ (ነዲድ፡ ነደ): አለ፡ ተቃጠለ፣ እሳት ሆነ፣ ተንቦገቦገ። ኀላፊ ትንቢቱም "ይነዳል" ቢል እንጂ፡ "ይነድዳል" አይልም።

ነደደ: ዐዘነ፣ ተበሳጨ።

ነደድ ገደደ: ደገኛ፣ ቈለኛ ወንድሙን ስለ ኑሮው ቢጠይቀው፡ "ነደድ ገደድ" አለው ይላሉ፡ ይኸውም ንግግር ሙቀትንና ችግርን ባንድነት ያሳያል። "ወይናን" አስተውል።

ነደድ: በወሎ ክፍል ያለ አገር ወይም ሜዳ።

ነደድ: ነዳጅ (ከጨሰ ግስ የመጣ)

ነደፈ (ነዲፍ፡ ነደፈ): በተነ፣ ጠቅ አደረገ፡ ጠዘጠዘ፣ ወጋ፣ ነከሰ (በደጋን፣ በጥርስ፣ በመርዝ፣ በፍላጻ)፡ ጥጥን፣ ሰውን (፪ሳሙ ፲፡ ፳፬፣ መክ ፲፡ ፲፩፣ ራእ )

ነደፈ: ለካ፣ በረ (ኢሳ ፵፬፡ ፲፫)

ነደፈ: በነገር፡ ነካ።

ነደፈ: ጠቅ አደረገ፣ ወጋ።

ነደፋ: ንድፊያ፡ ብተና፣ ጥዝጠዛ፣ ውጊያ።

ነዲድ: ነበልባል። በግእዝ ግን መንደድ ማለት ነው።

ነዳ (ነድአ): ቀረበ፣ ወሰደ፣ ተከተለ (፩ሳሙ ፮፡ ፲፣ ሰቈ፫፡ ፪) (ተረት): "ሥብ ሊያርዱ ጕፋያ ይነዱ። " "የሰጡን ይሰጧል፡ የገዙን ይነዷል። "

ነዳ (አስቀመጠ/አስቀዘነ): በብዙ አስቀመጠ፣ አስቀዘነ። "ይኸ ቀጯቸው አያስቀምጥም ሲሉ ይኸው ይነዳዋል ሰራዊቱን ሁሉ" (አለቃ በዛብኸ)

ነዳሊ: የነደለ፣ የሚነድል፡ ሸንቋሪ።

ነዳላ: የተነደለ፣ የተበሳ (ብስ፣ ቀዳዳ) (ሕዝ ፰፡ ፯፣ ዓሞ ፬፡ ፫)

ነዳቂ: ገንቢ።

ነዳያን: ድኾች (የሰው እጅ አይተው የሚያድሩ)

ነዳይ: ድኻ፣ የለት ጕርሥ፣ ያመት ልብስ ያለው፡ ከምስኪን ይሻላል።

ነዳደለ: በሳሳ፣ ሸነቋቈረ፣ አፈራረሰ።

ነዳጅ (ነዳዲ): የሚነድ፣ የሚቃጠል (ዕንጨት፣ ቅባኑግ፣ ጋዝ፣ ነፍት፣ ስበርቶ፣ ቤንዚን)

ነዳፊ (ፎች): የነደፈ፣ የሚነድፍ፡ ወጊ፡ ንብ፣ ተርብ።

ነድ (ዐረ): ዑድ (የሚጨሽ ሽቱ)

ነድ: ቀይ ቀለም (ጥቂት ጠቈር የሚል)

ነድ: ነበልባል፣ ነደደ።

ነድ: እሳት የሚመስል ቀይ ዶቃ፣ ትልቅ ድባ።

ነድ: ዝኒ ከማሁ፡ የእሳት ላንቃ፣ ነብ።

ነዶ (ዕብ፡ ዐናድ፡ አሰረ። ትግ፡ ሐባ ንድእ፡ ነዶ): ታጭዶ ከነብሩ የታሰረ (የስንዴ፣ የገብስ፣ የጠመዥ፣ ያጃ ዛላ)

ነዶ: አንድነትን፣ አንድ መኾንን ያሳያል፡ ሲበዛ ነዶዎች ያሠኛል (ሩት ፪፡ ፯፣ መዝ ፻፳፯፡ ፯) "ሰነደቀን" እይ።

ነዶ: የሩቅ ወንድ ቦዝ አንቀጽ (ከመቃጠል ግስ የመጣ)፡ ለሰውነትም ይነገራል (ተቃጥሎ) "ዋይ ነዶ" እንዲሉ።

ነጂ (ነዳኢ): የነዳ፣ የሚነዳ፡ የሚቀርብ፣ የሚከተል፣ እረኛ። ባቡር፣ መርከብ፣ ኦቶሞቢል፣ ካሚዎን፣ አይሮፕላን፣ ጋሪ ነጂ ቢል፡ መሪ፣ ጠባቂ ማለት ነው።

ነጂዎች (ነጆች): የነዱ፣ የሚነዱ፡ እረኞች፣ ጠባቆች (ኢሳ ፫፡ ፲፪)

ነገ/ነግ: ንኡስ አገባብ፡ ማግስት፣ ሁለተኛ ቀን (ከዛሬ ቀጥሎ ያለው) "ለነገ አትበሉ፡ ነገ ለራሷ ታስባለችና።"

ነገለ (ነጊል፡ ነገለ): ከሥር ተነቀለ፣ ፈለሰ (የግንድ) ነገለ: ሠሠተ፣ ነፈገ፣ ጮቀ፡ ቸርነት ከልቡ ራቀ።

ነገሌ: ሥሥታም፣ ቀብቃባ፣ ብዙ የሚበላ።

ነገል: ሥሥት፣ ንፍገት።

ነገሠ (መግዛት/መነገስ) ነገሠ (ነጊሥ፡ ነግሠ): ተቀባ፡ ዘውድ ደፋ፣ ጫነ፣ ተቀዳጀ፡ ሉል ጨበጠ፡ ንጉሥ ሆነ፡ በዙፋን ተቀመጠ፡ ሠለጠነ፣ ገዛ፣ ነዳ፡ ከበረ፣ ገነነ፣ በዛ። ነገሠ: ወጣ፣ ዞረ፣ ዑደት አደረገ (ታቦቱ)

ነገሥት (መጽሐፍ/ንጉሦች) ነገሥት: ነገሥታት፡ ንጉሦች። በግእዝ "ነገሥት"ብዙ፡ "ነገሥታት"የብዙ ብዙ ናቸው። ነገሥት: የመጽሐፍ ስም፡ የእስራኤልን ነገሥታት ታሪክ የሚናገር መጽሐፍ።

ነገረ (መናገር) ነገረ (ነጊር፡ ነገረ): አለ፣ አወራ፣ በዦሮ አፈሰሰ፡ አስተማረ፣ አስጠና፣ ተረከ፣ ሰበከ፣ አስታወቀ፣ አሰማ፡ መሰከረ።

ነገረ ማርያም: የመቤታችን የሕይወት ታሪክ (ቅዱስ ቴዎፍሎስ የጻፈው)

ነገረ ሠሪ: በሰው ላይ ነገር የሚሠራ ክፉ፣ ማሽንክ፣ ተንኰለኛ፣ አሳባቂ፣ አዋሻኪ።

ነገረ ሰይጣን: " በለው ሲሲ በለው፡ ለከፋው ክፋው፡ ደስ ላለው ደስ በለው።"

ነገረ ሥራ: የአካል ኹኔታ፡ ጡት አዘራር ኹናቴ።

ነገረ ደብተራ: ተዛዋሪ፡ ሰዋስውኛ።

ነገረ ግልባጭ: የልጆች ቋንቋ (ቤት ውሃ በማለት ፈንታ ትቤ ሃው እየተባለ የኋሊት የሚነገር)

ነገረ ፈጅ: ነገር ጨራሽ፣ ጠበቃ፣ ተጋች፣ የነገር አባት።

ነገረለት: መሰከረለት።

ነገረልኝ: መሰከረልኝ።

ነገረበት: መሰከረበት።

ነገረተኛ (ኞች): ባለነገር፡ በርስቱ፣ በገንዘቡ ሙግት፣ ክርክር ያለበት ሰው። "ተኛን" ተመልከት።

ነገረኛ (ኞች): ነገር ወዳድ፡ ጨቅጫቃ። "ነገረኛ ናቸው፡ አርቃችኹ ቅበሯቸው።" "ከነገረኛ ሰው ሥንቅ አይደባልቁም።"

ነገረው: "ሰምቶ ዝም አለው" እንዲሉ ልጆች።

ነገረው: ሰደበው።

ነገሩ ዐል ኾነ): ከማይረባ ተቈጠረ፣ ሳይዝ ቀረ።

ነገሪቱ: ያች ነገር (ማር ፬፡ )

ነገር (ሮች): ወሬ፣ ቃል፣ ዝና፣ ሙግት፣ ክርክር። "ከነገሩ፣ ጦም ዕደሩ።" "ነገር ፈጣሪውን እሾኸ፣ ዐጣሪውን።" "ነገር ከሥሩ፣ ውሃ ከጥሩ።" "ነገር አለብኝ ከማለት፣ ሥራ አለብኝ ማለት ይሻላል።"

ነገር ሠራ): ዐደመ፣ ቋጠረ፣ አሳበቀ፣ አዋሸከ፣ አጣላ።

ነገር ሠራ: አሳበቀ፣ አዋሸከ፣ አሳጣ።

ነገር ቋጣሪ: ነገር የሚቋጥር፣ ነገር ዠማሪ፣ አሢያሪ፣ ዐድመኛ።

ነገር ተዘረዘረ: ተነጠለ።

ነገር ዐላፊ: ትግሥተኛ።

ነገር አወጣ አወረደ: አሰላሰለ።

ነገር ዐዋቂ): ጠበቃ።

ነገር አዞረ: ለወጠ፡ ሌላ ስሜት ሰጠ፡ ምስጋናውን ስድብ አደረገ።

ነገር ዓለሙን ትቶታል: ቢሰጡት አልተቀበለም፡ ቢሰድቡት አልመለሰም።

ነገር ዓለም: የዓለም ነገር፡ ወይም ኹናቴ።

ነገር ወዳድ: ጨቅጫቃ፣ ነዝናዛ ሰው።

ነገር ዘሪ: ነገርን የሚዘራ፣ የሚበትን (ግብ ሐዋ፲፯፡ ፲፰)

ነገር ግን (ባሕቱ): ንኡስ አገባብ፡ የነገር አፍራሽ። "ጌታችን በሰውነቱ ታመመ፡ ነገር ግን በመለኮቱ አልታመመም። " "በሽተኛው ውሃ ይጠጣል፡ ነገር ግን እንጀራ አይበላም። " ይህ ደግሞ "ግን" የሚያዳምቅ ነው።

ነገር ግን: አንዳንድ ሰዎች ሻ፡ ሹ፡ ሺ፡ በማለት ፈንታ፧ እሻ፡ እሹ፡ እሺ፡ እያሉ ይጽፋሉ፡ ስሕተት ነው፡

ነገር ፈላጊ: ሳይነኩት የሚነካ፣ ሳይጣሉት የሚጣላ።

ነገር: "፪ኛው፡ ት፡ ይጠብቃል።"

ነገር: የማንኛውም ስምና ግብር በቂ። "እከሌ ከኼድክበት ስትመለስ ባዶ እጅኽን አትምጣ፣ አንድ ነገር ይዘኸ እንጂ።"

ነገርን ነገር ያነሣዋል: ያሳስበዋል፣ ያስታውሰዋል። "ነሣ" ብለኸ "አነሣን" ተመልከት።

ነገርን) አደመጠ ወይም ሰማ። ("ቀመቀመን" የሚለውን ይመልከቱ)

ነገሮችን ከፈከፈ: ደመደመ፣ ወይም (በተለይም ጠጉርን) አስተካከለ ማለት ነው።

ነገሮችን ደረደረ: ደረበ፣ አነባበረ፣ ዘመመ፣ ጐቸ፣ ወይም ቈለለ ማለት ነው።

ነገነገ (ነቀነቀ): ተሰማ (ድምፁ) ነገነገ: (ድምፅ ማሰማት)

ነጕላ (ሎች): ቂል፣ ሞኝ።

ነጋ (ነግሀ): ጠባ፣ በራ፣ ጧት ሆነ፡ ሌሊቱ ዐለፈ፡ መዓልቱ መጣ።

ነጋ ሌሊቱ: ሠጋ ሌማቱ (ችጋረኛ፣ ራብተኛ ሰው) "ሠጋን" ተመልከት።

ነጋ ጠባ: ጠባ ይቀድማል፡ "ዐረበ" ብለኸ "ዐረብን" እይ።

ነጋ: የሰው ስም፡ ሲነጋ የተወለደ ልጅ "ነጋ" ይባላል።

ነጋሢ: ነጋሽ። "ነጋሢ" የግእዝ፡ "ነጋሽ" የአማርኛ ነው። ነጋሢ: የሰው ስም፡ በ፲፯፻ . የነበረ የሺዋ ባላባት።

ነጋሪ (ዎች): የነገረ፣ የሚነግር፡ አውሪ፣ አስተማሪ (፪ጢሞ ፩፡ ፲፩) "ንባብ ነጋሪ" "ዜማ ነጋሪ" "ዐዋጅ ነጋሪ" "ቅኔ ነጋሪ" እንዲሉ።

ነጋሪተኛ (ኞች): ነጋሪት መቺ፣ ባለነጋሪት።

ነጋሪት (ቶች): በቁሙ፡ ጐኑ ሰፊ፣ ቁመቱ ዐጪር፣ እንደ አፍ የከበሮ ዓይነት መሣሪያ (በዐዋጅ፣ በግብር፣ በዘመቻ፣ በንግሥ ቀን የሚጐሸም፣ የሚመታ) ትርጓሜው በግእዝ "የነገረች" "የምትነግር" ማለት ነው። "ንጉሥ በሰፊ ነጋሪታቸው፣ በቈላፋ ዕንጨታቸው ዐዋጅ ነገሩ።" "ነጋሪት" እና "እት" በአማርኛ ይተባበራሉ። (ግጥም): "እንደነራስ ወሌ ነጋሪት የለኽ፡ በቶሎ አትኬድም ወይ ንጉሥ ሲጠሩኽ።"

ነጋሪት መታ: ጐሸመ (ድም ድም አደረገ)

ነጋሪት: የሠም፣ የሞራ ልጥልጥ።

ነጋሪነት: ነጋሪ መሆን።

ነጋሽ (ሾች): የነገሠ፣ የሚነግሥ፡ የንጉሥ ልጅ። "ባሕርን" እይ። ነጋሽ: የሰው ስም።

ነጋሽነት: ነጋሽ መሆን።

ነጋይ: የሚነግል፡ ተነቃይ።

ነግ (ነግህ): ጧት፣ ማለዳ።

ነግ ነግ አለ: ተነቃነቀ፡ አነገነገ።

ነግሥ (መጽሐፍ) ነግሥ: የመጽሐፍ ስም፡ እንደ መልክ ዐምስት ቤት እየሆነ በስንኝ የተደረሰ (በየወሩ ማሕሌት ሲቆም፣ ይልቁንም ታቦት በሚነግሥበት በዓልና ዐውዳመት የሚባል ድርሰት) ዐጤ ዘርዐ ያዕቆብ የደረሱት።

ነጐለ (መፈረጥ/ሞኝ መሆን) ነጐለ (ትግ፡ ለጐነ): ፈረጠ፣ ወጣ። ነጐለ: ቄለ፣ ተሞኘ።

ነጐለለ (መደንቈር) ነጐለለ: ደነቈረ፣ ደንቈሮ ሆነ። አንጐሉ ተናወጠ፣ ተነፋለለ።

ነጐለል/ነጕላላ: የነጐለለ፣ የሚነጐልል፡ ደንቈሮ፣ ነፈለል፣ ነፍላላ።

ነጐሊያም: ዝኒ ከማሁ፡ ንፍጣም።

ነጐሌ: የነጐል ዐይነት፣ ወገን።

ነጐል: ንፍጥ።

ነጐረ (መፍላት/መቅለጥ) ነጐረ: ፈላ፣ ቀለጠ፣ ፈሰሰ፡ ከእድፍና ከጕድፍ ተለየ (ቅቤው ያለቅመም)

ነጐድጓድ፡ የመብረቅ ግጭት፣ ጓታ፣ ግሩምና ታላቅ ድምጽ፣ የሚያስፈራ፣ የሚያንቀጠቅጥ።

ነጐድጓዶች፡ ግጭቶች፣ ጓታዎች (ራእ፲::)

ነጠለ (ነጸለ። ዕብ፡ ናጣል): ለጠጠ፣ ለየ፣ ነጠላ አደረገ፡ ዘረጋ።

ነጠለ፡ ለየ፡ ሽንጥ፡ አወጣ።

ነጠላ (ጨርቅ/ነገር) ነጠላ ትከሻ: የሌለው ሰው፡ ጥላ ቢስ፣ ከውካዋ፣ ቀላል። ነጠላ ግስ: ከፈለ፣ ዐወቀ እያለ በሩቅ ወንድ የሚነገር አንቀጽ። ነጠላ: ባላንድ ቍንጮ ተባት ዶሮ። ነጠላ: አጋማሽ፣ ቍና። ነጠላ: ዕጥፍ ያይዶለ፣ ኹለት ፈርጅ (ሸማ) የኩታ እኩሌታ (ዘፀ ፳፰፡ ፬፣ ፩ዜና ፲፭፡ ፳፯)

ነጠረ (መናር/መፍላት) ነጠረ (ነጢር፡ ነጠረ): ምድርን መታ፣ ናረ፣ ዘለለ፣ ጓነ፣ ወደ ላይ ተወረወረ። "መነጠረን" እይ፡ የዚህ መስም ግስ ነው። ነጠረ (ነጸረ): በሩቅ አየ፣ ተመለከተ። ነጠረ: ፈላ፣ ቀለጠ፣ ፈሰሰ፣ ተለየ፡ ጠለለ፣ ጠራ፣ ጥሩ ሆነ፣ ጣፈጠ፡ ተፈተነ፣ ተመረመረ።

ነጠረቀ: በኀይል መታ። "ነተረከን" እይ፡ አካኼዱ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።

ነጠረን፣ ፈነጠን እይ።

ነጠር: ጥራት፣ ጥሩነት፡ እውነት፣ ምርምር። "እከሌ በአፈሣ ተይዞ ነበር፡ ነገር ግን በነጠር ወጣ ተለቀቀ።"

ነጠቀ: ቀማ፣ ወሰደ፣ ሳበ፣ አፈጠነ (ገንዘብን፣ ሥጋን፣ ቅኔን፣ ድፎን፣ ዠርባን፣ እግርን) (ዮሐ ፯፡ ፲፭) "መነጠቀን" እይ። ነጠቀ: ቈነጠለ፣ ጥቂት ተማረ። ነጠቀ: አዳነ፣ አወጣ (መዝ ፻፴፮፡ ፳፬) ነጠቀ: የመነጠቀ ከፊል ነው።

ነጠቃ: መንጠቅ።

ነጠቅ ነጠቅ (ማፍጠን) ነጠቅ ነጠቅ አደረገ: እግሩን ፈጠን ፈጠን አደረገ።

ነጠቅ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ ለነጣቂ። "ጥራዝ ነጠቅ" እንዲሉ።

ነጠበ (መውደቅ/መቅሰም) ነጠበ (ነጥበ): ወደቀ፣ ጠብ አለ፡ ፈሰሰ። "በነጠበ በጐደለ" እንዲል ቀዳሽ ቄስ (ተገብሮ) ነጠበ: ደፈረ፣ ዘለፈ፣ ወረፈ፣ ሰደበ፣ ነቀፈ፣ አዋረደ፡ አሰረ (ገቢር)

ነጠባ: መንጠብ።

ነጠብጣብ (ቦች): ጠፈጠፍ፣ ብዙ ጠብታ፡ የቀለም፣ የመልክ ፍንጥቅጣቂ (ዘፍ ፴፡ ፴፭፣ ዘዳ ፴፪፡ )

ነጠነጠ (መደብደብ) ነጠነጠ (ትግ፡ ነጽነጸ፡ ነቀነቀ፡ አርገፈገፈ): ደበደበ። "ጠነጠነን" ተመልከት።

ነጠዘ (ዕብ፡ ናጣሽ፡ ጣለ): ተጣለ፣ እንዘጥ አለ (የምሉ እንስራ)

ነጠፈ (ነጢፍ፡ ነጠፈ): ጠለለ፣ ጠራ። ነጠፈ (ነፅፈ): ደረቀ፣ አቈረጠ (ጡቱ)

ነጠፈ) (ነጸፈ): አነጠፈ፡ ዘረጋ፣ አሰጣ፣ ሰተረ (ቍርበትን፣ ማንኛውንም ምንጣፍ፣ ደንጊያን)

ነጠፈ) (ነጸፈ): አነጠፈ፣ ዘረጋ፣ አሰጣ፣ ሰተረ (ቍርበትን፣ ማንኛውንም ምንጣፍ፣ ደንጊያን)

ነጠፈች: ወተቷን አቈረጠች፣ አቆመች (ላጝ)

ነጡር: ዘበኛ፣ ጠባቂ፣ ተመልካች።

ነጣ (ነጭ መሆን/ማጽዳት) ነጣ (ነጺሕ): መንጣት።

ነጣ (ነጻ መሆን) ነጣ (ነጽሐ): ነጭ ሆነ፣ ጠራ፣ ጸዳ፡ ከጥቍረት፣ ከእድፍ ራቀ። "ነጻን" ተመልከት። ነጣ የሕዝብ፡ ነጻ የካህናት ነው።

ነጣ ነጣ: መነጣጣት።

ነጣ አለ: ፈገግ አለ፡ ጥቂት ነጣ፣ ገረጣ።

ነጣ አወጣ: ገባርነትን አስቀረ (፩ሳሙ ፲፯፡ ፳፭)

ነጣ ወጣ: በራሱ ዐሳብ ዐደረ።

ነጣ: ዐከከ። "ዐጣን" "ፈገገን" "ገረጣን" እይ።

ነጣ: ጥጥ መሰለ፣ አረጀ፣ ሸመገለ። "አፍ፡ ቂጡ፡ ሸበተ፡ እንዲሉ። እንስሳትና፡ አራዊትም፡ ይሸብታሉ።"

ነጣሪ: የሚነጥር፣ የሚንር፡ ቀላ።

ነጣቂ (ቆች): የነጠቀ፣ የሚነጥቅ፡ ቀማኛ፣ ተኵላ፣ ጭልፊት፣ ባለዋገምት (መዝ ፳፪፡ ፲፫፣ ኢሳ ፳፬፡ ፲፯፣ ማቴ ፯፡ ፲፭፣ ፩ቆሮ ፮፡ ፲፱፣ ኢዮ ፲፪፡ )

ነጣቂነት: ነጣቂ መሆን፡ ቀማኛነት።

ነጣቢ: የነጠበ፣ የሚነጥብ፣ የሚወድቅ፡ ደፋር፣ አዋራጅ።

ነጣነት: ነጻነት።

ነጣይ: የነጠለ፣ የሚነጥል።

ነጣጠለ: ለያየ፣ ዘረጋጋ።

ነጣጣ: መላልሶ ነጣ።

ነጣፊ: የሚነጥፍ፣ የምትነጥፍ።

ነጣፋ: ዝርግ፣ ሰታታ (ድንጋይ)

ነጥር (ሮች/ልጥር): የሚዛን ልክ፣ ክፍልፋይ ብረት።

ነጥሮን: ባንዳንድ ስፍራ ከጨው ውስጥ የሚገኝ የልብስ ማጠቢያ ማዕድን (ከጥንት ዠምሮ የታወቀ) (ኤር ፪፡ ፳፪)

ነጥቆ: ቀምቶ። "ነጥቆ በረር" እንዲሉ። ነጥቆ: አንሥቶ። "ጋሻ ነጥቆ ዘገር ነቅንቆ።"

ነጥብ ( ): የቀለም ጠብታ፣ የቃል መለያ። "ተማሪው አለስሕተት ከነጥብ እነጥብ ያነባል" "ኹለት ነጥብ" "አራት ነጥብ" "ዘጠኝ ነጥብ" እንዲሉ። "ነቍጥን" "ይዘትን" "ሠረዝን" ተመልከት።

ነጥቦች: ኹለትና አራት ከነዚህም በላይ ያሉ ጠብታዎች።

ነጨ ዝንጀሮ: ዐመድማ (እንዳሞድ)

ነጨ: የነጭ ዓይነት።

ነጨሬ: ጯኺ፣ አልቃሽ።

ነጨቀ (መውጣት/መውረድ) ነጨቀ: ወጣ፣ ወረደ (ላይና ታች አለ) (ሸክሙ) ነጨቀ አልተለመደም። ነጨቀ: የመነጨቀ ከፊል ነው።

ነጩ (ነጸየ): አብዝቶ ነቀለ (ጠጕርን፣ ሣርን) "እንስሳ ሣር ነጭቶ ውሃ ተጐንጭቶ ያድራል።" ነጩ (ዘሌ፲፱፡ ፳፰): ወሸ፣ ፈተገ፣ ሞዠቀ፣ ላጠ፣ መለጠ፣ ቦጨቀ፣ አቈሰለ። ነጩ: ነቃቀለ፣ ላላጠ፣ መላለጠ። ነጩ: የሰውን ገንዘብ ነጠቀ፣ ወሰደ። ነጩ: ነጭ፡ የርሱ ነጭ። "ከጨርቅ ነጩ፣ ከበራ ልጩ፡ ይሻላል የቀረው ነው።" ነጩን: እይ።

ነጫነጭ: የነጭ ነጭ።

ነጫጭባ (ነጣ፡ ነጪ): ፊቱ/ፊቷ ነጫጭ ዕከክ፣ ፎከት፣ ንጭታት ያለበት/ያለባት ሰው/ሴት። እየብቻው ለማውጣት። ነጫጭባ (ነጫጭ፡ ): ነጭ እንዳለፈው፡ አለባት። ነጫጭባ: (የቆዳ ችግር)

ነጭ (ጮች): ጸዐድዒድ፡ ብዙ ነጭ። "ነጫጭ በጎች፣ ነጭ ፍየሎች፣ ነጭ ርግቦች" እንዲሉ። ነጭ ሐር: ቀለም ያልገባ። ነጭ ለባሽ: ነጭ የለበሰ፣ ቀዳሽ። ነጭ ለባሽ: ጸጥታ ጠባቂ። ነጭ ልብስ: ያላደፈ (ራእ ፫፡ ፬፡ ) ነጭ፣ ማኛ: ማለፊያ ጤፍ እንጀራ። ነጭ ስንዴ: ጣይ፣ ሶራ፣ ያቡን እግር። ከዚህም በቀር፡ ነጭ ገብስ፣ ነጭ ዶሮ፣ ነጭ ዥብ፣ ነጭ ኰርማ፣ ነጭ ሽንኵርት፣ ነጭ ተልባ እያለ በቅጽልነት ይነገራል። ነጭ ቀለም: የንጨት ደም ወይም ሰው ሠራሽ። ነጭ በግ: ጠጕሩ ወተት የሚመስል። ነጭ ቤት: ነጭ ጋጋሪ (ዐበዛ) ነጭ ቤት: የነጭ ጤፍ እንጀራ ቤት። ነጭ ቤት: ጥሩ የጸዳ ቤት፡ የመኳንንትና የነጭ ልጆች የሚማሩበትና የሚያድሩበት። ነጭ አሞራ: ራዛ፣ ሳቢሳ። ነጭ ኣባይ (ግዮን): ውሃው ነጭ የሆነ ዠማ። "አባይን" ተመልከት። ነጭ ዕከክ: ፎከት። ነጭ ደንጊያ: እብነ በረድ፡ ብክካ። ነጭ ጠላ: ጦጢ። ነጭ ጤፍ: ማኛ። ነጭ ፈረስ: ዐምባላይ (ራእ ፮፡ ) ነጭ ፍየል: ጥቍረት አልባ። ነጭ: ብዛት፣ ብዙነት። "የጥምቀት ለት የሰው ነጭ ታየ።" ነጭ: ንጣት የያዘው ሰው፣ ዐመዳም። (ተረት): "ወዛም ገማ ቢሉ፡ የነጭ ወሬ ነው።" ነጭ: ከስም አስቀድሞ እየገባ ቅጽልና ዘርፍ በቂ ይሆናል። ነጭ: የነጣ፡ ሥነ ፍጥረት። ነጭ: ፈረንጅ፣ የያፌት ልጅ። "እኔ መዩ ነጭ ባይ የምሸሽ ነኝ ወይ" ነጭ: ፈገግታ። "ዝናሙ በነጩ ይዞታል።"

ነጭ ማሽላ (ሌላ ስሙ ጨረቂት ነው) ደግሞ ትርጉሙ ደህና ማለፊያ ማለት ነው።

ነጭ፡ እሾኸ) መርዘኛ ሴት አፍ።

ነጭሎ (የቅጠል ስም) ነጭሎ: የቅጠል ስም (ከነጣ ግስ የመጣ) ነጭሎ: የንጨት ስም፡ ወዙ አረንጓዴ፣ ሰበከቱ ነጭ የሆነ ቅጠል፡ በወይናደጋ የሚበቅል። ነጭ በቁሙ፡ " አለው" ማለት ነው።

ነጭታ: የነጮች፣ የምትነጭ።

ነጭና ጥቍር ፈረስ: ዝንጕርጕር፣ ጠቃጠቆ (ዘካርያስ ፮፡ )

ነጮ ድኻ: ላጤ፣ መላጤ፣ ምንም የሌለው።

ነጮ: ነጭ ሆይ፡ ቃለ አኅስሮ ነው።

ነጮች: ፈረንጆች፣ የምዕራብ ሰዎች።

ነጯ: ካጥንት ላይ ሥጋን ዘነተረ፣ በላ። (ተረት): "ሲመትሩለት ይነጭ።"

ነጸረ (ነጽሮ፡ ነጸረ): አየ፡ ተመለከተ፡ አስተዋለ። "ነጠረን" እይ።

ነጸብራቅ፡ ብልጭታ።

ነጸብራቅ: ብልጭታ (ጸበረቀ)

ነጸብራቅማ፡ ሌሊት፡ የሚያበራ፡ ወፍ።

ነጸፈ: አነጠፈ፡ ዘረጋ (ግእዝ)

ነጻ (ነጽሐ): ጠራ፡ ጸዳ፡ ንጹሕ ኾነ (ከእድፍ፣ ከባርነት ራቀ) ከለምጽ ዳነ፡ ተፈወሰ (፪ነገ፡ ፩፡ ) "ነጣን" ተመልከት።

ነጻ አወጣ: "ከቤቴ ኺድ፡ በወደድኸበት ኑር" አለ።

ነጻ አደረገ: ባሪያን ለቀቀ።

ነጻ ወጣ: ሐርነት አገኘ፡ ከባርነት ተለቀቀ።

ነጻነት አገኘ: ባርነት ቀረለት።

ነጻነት: ነጻ መኾን፡ መለቀቅ።

ነጻዎች: የተለቀቁ ባሮች።

ነፈለ: ተለገደ፡ ነፍናፋ ኾነ።

ነፈለለ (ፈለለ): ተሞኘ፣ ቄለ፣ ነኾለለ፣ ጀለ፣ ደነቈረ።

ነፈለል: ነፍላላ፣ ቂል፣ ሞኝ፣ የማይረባ፣ ደንቈሮ።

ነፈሊያም: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ነፈላም: የነፈል ወገን፡ ነፈል ከርሱ ጋራ ያለ፣ ባለነፈል፡ ነኊራጣ፣ ነፍናፋ።

ነፈል: የአፍንጫ ውስጥ ትርፍ ሥጋ፣ ለገድ።

ነፈሰ (ነፍሰ): ረቀቀረቂቅ ኾነ

ነፈሰ: ሽው ሽውእብድ እብድ አለ (ማቴ፯፡ ፳፭)

ነፈሰ: ቀለለ (ሹመቱ፣ ክብሩ)፡ ከነፋስ ጋራ ኼደ (ወሬው)

ነፈሰበት: ጠላ በጋን ውስጥ፣ እንጀራ በምጣድ ላይ ነፋስ ነካው፡ ጣዕሙ፣ መልኩ ተለወጠጠፋ

ነፈረ (ትግ): ወደ ሰማይ በረረ ወጣ (የባለክንፍ)

ነፈረ (ነፊር፡ ነፈረ): እጅግ ሞቀፈላተፍለቀለቀተቀቀለ

ነፈረቀ (ፈረቀ): በብዙ ወገን መገለ አዠ ሞቀሞቀ

ነፈረቀ: በጣም አለቀሰተንሠቀሠቀአነባተስረቀረቀ

ነፈረቅ: ነፍራቃ፡ የነፈረቀ፣ የሚነፈርቅ፡ አልቃሽ

ነፈራረቀ: መጋገለ

ነፈቀ (ነፊቅ፡ ነፈቀ): ለየ፡ ከፈለ፡ እኩሌታ አደረገ።

ነፈነፈ (ነፍነፈ፡ አካፋ): ኣብዝቶ፡ በላ፣ ጋጠ፣ ነጨ (ርጥብ ሣርን፣ ሥጋን) "የፈረሴ ጕማጅ እቅብቅብ ገብቶ ሲነፈንፍ አገኘኹት" እንዳለ ቍንጨ።

ነፈነፈን ተመልከት።

ነፈነፍ: ነፍናፋ፡ ነኈረጥ፡ ነኍራጣ፡ ጕንፋናም፡ ሰርነ ሰባራ።

ነፈዘ (ነበዘ): ልብ ዐጣ፣ ቀለለ።

ነፈዝ: ልበ ቢስ፣ ቀላል።

ነፈገ (ነፈቀ): ለይቶ ተወ፡ ቤሰ፣ ሠሠተ፣ ጮቀ፣ ቀቀተ።

ነፈጠ (ነፍጸ): ወጣ፣ ወጥቶ ኼደ፣ ሸሸ። ነፈጠ ግእዛዊ ቃል ነው።

ነፈፈ: ጀለ፡ ተሞኘ።

ነፊ (ነፋዪ): የነፋ፣ የሚነፋ፡ አንዘርዛሪ።

ነፊ (ዎች) (ነፋኂ): የነፋ፣ የሚነፋ። "እንቢልታ ነፊ" እንዲሉ።

ነፊታ: የነፋች፣ የምትነፋ ሴት።

ነፊዎች (ነፋይያን፡ ት): ዱቄትን የሚነፉ ወንዶችና ሴቶች።

ነፋ (ነፈየ): አንዘረዘረ (ዱቄትን፣ ጥሬ ጤፍን) ከዐሠር፣ ከገለባ፣ ከእብቅ ለየ፣ አወረደ (ኢሳü፡ ፳፰)

ነፋ (ነፍኀ): ቀበተተ፣ አሳበጠ፣ አንገፈጠጠ፣ አንጠረዘዘ፣ ቀበጠጠ፣ እንዘረጠጠ (ስልቻን፣ ሆድን) "የነፋሽ የቀበተተሽ" እንዲል ጕልማሳ።

ነፋ: አካፋ።

ነፋ: እፍ አለ፣ በትንፋሽ አስጮኸ (ዋሽንትን፣ መለከትን) (ራእ፰፡ ፯፣ ፲፡ ፲፪) (አፍንጫውን ነፋ): ተነፋነፈ።

ነፋ: ወሬ ነዛ።

ነፋሲት (ነፋሳዊት): ነፋስ ያለባት ቀበሌ (ካስመራ በታች የምትገኝ)

ነፋስ (ሶች): ምድር መሠረት፡ የሰማይ ዐምድ፡ ካራቱ ባሕርያት ሦስተኛው ባሕርይ፡ ድምፁ የሚሰማ፣ አካሉ የማይታይ፣ የማይዳሰስ፡ የፍጥረት ኹሉ ሕይወት አንቀሳቃሽ፡ መዝጊያን የሚዘጋና የሚከፍት፡ ዕቃን የሚያነሣና የሚጥል፡ ባሕርን የሚወስድና የሚመልስ።

ነፋስ መውጫ: በጋይንት ክፍል ያለ አገር

ነፋስ፡ ስልክ) ራዲዮ፣ ማርኮኒ የሚባል ጣሊያን በንግሊዝ አገር ያወጣው።

ነፋስ ስልክ: ራዲዮ ስልክ

ነፋስ ገባው: ፍቅር አንድነት ስምምነት ዐጣተለያየ (ሕዝቡ)

ነፋስ: እብድዕርፊተ ቢስ ልጅ

ነፋሪ: የሚነፍር፡ በትግሪኛ ግን በራሪ ወፍ ማለት ነው።

ነፋሻ (ነፋሳዊ): ነፋሳም ስፍራ ቦታደጋ ተራራ አፋፍ

ነፋሽ: የነፈሰ፡ የሚነፍስ።

ነፋጊ: የሚነፍግ፡ ሠሣች።

ነፋፈሰ: መላልሶ ነፈሰ።

ነፋፋ ሞኝ: ("ነፈፈ" ጋር ተያያዥ)

ነፋፋ: መላልሶ ፈጽሞ ነፋ፣ አሳበጠ፡ ኹለንተናን ቅል አስመሰለ።

ነፋፋ: ሞኝ፡ ቂል፡ ጅል፡ ከርፋፋ።

ነፍሰ ቢስ: ለሰውነቱ የማይሣሣ፡ ጐበዝ

ነፍሰ እግዚሐር: ፈጣሪ (ነፍስን በሥጋው ያሳደረበት ቀጪን፣ ኰሳሳ ልጅ)

ነፍሰ ገዳይ: ነፍስን (ሰውን) የገደለ።

ነፍሰ ግዳይ: ነፍስ መግደል

ነፍሰ ጡር (ጸዋሪተ፡ ነፍስ): እርጉዝ ሴት (በማሕፀኗ ነፍስ የተሸከመች) "ጦረን" ተመልከት።

ነፍሰ ጡርነት: እርግዝናእርጉዝነት

ነፍሰ ጡሮች (ጸዋርያተ፡ ነፍስ): እርጉዞች ሴቶች

ነፍሰ ጥኑ: ቢያርዱ ኣይሞት (ውሻ)፡ ቶሎ የማይሞት።

ነፍሱን መረመረ: ለድኻ ምጿት ሰጠ

ነፍሳት (ተሐዋስያን): ከቍጭ ያነሱ ረቂቆች ፍጥረቶችተንቀሳቃሾች

ነፍሳት: ነፍሶች (ግእዝ)

ነፍሳውጪ (ነፍስ፡ አውጪ): ነፍስን ከሥጋ የሚያወጣ፣ የሚለይ፡ ፈጣሪመላከ ሞት

ነፍስ (ሶች): በቁሙ፡ ረቂቅ ፍጥረት፡ የመልአክ ዐይነት፡ ከፈጣሪ ለአዳም ልጅ ኹሉ የምትሰጥ። ሰው ሲፀነስ ዠምራ በሥጋው ታድራለች፣ ተውሕዳው ትኖራለች፡ በሞት ትለያለች (ምሳ፲፩፡ ፴፣ ዮሐ፲፱፡ ፴፣ ፩ጴጥ፡ ፫፡ ፲፱)

ነፍስ አሳለፈ: ሰውን ገደለ ሥጋን ወደ መቃብር፣ ነፍስን ወደ ሰማይ ስኬደ (ኣገባ፣ አወጣ)

ነፍስ አባት: ነፍስ አባት ቄስ፡ የንስሓ አባት

ነፍስ ዐወቀች: ባለአእምሮ ኾነች

ነፍስ አዋለ: እንጭጭ ኾነ

ነፍስ አድን: እንጀራ "እንቆቅልሽን" አስተውል።

ነፍስ ኾነ: ተወደደተጨበጠ

ነፍስ ወከፍ: ለልጅም ኾነ ለአዋቂ በነፍስ የሚያድል።

ነፍስ ዘራ: ተነፈሰተንቀሳቀሰ

ነፍስ ያለው: ያልሞተ፡ ያልከሳ፡ ያልቀጠነ።

ነፍስ: ሰው

ነፍት: ምድር ዘይት (በግእዝ ነፍጥ ይባላል)፡ ይኸውም ጋዝ ነው።

ነፍናፊ: የነፈነፈ፣ የሚነፈንፍ፡ የበላ።

ነፍጠኛ (ኞች): ባለነፍጥ፣ ወታደር፣ ነፍጥ ያለው (የንጉሥ፣ የሻለቃ አሽከር)

ነፍጠኛ()ነት: ነፍጠኛ መኾን፡ ወታደርነት።

ነፍጥ (ጦች): በያይነቱ ጠመንዣ፡ ከውስጡ ዐረር በወጣ ጊዜ ጠላትን የሚያሸሽ የጦር መሣሪያ። "ካሽከር ገበየኹ፡ ከነፍጥ ጐበዛየኹ" እንዲሉ።

ነፍጥ: ነፍጠኛ

(ንዑ፡ ንዓ): የቅርቦች ወንዶችና ሴቶች ትእዛዝ አንቀጽ። " ልጆቼ ስሙኝ ልንገራችሁ። " "ኑና እንተያይ። "

: አዳማቂ ምእላድ። "አሁን አሁኑኑ""እሱ እሱኑ""ወዲያው ወዲያውኑ" በን ፈንታ እየገባ ገቢር ሲሆን፡ "ቅድሙን ቅድሙኑ""ዱሮውን ዱሮውኑ" ይላል።

ኑስ (ንኡስ): ግማሽ ገንዘብ፡ አላድ፡ እኩሌታ። በአረብኛም "ታናሽ" ማለት ነው።

ኑር: ቁም፣ ቈይ፣ ክረም።

ኑርልኝ: የሰው ስም፡ "ቁምልኝ" "ቈይልኝ" ማለት ነው።

ኑሮ በዘዴ: (ሉቃ ፲፮፡ ፮፡ ፰)

ኑሮ ኑሮ: ቦዝ አንቀጽ (ቈይቶ ቈይቶ) "ውሎ ውሎ ከቤት፣ ኑሮ ኑሮ ከሞት" እንዲሉ።

ኑሮ ኑሮ: ከሞት።

ኑሮ: መኖር (ኖረ)

ኑሮ: መኖር፣ ትዳር፣ ንብረት። (ተረት): "ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል"

ኑና (ወንዑ): በቁሙ፡ ቸልታ። "ኑና እንተያይ" ማለት "መጥታችሁ" ማለት ነው። (ኢሳ ፩፡ ፲፰) "ኑን" ተመልከት።

ኑዛዜ: መናዘዝ፡ ምስጢረ ንስሓ መቀበል። ባላገር ግን "ንዛዜ" ይለዋል።

ኑዛዜው ፈሰሰ: ተነበበ፣ ተነገረ፣ ተገለጠ።

ኑፋቄ: ጥርጥር (ግእዝ)

(): የነገር ትራስ። "ጥንበኒ" "ግመኒ" "ሸወርኒ" "ጥንባታም፣ ግማም" ተብሎ ሊተረጎም ይቻላል።

ኒል: ሰማያዊ ቀለም

ኒል: ቀለም ስም "ነየለ"

ኒሻን (ዐረ): የእንቍ፣ የወርቅ፣ የብር፣ የንሓስ ሽልማት፡ ተሸላሚ በደረቱ ላይ የሚያንጠለጥለው ጌጥ። የኒሻን ዐይነቱ ብዙ ነው። ፈረንጆች "ሜዳይ" ይሉታል።

ኒሻን: (መደጋገም - ምናልባት ደስታ ተክለወጽ የተባለ ሰው የጻፈው መጽሐፍ ወይም ክፍልን ያመለክታል)

ኒሻኖች: ሽልማቶች።

ኒቆዲሞስ: የሰው ስም፡ ጌታችንን ከዮሴፍ ጋራ በማለፊያ ሽቱ በጥሩ በፍታ ገንዞ የቀበረ የአይሁድ አለቃ።

ኒኒ: የሴት ልጅ ስም። "ናኑ" "ጋሜ" "ገርዳሳ"

ኒካ: ስላም ጋብቻ ደንብ ሥርዐት

ኒኬል: ማዕድን ስም፡ በብር ፈንታ ገንዘብ፣ የቤት ዕቃ የሚሆን ነጭ ማዕድን (ፈረንጅ አመጣሽ)

(ምእላድ): ፍችው አነት። "ደረቀ ድርቅና""አረገዘ እርግዝና""ሰነፈ ስንፍና""ሞሸረ ሙሽርና""ላቀ ልቅና" በግእዝ መሠረቱ "" ነው።

(ነዐ): የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ፡ "ምጣ" ድረስ፡ የኺድ ተቃራኒ ነው። " ያሉት እንግዳ አራቱ ፍሪዳ። " " ብላኝ የት ኼደች። "

በለው: ጥራው፡ መጥተህ ምታው። "ባለን" ተመልከት።

(ነዐ ነዐ): ምጣ ምጣ፣ ድረስ ድረስ። "ሆያ ሆዬ በሰፊው ጐዳና" እንዲሉ ልጆች።

: በትእዛዝ አንቀጽ እየገባ አንቀጹን ያስቀራል።

: ቸልታ። "ውረድ እንውረድ ተባባሉና አስደበደቡት አፋፍ ቆሙና። "

: ንቀት፡ የንቀት ቃል ነው። "ሐዋርያት ተርበው ነበር ወይ፡ ሐዋርያት ይቅሩና ክርስቶስ እንኳ ተርቧል። " በግእዝ መሠረቱ "" ነው።

: ዐቢይ አገባብ፡ የነገር አስረጅ። "ዓለም በውሃ ጠፋ ኀጢአት ሠርቷልና። "

: አታግባና ስትዘል፡ ኑር። በግእዝ መሠረቶቹ "ኣና" "" ናቸው።

: አዳማቂ ወይም አጐላማሽ። "ሠልስት ሠልስትና""ቀበጥ ቀበጢና""ትላንት ትላንትና""ወዝ ወዘና" ምእላድም ሊባል ይችላል።

: አፋሪእና።

ናላ (ኖለወ): አንጐል ራስ ቅል ፍሬ

ናላው ዞረ: ተበላሸአእምሮ ዐጣ

ናሰ (ነሐሰ): ናስ ሠራ፡ ገነባ፡ እድሞ አበጀ።

ናሴ (ነሐሴ): የወር ስም፡ ፲፪ኛ ወር።

ናስ (ናሕስ): ግንብ፡ እድሞ፡ ያፈር ቤት ጣራ፡ በላዩ ሣር የሚበቅልበት (፩ሳሙ፡ ፲፰፡ ፲፩፣ ሕዝ፲፫፡ ፲፪፣ ዳን፭፡ ፭፣ ዕን፪፡ ፲፩)

ናስ (ንሓስ): ብር የሚመስል ብረት (ከመሬት የሚገኝ) (፩ሳሙ፡ ፲፯፡ ፭፡ ፮፣ ዳን፭፡ ፬፡ ፳፫)

ናስ ማሰር: ማሰሪያው፣ መሸቢያው ናስ የኾነ ትልቅና ትንሽ ጠመንዣ። "ናስ ማሰር ውዥግራ" እንዲሉ።

ናስ ጭራ: እንደ ጭራ ያለ የናስ ሽቦ፡ የዛገ ጌጥ ማጠቢያ፡ መወልወያ። "ኰላን" ተመልከት።

ናስ: ከናስ የተበጀ ታናሽ ገንዘብ፡ እንደ ቤሳ ያለ (ማር፮፡ ፰፣ ሉቃ፲፪፡ ፮)

ናስ: የአገር ስም፡ በተጕለት አውራጃ ያለ ገጠር። "ናስ ማሪያም" እንዲሉ።

ናሶች: ብረቶች፡ ግንቦች።

ናረ (ነሀረ): ነጠረ፡ ጓነ፡ ተወረወረ (ወደ ላይ)፡ ዘለለ (የውሃ፣ የእሳት፣ የኳስ፣ የደንጊያ)

ናረት (ቶች): ጭልፂ፡ ዳውላ።

ናረት ሆድ: ሆደ ትልቅ።

ናሪ (ነሃሪ): የናረ፡ የሚንር፡ ጓኝ፡ ዘላይ።

ናር (ንሂር): መናር።

ናር ናር አለ: መላልሶ ናረ፡ ኀይለ ቃል ተናገረ።

ናርኤል: የክረምት ኮከብ። "የአምላክ እሳት"፡ ወይም "ብርሃን" ማለት ነው።

ናርዱ: የሽቱ ስም (ግእዝ)

ናርዶስ: የናርዱ ቅጠል፡ ወይም ሽቱ።

ናርጅ (ናርዳዊ): ጌጠኛ የእንጨት ጮጮ፡ በሽቱ የጣፈጠ ቅቤ ማስቀመጫ።

ናሽ (ነሓሲ): የናሰ፡ የሚንስ፡ ናስ ሠሪ፡ ገንቢ።

ናቀ (ትግ፡ ነዐቀ): አኰሰሰ፡ እቀለለ፡ አዋረደ፡ ጠላ፡ ክብርን፣ መወደድን አሳጣ (ዘኍ፲፭፡ ፴፩፣ ኢሳ፳፫፡ ፱) (ተረት): "ዐወቅኹሽ፡ ናቅኹሽ" "ሰውን ሰው ናቀው፡ የራሱን ሳያውቀው"

ናቀ: መነነ፡ ተወ፡ ጣለ (ዓለምን)

ናቁስ: ድምፁ የሚያምር ጸናጽል (ነቀተ)(ነከተ)

ናቂ (ዎች): የናቀ፡ የሚንቅ፡ አኰሳሽ። (ሰው ናቂ): ትቢተኛ፡ ኵራተኛ።

ናቂያ: የመናቅ ኹናቴ፡ ጥላቻ።

ናቄ: የሰው ስም።

ናቅ አደረገ: ናቀ።

ናቅ: መናቅ።

ናበ (ነሀበ): ቀጠቀጠ፣ ሠራ (ብረትን)

ናበ: ጋገረ፣ አሰፋ (ማርን)

ናበለ (መበለ): ወደ ላይ ተወረወረ፣ ዘለለ፣ ጨፈረ፣ ከፍ አለ። "ፈረሱ ይናብላል" "ውሃው ይናብላል" እንዲሉ። "ናፈለን" ተመልከት።

ናበተ: ቀለጠፈ፣ ፈጠነ (ተገብሮ)

ናበተ: ቀማ፣ ነጠቀ፣ መነተፈ (ገቢር)

ናቡቴ (ዎች): የናበተ፣ የሚናብት፡ ነጣቂ። "እከሌ ናቡቴ ነው" እንዲሉ።

ናቡቴ: የሰው ስም፡ ኤልዛቤል ርስቱን ለመውሰድ በግፍ ያስገደለችው ሰው።

ናቡቴ: ፈጣን፣ ቀልጣፋ። (ግጥም): "የኛማ ልጆች ናቡቴዎቹ፡ ይናደፋሉ እንደ ንቦቹ።"

ናቢ (ነሃቢ): የናብ፣ የሚንብ፡ ቀጥቃጭ፣ ጠይብ፣ ጃን፣ ሸላሚ።

ናባል: የሰው ስም፡ ከዳዊት ቍጣ የተነሣ በድንጋጤ የሞተ፡ ናባል ደንቈሮ፣ አላዋቂ ማለት ነው።

ናብሊስ: ቃጭል፣ መርዋ። ዳግመኛም የአገር ስም ይሆናል (ግእዝ)

ናትራ: ነጭ ሽቱ (ሪሓን) (ትግሬና ጕራጌ)

ናትራን: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ናቸ: በዛ፡ ተኛ፡ ዘመተ፡ ተንጋለለ፡ ረዘመ (የተክሉ)

ናቸው (ነዮሙ፡ ነዮን): እነሱ ናቸው፡ አሉ።

ናቸው (አንቀጽ): የሩቆች ወንዶችና ሴቶች ነባር አንቀጽ። "ነው" እይ።

ናችሽ ናችሽ አለ: አለ (ጠራ)

ናችሽ: የተባት አህያ መጥሪያ፡ ለበቅሎና ለፈረስም ይነገራል።

ናችኹ (ነየክሙ፡ ነየክን): እናንተ ናችኹ፡ አላችኹ ይላል። "እንደ" ብለኸ "እንዴትን" እይ።

ናችኹ (አንቀጽ): የቅርቦች ወንዶችና ሴቶች ነባር አንቀጽ። "ነው" ተመልከት።

ናና (ናሕንሐ): በዛ፣ ፈላ፣ ገነፈለ።

ናና: ፩ኛው አንቀጽ፡ ፪ኛው ቸልታ። "መጥተኸ" ማለት ነው። "ናና እይ" (ዮሐ ፲፩፡ ፴፬) "ናን" አስተውል።

ናና: ሠየ፣ ጐመዠ።

ናኘ: አብዝቶ ሰጠ፣ ኣቀበለ፣ ዐደለ፣ ነዛ፣ በተነ፡ ዘራ፡ ኣዘዘ። (ተረት): "ባላዋቂ ቤት እንግዳ ናኘበት። "

ናኝ (): የኖኘ፣ የሚናኝ፡ ሰጪ፣ በታኝ።

ናዕናዕ: የተክል ስም፡ ሲያሸቱትና ሲመገቡት ጣዕም ያለው ቅጠል። በግእዝ አዛብ ይባላል።

ናእክ: ቃታ ጩኸት

ናኦድ: በ፲፭፻ .. የነገሠ፣ ማሪያምን የደረሰ የኢትዮጵያ ንጉሥ ስም። (ንኡድ) ክቡር ማለት ነው።

ናኵራ: በቀይ ባሕር (ኤርትራ) ውስጥ በአዳል መሬት አንጻር የሚገኝ ደሴት በዚህም ስፍራ በጣሊያን እጅ ብዙዎች ሐበሾች እየታሰሩ ዐልቀዋል።

ናወተ (ኖተወ): ተንከራተተ (በባሕር፣ በየብስ ላይ) "ኖት" ማለት ከዚህ ሊወጣ ይችላል። "ነወዘን" እይ።

ናዋች (ኖትያ): የናወተ፣ የሚናውት፡ ተንከራታች፣ ቋትለኛ።

ናዘረ: ዛዘነ፣ "ሚያው ሚያው" አለ፡ ዞረ፣ እንስት ፈለገ፡ የሚነድፈውን እንደሚሻ ነገር ናዜራ ሆነ።

ናዘረች: ዛዘነች፣ ተባት ፈለገች።

ናዘዘ (ናዝዞ፡ ናዘዘ): በተሳተ፣ በተገደፈ (ሲያውቁ በድፍረት፣ ሳያውቁ በስሕተት)፡ ከልጅነት እስከ ዕውቀት በተሠራ ኃጢአት (ሰይጣን ባሸመቀው፣ መንፈስ ቅዱስ ባወቀው)"እግዜር ይፍታ" አለ፡ ተስፋ ሰጠ፣ አጸናና፣ አረጋጋ።

ናዛዥ (ዦች): የናዘዘ፣ የሚናዝዝ፡ ቄስ፣ የነፍስ አባት።

ናዜራ (ሮች): ሸረሪት የሚመስል ጥቍር ተንቀሳቃሽ፡ ሰውን በነደፈ ጊዜ የሚሣቅይና የሚጠዘጥዝ፣ የሚነዝር። ሁለተኛ ስሙ ዳሞትራ ነው።

ናዝራዊ (ናዝሬታዊ): የናዝሬት ሰው፡ በናዝሬት ተወልዶ ያደገ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ (ማቴ ፪፡ ፳፫)

ናዝራዊ (ውያን): የክርስቶስ ወገን፡ ክርስቲያን።

ናዝራዊ: የናዝር ወገን፡ ጠጕራም፣ ባሕታዊ፣ መናኝ፡ እንደ ሶምሶን ያለ፣ ራሱን የማይላጭ፣ ሥጋ የማይበላ፣ ጠጅ የማይጠጣ።

ናዝሬት: የአገር ስም፡ በኢየሩሳሌም እውራጃ ያለች ቀበሌ፡ የተናቀች፣ የተዋረደች ማለት ነው (ኪ፡ ወ፡ ክ)

ናዝር (ዕብ፡ ናዚር): የብፅዐት፣ የስለት ልጅ ማለት ነው (ኪ፡ ወ፡ ክ)

ናዞ: የገብስ ስም (አንድ ዓይነት ገብስ)

ናዡድ (ናዝወርድ): ናስ፣ ጽጌ ረዳ የሚመስል ቀለም።

ናይ: ተረተረ፣ ፈታ (ልቃቂትን)

ናይት: ዝኒ ከማሁ።

ናደ (ነዐደ): ጐተተ፣ ዘረጠጠ፣ ሻረ፣ ኣፈረሰ፣ አወረደ፣ አንከባለለ፣ አወደቀ፣ አሸሸ (ክምርን፣ ግንብን፣ ገደልን፣ ጦርን) "ነዐደ" ጥንታዊ ዐማርኛ ነው፡ ይኸውም ሊታወቅ በክብረ ነገሥት ብቻ "ድል ነዓድ" ተብሎ ቅጽሉ ይገኛል።

ናደለ: ተጠገበ፣ ተዘለለ፣ ተጨፈረ።

ናደው: ናዴ፣ የሰው ስም።

ናዳ (ዶች): ከገደል፣ ከተራራ ተንዶ የተንከባለለ፣ የወረደ (ድንጋይ፣ ትንሹም፣ ትልቁም)

ናጅ (ነዓዲ፡ ነዓድ): የናደ፡ የሚንድ፡ አፍራሽ።

ናግራን: የአገር ስም፡ በየመን የነበረች ከተማ (፴፮ ሺሕ ሰማዕታት የተገደሉባት) "ሀገርን" እይ።

ናጠ (ትግ፡ ሐባ፡ ነሐፀ። ዕብ፡ ናጥ፣ ታወከተ ነቃነቀ): ገፋ፣ ወዘወዘ፣ ነቀነቀ፣ ወተትን።

ናጠረ) ነጠረ (ናደለ): አናጠረ ዘለለ መር መር አለ ጨፈረ (የፈረስ) (ግጥም): "ወይ እኔ አቶ ፈረስ በሰፈሩት ቍና መሰፈር አይቀር፡ ጋሪ በወገቤ ያናጥር ዠመር። "

ናጠጠ (ነጢጥ፡ ነጠ): ዘለለ፣ ፈነጨ፣ አነጠነጠ። "ናደለን" አስተውል።

ናጩርቲያም: ጩኸታም

ናጩርት: ጩኸት

ናጫ (ጮች): የዕንጨት ስም፡ ቅጠሉ እንደ ሳማ የሚለበልብ ዕንጨት፡ ልጡ ተልጦ ይጨርትና ገመድ ይሆናል። ጠጕሩ ዐይን ውስጥ በገባ ጊዜ እሾኸ በወጋት፣ ቅማል ያወጡታል። "ዐመልን" ተመልከት።

ናጫ: ዕንጨት (ነጩ)

ናጫጌ: በተጕለት ውስጥ ያለ አገር፡ ናጫ የበዛባት፣ የና፵ ምድር ማለት ነው።

ናጯ: የናጠ፣ የሚንጥ፡ ገፊ፣ ወዝዋዥ።

ናፈለ: ወደቀ፡ ተጨነቀ።

ናፈረ (ትግ ሐባ): ዘለለ "ናፈለንና" "ናበለን" እይ።

ናፈቀ (ናፍቆ፡ ናፈቀ): ሻ፡ ፈለገ፡ ተመኘ (ልጅ አባት እናቱን፡ አባት ልጁን፡ ወዳጅ ወዳጁን) (ምሳ፯፡ ፲፭፣ ፪ቆሮ፡ ፯፡ ፯፣ ፩ተሰ፡ ፫፡ ፮)

ናፈቀ: ተጠራጠረ።

ናፈቀች: እናት ልጇን ፈለገች፡ ተመኘች።

ናፈቅ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ። "አባቱን አያውቅ፡ አያቱን ናፈቅ" እንዲሉ።

ናፋሊ: የሚናፍል፡ የሚወድቅ፣ የሚጫነቅ።

ናፋቂ: የናፈቀ፡ የሚናፍቅ፡ የሚሻ፡ የሚፈልግ፡ ፈላጊ፡ ተጠራጣሪ።

ናፍቆት: ንፍቂያ፡ የዘመድ፣ የወዳጅ ፍለጋ፡ ፍላጎት (፪ቆሮ፡ ፯፡ ፲፩)

: ምእላድ ቅጽል፡ ፍችው የ። "አረም አረመኔ""ውስጥ ውስጠኔ""አስተኔ" ቢል ዓይነት ያሰኛል።

ንሓስ: በቁሙ ናስ።

ንሡ: ተቀበሉ፣ ውሰዱ (ዘዳ፴፩፥ ፳፮)

ንሣ ንሣ: የደጊመ ቃል፣ ንኡስ አገባብ፡ "እንዴት እንዴት" እንደ ማለት ያለ።

ንሣ: የነቀፌታ ቃል። "ንሣ ይህ ሰው ምን ይላል።" በባላገር ግን "እሣ" ይባላል።

ንሣማ: "" ቃለ አጋኖ ነው።

ንስሓ አባት: ንስሓን የሚነግሩት የንስሓ አባት፡ ዳግመኛም ነፍስ አባት ይባላል።

ንስሓ ገባ (ነስሐ): በክፉ ሥራው ዐዘነ፡ ተጸጸተ፡ በደሉን ገለጠ፡ ኀጢአቱን ተናዛረ፡ አመነ።

ንስሓ: ጸጸት፡ ሐዘን (በተሠራ ኀጢአት ምክንያት የሚደረግ)

ንስረ ተፈሪ: በ፲፱፻፳፩ .. መዠመሪያ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ የግርማዊ ንጉሥ ተፈሪ ጥያራ።

ንስረ ኢትዮጵያ: በ፲፱፻፴፰ .. መብረርና ሰው ማመላለስ የዠመረ የሐበሻ አይሮፕላን።

ንስር (ሮች): ከአየር ተወርዋሪ ታላቅ አሞራ፡ የፍየል ግልገልና ሠሥ አንሥቶ የሚወስድ፣ የሚበላ፡ ዐይነ ጥሩ። በአየር መጥቆ ወደ ታች በተመለከተ ጊዜ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታህል ሥጋ አትሰወረውም ይላሉ። ንስር ዐይነት ነው፡ ግልገል አንሣ፣ የሎስ፣ ጐሢ። በግእዝ ግን የወል ስም ነው።

ንስር ቃና (ንስረ ቃና): የድምፅ ቃና ያለው አሞራ ወፍ (ያሬድ፡ ከዜማው ጣዕም የተነሣ ምግብ ትቶ ይሞታል ይላል ማር ይሥሐቅ) የግእዝ ስሙ "አሮድዮን" ነው።

ንስር ቃና: እንቢልታ። "ምስር ቃናን" እይ። "ንስር" የግእዝ፡ "ምስር" ያማርኛ።

ንስር: ጥንበ በላ።

ንስሮች: ጥንሰ በሎች (ሉቃ፲፯፡ ፴፯)

ንስነሳ: ብተና፡ ጕዝጐዛ፡ ውዝወዛ።

ንስናሽ: የንስንስ ቅሬታ።

ንስንስ አለ: ተነሰነሰ።

ንስንስ አደረገ: ነሰነሰ።

ንስንስ: የተነሰነሰ፡ የተጐዘጐዘ፡ ጕዝጕዝ (ሣር፣ አበባ)፡ የተበተነ (ዐመድ፣ ትቢያ፣ ጥንጣን፣ ዱቄት፣ ጤፍ)

ንረታ: ድብደባ፡ ጥዘላ።

ንረት: ንጥሪያ፡ ጕኖሽ፡ ዝላይ።

ንርት: የተመታ፡ የተጠዘለ።

ንርት: የተነረተ፡ የተነፋ፡ ንፍ።

ንሮሽ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ንሺ: ተቀበዪ።

ንሽ ኾነ: ረጠበ፣ ራሰ ዕርሻው።

ንሽ: ርጥበት (ነሣ)

ንሽ: የመሬት ርጥበት የሚደርቅ፣ የሚነሣ፡ ወይም ማሳ ከዝናብ የነሣው፣ የተቀበለው ማለትን ያሳያል።

ንቀት: ሌላውን መናቅ፡ ለራስ መናቅ (አስ፩፡ ፲፰፣ ኢዮ፲፪፡ ፳፩) (ጥና) መናቅ፡ መጠላት።

ንቁፍ: የተነቀፈ፡ የተሰደበ፡ ስዱብ፡ ነውረኛ።

ንቃ: ዕድል።

ንቃ: የትከሻ ስም፡ ትከሻ። "ግንቃ ጠላ እንዲሉ"

ንቃሪ: የተነቀረ፡ ጭላጭ፡ ሙጣጭ፡ ጥንፋፊ።

ንቃሻም: ንቃሽ ያለበት፡ የበዛበት፡ ጕድፋም (ጥጥ፣ ጐፈሬ)

ንቃሽ (ሕጸጽ): ቈሻሻ፡ ጕድፍ። "የጥጥ ንቃሽ" እንዲሉ።

ንቃሽ: ጕዳይ፡ ጐደል፡ ቅናሽ።

ንቃቃት (ንቅዐት): መሬት እለት ሥንጥቃት

ንቃቃት: የመሬት ሥንጥቃት (ነቃ፡ ነቅዐ)

ንቃቃቶች (ንቅዐታት): ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች።

ንቃት (ንቅሀት): ብንንታእንቅስቃሴትጋትጥንቃቄመንቃት

ንቃይ: "ንቅል" ጋር ተመሳሳይ (ችግኝ፣ ምስማር፣ ቈርቈሮ) "የአንድ ጊዜ ንቃይ፣ የኹለት ጊዜ ንቃይ" እንዲሉ።

ንቅ (ንቁዕ): የነቃ፡ የተሠነጠቀ (ሥንጥቅ፣ ትርትር) "ንቅ ያለበት ዕንጨት፣ ታቦት አይኾንም"

ንቅ: ንቁ (ንቁህ): የነቃ፡ የተጠነቀቀ፡ ነቅቶ ተግቶ የተቀመጠ፡ ትጉህጠንቃቃ

ንቅለኛ (ኞች): ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ንቅላት: ውልቃት።

ንቅል አለ: ውልቅ አለ፡ ተነቀለ።

ንቅል አደረገ: ምንግል አደረገ።

ንቅል: ርስቱን ያጣ ሰው።

ንቅልቅል አለ: ውልቅልቅ አለ።

ንቅልቅል: የተነቃቀለ፡ ምንግልግል።

ንቅሳት: ውቅራት፡ ጥቍራት።

ንቅስ አደረገ: ንቅል አደረገ፡ ነቀሰ።

ንቅስ: የተነቀሰ (ጥርስ፣ ገላ)፡ የጌጥ፣ የቤት ዕቃ፣ የጦር መሣሪያ ሥዕል።

ንቅነቃ: ቅስቀሳ፡ ውዝወዛ።

ንቅናቄ (ንክናኬ): ውዝዋዜ፡ እንቅስቃሴ።

ንቅንቅ (ንክኑክ): ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ ውዝውዝ።

ንቅዝ (ንቁዝ): የነቀዘ፡ ጥንጣኑ የበላው።

ንቅዝ አለ: ነቀዘ።

ንቅፍቅፍ: የተነቃቀፈ።

ንቆች: ማዥራቶች፡ ትከሾች (ዘፀ፳፰፡ ፲፪)

ንቡ: ንብ፣ የርሱ ንብ።

ንቡረ እድ: በራሱ ላይ እጅ የተጫነበት፣ የኣኩስም ጳጳስ ሊቀ ጳጳሳት። በዘመን ብዛት ግን ይህ መንፈሳዊ ሹመት ለመኳንንት ተሰጥቷል። "ዕጨጌን" ተመልከት።

ንቡር: የተቀመጠ፣ የተጫነ (ግእዝ)

ንቡት: ባለያ ሴት፡ የሴት ዐምስትያ፡ ያን ሁሉ የምታውቅ ሴት በምሳሌ ንቡት ትባላለች።

ንባም: ንብ ያለበት፣ የበዛበት ስፍራ።

ንባስል (ንብ አስል): ነጭ ሽቶ የሚመስል ቅጠል። ዐዲሱን ቀፎ መዠመሪያ ጥድ፣ ሁለተኛ ንባዕል ያጥኑታል። "የንብ (ማእሰረ እግር) እግር ማሰሪያ ነው" ይላሉ። ዳግመኛም "ንብ አስኰብላይ" ተብሎ ይተረጐማል። "፪ኛውን ሰለለ" አስተውል።

ንባብ ቤት: የንባብ ቤት፣ ንባብ መማሪያ።

ንባብ ትምርት: የንባብ ትምርት። በግእዝ ትምህርተ ምንባብ ይባላል።

ንባብ ዐዋቂ: ንባብ የሚያውቅ፣ በበንግ የሚያነብ።

ንባብ: ንባብ መማር፣ ማሰማት።

ንባብ: ከወርድ ንባብ በኋላ ተማሪ እየጮኸና እያሰማ በፍጥነት የሚናገረው ከነቍጥ እስከ ነቍጥ ያለ፣ የሚነሣና የሚወድቅ፣ የሚጠብቅና የሚላላ የግእዝ ቃል። በግእዝም ነገር ማለት ነው።

ንብ (ቦች) (ንህብ): በቁሙ፡ ባለክንፍ፣ ተንቀሳቃሽ ተባትና እንስት፡ አበባን ሁሉ እየቀሰመች የምትጋግር የማር ዐበዛ፡ ትጉ (ትግህት) ሠራተኛ። ቀፎዋን የነካባትን እሾኽ በሚመስል ፍላጻዋ (መርዟ) ትነድፋለች። "ዐርኬና" በሚባል ዕልፍኝ የሚውሉ፣ በአጀብ የሚኼዱ አውራ ንጉሥና ንግሥት፣ ውሃ ቀጂ ድንጕል አሏት። አውራው ከንግሥቲቱ ጋራ ተራክቦ ካደረገ በኋላ ንቦቹ ይገድሉታል ይባላል፡ ከንግሥትም ንግሥት በተወለደች ጊዜ የናቷን ሰራዊት ከፍላ ከቀፎ ወጥታ ታጅባ ወደ ሌላ ስፍራ ትኼዳለች፡ ሥነ ሥርዐቷ አይቃወስም። የአማርኛ ገበታ ዋሪያ ተመልከት።

ንብ፡ አስል) ነጭ ሽቶ መሳይ የገደል ቅጠል፣ ዐዲስ ቀፎ ማጠኛ። "ንብ፡ አስኰብላይ፡ ማለት፡ ነው።"

ንብረታለም (ንብረተ ዓለም): የዓለም ንብረት።

ንብረት: መቀመጥ፣ አቀማመጥ።

ንብረት: ኑሮ፣ ትዳር፣ ገንዘብ፡ ጐዦና ጕልቻ።

ንብብር: የተነባበረ፣ የተደራረበ፡ ድርብርብ (በጐታ ውስጥ ያለ እኸል)

ንብዝ አለ: ተነበዘ፡ የማይለቅ ሆነ (እድፉ)

ንብዝ አደረገ: ቅምት አደረገ፣ ወሰደ።

ንብዝ: ልብ ማጣት፣ አደጋ፣ መከራ ወዳለበት መገሥገሥ፣ መፍጠን። በግእዝ እንባዜ ይባላል። "እከሌ ንብዝ ይዞታል" እንዲሉ።

ንብዣ: ቅሚያ፣ ገፈፋ፣ ሰለባ።

ንብጌ ( ንብ): ንብ ያለበት አገር (በቡልጋ ውስጥ የሚገኝ) የግእዝ መጽሐፍ "መሐግል" ይለዋል፡ ማሰሪያ ማለት ነው። ንብጌ: (አገር ናበ) - ይህ ንብጌ ከላይ እንደተብራራው የንብ መገኛ ወይም የመነጨበትን ቦታ ያመለክታል።

ንቦ: ንብ ሆይ።

ንቧ: ያች ንብ፣ የርሷ ንብ።

ንትረካ: ንዝነዛ፡ ብቀታ፡ ጭቅጨቃ።

ንትርካም: ባለንትርክ፡ ጭቅጭቃም።

ንትርክ: ንዝንዝ፣ ጭቅጭቅ፣ አተካራ።

ንትርክ: የተነተረከ፣ ንዝንዝ፣ ብቅት።

ንትቢያ (ንታፌ): የማለቅ ምልክት።

ንትብ (ንቱፍ): የነተበ፡ የተጐዳ።

ንትብ አለ: ነተበ።

ንን (ፊደል/አንቀጽ) ንን: አንደኛው ዝርዝር፡ ኹለተኛው ገቢር ነው። "እጃችንን ታጠብን" "ምሳችንን በላን"

ንኡሰ ክርስቲያን: እምነትና ጥምቀት ያልተፈጸመለት ሰው።

ንኡስ (ንእሰ): ያነሰ፣ ታናሽ።

ንኡስ አንቀጽ: አርእስት፣ ሳቢ፣ ዘር፣ ሣልስ ቅጽል፣ ሳድስ ቅጽል፣ ቦዝ። እነዚህ ሁሉ ማሰሪያነት የሌላቸው ናቸው።

ንኡስ አገባብ: "የጊዜ፡ ስም፡ የዛሬ፡ ተቀዳሚ፡ ቀን።"

ንኡስ አገባብ: በትጋት ተግቶ።

ንኡስ አገባብ: የነገር ጭማሪ።

ንኡስ አገብአብ: ጥግ፣ ሥር፣ ዝቅታ፣ ግርጌ።

ንኡስ: የዳዊት መዝሙር መጨረሻ፡ ትርፍ።

ንእከ: አናኸተጨነቀ እቃሰተ ጮኸወለሌ አለ

ንኪት: ተስቦ ጠንቅ ጕዳት

ንክ (ንኩይ): የተነካገጣባ ፈረስ በቅሎ አያ ግመላ

ንክ: ወፈፍተኛ ሰው

ንክሳት (ንስከት): ንክሻ፡ በጥርስ የቈሰለ ገላ ውግታት

ንክስ (ንሱክ): የተነከሰ ዐኝ የተባለ

ንክር: የተነከረ የተደፈቀ የራሰ

ንክሻ (ንስከት): ከዚህ ጋር ተመሳሳይ። "እከሌ ጠላቱን ባይን ጥቅሻ፣ በከንፈር ንክሻ አስገደለው። "

ንክት: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ንክች (ንክየት): መንካት

ንክች አደረገ: ጥቂት ላመል ነካ

ንክንክ: የተነከነከ የተበላ

ንክኪ: ባጥንት፣ በኮርቻ፣ በልብስ፣ በመኝታ የሚጋባ ቍስል ቂጥኝ

ንክኪት: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ።

ንዋየ ሐቅል: የጦር መሣሪያ (የበዳ፣ ጸብት) በሮማይስጥ "አርማ" ይባላል።

ንዋየ ማሕሌት: የዘፈን መሣሪያ (በገና፣ ማሲንቆ፣ ጸናጽል፣ ከበሮ፡ የመሰለው ሁሉ)

ንዋየ ቅድሳት: የተቀደሱ (የክርስቶስ ሥጋና ደም መያዣ፣ ማክበሪያ)፡ የቤተ ክርስቲያን ጻሕል፣ ዐውድ፣ ጽዋዕ፣ ጽና፣ ዕርፈ መስቀል፣ መሶበ ወርቅ፣ አልባሳት።

ንዋይ (ነወየ): የገንዘብ ስም፡ ዕንቍ፣ ፈርጥ፣ ወርቅ፣ ብር፣ ማዕድን፣ ልብስ፣ ማንኛውም ዕቃ።

ንውጥውጥ አለ: ተነዋወጠ።

ንውጥውጥ: የተነዋወጠ፣ የተነቃነቀ።

ንውጥውጥታ: ንቅናቄ፡ ካህናት ግን "ንውጽውጽታ" ይላሉ።

ንውጽውጽታ: ንውጥውጥታ። "ነወጠን" እይ።

ንዛት (ንዝሀት): የመንዛት ልክና መጠን። "ቈሎውን ቈልቼ አንድ ንዛት ቀርቶኛል"

ንዛዣም: ትንታም።

ንዛዥ: ብንታ፣ ትንታ።

ንዝ (ንዙህ): የተነዛ (በሠማ፣ ምጣድ ላይ ያለ እኽል)

ንዝህላል (ሎች) (ዛህለለ): ዝንጉ፣ እለል፣ ዘለል ባይ፡ ሞኝ፣ ቂል፣ ሰካር፣ ተላላ፣ ከረፈፍ፣ ሥራ ፈት፣ አውታታ። በግእዝ ግን "ንዝህሉል" "እንዝህሉል" ይባላል።

ንዝህላልነት: ንዝህላል መሆን፡ ዝንጋታ።

ንዝነዛ፣ ንዝናዜ: የመነዝነዝ ሥራ፡ ጭቅጨቃ።

ንዝንዛም: ንትርካም፣ ጭቅጭቃም።

ንዝንዝ: ሁለተኛው '' ይጠብቃል፡ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ፣ ውዝግብ (ስም)

ንዝንዝ: የተነዘነዘ (ቅጽል)

ንዣም (ሞች): ንዥ ያለበት፣ ባለንዥ።

ንዥ (): የበሽታ ስም (ከንፈርን የሚበላና የሚያቃጥል)፡ ቍስል፣ ዕከክ መሳይ። ይኸውም በፍየልና ባንዳንድ ሰው ከንፈር ላይ ተነዝቶ ይታያል። በፈረንጅኛ አፍት ይባላል።

ንዳዳም: ንዳድ ያለበት አገር፣ ወባም።

ንዳድ: ትኵሳት ያላት ወባ፣ ተቅማጥ (ዘዳ ፳፰፡ ፳፪፣ ሉቃ ፬፡ ፴፰)

ንዴተኛ (ኞች): ንዴት ያለበት፣ ተናዳጅ፣ ቍጡ፣ ብስጩ።

ንዴት (ንደት): ቅጥለት፣ ቃጠሎ፣ መናደድ፣ ብስጭት (ኢሳ ፲፫፡ ፲፫) በግእዝ ግን ድኽነት ማለት ነው፡ አንቀጹ "ነድየ" ነውና።

ንዴት (ንድየት): ድኽነት። (ንዴት ከቅጥለት የመጣው "ነደደ" ግስ ነው።)

ንዴት: ቅጥለት፣ ድኽነት (ከነደደ፣ ነደየ ግሶች የመጣ)

ንድ (ነደደ): ንድ (ንዱድ): የነደደ። "ዋይ ንድድ" እንዲሉ።

ንድ (ንዱእ): የተነዳ፣ የተወሰደ።

ንድላት: የውግታት ቀዳዳ።

ንድል (ንዱል): ዝኒ ከማሁ (ከሽንቁር ግስ የመጣ)

ንድል አደረገ: ብስት አደረገ።

ንድሎሽ: ዝኒ ከማሁ።

ንድቂያ: የመንደቅ (ግንብ) ኣሠራር።

ንድድ አለ: ቅጥል አለ።

ንድፋት: የፍላጻ፣ የመርዝ ውግታት። በግእዝ "ንድፈት" ይባላል።

ንድፍ (ንዱፍ): በቁሙ፡ በደጋን ዥማት የተነደፈ፣ የተበተነ ጥጥ። "ንድፍ" ቅጽልና ስም ነው።

ንድፍ: ድን አትጫን፡ እከሰል ውሃ በተነከረ ቀጪን ገመድ የተመታ፣ የተመለከተ (የሳንቃ፣ የማእዘን ቢጋር) (፩ነገ ፯፡ ፴፯) ፈረንጆች ፕላን ይሉታል።

ንድፍታም: ንድፍት ያለበት፣ ባለንድፍት አገር።

ንድፍት: የሚቈስል ዕብጠት፣ የበቅሎና የፈረስ፣ የግመል በሽታ፤ በቈላ ምድር ይይዛቸዋልና ይበጣጥሳቸዋል። "ንድፍት" በግእዝ የተነደፈች (የተወጋች) ማለት ነው፤ "" አይጠብቅም።

ንጉሠ ሰላም: የፍቅር፣ የደኅንነት ንጉሥ (መድኀኔ ዓለም)

ንጉሠ ነገሥት: የንጉሦች ንጉሥ፡ በበታቹ ሌሎች ንጉሦች ያነገሠ (እንደ ትግሬው ዐጤ ዮሐንስ ያለ) ወይም በንጉሠ ነገሥት ዐልጋ የተቀመጠ (ዳግማዊ ምኒልክን፣ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴን የመሰለ ዐጤ) ጃን ሆይ የሚባል።

ንጉሠ ጽድቅ: የውነት ንጉሥ (ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ)

ንጉሡ ምድር: ሞት የሚሽረው የምድር ንጉሥ።

ንጉሡ : የሠውት "" ስም።

ንጉሡ ሰማይ: የዓለም ጌታ እግዜር፡ ሞት የማይሽረው የሰማይ ንጉሥ።

ንጉሣዊ: የንጉሥ ወገን፣ መልከኛ።

ንጉሤ: የሰው ስም፡ የኔ ንጉሥ ማለት ነው።

ንጉሥ (ሦች): በቁሙ፡ የነገሠ፣ የአገር አውራ፣ የሕዝብ እረኛ፣ መሪና አሳዳሪ፡ ለወዳጁ ሹመት ሽልማት፣ ለጠላቱ እሳት ስለት የሚሰጥ፡ ከገበሬና ከነጋዴ፣ ከሌላውም ሠራተኛ ከ፲ አንድ የሚቀበል። ከሞተ ንጉሥ የቆመ ዐምባ ራስ። "ንጉሥ በመንግሥቱ፣ ጕልማሳ በሚስቱ።"

ንጉሥ ሚካኤል: የወሎ ባላልጋ።

ንጉሥ ተቈጣ: "ክተት ሰራዊት ምታ ነጋሪት" አለ፡ ዘመቻ አዘዘ።

ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት: የጐዣም ባላልጋ።

ንጉሥ: ዐሥር የዳዊት መዝሙር።

ንጉሥ: ከሰንጠረዥ መጫወቻ አንዱ።

ንጉሥ: የንብ አውራ፣ የንግሥት ባል።

ንጉሥነት: ንጉሥ መሆን።

ንጉሥና ንግሥት: የነገሠና የነገሠች (ጃን ሆይና ይተጌ)

ንጉሥኛ: የንጉሥ አነጋገር።

ንጕር፡ ቅቤ፡ አለቅመም፡ የቀለጠ።

ንጕር: የነጐረ፣ የፈላ፣ የቀለጠ። "ንጕር ቅቤ" እንዲሉ።

ንግል አለ: ንቅል ፍልስ አለ።

ንግል: የነገለ፡ ንቅል፣ ፍልስ።

ንግሥ (መንገሥ) ንግሥ: መንገሥ፣ አነጋገሥ፡ ንጉሥና ንግሥት መሆን (ቅባት) የታቦት ዙረት (ዑደት)

ንግሥተ ሣባ: ንግሥተ አዜብ። ንግሥተ ሳባ: የሳባ ንግሥት (ማክዳ)

ንግሥተ ነገሥታት: የነገሥታት ንግሥት (እንደ ግርማዊት .. ዘውዲቱ ምኒልክ ያለች) ንግሥተ ንግሥታት: የንግሥታት ንግሥት፡ የንጉሠ ነገሥት ባልተ ቤት፡ ባሏ ንጉሠ ነገሥት ሲባል እሷ "ንግሥተ ንግሥታት" ትባላለች።

ንግሥተ አዜብ: የአዜብ ንግሥት (የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ኢየሩሳሌም የኼደች)

ንግሥታት: ለብቻቸው የነገሡ ሴቶች።

ንግሥታት: የንጉሦች ሚስቶች (ይተጌዎች) ባላገር ግን መንግሥትን "ንግሥታት" ይለዋል።

ንግሥት ማክዳ: በሐበሻ፣ በትግሬ፣ ሳባ መዠመሪያ የነገሠች።

ንግሥት ቤተ ክርስቲያን: ፍሪዳ ሥጋ ወደሙ፡ አሞራ ሰይጣን፡ ወይም ማደሪያው ኀጢአተኛ ሰው ነው።

ንግሥት: ዐልጋው ያባቷ ሆኖ ባሏ ሳይነግሥ ብቻዋን የነገሠች (እንደ ማክዳ ያለች) ወይም ዐልጋው የባሏ ሆኖ ከባሏ ጋራ የነገሠች ይተጌ። ንግሥት: እንስት ንብ (እንቍላል የምትወልድ) ንግሥት: ከሰንጠረዥ መጫወቻ አንዷ "ንግሥት" ትባላለች።

ንግረኛ (ኞች): ንግር ያለው፣ ባለ ንግር፣ ወሬኛ።

ንግር: አስቀድሞ የተነገረ (ትንቢት)

ንግርተኛ (ኞች): ባለንግርት፣ ንግርታም።

ንግርት: የተነገረች፣ የተተነባች።

ንግግር: ጭውውት።

ንግግሮች: ጭውውቶች።

ንጠላ: ልየታ።

ንጣታም: ንጣት የያዘው፣ ባለንጣት፣ ችግረኛ።

ንጣት (ነጭነት/ጽዳት) ንጣት: ነጭ ዕከክ፣ ፎከት። ንጣት: ነጭነት፣ ጽዳት።

ንጣይ፣ ንጥል (ንጻይ፣ ንጹል): የተነጠለ፡ ልጣጭ፣ ልዩ ሐር፣ ድር።

ንጣጭ: የዋንጫ፡ የሳንቃ፡ የብረት ፍቄት (የመፋቅ ውጤት)

ንጣጭ: የዋንጫ ፍቄት (ዐነጠጠ)

ንጣፊ: ወተት የሌለው ጡት። "ዕራሪን" አስተውል።

ንጣፊ: የመሬት፣ የቦታ ምትክ፣ ለውጥ።

ንጣፍ: በቤት ውስጥ የተነጠፈ (ሉሕ፣ ልባጥ፣ ሳንቃ)

ንጥ: የተነጠጠ፡ የተፋቀ፡ የተሰነጠ፡ ስንጥ (የተፋቀ ወይም የተሰነጠቀ ነገር)

ንጥላት: የመነጠል ኹናቴ።

ንጥልጥል አለ: ልይትይት አለ፣ ተነጣጠለ።

ንጥልጥል: የተነጣጠለ።

ንጥሪያ: ጕኖሽ፣ ንሮሽ፣ ዝላይ።

ንጥር (ንጡር): የፈላ፣ የነጠረ (ቅቤ፣ ማር፣ ሜሮን፣ ቅባ ኑግ፣ ዘይት፣ ወርቅ፣ ብር፣ መድኀኒት)

ንጥር፡ ቅቤ፡ ከቅመም፡ ጋራ፡ የቀለጠ፡ የፈላ። (ተረት)"ድኻ፡ በልሙ፡ ቅቤ፡ ባይጠጣ፡ ንጣት፡ ይገድለው፡ ነበር። "

ንጥሻ: ማንጠስ (ዐነጠሰ)

ንጥሻ: ዝኒ ከማሁ (እንደ ዕንጥስታ)

ንጥቂያ: ቅሚያ (ኢዮ ፳፬፡ ፭፣ ሕዝ ፲፰፡ ፲፮፣ ዓሞ ፫፡ ፲፣ ናሖ ፪፡ ፲፫፣ ፫፡ )

ንጥበት: ነጠባ፣ ጠብታ።

ንጥቢያ (ድፍረት/ነቀፋ) ንጥቢያ: ድፍረት፣ ዘለፋ፣ ነቀፋ፣ ስድብ።

ንጥየ: ተነጠጠ፣ ዐነጠጠ።

ንጥጥር: ክርክር፣ ሙግት።

ንጥፍ (ንጹፍ): የተጸፈጸፈ (ድንጋይ፣ ደረጃ፣ ጸፍጸፍ፣ እብነ በረድ)

ንጥፍ (ንፁፍ): የነጠፈ፣ የደረቀ፣ ያቈረጠ (ወሽ)

ንጩ (ንጹይ): የተነጨ፣ ንቅል።

ንጭታት: በጕንጭ ላይ ያለ የሐዘን ቍስል፡ ጠጕሩ የተነጨ፣ ቈዳው የተላጠ።

ንጭት (ንጽየት): መንጨት፣ መነወት።

ንጭት አደረገ: ንቅል አደረገ።

ንጸራ (ንጻሬ): እይታምልከታማየትመመልከት

ንጹሕ ደም: የጻድቅ፡ የእውነተኛ ሰው ደም፡ በግፍ የፈሰሰ (ኤር፯፡ ፯፣ ማቴ፳፫፡ ፳፭)

ንጹሕ: የነጻ፡ የጠዳ፡ ከማመንዘር የራቀ ሰው፡ ነጭ፡ ጸዐዳ ልብስ።

ንጽሐ ልቡና: ልቡና ንጽሕና፡ የፍጹም ማዕርግ

ንጽሐ ሥጋ: ሥጋ ንጽሕና፡ የወጣኒ ማዕርግ

ንጽሐ ነፍስ: ነፍስ ንጽሕና፡ የማእከላዊ ማዕርግ

ንጽሐ ጠባይዕ: ባሕርይ ንጽሕና

ንጽሕ: ንጽሕና

ንጽሕና: ንጹሕ መኾን፡ ጥራት፡ ጥዳት (፪ቆሮ፡ ፮፡ ፮)

ንፉል: የናፈለ፡ ውዱቅ።

ንፉግ (ጎች): የነፈገ፡ ቢስ፣ ጩቅ፣ ሥሡ፣ ሥሥታም፣ ቅቅታም (ምሳ፩፡ ፲፱፣ ኢሳ፪፡ ፭)

ንፉግነት: ንፉግ መኾን፣ ቢስነት።

ንፋሻም: ንፋሽ የበዛበት እኸል፡ ባለንፋሽ

ንፋሽ: የተነፈሰ፡ ከፍሬ የተለየ ዐሠር

ንፋት (ንፍኀት): ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ ከረቦ መምሰል፣ ማስመሰል።

ንፋው ወሬኛ: "አባን" እይ።

ንፋው: አንዘርዝረው።

ንፌት: ዐፈር፣ ሰበር፣ ዐሠር።

ንፍ (ንፉኅ): የተነፋ፣ ያበጠ፣ የተቀበተተ።

ንፍር: የነፈረ፡ በጣም የሞቀ የፈላ፡ ሊነኩት የማይቻል፡ ቢቀርቡትም የሚልጥ፣ የሚመልጥ፣ የሚለመጥጥ። "ንፍር ውሃ" እንዲሉ።

ንፍርቅ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ። ንፍርቅ አለ፡ ነፈረቀ።

ንፍርቅርቅ: የተሠነጣጠቀ ቍስል ንፍርቅርቅ አለሥንጥቅጥቅ አለ

ንፍሮ: እስኪክክ ድረስ የተቀቀለ እኸል

ንፍቅ: የዲያቆን፣ የቄስ ምክትል፣ ተወራጅ። "ንፍቅ ያዲቆን፣ ንፍቅ ቄስ" እንዲሉ።

ንፍጊያ: ንፍገት፣ ሥሥት፣ ቅቅት (ምሳ፳፰፡ ፲፮፣ ኢሳ፶፮፡ ፲፩፣ ኤር፰፡ ፲፣ ፪ቆሮ፡ ፱፡ ፭፣ )

ንፍጣም (ሞች): ባለብዙ ንፍጥ፣ ካፍንጫው ንፍጥ የማይለይ፡ ሞኝ። ትግሬ ምጥዋም ንፍጥን "ነፍጥ"፡ ንፍጣምን "ነፋጥ" ይለዋል።

ንፍጥ: በቁሙ ካፍንጫ ውስጥ የሚወጣ ተረፈ አንጐል። (ተረት), "አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል። "

ንፍፊታም: ንፍፊት የያዘው፣ ያለበት፣ ባለንፍፊት።

ንፍፊት (ቶች): የጕያ፣ የብብት ዕብጠት (እጅና እግር በቈሰሉ ጊዜ የሚመጣ) "ፍርንትትን" እይ።

ንፍፊት ሞያ: ንፍፊት የሚያብጥበት፣ የሚታይበት የብልት ግራና ቀኝ።

ንፍፊት: የጕያ ዕብጠት ("ነፋ - ነፍኀ" ግስ ጋር ተያያዥ)

ንፎ (ትግ፡ ንፎኅ): እንደጕልላት ያለ ክብር የተሠራ ጌጥ።

ንፎ: (የአፍንጫ ቀለበት)(ነፋ - ነፍኀ)

ንፎ: የአፍንጫ ቀለበት፣ ትንፋሽ የሚያርፍበት፡ ጕትቻ።

ኖኅ (ኖኀ): የሰው ስም፡ በጥፋት ውሃ ባስረሽ ምቺው ጊዜና ከዚያም በኋላ የነበረ ሰው። ከሰብኣ ትካት ይልቅ ዕድሜው ስለረዘመ ኖኅ ተባለ ይላሉ።

ኖኅ: ብዙ ዝናም።

ኖህ: የሰው ስም (ኖኅ)

ኖኅት/ኖኂት: በተጻፈ ፊደል ራስጌና ግርጌ አግድም በመካከል ያለ ጽፈት አልባ።

ኖረ: በራ።

ኖረ: ተቀመጠ፡ ቈየ (ነወረ)

ኖረ: ተቀመጠ፣ እለ፣ ነበረ፣ ቈየ፣ ዘገየ፣ ከረመ።

ኖራ: በቁሙ፡ በእሳት የተቃጠለ (ድንጋይ ዱቄት - ዐመድ)፡ ነጭ ጠመኔ፣ በረቅ መሳይ። ከአሸዋ ጋራ ግንብ መገንቢያ፣ ቤት መለሰኛ፣ መለቅለቂያ፣ ድልድይ መሥሪያ ይሆናል። የኖራ ምስጢር ነጭነትና ብሩህነት፣ ብዙ ጊዜ መኖር ነው።

ኖራ: የደንጊያ ዐመድ (ነወረ)

ኖሬ ፋና: (ነወረ)

ኖሬ: የሰው ስም፡ የሕዝቅኤል አባት። ፋና ማለት ነው።

ኖሮ: ከዚህ ጋር ተመሳሳይ፡ ለኑሮ፡ ንኡስ አገባብ፡ የነገር ጭማሪ። "እከሌ ዋና ያውቅ ኖሮ ዠማውን አሻገረን" (፲፰ ክፍል ቍጥር ተመልከት)

ኖቀኖቀ) ነገነገ: አኖቀኖቀ፡ ድምፅ ሰጠ (የርግብ፣ ያውራ)

ኖባ: እምነትንና ጥምቀትን የተቀበለ (በሐዋርያት ዘመን ነው) በ፲፬፻ .. በአጤ ሰይፈ አርዓድ ጊዜ ጊዮርጊስ የሚባል ክርስቲያናዊ ንጉሥ በኖባ እንደ ነበረ ስንክሳር ይመሰክራል።

ኖባ: የሰው ስም፡ በቈላይቱ ኢትዮጵያ ከግብጽ ወዲህ የሚኖር የኵሽ ልጅ፣ የትግሬ ሳባ ታናሽ ወንድም። ዐቢይ ልዑል ማለት ነው።

ኖባ: የአገር፣ የነገድ ስም፡ ሁለተኛም በአረብኛ ሱዳን ይባላል። "ሱዳንን" እይ።

ኖብ: የሰው ስም፡ የታወቀ ጻድቅ።

ኖብያ: የኖባ አገር፡ ታችኛውና ላይኛው ሱዳን። በግእዝ "ኖባ" ይባላል።

ኖታ/ኖት: የሮማይስጥ ቋንቋ ነው። ትርጓሜውንም "ማስታወሻ" ይሉታል። "ከናወተ" ሊወጣ ይችላል።

ኖታ: የሮማይስጥ ዜማ ምልክት ሥረይ።

ኖት: በወርቅና በብር ፈንታ የታተመ ወረቀት፡ ገንዘብነት ያለው የገንዘብ ምልክት። "ባንክን" ተመልከት።

ኖን: የፊደል ስም "" ነሐስ፣ እባብ ማለት ነው።

ኖኖ: የአገር ስም፡ ዳር አገር።

ኗሪ: የኖረ፣ የሚኖር፡ ያለ፣ የነበረ፡ ከማለቅ፣ ከመጥፋት፣ ከመለወጥ የራቀ።

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ