Friday, June 6, 2025


፪ኛ ፊደል፡ በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ በፊደልነት ስሙ ቤት፡ በአኃዝነት በ፪ ይባላል
( ) የመና የፈ ተለዋዋጭ ዝናም ዝናብ፡ ኰረፍታ ኰረብታ
(ሶበ) በቁም ቀሪነቱን ሳይለቅ ከአንቀጽ በኋላ ጊዜን እያስከተለ አንቀጽ ያስቀራል። ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ ፀሓይ ለመ ከተናባቢ ሣልስ ቅጽል ሲወጣ መኪናን እይ
(በዘ) ዐቢይ አገባብ አዳም በበደለ መድኀኔ ዓለም ክሶ ቀራንዮ ቁማል ከለሜዳ ለብሶ
ቸልታ በቦታ እየገባ በትርፍ ዐማርኛ ኹኖ ቁሞ ያሠኛል አሞራ በሰማይ ሲያይሽ ዋለ
ደቂቅ አገባብ ማድረጊያ፡ ፍችው በቁም ቀሪ በመዠመሪያ እግዜር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ፡ በ፯ኛ ቀን ግን ዐረፈ
በኀ'ተራአሳበረ (አኅበረ) አንድ አደረገ (አስ ("(ኀብረ)" ተመልከት ")) ደረገ
በለ (ትግ) አለ ባለ (ዐድዋ) ባለ ብለኸ በልን ይበልን እይ፡ መዠመሪያውን የለ ተመልከት አለ በለ ባለ የለ እነዚህ ፬ቱ አንድ ዘር ናቸው
በለለ (በሊል በለ) በነነ በረረ፡ ጠፋ ተበላሸ መና ቀረ በለበለን እይ፡ የዚህ ደጊም ነው
በለል የሰለለ የጠፋ፡ ጥፉ ብላሽ አራያ በለል እንዲሉ
በለሰስ፡ በልሳሳ፡ የተገለጠጠ፡ የተበ
በለሱ ወንዴ በለስ
በለሳ ያገር ስም፡ በለሳም አገር
በለሴ በለሳዊ በለስማ፡ ዘክዛካ ሸክሻካ ሻካራ ልብስ፡ መካከሉ ተሸልሎ የሚለ በስ (ዘፍ ) አንዳንድ መምራን በለሳ በሚባል አገር ስለ ተሠራ በለሴ ተባለ ይላሉ
በለስ
በለስ፡ (መሰለ፡ በለሰ) በለስ፡
በለስ (ሶች) በቁሙ፡ የተክል ዕንጨት ስም፡ ከወይን ጋራ የሚተከል፡ የሾላ ወገን ወተታም ዕንጨቱም ፍሬውም በለስ ይባላል
በለስ (በለሶን) ዕፀ ኣእምሮ የገነት ዛፍ፡ አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተው ቅጠሉን የለበሱት፡ ክፉና መልካም የሚያስታውቅ
በለስ ዐምባ የበለስ ዐምባ፡ በለስ ያለበት የሚበቅልበት መንደር፡ በላይ ወግዳ ቈላ ያለ
በለስ አገኘ ገደለ፡ ቀናው ይህ ባህል የወሎ ነው
በለስ ዕድል እዱኛ ጐበዝ ስለ በለስ እንዲል ችግረኛ
በለስ ግዳይ፡ ሔዋን የበለስን ደም እንዳፈሰሰች የሰውን ደም ማፍሰስ ገዳይ በበለሱ ድኻ በንጉሡ
በለሷ በለሲቱ፡ ሴቴ በለስ (ዘፍ )
በለቀጠ ለየ ከፈተ፡ የሴትን ኀፍረት በረገደን እይ
በለቀጥ በልቃጣ የተከፈተ፡ ክፍት
በለበ ለበመ
በለበለ (በልበለ) በነፋስ ኀይል ወዘወዘ አውለበለበ፡ አስረጀ የምን ባል ነው ይበልብለውና እንዲሉ ሴቶች
በለተ፡ አደኸየ፡ ድኻ፡ ብቸኛ፡ አደረገ፡ ብቻ፡ አስቀረ
በለተተ ፈጽሞ አረጀ አፈጀ፡ አሮጌ ኾነ ከጕልምስና ከልምላሜ ተለየ ቀዘቀዘ፡ አፍ ቂጡ ሸበተ የሚነገረው ለሴት አካል ነው
በለተተአፈጀ በለተ
በለው (በለ) ከ፳፰ቱ የኵሽ ልጆች አንዱ በለው ይባላል በለው ከለው እንዲሉ
በለው ላት (በሎ ) ንገረው ራት፡ ምታው ( በለው) ናንን ተመልከት፡ ሞተ ብለኸ ሞትን እይ
በለው መካከለኛ ሰው አምጃር (ዘፍ. ፪፡ ፳፫፡ ፩ቆሮ. ፲፬፡ ፳፰)
በለው ንገረው ምታው፡ባለ
በለው አገርና ነገድ የበለው አገር የበለው ዘር በትግሬ በረሓ የሚገኝ ጕይዲ
በለው የሰው ስም
በለው የሰው ስም፡ባለ
በለዘ (በለሰ) ዘጐነ ጠቈረ፡ ያይን የጥርስ የገላ በረዘንን እይ
በለያ በጐዣም ውስጥ ያለ አገር
በለዲ ሕብሩ ቀለሙ ፍጹም ቀይ ያይዶለ ከፈይ የቀይ ዐይነት ግላስ የሚኾን ግምጃ፡ ባረብኛ ግን ያገር (ሀገራዊ) ማለት ነው
በለድ (ዐረ) የተወለዱበት አገር
በለገ በበጋ ዘነመ፡ በጋው ዝናም ኾነ በትግሪኛ ግን አቀጠለ አቈጠቈጠ ማለት ነው፡ ለቆንና የገቦን ያሳያል
በለጠ (ትግ በለጸ) አደገ ከፍ አለ፡ ላቀ ረዘመ፡ ተረፈ በዛ ፈደፈደ ብልኀ ኾነ፡ ገነነ ከበረ (ተረት) ባልንጀራዬ ሲበልጠኝ ቍንጣን ይፍለጠኝ ፈራ ፈረጠጠ ብለኸ ፈሪን አንፈራጠጠን እይ
በለጠ የወንድ መጠሪያ ስም
በለጠ, ላቀ, በዛ, ተረፈ፡ ከሌላው ልክና መጠን ዐለፈ (የቁመት/የመጠን) ("(ሳሙ. 12 23)") - በለጠ, ከፍ አለ, በዛ, ተረፈ፡ ከሌላው ቁመትና መጠን አለፈ ("(1ሳሙ. 12 23)").
በለጠገ (ብዕለ ጸገወ) ጌተየ፡ ጌታ ሀብታም ኾነ ብዙ ገንዘብ አገኘ፡ ከበረ ዘመነ
በለጠጠ (ፈሊጥ ፈለጠ) ዐይንን ከንፈርን ፈጽሞ ገለጠ፡ ቀለበሰ
በለጠጥ በልጣጣ ብልጥጥ፡ የተበለጠጠ የተገለጠ፡ መገለጢጥ
በለጤ በለጠች፡ የሴት ስም
በለጥ መብለጥ
በለጥ አለ ላቅ አለ
በለጨ (በረጸ በረቀ ፈለጸ ፈለጠ) በጥቂቱ ነደደ በራ፡ ፈለቀ አንጸባረቀ፡ ተገለጠ
በለጭ (በረጽ) ነጭ፡ አልማዝ፡ ቦረቦጭ ፈረንጆች ሚካ የሚሉት የምድር መስተዋት
በለጭማ (በረጸዊ) በግንባሩ ንጣት ነጭነት ያለው ከብት (ግጥም) የኔ አቶ እከሌ የሰጠኝ ሙክት፡ በለጭማ ነው ባለምልክት
በሉ ገዢሩ፡ ምቱ
በሉጥ
በሉጥ የዛፍ ስም፡ ጥንካሬው ከዕንጨት ኹሉ የሚበልጥ፡ ያብርሃም ዛፍ
በሊ ቡሊ ቡሊ ሲሏት ሰውን ቀባ ወዳለበት የምትመራ ዕጭ በሊታ ወፍ የቡሌ ቡሌማ ማለት ነው
በሊታ (በላዒት) የበላች የምትበላ የምታኝክ (ተረት) ጠፍር በሊታ ብት ኼድ ልጓም በሊታ መጣች
በሊት ዝኒ ከማሁ ድልሽ በሊት እንዲሉ
በላ (በሊኅ በልኀ) ሰላ ሾለ፡ ስል ሹል ስለታም ኾነ፡ ፈጠነ፡ ተባ ቢላዋን ቢላን እይ
በላ (በሊዕ በልዐ) ነከሰ ቦጨቀ ጋጠ ገመጠ ጐረሠ፡ አላመጠ ዋጠ ሰለቀጠ ተሴሰየ ተመገበ፡ ቈረጠመ ዐኘከ፡ አቃጠለ፡ ወሰደ አሰጠመ እሳት በላው ውሃ በላው እንዲሉ መሳንን እይ (ተረት) የበላ በለጠኝ፡ የሮጠ አመለጠኝ (ከነዕርሙ በላ) መርዶ ባለመስማቱ ሳያለቅስ ቀረ
በላ ልበልኻ (በልአ እበልከአ) የተጋችና የወርድ ነዢ ቃል ተናገራ ልናገርኻ፡ መልስ ልመልስልኻ
በላ ዐማ ነቀፈ (ቡዳ በላው) አሳበደው ዐመመው (ጕቦ በላ) ተቀበለ (ፊቴን በላኝ) አሳከከኝ (ፊት በላኹ) በብሩህ ገጽ ተቀበሉኝ (አይበሉብሽ) የውስጥ እጅ ዠርባ (አይበላሽ) የማይበላው ውሻ አይበላሽ ጥል እንዲሉ
በላለተ፡ ነጣጠለ፡ ከፋፈለ
በላላ ዝኒ ከማሁ፡ በናና
በላላ ጐራረሠ
በላሽ መት የወፍ የዝንጀሮ ማስፈ ሪያ
በላተኛ (ኞች) የበላት ወገን፡ ብዙ የሚበላ፡ ሆዳም አጥፊ ዘራፊ በፃ ፈጅ ዳግመኛም፡ በላ ተኛ ቢል ኹለት አንቀጽ ይኾናል
በላት (በላዕት) የሚበሉ በዮች
በላች፡ (ቾች) በላቲ) የበለተ፡ የሚ በልት፡ በጋማች፡ ሥጋ፡ ቤት፡ ዐራጅ፡ ባለወግ መበለት፡ (በልቶ) መለየት፡ መነ ጠል፡ ብልት፡ ማውጣት "
በላይ በሰማይ። እንጃ፡ ብለኸ፡ እንጂልኝን፡ አስተውል
በላይ፡ ነኸ፡ ነሽ፡ የወንድና፡ የሴት፡
በላይ፡ ነኽ፡ ቶራ፡ ያዳባይ፡ ዥረት፡ ሐርበኛ። (ግጥም) በላይ፡ ነኸ፡ ቶራ፡ እሱ፡ ባል ነበር፡ ሰው፡ እንደ፡ በሬ፡ ይታረድ፡ ነበር።
በላይ የሰው፡ ስም። (ካንገት፡ በላይ) ከልብ፡ ያልኾነ፡ ነገር። (ግጥም) እንዴት፡ ዐደራችኹ፡ ካንገቴ፡ በላይ፡ የነደደውማ፡ ሆዴ፡ አይደ ለም፡ ወይ።
በላጭ የሚበልጥ፡ ላቂ
በሌ ዝኒ ከማሁ፡ ውረድ በሌ፡ ታች በሌ እንዲሉ ደበለን እይ
በሌ የሰይ ወገን ዶሮ በሌ ሰው በሌ እንዲሉ
በል (በለ) የአለና የባለ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ፡ ተናገር እዘዝ (ማቴ ) እኮና ሲያጐላምሱት፡ በል እኮ በልማ ይላል፡ ዠምር አድርግ ሥራ ምታ ማለት ነው
በልበላ ነፋስ የሚወዘውዘው የደስታ ድንኳን መደረቢያ የበልበላ ምድር እንዲሉ በጋልኛ ግን ዘንጋዳ ማለት ነው፡ ላንፋውን ያሳያል
በልክ) በመጠን፡ በስፍር
በልዩ፡ በውቅ።
በልዩ የወንድና፡ የሴት፡ ስም።
በልግ (ጎች) (ተወን) የበጋ ዝናም፡ የበጋ ቡቃያና መከር የበልግ ገብስ እንዲሉ
በልጣጭ የበለጠጠ የሚበለጥጥ፡ ዝንጀሮ ሐኪም
በሎ (ዎች) የላሽ ወገን፡ ባለ አራት እግር አረንጓዴ ቀለም ራሱን የሚያንቀጠቅጥ አውሬ፡ የጕበና እንቃቅላየእስቆሮቱ ይሁዳ ምሳሌ
በሎታ፡ (ቀስታም) ባ፩፡ ወይም፡ ባ፬፡ ወገን፡ ስለት፡ ያለው፡ የንት፡ የብረት፡ ዱላ፡ በመቱበት፡ ጊዜ፡ ራስ፡ ቅል  የሚበልት፡ ቈዳን፡ ከሥጋ፡ ዐጥንትን፡ ካጥንት፡ የሚለይ፡ (ኢዮ፵፩፡ ፳፩) ዐጪሩ፡ ቈመጥ' ይባላል፡ ጐመድን፡ ተመ ልከት
በሎታ፡ ባለማንጠልጠያ፡ ራሳም፡ ከን ተሮ፡ ሰንበር፡ ያለው፡
በመላ ኼደ) ሳይጠይቅ መሪ መን
በመላ ኼደ) ሳይጠይቅ መሪ መንገድ ሳይዝ በዳበሳ እንዲያው ተራመደ ዕውሩ መንገደኛው። (በመላ ተናገረ) ሳያውቅ/ሳይረዳ አወራ።
በማሪያም እጅ ተይዛለች ሴቲቱ ነፍሴ ጡር ኾናለች።
በሞተ፡ ከዳ በሞተና፡ በከዳ፡ ፈንታ፡ ተተኪ፡ ምትክ፡ (ወታደር)
በሰ
በሰ፡ ገበታ
በሰ) (ጠበሳ) አጭበሰበሰ ("አላስነድድ ኣላሳይ አለ አጨሰ በትክክል መንደድን ማየትን ከለከለ አጭፈነፈነ ጨነበሰን እይ የዚህ ዘር ነው")
በሰለ (በሲል በሰለ) ከከ ተንደረከከ ሸተ ጐመራ ደረቀ፡ ጠነከረ
በሰለ መግል ያዘ ላላ ዕባጩ (ጕንፋኑ በሰለ) መውረድን መንቈርቈርን ተወ ንፍጡ
በሰላ (ትግ) ማሳ ቅብቅብ የለሰ ለሰ ዕርሻ
በሰላ ለባለዳ የሚከፈል ገንዘብ፡ መከፈሉ የታወቀ ርግጥ የኾነ የበሰላ ዋስ እንዲሉ
በሰሎ መብል መጠጥ
በሰሰ (ዐረ በጸ) ሰለለ ሰበቀ አሳበቀ አዋሸከ
በሰቈለ የሕዝብ፡ ጐሰቈለ የካህናት ነው
በሰቈለ ጐሰቈለ
በሰበሰ (በስበሰ አንበስበሰ) ራሰ ረጠበ ሾቀ ሻገተ፡ ተበላሸ በሸቀጠ፡ ጠቈረ ተለወጠ (ዳን ፲፭ ፳፫ ፳፭ ዮኤ ) ቦከቦከንንና ቦነቸንን እይ
በሰበስ በስባሳ ብስብስ ብስባሽ የበሰበሰ የሻገተ የተለወጠ የቦከቦከ የጠቈረ ዕንጨት ሣር ገለባ ሥጋ ቈዳ፡ በሽቃጣ ሻጋታ (ኢዮ ፳፭ )
በሰና (ትግ በስነወ) ባሰ ማሰነ ተለወጠ፡ ጎማ ከረፋዞ
በሰከ በተከ ቈረጠ በጠሰ በቀላል
በሰውነቱ) ሰው በመኾኑ ሥጋ በመልበሱ ነፍስን በመንሣቱ።
በሳ (ትግ በስዐ) ሰረሰረ ፈለፈለ ሸነቈረ ቀደደ ነደለ (ዘፀ ፳፩ )

በሳሳ ሸነቋቈረ ቀዳደደ ነዳደለ እንደ መስቀሉ ይበሳሳኝ እንዲል ማለኛ

በሳስ (ሶች) ሰባቂ አሳባቂ ነገረ ሠሪ ቀጣፊ

በሳስነት ሰባቂነት አዋሻኪነት

በሳይ በሳል፡ የሚበስል፡ ጥሬ እኸል ተክል

በስቋላ (ሎች) ጐስቋላ

በስባሽ የሚበሰብስ፡ ሰው ፈራሽ ተለዋጭ

በስተ (በኩል እስተ)

በስተቀረ - በስተቀር ዝኒ ከማሁ የቀረ የተተወ ያለፈ የተረሳ ነገር

በስቲያ (ወዲያ እስተ)

በስከ (በኩል እስተ) (በሸከከ) አንበሸከከ አንቀባረረ አንበጠረረ

በሶ (ትግ በሰወ አበሰበሰ በሶን) በቁሙ፡ ከገብስ ቈሎ የተፈጨ ዶቄት በውሃ የራሰ የተበሰበሰ

በሶብላ (በሶ ብላ) ለወጥ የሚ ኾን ተክል፡ ፍሬው እበሶ ምጥን ውስጥ የሚገባ፡ ቃናው ቅቤ ቅቤ የሚል ቅመም፡ ጐን ደሮች ዘቃቅቤ (ዜጋ ቅቤ) ይሉታል ሹሮን ወጥን ቅቤን በሱ ብላ ማለት ነው (የማር በሶ) ሻሜት ጣፋጭ ምግብ (ግጥም) ድኻ ሲናገር ሬት ኮሶ፡ ሀብታም ሲናገር የማር በሶ ሻሜትን እይ

በረ

በረ ከተማ ("የከተማ በር በጥንካሬ የተበጀ የማንኛውም ዐጥር በር ጠንካራ ከኾነ ከተም በር ይባላል ከተማ ቀጪኔ ከንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እስከ ዐጤ ምኒልክ የነበሩ ዐዛውንት ቁም ነገርን ቀልድ አስመስለው የሚናገሩ አለቃ ሐሤቱ በሃይማኖት ተከሰው አፈ ንጉሥ ነሲቡ ችሎት በቀረቡ ጊዜ እንዲህ ብለው ተቹ ይባላል አባቴ የርስዎን ሃይማኖት ጌቶቻችንም እኛም እናምንበት ነበር ነገር ግን ይህች ዐዲሷ ሃይማኖት ለመንግሥት ደግ ናት ስለ ተባለች ተቀብለናታል። ርስዎም ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ሃይማኖት ሳይቀበሉ እስከ ዛሬ ከቈዩ ይቀጡ በቃ ")

በረሓ (በርሖ በርሐ) ዱር ምድረ በዳ ውድማ ደን ቈላ ውሃ አልባ

በረሓኛ (በረኸኛ ኞች) ሐቃላዊ (ገዳማዊ) የበረሓ በረሓዊ፡ በበረሓ የሚኖር ዘላን ዐዳኝ ሽፍታ፡ መናኝ ባሕታዊ

በረሰ ተሰረዘ በረደ ቀዘቀዘ፡ ፍል ውሃው

በረሰ ተሻረ ጠፋ ከንቱ ብላሽ ኾነ፡ የንቍጣጣሽ መንቀያ ለት ስላልተቀበረ ረከሰ፡ ያስማት ያይነ ጥላ የክታብ የመድኀኒት የሥራሥር (የጠንቋይ ማታለል)

በረረ (በሪር በረ) ቱር አለ ከነፈ ተጣደፈ፡ በአየር በምድር ሮጠ ፈረጠጠ ጋለበ ሸሸ ሸመጠጠ (ዘኍ ፲፮ ፴፬ ፩ሳሙ ፲፱ ፲፪) ወደ ሰማይ ኼደ ወጣ አሞራውም በረረ፡ ቅሉም ተሰበረ እንዲሉ

በረረ ዐለፈ ዘለቀ ገባ የጊዜና ኀላፊ ትንቢቱም ይበር ይበራል ቢል እንጂ፡ ይበርር ይበርራል አይልም፡ ቢልም ስሕተት ነው

በረረ, ፈጠነ, ጋለበ, ፈረጠጠ, ሸመጠጠ - በረረ, ፈጠነ, ጋለበ, ፈጠነ, ሮጠ። (ተረት) ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል - (ምሳሌ) በችኮላ የያዙት በችኮላ ይለቃል። ገጠጠ ብለኸ አንጋጠጠን ተመልከት - ቀና ብለህ ወደ ላይ ተመልከት።

በረራ ሩጫ ፍርጠጣ ግልቢያ

በረር የበረረ ነጥቆ በረር እንዲሉ

በረሮ (ዎች) በቁሙ፡ ጥቍር ጥን ዝዛ መሳይ፡ በክንፍና በእግር የሚሮጥ፡ ቈዳና ዐይነ ምድር አተላ የሚበላ የሚገምጥ፡ በቈላ የሚኖር የሚቀመጥ

በረቀ (በሪቅ በረቀ) ብልጭ አለ፡ ፈለቀ በራ (ኢዮ ፴፱ ፳፫)

በረቀ ተመዘዘ ተወረወረ

በረቀ ነጣ፡ ብርቅ ድንቅ ኾነ (ጸበረቀ) እይ

በረቀሰ (በረቀ) ነደለ በሳ ጣሰ አፈረሰ ጣለ፡ ያጥር የቅጥር የዦር የድልድል

በረቀቀ (ትግ ሐባ በርቀቀ) ፈሱን ለቀቀ፡ መቋጠር አቃተው ከርጅና የተነሣ

በረቃቀሰ በብዙ ወገን አፈራረሰ በታተነ

በረቈጠ በረከተ በዛ፡ ተጨመረ ከለ ረዘመ ታደሰ፡ የነገር

በረቅ በቁሙ፡ ነጭ ዐፈር፡ ደንጊያ ብሓ ብክካ ቤት መለቅለቂያ የምድር ኖራ ጠመኔ (ኤር ፳፪ ፲፬) በገረንን እይ

በረቅ ገበያ ግሃ፡ በረቅ ያለበት ዐፈሩ በረቅ የኾነ ገበያ

በረቋ ነጣ ገረጣ፡ በሰለ ደረሰ የበረቋ የበረቋውን፡ የነጣ የነጣውን፡ ትልቅ ትልቁን (ዕድ)

በረበረ (በርብሮ በረበረ) በዘበዘ ዘረፈ፡ ጎለበጠ፡ የላዩን በውስጥ የውስጡን በላይ አደረገ መረመረን እይ

በረበረ ቦረቦረ

በረታ (ትግ በርትዐ) ዐየለ ጠና ጠነከረ፡ ጐበዘ ጐለበተ ዛሬ ግን ትግሮች በርትዐን በርትዔ ይሉታል

በረት (ቶች) በጥብቅ የተሠራ የከ ብት ማደሪያ፡ የሚሠራውም በካብ በግርግር በማገር በሽምጥ ዐጥር ነው (ሕዝ ፳፭ )

በረነነ (ባሕረረ) ባነነ ቃዠ ደነ ገጠ

በረንዳ በቤት በራፍ ያለ መለሳ፡ በዙሪያ የተበጀ ሰበሰብ፡ ደረጃ ንጣፍ ደንጊያ ያለበት ስፍራ በረንዳ የፈረንጅ ቋንቋ ነው

በረኛ (ኞች) (አንቀጻዊ) በር ባቂ ኬለኛ (ዮሐ ) ወንድና ሴትን ለመለየት

በረኛነት በር ዘጊነት ከፋችነት ጠባቂነት

በረኛዋ ያች በረኛ፡ የርሷ በረኛ

በረኛው በረኛ፡ የርሱ በረኛ

በረኛዪቱ ዝኒ ከማሁ (ዮሐ ፲፰ ፲፮)

በረከ በረከከ (በሪክ በረከ) ሸብረክ አለ፡ ጕልበቱን ዐጥፎ በጕልበት ቆመ፡ ለመውለድ ለመስገድ ተጣጥፎ ተኛ ተኰደኰደ (ግጥም) አዳል ግመሊቱን ይላታል ብረኪ፡ መንደሮቹ ጥቂት፡ ሰዎቹ አነካኪ

በረከተ (ባርኮ ባረከ በረከት) በቁሙ፡ በዛ ተጨመረ፡ ተረፈ ተትረፈረፈ ፈዶፈደ፡ የምግብ የሀብት የገንዘብ

በረከተ ሰነበተ ቈየ እብድ የያዘው መልክ አይበረክትም እንዲሉ

በረከተ ሥጋ ሀብተ ሥጋ

በረከተ ቢስ አሲዳም

በረከተ ነፍስ ሀብተ ነፍስ

በረከተ ዐበጠ ተነፋ፡ የሆድ

በረከታም ባለበረከት፡ ረድኤታም
በረከት ምርቃት ጸጋ ሀብት ዕድል ድልብ ዐላባ ረድኤት ብዛት (ዘዳ ፳፫ )
በረከት በቁሙ፡ በረከተ
በረካ የወሎ ምርቃት በረካ ኹኑ እንዲል ወልይ
በረኰተ ሊጥን ቀበረ ደፈነ ረመጠ ርሚጦ ጋገረ ኣበሰለ
በረኸት ያገር ስም፡ ከቡልጋ በታች ከአዳል በላይ ያለ አገር ግእዝ (በረከት) በረከች ተንበረከከች ይላልና፡ ፮ቶ በሚባለው ከተማ የግመሊቱን መንበርከክ ያስረዳል።
በረዘ (በሪዝ በረዘ) ጠጅ ጣለ በጠበጠ ዘለለ፡ ጠላን ወይም ውሃን ከማር ቀላቀለ ደባለቀ በረሰንንና በረዶን እይ
በረዘ ቀዝቃዛ ውሃን በፍል ውሃ ላይ ጨመረ
በረዥ (በረየ) አነሰ ጐደለ፡ ብልጭ አለ
በረዥራዣ የተብረዠረዠ፡ ጭፍን ጭፍንፍን
በረየ በረገገ በሬኛ ወገሸ ደነበረ፡ ፈራ ደነገጠ፡ በረረ ሸሸ (ተረት) እባብ ያየ ልጥ ቢያይ በረየ
በረደ (በሪድ በረደ) በቁሙ፡ ቀዘቀዘ፡ በረዶ፡ ሙቀት አልባ ኾነ፡ ቍጣው ጠቡ ውሃ ጥሙ አየሩ በረደና በረዘ በረሰ በምስጢር አንድ ናቸው
በረደ ሞረደ ፈገፈገ ዘረዘረ በረዶ እንዲሉ
በረደ ደከመ ደነዘ ስለቱ በረደ
በረደደ (በርዶዶ) ረጋ ጸና ጠነ ከረ ከበደ በረታ
በረደደ ቀጠቀጠ መታ በረደደ ዐጕልና ገቢር መኾኑን አስተውል
በረደድ በርዳዳ የበረደደ የጸና የበ ረታ የከበደ፡ ጽኑ ጠንካራ ብርቱ
በረደድ የሰው ስም
በረድ ነጭ የብርሌና የብርጭቆ ዐይነት ደንጊያ እብንን እይ
በረድፍ በረድፉ፡ በየረድፉ) በተራ በተራው፡ በየተራው - በተራ በተራ።
በረዶ (በረድ) የዝናም ደንጊያ፡ የውሃ ጠጠር፡ የእኸልና የአትክልት ፀር (ፈረንጅ ሠራሽ በረዶ) እየተሰበረ የሚሼጥ የሚታደል በረድ ግእዝኛ ነው
በረዷም (ዘበረድ) በረዶ ያለበት ደጋ ተራራ፡ የወልን ቧሒትን የመሰለ
በረጀ ብልጭ አለ፡ በረዠ
በረገደ ከፈተ ከፈለ ተረረ ኹለት አደረገ ፈለጠ
በረገድ / በረገዱ፡ በክፍል በክፍሉ ("በወገን በወገኑ")
በረገድ በርጋዳ የተከፈተ ክፍት፡ የተፈለጠ ፍልጥ
በረገገ ተገታ ደነገጠ ፈራ ደነበረ በረየ አፈገፈገ፡ ዦሮውን ቀፈረ፡ ዐይኑን ተኰረ
በረገገ ፈነከተ ሰበረ ወለለ ራሱን በረገገው እንዲሉ
በረገግ በርጋጋ የደነበረ ደንባራ
በረገግ አለ በረገገ
በሪ (በራሂ) የሚበራ
በሪድ በራድ የበረደ የቀዘቀዘ፡ ቀዝቃዛ ውሃ
በራ (ዎች) (በርሖ በርሐ በራሕ) መላጣ ራሰ ገላጣ ጠጕሩ የሸሸ ከቦታው የታጣ፡ ቡሓ (ግጥም) እንካ ብላ አለችኝ ደረቁን እንጀራ፡ እሷ በነካካው በራሰው ልትበላ
በራ ባራ (በሪህ በርሀ) ቦግ ተግ አለ፡ ታየ ተገለጠ፡ ወገገ ፈካ ነጣ ሸበረቀ ዕውርን ምን ትፈልጋለኸ ቢሉት፡ ዐይኔ እንዲበራ አለ (ማር ፶፩)
በራሕ በግእዝ ("በራ" - መላጣ ማለት ነው ")
በራሪ (ዎች) የሚበር የሚከንፍ የሚያልፍ፡ አንበጣ፡ ወፍ፡ አሞራ፡ ጠያር፡ ጥያራ (ምሳ ፳፮ ዘካ )
በራቂ የበረቀ የሚበርቅ፡ ብልጭ ያለ የሚበራ
በራቂት ያገር ስም፡ በትግሬ ውስጥ የምትገኝ አገር የምትበርቅ ባለበረቅ ማለት ነው
በራብ ዐለንጋ ተገረፈ) "ይልሰው ይቀምሰው ዐጣ"
በራነት (ብርሐት) በራ ቡሓ መኾን፡ ቡሕነት መላጣነት (ዘሌ ፲፫ ፵፪)
በራኪ የሚበርክ
በራዥ (ዦች) የበረዘ የሚበርዝ የሚበጠብጥ፡ በጥባጭ ጠጅ ጣይ መሸተኛ ዐጣሪ
በራይ ረገጣ አኺዶ
በራጅ የሚበርድ፡ ቀዝቃዛ ብረት ቍርበት
በራፍ ያጥር የቅጥር የቤት መግ ቢያ፡ አፈ በር ማለት ነው
በሬ (ብዒር በዐረ ብዕር) ስሙን አይምጣ ተላይ አይቸግረው ተጅ አይጡ የሚሉት እንስሳ፡ የቀንድ ከብት ተጠምዶ የሚያርስ፡ ሞኝ አላዋቂ (አልቃሽ) በሬ ሆይ ሣሩን ኣየኸና ገደሉን ሳታይ በሬ ከበረየ የወጣ ነው አባትን ተመልከት
በሬ ወለደ የውሸት ውሸት
በሬሳ (ኦሮ) ወንዝ፡ የወንዝ ስም፡ ትርጓሜው ሸልሙ ማለተ ነው በሬሳ ወንዝ እንዲሉ በወግዳና በተጕለት ቈላ ግን ሱላይ ይባላል፡ ይኸውም የደብረ ብርሃን ዠማ ነው
በሬው በሬ፡ የርሱ በሬ
በር (ሮች) ደጃፍ ክፍት ኅዋ መውጫና መግቢያ ማለፊያ መዝለቂያ፡ ብስ ነዳላ፡ ኬላ ዐራዳ (ስርቆሽ በር) ነገሥታት መኳንንት ተሰርቀው (ተደብቀው) የሚወጡበት ኋለኛ በር (የወንድ በር) በጠላት ሠራ ዊት መካከል የጐበዝ መተላለፊያ መንገድ (፪ነገ ፳፫ ፲፯) (የጐድን በር) ለግብር ወደ ቤተ መንግሥት አዳራሽ ሥጋ የሚገባበት
በር መታ ክፈቱልኝ አለ
በር በረበረ
በር ከፋች በቁሙ፡ ቍልፍ ያዥ
በር ከፋች (እምነ) የግእዝ አገባብ ተመልከት
በር ዘጊ (ዐጻዌ ኆኅት) በርን የሚዘጋ የሚቈልፍ
በር ደጃፍ፡ በረረ
በርሚል (ሎች) ከብረት የተሠራ ባለ፪ መቀነት ባላ፩ ፍንጭ የድብኝት ዐይነት፡ ወይም በብረት መሸቢያ የተገጣጠመ የን ጨት ቀፎ (ሻታ) በብረቱ ከባሕር ጋዝና ቤንዚን ስቢርቶ፡ በንጨቱ ዘይትና ወይን ጠጅ ይመጣበታል በርሚል ዐረብኛ ነው
በርሞሌ የሽቱ ስም፡ ቀረሻሽንቦ ከሚመስል ቅጠል የሚሠራ ሽቱ
በርቀቅ አለ ላጥ ቀደድ አለ፡ ተፈሳ
በርቃሳ ብርቅስ የተበረቀሰ የተ ጣሰ የፈረሰ
በርቆ ብልጭ ብሎ (ተረት) ባልነቃ ሠንጥቆ ባልደመነ በርቆ ገና በርቆ ገና ዘንሞ
በርበራ የሱማሌ አገር፡ አቅኒውና
በርበሬ (በርበሪ በርበራዊ) መልኩ የበርበርን ጠጕር የሚመስል ቍንዶ በርበሬ ቍንዶን እይ
በርበሬ በቁሙ፡ ቀዮ፡ ከበርበር የመጣ ተክል ሲበሉት የሚያቃጥል የሚለበልብ የሚ ተኵስ፡ ከሽንኵርትና ከጨው ጋራ የሚደለኸ የሚዘጋጅ በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ እንዲሉ ሚጥሚጣንና ቃሪያን እይ (የውሻ በርበሬ) ፍሬው የማይበላ የዱር በርበሬ
በርበር (ሮች) ያልተማረ ያልሠለጠነ ሕዝብ፡ ጭንጩ አረመኔ፡ ሽፍታ ወያኔ ዘራፊ ከግብጽ ቀጥሎ የሚገኝ የነገድና ያገር ስም፡ የአፍሪቃ ክፍል እነዚህሁም ማሮክ አልዤሪ ቱኒስ ትሪፖሊ ናቸው፡ በግእዝ ሐቃል ይባላሉ (ቈላ ፲፩)
በርባሪ የበረበረ የሚበረብር የሚገለብጥ፡ ባለመንሽ፡ ወራሪ ዘራፊ
በርባሮስ ታላቅ ሰፊ ጕድጓድ የጥልቅ ጥልቅ ታች መጨረሻ መቀመቅ
በርባን የሰው ስም፡ በወንጌል የተነገረ ሽፍታ ወንበዴ ቀማኛ የወንበዶች አለቃ
በርተሎሜዎስ የሰው ስም፡ ካ፲፪ቱ ሐዋርያት ፩ዱ
በርታ አለ በረታ
በርታ አለ ጠንክር አለ በርታ በል፡ ጠንከር በል፡ አበረታት፡ አጠናን፡ አጠነካከር፡ መበርታት
በርታ ጥና ጠንክር ጨክን ዐይል (ሐጌ )
በርኖሴ (በርኖሳዊ) ተምች ጥቍር ትል፡ በርኖስ የሚመስል
በርኖስ (ሠቅ) ከበግ ጠጕር የተ ሠራ ማቅ ዝተት
በርኖስና ካባ በለበሱ ጊዜ ቆቡንና ኳሱን ወደ ደረታቸው መላሰሻውን ወደ ዠርባቸው ያደርጋሉ፡ ዘወትር በበቅሎ ተቀምጠው ፈረስ
በርከት መበርከት
በርከት አለ በረከተ፡ በዛ አለ
በርከት አደረገ አበረከተ
በርከክ መንበርከክ
በርከክ አለ ተንበረከከ፡ ቀስትን ጥይትን ለመንደፍ ለመተኰስ
በርካ (ዐረ ቢርካ) ድልድል ዦር የውሃ መቆሚያ መጠራቀሚያ
በርካታ የበረከተ የበዛ፡ ብዙ
በርካች የሚበረክት የሚበዛ
በርደዶ ብርቱ ኀይለኛ ራስ የሚመታ ጠላ ሸሎንን እይ
በርጋጅ የበረገደ የሚበረግድ የሚ ከፍት ረር
በርጋጊ የበረገገ የሚበረግግ፡ ደንባሪ
በርግጥ፡ ሰውነት
በርጣጣ ኵሩ ዕጅር፡ በጥራራ
በርጩማ (ኦሮ) ግርንቡድ እግር ያለው ክብ መቀመጫ፡ ደቅ መሳይ፡ ወይም በምስማር የተበጀ ሞላላ የሳንቃ ቍራጭ
በሮ ከንፎ ሮጦ ተጣድፎ (ኢሳ ) በርሮ አለማለቱን አስተውል
በሮች (አባዕር) ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ እንስሶች (ዘፀ ፳፬ )
በሸረከ በጠረቀ ቀደደ ሸረከተ
በሸረክ በሽራካ የተበሸረከ ቀዳዳ ሸርካታ
በሸቀ ዐዘነ ተከዘ፡ ተበሳጨ ተናደደ ልቡ በሽቋል እንዲሉ በትግሪኛ ግን ተላጠ ማለት ነው
በሸቀጠ ፈጽሞ ራሰ ረሰረሰ፡ በሰበሰ በከተ ተበላሸ
በሸቀጥ በሽቃጣ (ጦች) ብሽቅጥ የበሸቀጠ የራሰ የረሰረሰ፡ በክት ነው ረኛ ከት
በሸበሸ ተጠመቀ፡ መላ ተረፈ ወፈረ ለሰለሰ
በሺ የበሳ የሚበላ የሚነድል፡ ሸንቋሪ
በሻቃ ብሽቅ የበሸቀ ያዘነ የተ ከዘ የተናደደ
በሻኸ የሰው ስም ("በፈለገኸ/በፈቀደኸ") "በሻኸ ውረድ" ዝኒ ከማሁ
በሽ (ቅልብሽ) ልሽልሽ መቅለሽለሽ፡ ቅልብሽ ዞበሽ አለው፡ አቅለሸለሸው፡ ልውጣ ልመለስ አለው በሽታን እይ፡ የዚህ ዘር ነው ምእላድ ኹኖ ስለ ተጨመረበት በዚህ አልተጻፈም
በሽሎ የበጌምድር ወንዝ ስም፡ በወሎና በየጁ መካከል ያለ ዠማ
በሽበሽ የመላ የተረፈ፡ ምሉ ትርፍ
በሽቢያ ጋለበ) ሥር የሌለው ነገር ተናገረ
በሽተኛ (ኞች) ዕመምተኛ ጤና የሌለው ዱያታም
በሽተኛነት ዕመምተኛነት ጤና ቢስ ነት
በሽታ (በሸበሸ) በቁሙ፡ ዕመም፡ ራስ ምታትና ፍልጠት፡ ሆድ ቍርጠት፡ ቍርጥማት ውጋት ተስቦ ወባ ትኵሳት ምች፡ የመሰለው ኹሉ። (የኅዳር በሽታ) ባ፲፱፻፲፩ ኅዳር ቀን ላሙስ አጥቢያ ከሌሊቱ ደረቅ የመዓት ካፊያ አካፋ፡ ከዚህ የተነሣ ዐፍለኛ ወንድና ሴት ልጅ እግር ኹሉ ዐለቀ ነገር ግን ወግዳ ሕርያቆስ አገር አልገባም (የከብት በሽታ) በሬን ላምን የሚያስለቅስና የሚያስቀዝን ዐለቀን እይ አንዳንድ ሰዎች ታን ያጠብቁና በሽታ ከሸተተ የወጣ ነው ይላሉ
በሽታ ሰከረ) ሳይጠጣ መጠጥ ስለ ሸተተው።
በሽታ በሽ ማለት
በሽታ ወጣለት ለቀቀው ዳነ
በቀለ (በቊል በቈለ በቀሎ በቀለ) በቁሙ፡ ጐነቈለ፡ ካፈር ከመሬት ተዛመደ ተዋሐደ፡ ጸደቀ፡ ሥርን ወደ ታች ቅጠልን ወደ ላይ ሰደደ፡ ሠረጸ ተገኘ በልብ ዐደረ ተያዘ፡ ቂሙ ጠቡ ጥሉ።
በቀለኛ ደመኛ ቂመኛ፡ ደም መላሽ
በቀላል ተኰሰ ("አቃጠለ ' ገረፈ ጠበሰ ፈጀ አንገበገበ ገመለን ተመልከት ለበለበ ጠለፈ አሰረ እገናኘ አያያዘ ለበለበ ለፈለፈ ለብላቢ የለበለበ የሚለበልብ የሚያቃጥል እሳት በርበሬ ሳማ ፌጦ ዝንጅብል ለብላቢት አለብላቢት ") ("ቶች")
በቀል (ሎች) የበቀለ የወጣ፡ እወ ጣጡ፡ እንደ ዘንባባ ያማረ የሰመረ ወጣት አንድ በቀል ዐብሮ በቀል እንዲሉ።
በቀል በቁሙ፡ ቅጣት የክፉ ብድራት ዕዳ ፍዳ ቂም ደም ዐሎ (ሮሜ ፲፪ ፲፱)
በቀል ዐረቦች ሥሩን ጥሬውን የሚበሉት ተክል
በቀልት (ግእዝ) ዘንባባ
በቀረ ምኞትና ጸጸት "ጥፋተኛ ሰው እቤታችን ዐድሮ ከሚያስቀጣን ምነው ሳይመጣ በቀረ" ።ንኡስ ኣገባብ ሲኾን
በቀር "ከጻድቃን በቀር ኃጥኣን መንግሥተ ሰማይ አይገቡም" "ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ከዮሐንስ በቀር ሌላ አልተገኘም"
በቀር በቁሙ፡ ቀረ
በቀቀ ባቀቀ (በቂቅ በቀ ዕብ ባቃቅ አስራቈተ ባዶ አደረገ በቂው በቀወ) ተከፈተ ተለቀቀ፡ ክፍት ኾነ፡ ዋሻ መሰለ፡ የአፍ የጕድጓድ ኦሮ ንቃቃትን በቀቃ የሚለው ከዚህ ጋራ ይሰማማል በቀበቀን ተመልከት፡ የዚህ ዘር ነው
በቀበቀ (በቂቅ በቀ በቅበቀ) ሠነጠቀ ተረተረ ዕዳሪ አወጣ፡ አጥልቆ ዐረሰ በረበረ
በቀበቅ በቅባቃ የሚንሰቀሰቅ፡ ሳም ላጤ
በቀተ ነዘነዘ ነተረከ ጨቀጨቀ ዘበዘበ
በቀንዱ ዐፈር ያዘ) ጠብ ፈለገ አረ ያውራሪሥ ቀንድ ባፍንጯው ላይ እንዲታይ እንደ ዝኆንና ዕሪያ፡ ጥርስ ቀንዱ የኾነ ሞርስ ፍንጭት የሚባል የባሕር አውሬ አለ ።የዝኆንም ጥርስ በግእዝ (ቀርን) ቀንድ ይባላል
በቀኝ አውለኝ) ቀኑን ሙሉ ጠብቀኝ፡ ክፉውን አርቅልኝ
በቀደም ለት) ካለፈው ሳምንት ባንዱ ቀን
በቁሙ ሳይቀመጥ ሳያርፍ "እከሌ ከኼደበት በቁሙ ተመለሰ"
በቁሙ በሕይወቱ ሳይታመም ሳይሞት ከነነፍሱ "ወንጀለኛውን በቁሙ ቀበሩት"
በቁሙ ዐይን እግር ተብሎ በግእዝ የተነገረውና ሌላውም ይህን የመሰለው ኹሉ ባማርኛም እንዲሁ ስለ ኾነ ትርጓሜው በቁሙ ይባላል ዳግመኛም በግእዝ ገደለ ነገረ ሰበረ ብሎ ባማርኛ ፪ኛውን ፊደል ከማጥበቅ በቀር ልዩነት ስለሌለው በቁሙ ያሠኛል።
በቁም ቀሪ (በግእዝ በፈጣሪ ለፈጣሪ የተባለው ባማርኛ ስለማይለወጥ በቁም ቀሪ ተባለ ")
በቁም ቀበረ) ወንጀለኛን ከራሱ በታች እመሬት አገባ እንደ ራስ ዐምዶ
በቁም እንዳለ ሳይለወጥ
በቁምኸ ቁመሽ ሳለኸ (እንደ ቆምኸ ሳትቀመጥ ታዘዝ ማለት ነው ") "በቁምኸ ማርያም ቈሎ ታቈርጥምኸ" እንዲሉ።
በቍርጥ ሠራ) በተወሰነ ጊዜ ጨርሶ ሊያስረክብ (ዐነጠ ገነባ ማንኛውንም ሥራ ሠራ አበጀ ")
በቍርጥ ዐደር) በታወቀ ጥቅም ያደረ
በቂ (በቋዒ) የበቃ ልክ የኾነ የሚበቃ የማያንስ የሚጠቅም፡ ጠቃሚ
በቂ () የገደለ ገዳይ፡ የሞተ የስም ምትክና ቅጽል ኹሉ።
በቂ ሲኾን፡ ዘርቶ አይቅም፡ ወልዶ አይስም ይላል
በቂታ (በቋዒት) የበቃች ልክ የኾነች፡ ያደገች የደረሰች የቈነዠች
በቃ (በቊዕ በቍዐ) ልክ ኾነ፡ ተገባ፡ ሰለቸ ተጠገበ፡ ተወረሰ ተፈጸመ ደረሰ በሀብት በውቀት ሠለጠነ፡ በቅድስና ከበረ፡ ፍጹም ኾነ፡ ጣዕም ቀመሰ ጸጋ አገኘ (ይሞት በቃ) ተገባ (ለዘር በቃ) ደረሰ አደገ ጐለመሰ ረባ ጠቀመ (ቤቱ በቃ) አልጠበበም (እንጀራው በቃ) አላነሰም (የርሱ ነገር በቃኝ) ሰለቸኝ (አንዱ በቃኝ) ጠቀመኝ (የበቃ) ቅዱስ የኾነ፡ አረፍት ግዘፍ የማይከለክለው፡ ኀላፍያትንና መጻእያትን የሚያውቅ እሴይ የበቃ የነቃ ልጅ ወለደ
በቃ በለው ማረው፡ ወይም ግደለው፡ ከሥቃይ አሳርፈው
በቃቀለ የበቀለ ድርብ
በቃቃ መላልሶ በቃ (ኢሳ ፳፱)
በቃች (ቾች) የበቀተ የሚበቅት የሚነተርክ፡ ነትራኪ
በቃይ (በቋሊ) የሚበቅል የሚወጣ፡ ጸዳቂ
በቈልት (ቶች) በውሃ ርሶ ዝናም መቶት የበቀለ ያጐነቈለ ባቄላ ስንዴ
በቈሎ (ዎች) ባር ማሽላ (ከባሕር የመጣ ማሽላ) ስለሸቱ ጣዕም ማር ማሽላ ይሉታል
በቅ
በቅ ብቁ (በቋዒ ብቁዕ) በቂ
በቅል (ሱማሌና ሐረርጌ ጕራጌ) የቍጥር ስም፡ መቶ ሸማኔዎችና ዝሓ አዝጊዎች (ድር አድሪዎች) ዝሓውን (ድሩን) አንድ በቅል ኹለት በቅል እንዲሉ
በቅሎ (ዎች) (በቅል አብቅልት) በቁሙ፡ አጋሰስ፡ ከአህያ ከፈረስ የሚ ደቀል፡ አባቱ አህያ እናቱ ፈረስ ባላገሮች ከጥንት ከፍጥረት ስላልነበረ፡ አህያና ፈረስን በማራከብ በሰው ዘዴ ስለ ተገኘ፡ በምድራችን እንዲህ ያል በቅሎ አያውቅም ተባለ ይላሉ፡ የስሙም ምክንያት ይህ እንደ ኾነ ይተርካሉ (የጭን በቅሎ) መቀመጫ ሠጋር ግራጫን ዋርዳን ጨበርን ሸክላን ሳሙናን እይ (ተረት) በቅሎ አባትኸ ማነው ቢሉት፡ እናቴ ፈረስ ነች አለ
በቅሎኛ (በቅላዊ) ሳለበቅሎ፡ በቅሎ ያለው በበቅሎ የተቀመጠ ሰው
በቅጥ በሥርዐት ቀጣ
በቋል () ጨረባ ጥሬ ፈጅ፡ ጐዦ ለመሥራት ቡቃያ ቈራጭ
በበተ አገባ ከተተ በውስጥ አደረገ
በተ
በተሓ (ትግ በቲሓ) ብርዝ፡ ለጋ ጠጅ፡ ጌሾ ያልበዛበት ያልበሰለ (፪ነገ ፲፱ ፴፪ ዮኤ )
በተለየ፡ ንዳ፡ በጠራ፡ ቅዳ፡ እንዲሉ።
በተለየ ይ፡ በብቻ፡ በክፍል።
በተል የስሜን ዐምባ ተራራ
በተበተ (በትበተ) ቦጠቦጠ ፈለፈለ ውስጥ ውስጡን በላ አቃጠለ በገበገ
በተተ ዐለቀ አረጀ፡ የልብስ
በተነ ኣደረገ፡ የምግብ
በተነ ወረወረ፡ ዘሪ አዘራ መንሽ አለ፡ ዘረዘረ ዘረረ፡ ፈታ ለየ ፈነጠቀ ነሰነሰ፡ የዘር ያኺዶ የገንዘብ ያፈር የሸንጎ የደም የሣር (ሩት መዝ ፻፲፪ ሉቃ ፲፭ )
በተን
በተከ (በቲክ በተከ) በሰከ በጠቀ በጠሰ ቈረጠ ኣባላ መታ
በታተነ ፈታታ ለያየ፡ እየብቻ አደረገ፡ ፈነጣጠቀ ነሳነሰ
በታተከ በብዙ ወገን ቈረጠ
በታኝ (ኞች) የበተነ የሚበትን የሚዘራ፡ ወርፃ ዘሪ ኣዝሪ (ምሳ ፲፰ )
በት (ቦቱ) በኀላፊና በትንቢት በዘንድ በትእዛዝ አንቀጽ መጨረሻ እየገባ ይነገራል። መጣበት፡ ይመጣበት፡ ይመጣበትዘንድ፡ ይምጣበት፡ ይኸውም የክፉ ነው ለትን ተመልከት መጽሐፍ ግን በት በማለት ፈንታ ለት ይላል፡ ስሕተት ነው (፩ሳሙ ፲፪ )
በትረ ሙሴ የማርያም ዘንግ፡ ችርንችር፡ ባለማእዘን ዕንጨት፡ ወላድ በምጥ ጊዜ የምትይዘው
በትረ ቃቃን ዱቅንዱቅ፡ መንደልት፡ የካክራ ብረት በትር፡ ድጅኖ በግእዝ ምንኃል ይባላል ቃቃንን እይ
በትረ ወርቅ ከወርቅ የተሠራ ዘንግ
በትረ ያሬድ የተድባበ ማርያም አለቃ፡ ሊቀ ጳጳስ መዠመሪያ አባት ማለት ነው
በትረኛ ተማች ዱለኛ
በትር (በቲር በተረ በትር) ዘንግ ሽመል፡ ምርኵዝ ዱላ ጐመድ ከንተሮ መንደርቶ፡ ለበቅ ንገር የፈሪ በትር ዐሥር እንዲሉ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመን ይህ ተረት ተፈጽሟል አንድ ሠዓሊ ሚስቱን ከወንድ በያዛት ጊዜ በቤቱ ውስጥ አንድ ሸክም ፍልጥ ነበረና እንዳንዱን እየመዘዘና እያማረጠ ጥሎ ከወረሰ በኋላ የሚስቱን ውሽማ ምሬኻለኹና ኺድ አለው እየተባለ ይወራ ነበር
በትር የጐራዴ ምት
በትባች የበተበተ የሚበተብት የሚ በላ፡ ውሻ ዥብ እሳት ቂጥኝ
በትን ዝኒ ከማሁ፡ ዐጭዶ በተን እንዲሉ
በትኩሱ) ሳይበርድ ሳይቈይ
በቶ (መዥርጥ) ኮሶን ገድሎ መዥርጦ ከሆድ የሚያወጣ መድኀኒት፡ ወይም ቅጠል
በቾ (ኦሮ) የነገድና ያገር ስም
በቾ የኮከብ ስም ወቦንን እይ
በነቂስ ባንድ አይቅር ("እስራኤል ከግ ብጽ በነቂስ ወጡ")
በነበሩ የሰው ስም (ሳይወለድ አባቱ የሞተ ልጅ "በነበሩ" ይባላል)
በነነ ቦነነ (ባህነነ) ተነነ በለለ
በነገውም በማግስቱም (፩ሳሙ. ፲፰፥፲)
በኒን የሰው ስም፡ ይሁዲ
በናና ብኩን በረከተ ቢስ ገንዘብ፡ ያልተመረቀ ልጅ
በናና የበነነ የባከነ ከንቱ
በናኝ የሚበን፡ ጉም ጪስ ዶቄት
በንቅልፍ ልብ) የእውን፡ ተቃራኒ፡ ሰው፡ ተኝቶ፡ ሳለ፡ ሳይነቃ
በኖ ሰይጣን እንደ ጪስ በኖ እንደ ጉም ተኖ ጠፋ
በከ
በከለ ቀባ አሳደፈ አበላሸ ኰለፈ አጠፋ፡ የልብስ የስም
በከረ (በኲር በኰረ) መውለድ ዠመረ፡ መዠመሪያ ወለደ አፈራ፡ አላቀ ከፍ አደረገ፡ አበለጠ፡ አባት ወይም የናት ሆድ
በከራ ታላቅ ጋሻ፡ አላባሽ አግሬ (፩ሳሙ ፲፯ ፵፭)
በከራ ኹለት የንዝርት ራስ መሳይ ልጆች መካከሉን በንጨት አጋጥመው በቀጪን ገመድ አብተው (አስረው) ሳብ ረገብ እያደረጉ የሚጫወቱበት መጫወቻ፡ የጋሻ ተምሳሊት
በከበከ (በከከ) ደገደገ፡ ፈላ ዘለለ በቀበቀንን እይ
በከተ (በቲክ በተከ ተበትከ) ራሰ በሸቀጠ በሰበሰ፡ ጠነባ ገማ ሸተተ፡ ተበላሸ ከረፋ
በከተ፡ በሰበሰ፡ ነቀዘ፡ ቀለጠ፡ ተናዶ፡ ፈረሰ፡ ደፈ፡ ተሰበረ፡ ተቀደደ፡ ጠፋ፡ (ዘፍ፮፡ ፲፩)
በከንቱ፡ በብላሽ ("አለዋጋ")
በከንካና ብክንክን የተብከነከነ፡ ቅብዝብዝ
በከከ (በኪክ በከ) ጠፋ ፈረሰ፡ ብላሽ ኾነ
በኩል ዘንድ ስፍራ፡ (መዝ ፻፯፡ ) ባንተ በኩል በርታ፡ በኔ በኩል አታስብ ዳግመኛም ፪ኛ ጨምሮ፡ በበኩሉ፡ በበኩልኸ እያለ በ፱ መደብ ይዘረዘራል።
በኩል ዘንድ፡አከለ
በኵረ ሎሚ ከሎሚ የሚበልጥ ፍሬው ጥፍጥ ብርቱካን
በኵራት ታላላቆች ፍሬዎች መዠመሪያ የበሰሉ ዓሥራት በኵራት እንዲሉ
በኵራት ፊት የተወለዱ ሴቶች ልጆች
በኵር (ሮች) በቁሙ፡ መዠመሪያ አንደኛ ልጅ፡ ታላቅ አለቃ አንጋፋ ግንባር ቀደም ፊተኛ በክር ያማርኛ፡ በኵር የግእዝ ነው ጌታችንም እንደ ሰውነቱ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለመላእክትና ለጻድቃን በኵር ይባላል ክርስቶስ በራችን ኣይዶለም ማለት ይቅርብን ማለት ነው የሰማዩ ርስት (አለቃ ዕንቈ ባሕርይ)
በኵርነት (ብኵርና) በኵር መኾን በፊት መወለድ፡ ልቅና ቅድምና (ዕብ ፲፪ ፲፮)
በካር (ሮች) (በኳሪት) መውለድ ዠማሪ፡ አንድ ጊዜ መዠመሪያ ወላድ
በካከለ ቀባባ፡ ኰላለፈ፡ አጠፋፋ
በካከነ ፈጽሞ ባዘነ ተበተነ
በካይ (ዮች) የበከለ የሚበክል የሚያሳድፍ፡ ስም አጥፊ
በካፋ የሰው ስም፡ ዐጢ በካፋ እንዲሉ ትርጓሜው እጀ ሰፊ ማለት ይመስላል ካፍን እይ
በክ በቁሙ፡ ብላሽ ከንቱ (ግእዝ) ቢያክን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው
በክር በኸር የቀደመቀዳሚ የበክር ልጅ እንዲሉ (መዝ ፻፭ ፴፯ ሉቃ )
በክት በከቻ ብክት (ብትክ) የበከተ የበሰበሰ፡ ታንቆ ታፍኖ የሞተ፡ ኣባላ የተመታ ጥንብ ውዳቂ
በኸረ ሎሚ (ባሕረ ሎሚ) ዝኒ ከማሁ፡ ፑርቱጌዞች ከባሕር ያመጡት (ሎሚ ባሕር) የባሕር ሎሚ
በውል፡ በደንብ/በሚገባ/በጣም
በውቅ የተሠራ) ለዘመድ ለወዳጅ ጥሩና ንጹሕ ኹኖ የተበጀ ዕቃ
በውኑ (ቦኑ) በውነቱ ንኡስ አገባብ ነው (ኢዮ ፳፭ ፴፩)
በውኑ በውነቱ፡ እውን
በዘልማድ) በልማድ፡ ሲደረግ፡ የሚኖር፡ ልማደ፡ ሀገር፡ ያገር፡ ልማድ፡ ካባት፡ የወረደ። በፈረንጅኛ፡ ኩቲም፡ ይባላል። ግዕዝን፡ እይ።
በዘበዘ (በዚዝ በዘ በዝበዘ) በቁሙ፡ ዘረፈ ቀማ በረበረ፡ ዘራ በተነ አባከነ (ኢዮ ፲፱ ናሖ ) ወሰደንን እይ
በዘበዘ አጥበረበረ ትክክል ማየት ከለከለ ኣንጸባረቀ
በዚህ በቁሙ፡ዚህ
በዚያ በቁሙ፡ዚያ
በዚያ በዚያው፡ በዚያውም፡ ላይ፡ በዚያም፡ ፪ቱም፡ ም፡ ዋዌ፡ ነው፡ በቂና፡ ቅጽል። በዚያኛው በዚያ፡ ጊዜ፡ ቅጽል፡ በዚ ያን ጊዜ፡ ማለት፡ ስሕተት፡ ነው፡ ወደዚያ በቂ
በዛ (በዚኅ በዝኀ) ፈደፈደ ተረፈ፡ ከልክ ዐለፈ ረባ በረከተ፡ ዐየለ በረታ፡ ወለደ ከበደ (ተረት) ነገር ቢበዛ ባህያ አይጫንም ማር ሲበዛ ይመራል
በዛ (በዚኅ) በርከት
በዛ አለ በርከት አለ
በዛብሽ የሴት ስም
በዛብኸ (በዝኀ ብከ) የሰው ስም፡ ያባትኸ ዘር ባንተ በዛ ማለት ነው
በዛኹ ቀንሱልኝ አለ ይይዘውን ዐጣ
በዝ
በዝባዥ የበዘበዘ የሚበዘብዝ የሚዘርፍ፡ ዘራፊ ቀማኛ
በዝባዥነት ዘራፊነት ቀማኛነት
በዝባዦች ዘራፎች ቀማኞች (፪ነገ ፲፯ ኢሳ ፳፬ ፲፮)
በዝብዝ ትእዛዝ አንቀጽ፡ ዝረፍ ቀማ (ኢሳ ) ያጤ ዮሐንስ ፈረስ ካሳ በዝብዝ፡ አባ በዝብዝ ካሳ እንዲሉ
በዞ ሜዳ የበዞ ሜዳ
በዞ ያገር ስም፡ በተጕለት ወረዳ በሞጃ ኣጠገብ ያለ አገር
በዠድ (ዶች) ከብልት በላይ ከንብርት በታች ያለ ገላ
በዠገደ (ዠገደ) ዦዠ ነገር ሳተ
በዢ (በዛኂ) የሚበዛ በርካች
በዥር (በጅር) ጀና ተወራራሽ ስለ ኾኑ በጅር በማለት ፈንታ በዥሮንድ ሊባል ይቻላል
በየ (በበ) በእየ፡ ደቂቅ አገባብ በየቤቱ በየወገኑ በያኳያው በየሥራው በየፊናው በያገሩ በየወንዙ እያለ በብትን ሲነገር በቁም ቀሪነቱን ያሳያል እየን ተመልከት
በየነ (በይኖ በየነ) ዐወቀ ተቸ ፈረደ፡ ለየ
በየነ የወንድና የሴት ስም
በየነለት ፈረደለት
በየነበት ፈረደበት
በየደ ደለዘ ሰመረገ ደፈነ ቀባ
በዪ (በሊ) ንገሪ፡ ምቺ
በያኝ (ኞች) (በያኒ) የበየነ የሚበይን የሚፈርድ፡ ፈራጅ ዳኛ ሹም
በያጅ (ጆች) የሚበይድ የሚደፍን፡ መራጊ
በይ (በላዒ) የበላ የሚበላ የሚያቃጥል፡ ሲበዛ በዮች ይላል (ዮሐ ፲፫)
በደለ (ዐረ ለወጠ ቀየረ) በቁሙ፡ ዐመፀ ገፋ በደግ ፈንታ ክፉ መለሰ፡ አደረገ ሠራ (፩ቆሮ ) ዕንጨት ኹኖ የማይጨስ፡ ሰው ኹኖ የማይበድል ለም አበሰንን እይ
በደለኛ (ኞች) የበደለ በዳይ፡ ዐመፀኛ ግፈኛ ክፋተኛ (ዘዳ ፳፭ ምሳ ፳፩ ፲፰ ኢሳ ፲፬ ፪ጢሞ ) በደለኛው እኔ፡ ዐሳረኛው እኔ፡ አምላኬን ትቼ ሰው ማመኔ እንዳለ ጠቦ
በደለኛ የተበደለ በደል የተቀበለ (ኢዮ ፳፬ )
በደላ ብደላ፡ የግፍ ሥራ
በደል ዐመፅ ግፍ ክፉ ሥራ (፪ዜና ሕዝ ፲፰ ፲፯)
በደረ (በዲር በደረ) ሮጠ ፈጠነ ቀደመ (ግእዝ)
በደረገ (በደገ በረገደ) አፈጠነ ተነሥቶ መኼድን
በደበደ (በድበደ) ታመመ ለመመ
በደበድ በድባዳ የተንበደበደ የሚ ንበደበድ፡ የሚፈራ፡ ፈሪ ቡከን
በደነ (በዲን በደነ) በቁሙ፡ ዘዘ ደነዘ፡ ሬሳ ኾነ
በደነፍስ (በድነ ነፍስ) ሰውነተ በድን፡ ድንጉጥ
በደኖ በሐረርጌ ውስጥ ያለ አገር
በደኖ የዛፍ ስም፡ ዓሣን አስክሮ ሚገድል፡ በድን የሚያደርግ፡ እሾኻም የበረሓ ዕንጨት
በደዊ (በዳዊ) ዘላን የበረሓ ሰው በረኸኛ
በደዊዎች (በዳውያን) በምድረ በዳ የሚኖሩ ዘላኖች በረኸኞች
በደው (በዲው በድወ በድው) ዱር በረሓ ምድረ በዳ
በደው የነገድ ስም፡ በሐባብ ያለ ነገድ
በደገ ሠነጠቀ ለየ ከፈለ ገደበንን እይ
በዳ (በዲው በድወ አብደወ ዕብ ባዳእ ትግ ሐባ በድዐ) በቁሙ፡ ወጣ በላይ ኾነ፡ ሰረረ ጠቃ መታ ገሰሰ አጠፋ ፈታ የድንግልና መስረር የአራዊት የእንስሳት የአዕዋፍ፡ መጥቃት የወይፈን ብቻመምታት የድንጕላና ያለሌ፡ መግሰስ ማጥፋት የጕልማሳ መምህራን ግን ዐወቀ ይላሉ
በዳ ቀማ ወሰደ ጕራጌ ቀማ ሲል በዳ እንዲል
በዳይ (ዮች) የሚበድል የሚያምፅ የሚገፋ፡ ለዋጭ ገልባጭ (ኢዮ ፳፪ ፲፱ ፪ቆሮ ፲፪) ድኻ በዳይ እንዲሉ
በድሉ (በዕድሉ) የሰው ስም
በድል ነጐድ የወንጭፍ ስም፡ የጠ ፍር ወንጭፍ ወፈ በድል አብርር በትን ማለት ነው ነጐድን እይ
በድል ናኝ፡ ባ፲፭፻ . . የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ("ድልን ለወገንኸ ናኝ ማለት ነው")
በድል ዐምፅ ግፋ
በድረግ አለ ሳይታሰብ በድንገት ፈጥኖ ተነሣ፡ አፈፍ አለ፡ ሮጠ
በድረግ ፈጠን
በድን (ኖች) ሬሳ፡ የማይሰማ የማይለማ ነፍስ የተለየችው ሥጋ (፪ነገ ፲፱ ፴፭)
በድን ኾነ በደነ ፈዘዘ ደነጋ
በድንነት ሬሳነት ፈዛዛነት፡ አለመ ስማት አለመልማት
በዶስ፡ በኀይል
በዶስ፡ ዛር ክፉ መንፈስ ወንደ ገሪ ("ገላን ልምሾ የሚያደርግ")
በጀ (በገየ) ሰመረ አማረ ተዋበ መልካም ኾነ፡ ተገባ ተሻለ ረባ ጠቀመ፡ በጅ ተሠርቶ ተዘጋጅቶ ሲገደገድ ያልበጀው፡ ሲዋቀር እሳት ፈጀው እንዲሉ (ተረት) ለኔ እናት ምን በጄት (ተሻላት ረባት) አረጀን ፈጀን እይ
በጃለ (በእዴየ ብህለ) ዕሺ አለ፡ ታዘዘ
በጄ (በእዴየ) ዕሺ በጎ በጄ እሠራለኹ፡ ይኹን ማለት
በጅ አይልም አይሰማም፡ ዕሺ አይልም፡ አይታዘዝም
በጅር (በድራ) በዥር፡ ብድር የብ ሱን ዙሮ ባሕሩን ተሻግሮ ወጥቶ ወርዶ ጕልበቱን ለመንግሥት ላበደረና ላገለገለ ሰው የሚሰጥ ገንዘብ
በጅሮንድ (በጅር ወንድ) ጅር ጭፍራው ሰራዊቱ፡ ወንድ ሻለቃው ሥራ መሪው በዥርን እይ
በጅሮንድ (ዶች) (በድራ ወንድ) የወርቅና የብር አፍሳሾችና ያንጥረኞች አዛዥ የገንዘብ ሹም፡ ግምጃ ቤት በጅር ግር ከማለት ከበገረ የቅርብ ትእዛዝ ቢወጣ ግን፡ በጅሮንድ ወንደ በግር ተብሎ ሊተረጐም ይችላልና፡ ገንዘቡን ያሳያል
በገ ሰማይ ዕሪያ ቋንጣውን ውርዴ የሚበላው
በገ ፈጅ ታላቅ ድስት፡ ሰታቴ፡ ያንድ በግ ሥጋ የሚቀቅል
በገረ (በጊር በገረ) ዐጒልና ገቢር አደገ ጐለመሰ፡ ብጕር አወጣ
በገረ ሞከረ ፈተነ፡ ነደፈ መጠነ ለካ፡ ምልክት አደረገ
በገረ ደፈረ ማን በግሮ እንዲሉ
በገር ማስነደፍ ማስበተን/ማስጠዝጠዝ ማስ
በገበገ (ገበገበ) ፈጀ ተኰሰ አቃጠለ፡ ገረፈ አቈሰለ ኦሳመመ
በገነ (ዕብ ናጌን) ቃኘ ነዘረ መታ ደረደረ
በገነ (ገምኖ ገመነ) ደረቀ ከረረ፡ ዐበጠ ቈረበል፡ ከሰለ ዐረረ
በገና
በገና (ዎች) ከገበቴ ከ፪ ቋሚና ካ፩ አግዳሚ ዕንጨት የተዘጋጀ መዘመሪያ መንፈሳዊ ምስጋና ማመስገኛ መዝሙር ባላ፲ አውታር የሚቃኝ የሚነዘር የሚደረ ደር ዳዊት በገናውን ዕዝራ መሰንቆውን እንዲሉ በገና የዥማቱን መድረቅና መክረር ያሳያል ገናን እይ
በገና መታ ነዘረ ደረደረ፡ ዘመረ ከቶ አይቀርም ሞቱ ምንም ቢታክቱ አለ
በገና መቺ
በገና መቺ በገና የሚመታ የሚደ ረድር ጠቦ፡ ወይም ሌላ
በገዛ፡ በራስ/በሰውነት/በባለቤት
በገድ (ትግ) ኀፍረተ ብእሲት በረገደ ማለት ከዚህ የወጣ ነው
በጉ
በጉ (በግዑ) በግ፡ የርሱ በግ
በጊቱ (በግዕታ) ያች በግ በማለት ተባቱና እንስቱ ተለይተው ይታወቃሉ
በጋ (በግዖ በግዐ) ሐጋይ ድርቅ፡ የድርቅ ወራት፡ ካ፬ቱ ክፍለ ዘመን አንዱ እጅ፡ ወር ወይም ፳፩ ቀን ተሩብ፡ ከታኅሣሥ ፳፮ እስከ መጋቢት ፳፮ በባላገር ግን ከመስከረም ዠምሮ እስከ ሠኔ በጋ ይባላል፡ ይኸውም ከመስከረም ፳፯ እስከ ሠኔ ፳፮ ማለት ነው ለሞኝ ሠኔ በጋው፡ መስከረም ክረምቱ ወር በጋ ባጀ በጋ ከማለት የወጣ ነው
በጋማች (ሐማቴ በግዕ) በግ ዐማች፡ በግን የሚያርድ የሚያወራርድ የሚጠብስ፡ ሥጋ ቤት ሥጋ ሸያጭ ዐመተን እይ
በጋማች) በግ ዐማች (የበግን "(የፍየልን የበሬን)" ሥጋ እየቈረጠ የሚሼጥ ")
በጋሪ የበገረ የሚበግር የሚሞክር የሚፈትን፡ ሞካሪ ፈታኝ
በጋር (ሮች) ጸርከል ዙሪያ ክብ መንደፊያ መበገሪያ መሣሪያ
በጋር ገመድ በረቅ ከሰል
በጋኝ የሚበግን፡ ደራቂ
በጌ የኔ በግ
በጌምድር (ምድረ በግዕየ) በግ ያለበት የሚረባበት፡ የኔ በግ ምድር (በግዓዊ) የበግ በጋም ማለት ነው
በጌምድር በጎ ማለፊያ ለም ምድር ደንቢያንና ፎገራን ያሳያል
በግ (በግዕ) በቁሙ፡ የቤት እንስሳ፡ ከላይ የፊት ጥርስ የሌለው የሚያመሰኳ ከብት፡ የጻድቅ ምሳሌ (ዮሐ ፳፱) (ተረት) ሞኝ ካመረረ በግ ከበረረ ተባቱም እንስቱም በግ ይባላል ነገር ግን፡
በግር (በጅር) ሞክር ፈትን በደረንን ተመልከት
በግሮ ሞክሮ ፈትኖ ደፍሮ
በግባጊ የበገበገ የሚበገብግ፡ አቃጣይ ገራፊ አቍሳይ ቂጥኝ
በጎ (በግዓዊ) ደኅና ደግ ማለፊያ መልካም ሥራ ሰው ነገር (መዝ ) ዕሺ በጎ ዐይነ በጎ እንዲሉ
በጎ ነው ደኅና ነው፡ ተሽሎታል
በጎ አድራጊ ደግ ሠሪ (ነሐ ፲፯)
በጎ አድራጎት የጽድቅ ሥራ ማድረግ መሥራት፡ ምግባረ ሠናይ
በጎ ኾነ (ጥዕየ ሐይወ) ዳነ ተፈወሰ፡ ጤና ኣገኘ
በጎች (አባግዕ ዓት) የቤት እንስሶች ከብቶች የጻድቃን ምሳሌዎች (ዘፀ ማቴ ፵፭)
በጎነት በጎ መኾን መዳን
በጎነት ደግነት ቸርነት (ዘዳ ፳፰ ፲፩ ኤር ፲፰ )
በጓ
በጓ ያች በግ፡ የርሷ በግ ፪ኛውን አለ እይ
በጠለ (በጺል በጸለ ተበጽለ) ተበጨቀ ተነጨ ተቈረጠ ተላጠ፡ ተቀደደ
በጠለለ (በጠለ ባጠለ) በለለ ጠፋ፡ የነገር
በጠሰ (በተከ መተረ ቈረጠ ሰከ ጐመደ ቦደሰ) የገመድ የጠፍር የፈትል የቅጠል ያንገት ያንዠት የስልክ ቀነጠሰን እይ
በጠረረ (በጠረ ጠረረ) ኰራ ታበየ
በጠረር በጥራራ የኰራ የታበየ
በጠረቀ (በጠረ ጠረቀ) ነደለ በሳ ሸነቈረ፡ ዕንጨትን ልብስን
በጠቀ በጨቀ
በጠበጠ (ትግ በጥበጠ) ጦር ሰበቀ ወጠወጠንን ተመልከት
በጠበጠ (ዐረብና ትግ በጽበጸ) ጠመቀ በረዘ መታ ሰበቀ ወዘወዘ፡ ዐሸ ዐመሰ ኣደፈረሰ፡ አተራመሰ አወከ፡ የጠላ የጠጅ የተልባ የኮሶ የሆድ የባሕር የሕዝብ (ተረት) ዓሣ ያለበት ባሕር ዕውር ያለበት ደብር ሳይበጠበጥ አያድር (ግጥም) ይህስ ጠጅ ቤታችኹ በጣም ይገርማል፡ በሚጠጣበት ቀን ይበጠብጣል
በጠጠ (ትግ በጠ) ለጥ አለ፡ በጠጥ ጣለ
በጠጣም በጠጥ ያለው ባለበጠጥ፡ በጠጠ ብዙ፡ በግን ፍየልን የመሰለ እንስሳ
በጠጥ (ጦች) በቁሙ፡ እንዳተር የተድበለበለ የበግና የፍየል የሠሥ የድኵላ የብሖር ኵስ
በጢሕ የዱባ ዐይነት ተክል ብርጭቅ (ዘኍ ፲፩ )
በጣ (በጢሕ በጥሐ) ፈቃቈራ ተፈተፈሠነተረ ሠነጠቀ ጋረጠ፡ ለጌጥ ወይም ለመድኀኒት
በጣኄ ምኒልክ ጊዜ የነበሩ፡ በዕንባቦና በዐድዋ ጦርነት የተዋጉ
በጣም፡ ንኡስ አገባብ ("አለልክ በጅጉ በብዙ በጸና") (መዝ. ፷፬፡ ፮፡ ማር. ፯፡ )
በጣም እጅግ ብዙ ጣመ ጣም
በጣሳ ብጥስ የተበጠሰ የተበተከ የተበሰከ
በጣሽ የበጠሰ የሚበጥስ የሚቈርጥ፡ ቈራጭ
በጣጠሰ መታተረ ቈራረጠ በሳሰከ (ዳን ፳፬)
በጣጣ (ዐረ) ድንች
በጥ
በጥ አለ በጠጠ፡ አለ
በጥራቂ የሚበጠርቅ የሚነድል የሚበሳ በሺ ሸንቋሪ
በጥባጣ የደፈረሰ የታወከ፡ ብስጩ
በጥባጭ (ጮች) የበጠበጠ የሚበጠብጥ የሚያደፈርስ የሚያውክ፡ ሰባቂ አዋኪ በጥባጭ ሳለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ
በጥባጭነት ዐማሽነት አዋኪነት
በጥብጥ ዝኒከማሁ ለበጥባጭ ደብረ በጥብጥ እንዲሉ
በጨቀ (በቲክ በተከ) በጠሰ ቈረጠ መተረ በሰከ፡ የጨርቅ የቅጠል
በጨበጪ (ዕብ ባጻጽ ባጽቤጽ) ድምፅ ሰጠ፡ ፈለቀ መነጨ፡ ፈሰሰ ወረደ የቅዘን
በጨበጭ በጭባ የሚንበጨበጭ የሚፈልቅ የሚመነጭ
በጨጓራኸ ይቈረባል) አይቀጡ ቅጣት ትቀ ጣለኸ ማለት ነው ("(መዝ. ፻፮፥ ፴፯)")
በጨጨ ወራ ወረቀ፡ ብጫ የልጅ ቅዘን አስኳል ዐደይ መሰለ
በጪ (ዎች) (በጣሒ) የበጣ የሚበጣ፡ ተፍታፊ ሠንታሪ
በጫቂ የበጨቀ የሚበጭቅ የሚበጥስ፡ በጣሽ ቈራጭ
በጫጨቀ በጣጠሰ ቈራረጠ
በጭት ታሠሠ) ታላቅ ጭንቅ ኾነ ተደረገ
በፍታ ረዥም ሸማ ልስልስ፡ ወይም ሻሽ፡ ዐዲስ ነጭ ጸዐዳ (ዘፀ ፳፮ ፴፩ ሉቃ ፳፬ ፲፪)
ቡሓ ራስ ራሰ መላጣ ራሰ በራ፡ ወይም እብቅና በረቅ የሚመስል ዕከክ በራሱ ላይ ያለበት ራስ ቡሓ ሰው
ቡሓ በግ ራስ ነጭ በግ
ቡሓ ነጭ ዕከክ፡ ለምጽ መላጣ በቡሓ ላይ ቈረቈር እንዲሉ
ቡሔ (ቡሓዊ) የበዓል ስም፡ ደብረ ታቦር፡ የቍርባን ምሳሌ ኅብስት፡ የጌታችንን ግርፋት የሚያሳስብ ጅራፍ የሚዘጋጅበት
ቡሔ በዓል፡ቡሕ (ቦሐ)
ቡሄ የበዓል ስም፡ቡሕ
ቡሔ የብርሃን ብርሃናዊ፡ ብርሃኔ የኔ ብርሃን መብራቴ ችቦዬ ዳቦቴ ቡሔ በሉ ልጆች ኹሉ። ቡሔ ማለት በደብረ ታቦር ብሎ የተገለጠውን የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል፡ የልብሱንም እንደ በረዶ ነጭ ጸዐዳ መኾን ያስረዳል ዳግመ ኛም እረኞች፡ አክሥቴ ቤት አለኝ ለከት ይላሉና፡ ቡሔ (ብሑእየ) ቡሖዬ ተብሎ ቢተረጐም የታቦር ለት ተቦክቶ የሚጋገረውን ኅብስት ያሳያል የየቡሔ ቢል፡ የነጐድጓድ ምሳሌ ጅራፍን ይገልጻል
ቡሕ (በዊሕ ቦሐ) ብርሃን፡ የታየ የተገለጠ የጐላ የበራ፡ ጸዐዳ የምድር ኖራ በረቅ ነጭ ኆጻ በለጭን እይ
ቡሕ (ነቢሕ) ቡፍ መጮኸ ውሻ
ቡሕ አለ (ነብሐ) ቡፍ አለ፡ ጮኸ
ቡሕነት (ብርሃት) ዝኒ ከማሁ፡ ቡሓ መኾን (ዘሌ ፲፫ ፵፪) መላጣነት በራን እይ
ቡሖ (ብሒእ ብሕአ ብሑእ) የቦካ የበሰለ የሖመጠጠ መፃፃ ሊጥ ለቀለምና ለጭቃም ይኾናል። ቦካን ተመልከት
ቡሖቃ የቡሖ ዕቃ፡ የርሾና የሊጥ መቀመጫ እንስራ ማድጋ ገበርሾ ገንዳ
ቡሊ ባለ
ቡላ ቡላ (ትግ) አንቡላ የጠጅ አተላ የንሰት ዶቄት ነጩ ጥሩው ጋሎች ቡልቡላ የሚሉት ከዚህ ጋራ አንድ ነው
ቡላድ እሳት የሚወጣው የቦረቦጭ ደንጊያ (ኢዮ ፳፰ ሕዝ ) ቡላድ ባረብኛ ፉላዝ ይባላል (ተረት) ከምድር አደላድሎ ካህያ፡ ከቡላድ አደላድሎ ከቋያ ዲናሞን እይ
ቡሌ ትኵስ ወተት የሚመስል ኀይለኛ የጐንደር ጠላ
ቡሌ ጠጕሩ ፈገግ ያለ ዐይጥማ በሬ፡ ኩባያ እይ
ቡሌማ ዝኒ ከማሁ፡ የቡሌ ዐይነት
ቡል ቡል አለ ቡልቅ ቡልቅ አለ (ቦለቦለ) እይ፡ የዚህ ደጊም ነው
ቡል አለ በኀይል ጨሰ፡ ቡን አለ
ቡልማ የቡላ ወገን ትል
ቡልቅ (ፍልቅ) የፈለቀ የወጣ ፈረንጆች ቦልካን የሚሉት እሳተ ገሞራ ከዚህ ጋራ ይሰማማል
ቡልቅ አለ (ቦለቀ) ፍልቅ እለ፡ ዘለለ ናረ ተወረወረ፡ የውሃ የጪስ የእሳት
ቡልኮ የጋሎች ጋቢ፡ ድረ ቀጪን ማገ ወፍራም፡ የሚደምቅ የሚሞቅ፡ ቁመተ ረዥም በውድ የሚሼጥ
ቡልጋ ያገር ስም፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱበት እቲሳ
ቡልጌ የቡልጋ ሰው፡ ቡልጎች፡ የቡልጋ ተወላጆች
ቡሴ የዛፍ ስም፡ ዕንጨቱ ቀጥ ያለ፡ በስተላይ ለጣራ ማገር የሚኾን ዛፍነቱ ቅጠ ሉን የሐር ትሎች የሚበሉትን ቱት ይመስላል
ቡረቃ ዝላይ ፍንታ
ቡሩኬ የኔ ቡሩክ፡ የቍልምጫ ንግግር ነው
ቡሩክ የተባረከ የተመሰገነ የተመረቀ የተቀደሰ፡ ክቡር ምስጉን ምሩቅ ቅዱስ ቡሩክ ኾነ፡ ተባረከ ተመረቀ ተቀደሰ፡ ምሩቅ ኾነ
ቡራ ከረዩ አለ አመረረ ተቈጣ፡ ጠብ አነሣ
ቡራ የከረዩ በሬ፡ ዶባ አውሬ ቡራ ከረዩ እንዲሉ ጕራጊ በሬ ሲል ቦራ የሚለው ከዚህ ጋራ አንድ ነው
ቡራቅ ክንፍ ያለው የመብረቅ ፈረስ፡ እስላሞች መሐመድ በርሱ ተቀምጦ ወደ ገነት ወጣ ይላሉ
ቡራቡሬ የቡሬ ቡራ፡ ነጠብጣብ ሰመግ
ቡራኬ (ዎች) የመክፈልት ወግ፡ ታላቅ ዕድል ለቄስ ላቃቢ ለባለቤት የሚሰጥ፡ ተባርኮ የተቈረሰ ዳቦ
ቡራኬ ምርቃት ምስጋና፡ መባረክ መቀደስ፡ በተገብሮነትም ይፈታል (ግእዝ)
ቡሬ ዝንጕርጕር ነጭና ጥቍር በሬ፡ ብርሃናዊ ማለት ነው ቦሩን እይ
ቡሬማ የቡሬ ዐይነትና ወገን
ቡሬነት ዝንጕርጕርነት
ቡርሳ በሲዳሞ ውስጥ ያለ ቀበሌ
ቡርሳ የጭፍራ ስም፡ የቀድሞ ዘመን የጦር ሰራዊት
ቡርሽ ከጠጕር የተበጀ ቀለም መቀቢያና ልብስ መጥረጊያ ዕቃ ማጠቢያ ሙሬ ቡርሽ እንግሊዝኛ ነው
ቡርቅ የተቦረቀ የተዘለለ የታለፈ፡ ውርብ ቦቀረ ብለኽ ቡቅርን እይ
ቡርቅቅ አለ ተንቦረቀቀ አለልክ ሰፋ
ቡርቅቅ የተንቦረቀቀ
ቡርቡጭ (ጥቋ) መቋጠር
ቡርቡጭ አለ በጥቂቱ መላ፡ የሆድ
ቡርቲ (ኦሮ ቡርዲ) በላይኛ ከንፈር መካከል ያለ ያሞጠሞጠ ትርፍ ሥጋ አርቲ ቡርቲ እንዲሉ
ቡርፉጭ ረብ ማለት፡ መተኛት ቡርቡጭና ቡርፉጭ ከረፈጠና ከረፈቀ የወጡ ናቸው
ቡርፉጭ አለ በፈር ላይ ተኛ ወይፈኑ፡ እንደ ተቀመጠ አንቀላፋ ሰውየው
ቡሽ በቁሙ፡ የጠርሙስ (ቃሩራ) መክደኛ መግጠሚያ ማፈኛ፡ ለስላሳ ዕንጨት
ቡሽት ጠንካራ የዝናም ልብስ የቀ ድሞ ዘመን
ቡቃ በቁሙ፡ ቡኣ
ቡቃያ (ዮች) (በቍል) ከመሬት የወጣ የቅንጣት ልምላሜ፡ ያትክልት ፍል ችግኝ ግልግል፡ ሣሩም ቅጠሉም እኸሉም ቡቃያ፡ ዐራስ ልጅ ጨቅላ ብቋያ፡ ዝኒ ከማሁ ለቡቃያ (ዘፍ ፲፩ ፲፪)
ቡቃያ በቁሙ፡ በቀለ
ቡቅራት ልጭታት
ቡቅር (ሮች) የተቦቀረ አሻራ
ቡታ ሰደደ እሪ አለ፡ የደረሰበትን ግፍና በደል አስታወቀ (መሳ ፲፱ ፳፱)
ቡታ ታላቅ ጩኸት እሪታ፡ የሰው ያለኸ ድረሱልኝ ማለት በጋልኛ ነጣቂ ማለት ነው
ቡትርፍ አለ በጭቅ አለ
ቡትርፍ አደረገ ቡጭቅ አደረገ
ቡትርፍ የተቦተረፈ የተበላሸ፡ ቡጭቅ
ቡቺ () የውሻ መጥሪያ፡ ነቲ ቡች ቡች፡ ዝኒ ከማሁ፡ ኵቲ ኵቲ
ቡቺ ኵቲ፡ ቡችላ
ቡችላ (ሎች) የውሻ የዥብ የተኵላ የቀበሮ የነብር የግስላ ያንበሳ ግልገል (ማቴ ፲፭ ፳፯)
ቡና በቁሙ፡ የታወቀ የተክል ዕንጨት ስም፡ ፍሬው ተቈልቶና ተወቅጦ ፈልቶ የሚጠጣ አንዳንድ ሰዎች ቡኖ በሚባል አገር ስለ ተገኘ ቡና ተባለ ይላሉ ፈረንጆች ግን በከፋ ስላገኙት ካፌ (ከፋዊ) ይሉታል
ቡና ቦና ከቦነነ ሊወጣ ይችላል
ቡን ብን መብነን
ቡን አለ ብን አለ ቦነነ በነነ
ቡንኝ የበሬ ኵልልት ደደቆ ከሣርና ከውሃ የሚመጣ
ቡንኝ ጥቍር ጤፍ ዛላው ብን የሚል
ቡኖ ያገር ስም፡ የሚገኝበትም በኦሮ ቤት ኢሉባቦር ነው
ቡኣ (በዊእ ቦአ) አንዠት ያን ዠት መውረድ መዛወር መጠምዘዝ አለስፍራው መግባት ፈረሰኛው ቡኣ ወረደው እንዲሉ ንፍጥና አክታ የሚመስል ያንዠት ውስጥ በሽታ ኦሮ ወረደ ሲል ቡኤ ይላ ልና፡ ቡኣ ማለት ከጋልኛ ይሰማማል
ቡከን ባካና ፈሪ ቅዘናም ቡከን ዘረጥራጤ እንዲሉ
ቡከንፈሪ ባከነ
ቡከኖች ፈሪዎች
ቡክቡካ (ብኍብኍ) የበሰበስ የጪስ ዕንጨት፡ የወይባና የሸፈሬ የዋንዛ ቡጥ የንግ ሥር፡ ሴቶች ቀምመው የሚያጨሱት የሚታጠኑት ሽታ ያለው ማንኛውም ፍልጥ
ቡዪት ከቻች ዝቅ የምትል መስቴ፡ ወይም ጥዋ ቡያማ የቡያ ዐይነት ማለት ነው፡ የመጠኗን ትንሽነት ያሳያል
ቡያ (ዮች) ከርግብና ከዋኔ የምታ ንስ ከወፍ የምትልቅ የዋኔ ወገን
ቡደን የመሬት ዳርና ዳር ትልም ፈር ማቀባበያ
ቡዳ ቡዳሃ
ቡዳ ዐጣኝ ቡዳ የበላውን ሰው እያ ጠነ የሚያስጮኸ የሚያስለቅቅ ባለመድኀኒት
ቡዳ ዛር ጋኔን ምትሀት፡ እጀ ሰብ ዐይነ ወርቅ ዐይነ ወግ ሰውን የሚይዝ የሚያሳብድ የሚያስለፈልፍ፡ አተላ የሚያስጠጣ፡ እንደ ዥብ የሚያስጐነብስ ዐንካሳ የሚያ ደርግ፡ አዉ የሚያሠኝ ሰውየው ስለሚከሳና ስለሚመነምን ቡዳ በላው ይባላል ያማርኛ ገበታዋሪያ ተመልከት (ግጥም) እሱ ያመጣውን እሱ እስኪመልሰው፡ ሥጋ ጠጅ ይወድም ቡዳ የበላው ሰው ዐጤ ዮሐንስ በግድ ቍረብ ያሉት ቃልቻ
ቡዳ የህንዶችንና የሺኖችን የጃፓኖችን ሃይማኖትና ምግባር ያደሰ የህንድ ንጉሥ ልጅ እውነተኛ መናኝ ግሑሥ ባሕታዊ ህንዶች ቡዳሃ ይሉታል፡ ፈላስፋ ብልኅ ዐዋቂ ብርሃናዊ ማለት ነው ብላቴን ጌታ ኅሩይ የጻፉትን የጃፓን ታሪክ ተመልከት
ቡዳ ጠይብ (ጠቢብ) ቀጥቃጭ ባለጅ ሥራ ዐዋቂ ሠራተኛ ጃን ሸላሚ አንጥረኛ፡ በጥቂት ብልኀት የሰውን ድካም የሚበላ ብልኀተኛ ፋቂ ሸማኔ፡ ከሰው ቡዳ ከብት ጐዳ ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው ይህ ስም ያገራችን ሰዎች የቡዳሃን ሃይማ ኖት አለመቀበላቸውን ያሳያል ወረኃን እይ፡ ወንጀልን ተመልከት ዳግመኛም ከህንድ በመጡት ፈላሾች ገዳም በመንዝ ይልማ በተጕለት ይጣ ምግል ዋሻ የቡዳሃ ምስል መኖሩን አቶ በእደ ማርያም ደስታ ይመሰክራሉ። የጠይብም ቡዳ መባል ምክያቱ ይህ ነው
ቡዳነት ቡድነት ጠይብነት ምትሀትነት፡ ቡዳ መኾን
ቡድስ አለ ግምስ ጕምድ ብጥስ አለ ቦዳ ማለት ከዚህ የወጣ ነው
ቡድስ የተቦደሰ የተገመሰ የተጐመደ፡ ጕምድ ግምስ ደበል ወደሮ ዕርሻ
ቡድኖች የጨዋታ ጓዶች
ቡዶች ጠይቦች ባለጆች ቀጥቃጮች አንጥረኞች ቍንጣሮች
ቡግሪት እንደ መንቀል ያለች ታናሽ ጥዋ የሐረግ ቢጋር (ንድፍ) ያለባት፡ የተጠማ ሰው በውስጧ ያለውን መጠጥ አንድ ጊዜ ጠጥቶ ለመጨረስ (ለመጨለጥ) የሚበግራት
ቡጢ (ዎች) የቡጥ ዐይነት ጡጫ፡ ኵርኵም ቡጢ ያሠኘው ባራቱ ጣቶች መካከል እንደ ጕጥ ኹኖ የሚታየው አውራ ጣት ነው (ኤር ፲፭ ፳፩ ፩ቆሮ ፲፩)
ቡጢ ጡጫ ቦጠቦጠ
ቡጣም ቡጥ ያለው ባለቡጥ፡ ወፍራም ዕንወት ዳቦ
ቡጥ (ጦች) ውስጥ ልብ፡ የዳቦ የንጨት
ቡጥ በቁሙ፡ቦጠቦጠ
ቡጥልቅ አለ ተቦጠለቀ፡ ተከፈለ፡ በኀይል ወይም በድንገት ወጣ
ቡጥልቅ የተከፈለ የወጣ
ቡጥቦጣ ጕርጐራ ጕጥጐጣ
ቡጥ መቧጠጥ መጠጥ
ቡጥ ከድስት እየተቧጠጠ የሚወጣ ቅባኑግና ቅመም የገባበት የሽንብራ ወጥ
ቡጨቃ ዐጨዳ ቈረጣ ሐሜት
ቡጭር የተቧጨረ የተጫረ፡ ጭር
ቡጭርቅታ ውሃ በተመታ ጊዜ የሚሰጠው ድምጥ
ቡጭቃት ዐንገትጌ ያንገት ማግቢያ
ቡጭቅ አለ ተቦጨቀ
ቡጭቅ አደረገ ቦጨቀ
ቡጭቅ የተቦጨቀ፡ ዕጭድ ቍርጥ፡ ባዘቶ ሣር ገላ
ቡጭቡጭ አለ ተበጠበጠ ታወከ፡ ዐዘነ ፈራ፡ የሆድ
ቡፌ የንስራ ሽንቍር፡ የወተት መተንፈሻ
ቡፍ በአፍንጫ መተንፈስ፡ ትንፋሽ ማውጣት፡ ያህያ የበቅሎ የፈረስ
ቡፍ አለ አፍ አለ፡ ተነፈሰ
ቡፍ አለ ድምፁን ኣሳንሶ ጮኸ፡ ውሻው
ቡፍና እንቡሽቡሽ፡ ያልፈላ ጕሽ፡ ወይም መናኛ፡ ሆድ የሚያገሣ የሚያስገሣ
(እመ) ዐቢይ አገባብ ላሳር የጣፈው ቢነግድ አይተርፈው በሩቆች ወንዶችና ሴቶች ትንቢት አንቀጽ ሲገባ፡ ቢተኙ ነገር ያገኙ፡ ቢነሡ ነገር ይረሱ ይላል ካሉታ ጋራ ሲነገር ራብዕ ይኾናል
ቢላ የሣር ጭጐጐት፡ እልብስ ላይ የሚሰካ
ቢላ የሣር ጭጐጐት፡ ቢላዋ
ቢላሖ (ባልሐ) እንደ ወርካና እንደ ሾላ ያለ ነጭ ዛፍ ዐጽቃም፡ ጥላው ከፀሓይ የሚያድን
ቢላሆ ዛፍ፡ ቢላሖ
ቢላቢሎ (ብልባሌ) ሥሥ ልብስ፡ ወይም ቅዳጅ፡ የቢሎ ቢሎ
ቢላዋ
ቢላዋ (በልኀ በሊኅ ብልኅ) በቁሙ፡ ካራ ማረጃ ማወራረጃ መጥ ቢያ መሰለቻ አባን እይ
ቢላዎች ካሮች ማረጃዎች
ቢል ቢናገር፡ ቢመታ።
ቢልልኝ የሰው፡ ስም፡ ቢፈቅድልኝ፡ ማለት፡ ነው
ቢልቢል አለ ነደደ፡ ተቃጠለ በጥ ቂቱ
ቢሎ ዝኒ ከማሁ ቢሎ አንድነትን፡ ቢላቢሎ ብዛትን ያስተረጕማል
ቢሰበር ዕዳ) ሰበበኛ ሰው።
ቢሰኛ ክፉ ዐሳቢ ቢሰኛኸን ያርቅ እንዲሉ
ቢስ (ሶች) (ብኡስ) የቸር ተቃራኒ፡ ደረቅ ዐይነ መጥፎ፡ ክፉ ንፉግ ጩቅ (ገድን ልብን ዐቅምን እይ) ቢስ አይይኸ እንዲሉ ቸርን ቢያጠብቁት ቢስ ይኾናል
ቢስ ንፉግ፡ ባሰ
ቢስ ገላ ድል ቍምጥና ያለበት የተበላሸ ገላ አካል
ቢስነት ንፉግነት ክፋት
ቢራ የፈረንጅ መጠጥ፡ ጠላ
ቢራራ የሰው ስም፡ ቢያዝን ይህን ደግሞ ባይገድል ማለት ነው።
ቢሹ/ቢሹም ቢፈልጉ/ቢፈልጉም "ቢሹም አይገኝ" እንዲሉ።
ቢሻን (ኦሮ ውሃ) ቢፈልገን "ቢሻን እንጠጣለን ባይሻን እንተዋለን" (ጠላ ስለ ቀጠነ)
ቢሻኸ ቢፈልግሽ/ቢፈቅድኸ
ቢሻው ቢፈልገው/ቢፈቅደው (ተረት) "ሊጠጣ ቢሻው ይዋኛል ሊቀማ ቢሻው ይዳኛል"
ቢሻው ንኡስ አገባብ (በጎ ደግ ማለፊያ)
ቢተዋ (፪ሳሙ ) እንደ ዋንጫ ያለ የክንድ እንባር፡ በ፪ ወገን ማጠፊያ ያለው፡ በሽቦ የሚጋጠም፡ ያ፲፪ ገዳይ ሽልማት፡ በትግሪኛ ቢታ ይባላል
ቢትወደድ (ብሑት) የሠለጠነ ሥሉጥ፡ ባለመብት ባለሙሉ ሥልጣን ቢት ንጉሥ፡ ወደድ ወዳጅ የንጉሥ ወዳጅ፡ ንጉሥ የሚወደው፡ ንጉሥን የሚወድ፡ ዋና ባለል ማለት ነው (ዘፍ ፴፱ ) ሲበዛ ቢትወደዶች ይላል
ቢትወደድ ባለሙሉ ሥል ጣን
ቢቸግርሽ ሳታውቂ ቢሳንሽ ቢጨንቅሽ ባትችዪ ("ገረዘን" እይ)
ቢወጣ/ብትወጣ፡ የወንድና የሴት ስም ("ቢያድግ ብታድግ ማለት ነው")
ቢዘን የተራራ ስም፡ በሐማሴን ግዛት ያለ ታላቅ ደብር ገዳም ደበረንን ተመልከት
ቢዘኖች የቢዘን መነኵሴዎች
ቢያ ( እስመ) ንኡስ አገባብ ኾነ ቢያ ይኾናል ቢያ እያለ የአንቀጽ ትራስ በመኾን ይነገራል እኮንን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው፡ ጋሜንን እይ
ቢያርዱ አይሞት) የተንቀሳ ቃሽ ስም (እንጭራር - ሞተ ብለው ' ሲተ ዉት እንደ ገና ይንቀሳቀሳል ")
ቢያኩሽ በቁሙ፡ዐከከ
ቢያኩሽ የሥንብጥ እኩሌታ
ቢያክ ቢያክ አለ እንደ በክት እንደ አክታ አየ አደረገ፡ እቤተ ክሲያን የገባ ውሻ ዐር የነካው ዕንጨት አስመሰለ፡ እረከሰ አጸየፈ አጥላላ፡ ወዲያ ወዲያ አለ፡ አላገጠ አፌዘ ቢያክ በግእዝ በቢክ ይባላል
ቢያጥቡ አይጠራ ሽንፍላ፡ዐጠበ
ቢዶ (ዎች) ፈረንጆች እንደ ቀርበታ በግመልና በአገሰስ በሃያ ዠርባ የሚጭ ኑት የውሃ ዕቃ ከብረት የተበጀ ቢዶና ቤዶ የባዶስ ዘር ናቸው
ቢጆ ብጁ የተበጀ፡ ጕርሻ አንድ አፍ እንጀራ እንክብክብ
ቢጋር
ቢጋር (ሮች) በገመድ በከሰል በበ ረቅ የተበገረ የተሣለ የተመለከተ ምልክት ንድፍ መጠን መሠረት ፈረንጆች ፕላን ይሉታል።
ቢጣ (ቢጻ) ባልንጀራዋ ጓደኛዋ
ቢጣ ጐን ጡንቻ ዕንብርን እይ
ቢጤ (ቢጽየ) ባልንጀራዬ ባልንጀሬ ጓደኛዬ ጓዴ (የኔ ቢጤ) የኔ ባልንጀራ የኔ ዐይነት፡ ድኻ ለማኝ
ቢጤዎች (አብያጽ ) እኩ ዮች ቼ፡ የኔ አቻዎች
ቢጥ ቢጤ (በዪጽ ቤጸ ቢጽ) ባልንጀራ ጓደኛ ባልደረባ እኩያ አምሳያ ወደር አቻ ቢጤ ከቢጤው እንዲሉ
(እመ ) በላይነኸ ቶራ እሱ ባልነበር ሰው እንደ በሬ ይታረድ ነበር ሣልሱ በትንቢት፡ ራብዑ በኀላፊ እንደ ገባ አስተውል
የበግ ጩኸትና ጥሪ በጉ ይላል ምን ይላል፡ ይላል በቅርብ ወንድና እኔ በሚል በትንቢት ሲገባ ሳድስ ይኾናል
ባሐላት ጥርኝ የዝባድ አውሬዞ
ባህል (ብሂል ብህለ) ነገር ቃል ድምፅ፡ የነገር ስልት አነጋገር አባባል።
ባህል ልማድ ደንብ
ባሕረ ሐሳብ (ኍልቈ ዘመን) የቀን የሳምንት የወር ያመት፡ የፀሓይ የጨ ረቃ ቍጥር ያለበት፡ የበዓላትና ያጿማት ማውጫ የሚነገርበት ቍጥር ያለው ዘመን፡ ወይም የዘመን ቍጥር ፲ዓመተ ዓለም (ሐሳበ ባሕር) ከባሕር የመጣ ቍጥር
ባሕረ ሎሚ የባሕር ሎሚ ብርቱ ካን፡ በኵረ ሎሚ
ባሕረ ሸሽ ባሕር የሸሸው የሸሸበት የራቀው የለቀቀው ትቶት የኼደ መሬት ዕርሻ
ባሕረ እሳት የእሳት ባሕር፡ ፍል ውሃ
ባሕረ ወጥ (ወፃኤ ውፁአ ባሕር) ከባሕር የወጣ (የመጣ) ሰይፍ ጐራዴ
ባሕረ ጃን (ጃነ ባሕር) ወርቅና ብር መሳይ በለጭ፡ የማዕድን ወረቀት ቀሠብ፡ ቀይ ነጭ አረንጓዴ፡ ሥሥ ረቂቅ ታኒካ በርሱ የተሸለመና የተጌጠ፡ የበቅሎ ዕቃ ዳግመኛም ባሕረ ጃን ባሕር ነጋሽ የባሕር ንጉሥ ከማለት ጋራ ይሰማማል በፈረንጅ ዦን ብጫ፡ ባማርኛ ጃኖ ቀይ ማለት ነውና፡ በብና በቀይ የተጠለፈ አረንጓዴና ሰማያዊ ከፈይም ያመለክታል
ባሕረ ጃን ባሕረ ንጉሥ፡ የንጉሥ ባሕር
ባሕረ ጃን የባሕር ጃኖ ይኸውም በቀዩ መደበኛነት ነው
ባሕረኛ (ኞች) የባሕር መንገድ ዐዋቂ (ሕዝ ፳፯ ፳፱) ቋትልን እይ
ባሕሪ ባሕራዊ የባሕር
ባሕሬ (ባሕርይ) ዝኒ ከማሁ፡ ጠባይ ዐመል የፍጥረት ኹሉ ሥር መሠረት፡ መሬት ውሃ ነፋስ እሳት ዐመል በአረብኛ ሥራ ሲኾን፡ ባማርኛ እንደ ጠባይ ይታሰባል
ባሕር
ባሕር (ብሒር ብሕረ) የውሃ ቦታ መቆሚያ መከማቻ ሰፊ ጥልቅ ውሃው የማያልቅ የማይደርቅ፡ ስፋቱ ከየብስ የሚበልጥ እጅ የሚልቅ፡ የረጋ የተኛ የተንጣለለ ውቅያኖስ ለሐይቅ ለኩሬ ለፈሳሽም ኹሉ ይነገራል ሲበዛ ባሕሮች ያሠኛል (ዘፍ )
ባሕር መዝገብ ያመት ዘገብአና ዘወፅአ የሚጻፍበት ትልቅና ሰፊ መዝገብ በባሕር ውስጥ ብዙ ተንቀሳቃሽ ትልቅና ትንሽ፡ ቀን ከርሱ ሌት ከየብስ የሚውልና የሚያድር እንስሳ እንደሚኖር፡ በመዝገብም ገቢና ወጪነት ያለው አሞሌ ሎሴ ጠገራ ብር አላድ ሩብ ተሙን መሐለቅ ቤሳ ተጽፎ ይገኝበታልና፡ ባሕር የሚል የስም ቅጽል ተሰጠው
ባሕር ሰገድ የሰው ስም፡ ባሕር የሰገደለት ማለት ነው
ባሕር ታናሽ የምድር ማእዘን፡ በሰሜንና በምዕራብ መኻል ያለ የሰሜን ምዕ ራብ የሊባ አፋዛዥ ትይዩና አንጻር
ባሕር ነጋሽ (ነጋሤ ባሕር) በባሕር ዳር የነገሠ የተቀመጠ፡ እንደ ምጥዋ ያለውን ወደብ ጠባቂ የሐማሴን ገዥ፡ ወይም የባሕር ንጉሥ አርማሕ ባሕር ነጋሽን የመሰሉ ባሕረ አስግድ ባሕረ ኤክላ የተባሉ ሌሎች ነገሥታትም አሉ
ባሕር ዐረብ (ዐረበ ባሕር) የባሕር ዐረብ፡ ቀይ ንት ተንቤን አንቀልባ ዐረብ ማለት ቅላቱን እንጂ፡ ከዐረብ አገር መምጣቱን ብቻ አያሳይም
ባሕር ኮሶ፡ የኮሶ ብጥብጥ (እንቆቅልኸ) ትንሽ ባሕር ዐጤን ታስፈር
ባሕር ወላድ (ዘፍ ፳፩) የብዙ ልጅ እናት፡ ባመት ጥጃ፡ ሱሪ ቢጥሉ ባት የምትወልድ
ባሕር ዛፍ (የባሕር ዛፍ) ፍሬው ከባሕር የመጣ ዕንጨት

ባሕር ያገር የምድር ዳር ከባሕር እባሕር እንዲሉ

ባሕርን በዋና ቈረጠ) ተሻገረ

ባሕርይ (ህላዌ መለኮት) ያልተፈጠረ የማይመረመር የማይታወቅ ኅቡእ ረቂቅ፡ ቅድስት ሥላሴን አንድ የሚያደርግ በሥርው በጕንድ በነቅዕ የተመሰለ የፈጣሪ ባሕርይ፡ አምላክነት

ባሕርይ የባሕር ዕንቍ (ግእዝ)

ባሕታዊ ንጉሤ በ፲፰፻ በሃይማኖት ምክንያት ከደብረ ሊባኖስ ተይዘው ጅማ ኣባ ጅፋር ዘንድ ታስረው ሞቱ እውነተኛ ኦርቶዶክስ፡ ትውልዳቸው ላስታ

ባሕታዊ (ባሕተወ) ባተሌ ባታይ ብቸኛ፡ ከሰው ተለይቶ በበኣት (ዋሻ) ተከቶ ተዘግቶ ለብቻው በዱር በገደል በተራራ የሚኖር ነቢይ መናኝ መነኵሴ ናዝራዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ የግዜር ሰው

ባሕታዊነት (ብሕታዌ) ብቻ ኾን፡ ብቻ ብቸቻ ብቻነት

ባሕታዊዎች (ባሕታውያን) ብቸኞች መናኞች ጻድቃን ቅዱሳን

ባለ (በአለ) በተናገረ፡ በፈቀደ

ባለ (ብሂል ብህለ) አለ ነገረ ተናገረ ቃል አሰማ ምን ባለ እንዲል ጕራጌ፡ ምን አለ ሲል

ባለ መታ በበትር ጠዘለ ደበደበ (ግጥም) ካንተ ተኝታ ሌላ ካማራት፡ በል ተነሣና በዱላ በላት ብህለ ባማርኛ ባለ መባሉ በን ራብዕ አድርጎ ስለ ተጐረደ መኾኑን አስተውል ዳግመኛም በባለ ፈንታ በለ ይላል

ባለ ሲናበበው (ባለጋራ) ጠላት ደመኛ ከሳሽ አሳጭ በሐሰት በተንኰል የሰውን ጥቅም የሚወስድ

ባለሃይማኖት ሃይማኖተኛ ሃይማኖት አክባሪ

ባለሕግ (ጎች) (በዓለ ሕግ) ባለተክሊል፡ በሕግ በሥርዐት በቍርባን የሚኖር እውነተኛ ክርስቲያን ባላንዲት ሚስት

ባለላም

ባለላም (ባዕለ ላሕም) ላም ያለችው፡ ላም ዐላቢ፡ ኣቢላም፡ የላም እረኛ

ባለል (ሎች) ውድ ወዳጅ፡ ታማኝ፡ ከንጉሥና ከመኳንንት ጋራ የሚውል (ዘፍ ፴፱ ) (ተረት) የባለጌ ባለል ቂጥ ገልቦ ያያል

ባለል ተክሌ የባለሎች አለቃ፡ በዐድዋ ጦርነት የሞቱ

ባለልነት ወዳጅነት ታማኝነት

ባለመለዮ ሰራዊት ጭፍራ

ባለመርከብ መርከበኛ፡ የመርከብ አዛዥ

ባለመሸታ መሸታ ጠጭ/ወስላታ።

ባለመብት ባለፈቃድ፡ ሥልጣን ሹመት ያለው አዛዥ

ባለመደረቢያ ኹለት ጣራ ያለው ድንኳን

ባለመዳኒት (በዓለ መድኀኒት) ሐኪም፡ መዳኒተኛ፡ መዳኒት ዐዋቂ ቀማሚ ሸያጭ (ማቴ ፲፪) ዐቀበ ብለኸ ዐቃቢን እይ

ባለማኅተም ማኅተም ያለው ሰው፡ የማኅተም ባለቤት

ባለማደሪያ በመትከያ መንቀያ የመንግሥት መሬት የሚኖር ወታደር

ባለምልክት በለጭማ ከብት፡ ድጓ

ባለምንዣኸ የምንዣኸ ማውረጃ ቀጪን ጕሮሮ።

ባለምድር የርስት የመሬት ጌታ

ባለሞረድ መውዜር ጠመንዣ ሞረድ ያለው

ባለሰሞን ሰሞነኛ፡ ከሰኞ እስከ እሑድ የሚቀድስ ቄስ ዲያቆን

ባለሰገጥ ጥልፉ ሰገጥ የሚመስል

ባለሳምንት በሚመጣው ወር ማኅበር የሚደግስ፡ ጥዋ ወሳጅ

ባለሥልጣን ቄስ ሹም ሥልጣን ያለው

ባለስም ስሙ የተጠራ፡ ዝናው የተሰማ፡ ወይም መንግሥት የሹመት ስም የሰጠው

ባለሦስት በ፫ኛ ወር ማኅበር የሚ ደግስ

ባለርስት ርስት ያለው፡ የርስት ጌታ፡ ርስተኛ

ባለቀ (በሊቅ በለቀ) ዐጕልና ገቢር ለዘር በቃ፡ አደገ ጐለመሰ በሕልም ወይም በውን ዘር ኣፈሰሰ፡ ሴት ዳሰሰ (ተረት) የታጠበ እጅ ያልባለቀ ልጅ ገና ተወራራሾች ስለ ኾኑ ባለገና ባለቀ በምስጢር ይገጥማሉ።

ባለቀላድ የገመድ የመሬት ጌታ

ባለቀሚስ (ሶች) ቀሚሳም፡ ቀሚስ የተሸለመ የለበሰ፡ ካህን ወታደር

ባለቀትር ባለጊዜ፡ ደሙ የፈላ

ባለቅኔ ቅኔ ዐዋቂ፡ ቅኔ የሚቀኝ

ባለበግ (በዓለ በግዕ) የበግ ጌታ፡ በግ ያለው፡ በጋም የበግ እረኛ

ባለባል ገለሞታ ያይዶለች ባል ያላት ሴት

ባለቤቱ የቤቱ ጌታ፡ ርሱ፡ ወይም ሚስቱ

ባለቤቲቱ ዝኒ ከማሁ፡ እሷ

ባለቤት (ቶች) (ባዕለ ቤት) ቤት ንብረት ያለው፡ የቤት ጌታ (ተረት) አለባለቤቱ አይነድም እሳቱ ባለቤት፡ ባል

ባለቤት ሚስት ባልተቤት ሴትን ከወንድ ለመለየት፡ ባለቤቷ ባለቤቲቱ ይላል (፩ነገ ፲፯ ፲፯)

ባለቤት አከል ባለቤትን የሚያኸል፡ እንደ ባለቤት የሚያዝ፡ ቤት አዛዥ የቤት ዋና፡ አሳዳሪ መጋቢ ኣስተንታኝ ቤት አባት

ባለቤት ከ፫ቱ ኅብስተ ቍርባን ፪ኛው መካከለኛው የክርስቶስ አካል ምሳሌ፡ ቄስ ሲባርከው ሥጋ አምላክ የሚኾን፡ የቤተክሲያን ራስ አለቃ

ባለቤት የነገር ዋና፡ የዘርፍ የቅጽል ጌታ፡ አንቀጽ ተቀባይ ክርስቶስ ተወለደ ሞተ፡ ተነሣ፡ ዐረገ ዳግመኛም ይመጣል

ባለቤትኸ አንተ፡ ሚስትኽ

ባለቤትዎ ርስዎ፡ ሚስትዎ

ባለቤቷ ያች ርሷ፡ ወይም ባሏ

ባለተ ታሠሠ ተወለወለ (ጐዣም)

ባለተስፋ አገኛለኹ ባይ፡ ባላለኝታ

ባለተራ ተከታይ፡ ባለረድፍ፡ ሥራው ጊዜው የርሱ የኾነ

ባለነገር (በዓለ ነገር) በርስቱ በገንዘቡ የሚማገት የሚከራከር ነገረተኛ፡ ወይም ነገረኛ ነገር ወዳድ፡ ነገራም

ባለነጋሪት ነጋሪት ያለው ራስ ደጃ ዝማች

ባለነጭ (ጮች) የነጭ ልብስ የነጭ ጤፍ እንጀራ የሥብ ሥጋ ባለቤት (አረጋ መን ገጽ )

ባለንብረት ትዳር ያለው ያላት

ባለአእምሮ ዕውቀት ያለው፡ የውቀት ጌታ፡ ከእንስሳ የተለየ ሰው

ባለዕውቀት ዕውቀት ያለው፡ ባለማወቅ ፪ኛውን ኣለ እይ

ባለእግዚሐር ባለወልድ

ባለከል ልብሱ በከል የተነከረ፡ ከል ለባሽ ዐዘነተኛ

ባለኩል (ሎች) የባሏን ትዳር እኩሌታ የምትካፈል ሚስት

ባለኩልነት በትዳር እኩያነት ትክክልነት፡ የሚስት ከባል

ባለኹለት በኹለተኛ ወር የሚደግስ ማኅበረተኛ

ባለወልድ (በዓለ ወልድ) ወር በግባ በ፳፱ ቀን የሚከብር፡ ጌታችን በድንግል ማርያም ማሕፀን ተፀንሶ መወለዱንና ሙቶ መነሣቱን የሚያሳስብ በዓል።

ባለወስፌ ወስፊያም፡ ወስፌ ያለው ሰው ዣርት

ባለወንበር (በዓለ መንበር) ሊቅ መምር በወንበር ተቀምጦ የሚያስተምር

ባለወገን ዘመዳም፡ ባለብዙ ዘመድ፡ ወገን ያለው፡ የወገን ጌታ እረኛ ወገንን ተመልከት

ባለወግ (በዓለ ወግዕ) ወገኛ ወግ ዐዋቂ፡ ባለአበል ወግን እይ

ባለወግ ሰቃይ ቈራጭ ገዳይ

ባለው ስምና አንቀጽ መጨረሻ እየተጨመረ የሚነገር ፊደል ("ይኸውም ነው በመ ተራ ምን ተመልከት")

ባለውሃ (በዓለ ማይ) ውሃም፡ ውሃ ያለው፡ ውሃ ተሸካሚ፡ የውሃ ጌታ ባለውሃ፡ እንዳይግል በጐኑ ውሃ የሚቀመጥበት መትረየስ

ባለውለን፡ ደንቈሮ/ዝግ ("የማይሰማ የማይለማ")

ባለውል ውለኛ፡ ውል አክባሪ፡ ቁም ነገረኛም

ባለውቃቢ ዛራም ቆሊያም

ባለዘርፍ (በዓለ ዘፈር) ዘርፋም፡ ዘርፍ ያለው ልብስ ምንጣፍ

ባለዘውድ ዘውድ ያለው፡ ንጉሥ ጳጳስ በራሱ ላይ ዘውድ የደፋ የተቀዳጀ

ባለዚህ የዚህ ጌታ፡ የዚህ ባለቤት የጥያቄ ቃል ነው

ባለዛፍ ዛፋም፡ ዛፍ ያለበት ዱር፡ የዛፍ ሥዕል ያለው ልብስ

ባለዝና (በዓለ ዜና) ስመ ጥር

ባለያ (በዓለ ሙዓል) ብልኅ ዐዋቂ፡ ባለብዙ ዕውቀት፡ በውቀቱ ሲሠራ የሚውል ፈረንጆች ፕሮዱክተር ይሉታል ባለሙሉ ሥልጣን፡ ቢትወደድ እንደራሴ

ባለይሉኝታ የይሉኝ አይል ተቃራኒ፡ ትዝብትን ነቀፋን የሚፈራ

ባለደም ነፍሰ ገዳይ፡ ተበቃይ

ባለዳ (ባዕለ ዕዳ) አበዳሪ፡ ወይም ተበዳሪ፡ ዕዳ አስከፋይ ከፋይ (ተረት) ከክፉ ባለዳ ጐመን ዘር ተቀበል ወንድና ሴትን ለመለየት፡

ባለዳነት ባለዳ መኾን

ባለዳዋ ያች ባለዳ፡ የርሷ ባለዳ

ባለዳው ባለዳ፡ የርሱ ባለዳ

ባለድባብ ድባብ ያለው ድባብ ያዥ

ባለጅ (ጆች) (በዓለ እድ) ሠራተኛ ቀጥቃጭ ጠይብ አንጥረኛ እጃም እጀኛ፡ እጀታ ያለው ዕቃ መሣሪያ

ባለገ (ዕብ ባላግ) በረታ ቻለ

ባለገ ባለቀ፡ ከሕግ ወጣ፡ ሥርዐት አልባ ኖረ፡ ሥልጣኔ ዐጣ፡ ባላገር ኾነ

ባለገዳም የገዳም ጌታ የገዳም ሹም፡ የገዳም አባት (ኣበ ምኔት) መምር ኣበ ማኅበር

ባለገድል (በዓለ ገድል) ገድላም ገድለኛ፡ ገድል ያለው ጻድቅ ሰማዕት

ባለጊዜ (በዓለ ጊዜ) ዘመናይ ሹም፡ ንጉሥ እንደ ወደደ የሚያደርግ (ግጥም) ያረገውን አርጎ አበጀኹ ቢላችኹ፡ ይህን ባለጊዜ ምን ትሉታላችኹ አለ በመነሻ ኹኖት ከባል ጋራ መተባበሩን አስተውል

ባለጋራ በዛበት ብዙ ሰው ጠላው ከሰሰው

ባለጋራ ደመኛ ጠላት ምቀኛ ከሳሽ አሳጭ ï በሐሰት በተንኰል የሌላውን ጥቅም፡

ባለጋራ()ነት ደመኛነት ጠላትነት፡ ባለጋራ መኾን

ባለጋሮች ደመኞች ጠላቶች (ኢሳ ፶፱ ፲፰)

ባለጌ (በዓለ በዓለ ምድር) ባለምድር፡ የምድር ጌታ

ባለጌ ባለ ምድር ባለገ

ባለጌ አግድሞ አደግ ስድ መረን ያልተቀጣ ያልተገሠጸ ነውረኛ ነውር ጌጡ፡ አያት ያሳደገው ልጅ ባለጌን ካሳደገው የገደለው ይጸድቃል። ባለጌ የጠገበ ለት ይርበው አይመስለውም

ባለጌ ኾነ ባለገ በባላገር ኖረ

ባለግርማ መፈረት መፈራት አስፈሪነት ያለው፡ ተፈሪ አስፈሪ ግርማም

ባለጠጋ (በዓለ ጸጋ) ሀብታም ከበርቴ እዱኛው የበዛ፡ የከበረ የበለጠገ የዘመነ የጌተየ፡ ብዙ ሀብት ያለው ዕድለኛ ባልን እይ

ባለጠጋ ሀብታም በለጠገ

ባለጠግነት ጌትነት ሀብታምነት፡ ማግኘት (፩ዜና ፳፱ ፲፪ ምሳ ፲፱ ፩ጢሞ ፲፯)

ባለጠጎች ሀብታሞች ጌቶች

ባለጤና (በዓለ ጥዒና) ጤናማ፡ ደኅነኛ፡ ቃር አያውቅሽ

ባለጥላ (በዓለ ጽላል) ጥላ ያለው፡ ጥላ ያዥ ትከሻም፡ የከበደ የከበረ ሰው

ባለጥንግ የጥንግ ጌታ፡ የጥንግ ዐይነት ድርብ ባለጥንግ ድርብ እንዲሉ

ባለጨረቃ በላዩ ጨረቃ የተሣለበት ሰይፍ፡ ወይም ዕቃ

ባለፈርጥ ፈርጣም፡ ፈርጥ ያለው ልብስ፡ በፈርጥ ያጌጠ ሰው

ባለፈቃድ ውሰድ የተባለ፡ ፈቃድ የተቀበለ

ባለፋንታ ፋንታ የደረሰው፡ ባለተራ ባለወረፋ

ባሊኆ (በሊኅ) የበላ የሰላ የሾለ፡ ስል ትብ ሐኔ ማረጃ ቢላዋን እይ

ባላ (ሎች) (ባልሐ ባልሕ) በቁሙ፡ ቤትን ከመውደቅ የሚያድን የሚደግፍ ራሰ መንታ ዕንጨት

ባላ ባልቾ የባሎች ባላ፡ እንደ ዋላና እንደ ርኤም ቀንድ፡ በባላ ላይ ባላ ያለው ዛፍ፡ ወይም ሜንጦ ዋላ የተባለ ሀየል ነው

ባላ የሰው ጭንና ጭን፡ ወይም ኹለት እግር

ባላህያ (በዓለ አድግ) (ባለአህያ) አህያ ያለው፡ ያህያ ጌታ፡ ጠባቂ

ባላልቦ ዐልቧም፡ ዐልቦ ያላት ሴት፡ ወይም ባል የሌላት አልቦን እይ

ባላልጋ ዐልጋ ዙፋን ያለው፡ ያልጋ ጌታ፡ ባላባት ንጉሥ

ባላምባራስ (በዓለ ርእሰ ዐምባ) ያምባ ራስ ጌታ፡ ዐምባ ራስን የሚያዝ፡ ከመንግሥት ባምባ ራስ ላይ የተሾመ ዐምባ ራስን እይ ዛሬ ግን ባላምባራስ የሚባል ወይም ሻምበል አዛዥ ነው

ባላረግ (በዓለ ሐረግ) ያረግ ጌታ ባለቤት፡ የሐረግ ንድፍ ወይም ሥዕል ያለበት መጽሐፍ

ባላረግ ዘመዳም ወገናም ሰው

ባላራት ሰራተኛ ወር ማኅበር ደጋሽ

ባላባት (ቶች) ትልቅ አባት ያለው፡ አባተ ትልቅ አባታም

ባላት (በዓላት) ቅዱስ ዮሐንስን መስቀልን ገናን ጥምቀትን ስቅለትን ፋሲካን ዕርገትን ጰራቅሊጦስን ፍልሰታን የመሰሉ የዕረፍት ቀኖች

ባላና ደንቈሮ ባላ ያለውና የሌለው የድር ማድሪያ ኹለት ዕንጨት

ባላና ደንቈሮ የድር ጫፍና ጫፍ፡ ባላ መቋጠሪያው፡ ደንቈሮ መቍረጫው አንዳንድ ሰዎች የብልኀት ሥራ ስላለበት፡ ድር ስለሚሠባጠርበት፡ ባላን በደንቈሮ አንጻር ብልኅ ይሉታል

ባላን() (ጦች) አምጣ ባይ፡ ርስት ተካፋይ ተወላጅ ዘመድ

ባላገር (ሮች) (በዓለ ሀገር) ባለጌ ባገር ቤት የሚኖር ሰው (ዘሌ ፲፯ ፲፭) ባላገር፡ አገሬ ያገር ተወላጅ

ባላገር አገር ቤት እባላገር ከርሜ መጣኹ

ባላጊ ባለጌ (ዎች) የባለገ የሚ

ባላጐዛ ባጐዛ የሚቀመጥ መምር፡ ዐጐዛ የሚለብስ ሐርበኛ ባለሎፊሳ

ባላጥንት (ባለዐጥንት) የጨዋ ልጅ ዐጥንትን እይ

ባሌ (በዓልየ ምትየ) በቁሙ ፬፡ የኔ ባል፡ የኔ ባለቤት፡ ባለቤቴ

ባሌ ካሩሲ ቀጥሎ ያለ አገር፡ በግእዝ መጻሕፍት ባሊ ይባላል

ባሌን አሞኘኹት የቤት (የእጅ) ፈትል መሳይ ማለፊያ ቀጪን የፈረንጅ ድር (ግጥም) እጓዳ ፈትዬ እጓዳ አደራኹት፡ አትንገር ሸማኔ ባሌን አሞኘኹት

ባል ("ኹለት ነጥብ አራት ነጥብ ዘጠኝ ነጥብ" እንዲሉ - "ነቍጥን ይዘትንና ሠረዝን" ተመልከት)

ባል (በዓል) በቁሙ፡ የደስታና የእረፍት ቀን፡ በዓመት በወር በሳምንት የሚከብር (የባለጌ ግጥም) አንጫወትም ወይ ሰኞ ተገናኝተን፡ ባልማ ሲመጣ ወዴት ተመችቶን ሰነፍ ባል ያበዛል እንዲሉ (የማሪያም ባል) ወር በባተ በ፳፩ኛ ቀን የሚከብር ባል እየተናበበ ሲነገር እንደ ሚስማማው የዐጸፋና የቅጽል አፈታት ይፈታል

ባል (ብዕለ ባዕል በዓል መትሀ ምት) ሚስት ያለው ወንድ ተባት፡ የሴት ገዥ አዛዥ ጌታ ባለቤት (ሮሜ ) ባልና ሚስት እንዲሉ አባን እይ፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው (ተረት) አገባሻለኹ ያለሽ ላያገባሽ ከባልሽ ሆድ አትባባሽ የአህያ ባል ከዥብ አያስጥል

ባል ባልና ሚስት፡ የልብስ ቍልፍ

ባልተቤት (በዓልተ ቤት) ሴት እመቤት፡ ሚስት በልማድ ግን ባለቤት ትባላለች

ባልታ (ብሂሎት) ማለት ኹለተኛውን አለ እይ

ባልታ ማለት፡ ባለ

ባልቴ ባል ብቻዋን የምትኖር (፬ነገ ፲፯ ግብ ሐዋ )

ባልቴት፡ (ቶች) ባል፡ ተየት) ያረጠች፡ ሴት፡ ደራቁቻ፡ አሮጊት፡ የበቃት፡ አለ

ባልቴት ያረጠች፡ በለተ

ባልትና ቢስ የሌላት ሴት

ባልትና ዕውቀት ያ፡ የባልቴት ዘዴ

ባልትና በለተ

ባልቻ (ኦሮ) ምትክ ማለት ነው

ባልና ሚስት በቁሙ፡ ወንድና ሴት ባልና ሚስት ሎሚ ከኹለት እንዲሉ

ባልንጀራ (በዓለ እንጀራ) የንጀራ ባለቤት የንጀራ ጌታ

ባልንጀራ እኩያ ባልደረባ፡ አቻ ዐብሮ አደግ ጓደኛ፡ እንጀራ አቋራሽ (ዘፍ ፲፩ ኢሳ ፵፬ ፲፩)

ባልንጀር ዝኒ ከማሁ፡ የጥሪ ቃል

ባልንጀርነት እኩያነት ባልደረብነት (፪ቆሮ ፲፭)

ባልንጀሮች ባልደረቦች ጓደኞች (ሮሜ ፲፯)

ባልኛ ባለባላ

ባልያ እንደ ምሽግ ያለ ዐምባ ተራራ

ባልደረባ ጓድ ያለው ባለጓድ የድሜ የሥራ ጓደኛ ዐብሮ የሚኖር የሚሠራ፡ ባልንጀራ እኩያ አምሳያ ሚስት አለቃም ለጭፍራው ባልደረባ ይባላል ደረበን ተመልከት

ባልደረብነት እኩያነት ጓደኝነት ባልንጀርነት

ባልደረቦች ጓደኞች አኩዮች

ባልደራስ (ሶች) የደራስ ጌታ የደራስ ባለቤት፡ የፈረስ ሹምና ገሪ (፩ነገ ፳፪) ደራስን እይ

ባልደራስነት የፈረስ ሹመት፡ ገሪነት ጠባቂነት

ባልዲ

ባልዲ (ማሕየብ) መጥለቂያ የውሃ መቅጃ መሳቢያ መጐተቻ፡ ሰዎች ማንጠልጠያው ገመድ አስረው ከጕድጓድ ውሃ የሚያወጡበት ባልዲ ሥራውም ስሙም የፈረንጅ ነው ደለይን ተመልከት

ባልግ ባላገር ከርሻና ከቍፋሮ በቀር ሌላ የማያውቅ አገረ ሰብ፡ ሥልጣኔና ዕውቀት የሌለው ባለጌ ይባላል

ባልጩት (ቶች) (ብልጩት ብልጭት ብልቲት እዝኅ) የቦረቦጭ ሱፋጭ ሻፎ፡ ሥጋ የሚቈርጥ የሚበልት ስለታም ደንጊያ (ዘዳ ፲፭ ኢሳ )

ባልጪ (ኦሮ) ቦጨቦጭ ቦረቦቼ

ባሎች (አምታት) ባለሚስቶች፡ ሚስቶች ያሏቸው ወንዶች

ባምባዛፍ ባባ

ባሰ (ብኢስ ብእሰ) ጠና ከፋ በረታ አገረሸ፡ መጥፎ ኾነ (ተረት) እግር ይብሳል፡ ያበሰብሳል

ባሰ በለጠ ከበረ አንተ ትብስ እን ዲሉ

ባሰ ተቀየመ ተበሳጨ ዐዘነ ተከዘ

ባሰ ቸገረ ገደደ ምን ባሰው እንዲሉ

ባሰኸና በሹሮ ፈንታ የጤፍ ዱቄት አሳርረው የሚሠሩት ዐልጫ ዶዮ ትርጓሜው፡ ይህን ብታገኝ (ባሰኸና) ከፋኸና መጥፎ ኾነብኸና ማለት ነው

ባሰኸና ዶዮ፡ ባሰ

ባስልዮስ የሰው ስም፡ ትርጓሜው በጽርእ ንጉሥ ማለት ነው ይላሉ

ባረቀ በድንገት ሳይታሰብ ፈነዳ፡ ተተኰሰ፡ መብረቅኛ ጮኸ፡ የሽጕጥ የነፍጥ ዘባረቀን ተመልከት

ባረከ (ባርኮ ባረከ) አመሰገነ ምስጋና አቀረበ መረቀ (ማቴ ፵፬)

ባረከ አማተበ ቀደሰ አበዛ

ባረከ ዠመረ ፈቀደ፡ ገመሰ ቈረሰ ዳቦን እንጀራን

ባረከ ገዘገዘ ከረከረ ዐረደ ፍሪዳን

ባሩድ ቤት ዐጤ ምኒልክ በየሻለቃው የሠሩት የቍጥር ጦር፡ ታማኝ ሰራዊት (የባሩድ ቤት ዘበኛ)

ባሩድ ቤት የጦር መሣሪያ በያይነቱ የሚቀመጥበት ቤት

ባሩድ ድኝና የእሓያ ከሰል ጨው ባሩድ የሚባል፡ ደንጊያ ባንድነት ተወቅጦ የተደራጀ፡ በጠመንዣና በሽጕጥ በመትረየስ በመድፍ ቀለሕ ውስጥ በከምሱርና በዐረር መካከል የሚደረግ ዕይር

ባሪያ (ነገርጋር) አዙሪት የደም ሥር በሽታ፡ በሰውና በበግ የሚጠና

ባሪያ ሰደድ ጥኑ ጠንካራ ገብስ፡ በወፍጮው ምክንያት ባሮች ስለ ጠፉና ስለ ኰበለሉ ባሪያ ሰደድ ተባለ ይላሉ

ባሪያ ሰደድ) የገብስ ስም (ሲፈጩት የሚጠና/የሚጠነክር ገብስ)

ባሪያ ቀይሕ በባሪያ ጸሊም አጠ ገብ ያለ አገርና ቀይ (ጠይም) ሕዝብ ገባር

ባሪያ ባርያ (ባርዮ ባረየ) ገብር፡ ከወገኑ ተለይቶ ከአገሩ ወጥቶ የተገዛ ግዝ፡ የተማረከ ምርኮ፡ እንደ በሬ በግድ የሚሠራ፡ በጌታው ዐሳብ ዐዳሪ፡ ነጻነት የሌለው፡ ባለመከራ ሻግያ ባርነት ሲጸናበት ኰብሎ የሚጠፋ፡ ውላጅ ፍናጅ ቅናጅ አሠለጥ አመ ለጥ፡ ማን ቤቴ ደረባ ቤቴ ዱር ቤቴ የሚባል፡ ሲበዛ ባሮች ይላል ተበዳሪ ያበዳሪ ባሪያ ነው (ምሳ ፳፪ ) ባሪያ ለወንድም ለሴትም ይነገራል ደበቀን እይ

ባሪያ ታማኝ አሽከር፡ ባለል፡ ወታደር ሲፎክር እኔ ባሪያኸ እንዲል

ባሪያ ድንጋይ ጥቍር ድንጋይ፡ አለት ጠንካራ፡ ግንብ ሲገነባ ከብሓ በታች እንጂ በላይ የማይኾን ከባድ

ባሪያ ጋብር (ትግ) ያቦ ባሪያ ጋብር፡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

ባሪያ ጣለው ጋኔን ደበለለው፡ አንከባለለው፡ ከመሬት መታው፡ ደበተው ጠንቋዮች ዐይነ ጥላ ሲጥፉ፡ ባርያ ወሌጌዎን ይላሉና፡ ባሪያ ጣለው ማለት በዚህ ምክንያት ነው እሱንም ባላገሮች ልክስክስ የጕድፍ ጋኔን ዛር ውላጅ (የጋኔን ተወራጅ) ይሉታል ባሪያ መባሉም ጥቍረቱን የምጣድ ቂጥ ምሰሉን መደብ አድርጎ ለአለቃው (ለሌጌዎኑ)

ባሪያ ጸሊም የነገድና ያገር ስም፡ ጥቍር ጠቋራ ሻንቅላ ከሰልማ ማለት ነው፡ የሚገኘውም በከረን ጠረፍ ነው

ባሪያ ፈንጋይ ባሪያን ጨርቅ አልብሶ ኳስ አጕርሦ የሚሼጥ የደከመውን ለማስፈራራት አጋድሞ ፈንግሎ የሚያርድ፡ ባሪያ ነጋዴ ወርጅ

ባሪያዋ ያች ባሪያ፡ የርሷ ባሪያ

ባሪያው ባሪያ፡ የርሱ ባሪያ

ባሪያዪቱ ዝኒ ከማሁ (ገላ ፳፫)

ባራቂ የሚባርቅ፡ ሳይተኩሱት የሚመባረቅ፡ መተኰስ መጮኸ መፈን ዳት

ባራኪ ዠማሪ ቈራሽ ቄስ ማእድ ባራኪ እንዲሉ

ባራኪ የባረከ የሚባርክ የሚመርቅ የሚቀድስ፡ መራቂ ቀዳሽ

ባሬታ (ቶች) ከመዳብ ከቅል ከሸክላ የተሠራ የሽንት መሸኛ መክፈያ ቶፋ፡ ወይም ሌላ

ባር ሆድ የሆድ ውስጥ

ባር ማሽላ የባሕር ማሽላ፡ በቈሎ፡ ማር ማሽላ

ባር ሜጣ ከባሕር የመጣ የፀሓይ ቆብ

ባር ቍልፍ ከባሕር የመጣ ቍልፍ

ባር ቅል (ሎች) የባሕር ቅል፡ ዱባ ዐይንን እይ

ባር ባሕር የተንጣለለ ውሃ፡ ውቅያ ኖስ ባር ዐማርኛ፡ ባሕር ግእዝ ነው

ባር ባር አለው (አባሕረሮ) ፍራት ፍራት አለው፡ አባነነው አበረገገው፡ ዘለኸ እባሕር ግባ አለው ሆዴን ባር ባር አለው እንዲል ባላገር

ባርሜጣ የፀሓይ ቆብ፡ ባር

ባርሰነት (ቶች) የባሕር ሽነት የአደስ ዕንጨት በግእዝ ምርስኔ ይባላል

ባርኮ ሥሉስ ቅዱስ ሥላሴ ባርከው ቀድሰው፡ አብዛው ዐይጥን ከማገር ሰላ ቢን ካገር አጥፋ ለምርትና ለቡሖ ይነገራል

ባሮክ የሰው ስም፡ በምስጢር ከቡሩክ ጋራ አንድ ነው

ባሻ (በዘአፍተወ) ባስፈለገ ገንዘብ

ባሻ (ፓሻ) የቱርክ ጦር አዛዥ ዋና ዳኛ አለቃ፡ እንደ ራስ ያለ ቱርክ ባሻ ታምሬ እንዲሉ ባገራችን ግን ወታደር ለበላዩ የሚሰጠው የከበሬታ ስም ነው ባላም ባራስነትን ከመንግሥት ወይም ከሻለቃ እስቲያገኝ በዚህ ስም ይጠራል ሻየ ብለኽ ባሻን እይ፡ ቱርክን ተመልከት

ባሻ ሆዱ፡ ያዘነ የተከዘ ነገር የማይችል በጥቂት ምክንያት የሚቀየም፡ ቍጡ ብስጩ ኵርፍተኛ አልቃሽ እከሌ ሆደ ባሻ ነው እንዲሉ

ባሽ (በኣሲ) የባሰ የከፋ፡ ክፉ መጥፎ

ባሽ ባዙቅ በፊት የቱርክ የነበረ ኋላም ለጣሊያን ያደረ ወታደር፡ የፓሻ ባዙቅ ማለት ነው ባዙቅን እይ

ባቄላ (ሎች) የታወቀ የአበባ እኸል፡ በ፪ ቀን የሚያጐመጕም በ፫ ቀን የሚያጐነቍል፡ አደፍ ድበላ ባቄላ የራብ ዱላ እንዲሉ

ባቄሎ ባቄላም አገር

ባበለ ተደባለቀ ተቀየጠ ተቀላቀለ (ግእዝ)

ባበለ ኾነ ተደረገ ልመናው ቍልምው

ባቡ የሰው ስም፡ ጠላቶች ፈሩ ገነገኑ ማለት ነው

ባቡሬ ከዠርባው ወይም ከሆዱ ነጭ የኾነ ዓሣ

ባቡር (ሮች) በውሃ ጪስ የሚኼድ መኪና ፈረንጆች ባፐር ይሉታል።

ባቡቴ ክብ እንክብል ኅብስት ሴቶች በዔሊ አምሳል የሚጋግሩት አርባ ባቡቴ እንዲሉ ኣበቡቴን ተመልከት

ባቡት ራሷንና እግሯን ከደንጊያ ውስጥ የምትበብት የምታግባ የምትከት ድንጋይ ልብሷ ዔሊ፡ ፊቷ እባብ የሚመስል፡ እባብማ እባቡት

ባቢ የሚባባ፡ ሠጊ ገንጋኝ

ባቢሌ ያገር ስም፡ በሐረርጌ አውራጃ ያለ አገር

ባቢሎን የከተማ ስም፡ ድብልቅልቅ ዝብርቅርቅ ቅይጥ ውጥንቅጥ ማለት ነው መዠመሪያውን ባበለ ተመልከት

ባባ (ስም) ፍሬው የሚበላ የወርካና የሾላ ዐይነት ዛፍ፡ ባሕታውያን ፈልፍ ለው በውስጡ የሚቆሙበት፡ ቅርንጫፉ እንደ ዘንባባ የሚዘረጋ ፊተኛውና ኋለኛው ባባና ባባ የሚለዩት በመጥበቅና በመላላት ነው

ባባ (በሕብሐ) ፈራ፡ ሠጋ ባነነ በረገገ ገነገነ (ግጥም) እንቢ አለኝ እንጂ ሆዴ እየባባ፡ ውልድሽ ኣንኮበር ኑሮሽ ሐር ዐምባ

ባባ አለ (ቤበየ) ጮኸ፡ ጐተጐተ እንስትን በግሩ ወጠጤው ባባ ይላል

ባቤሎ ነጭ አደንጓሬ፡ ዐረቦች ፈሱሊያ የሚሉት ደንጐሎን እይ

ባብ (ዐረ) በር መግቢያ

ባብ እልመንደብ በኦቦክና በዓደን መካከል ያለ የጭንቅ የመከራ በር መነደበን እይ

ባቦ ዕሺ በጎ በጄ ደግ

ባተ (ብሒት ብሕተ) ገባ ሾመ ሠለጠነ፡ ተዠመረ ተቈጠረ፡ የወር ያመት

ባተ መልካም ባቱ ያማረ ሞንዳላ ባትኸን አሳየኝ፡ ቶሎ ቶሎ ኺድ

ባተለ (ዕብ ብቱላ ልጃገረድ) ሚስት ኣልባ ኾነ፡ ብቻውን ሠራ ለፋ ደከመ

ባተሌ (ዎች) ሚስት የሌለችው ወንድ፡ ባል የሌላት ሴት

ባተሌ ኾነ ባተለ ባታይ ኾነ

ባተሌ የባታይ ወገን ብቸኛ

ባተሌነት ብቻነት ብቻ መልፋት ራት

ባተሎ ዘባተሎ (ብጡል ዘበጠለ) ዕላቂ ውዳቂ የባተሌ ልብስ

ባቲ (ኦር) የጨረቃ ስም፡ ለጋ ጨረቃ በየወሩ የምትብት ማለት ነው

ባቲ በዐውሳ ውስጥ ያለ አገር

ባቲ አመልካች ወፍ፡ ቡሊ ቀርቃሬ

ባታ (በአታ ለማርያም) ታቦት፡ የታቦት የጽላት ስም፡ ወር በገባ በ፫ የሚከብር በዓል

ባታ (በዊእ ቦአ በአት) እመቤታችን ቤተ መቅደስ የገባችበት የታኅሣሥ ሦስተኛ ቀን ታኅሣሥ ባታ እንዲሉ

ባታላጋኝ) ባታቈራቍሰኝ

ባታም (በዓታዊ) ባተ ወፍራም፡ ባተ ደንዳና ሰው

ባታይ የባተለ የሚባትል፡ ባሕታዊ ብቻውን የሚኖር፡ ፈት

ባት (ቶች) (በዓት ባሕት) በቋ ንዣና በቅልጥም መካከል በስተኋላ ያለ አካል በአግር ላይ የባተ (ኢሳ )

ባነነ (ባህነነ ባሕረረ) ደነገጠ ጮኸ በንቅልፍ ልብ

ባኒያን (ኖች) በህንድ አገር ከነበሩት ነጋዴዎች ወገን የኾነ ያንድ ሰው ስም በግእዝ ባንያ ይባላል፡ ማኒን እይ

ባኒያን በወደቀበት የሚጸድቅና በቶሎ ደን የሚኾን የበለስ ዐይነት ዛፍ

ባና በቅላትና በንጣት መካከል ያለ የበግ ጠጕር ባና ፓና ከማለት ጋራ ይሰማማል በትግሪኛም ባና ውጋገን ማለት ነው ፋናን እይ

ባና ነጭ ወይም ዥጕርጕር ዝተትየመንዞች ሥራ፡ ጥቍሩ በርኖስ እንጂ ባና አይባልም

ባናኝ (ኞች) የባነነ የሚባንን፡ ድንጉጥ ጯኺ ብቡ

ባንቼ ከፊለ፡ ስም

ባንች (በአንች) ባንቺ

ባንች፡ ይለኩ የሴት፡ ስም፡ ሌሎቹ፡ ሴቶች፡ ባንቺ ይመጠኑ፡ ማለት፡ ነው

ባንክ (ኮች) (ማእድ) የግንዘብ መቊጠሪያና መደርደሪያ ሞላላ ገበታ (ጠረጴዛ)

ባንክ በወለድ የሚያበድርና ሐዋላ የሚያደርግ የገንዘብ ትርፍ ሥራ የሚሠራ የንግድ ቤት

ባንክ ኖት ኖት ምልክት ማስታወሻ ማለት ነው በሕግ ተፈቅዶ ለመገበ ያያ ባንክ የሚያወጣው የገንዘብ ወረቀት፡ ይኸውም በእንግሊዝ ቋንቋ መጠሪያ ስሙ ነው

ባንዱራ ማላጋ የባሕር ጐመን፡ አንደ ትማትም ያቡን ወጥ የሚባል።

ባንዲራ በቁሙ፡ ዐላማ፡ የመንግሥት ምልክት ባንዲራ የጣሊያን ቋንቋ ነው፡ ከዐድዋ ጦርነት ወዲህ ተለምዷል ፊርማን ተመልከት

ባንድነት ቈረበ) በቅዱስ ቍርባን ተማመነ

ባንጃ በወገን አንጃ

ባንጓ ገጋ የማር ቀለሕ

ባዕድ ቀለም እን () ሽ፡ እነዚህም ለቃል መነሻ እየኾኑ ይነገራሉ።

ባዕድ ባዳ ባድ፡ ባዕድ የግእዝ ነው

ባከነ ባዘነ ዛበረ ተገላመጠ ቃበዘ፡ ተዘራ ተበተነ ጐደለ፡ ያሳብ የገንዘብ ያይን የምስጢር

ባከነ ጠፋ ተበላሸ ከንቱ ኾነ፡ ጨሰ ተበተነ፡ ነፋስ ወሰደው

ባካኝ ባካና የባከነ የባዘነ የተበተነ፡ ቀበዞ ባዛኝ

ባዘቀ ተቀላቀለ ተደባለቀ፡ ተዘባረቀ ተማሰለ፡ እንደ መብረቅና እንደ ባዜቃ አለስፍራው አላኳያው ገባ

ባዘቀ ተደባለቀ ባዜቃ

ባዘተ (በዝቶ በዘተ) ተፈለቀቀ ተቦጨቀ እጀ ሥራ ገባ፡ ተፍታታ ለሰለሰ ደቀቀ ለተተ፡ የጥጥ የሰውነት ዛሬ በመንገድ ውዬ ሰውነቴ ባዝቷል (ተገብሮ)

ባዘተ ቦጨቀ አደቀቀ (ገቢር)

ባዘቶ በ፲፰፻፷ የነበረች ፈን

ባዘቶ የተነቀሰ የለሰለሰ ፋቶ ጣጣ

ባዘቶ ገላ አካለ ለስላሳ ሴት

ባዘነ ዞረ ተንከራተተ ዛበረ የባዘነ ጥይት እንዲሉ

ባዘዘ ቧዘዘ (በዚዝ በዘ) ባዘነ ዞረ፡ ባከነ ተንቀዋለለ፡ ፈዘዘ ነኾለለ ባዘዘና አዘዘ ባማርኛ ይተባበራሉ (ግጥም) አሽከር የለውም ወይ ጭቃና ምስለኔ ለስመኝ እንግዳ ባዘዝኹለት እኔ

ባዙቅ (ቆች) ዝኒ ከማሁ፡ አለወገኑ አላለቃው ለጠላት ያደረ ከሓዲ ጭፍራ ባሰ ብለኸ ባሽን እይ

ባዙቅነት ድብልቅነት ከሓዲነት

ባዛ ጭንጫ ያለበት የበዛበት መሬት፡ ግርግራ

ባዛቂ የባዘቀ የሚባዝቅ የተደባለቀ

ባዛች (በዛቲ) የባዘተ የሚባዝት የሚቦጭቅ፡ እጀ ሥራ የሚያገባ

ባዛኝ (ኞች) የባዘነ የሚባዝን፡ የዞረ የተንከራተተ፡ ዘዋሪ ከርታታ ዛባሪ፡ ዕር ፊተ ቢስ ሰው፡ ከመንጋ የተለየ ከብት

ባዜቃ (ዐረ ዘይበቅ) በቁሙ፡ ወርቅን ከብርና ከሌሎች ማዕድኖች ጋራ የሚያዛምድ ዝቡቅቡቅ ፈሳሽ ማዕድን

ባዜቃ (ዕብ ባዛቅ) መብረቅ ነጸ ብራቅ ብልጭልጭታ

ባዜቃ ነከረ ድርን ከፍል ርሾ አገባ አጸና አበረታ

ባዜቃ ድርን የሚያጸና የሚያበረታ ከውሃ ጋራ የፈላ ርሾ ወይም ቀረራው የንዶድ ፍሬ

ባዜን በትግሬ በረሓ ያለ አገር ቢዘንና ባዜን አንድ ዘር ነው

ባዜን ጌታችን በተወለደ ጊዜ የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ስም

ባዝራ (ሮች) (ዐረ በዘረ ተከለ ብዝር ፍሬ ቅንጣት) በቁሙ፡ ፈረስን በቅሎን የምታፈራ የምቶልድ ኦሮ ቀላማ የምትላት እንስት ፈረስ

ባዝራ ተድንጕላ እንስት ከተባት ጋራ ወይም ሴት ከወንድ ጋራ ይህ ቃል የወንድና የሴትን መንታ ኹኖ መወለድ ያሳያል ባዝራና ድንጕላ ለግመልም ይነገራል።

ባዝራ ተድንጕላ ወለደ አስቀድሞ ሴት ልጅ ቀጥሎ ወንድ ልጅ ማለት ነው

ባይ (በሃሊ) ያለ የሚል የሚናገር፡ ተናጋሪ አልኹ ባይ ይቅር ባይ እንዲሉ (እበላ ባይ) ለጥቅም ብሎ ባለጠጋን የሚያመሰግን የሚኰፍስ አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል ወደደ ብለኸ ተወደደን እይ

ባይ (ብአይ) እኔ ብመለከት ባስተውል ባገኝ

ባይ ሣሣኹ (እመ እሬኢ ሠሣዕኩ) የሰው ስም፡ ልጅ ባይ ሠሠትኩ፡ ባይሤ፡ ባይ ሣሣኹ ከፊል።

ባይሉል (ሉል ባይ) የሰው ስም (ኣባ ባይሉል) የሽንት መውጫ ያኸል ልት ያላቸው ኹለት ወንዶች ልጆች የወለደ

ባይተዋር (ሮች) (በሃሊ እምዋዕር) ጊዜና ዘመን ሲለወጥ አገኛለኹ የሚል ስደተኛ መጻተኛ ዋርን እይ፡ አየንን ተመልከት

ባይተዋርነት ስደተኛነት መጻተኛነት እንግድነት ባዳነት ተንከራታችነት

ባዮች ያሉ የሚሉ፡ ተናጋሮች (ሉቃ )

ባደ (በዐደ) ተለየ ተነበለ ተወገደ ራቀ ተገለለ

ባደግ ቢያድግልኝ፡ የሰው ስም

ባዳ ባድ (ባዕድ) ባጋም በቀጋ የማይወለድ፡ ሌላ ልዩ፡ እንግዳ መጤ የውጭ አገር ሰው፡ ከብት በባዳ ቢቈጡ፡ በጨለማ ቢያፈጡ ተለይ ባዳ እንዲል እረኛ ላገሩ እንግዳ፡ ለሰዉ ባዳ ባድማን ተመልከት፡ የዚህ ዘር ነው

ባድማ (ብዑዳዊ በዳዊ) ባዶማ፡ የባዶ የወና የጠፍ ወገን፡ ወናም ጠፋም፡ ከቤት ከንብረት ከሰው ከመኖሪያነት የተለየ ስፍራ ባድን እይ፡ ዘሩ ርሱ ነው በግእዝ መዝበር ይባላል (መዝ ፻፪ )

ባድማ ኾነ (ኮነ በድወ) ባዶ ጠፍ ኾነ፡ ጠፋ ተፈታ ፈረሰ ተደመሰሰ

ባዶ (ብዑድ በድው) ወና የተፈታ የፈረሰ የጠፋ የተደመሰሰ፡ አስቀድሞ ቤት ንብረት የነበረበት ቦታ ባድማ፡ አንዳች አልባ ሆድ ባዶ ይጠላል እንዲሉ

ባዶ አደረገ (ገብረበድወ) አጠፋ ደመሰሰ አፈረሰ፡ ለየ አራቈተ

ባዶ እጅ በትር ያሊያዘ ሰው

ባዶ ኾነ (ብዑደ በድወ ኮነ) ጠፋ ተደመሰሰ ፈረሰ፡ ተለየ ተራቈተ ቦታው ዕቃው

ባዶ ወገሜት ቅቤ የወጣለት ወተት (ግጥም) ድልኸና ቅቤ ሞልቶ በቤትኻ ምን ቸግረኸና'በባዶ በላኸ ባዶ በጋልኛ አሬራ ይባላል

ባዶ ውሃ የሌለበት ማድጋ (ኤር ፲፬ )

ባዶች (ባዕዳን) ዝምድና የሌላቸው እንግዶች

ባጀ (ሐገየ) ደረቀ፡ በጋ ኾነ

ባጀ በጋውን ባንድ ስፍራ ወይም ባንድ አገር ተቀመጠ ቈየ (ኢሳ ፲፰ ) በጋ ባጀ ተብሎ አንቀጽ ኹኗል፡ ዳግመኛም ትግሬ በሀገ ብሎ ተመኘ ይላልና፡ ባጀ የበሀገ ዘር ሊኾን ይችላል

ባጂ የባጀ የሚባጅ

ባጕም (ትግ ዝምተኛ) የዝንጀሮ ጩኸት፡ ልጆች እንደ ዝንጀሮ እያኰበኰቡ የሚጫወቱት ጨዋታ ባጕም ባጕም አለ (ግጥም) የገደል ዝንጀሮ ይላል ባጕም ባጕም፡ አይዘነጉም ለባዳና ለጉም

ባጕስ የሚወግስ የሚጨብጥ የሚቈርጥ፡ ዦሮ ቈራጭ የባጕስ ጭብጦ አጐርሥ እንዲሉ ልጆች ማጉስን እይ፡ መቀሰንን ተመልከት

ባጐሰ (መቈሰ) ወገሰ፡ ያዘ ጨበጠ፡ ጠመዘዘ ጐተተ ቈረጠ፡ የዦሮ

ባጠለ (በጢል በጠለ) ጠፋ ተፈታ ፈረሰ ተሻረ ብላሽ ቀረ፡ የጠባይ የግብር

ባጠጠ (ዕብ ባዐጥ) ወደ ላይ ዘለለ፡ መር እንጣጥ አለ፡ ተቀማጠለ፡ የልጅ

ባጢ ምኒልክ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ትሊ

ባጣ ቈዪኝ) "ካንቺ የተሻለች ሴት ባላገኝ ባል ሳታገቢ ጠብቂኝ"

ባጣጭ የባጠጠ የሚባጥጥ፡ ዘላይ

ባጥ ባጥይ ከመሬት ከፍ ብሎ በግንብና በግድግዳ ላይ ያለ ጣራ (ምሳ ፲፱ ፲፫) ቀባጠረንን እይ

ባጥ አለ ባጠጠ፡ እንጣጥ ኣለ፡ ፈነጩ

ባጥ ጣራ፡ባጠጠ

ባጥይ ጣራ፡ባጠጠ

ባጨ (ቤጸ ተበይጸ) ተለየ ተከፈለ፡ ተበተነ

ባጪር ኣስቀረ) ቶሎ ገደለ ቀሠፈ

ባፈና የሴት ስም ("ባጀባ" ማለት ነው ")

ቤል የጣዖት ስም፡ የባቢሎን ጣዖት

ቤል የፈረንሳይ ሽጕጥ ጐራሽ

ቤሰ ቢስ ኾነ፡ ነፈገ ሠሠተ

ቤሰ ነፈገ፡ ባሰ ቢስ

ቤሳ (ዐረ) በብር የሚሸረፍ የሚመነዘር የመዳብና የንሓስ ታናሽ ገንዘብ ቤስቴን ቢል ቤሳ ማለት ነው ፩ዱ ቤሳ ሳንቲም ተኩል ይኾናል የወጣውም ሰን ግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመን ነው

ቤሳኝ የሴሰነ/የሚሴስን/የሚያመነዝር...ሸርሙጣ

ቤተ ልሔም (ቤተ ኅብስት) የሰው ስም፡ የዳቦ የንጀራ ቤት ማለት ነው (፩ዚና ፶፩ ፶፬)

ቤተ ልሔም በበጌምድር ውስጥ በዙራምባ አቅርቢያ ያለ ቀበሌ፡ ቁም ዜማ የሚመሰከርበት

ቤተ ልሔም በይሁዳ ዕፃ በኤፍራታ ውስጥ ያለች ቀበሌ ጌታችን የተወለደባት (ሚክ ማቴ )

ቤተ ልሔም ከካህን በቀር ማይምን (ጨዋ) የማይገባባት ቍርባን የሚሠራባት የምስጢር ቤት ቤት እመቤታችን፡ ልሔም ጌታችን

ቤተ ልሔሞች የቤተ ልሔም ተወላጆች፡ የምስጢር ቤቶች

ቤተ መምህራን ያስተማሪዎች ቤት ፈረንጆች አካዴሚያ ይሉታል

ቤተ መቅደስ ቤተእግዚአብሔር መቅ ደሰ ኦሪት መቅደሰ ወንጌል ቤተ ክሲያን

ቤተ መንግሥት ነገሥታትና መኳንንት የሚገቡበት ሥራ የሚሠሩበት የመንግ ሥት ቤት፡ የንጉሥ ግቢ

ቤተ ማርያም እመቤታችን የነበረችበት የቅዱስ ዮሐንስ ቤት (ዮሐ ፲፱ ፳፯)

ቤተ ሠሪ ኋላ ይመጣል ያለቀውን ሕንጻ ይነቅፋል

ቤተ ሠሪ ቤት የሚሠራ (ተረት) ዘማች ለባልንጀራው እኔ የገደልኩት ደም አልወጣውም ቢለው፡ ቤተ ሠሪውን ገድለኸ ይኾናል አለው ይላሉ

ቤተ ሰብ (ሰብአ ቤት) የቤት ሰው፡ ለባለቤት የሚታዘዝና የሚያገለግል፡ ታዛዥ አገልጋይ ተቀላቢ ግብረ በላ ቤተኛ፡ የቤት ውልድ ሐዋርያት አርድእት ምእመናን ፻፳ው ቤተ ሰብ እንዲሉ

ቤተ ሰቦች የቤት ሰዎች

ቤተ ቀሊል የቀሊል ወገን፡ ወይም ነገድ

ቤተ ቈማጣ የቈማጣ ትውልድ (ተረት) ከቤተ ቀሊል ቤተ ቈማጣ ይሻላል

ቤተ በረከት ጥቂቱ ብዙ የሚኾንበት (፩ነገ ፲፯ ፲፱ - ፲፭ ፲፮)

ቤተ ተውኔት የጨዋታ የሣቅ የሥላቅ ቤት ፈረንጆች ቴአትሮን ይሉታል

ቤተ ንጉሥ ሞላልኛ ሰቀልኛ ያይዶለ ክብ ቤት አዳራሽ (ዳን ) በዚህ አይነት የተሰፋ ደስታ ድንኳን፡ የንጉሥ ቤት ማለት ነው

ቤተ ንጽሕ መታጠቢያ ቤት

ቤተ አይሁድ የአይሁድ ትውልድ

ቤተ እስራኤል የእስራኤል ነገድና ዘር

ቤተ እግዚሐር የእግዚአብሔር ቤት፡ ቤተ መቅደስ

ቤተ ክህነት የካህናት ወገን

ቤተ ክህነት ዲያቆን ቄስ መነኵሴ ደብተራ ጳጳስ የክህነት ሥራ የሚሠሩበት የሚያገለግሉበት ቤተ መቅደስ ቤተ ክሲያን

ቤተ ክሲያን (ቤተ ክርስቲያን) በቁሙ፡ የክርስቶስ ወገኖች ለጸሎትና ለምስ ጋና ለስግደት ለቍርባን የሚሰበሰቡባት ታቦትና መስቀል ሥዕል ያለባት የክርስቲያን ቤት፡ ባለ፫ ክፍል፡ እነዚሁም ቅኔ ማሕሌት ቅድስት መቅደስ ናቸው ምእመናኑም ቤተ ክሊያን ይባላሉ

ቤተ ክሲያን ሳሚ ቤተ ክሲያን የሚስም የሚሳለም ጠበለተኛ እጠድቅ ባይ

ቤተ ክሲያኖች (አብያተ ክርስቲያናት) ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች

ቤተ ክርስቲያን መሳሚያ) የክት ልብስ።

ቤተ ወጣ (ወፃኤ ቤት) ካንድ ቤት የወጣ ብዙ ሰው፡ ወንዱም ሴቱም ልጁም ዐዋቂውም

ቤተ ዘመድ የባልና የሚስት ወገን፡ ወይም አበ ልጅ ቤት

ቤተ ዝሙት የምንዝር የሽርሙጥና ቤት

ቤተ ደራስያን የደራሲዎች ቤት፡ ቤተ መምህራን

ቤተ ደንብ መሥሪያ ቤት፡ ደንብ እየተጻፈ የሚቀመጥበት

ቤተ ጥበብ የውቀት የብልኀት የፍልስፍና ቤት

ቤተ ጸሎት የጸሎት ቤት ምኵራብ መስጊድ

ቤተ ፈት አግንቶ ያጣ ከብሮ የተዋረደ አዳምን የቤተ ፈት ልማድ አላገኘውም እንዲሉ መተርጕማን

ቤተሳልገኝ የሥጋ ብልት፡ ጐድ ንና የወርች ሥጋ

ቤተኛ (ኞች) (አብያታዊ) የቤት

ቤቱ ቤት፡ የርሱ ቤት

ቤቱን ሰው አያውቀውም አንድ ቀንም ሰውን አልጋበዘም፡ አላበላም፡ አላጠጣም

ቤቱን አሸነፈ ራሱን ቻለ፡ ችግርን አራቀ

ቤታም በቤት የሚኖር ዘመድ አሽከር ሎሌ የቤት ሰው

ቤቴ ቤቴ አለ ለትዳር ለንብረት ዐሰበ ተጋ፡ ተትኰረኰረ

ቤቴል (ቤተ ኤል) ቤተ አምላክ፡ ያምላክ ቤት (ዘፍ ፳፰ ፲፱ ፴፭ ፲፭ ፲፯)

ቤት

ቤት (በዪት ቤተ ቤት) በቁሙ፡ ማደሪያ መኖሪያ፡ በደንጊያና በጡብ፡ በጠርብ በጨፈቃ በኖራ በጭቃ በስሚንቶ በጭድ በሰንበሌጥ በቈርቈሮ በሳንቃ የተሠራ ግንብና ግድግዳ ጣራ ውስጠ ክፍት ቦታ፡ ዕቃ ዋሻ ፍርኵታ ጐሬ ጕድጓድ ለሰው ጥቅም የሚኾን ነገር ኹሉ ተሠርቶ የሚገኝበትና የሚቀመጥበት (ዘርፍ እየቀደመው ሲነገር) እንግዳ ቤት እንጀራ ቤት አስር ቤት ባሩድ ቤት ግምጃ ቤት ወህኒ ቤት ወጥ ቤት ወፍጮ ቤት ጠጅ ቤት ጠላ ቤት ላይ ቤት ማድ ቤት ምድር ቤት ማለፊያ ቤት መቃብር ቤት መሸታ ቤት ነጭ ቤት ሥጋ ቤት ሥራ ቤት ዕቃ ቤት ራስጌ ቤት ሰማይ ቤት ተማሪ ቤት ታች ቤት (ዘርፍ ኹኖ ሲነገር እመቤት ይላል) የኹሉንም ትርጓሜ በየስፍራው እይ (የወፍ ቤት) በቀን ብዛት ከሣር የተበጀ (የወረንጦ ቤት) የተሸበለለ ሢር ወረንጦ መክተቻ (የኩል ቤት) የበላ ይና የበታች አዛዥና ታዛዥ የሌለበት (የምሥጥ ቤት) ኵይሳ (የንጨት ቤት) ከሳንቃ ተሠራ ሕንጻ (የቀበጠ ቤት) ያጌጠ የተሸለመ ያማረ ዕልፍኝ (ያራስ ቤት) በመ ቃኑ ላይ ሴቴ ሬትና ሰሪቴ ያለበት

ቤት ፲፪ የገበጣ ጕድጓድ

ቤት ለቤት የቀረው ነው፡ ከቤት ወደ ቤት

ቤት ለንቦሳ ዐዲስ ቤት ከተሠራ በኋላ እንዲህ ይባላል እንቦሳን እይ

ቤት ለንግዳ እንግዳን ግባ ለማለት የሚነገር

ቤት መለስ ባልትና ዘዴ የቤት አስተዳደር እከሊት ቤት መለስ አታውቅም እንዲሉ

ቤት መምቻ የመወድስና የሌላውም ቅኔ መዠመሪያ ቤት (ስንኝ)

ቤት መታ የማንኛውንም ቅኔ ንኝ ዠመረ

ቤት ሙሉ ሰጠ) አለልክ ናኘ።

ቤት ማያ የግብዣ ስም፡ ሙሽሪት ከሙሽራው ጋራ የአባት የናቷን ቤት የምታይበት ከዘመድ የምትቀላቀልበት የሰርግ ሳምንት ድግስ መለሰ ብለኸ መልስን እይ

ቤት ሥጋ የነፍስ ማደሪያ (ዘፍ ዮሐ ፳፩)

ቤት ንብረት ትዳር ኑሮ (አልቃሽ) ትልቁም ትንሹም እምዬ ይልሻል፡ አንቺውስ ምንኛ ቤት አጥፊ ኑረሻል

ቤት አሳየ ምላሽ ጠራ

ቤት አቃጣይ ሽፍታ ወንበዴ

ቤት አቃጣይ) ዐመፀኛ ወንጀለኛ

ቤት አባት (አበ ቤት) አዛዥ መጋቢ፡ ወንድ ወይም ሴት

ቤት አባቶች አዛዦች መጋቢዎች

ቤት አንሣ የጭፍራ ስም፡ የዱሮ ዘመን

ቤት አዛዥ የቤት አዛዥ አሳዳሪ

ቤት ዐይጥ የቀድሞ ጭፍራ ስም

ቤት አይጸድ የቀድሞ ጭፍራ ስም

ቤት አፈረሰ በቁሙ፡ ናደ ስንኝን ግጥምን ለወጠ

ቤት ከቤቱ ገባ የሚስት ወገን ለባል ወገን ተዳረ

ቤት ወገን ነገድ፡ ያገር ክፍል ሰባት ቤት አገው፡ ሰባት ቤት ወሎ፡ ኦሮ ቤት ኣራት ቤት ጭፍራ እንዲሉ ጐዦን ቦታን ተመልከት

ቤት ዘመድ ትውልድ ቤት ቤት ቤት ቤት እንዲሉ

ቤት የመለሰው በቤት ውስጥ ያለ ማንኛውም ዕቃ

ቤት የአኃዝ ተራ ረድፍ ያ፩ ያ፲ የ፻ የሺ ቤት እንዲሉ

ቤት የእግዚአብሔር ነው እንግዳ ያድርበት ይገባል

ቤት የዘፈን የቅኔ የመልክ የሰላምታ የነግሥ የዐርኬ ግጥም፡ ወይም ስንኝ

ቤት የዜማ ዐይነት፡ ወይም ስልት

ቤት የግስ አለቃ

ቤት የፊደል ስም፡ አለፈን እይ (ግጥም) አሌፍ ብሂል ብዬ እታው ድረስ ሳውቀው፡ ቤት እመኻል ገብቶ ልቤን አስጨነቀው (መዝ ፻፲፱ )

ቤት ያፈራው መብል መጠጥ

ቤት ጠባቂ የቤት ዘበኛ

ቤቶች (አብያት) ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ብዙዎች

ቤቶች ሰዎች ቤቶች ብቅ በሉ እንዲሉ የዚህ ቤቶች ቢል ግን፡ የዚህ ቤት ሰዎች ማለት ነው ማንን እይ

ቤቷ ያች ቤት፡ የርሷ ቤት

ቤን ሐዳድ) የቀጥቃጭ ልጅ ( ነገ. ፲፫፡ )

ቤንዚን () ከደንጊያ ከሰል ከሚገኝ ቅጥራን የሚወጣ እንፋሎት፡ ወይም የሚ በን ዘይት፡ ፈጥኖ ነዳጅ በመኾኑ ለልዩ ልዩ ይልቁንም በርቀት ለተሠሩ ሞተሮች ማስኬጃ ማገዶ ይኾናል

ቤዛ (ቤዝዎ ቤዘወ) በቁሙ ዋጋ ካሳ ለውጥ ምትክ፡ ዋቢ ዐላፊ ዋስመድን ተያዥ (የእጅ ቤዛ) የቈዳ እጅጌ ባጨዳ ጊዜ እጅ የሚያጠልቀው (የጣይ ቤዛ) ጥላ (የጣት ቤዛ) በስፌት ጊዜ መካከለኛ ጣት የሚገባበት የብረት ቆብ ፈረንጆች ደይ ይሉታል

ቤዛ የሰው ስም፡ ከመንዝ ባላባቶች አንዱ የቤዛ ዘር እንዲሉ

ቤዛነት ቤዛ መኾን፡ ለውጥነት ምትክነት

ቤዠ (ቤዘወ) አዳነ ታደገ ገንዘቡን ወይም ራሱን ለውጥ ሰጥቶ ከጭንቅ ከባርነት አወጣ፡ ከባለዳ እጅ ገዛ ዋጀ

ቤዶ (ባዶስ) እንደ ጕርዝኝ ያለ አራተ ፈጅ ቍና የዋድሎች መስፈሪያ

ቤጣ የፊደል ስም፡ ቤት

ነገድ ወገን፡ ሕብራቸው ቀለማቸው የኾነ ሺንና ጃፓን

አንተ ብትኖር ወንድሜ ባልሞተም ነበር ብኖር ዓመት፡ ብበላ ጋት በቅርቦች ወንዶችና ሴቶችም እንደዚሁ ይገባል

ብሓ ነጭ ደንጊያ ብሓ ድንጋይ እንዲሉ ብክካንን ተመልከት

ብሄሞት (ብሂም ብህመ) ጕማሬ የባሕር እንስሳ የወንዝ አውሬ ሌሊት ከውሃ እየወጣ ሣር የሚበላ (ኢዮ ፲፭) ጅንን እይ

ብሄሞት የየብስ ዓሣ ነባሪ የምድር አራዊትና እንስሳት ንጉሥ ከባሕር ተፈ ጥሮ በየብስ የሚኖር፡ ምድርን በስተየብስ የከ በበ፡ የሌዋታን ጣምራ አቻ ወደር (ሔኖ ) ባማርኛ ዘንዶ ይባላል (ኢዮ ፵፩ ) ዘወረ ብለኸ ዙሪያን ተመልከት

ብሔረ ሕያዋን ሔኖክና ኤልያስ እነሱን የመሰሉ ሰዎች የሚቀመጡበት ዓለም

ብሔረ ብፁዓን የበቁ ሰዎች ቅዱሳን ባሕታውያን የሚኖሩበት ስፍራ ጌታ ችን ባ፲፪ ዓመቱ ገብቶ ያስተማረበት ትቤትን ተመልከት

ብሔረ ኦሪት ፭ቱ ክፍል ኦሪት

ብሔር አገር ዓለም (ግእዝ)

ብሖር ቡኸር (ሮች) ሲጮኸ ቡሕ የሚል፡ የዋላ የድኵላ ዐይነት፡ የበረሓ

ብሖር የዱር ፍየል (ኢዮ ፴፱ ) ተባቱም እንስቱም ብሖር ይባላል

ብሆር የዱር ፍየል፡ብሖር

ብሉል ሎቲ፡ የሎቲ ዐይነት

ብሉል የርግብ ዐይነት፡ የምትበር ዋኖስ ጕራጌ ግን ርግብን ቡላል ይላል

ብሉይ (በልየ) ኣሮጌ ያረጀ ያፈጀ ኦሪት ነቢያት

ብሉይ ተሐዲስ ኦሪት ከወንጌል ጋራ

ብላ (ብላዕ) ጕረሥ፡ ተመገብ ሳትወልድ ብላ እንዲሉ

ብላ ተባላ (ብላዕ ተባላዕ) ኣንዱን አንዱ የሚቀማበትና የሚገድልበት ክፉ ጊዜ

ብላ ተናግራ፡ባለ

ብላሽ፡ ብልሹ፡ የተበላሸ፡ በክት፡ ሙቶ፡ ያደረ፡ ከንቱ፡ የማይረባ፡ ነገር

ብላሽነት፡ ብላሽ፡ መኾን ብልሽት፡ ጥፋት፡ መሰናክል ብልሽት፡ አለ፡ ጥፍት፡ ብክት፡ አለ መበላሸት፡ መጥፋት፡ ብላሽ፡ ጥፉ፡ መኾን

ብላታ ብልኅ ሥልጡን ስብቅል ሰው፡ የነገር ብልት ዐዋቂ

ብላታ የማዕርግ ስም

ብላቴና ልጅ ጕብል ወጣት ሦታ አሽከር፡ ክፉና መልካም የለየ

ብላቴና ሴት ልጅ፡ ልጃገረድ

ብላቴናልጅ በለተ

ብላቴናው አሽከሩ ልጁ ወጣቱ ለጋው (ዘፍ ፳፩ ፲፪ ፲፬ ፲፭) የሴቷን በብላቴናው አንጻር ብላቴናዋ ይሏል

ብላቴናዪቱ አሽከሪቱ ወጣቷ ለጋዪቱ ልጃገረዲቱ (ዘፍ ፳፬ ፲፮ ፶፭ ፶፯)

ብላቴን (ኖች) ጌታ፡ የብላቴኖች የጥቃቅኖች ሹም፡ አዛዥ መጋቢ አሠልጣኝ ምክር ዐዋቂ አውፋሪን ተመልከት፡ ወፈረ ዋዛን እይ

ብላቴንነት ልጅነት ወጣትነት አሽከርነት (ዘሌ ፳፪ ፲፫ ፪ጢሞ ፳፪)

ብላቴኖች ልጆች የውስጥ አሽከሮች ጥቃቅኖች (ዘፍ ፳፪ ፲፱) ጪጪን እይ ለታላላቆችም ይነገራል (፪ሳሙ ፲፯)

ብላት

ብላት ዕውቀት፡ ብልኅ

ብላቶ (ብላዕ) ያውሬ ትራፊ ሥጋ፡ ዕኝክ ግትን፡ ያገዳ ምጣጭ

ብላጊ (ጸደይ) የበለገ፡ የበልግ ጊዜና ወር

ብላጥ ልባጥ ለበጠን እይ

ብላጥ በለ

ብሌን (ኖች) በሐማሴን ክፍል በከረን አጠገብ ያለ ያገርና የነገድ ስም

ብሌን (ዕፀ ኵሕል) ያይን ሚቶ ጥቍሪቱ ብረቲቱ (መዝ ፲፯ ዘካ ) (የዦሮ ብሌን) መስሚያ

ብል (እመ እብል) ብናገር ፈጣሪ ካላለ እኔ ብል አይኾንም ባለን እይ

ብል (ጮች) ከወሸከራና ከወደ ላት የሚበልጥ፡ በዠርባው ሲንጋለል በስተሆዱ ብልጭ የሚል ዓሣ

ብል የሸማ የልብስ የቈዳ ትል ብል በላው፡ በሳው በጠረቀው

ብልኀ (ኆች) በቁሙ፡ ዐዋቂ ጠቢብ ጥበበኛ አስተዋይ ፈጣን ቀልጣፋ በግእዝ ግን ስለት ሹለት ማለት ነው

ብልኀተኛ (ኞች) ብልኅ የእጅ ጥበብ የናላ ዕውቀትና ማስተዋል ያለው ሰው፡ ባለአእምሮ ፈላስፋ ሐኪም ወጌሻ፡ ሞፈር ቀንበር ጕርዳ በሺ፡ ዕርፍ ዐራቂ ድግር ጠራቢ፡ ወይፈን ወጠጤ ወቃጭ፡ መዝጊያና መስኮት ገጣሚ፡ ጣራ አዋቃሪ ከዳኝ፡ ሱሪ በርኖስ ልብስ ድንኳን ጥላ ሰፊ፡ የዘርን ጊዜ ዐዋቂ፡ ወለምታና ውልቃት ስብራት ጠጋኝ፡ ገራዥ እንጥል ቈራጭ፡ ዐይን እብራ (ዳን ማቴ ፳፭ )

ብልኀተኛ ኾነ (በልኀ ጠበ) ፈለሰፈ፡ ብልኀትን ጥበብን ፈጠረ አገኘ አወጣ ባየር ሰፈፈ መጠቀ፡ በውቅያኖስ ውስጥ ኼደ ጠለቀ

ብልኀት ምክንያት ሰበብ እከሌ ገንዘቤን አለብልኀት ወሰደብኝ

ብልኀት ብላት፡ ፈሊጥ ዕውቀት ጥበብ ዘዴ ማስተዋል በግእዝ ግን መስላት መሾል መፍጠን ይባላል (ተረት) የእጅ ብልኀት ባርነት፡ ያፍ ብልኀት ጌትነት ሠባን እይ

ብልኀት ዐለቀበት መውጫ ቀዳዳ ዐጣ፡ ተያዘ ተጨበጠ፡ ከጠላቱ በታች ኾነ፡ እንደ ሶምሶን እንደ ናፖሊዮን

ብልኅነት ጥበበኛነት ዐዋቂነት ሐኪምነት ወጌሻነት

ብልስ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ የተበለሰሰ፡ የው ርዴ ዐይን

ብልስስ፡ አለ፡ ተበለሰሰ፡ ተበላሸ አበለሳሰስ፡ አሰለጣጠጥ፡ መበልሰስ በለስና፡ (በለሸ) ከበለሰሰ፡ ጋራ፡ አንድ፡ ናቸው፡ ሰው፡ በበለስ፡ ምክንያት፡ መጐዳቱን፡ ያስረዳሉ በለተ፡ (በልቶ፡ በለተ) ለየ፡ ነጠለ፡

ብልቃጥ (ጦች) በቁሙ፡ ታናሽ ጠርሙስ የሚከፈት የሚዘጋ፡ የዘይት የሽቱ የመድኀኒት የመርዝ መቀመጫ መኖሪያ ( ሳሙ ) ብልቃጥ ዐረብኛ ነው

ብልቅጥ ዝኒ ከማሁ፡ የተበለቀጠ

ብልብላ (ኦሮ) በሕፃን በጥጃ በበቅሎ በፈረስ ዐንገት የምትንጠለጠል ታናሽ ቃጭል (ዘካ ፲፬ )

ብልቱግ በትግሬ ወረዳ በብሌን የሚበቅል የማሽላ ዐይነት እኸል፡ ዐረቦች ድኁን ይሉታል

ብልቲት፡ ጎላ፡ የሚበጣ፡ ራስ፡ የሚ ላጭ፡ ብልጩት

ብልቲትባልጩት H በለተ

ብልት (ብልዐት) መብላት

ብልት፡ (ቶች) ብሉት) የተበለተ፡

ብልት በቁሙ፡በለተ

ብልት፡ ዐቅድ፡ ስልት፡ አዝማሚያ እንዲሉ

ብልት፡ አወጣ፡ ሥጋን፡ አወራረደ፡ ቈረጠ፡ ለየ፡ ከፈለ፡ ፲፪፡ አደረገ

ብልት አውጪ፡ ብልት፡ የሚያወጣ፡ ዐራጅ፡ አወራራጅ

ብልት አደረገ ፈጥኖ በላ

ብልዝ (ዞች) የበለዘ የዘጐነ፡ ዝጕን ብልዝ ዐይን ብልዝ ጥርስ እንዲሉ

ብልዝ አለ በለዘ፡ አቦልሴ ኾነ፡ በረሰ በለሰ

ብልግ ልዕልና ከፍታ ክብር ላቂያ (መክ ፲፪ ሕዝ ፲፭ )

ብልግ አለ ፈጽሞ ባለገ፡ ባለጌ ነውረኛ ኾነ

ብልግ የባለገ

ብልግና ሕገ ወጥ ሥራ፡ ሳይዳሩ ሳይኳሉ ማግባት (መዝ ፵፱ )

ብልጠት ፈሊጥ ዕውቀት ብልኀት ዘዴ፡ ምስጢሩ ብልጫን አይለቅም

ብልጣብልጥ የብልጥ ብልጥ፡ ብል ጠቱ የበዛ የጦጣ ብልጣብልጥ እንዲሉ

ብልጥ (ጦች) ብልኀ ዐዋቂ፡ በውቀት ከሌላው የበለጠ

ብልጥ ራሱን አይጥልም ሰውነቱን አያዋርድም፡ ገንዘብ አያጣም፡ አይቸገርም

ብልጥ አለ ረዘም አለ

ብልጥነት ብልኅነት ዐዋቂነት

ብልጥግና በቁሙ፡ ክብር ድልብ፡ ብዙ ገንዘብ፡ እዱኛ ዘመን

ብልጭ (ብሩጽ) የበራ ቍልጭብልጭ ያለ

ብልጭ አለ ተግ ቦግ አለ፡ ፈገገ በለዉ

ብልጭ አደረገ አነደደ አበራ፡ ኣበለጨ

ብልጭ ድርግም አለ ከመ ቅጽበት በራ፡ ጠፋ ያማርኛ ገበታዋሪያ እይ (ገጽ ፴፬)

ብልጭልጭ አለ አካቶ ፈጽሞ ፍልቅ ፍልቅ አለ፡ ተብለጨለጩ (፩ዜና ፳፱ )

ብልጭልጭ አቦ ከደብረ ሊባኖስ በስተደቡብ ያለ አገር ያቦ አጥቢያ የብልጭልጭ አቦ ማለት ነው

ብልጭልጭ የተብለጨለጨ የሚብለ ጨለጭ፡ ዐይን የሚያፈዝ የሚበዘብዝ፡ የፀሓይ የመብረቅ የእሳት የኤሌትሪክ የውሃ የመስተዋት ብርሃን (ናሖ )

ብልጭልጭታ በጋለ ምጣድና ድስት ቂጥ ላይ የሚታይ የነበልባል ነጠብ ጣብ በግእዝ ቀለምጺጽ ይባላል

ብልጭልጭታ የብልጭታ ድጋሚ፡ ብልጭልጭ ማለት፡ ብርቅርቅታ ብዛቱን ያሳያል (ዳን ፴፩)

ብልጭታ ቦግታ ብርሃን ነጸብራቅ

ብሎት (ብልዐት) ፍስክ፡ የጦም ቀን ያይዶለ፡ እሑድ ሰኞ ማግሰኞ ዐሙስ ቅዳሜ፡ ከብት የሚታረድበት ሥጋ የሚበላበት ጊዜ

ብማቴ ብዊ፡ብ

ብም አለ ድም አለ፡ ድምጥ ሰጠ ጮኸ፡ ሰማዩ ገደሉ ናዳው ከበሮው ብም ባማ ከማለት ከግእዝ የወጣ ነው

ብም የመብረቅና የናዳ የመርግ የከበሮ ድምጥ

ብሰሳ ስለላ ሰብቅ ነገር መሥራት ቅጥፈት

ብሳና (ኖች) (ምሳና) በቁሙ የታ ወቀ የወይናደጋ ዕንጨት ምሳና ማለት ነቀዛምነቱን ያሳያል ማሰነንን ሸንኰርን እይ ዳግመኛም (ብሳና) በስተኸ ቀንበር አድርገው ብሎ ይተረጒም

ብሳይ ፍግ ዐዛባ፡ በበረት ወይም በጕድጓድ ውስጥ ቈይቶ የበሰለ የተብላላ ዕርሻ የሚያሳምር፡ መድረቁንና ጠቦት መኾኑን ያሳያል

ብስ (ሶች) የተበሳ፡ ፍልፍል ሽን ቍር ቀዳዳ ነዳላ ንድል

ብስ (ዐረ ቢስ) ያንበሳ ወገን ድመት ባማርኛ ግን ክፍ ኺድ ወግድ በቃ ማለት ነው ዐረብም በቃ ሲል ብስ ይላል አንበሳ እንቦሳ አንባሻ በግእዝ የበስበሰ ዘሮች ናቸው

ብስ ክፍ፡ በሰበሰ

ብስል ሰው ዋና ጠንካራ ሰው፡ ዐዋቂ ቁም ነገራም

ብስል ተቀሊል ጥሩ ታደፍ፡ ጤፍና ስንዴ ገብስ፡ ከባቄላና ካተር ከሽንብራ ከምስር ካገዳ ጋራ

ብስል አለ ተቀቀለ ተከነ ነፈረ

ብስል የበሰለ፡ እንጀራ ቈሎ ንፍሮ ገንፎ ሥጋ፡ የተቀቀለ ቅቅል የጠነከረ የጠና ጥሩ ማለፊያ፡ የጐመራ ሰብል

ብሥራተ ገብርኤል ቅዱስ ገብርኤል ለመቤታችን መጋቢት ፳፱ ቀን የነገራት ምሥራች፡ ይኸውም ታኅሣሥ ፳፪ ቀን ይከብራል (ሉቃ ፳፮፡ ፴፰)

ብሥራት ምሥራች፡ ደስ የሚያሠኝ ወሬ

ብስቍል የበሰቈለ፡ ጕስቍል

ብስቍልና ጕስቍልና

ብስበሳ ርጥበት ርሰት

ብስት አደረገ በፍጥነት በሳ

ብስትስት አለ ተበሳሳ

ብስትስት የተበሳሳ፡ ሽንቍርቍር

ብስና ክፉ ሽታ ግማት ክርፋት ካፍ የወጣ፡ የፈስ ዐይነት የኮሶ የኰረፌ ግሣት

ብስናም ባለብስና ግም።

ብስናታም ግማታም ክርፋታም

ብስናት ዝኒ ከማሁ ለብስና

ብስኪያም የብስክ ብጣሻም፡ ድርና ማግ ገመድ ጠፍር የመሰለው ኹሉ

ብስክ (ብቱክ) የተበሰከ የተሰተከ፡ ብትክ ብጥስ

ብስክ አለ ቍርጥ ብጥስ አለ

ብስክስክ ብስክሳኪ የተብሰከሰከ የተቀማጠለ የተንበሸበሸ፡ ብትክትክ ብጥስጥስ

ብስጥ በቀድሞ ዘመን ከፋርስ የሚመጣ ምንጣፍ፡ ባረብኛ ብሳጥ ይባላል

ብስጩ (ዎች) የተበሳጩ የተቈጣ፡ ቍጡ ጠበኛ

ብስጭት ቍጣ ንዴት ጩኸት ግሣጽ

ብስጭት አለ ተበሳጩ

ብስጭትጭት አለ ተበሰጫጩ

ብሶል በየብስና በባሕር በአየር ለሚኼዱ ሰዎች ሰሜንን የሚያመለክት መሣሪያ፡ ፲፰ ሠላጤ ያለው መርሐ ሰሜን ከክርስቶስ በፊት ፲፻ ዓመት በሺን አገር ነበረ ይባላል

ብሶት የባሰ የጠና መከራ ሥቃይ ችግር ጭንቅ

ብረ ሰብስብ ዕንብርት ያላት ብር

ብረ ሰብስብ) ሴቶች ከክታብ ጋራ የሚይዙት/የሚያንጠለጥሉት ብር፡ ሌላውን ብር ሁሉ እክብ/አከማች/አጠራቅም ማለት ነው።

ብረ ሸሽ ዐጥንቱ የቀጠነ፡ ሰው ነቱ የመነመነ ኰሳሳ ሰው ብር የተባለ አገዳው ቅልጥሙ ነው

ብረተ ፈጅ ብረትን የሚበላ የሚፈጅ የሚጨርስ የሚያሰላ ሻካራ ደንጊያ ገርጋራ መሳል

ብረታብረት ከጕጣ ከዕላቆ ብረት የተሠራ የብረት ብረት፡ ብዙ ዐይነት፡ ዶማ ማረሻ ወገል ቢላዋ መጥረቢያ ማጭድ የመሰለው ኹሉ

ብረት (ብንተ ዐይን) በነጭ የተ ከበበ ያይን መካከል ጥቍሩ እንደ መስተዋትና እንደ ውሃ እንደ ጥሩ ብረት ረቂቅ መልክ የሚያሳይ ባይኔ በብረቱ አየኹት እንዲሉ

ብረት (ቶች) (ኀጺን) በቁሙ፡ ዕንጨት የሚቈርጥ፡ ደንጊያ የሚሰብር የሚፈልጥ፡ ጠይቦች ከጥቍር ዐፈር አንጥረው የሚያወጡት ጠንካራ ካክራ ማዕድን ዐረብ ብረት እግር ብረት እንዲሉ (ንጥር ብረት) ድጅኖ በትረ ቃቃን

ብረት ለበስ ስማርድ፡ ፈረንጅ ሠራሽ የጦር መሣሪያ

ብረት ምጣድ ከብረት ሰሌዳ ወይም ሉሕ የተበጀ የብረትምጣድ (ዘሌ )

ብረት ሠራ (ነሀበ) ብረት ቀጠ ቀጠ አበጀ

ብረት ቈሎ የብረት ቈሎ፡ የማይፈነ ከት የማይነካ የማይበገር የማይደፈር ጐበዝ

ብረት አዝባጭ ባለጅ ጠይብ

ብረት ወይም ሴት

ብረዛ ብጥበጣ ዝለላ ቅልቀላ

ብሩ

ብሩ ብሪቱ የወንድና የሴት ስም

ብሪንጥ ያረቄና የወይን ጠጅ አተላ ዝቃጭ

ብሪካ ጌታ የሌለው ከብት ወይም ገንዘብ፡ ላምጪው የሚመረቅ

ብራ ዝናም የሌለበት ቀንና ሌሊት፡ ብራ ኾነ (ጽሕወ) ሳይጥል ቀረ ዝናሙ

ብራማ ብራህማ ከ፫ቱ የህንድ አምላኮች አንደኛው፡ በሥዕል ከታች አንድ፡ ከላይ ገጽ ኹኖ የሚታይ ባኒያኖች በፈጣ ሪነቱና መዠመሪያ ሥጋ በመልበሱ ብራህማ፡ በገዳይነቱ ሴዋ፡ ባዳኝነቱ ዊሺኑ ተባለ ይላሉ

ብራሪ ዝኒ ከማሁ፡ ፍንጣሪ

ብራቅ የእሳት ሰይፍ የእሳት ፍላጻ፡ በዝናም ጊዜ ከደመና አፎት የሚመዘዝ የሚወረወር ብራቅ ጣለ፡ ብራቅ መታው እንዲሉ

ብራብሪት ታናሽቱ እንስቲቱ

ብራብሮ (ዎች) በበጋ ይሞትና በክረምት ታድሶ የሚበር የሚከንፍ ተንቀሳቃሽ ባለብዙ ቀለምና ሕብር፡ በባበባ ወራት ከመስ ከረም ፳፭ እስከ ኅዳር የሚበዛ

ብራብሮ በቁሙ፡ በረረ

ብራና (ኖች) (ብርሃና) ከበግ ከፍየል ከጊደር ከፈረስ ቈዳ ደደቡና ጠጕሩ ተፍቆ የተዘጋጀ መጻፊያ ያልተቀጻ፡ በነጭ ኆጻ ታጥቦ የጠራ የበራ ማለት ነው፡ አንቀጹ በግእዝ በርሀ ነው

ብራኳ የትከሻ ዐጥንት ከወደ ኋላ ያለ

ብር (ሮች) (በሪር በረ ብሩር) በቁሙ፡ ለመገብያ ካንዱ ወዳንዱ የሚተላ ለፍ፡ የተመረጠ የተለየ፡ ልዩ ልቅም ጥሩ ነጭ ማዕደን ክቡር ገንዘብ የወርቅ ምትክ (ዘፍ ፳፫ ፲፮) በተባትና በእንስት ለመናገር ብሩ፡ ብር፡ የርሱ ብር ብሯ፡ የርሷ ብር

ብር (በሪር) መብረር ፊትን እይ

ብር (ብሩህ) የበራ የጠራ የነጣ ነጭ፡ የታየ ግልጥ፡ ብልኅ እከሌ ልበ ብር ነው እንዲሉ ዐይንን እይ

ብር (ብርዕ) በቁሙ፡ ከሸንበቆና ከጐሽ መቃ ከቀስተኒቻ (ሰሪቴ) ከብረት የተቀረጸ የጽፈት መሣሪያ ብርና ቀለም እንዲሉ ውስጠ ክፍት ኣገዳ ገለባ የገብስ ብር የስንዴ ብር እንዲሉ (ተረት) ድንቢጥ እንዳቅ በብር ትታገማለች ከግእዝ የራቁ ሰዎች ግን ብዕር ይሉታል

ብር መፈተኛ) ብራና ወረቀት ቀለም

ብር ቂንጥ ቱር ቂብ

ብር ቂንጥ አለ ሮጠ ተቀመጠ

ብር ብር አለ ርግብ ርግብ አለ፡ ያይን የልብ

ብር ብር አደረገ አኹንም አኹንም ቶሎ ቶሎ አበረረ፡ ዕረፍት ነሣ

ብር ነቀል (ሎች) ከተማሪ ቤት ተምሮ የወጣ የመምሩን ብር ያነሣ ዐዲስ ደቀ መዝሙር ብር ትምርቱ ጽፈቱ፡ ነቀል ዕውቀቱ

ብር አለ በረረ ሮጠ መጣ ብለኸ መጭን ተመልከት

ብር ዐለንጋ (የብር ዐለንጋ) የዛር ስም፡ ቀይ ዶሮ ዱልዱም የሚገብሩለት ዛር ብር እጀታው፡ ዐለንጋ ጕማሬው

ብር አንባር (የብር አንባር) ክብርና ድንግልና

ብር ዋንጫ (የብር ዋንጫ) በፈረስ ግልቢያ ለቀደመና በኳስ ጨዋታ ለበለጠ የሚሰጥ ሽልማት

ብርሃነ ልብ የልቡና ጥራት

ብርሃነ ልደት ጌታችን የተወለደ ለት የታየ ብርሃን

ብርሃነ መስቀል መስቀል ከጕድጓድ በወጣበት ቀን የተገለጸ ብርሃን

ብርሃነ ብርሃናት የብርሃኖች ብርሃን ጌታ ፈጣሪ

ብርሃነ ትንሣኤ ጌታችን ሙቶ በተነሣ ጊዜ የበራ ብርሃን

ብርሃናት ብርሃኖች

ብርሃን (ኖች) በቁሙ፡ ጸዳል ውጋ ጋን እሳት ፍም ነበልባል ቀን ዐይን፡ ዕውቀት ልቡና ደበረን ደጅን ከሠተን ተመልከት

ብርሃን ሰገድ የ፪ኛ ኢያሱ ስመ መንግሥት

ብርሃን ኾነ ተፈጠረ ተገኘ (ዘፍ )

ብርሌ (ዎች) (ቢረሌ) በቁሙ፡ ነጭ ጥሩ የባሕር ዕቃ፡ በመንቀል አምሳል የተሠራ፡ የቦረቦቼ ዐይነት፡ ልሙጥ ሹርቤ ስጕዳ አረንጓዴ (ተረት) ብርሌ ከነቃ አይኾንም ዕቃ፡ ጠጅ በብርሌ፡ ዜማ በሃሌ፡ ቀይ እንደ በርበሬ፡ ጥሩ እንደ ብርሌ ሞንን ተመልከት

ብርቄ የኔ ብርቅ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም

ብርቅ ነኽ ነሽ ወልዶ የማያውቅ በወለደ ጊዜ ለልጁ የሚሰጠው ስም ነው

ብርቅ ዘወትር የማይታይና የማይገኝ ዐዲስ እንግዳ ነገር፡ ድንቅ ሥራ፡ ጕድ ታምራት ብርቅና ድንቅ አላንድ ቀን አይደምቅ ቈመጠ ብለኽ ቈማጣን እይ

ብርቅስ አለ ተበረቀሰ ፈረሰ

ብርቅስ አደረገ በረቀሰ ጣሰ

ብርቅስቅስ የፈራረስ ፍርስርስ

ብርቅርቅ የተብረቀረቀ

ብርቅርቅታ ብልጭልጭታ

ብርቅዮሽ የብርቅ ዐይነትና ወገን

ብርበራ ብዝበዛ ዘረፋ ወረራ በግእዝም በርበር ይባላል

ብርባሮ ግልበጣ መገልበጥ

ብርብራ (ዎች) (በርባር) የዛፍ ስም፡ ፍሬው ዓሣ የሚያሰክር የሚበረብር፡ ባሕር የሚያሸብር

ብርብር (ብርቡር) የተበረበረ፡ ውሃ የበረበረው ወንዝ ማለት ነው

ብርብር በገሙ ውስጥ ያለ አገር የማሪያም አጥቢያ ብርብር ማሪያም እንዲሉ

ብርተቃቃን ድጅኖ በትር

ብርቱ (ዎች) (ብርቱዕ) የበረታ የጠነከረ፡ ኀይለኛ ጠንካራ ጕልበታም ጐበዝ (ኢሳ ፳፩ ሕዝ ፴፱ ) (ተረት) ላንድ ብርቱ ኹለት መዳኒቱ

ብርቱነት ኀይለኛነት ጠንካራነት

ብርቱካን (ዐረ) በኵረ ሎሚ

ብርቱዋ ብርቱዪቱ ጠንካራዋ ጠን ካራዪቱ (፩ነገ ፵፪)

ብርታት ጥናት ጥንካሬ ኀይል ጕብዝና ጕልበት (ዘዳ ፲፰ ምሳ ፲፬)

ብርት (ቶች) ቀይ ብረት፡ መዳብ፡ ማዕርጉ ከብረት ኹለተኛ የኾነ ብርት የግ እዝ፡ መዳብ ያማርኛ ነው፡ ንሓስም በግእዝ ብርት ይባላል

ብርት ከመዳብና ከንሓስ የተበጀ ባለወንፊት ሳሕን (ደቅ) የእድፍ መፍሰሻ ማረፊያ ሰንና ብርት እንዲሉ ዳታንን እይ

ብርንዶ (በረደ) ያልተጠበሰና ያልተቀቀለ ጥሬ ሥጋ፡ ሥብ ያይዶለ ቀይ ሙዳ፡ ትርጓሜው በሪድ ማለት ነው ሲበዛ ብርንዶች ይላል

ብርንጎ በቀጪኑ የተሠራ ቍንጮ

ብርከታ ብዛት ፍድፈዳ

ብርኵማ (ሞች) የሽባ መንፍቀ ቂያ፡ ዐጪር ቍራጭ ዕንጨት፡ እጅ ማግቢያ ያለው ኹለት ዐይነት፡ የእጅ መጫሚያ (ብርካዊ ዘብርክ) ማለት ነው

ብርኵማ ባለሽሩሶች የሚንተራሱት ትራስ፡ ከጥቍር ዕንጨት (ዞጲ) ከሰንደል የተበጀ፡ በግእዝ መሥዕርት ይባላል ብርኰትን ተመልከት

ብርኵማ እንደ ፊደል የተቀረጸ የበገና አውታር ደጋፊ፡ ከጠፍር ቍርጥራጭ ጋራ በስተታች አውታሩን (ዥማቱን) ወትሮ ገትሮ የሚይዝ

ብርኵማ የበርበሬ ዛላ ሥር (ቂጥ) የቅንጣሽ ጫፍ

ብርኵታ (ቶች) በፍም የሚበስል ርሚጦ ቂጣ፡ ሲበሉት የሚያጠግብ የሚበረክት የሚመክት የጭብጦ ዐይነት ትግሮች በጋለ ደንጊያ ሊጡን አድበልብለው ያበስሉታል፡ ሺዎች ግን ጕድጓድ ምሰው ሊጡን በቅጠል ጠቅለው ከጕድጓድ ውስጥ አግብተው በላዬ እሳት ያነዱበታል፡ ወይም በፍም ውስጥ ይረምጡታል በግእዝ ዳፍንት ይባላል

ብርክ ጕልበት መታጠፊያ የጕል በት ማነስ ፍርሀት ድካም ብርክ ያዘው፡ ብርክ ብርክ አለው እንዲሉ

ብርክርክ አለ ተብረከረከ፡ ዐቅም አነሰው

ብርክርክ የተብረከረከ፡ እንቅጥቅጥ

ብርኰት (ብርኵት) ቈዳ የለበሰ የንጨት ትራስ ብርኵማ ብርኳኔ ብርኰት ከብርክ ይወጣሉ

ብርኳኔ ዝኒ ከማሁ፡ የንጨት ትራስ

ብርዝ (ብሩዝ) የተበረዘ የተቀላ ቀለ፡ ቅልቅል (ቅጽል)

ብርዝ ውሃና ማር፡ ማርና ጠላ፡ የባላገር መጠጥ ወይም የጠጅ ብጥብጥ (ስም)

ብርዥ ብልጭታ ጥቂት ብርሃን ጥርዥ ብርዥ እንዲሉ

ብርዳም ውርጫም ቅዝቃዜያም፡ እንደ ጣርማበርና እንደ መገዘዝ ያለ ስፍራ

ብርድ ልብስ (የብርድ ልብስ) በብርድ ጊዜና ሌሊት የሚለበስ ወፍራም ልብስ፡ ከጥጥ ከጠጕር ፈረንጅ የሠራው

ብርድ ብርድ አለው በረደው ቀዘቀዘው

ብርድ ውርጭ ዐመዳይ ቍር ቅዝቃዜ ቈፈን፡ ከጥቅምት ፲፫ እስከ ጥር ፲፫ የሚሠለጥን

ብርገጋ ድንጋጤ ፍራት

ብርጕድ እንደ ዕጣን ያለ ጥቍር ሙጫ፡ ሴቶች የሚታጠኑት የሚሞቁት፡ ነጋዴዎች ከባሕር የሚያመጡት ወንዴ ብርጕድ ሴቴ ብርጕድ እንዲሉ

ብርጋና የወፍ ስም፡ ከፀሓይ ጸዳል ዕንቍ የምትወልድ የባሕር ወፍ፡ የመቤታችን ምሳሌ በግእዝ አዋልድ ትገኛለች፡ ባኹኑ ዘመን ኣትታወቅም

ብርግድ አለ ክፍት አለ፡ ተበ ረገደ

ብርግድ ዝኒ ከማሁ፡ የተበረገደ ኀፍረተ ብእሲት

ብርግግ የተበረገገ የተወለለ ውልውል

ብርጭቅ (በጢሕ) የዱባ ዐይነት ተክል፡ ውስጠ ቀይ ክብ እንክብል ማር ማር የሚል

ብርጭቆ (ዎች) ከክርስቶስ ልደት በፊት ሺህ ዓመት ግብጦች አሸዋ አንጥረው በዋንጫና በጥዋ አምሳያ ሠርተው ያወጡት የብርሌና የመስተዋት ዐይነት ዕቃ ብር ጭቃ (ራእ ) ዐረብ ኩባያ ይለዋል

ብሮት በሕፃን ገላ ላይ ያለ ጥቍር ነጠብጣብ፡ ማሪያም የሳመችው ነው ይባላል

ብሮች (አብራዕ) መጻፊያዎች

ብሯ ብሪቱ ያች ብር

ብሽርክ አለ ተበሸረከ፡ ቅድድ ኣለ፡ ሽርክት አለ

ብሽርክ ዝኒ ከማሁ፡ ሽርክት

ብሽርክርክ የተቀዳደደ፡ ሽርክትክት ብጭቅጭቅ

ብሽሽት ከንፍፊት በስተላይ ያለ፡ ልም ገላ ጕያ

ብሽቅ አለ በሸቀ

ብሽቅጥ አለ ብክት አለ

ብሽቅጥቅጥ አለ በሸቀጠ ተበሻ ቀጠ

ብሽቅጥቅጥ ፈጽሞ የራሰ የበከተ

ብቀታ ንትረካ ንዝነዛ

ብቃት (ብቍዐት) ንጽሐ ሥጋን ንጽሐ ነፍስን ንጽሐ ልቡናን አግኝቶ መልአክን ነፍስን ዕመቀ ዕመቃትን ሰማየ ሰማያትን ሥላሴን ማየት፡ ፍጹምነት ቅድስና

ብቅ (በቊል) መብቀል

ብቅ መውጣትበቀለ

ብቅ አለ ወጣ ተገለጠ ታየ፡ ከፍ አለ

ብቅ አደረገ ከውስጥ አወጣ አሳየ

ብቅ ጥልቅ አለ ወጣ ገባ አለ ተመለሰ፡ ራሱን አሳየ ደበቀ ሲዋኝ

ብቅ ጥልቅ አንዳንድ ምታሪ ሥጋ ከሹሮ ወጥ ጋራ

ብቅል (ሎች) (ብቁል) በውሃ ርሶ በቅጠል የተሸፈነ በመሬት ተቀብሮ የበቀለ የጫጩት አፍ መሳይ ገብስ፥ ወይም ስንዴ፡ የጥሬው ግግር ጕንቍል፡ የጠላ ርሾ (ጥንስስ) ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል እንዲሉ።

ብቅል ሰቃይ ረዥም ሰው፡ ኦሮ ሞፈር

ብቅል ረገጠ የገብስን ጕንቍል በቅጠል ሸፈነ፡ እመሬት ቀበረ፡ በጫማው ጨቈነ፡ ደንጊያ

ብቅቡቅ (ትግ) እብቅ ገለባ (፪ነገ ፲፫ )

ብቅታ በሬ

ብቅታ ከፍታ መገለጫ መታያ ደፈር ኰረብታ ተራራ ገመገም የተረተር ግፍ ብቅታ፡ ብቅ ማለት

ብቅታ ደፈር በቀለ

ብቅት አለ ድክም አለ ተረፈቀ፡ በቤት ዋለ በድካምና በርጅና ምክንያት

ብቅት ዐቅም ማጣት

ብቅት የተበቀተ፡ ንዝንዝ

ብቅትየተበቀተ በቀተ

ብቡ የሳባ የፈራ የሠጋ የበረገገ፡ ፈሪ ሥጉ

ብብት ብብቻ፡ ሕፅን ውስጥ ከጣቶች አንዱ ቢቈስል መካከሉ የሚያብጥ (ዘፀ = ሰቈ ፲፪) (ተረት) የቈጡን ኣወርድ ብላ የብብቷን ጣለች

ብብቶች ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ

ብተት መባት (—ባተ)

ብተት መባት መግባት መሾም፡ ገባብ አሠለጣጠን የሌሊትና የቀን ቍጥር

ብተና ውርወራ ዝርዘራ ፍንጠቃ

ብቴ ብጫ የመሰለ የብጫ ዐይነት፡ ፊላ ፊላዊ በጨንን ተመልከት፡ ከዚህ የወጣ ነው

ብትበታ ቡጥቦጣ ብግበጋ ፍልፈላ

ብትቱ ዕላቂ ውዳቂ ዘባተሎ ጨርቅ በተበተን እይ፡ የዚህ ዘር ነው

ብትታ ብቻ መኾን መለየት ልዩነት

ብትን ሰዋስው ቦታ ጊዜ አካል ባሕርይ ስም ግብር ነገር

ብትን አለ ተበተነ

ብትን አደረገ በተነ

ብትን የተበተነ የደቀቀ ደቃቅ ደቄት

ብትን ድልኸ ስልቅ የድልኸ ቄት፡ የላመ በርበሬ

ብትንትኑ ወጣ ፈረሰ ተናደ ተመሳ ቀለ

ብትንትን አለ ተበተነ

ብትንትን አደረገ በተነ

ብትንትን የተበታተነ የተለያየ፡ ብዙ ስፍራ የተዘራ (ግጥም) እንትኑን ብትንትን አደረገው ብትንትን

ብትክ (ብቱክ) የተበተከ የተበጠሰ፡ ቋንዣው የደም ሥሩ መትኑ የታቈረጠ፡ አባላ የተመታ፡ ጥንብ ውዳቂ፡ ታንቆ የሞተ ከብት ማንኛውም እንስሳ

ብትክትክ አለ ብስክስክ አለ፡ ተበ ጣጣጠሰ ተበላሸ

ብትክትክ ዐይነ በጎና ሰፍነግ መሳይ ጤፍ እንጀራ

ብትክትክ የተበታተከ፡ ብጥስጥስ ርጥርጥ ብስክስክ

ብቸና ያገር ስም፡ በጐዣም ውስጥ ያለ አገር

ብቸኛ ባተሌ ባታይ፡ ባሕታዊ መናኝ

ብቻ (ባሕቱ) ዐቢይ አገባብ ቁሙ፡ እንጂ ግን አላቻ ጋብቻ፡ ቈይ ብቻ (፪ዜና ) አርባ ኹነኸ ና፡ ዐጪርና በራ ሰው አታምጣብኝ ብቻ

ብቻ (ባሕቲት) ቅጽልና በቂ እሱ ብቻ ! አንተ ብቻ ! ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ብቻ ሰው ብቻ አይዶለም፡ በተዋሕዶ (ባንድነት) አምላክና ሰው ነው እንጂ፡ ቅጽል ብቻውን የበላ ብቻውን ይሞታል፡ በቂ ንኡስ አገባብም ይኾናል (መዝ ) ብቻኸ ብቻቸው ብቻችኹ ብቻዋ ብቻሽ ብቻዬ ብቻችን እያለ እስከ ይዘረዝራል በደቂቅ መነሻነት ሲነገር

ብቻ ለብቻ አንድ ለአንድ ዳዊትና ጎልያድ እስክንድርና ፉዝ ብቻ ለብቻ ተገናኙ

ብቻነት ብቸኛ()ነት፡ ዝኒ ከማሁ፡ ባተሌነት ባሕታዊነት መናኝነት (መዝ ፳፪ )

ብኑን (ብህኑን) በካና

ብናኝ (ባህናን) የሥራይ ዶቄት ቅመም ትቢያ ዐቧራ ዐመድ

ብንታ ብን ማለት ነዘዘን እይ

ብንያም የሰው ስም፡ የነገደ እስራኤል መቍረጫ መጨረሻ ልጅ

ብከላ ለፋ የማሳደፍ ሥራ፡ መበከል፡ ማሳደፍ መኰለፍ ማበላሸት፡ ስም ማጥፋት

ብክላት ብከላ መበከል።

ብክል አለ ተበከለ

ብክል አደረገ በከለ

ብክል የተበከለ ያደፈ የጠፋ ጥፉ፡ አዳፋ አስቀያሚ

ብክት መብከት

ብክት አለ ፈጽሞ ራሰ በከተ ረሰረሰ

ብክነት ባካና መኾን፡ ጕድለት

ብክንክን አለ ተብከነከነ

ብክካ (ብሓ) እንደ ገል የሚሰ በር፡ እንደ ጓል የሚፈርስ ነጭና ቀይ ደንጊያ

ብው

ብው (በዊሕ) ማለት፡ መንደድ መቃጠል

ብው አለ (ቦሐ) ነደደ ተቃጠለ፡ ቋያው ጥሻው ችቦው ፋናው

ብዙ (ብዝኁ) ትእዛዝ አንቀጽ ብዙ ተባዙ፡ ምድርን ምሏት (ዘፍ ፳፰)

ብዙ (ዎች) (ብዙኅ) የበዛ የተረፈ የተትረፈረፈ፡ እጅግ ዐያሌ

ብዙ ነኽ፡ ብዙ ነሽ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም

ብዙ አንድነት ማኅበረ በኵር

ብዙኃን ማርያም ኦርዮስን ለማውገዝ ፫፻፲፰ ሊቃውንት በተሰበሰቡበት መስ ከረም ፳፩ ቀን በዓሏ የሚከብር የብዙዎች ማሪያም ማለት ነው

ብዙኃን ብዙዎች (ግእዝ) ብዙኃን ይመውኡ፡ (የግእዝ ተረት) ብዙዎች ያሸንፋሉ

ብዙነት ብዙ መኾን

ብዙዉን (መብዝኅቶ) እጅጉን ዐያሌውን፡ ብዙ ጊዜ

ብዝቅ መባዘቅ

ብዝቅ ባዜቃ የገባ የተነከረ፡ ዝብ ርቅ

ብዝቅ አለ ባዘቀ ተዘባረቀ

ብዝበዛ ዘረፋ ቅሚያ ብርበራ ብተና (፪ሳሙ ፲፪ ሕዝ ፴፰ ፲፪ ሚክ ዘካ ፲፬ )

ብዝብዝ አደረገ በዘበዘ

ብዝብዝ የተበዘበዘ የተዘረፈ የተቀማ የተበረበረ፡ ብርብር ብትን

ብዝት (ብዙት) የተባዘተ የተነቀሰ የተፍታታ ጥጥ የበግ ጠጕር

ብዝት አለ ድቅቅ ልትት አለ

ብዥ ብዛት (ብዝኅ ብዝኀት) መብዛት ብዙነት፡ ላቂያ ብል (ማቴ ፲፯)

ብዥብዥ አለ (ቤዘ) ጥቂት ጥቂት ታየ

ብየና (ብያኔ) ዕውቀት ፍርድ ፈሊጥ ሥርዐት

ብየኛ (ኞች) ካሳ የተቀበለ የወሰደ የበላ

ብየዳ ድለዛ መረጋ ደፈና

ብያ (ኦሮ ብዬ) አገር፡ ዐፈር አባ ብያ እንዲሉ

ብይ (ዮች) የደንጊያ የብርጭቆ ጠጠር፡ ልጆች እየወረወሩና እያጋጩ የሚወቱበት

ብይ ካሳ ኣፈ ላማ

ብይ ጠጠር፡በላ

ብይን ፍርድ ፍት (ጥሬ)

ብይን (ብዩን) የተበየነ የተፈረደ

ብይዳት ብየዳ የመበየድ ሥራ

ብይድ የተበየደ የተደለዘ፡ ድልዝ ግብዝ

ብደራ (ልቃሔ) የብድር ስጦታ

ብድል የተበደለ የተገፋ

ብድራም የብድር ጐሬ፡ ዕዳ ብቻ ብድር መለሰ፡ ዕዳን ወይም ደምን ከፈለ

ብድራት ለሠሪው የሚመለስ የፍዳ የበቀል ሥራ፡ ዕዳ ቂም ደም (ኢሳ ፴፬ ፴፭ ዐብድ ፲፭ ሉቃ ፲፬ ፲፪ ቈላ ፳፭)

ብድር (ሮች) (ብዱር) ካበዳሪ እጅ ለተበዳሪ ያለፈ ያራጣ የልቆ የወለድ ገንዘብ በምድር አይቀር ብድር እንዲሉ

ብድግ አለ (ተበደገ) አፈፍ አለ ተነሣ ቆመ

ብድግ አደረገ (በደገ) አነሣ አቆመ

ብድግ ያኸል ትልቅ አንዳች አን ድስን እይ

ብጀታ መበጀት፡ ውበት

ብገራ ሙከራ ፍተና ምጠና፡ የመበገር ሥራ

ብገናም ጨብጣም ዕብጠታም ግምላም ጠባሳም

ብገን (ትግ ሐባ ጨብጥ) የቈረሰጪ ቍርብጭ፡ ጅግል ግምል

ብገን የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ድረቅ፡ ክረር

ብጕራም በፊቱ ላይ ብጕር ያለበት የበዛበት

ብጕር ብግር፡ በጕልማሳና ባፍለኛ ፊት ላይ የሚወጣ ያፍላ ምልክት፡ የደም አበባ ፊትን የሚበግር (ዘሌ ፲፬ ፲፯)

ብጕንጅ (ጆች) በብጕርና በዕባጭ መካከል ያለ የበገነ የከረረ ትኵሳታም ዕብጠት ብጕንጅ ኹለት ዐይነት ነው፡ ትልቅና ትንሽ ትንሹ ያይጥ ብጕንጅ ይባላል

ብግበጋ ገረፋ ትኰሳ

ብግብግ የተበገበገ፡ ግርፍ

ብግነት ድርቀት፡ ቍርብጭታ

ብግን አለ ፈጽሞ ገመነ ዐረረ

ብግን የበገነ የደረቀ የከረረ የገመነ ያረረ

ብጠሳ ቈረጣ የመበጠስ ሥራ

ብጠራ ልየታ ምየዳ

ብጡል (ዐረ በጥለ ጐበዘ) ዠግና ሐርበኛ ኀይለኛ ብርቱ ይኸውም ሊታወቅ የይተጌ ጣይቱ አባት ደጃች ብጡል ባንድ ጦር ኹለት ሰው ደርበው ወግተው ገድለዋል ይባላል ዳግመኛም

ብጡል ቅምጥል ድልድል ሥራ ፈት ተብሎ ይተረጐማል

ብጡል የበጠለ የባጠለ የጠፋ ጥፉ መጥፎ ብልሹ ከንቱ፡ ፲፭፻ ዘመነ አበው የሚያጐድል ኦሪተ አይሁድ

ብጣሪ ንፋሽ ዐሠር ገለባ እንችፍ

ብጣሻም የብጣሽ ዐይነት ወገን ብጣሽ ያለው ባለብጣሽ

ብጣሽ ታናሽ ቍራጭ

ብጤት ዐመል ሥረት ምርጫ ሐሳብ ሰው እንደ ብጤቱ ይኖራል

ብጥ (ብጡሕ) የተሰጣ የተቈራ የተጋረጠ፡ ትፍትፍ ሥንትር

ብጥሌ የብጥል ታናሽ ዕንጐቻ (ኦሮ) ዳደደ

ብጥል ዕላቂ ብማቂ ብጣሽ

ብጥልጣይ (በጸላዊ) የብጥልጥል ወገን ዐይነት

ብጥልጥል (ብጻል) ብትንትን ጭቅጭቅ ሥንጥቅጥቅ

ብጥልጥል አለ ተብጠለጠለ፡ ብትንትን አለ

ብጥስ አለ ተበጠሰ፡ ጕምድ ቍርጥ

ብጥስ አደረገ በጠሰ

ብጥስጣሽ ቍርጥራጭ

ብጥስጥስ በብዙ ወገን የተበጠሰ የተቈራረጠ

ብጥስጥስ አለ ቍርጥርጥ ብስክስክ አለ

ብጥስጥስ አደረገ በጣጠሰ (፩ሳሙ ፲፩ )

ብጥረቃ ሽንቈራ፡ የመብሳት ሥራ

ብጥራት የማበጠር የማንፈስ የማጐ ተን ሥራ

ብጥር አለ ተበጠረ

ብጥር አደረገ አበጠረ

ብጥር የተበጠረ የተነፈሰ የጠራ፡ ጥሩ

ብጥርቅ አለ ተበጠረቀ፡ ንድል ብስት አለ

ብጥርቅ የተበጠረቀ፡ ብስ ሽንቍር

ብጥበጣ ጠመቃ ብረዛ፡ ሁከት

ብጥብጥ ንዝንዝ ጭቅጭቅ ሁከት ሽብር ጦርነት ግርግር

ብጥብጥ አደረገ አካቶ ፈጽሞ በጠበጠ፡ አገርን ፍቅርን አንድነትን አጠፋ

ብጥብጥ የተበጠበጠ የታሸ የማር ብጥብጥ፡ የተልባ ድርጥ እንዲሉ

ብጥታት (ብጥሐት) ብጥነት፡ ፍቅታት ቍርታት ትፍትፋት

ብጥንቅር የማይፈለግ ነገር

ብጨቃ ብጠሳ

ብጫ (ጮች) (ብጻ) በቁሙ፡ ከጥቍር ካረንጓዴ የተለየ ዐይን አበባ ሱፋላ በወይባና በነጭ መካከል ያለ ቀለም መልክ ዐደይን ተመልከት

ብጫ ቅጽል ወይም ዘርፍ ሲኾን

ብጫ ጥለት ብጫ የኾነ የብጫ ጥለት

ብጫቂ ብጭቅ (ብቱክ) የተበ ጨቀ የተቈረጠ፡ ብጣሽ

ብጭርቅርቅ አለ ሳያምር ቀረ፡(ጨበረቀ)

ብጭቅ አለ ተበወቀ ተባቀ ተባጠሰ

ብጭቅጫቂ ዝኒ ከማሁ፡ የተበታተከ የተበሳሰከ

ብጭቅጭቅ ብጥስጥስ ቍርጥርጥ

ብጭቅጭቅ አለ ብጥስጥስ ብትንትን ኣለ

ብጭጭ አለ ዝኒ ከማሁ

ብጹዕ (በፂዕ በፅዐ) ክቡር ምስጉን ምሩቅ ቡሩክ ጻድቅ ቸር የእግዚአብሔር ሰው በክቡርና በቅዱስ መካከል ላለ ይነገራል

ብጹዕ ክቡር፡ ብፁዕ

ቦለ ቦረቦጭ ሰበረ፡ ስለት አወጣ

ቦለለ ሰፋ ሰፊ ኾነ፡ የሱሪ ወለለን እይ ተትጐለጐለ ቦነነ፡ የጪስ ቡላንን ተመልከት፡ የዚህ ዘር ነው

ቦለቀ ፈለቀ ወጣ ቦጠለቀንን እይ

ቦለቲከኛ ዘዴኛ ባለፈሊጥ፡ ዐዋቂ በነገር ተራቃቂ

ቦለቲክ (ፖለቲክ) የነገር ዘዴ፡ ውስጠ ተንኰል ፈሊጥ ቦለቲክ በግእዝ ጕሕሉት ኂጣን ሚን ይባላል፡ (ላዩ ዳባ ውስጡ ደባ) ድለላ ሽንገላ ማለት ነው

ቦለደ ለየ ከፈለ አራቀ፡ አስገለለ

ቦለደ መታ አጋጩ ኣፋል፡ በብረት ከባልጩት እሳት አወጣ በለጨ ብለኸ ኣበለጩን እይ

ቦለዴ ከጅር የተለየ፡ ከገመር የሸፈተ ዝንጀሮ፡ ቦለዳዊ፡ የቦለድ

ቦለድ (ዶች) የመጥረቢያና የምሣር መካከለኛ፡ መፍለጫ መሠንጠቂያ ማጤ

ቦለድ ከሰው የተለየ ሽፍታ ወያኔ

ቦላላ ሰፊ ሱሪ፡ ተነፋነፍ

ቦላሌ ስፋት ሰፊነት ያለው፡ የቦላላ ዐይነት

ቦልካን ከምድር ፈንድቶ የሚወጣ እሳተ ገሞራ ቦልካን የፈረንጅ ቋንቋ ነው ቦለቀንን ተመልከት

ቦምባ የብረት አሸንዳ ውሃ የሚወርድበት፡ ውስጠ ክፍት ብረት ባገራችን አሸንዳ የሚኾኑ ቊልቋልና ቀርክሓ ናቸው

ቦምባይ የህንድ አገርና ከተማ

ቦምብ ፈረንጆች በመብረቅ ምሳሌ የሠሩት ቍልቍል ወይም አግድም ሲወረውሩት ፈንድቶ ቤት የሚያፈርስ የሚያቃጥል፡ ሰው የሚገድል፡ ሲጮኸ ብም የሚል፡ ክብ ሞላላ የአይሮፕላን መርግ በንቍላል አምሳል የተሠራ ሾጠጥ ያለ ባለከምሱር፡ ውስጡ ባሩድ የተመላ የብረት ማሰሮ ነው

ቦስጣ ፖስታ፡ ደብዳቤ

ቦረቀ (በጠሰ)

ቦረቀ (ቦቀረ) ጮቤ መታ ዘለለ ፈነወ ወረቀን እይ

ቦረቀ ዐልፎ ዐልፎ ዐወደ ሠራ፡ ወረበ ቦረቀና ቦቀረ ከፊደል መዛወር በቀር የምስጢር ልዩነት የለውም ቦረቀ የሣር፡ ቦቀረ የጠጕር ነው

ቦረቀቅ ቦርቃቃ የሰፋ ሰፊ፡ ቦላሌ ሱሪ

ቦረቦረ (በረበረ) ጐረጐረ ፈለፈለ ባዶ አደረገ፡ አገራ ሞረሞረንና ቦጠቦጠን ሸረሸረን እይ

ቦረቦር ቀይ ዐፈር ፈርካሳ ውስጡ የሚቦረቦር

ቦረቦጭ (ጮች) በያይነቱ ቀለም ያለው ድንጋይ ብርጭቆ መሳይ

ቦረቸ ተንፍቀቀ፡ በንፉቅቅ ኼደ

ቦረና የቦረን አገርና ነገድ፡ በሲዳሞ ክፍል ያለ

ቦረን (ኦሮ) የኦሮ ኹለተኛ ነገድ በሬንቱማን የመሰለ

ቦረንትቻ በግንቦት መባቻ ዠምሮ የሚደረግ የቦረን አምልኮ፡ አምልኮውም በበረት በግ ማረድ፡ ጌሾ ያልገባበት ጕሽ መጠ ጣት፡ በያይነቱ ቈሎ መብላት፡ ከሥጋው ብልት ኹሉ ቀንጥቦ ፈርስና ርሚጦ ጨምሮ በበረቱ ፉካ ማኖር ነው (ተረፈ ዳን ፲፫ ፲፯) ነበየ ብለኽ ፪ኛውን የነቢ ቂጣን እይ

ቦሩ (ቡሬ) የበሬ ስምና መጠሪያ

ቦራ (ኦሮ) ብጫነት ያለው ፈረስ

ቦራ በሬ (ጕራጌና ወላሞ)

ቦራሌ ብርሌ የሚመስል ነጭ ቦረ

ቦራቂ (ዎች) የቦረቀ የሚቦርቅ የሚዘል፡ ዘላይ

ቦራቂ ዐጫጅ ወራቢ

ቦሬ ዝኒ ከማሁ፡ ነገረ ግልጥ ፎለፎል

ቦሬሳ ያጤ ዮሐንስ የስም ቅጽል፡ ወይም ፉከራ ድንፋታ፡ ወሪሳ ቦሬሳው ካሳ ይዋጋል ከቱርክ እንኳን ካንካሳ

ቦርማ የቦራ ዐይነት በሬ፡ ፊተ ነጭ፡ ቦራን የሚመስል

ቦርሳ የገንዘብና የወረቀት መያዣ የዕቃ መክተቻ ኰረጆ ማፉዳ ቦርሳ ጣሊያንኛ ነው

ቦርቅ የሚዘል ውሃ፡ ቦቅ

ቦርቦር አለ በገርነት በየዋህነት ተናገረ፡ ከተንኰል ባዶ ኾነ

ቦርቦርቲ (ጌራ) የብረት ቆብ፡ የራስ ቍር

ቦርቧራ ገር የዋህ ተንኰል የሌለው ሰው

ቦርደዴ በሐረርጌ አውራጃ ከዐዋሽ ቀጥሎ የሚገኝ ቀበሌ በረሓ ምድረ በዳ

ቦርጫም (ሞች) ቈለፈታም ዘርጣጣ ወፍራም፡ ዶሮ የበላች ፯ኛ ዶሮ በሌ

ቦርጭ ቈለፈት ቀፈት የበዠድ ግድ ቦርጭ የበለጠና የፈለጠ ዘር ነው

ቦሸሽ የሸሸ የጠፋ የታጣ ኮከብ አስታር ቦሸሽ እንዲሉ

ቦቀረ (ዕብ ባቃር መረመረ ፈተነ) ቍንጮ ያን አሻራን በጥቂቱ ላል ሳዱላ አወጣ

ቦቀቦቅ ቦቅቧቃ የተንቦቀቦቀ የሚ ንቦቀቦቅ፡ የፈሰሰ የወረደ፡ ፈሪ ጡርቂ

ቦቂት የዱሮ ነፍጥ ባለ ናስ ማሰር፡ ቦቂት ያሠኛት ናሱ ነው

ቦቂትጠመንዣ ቦቃ

ቦቃ (ኦሮ) ግንባረ ነጭ በሬ ወይም ላም ጨረቃ ጭንብር ቦቃ፡ ዐጤ ቤት ገባች ዐውቃ እንዲሉ ልጆች

ቦቃሪ የቦቀረ የሚቦቅር የሚላጭ፡ ጨት

ቦቅ ኀይለኛ ዝናም፡ ቤት የሚነድል የሚያፈርስ ፈሰስ

ቦቅ ፈሰስ፡ (ቦቀቦቀ)

ቦቅማ የቦቃ ዐይነት፡ የቦቃ ወገን

ቦተረፈ (ተረፈ) ነከሰ፡ አብዝቶ ቦጨቀ፡ ቂጥን ንን ባትን ቦቆ ወሰደ

ቦታ

ቦታ (ዎች) (ዐጸድ መካን) ስፍራ ሰፈር ማደሪያ መኖሪያ፡ ቤት ዐጥር ቅጥር ያለውና የሌለው ወጀድ (በኣት) ቤትና ቦታ አንድ ዘር ናቸው

ቦነቸ ቦከቦከ በሰበሰ

ቦነነ በቁሙ፡ በነነ

ቦና ኦሮ በጋ ድርቅ የቦና ጥጃ እንዲሉ

ቦከቦከ (በኍበኈ) ወፈረ ደነደነ ሠባ ቦነቸ በሰበሰ፡ ሸተተ

ቦኸየ (ቦሐ በርሐ) በራ ተገለጠ፡ በራ ኾነ ተመለጠ፡ ነጣ

ቦዘ (ዕብ ባዝ) ተናቀ ተሰደበ ተዋረደ፡ ደከመ ፈዘዘ ዘነጋ፡ ያይን የልብ

ቦዘነ (ባዘነ) ታከተ ደከመ ተኛ ተጋደመ ሰነፈ ዐረፈ፡ ተዘለነ ተዘለለ ዞላ ዋለ ቀረ ታጐለ ቆመ፡ ሥራው

ቦዘና ሹሮ ክትፎ ያለበት ሹሮ ወጥ

ቦዘኔ የቦዘን ቦዘናዊ ቦዘን ወዳድ ምን ያመጣል ሠኔ፡ ምን ይሠራል ቦዘኔ እንዲሉ

ቦዘን ሀኬት ስንፍና ዞላ

ቦዘንተኛ (ኞች) ሀኬተኛ ሰነፍ ሥራ ፈት

ቦዘንተኛነት ሀኬተኛነት ዞላነት

ቦዛኝ (ኞች) የሚቦዝን የሚሰንፍ

ቦዝ (ዕብ ቡዝ) ፈዛዛ ዝንጉ፡ የተናቀ የተዋረደ

ቦዝ አንቀጽ ገቢር ከመሳብ በቀር አንቀጽ የማያስቀርና የማያስር ደካማ አንቀጽ ዐስቦ ዐውቆ ገድሎ የመሰለው ኹሉ። ኖሮ ኖሮ ከሞት ዞሮ ዞሮ ከቤት እንዲሉ ገቢር መሳቡም አንቀጹ ገቢር ሲኾን ነው

ቦዝ ኹለት የበገና ዥማት በድምፅ ከሊቃውንትና ከአማሪት የሚያንስ

ቦየ ተማሰ ተቈፈረ ተገመሰ

ቦይ (ዮች) የክረምትና የበጋ ውሃ መኼጃ መውረጃ፡ በርሻና በሜዳ መካከል የተማሰ የተገመሰ መስኖ ቦይ ለውሃ፡ ጐመን ለድኻ እንዲሉ በእንግሊዝ ቋንቋ ግን ልጅ ማለት ነው

ቦደሰ (በጠሰ) ገመሰ ጐመደ፡ የመሬት የወፍራም ገመድ የአካል

ቦደነ ልብስን ከቀኝ ብብት በታች አደረገ፡ ቀኝ እጁን አወጣ

ቦደነ በመቅን ወረሰ ተለመ፡ የድንበርንና የወሰንን አጠገብ

ቦደነ ጠመረ ገጠመ፡ ዐንገት ያዘ

ቦዳ ጭንጫ ግርግራ የሌለበት ወፍራም መሬት፡ ቀልዝ

ቦዳሳ ገማሳ በጣሳ

ቦዳሽ የቦደሰ የሚቦድስ፡ ጐማጅ

ቦዳኝ የቦደነ የሚቦድን፡ ገጣሚ ላሚ

ቦድስ ጥቍር ውዥግራ

ቦጋለ (ቦግ አለ) ፈጥኖ በኀይል በራ፡ አለ፡ በረቀ
ቦጋለ ቦጋለች የወንድና የሴት ስም፡ ዐይናሞች መኾናቸውን ያሳያል ቦግ ቦግ አለ፡ ተግ ተግ አለ፡ ተንቦገቦገ
ቦግ መብራት መዝለል
ቦግታ ብልጭታ፡ ነጸብራቅ፡ የመብረቅ ብርሃን
ቦጠለቀ (ቦለቀ) ከፈለ ሠነጠቀ፡ በኀይል አወጣ፡ የነገር ያክታ
ቦጠቦጠ በተበተ ቦረቦረ ጐረጐረ ጐጠጐጠ፡ ውስጥ ውስጡን ልብ ልቡን በላ ተመገበ
ቦጥቧጭ የሚቦጠቡጥ የሚቦረቡር፡ ጐርጓሪ
ቦጨረቀ (ጨረቀ) ረገጠ መታ ውሃን
ቦጨረቅ ቦጭራቃ የሚረግጥ የሚ መታ
ቦጨቀ (በጨቀ) ባዘተ፡ ዐደ ቈረጠ፡ ደም እስኪወጣ ዐከከ፡ የዳመጦ የሣር የገላ ያንገትጌ
ቦጨቀ በላ ነከሰ ቀደደ፡ የሰውን ሥጋ ወሰደ
ቦጨቀ ዐማ ስም አጠፋ
ቦጨቦጨ ተበጠበጠ ታወከ፡ ፍልቅ ፍልቅ አለ፡ ፈሰሰ
ቦጨቦጭ ደቃቅ አሸዋና ቦረቦጭ የብርሌ ዐይነት ደንጊያ በዶሮ መቋደሻ ውስጥ የሚገኝ
ቦጫቂ (በጫቂ) የቦጨቀ የሚቦጭቅ የሚያጭድ የሚባዝት
ቦጭረቅ ቦጭረቅ አለ ተንቦጫ ረቀ
ቦጭቦጭ አለ ዋለለ ጮኸ፡ የንስራ ውሃ
ቦፌ ዝናም የመታው ያበሰበሰው ዕንጨት፡ ውፍረትና ቅለት ያለው ልብስ
ቦፍ መውደቅ
ወራሽ ጯረ ቧወረ (በዊሕ) መብራት፡ 'ቦግ ማለት አለ (ቦሐ) በራ፡ 'ቦግ አለ
ቧሒት (ቡሓዊት እንተ ቡሕ) የተራራ ስም፡ በስሜን ወረዳ የሚገኝ ረዥም የቅዱስ ያሬድ ተራራ ዘወትር በላዬ ከሚታ የው በረዶና ጉም የተነሣ ሻሽ ጠምጣሚ ደብተራ ስለ መሰለ ቧሒት ተባለ ይላሉ ፈረንጆች ግን ራስ ዳሸን (ራስ ዘዐሸን) ይሉታል፡ የፈረንሳይኛ ዘርፍ አያያዥ ነውና፡ የበረዶ ዐሸን ራስ ማለት ነው ዳግመኛም በአረብኛ ደና ይወራረሳሉ፡ (ዳል ዛል)
ቧሒት ተራራ፡ቡሕ ቡሓ ቧሕ
ቧሔ በራሱ ላይ ነጭ ያለበት የኖኅ ቍራ ያሞራ ኹሉ ማእድ ባራኪ የቧሕ ቡሕማ የቡሕ ማለት ነው፡ ቧሔ ቅጽልና በቂ መኾኑን አስተውል
ቧሔ ነጭ ዐረግ፡ ያረግ ሬሳ፡ ዕፀ ሳቤቅ ቧሔ ዐረግ እንዲሉ
ቧሔ ከመንደርደሪያ ቀጥሎ ያለ የመወድስ ሐረግ ቤት መምቻ ያይዶለ
ቧሕ ቡሕ፡ ሦስተኛውን ቡሕ ተመልከት
ቧለተ ተፌዘ ተተረበ ተዘበተ ተቀለደ
ቧለው የሰው ስም፡ አለው ያለው፡ ዐይናማ ማለት ነው ደጃች ቧለው እንዲሉ ቡሕን ተመልከት
ቧለው የሰው ስም፡ቧ
ቧልተኛ (ኞች) ዋዘኛ ተረበኛ ቀልደኛ (ተረት) ስምኸ ማነው፡ ላገር አይመች፡ ማን አወጣልኸ ጎረባብቶች እናትኸ ማነች፡ ሳልወለድ ሞተች
ቧልተኛነት ዋዘኛነት ቀልደኛነት
ቧልት ፌዝ ከቁም ነገር የተለየ፡ ዘበት ተረብ ዋዛ ፈዛዛ ቀልድ
ቧምቧ በቁሙ ቦምባ
ቧሪ (ዎች) የቧጨረ የሚቧጭር የሚጭር፡ ጫሪ ጫሪ
ቧሸሸ (ሸሸ) ሸሸ ጠፋ ታጣ ዕልም አለ
ቧቀሰ (ዕብ ባቃሽ ፈለገ) ደከመ ሰለተ ጠወለገ
ቧንግዝ ፋደት (ጐዣም)
ቧገተ (ወገተ) በቁሙ፡ ዞረ ተንከራተተ፡ ለመነ ቀለተ
ቧገታ ቀለታ ልመና
ቧጋች (ቾች) የቧገተ የሚቧግት የሚዞር የሚቀልት፡ ቀላች ለማኝ
ቧጠጠ ጠጠ፡ ጨረ፡ ጠረገ ገላን ጭቃን ዐዛባን ጕረሮን
ቧጣጭ የቧጠጠ የሚቧጥጥ የሚጥጥ፡ ጠራጊ ማሪ ነብር ወጌሻ ረግ
ቧጨረ ጨረ ማረ፡ ሰነዘረ ዐከከ

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ