ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ዐ፡ የሐኀ ወራሽ (ወራሽነቱንም ወደ ፊት ይመለከቷል - "ኣን" እይ) ።
ዐለለ (ዐልሎ ዐለለ/ሤረየ)፡ የስፌት ሣርን ፈትልን በያይነቱ ቀለም ነከረ አገባ ("(በደም ዐለለ)" - እደም ውስጥ ዘፈቀ ለወሰ ልብስን ገላን ") ።
ዐለላ (ዎች)፡ ቀለም የገባ ስንደዶ አክርማ ።
ዐለላ ሙዳይ፡ ዐለላ ዘርፍ (ሙዳይ ባለቤት ነው - ባለላ የተሰፋ ሙዳይ ") ።
ዐለመ (ሐለመ)፡ ዕልም አየ ።
ዐለመ (ሐለመ)፡ ዕልም አየ ።
ዐለመ (ዐልሞ ዐለመ)፡ አመለከተ (ምልክት ሰጠ - ሦስተኛውን "ዐለበ" ተመልከት ") ።
ዐለመ፡ አጠፋ አወደመ ።
ዐለቀ (ኀልቀ)፡ ተጨረሰ ተፈጸመ ተደመደመ ተቈረጠ፡ ሞተ ሽቅ አለ ተጠነገደ ("ውሃ ቢደርቅ ዓሣ ያልቅ" እንዲሉ - "(በውሃ ይለቅልሽ)" - ዐዲስ ልብስ የለበሰውን ሰው እንዲህ ይሉታል - ውሃ ዕጥበትን ያሳያል - በ፰ኛው ሺ ሰው ኹሉ ያልቅና ምድር ባዶ ስትኾን ምነው ይኸ ዛፍ ሰው በኾነ የሚባል በት ጊዜ ይመጣል ይላሉ ") ።
ዐለበ (ትግ)፡ ለበሰ ታጠቀ ።
ዐለበ (ዐለመ አመረ)፡ ምልክት ' አደረገ (ጥይት አጐረሠ አነጣጠረ አዘገበ ደከረ ") ።
ዐለበ፡ ላምና ጥጃን አገናኘ "
ዐለት (ዐራት)፡ ዐልጋ ("(መንበር)") ።
ዐለት፡ የወንዝ ደንጊያ አ ለት ።
ዐለንጋ (ጎች)፡ ጕማሬ አኰርባጅ መ ግረፊያ መሸንቈ ("(ምሳ. ፲፥፲፫)") ። በአንቆቅል ሽም "ዐልቅት ዐለንጋ" ይባላል ። "ትንሽ ዐለ ንጋ ወንዝ ለወንዝ ትላጋ" ። ("የምድር 'ዐለንጋ)" ቱልት ።
ዐለንጋ ቍልፍ)፡ ፵ፍና ፉ ብስ ኾኖ በጠፍር (ዐለንጋ) የሚዘጋ ቅርቃር ።
ዐለያ (ኀለየ)፡ ዐሳቢ ።
ዐለያ ነሽ፡ የሴት ስም ("ዐሳቢ ነሽ" - ዳግመኛም በዐሊ አንጻር ዐለያን ልዕልት ብሎ መተርጐም ይቻላል ") ።
ዐለጠ (ሐለጸ/ዐረ/ኸለጸ/ቀላ ቀለ)፡ ዐልጫ ኾነ (ጣም ዐጣ ወጡ ") ።
ዐለፈ (ኀለፈ)፡ ኼደ ተራመደ ተሻ ገረ ዘለለ ("(፩ሳሙ. ፱፥፳፯)") ። "ለፋ" ብለኸ "ኣለ ፋን" እይ ("(ሰዓቱ ዐለፈ)"፲፮ የነበረው ፯ ኾነ ") ።
ዐለፈ፡ ለሰጠው ላደረገው ኣለኹ አለ
ዐለፈ፡ ሞተ ጠፋ ("ነፍሱ ወደ ሰማይ ሥጋው ወደ መቃብር ወጣ ወረደ - እከሌ በጁ ነፍስ ስላለፈበት አገሩን ለቀቀ ") ።
ዐለፈ፡ ተረፈ መጣ ("ያን ለት ገንዘብ ስንካፈል ያንተ ወደኔ ዐልፋልና እመልስልኻ ለኹ ") ።
ዐለፈ፡ ተሻረ ቀረ ተተወ ("(ጕልበት ዐለፈበት)" - የሥራ ዋጋ ጨርሶ አልተቀበለም - ቀርቶበታል ") ።
ዐለፈ፡ ተነሣ ተወሰደ ("(ዳን. ፬፥፴፩)") ።
ዐለፈ፡ ደፈረ (ትርፍ ነገር ተናገረ - "ዐለ ፍከኝ" እንዲል ተማጋች ") ።
ዐለፈ፡ ገፋ ("ወሰንን ዐለፈ" እንዲሉ) ።
ዐለፈ፡ ጥሩ ኾነ አማረ ።
ዐለፈለት፡ አገኘ ተረፈው (ችግር ለቀ ቀው - እንጀራ ጠገበ ") ።
ዐለፈበት፡ ዐጣ ነጣ ደኸየ ተቸገረ ።
ዐለፋ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ።
ዐለፋ፡ ፍድፋጅ ።
ዐለፌታ፡ ትርፍ ነገር
ዐለፍ፡ ዝኒ ከማሁ ለዐላፊ (የዘለለ - "ይህ ተክል ስለ በዛ አንድ ዐለፍ ንቀለው ") ።
ዐለፍከኝ፡ ዘለልከኝ ተውከኝ ደፈር ከኝ ሰደብከኝ ("ኣንቱ ብለኸ አንተ አልከኝ ") ።
ዐሊ (ዐረ)፡ ልዑል (ከፍ ያለ ") ።
ዐሊብ (ሐሊብ)፡ ማለብ ("(ኣርእስት)") ።
ዐሊብ (ሐሊብ)፡ ትኵስ ወተት (የበ ሰለ ደም ነጭ የሥጋ ፈሳሽ - የሕፃን የግል ገል የጥጃ የውርንጭላ የቡችላ ምግብ - ጥሬ ዘር ") ።
ዐሊብ (ሐይብ)፡ ዐይብ ("(ተረት)" - ላም አለኝ በሰማይ ወተትም አልጠጣ ዐሊቡ ንም አላይ - የና ለ ይዋረሳሉና ዐይብ ዐሊብ ተባለ - "ዐየበን" ተመልከት ") ።
ዐላሚ (ዎች)፡ ያለመ/የሚያልም (ባለ
ዐላሚ (ዎች)፡ ያለመ/የሚያልም (ባለ
ዐላማ (ዎች/መጠራ)፡ ብራኳ ጊጤ (በጥይት የሚመቱት በሹል ዕንጨት ") ።
አላማ፡ አያያዘ፡ አጋጠመ፡ (በመላሚያ፡ አሰረ፡ ጠገነ) ።
ዐላማ፡ የዓለም መንግሥታት ኹሉ የነጻነትና የሃይማኖት ምልክት (ባንዲራ በያይ ነቱ ቀለም ያለውና የሌለው የሐር ልብስ ክፍል የቀስተ ደመና ምሳሌ - ዘፀ. ፲፯፥፲፭፡ ዘኍ. ፪፥፫፡ ኤር. ፶፩፥፲፪ - ይኸውም በሰንደቅ ላይ የሚሰቀል የሚንጠለጠል ነው - "ሰንደቅ ዐላማ" እንዲሉ) ።
ዐላማ፡ ድምር (ርጥብ የደመራ ዕንጨት ነበልባል ባለው ችቦ የሚወጋ ") ።
ዐላቂ፡ የሚያልቅ/የሚጨረስ (ጥናት ጥንካሬ የሌለው ") ።
ዐላቢ (ዐላሚ)፡ ያለበ ("(ጥል)" የሚያ ልብ - አነጣጣሪ ") ።
ዐላቢ (ዎች/ሐላቢ)፡ ያለበ/የሚያ ልብ ("ላም ዐላቢ" እንዲሉ) ።
ዐላባ፡ ነጭ ማዕድን (ማንኛውም ምድር የምትሰጠው ውጤት ") ።
ዐላባ፡ እኸል በያይነቱ ("ዐላባ ገለባ" እንዲሉ) ።
ዐላባ፡ ከጕራጌ ነገድ አንዱ ።
ዐላባ፡ የምድር ፍሬ (ወተት የሚመ ስል ጠመቅ ") ።
ዐላይ (ዮች)፡ ያለለ/የሚያልል (ቀ ለም ኣግቢ ") ።
ዐላፊ (ዎች/ኀላፊ)፡ ያለፈ/የሚያልፍ (በቀጥታ ኻያጅ - "ዐላፊ አግዳሚ ዐላፊ ጠፊ" እንዲሉ - "ነገረ" ብለኸ "ነገርን" ተመልከት ") ።
ዐላፊ፡ ዋቢ ዘበኛ ።
ዐላፊነት፡ ዐላፊ መኾን (ዋቢነት ተያ
ዐላፎች፡ ዐላፊዎች ኻያጆች ("(ኢሳ. ፶፩፥፳፫)") ።
ዐሌ (ዐለየ)፡ ዝኒ ከማሁ ለዐሎ "
ዐሌ አለ፡ አስተባበለ ("የለም አይዶ ለም አለ" -
"ሸፈጠን ካደን" እይ ") ።
ዐል፡ በርበሬ ያልገባበት የሹሮ የስጋ ወጥ ።
ዐልቅታም፡ ዐልቅት ያለበት የበዛበት ምንጭ ዦር ።
ዐልቅት (ቶች/ዐለቅት)፡ ከረጢ ትነት ያለው የውሃ ውስጥ ተንቀሳቃሽ ("(ኢሳ. ፴፬፥፳፫)") ። በበሬ ጕረሮ ተለጥፎ ደም እየ ጠጣ ያድጋል ("(ተረት)" - ዐልቅትና ድኻ ውሃ ለውሃ ") ።
ዐልባ (ትግ/ዐለባ/ልብስ)፡ ዝምዝ ማትና ጥልፍ ያለው ጌጠኛ የሴቶች ሱሪ ("ል ብን" እይ ") ።
ዐልቦ መጋት፡ ርባና ቢስ ሥራ
ዐልቦ ማለት የወርቁንና የብሩን መቅለጥና መፍሰስ ያሳያል ("(የበቅሎ ዐልቦ)" - ወርቅ ቅብ የብር ዶቃ በበቅሎ ዐንገት የሚ ጠለቅ - "አልባን አልቦን" አስተውል ") ።
ዐልቦ፡ ከወርቅና ከብር በዶቃ አም ሳል የተሠራ የሴቶች እግር ጌጥ ("(ኢሳ. ፫፥፲፰)") ።
ዐልቦ፡ ጡትን ስቦ ጐትቶ ወተትን ኦ ።
ዐልቴት፡ የዛፍ ሙጫ—አል ቴት ።
ዐልጋ (ዐለገ)፡ አራት እግር ኹለት ዘንግ ኹለት ደንብ ያለው (መካከሉ በጠፍር የተታታ መኝታ - ረዥሙ ዙፋን ዐጪሩ ድ ንክ ይባላል - ሲበዛ "ዐልጋዎች" ያሠኛል - "(ጐ በዝ ዐልጋ)" - መካከለኛ - "(የብረት ዐልጋ)" - ከብረት ብቻ የተሠራ በሽቦ የተታታ - "(የወርቅ ዐልጋ)" - ከወርቅ የተበጀ የተዘጋጀ ") ።
ዐልጋ ነቀነቀ፡ ከዳ ሸፈተ ።
ዐልጋ ወራሽ፡ ያባቱን ዙፋን የሚወ ርስ (የንጉሥ ልጅ ") ።
ዐልጋ፡ የጣራ መሥሪያ (ረዥምና ሰፊ ቈጥ ") ።
ዐልጋ፡ ያንድ ንጉሥ ግዛት (መንበረ መንግሥት - "ባልጋ በመንግሥት" እንዲሉ) ።
ዐልጫ መረቅ፡ የመረቅ ዐልጫ (ወ ይም ያልጫ መረቅ - በቅቤና በጨው በቃ ሪያ በርበሬ በነጭ ሽንኵርት የተቀቀለ የሥብ መረቅ - ጤፍ እንጀራ እየፈተፈቱ ይበ ሉበታል ") ።
ዐልጫነት፡ ዐልጫ መኾን ("(ነገሩ ዐ ል ኾነ)" - ከማይረባ ተቈጠረ - ሳይዝ ቀረ ") ።
ዐልፎ፡ ቀርቶ ተትቶ ።
ዐልፎ፡ ተራምዶ ዘሎ ("ዐልፎ ካያጅ" እንዲሉ) ።
ዐልፎ ዐልፎ መጣ፡ አንዳንድ ጊዜ እያሠለሰ ።
ዐሎ (ዐለወ)፡ ሐሰት ክሕደት ("ዐሎ ብሎ የተረታ መኻል አገዳውን የተመታ" እን ዲሉ - "አልን" ተመልከት ") ።
ዐሎ፡ ብድራት በቀል ።
ዐሎ አለ፡ ካደ (አላመነም አልተቀ በለም ") ።
ዐሎኛ፡ ከዳተኛ ሸፍጠኛ ፥ ተቃራኒ ።
ዐሎውን ከፈለ፡ ብድሩን መለሰ (አ ጥቂውን አጠቃ ") ።
ዐመለ (ሐመለ)፡ ለመለመ (ወየበ ደነ በሸ ከቅዝቃዜ የተነሣ ") ።
ዐመለ ልስልስ፡ ደግ ሰው (ደንሴ አይቈረቍሬ አያስቀይሜ ") ።
ዐመለ ቢስ፡ ዐመለ ክፉ ።
ዐመለ ናጫ፡ ጨቅጫቃ ሰው ።
ዐመለ ወርቅ፡ የሴት ስም ።
ዐመለ ጌታ፡ በውርደት ቦታ የማይ ገኝ ሰው ።
ዐመለኛ (ኞች)፡ ልማደኛ ሠሠኛ (መጥፎ ዐመል ያለው ሰው ") ።
ዐመል (ሐመል)፡ የኮከብ ስም (የበግ አውራ የሚመስል የመጋቢት ኮከብ ") ።
ዐመል (ዐረ/ሥራ)፡ ልማድ ሐራራ ሡሥ (በሥራ የሚገለጥ ክፉና ደግ ጠባይ - "(ተረት)" - ዐመልኽን በጕያሽ ሥንቅሽን ባህ ያኸ - "ዐመል ያወጣል ከመኻል ዐመል ያገ ባል እመኻል - ሞት ላይቀር ፍራት ዐመል ላይቀር ቅጣት ") ። "መለመለ" ብለሽ "አመለመለን" እይ ።
ዐመል፡ አኳዃን ኹኔታ ("ጐባጣን እን ዴት ይቀብሩ ቢሉ እንዳመሉ ") ።
ዐመል አወጣ፡ ጠባዩን አካኼዱን ለ ወጠ (ከፋ ክፉ ኾነ ") ።
ዐመል እሳት፡ ጠንቋዮች ቍጡነትና ተናዳጅነት ያለውን ሰው ኮከቡ ዐመል እሳት ነው ይሉታል ።
ዐመል የለሽ፡ ቈጭባራ ("ዐመል የለሽ የሰው አትበዪ ሀብት · የለሽ የራስሽን አትበዪ" እንዲሉ) ።
ዐመል፡ የግስን አካኼድ የሚለውጡ "አና/ሀ/ወና/የ" ዐመል ይባላሉ ።
ዐመልሳ፡ በመርሐ ቤቴ ክፍል ያለ እ ገር ነት የሚሠራበት ።
ዐመመ (አሕመመ)፡ ራስን አዞረ (ሆድን ቈረጠ ጐንን ወጋ እጅና እግርን ቈረ ጠመ ነዘረ በሸተ ጤና ነሣ ") ።
ዐመመ፡ በዛ በረከተ ("(ግእዝ)") ።
ዐመም (ሐሚም)፡ ማመም ።
ዐመም አደረገ፡ በቀላል ዐመመ ።
ዐመሰ (ኀመሰ)፡ ዐምስት አደረገ ።
ዐመሰ (ሐመሰ/ዋኘ)፡ በቀላል እ ሞቀ አንቃቃ (የላዩን ወደ ውስጥ የውስጡን ወደ ላይ ገለበጠ አዛወረ - የስጥ ") ።
ዐመሰ፡ ኣወከ አተራመሰ ሕዝብን ።
ዐመቀ (ዐሚቅ ዐመቀ)፡ ጥልቅ አ ደረገ ።
ዐመቀ፡ ኣበቀ ወደ ውስጥ ተጫነ ጨቈነ ረጠጠ (ዶቄትን ዐመድን እብቅን - "ደረነቀን" እይ - ከዚህ ጋራ አንድ ነው ") ።
ዐመተ (ሐመሰ)፡ ዐመሰ ክትፎን ።
ዐመተ (ሐመተ)፡ በላ አነደደ አቃ ጠለ ፥ አከሰለ (ዐመድ አደረገ - "ዐመደን" እይ ") ።
ዐመተ (ትግ/ሐመተ)፡ ቈረጠ መ ተረ ከተፈ ።
ዐመተ፡ ዐማት አደረገ ።
ዐመተ፡ ዓመት፡
ዐመቸ፡ ዐማች አደረገ ።
ዐመደ (ሐመደ)፡ ዐመተ ቈረጠ ïደፈ
ዐመደ (ዐምዶ ዐመደ)፡ ደገፈ ተሸ ።
ዐመደ በል፡ ዐመድ የሚቅም/የሚበላ (አህያ ") ።
ዐመደ፡ አሳት አጠፋ (ዐመድ አደረገ ' አደቀቀ ") ።
ዐመደ ፈጭ፡ ዐመድ የሚፈጭ
አመዳመድ፡ አቈራረጥ፡ መመድመድ።
ዐመዳም (ሞች)፡ ባላመድ (ወዘ ቢስ ነጮ ድኻ ንጣታም ደረቅ ") ።
ዐመዳይ (ሐመዳ)፡ ዐመድ መስሎ በብርድ ጊዜ የሚዘንም (በውሃና በመሬት ላይ እንደ መስተዋት የሚጋገር ብትን ውርጭ እ ኸል አጥፊ - ነጭ ዐመድማ - "ዋግን" እይ ") ።
ዐመዴ፡ የንብ ስምና መልክ ።
ዐመድ መስኩ፡ ባመድ ላይ የሚቀ መጥ ፥ የሚተኛ ።
ዐመድ ማዶ (ዐመድ ማዱ)፡ ባመድ ላይ የሚበቅል ቅጠል (ዐመድ ወ ዳድ - "ማዱ ዐመድ የኾነ ") ።
ዐመድ፡ ብዛት ("ግንድን" ተመልከት ") ።
ዐመድ ዐፋሽ፡ ከወዳጁ ወረታ የማ ያገኝ ("እጅን" እይ ") ።
ዐመድ፡ እሳት የበላው ያቃጠለው ነጭ የንጨት የደንጊያ የመሬት ዱቄት (ኖራ ዐቧራ - "(በረቅ ጕብጕባ)") ። "ዘመድ ከዘመዱ አህያ ካመዱ"
("(ተረት)" - ያህያ ሥጋ ዐልጋ ሲሉት ዐመድ ") ።
ዐመድ ያጠለቀው ጕልቻ የላ ቀው፡ ፍጹም ድኻ ምስኪን (ይልሰው ይቀ ምሰው የሌለው ") ።
ዐመድማ (ሐመዳዊ)፡ ዐመድ የሚመስል (አህያ ፈረስ ") ።
ዐመዶ፡ ነጭ ገብስ ።
ዐመዶ፡ ነጮ አበቅማ ።
ዐመጃ፡ ከዐመገ ቢወጣ የንጨቱን ብዛት ጥቅጥቅነት ያሳያል ።
ዐመጃ/ዐምጃ/ዐመጃይ (ሐመዳዊ)፡ ሰበከቱ ዐመድ የሚመስል ቅጠል (በወይናደጋ የሚበቅል ") ።
ዐመገ (ሐመገ)፡ ሰበሰበ አከማቸ መ ሰገ ("ገና ቀ ተወራራሽ ስለ ኾኑ በዐመቀ ፈ ንታ ባላገር ዐመገ ይላል ") ።
ዐመጠ (ዐመፀ)፡ ከዳ ሸፈተ (ግብር ነሣ ከለከለ በደለ ገፋ ") ።
ዐመጠኛ/ዐመፀኛ፡ ከዳተኛ ሽፍታ ግ ፈኛ (በእጁ የገደለ በቃሉ የበደለ - ዕዝ. ፬፥፲፱) ።
ዐመጠኛነት/ዐመፀኝነት፡ ዐመጠኛ መኾን ፥ ("(፩ሳሙ. ፲፭፥፳፫)") ።
ዐመጥ (ዐመፅ)፡ ክዳት በደል ።
ዐመፀ፡ ዐመጠ ።
ዐመፀኛ (ኞች)፡ ዐመጠኛ ።
ዐመፀኛው (ዋ/ይቱ/ቷ)፡ ወንድና ሴትን ለመለየት ይነገራል ("(ኤር. ፫፥፲፩)") ።
ዐመፅ (ዐመፃ)፡ ዐመጥ ።
ዐሙስ (ኀሙስ)፡ ፭ኛ ቀን ከእሑድ ("አበደ" ብለሽ "እብድን" እይ ") ።
ዐሙስ የቀን ቅዱስ፡ ፳፰ መጋቢት (ቅዱስ ቍርባን ለሐዋርያት የተሰጠበት ") ።
ዐሙድ ላይ ተንከባላይ፡ አህያ ("ሀ ባይን" ተመልከት ") ።
ዐሚ (ሐማዪ)፡ ያማ/የሚያማ ።
ዐሚተኛ (ኞች)፡ ዐሚታ ወዳድ (አፉ የማያርፍ - ስም አጥፊ - ምሳ. ፩፥፲፱) ። ("እያሙ ፍቅር)"፡ የውሻ ስም ("ሤራን" ተመልከት ") ።
ዐሚታ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዐሚታ ጠባቂ፡ ሲያውቅ አበድ አ ጫዋች ("እንዲህ አሉ ባይ ") ።
ዐማ (ሐመየ)፡ ነቀፈ ስም አከፋ ("ሰውን ሰው ዐማው የራሱን ሳይሰማው - አፍ' ሲያርፍ ወዳጁን ያማል - "(አትማ ንጉሥ)" - ሞት የተፈረደበት ሰው የሚመታበት ዱላ - "በራስኸ ፍረድ እንጂ ንጉሥን ኣትማ ማለት ነው" -
"(አንተን ዐማኹ)" - ታዘብኩ ") ።
ዐማመመ፡ ቀረጣጠፈ ቈራረጠ ሰውነ ትን ሆድን ።
ዐማሚ (አሕማሚ)፡ ያመመ፥የሚያም ።
ዐማምቻ፡ የጋብቻ ጋብቻ ("እቱን ድሮ የእቱን ባል እት እንደ ማግባት ያለ ነው ") ።
ዐማራ (ዐም ሐራ)፡ ዐም ሕዝብ (ሐራ ነጻ - በተገናኝ ነጻ ሕዝብ ገዢነት እንጂ ተገዢነት የማይስማማው ማለት ነው - "አማረን" አስተውል ") ።
ዐማራ ሣይንት፡ የሣይንት ዐማራ ("ሣይንት ባለቤት - ዐማራ ዘርፍ ኹኖ ቢተ
አማራ፡ ነጻ፡ ሕዝብ፡ ዐማራ።
ዐማራነት፡ ዐማራ መኾን (ተገዝሮ ተ ጠምቆ ማተብ አስሮ ") ።
ዐማሬ፡ የስንዴ ስም (ውሃ የሚመስል ስንዴ ") ።
ዐማሬ፡ ያማራ ተወላጅ (ያማራ ዘር - የሣይንትም አባት ዐማሬ ይባል ነበር ይላሉ) ።
ዐማርኛ፡ ተዛዋሪ ምስጢራዊ ነገር (መል ካምና ክፉ ባንድ ጊዜ የሚያናግር ኅብር ቃል - "(ማስረጃ)" - አትሙት - "(ኢትሙት)" - ሞት ኣይ ንካኸ - አትሙት - "(ኢትሕምይዎ)" - ስሙን በክፉ አታንሡት አታጥፉት " ዐትሙት - "(ኅትምዎ)" - ደብዳቤውን ማኅተም ኣድርጉበት - "የለቅሶ ዜማ ግጥም" እይ ") ።
ዐማርኛ፡ ያማራ ቋንቋ (ከግእዝ የሚወ ለድ - ከሱርስትና ከዕብራይስጥ ከዐረብ የሚዛ መድ ሴማዊ ልሳን ") ።
ዐማሮ፡ ያገር ስም (በሲዳሞ ያለ አ ገር ያማራ ዘር የነበረበት - ሌላም አፈታት ይኖረዋል ") ።
ዐማሮች፡ ሺዎች ላስቶች በጌምድሮች ጐዣሞች ወሎዎች ።
ዐማሽ (ሾች)፡ ያመሰ/የሚያምስ (አ
ዐማቂ፡ ያመቀ/የሚያምቅ (ረጣጭ ") ።
ዐማቂት፡ የደም ምች ("ያመቀች የምታ ምቅ" ተብሎም ይፈታል) ።
ዐማት (ሐማት)፡ የባል እናት ("(ተረት)" - ዐማትና ምራት ሳይስማሙ መሬት ") ።
ዐማት፡ የሚስት አባትና እናት ("ወንድ ዐማት ሴት ዐማት" እንዲሉ - "(ተረት)" - ከሞ ተች ሚስቴ ምን አለኝ ካማቴ ። ለቅልብ ልብ ዐማት ' ሢሶ በትር አላት - በግእዝ ግን ወንዱ ሐም ሴቷ ሐማት ይባላሉ ") ።
ዐማች (ሐማቲ)፡ ያመተ/የሚያምት ።
ዐማች (ሐም)፡ የልጅና የእት ያክ ሥት የዘመድ ባል ("(ዮሐ. ፲፰፥፲፫)" -
"(ተረት)" - ዐማች ኣስታርቆ ቀንበር አርቆ ") ። መጽሐፍ ግን በወንድ ዐማት ፈንታ ዐማች ይላል (ስሕ ተት ነው - ዘፀ. ፲፰፥፲፪፡ ፲፬፥ ፲፭፥ ፲፯፥ ፳፬) ።
ዐማች ኾነ (ሐመወ)፡ ልጃገረድን አገባ ።
ዐማኑኤል፡ ስመ ተዋሕዶ ("ዐማኑ ከኛ ኤል አምላክ - አምላክ ከኛ ጋራ" ማለት ነው - ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ኣምላክና ፍጹም ሰው መኾኑን የድንግል ማርያምን ሥጋ መልበሱን ያሳያል ") ።
ዐማኔል፡ ዝኒ ከማሁ ("የሕዝብ ኣነጋገር ነው" -
"ሚጣቅ ዐማኔል" እንዲሉ) ።
ዐማጅ፡ ያመደ/የሚያምድ (ቈራጭ ደፍጣጭ ") ።
ዐማጊ፡ ያመጎ/የሚያምግ (መሳጊ ") ።
ዐማጋ፡ ምሳግ (የሜዳ በረት - ቀዬ የበር ውጭ ") ።
ዐማጭ (ዐማፂ)፡ ያመጠ/የሚያምጥ ("መጣን" እይ ") ።
ዐሜት (ሐሜት)፡ ማማት ፥ ነቀፋ ።
ዐሜዳ (አልዐሜዳ)፡ ባ፭፻ ዓ ም የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ("ትርጓሜው ብዙ ነኸ ማለት ነው - "ሐመደን" አስተውል ") ።
ዐምሌ (ሐምሌ)፡ የወር ስም (፲፩ኛ ወር ከመስከረም - "ቅጠላም ባለቅጠል" ማለት ነው - "ዐምሌና ናሴ" እንዲል ባላገር) ።
ዐምሞ፡ በዝቶ ("ቄሱ ዐምሞ ጠምጥሞ መጣ ") ።
ዐምሳ (ኀምሳ)፡ ፭ ጊዜ ፲ ወይም ፲ ጊዜ ፭ (፶ - ተራ ቍጥር ሲኾን ዐምሳኛ/ ዐምሳኛው ይላል ") ።
ዐምሳ አንድ (፶፩)፡ ኣምሳና አንድ ።
ዐምሳ እግር '
ዐምሳ እግር፡ የትል ስም (በክረምት የሚታይ ተንቀሳቃሽ - በስተፊት ሲነኩት ጥቅ ልል ይላል ") ።
ዐምስተኚት፡ ዐምስተኛዪቱ ክፍል ።
ዐምስተኛ (፭ኛ)፡ ያምስት ወገን ።
ዐምስተኛዋ፡ ያች ዐምስተኛ (የርሷ ዐ ምስተኛ ") ።
ዐምስተኛው፡ ያ ዐምስተኛ (የርሱ ዐ ምስተኛ ") ።
ዐምስተኛዪቱ፡ ያች ዐምስተኛ "
ዐምስት (ኀምስት)፡ የመደበኛ ቍጥር ስም (፭ - በአራትና በስድስት መካከል ያለ አ ኃዝ - የማዕርግና የተራ ቍጥር ሲኾን ") ።
ዐምስት አደረገ፡ ፭ አለ (ባ፭ ከፈለ ") ።
ዐምስትነት፡ ዐምስት መኾን ።
ዐምስትያ፡ ዐምስት መቶ ድር ።
ዐምስትዮ/ዐምስትዮሽ፡ ካምስት አ ንድ የኾነ ሽርብና ድርብ ንብብር ነገር ።
ዐምስቶ፡ ያምስት ሰው ጉባኤ (ወይም አንድነት ") ።
ዐምሾ፡ ካምስት አንድ
ዐምቆ፡ ዐብቆ ረጥጦ ("ዐምቆ ደርንቆ እ ንዲሉ ") ።
ዐምበላይ (ሐንበላዊ)፡ የዐምበል ወገን (ባለጥሩር - "ዐምበላይና ዐምባላይ ' ልዩዎች መኾናቸውን ልብ አድርግ ") ።
ዐምበላይ፡ ዐውሎ ነፋስ (ባሕርን የሚደርጥ ጣራን የሚገለብጥ ") ።
ዐምበል (ለባሴ ሐንበል)፡ ዐምበል ለባሽ (የፈረሰኛ ባልደራስ ገሥጋሽ ወራሪ ጦር መሪ የሰራዊት አዛዥ ፥ ሻለቃ - "ያ፶ ፥ የ፫ ዐምበል ሻምበል" እንዲሉ - "ዐጤ ቴዎድሮስ የሺሑን ጭፍራ አጋፋሪ ዐምበል (ሐምበል) አሉት" - ታሪ. ቴዎ) ።
ዐምበል (ዐረ/ሐንበል/ግእዝ/ሕንባል/ኮርቻ)፡ የፈረስ መጣብር (ከብርና ከወርቅ የተሠራ - ወይም ከንሓስ የተበጀ - ወርቅ ቅብ ጕብጕብነት ቀለበትነት ያለው የኮርቻ ጌጥ ") ።
ዐምበል (ድርዐ/እንግድዓ)፡ ጥሩር የደረት ልብስ ውስጠ ነት (የብረት ጥብቆ ሳንቃ መጋጠሚያ ያለው ሐርበኛ ጦረኛ የሚ ያጠልቀው ") ።
ዐምበል፡ ታፋንና እንቢያን ከፍላጻ ከ ልክል (ከብረት የተዘጋጀ የፈረስ ቤዛ - "ጥሩርን" እይ ") ።
ዐምበል፡ ከኒሻን በላይ ያለ ክብ የሐር ጥብጣብ (ሰንደቅ ዐላማ - "እከሌ ባላም በል ኒሻን ዐምበል የሌለው ኒሻን ተሸለመ" እንዲሉ) ።
ዐምበሎች፡ መጣብሮች (ጥሩሮች የጦር አለቆች ባለጥሩሮች - ራእ. ፲፱፥፲፰) ። "ሐምበልና ዐንበል ከዐምበል ጋራ አንድ ነው - ይኸ ውም የሐንና የዐን የመንና የነን መወራረስ ያሳያል ") ።
ዐምበር፡ ሽቱ—ዐንበር ።
ዐምባ (ዐም ባ/ሕዝብ ባ)፡ የተራራ ስም (ዕርድ ምሽግ ያለበት ተራራ - ትርጓሜው "ሕዝብ አላት/አለባት" ማለት ነው - ፩ሳሙ. ፳፫፥፲፬ - "(ተረት)" - ቀን ቢደ ርስ ዐምባ ይፈርስ - ኢያ. ፮፥፳) ።
ዐምባ፡ ለጦርነት የተደለደለ መሬት ("(ሕዝ. ፳፩፥፳፪)")
ዐምባ ራስ (ርእሰ ዐምባ)፡ የተ ራራ ራስ ጫፍ '
ዐምባ ራስ (ያምባ ራስ)፡ ያምባ ሹም (ዋና ግንባር ቀደም - "(ተረት)" - ከጐንደር ንጉሥ ያገር ዐምባ ራስ - "ዐምባ ራስን የሚ ያዝ ባላምባራስ' ይባላል" -
"ባልን" ተመልከት ") ።
ዐምባ ራስ፡ ጣብ የሚባል ጨዋታ ።
ዐምባ፡ በማንኛውም ስፍራ የተሠራ መንደር ጎረቤት ("ጽኑ ዐምባ ወይራ ዐምባ ታላቅ ዐምባ ታች ዐምባ ላይ ዐምባ" እን ዲሉ - "መንደር ዐምባ' መባሉ የቀድሞ ሰዎች ") ።
ዐምባ፡ በተራራ ላይ ያለ መንደር ("በግእዝ ሀገር ይባላል ") ።
ዐምባ ገነን (ኖች)፡ ንጉሥ ያልሾ መው ባላባትነት የሌለው በተራራ በመንደር የገነነ ሰው
ዐምባ ጓሮ (የዐምባ ጓሮ)፡ የዐ ምባ ኋላ ("የመንደር ' ጠብ ጥል ጠብ' የተባ ለው ጓሮ መኾኑን አስተውል - "(ተረት)" - አላሽከር በቅሎ ኣለወንድማማች ዐምባ ጓሮ ") ።
ዐምባ ጓሮኛ (ኞች)፡ ጠበኛ (ጠበ ወዳድ ጥል ያለሽ ፥ ዳቦ የሚል ") ።
ዐምባላ (ዐም ባ ላ/ሕዝብ ባ ላ)፡ ሕዝብ አላት ("ብዙ ኹኖ የሚኼድ ነጭ የዥረት አሞራ ወይም ወፍ - "ዐምባላ ሐባብኛ ነው" - መዝ. ፹፫፥፫) ።
ዐምባላይ (ትግ/ሐባ/ሐምበለይ)፡ ነጭ ጸዐዳ ፈረስ ሻሾ ("ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ባላምባላይ ፈረስ" - ታቦት ዘፋኝ ") ። መጽሐፍ ግን "አን(ም)በላይ" ይላል ("(ዘካ. ፩፥፰፡ ፮፥፲፥፫፡ ራ እ. ፲፱፥፲፩፥፲፬)") ።
ዐምባላይ፡ የዐምባላ ዐይነት ነጭ ፍጥረት ።
ዐምባላይነት፡ ዐምባላይ መኾን (ንጣት ነጭነት - በልማድም "አምባ/አንባ/አምበል/አ ምባላ/አምባላይ" እየተባለ ይጻፋል ") ።
ዐምባላዮች፡ ነጫጭ አሞሮች ወፎች ነጐዴዎች ፈረሶች ። መጽሓፍ ግን "አንበላዮች" ይላል ፥ ("(ዘካ. ፮፥፮)") ።
ዐምባላጌ፡ የዐምባላ ምድር አገር ("ዐ ምባ ዐላጊ ቢል ግን ትርጓሜው ሌላ ነው ") ።
ዐምባሰል (ዐምባ ዐሰል)፡ በወሎ ግዛት ውስጥ ያለ አገር ("የማር ዐምባ መን ደር ተራራ" ማለት ነው ") ።
ዐምባት፡ ዝኒ ከማሁ ("በመራቤቴ ክ ፍል ያለ ደጋ ") ።
ዐምባው)። (ግጥም)፡ ይታመሳል፡ አሉ፡ ከፋና፡ ቦረና፡ አማን፡ አይደሉም፡ ወይ፡ እነራስ፡ ጐበና ።መዠመሪያውን፡ አማን፡ እይ ።
ዐምቦ ("ከብት ሲጠ ጣው ጨው ጨው የሚል ውሃ ዐፈር ኾራ በኦሮ ዐምቦ ባማርኛ ነው ምስጢሩ ከኩሬነት አይወጣም ኮራን ተመልከት ኹሽ ")
("ኩኪ") ።
ዐምቦ (ዐም ቦ/ሕዝብ ቦ)፡ ጨው ጨው የሚል ዐፈር ፲ ወይም ጭቃ እየ ተሰፈረ የሚሼጥ ("ትርጓሜው ሕዝብ አለበት ማለት ነው ") ።
ዐምቦ፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ያለ ባ ለጪስ ዦርለስ ያለ ጠጅና ጠላ የሚያፈ ላና የሚያሳምር ።
ዐምቦ ዋሻ (የዐምቦ ዋሻ)፡ በው ስጡ ዐምቦ ያለበት ዋሻ ("እሱም በላይ ወግዳ በጐሽ ውሃ ቈላ ይገኛል ") ።
ዐምቦ፡ ውሃ ("ብዙ ሕዝብና ከብት የሚሰበሰብበት ባለማዕድን ምንጭ - "አንቦ" ተብሎ ሊጻፍ ይችላልና "ነባን" እይ ") ።
ዐምቦች፡ ተራሮች መንደሮች ("(፩ሳሙ. ፳፬፥፩)") ።
ዐምቻ (ታሕማ)፡ ጋብቻ (የጋብቻ ዝ ምድና ዐማችነት ") ።
ዐምዛ፡ ወፍራም የጤፍ እንጀራ ዳቤ ("ዐበዘን" ተመልከት ") ።
ዐምደ እሳት፡ የእሳት ምሰሶ ።
ዐምደ ወርቅ፡ በወርቅ የተለበጠ ደ ገፋ (በቅኔ ማሕሌትና በቅድስት መካከል የ ቆመ ") ።
ዐምደ ወርቅ ዐምደ ጽዮን፡ ፲፬፻ ዓመተ ምሕረት የነበረ የሐበሻ ንጉሥ ።
ዐምደ ደመና፡ የደመና ምሰሶ ።
ዐምድ (ዶች)፡ ምሰሶ ደገፋ ("(ኤር. ፳፯፥ ፲፱)") ።
ዐምድ፡ በዐምድ የተከፈለና ያልተከፈለ' ጥፈት ("፩ ዐምድ ፪ ዐምድ ፫ ዐምድ" እን ዲሉ) ።
ዐምድ፡ በጥፈትና በጥፈት መካከል (ከ አርእስት እስከ ኅዳግ ያለ የገጽ መክፈያ ባዶ ብራና - "ሐውልትን" አስተውል ") ።
ዐሞቱ ዳውላ አከለ፡ ሰነፈ ታከተ ።
ዐሞታም (ሐሞታዊ)፡ ቍጡ ደፋር ጐበዝ መራር ።
ዐሞት (ሐሞት)፡ መራራ ሖምጣጣ የደም ቅራሪ (በሆድ ውስጥ ከኍበት ጋራ የሚገኝ - ሲበዛ ሰውነትን ብ ያስመስላል - የከብቱን በድልሽ እየበጠበጡ ሥጋ ይበ ሉበታል ") ።
ዐሞድ፡ "እንዳሞድን" ተመልከት ።
ዐሞጭ (ጮች)፡ የቅጠል ስም (በሥሩ የሚያፈራ ዕፅ - ፍሬው ቢበሉት የሚያቃጥል - ዝንጀሮ ዐሞጩን ጐመጩን ሲበላ ይውላል ") ።
ዐሰለ (ትግ)፡ በላይ ኾነ ተቀመጠ ሰፈረ (የንብ ") ።
ዐሰላ፡ በግንብና በካብ ቅጥር ላይ የተቀመጠ የደንጊያ ቀጸላ ክዳን ።
ዐሰል፡ ማር ("(ዐረብኛ)") ።
ዐሰል፡ የጨው ባሕር—አሰል ።
ዐሠሠ (ኀሠሠ)፡ ዞረ ሻ ፈለገ አዘጋጀ ("ዋሻን ጐሬን ቀፎን ቤትን ") ።
ዐሠሠ፡ ጠረገ ወለወለ አበሰ ዐደፈ ምጣድን ።
ዐሠሣ፡ ኹሉን የሚጠርግ ጐርፍ ("ሱ ቃያውን ዐሠሣ ወሰደው ") ።
ዐሠሣ/ዕሠሣ (ኀሠሣ)፡ ጠረጋ ውልወላ ።
አሠሣሠት፡ አነፋፈግ (መሠሠት) ።
ዐሠሥ፡ አበስ ።
ዐሠሥ፡ ያውድማ ጥራጊ ("አህያ ዐሠ ሡን ወሰሱን ይቅማል ") ።
ዐሠር (ሐሠር)፡ የገለባ ስም (የገብስ ዐሻሮ ገለባ ") ።
ዐሠር፡ ውሃ (የጠላ ቅናሽ - "ያሠር ' ውሃ" ወይም "ዐሠር ያለበት ውሃ" ማለት ነው ") ።
ዐሠርቱ ቃላት፡ ከግዜር ለሙሴ የ ተሰጡ ዐሥር ቃሎች ("(ሕግና ትእዛዝ)") ።
ዐሠርቱ፡ ዐሥር ዐሥሩ ።
ዐሰቀ፡ ጠለፈ አስጌጠ አዥጐረጐረ ልብስን ("(ግእዝ)") ።
ዐሰበ (ሐሰበ)፡ ነገርን በልቡ አ ጤነ አሳደረ አወጣ አወረደ (ያለፈውን አስ ታወሰ አስተነተነ - ግብ. ሐዋ. ፲፱፥ ፳፩) ።
ዐሰበ፡ ሒሳብ አደረገ አሰላ ።
ዐሰብ (ዐረ/ዐጸብ)፡ በአዳል አገር ጫፍ ያለ ወደብ (እንቅልቅል በረሓ ጭንቅ ማለት ነው - በግእዝ "ዐጸባ" ይባላል ") ።
ዐሰቦት፡ በሐረርጌ ግዛት በቈላ በበ ረሓ ያለ ረዥም ተራራ ። ትርጓሜው ጭን ቅንና ዋጋን ያሳያል ። የግእዝ መጽሐፍ ወገግ ይለዋል ።
ዐሰተኛ (ኞች)፡ ሐሰተኛ ' ("(ምሳ. ፲፪፥ ፲፱ - ፳፪፡ ዮሐ. ፰፥ ፶፭፡ ፪ጴጥ. ፪፥ ፩)") ።
ዐሰተኛነት፡ ሐሰተኛነት "
ዐሰት ጽድቁ፡ ዐሰት እውነቱ ። "ሐሰ ትን" ተመልከት ።
ዐሰት: ፡ ሐሰት "
ዐሣማ
ዐሣማ (ሐሠመ/ሐሣማ)፡ መልከ መጥፎ የቤት እንስሳ (በልቶ የማይጠግብ - እድፍ ጕድፍ የሚበላ የሚጠጣ - በጭቃ ላይ የሚንከባለል - አፉ ዐይጠ መጐጥ የሚ መስል ") ።
ዐሣማ፡ ሆዳም ሰው ።
ዐሣሞች፡ ሆዳሞች እንስሶች ሰዎች በ ላተኞች ።
ዐሳረኛ (ኞች)፡ ዐሳር ያገኘው የተዋረደ መከረኛ ጐስቋላ ። "(የበገና ግጥም)" - ዐሳረኛው እኔ (መከረኛው እኔ -
ዐሳር (ኀስረ/ኀሳር)፡ ውርደት ጕስ ቍልና መከራ ጭንቅ ("(ሉቃ. ፩፥ ፳፭)") ። "(ተረት)" - ላሳር የጣፈው ቢነግድ አይተርፈው ።
ዐሣር፡ ውርደት—ዐሳር ።
ዐሣሽ (ሾች)፡ ያሠሠ/የሚያሥሥ (ፈላጊ አዘጋጂ ንብ ሹም - ጠራጊ ወልዋይ ") ።
ዐሣሽነት፡ ዐሣሽ መኾን ።
ዐሳበ ቢስ፡ ዐሳበ መጥፎ ።
ዐሳቢ (ዎች)፡ ያሰበ/የሚያስብ (አስ ታዋሽ ") ። "(ተረት)" - ሩቅ ዐሳቢ እቅርብ ዐዳሪ ።
ዐሳብ (ሐሳብ)፡ ኅሊና የነገር ፅንስ ።
ዐሳብ የለሽ፡ ግድ የለሽ ("ምን ቸገ ረኝ ባይ ") ።
ዐሳብ ገባው፡ አንድ ነገር በመስ ማት እንቅልፍ ዐጣ (ሌት ተቀን እሱኑ አውጠነጠነ ") ።
ዐሥረ ፈጅ፡ እንቅብ ላዳን ዐሥር ቍና እኸል የሚይዝ የሚጨርስ ።
ዐሥረኚት፡ ዐሥረኛዪቱ ክፍል ።
ዐሥረኛ ቀን፡ ፀሓይ የምትሞቅበት ።
ዐሥረኛዋ/ዐሥረኛዪቱ፡ ያች ዐ ሥረኛ ።
ዐሥረዬ፡ ዐሥር ጊዜ ("ዬን" እይ ") ።
ዐሥሪያ፡ ካሥር አንድ የኾነ ።
ዐሥራ (ዐረ/ዐሸራ)፡ ዐሥራ አንድ "(፲፩)" ዐሥራ ኹለት "(፲፪)" ዐሥራ ፥ አራት "(፲፬)" ዐሥራ ዐምስት "(፲፭)" ያሠኛል ። ትር ጓሜውም ዐሥርና አንድ ... ዐሥርና ዐም ስት ነው ።
ዐሥር አደረገ (ዐሠረ)፡ እስካሥር ቈጠረ (ባሥር ከፈለ ") ።
ዐሥር፡ የቍጥር ስም (፲ - ከዘጠኝ ቀጥሎ ያለ አኃዝ - ተራ ቍጥር ሲኾን ዐ ሥረኛ "(፲ኛ)" ዐሥረኛው "(፲ኛው)" ይላል - ሲ ናበብም ") ።
ዐሥርነት፡ ዐሥር መኾን ።
ዐሥርዮሽ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዐሥሮ/ዐሥሪዮ፡ ዐሥርነት ያለው ነገር ውስጠ ብዙ ።
ዐስበ ተፈሪ፡ የከተማ ስም (በሐረርጌ ግዛት በጨርጨር አውራጃ ያለ ከተማ ") ።
ዐስበ ዲያቆን፡ ቍርባን የዲያቆን ፈንታ ድርሻ ።
ዐስቢት፡ የእባብ ስም (አንድ ዐይነት የበረሓ እባብ ") ።
ዐስቤ (ዐስብየ)፡ የሰው ስም (ምን ምንዳ ማለት ነው ") ።
ዐስብ (ዐስቦ/ዐሰበ)፡ የሥራ ዋጋ ።
ዐስብ፡ ዐሸመ፡
ዐስቦ፡ የደብረ ሊባኖስ ስም (ደብረ ሊባኖስ ከመባል አስቀድሞ ዐስቦ ይባል ነበር - በግእዝ ዋጋውን ተብሎ ይተረጐማል ") ። "ደበረን" እይ ።
ዐረ. ነጽር)፡ መዋኢ አሸናፊ ("(ማር ይሥ መቅ)") ።
ዐረመ (ሐረመ)፡ ተወ ከለከለ (ለየ ቀደሰ - ፬ነገ. ፳፥ ፵፪፡ ፩ጢሞ. ፬፥ ፫) ።
ዐረመ፡ ቈረጠ ከፈለ መሬትን ።
ዐረመ፡ ኰተኰተ ነቀለ ። "(ተረት)" - አያ ርም ዐራሽ (አያጥብ ለባሽ ") ። "(ግጥም)" - ጤፉን ዳዋ በላው ቀለባችንን (አንቺ ሰው ዐርሚ እንጣላለን - ተወ - ያላህን ነገር ምኑን ዐውቀ ሽው - ወይ እኔ እበላው አንቺ ዐርመሽው ") ።
ዐረመ፡ ግድፈትን መላ (ትርፍን አስ ገለለ ") ።
ዐረመኔ፡ ያልተጠመቀ—አረመኔ ።
ዐረማም፡ ዐረም የበዛበት ባላረም መሬት ።
ዐረማሞ፡ ሞ ቃለ አኅስሮን ያሳያል (ዝናም ሳያጠግብ የተዘራ የስንዴና የገብስ ያገዳ ፍሬ በሽታ ጥቀርሻ መሳይ ") ።
አረማረም፡ አረጋገጥ፡ መረምረም።
ዐረም (ሞች)፡ ከብቋያ ውስጥ የሚ ነቀል (በያይነቱ ቅጠልና ሣር ") ።
ዐረም ተነበት፡ ተደበቀ ታባ ተሰወረ ነውሩ ነገሩ ።
ዐረሰ (ኀረሰ)፡ መገበ ቀለበ የወለ ደች ሴትን ።
ዐረሰ (ሐረሰ)፡ ተለመ ጨፈለቀ ተረ ተረ ገመሰ ሰበተ ገለገለ ከረበተ ደገመ ቀበቀበ ዐየመ አለሰለሰ "
"ሸመተን" እይ ።
ዐረሰ፣ ዐራሽ ።
ዐረሰ፡ ዐሸ፡
ዐረሳ፡ ገመሳ ግልጋሎ ።
ዐረስ፡ ዝኒ ከማሁ ("ጐሽ ዐረስ" እን ዲሉ) ።
ዐረረ (ሐረረ/ሐለለ)፡ ነደደ ተቃ ጠለ ገመነ ጠቈረ ከሰለ ። "(ተረት)" - ያረረ በት ያማሳል ። ሆድ ሲያር ጥርስ ይሥቃል ። ዐረረ፡ ነጠፈ ደረቀ ተኰማተረ (ዐጪር ኾነ ") ።
ዐረረ፡ ዐለቀ ተበጣጠሰ ("እከሌ ልብስ ዐሮበታል" እንዲሉ) ።
ዐረሩ፡ የወንድ ባሪያ ስም ።
ዐረሩ፡ ጥቍር አህያ ።
ዐረር፡ የርሳስ ስም (በቀለሕ ጫፍ ያለ ርሳስ - ከጠመንዣ በተተኰሰ ጊዜ ሰውን እንስሳን አውሬን ወፍን አሞራን ማንኛውንም ተንቀሳቃሽ ፍጥረት አሳርሮ የሚገድል - ዘኍ. ፴፩፥ ፳፪) ። "ዐረር" የግእዝ ("ርሳስ" ያማርኛ ነው ") ።
ዐረር፡ ድርቅ ደረቅ ቦና ("ውሃ ጠፍቶ ባረር ይለቀሳል" እንዲሉ) ።
ዐረቀ (ዐሪቅ/ዐረቀ)፡ አቀና አረታ ፥ ቀጥ አደረገ (የዕርፍ የሞፈር የድር - ቅዱስ ዲሜጥሮስ ዕርፍ ዐርቆ ተክል አጽድቆ ይኖር ነበር ") ።
ዐረቀ፡ በክርን መታ ደሰቀ ።
ዐረቀ፡ አጐበጠ ቀለሰ ለመጠ ቀጥ ታውን ።
ዐረቀ፡ ጭነትን መለሰ አስተካከለ ።
ዐረቂ (ላህባዊ)፡ የላብ ዐይነት (ይኸ ውም በአረብኛ ነው ") ።
ዐረቄ (ዐረ/ዐረቅ/ላብ)፡ የእኸልና የቅመም የማር ላበት (የሚያሰክር ብዙ ዐይነት መጠጥ - ሲበዛ ልብ የሚነሣ ቀልበ ቢስ የሚያደርግ ፈሳሽ ") ።
ዐረቄ መርፌ፡ ዐጪር ቀጪን መርፌ ። "ዐረቄ" መባሏ ላብ የወጣበት እንዳይታወቅ (ርሷም የገባችበትና የወጣችበት ልብስም ቢኾን ገላ ስለማይታወቅ ነው ") ። ዳግመኛ ግእዝ ("ዐራቂ" - አስታራቂ በሚለው ዘይቤ ቢፈቱት በመጠን ለሚጠጣው ዐረቄው ምግብን መርፌው የተቀደደ ሆድን ማዋ ሐዱን ማሰማማቱን ማገናኘቱን ያሳያል ።
ዐረቄ፡ ዐረሰ፡
ዐረቄ ወገብ፡ ወገበ ቀጪን ሴት ።
ዐረበ (ዐሪብ/ዐርበ)፡ ጠለቀ ገባ (ጥንቅር አለ ") ።
ዐረበ፡ መለጠ ፋቀ አቀላ ።
ዐረቢ (ዐረባዊ)፡ ያረብ አገር ሰው ያረብ ተወላጅ ("(ኢሳ. ፲፫፥ ፳)") ።
ዐረቢ፡ ቀይ እንዶድ ።
ዐረቢ፡ ዐረብኛ (ያረብ ፊደል ") ።
ዐረቢት (ዐረባዊት)፡ ያረብ ሴት ።
ዐረቢትን ዐረቧት፡ ብልጧን በለ ጧት (ሌባን ሌባ ሰረቀው እንደ ማለት ") ።
ዐረብ (ቦች)፡ የነገድ ስም (በበረ ሓና በጀንበር መጥለቂያ ያለ የሴምና የካም ዘር በእስያና በአፍሪቃ የሚገኝ ቀይ ሕዝብ እስላም ") ።
ዐረብ፡ ቀይ ቈርበት (ተንቤን ነት - ቅላት ቀይነት ያለው የበግና የፍየል ቈዳ - ዘፀ. ፳፭፥ ፭) ። "ባሕር ዐረብ" እንዲሉ ። (ጥቍር ዐረብ)፡ ጥቍር ቀለም የገባ የበግ ቈዳ ("(ዘፀ. ፳፮፥ ፲፬)") ።
ዐረብ ብረት፡ ካክራ ጠንካራ ያረብ ብረት ።
ዐረብኛ፡ ያረብ ቋንቋ ወይም ልሳን (የሱርስትና የዕብራይስጥ የግእዝ ወንድም ") ።
ዐረብያ፡ ጋሪ ሠረገላ ።
ዐረቦ፡ መላጣ ከብት ("(በሬ)" - ጠጕሩ በኖ ያለቀ ") ።
ዐረቦን (ዐርበ)፡ መያዣ ፈለማ ቃ
ዐረቦን (ዐርበ)፡ መያዣ ፈለማ ቃ
ዐረቦን ግእዝ ("ዕርቡን" ዐረብኛ ነው ") ።
ዐረንቋ፡ —ማጥ፡ አረንቋ ።
ዐረንዛ፡ ብዙ
ዐረንዛ፡ ዐረፈ፡
ዐረዘ (ዐሪዝ/ዐረዘ/አለበሰ)፡
ዐረደ (ሐረደ)፡ የከብትን የሰውን የዶ ሮን ዐንገት ጎዘጎዘ ከረከረ ቈረጠ ቀረደደ ("(፪ነገ. ፲፥ ፯፡ ሉቃ. ፲፭፥ ፳፯)") ።
ዐረደ፡ መሬትን ማሰ ጐደበ አጐደጐደ ።
ዐረደ፡ ሰረቀ ሞጨለፈ ።
ዐረደ፡ አታለለ አሞኘ ("እከሌ እከሌን በማዥራቱ ዐረደው" እንዲሉ) ።
አረደ፡ ዐንገት ቈረጠ ፥ —ዐረደ ።
ዐረደ፡ ከለለ ጋረደ መከታ አበጀ ' መሸገ ።
ዐረደ/ዐነቀ/ነፍስ አሳለፈ/አጠፋ/ቀተለ (ሌላውን ወይም ራሱን)።
ዐረዳ (ሕርደት)፡ ክርከራ ቈረጣ ' ራስን ቸብቸቦን ።
ዐረድ (ዶች)፡ ዋና ሌባ አታላይ
ዐረገ (ዐርገ)፡ ወደ ሰማይ ኼደ ወጣ ከፍ ከፍ አለ ።
ዐረገ፡ እፈጣሪ ፊት ደረሰ ቀረበ መ ሥዋዕቱ ጸሎቱ ።
ዐረጉን፡ መዘዘ)፡ ዘሩን፡ ቈጠረ፡ እከሌ፡ ቢወልድ፡ እከሌን፡ አለ፡ ቃይ ።
ዐረግ (ጎች/ሐረግ)፡ በዱር በገደል በዛፍ ላይ እየተሳበ የሚያድግ (ያጥር የግድ ግዳ ማሰሪያ መማገሪያ - ዐዞ ቋንዶ ጠሮ ሞይደር ላንቍሶ የመሰለው ኹሉ ") ። "(ተረት)" - አንድ ዐረግ ቢስቡ ዱር ይሰበስቡ ። "አደረገና ሀረግ" በአማርኛ ይተባበራሉ ። "(ግጥም)" - ዕንጨት ሰብሮ ሰብሮ ማሰሪያው ምንድነው (እኛስ ባገራችን አረግነው - አረግ ነው - "(ዐ ረግ ነው)") ።
ዐረግ ሬሳ፡ ያረግ ሬሳ (ቧሔ ዐረግ ዕፀ ሳቤቅ ") ።
ዐረግ፡ ዐረደ፡
ዐረግ፡ ዘር ወገን ነገድ ። "መዘዘን" እይ ።
ዐረጠ (ሐረጸ/ዕብ/ሐሬጽ/ቈ ረጠ)፡ ደረቀ ነጠፈ (የደም ") ። ከዚህ የተነሣ
ዐረጠ፡ ባራጣ አበደረ ለቃ አተረፈ ።
ዐረፈ (ዐሪፍ/ዐረፈ)፡ ከሥራ ከመንገድ ከነገር ተለየ (ዝም አለ ተቀመጠ እፎይ አለ - ዘፀ. ፪፥ ፲፭፡ ፪ሳሙ. ፲፮፥ ፲፬) ። "(ተረት)" - አፍ ሲያርፍ ወዳጁን ያማል ።
ዐረፈ፡ ቈረጠ ሸማን ዕንጨትን ። "ዐረፍኩኸ የወር ጨው" (ሰው በሞተ ጊዜ እንዲህ አለ ይላሉ ") ። "ጨውን" እይ ።
ዐረፈ፡ ዐለፈ ሞተ ።
ዐረፈ፡ ከጭነት ከሸክም ዳነ ("አህያ በወለደች ታርፋለች ") ።
ዐረፈ ጣቴ፡ የፈትል ስም (ውሃ ' የሚመስል የባሕር ድር - ቀጪን ሞናና ") ።
ዐረፋ (ዐረ/ዐረፈ/ዐወቀ)፡ የበዓል፥ ስም (ያዳምና የሔዋን መተዋወቅ ") ። ዳግመኛም እስላሞች ኦሪትን በማስተባበል በይሥሐቅ ፈንታ አብርሃም ይስማኤልን ሲሠዋ አላህ በጀነት በግ ተቤዠው እያሉ በየቤታቸው በግ በማረድ የሚያከብሩት በዓል ነው ።
ዐረፋ (ዎች/ሐረፈ/ሐረፋ)፡ የንዶድ የሳሙና የሥጋ የስብቅ ነጭ ውጤት (በውሃ ላይ ሰፎ የሚታይ ") ።
ዐረፋ፡ ምራቅ ቈበር ("እከሌ በድን ገት ታመመና ዐረፋ ደፈቀ ") ።
ዐረፋት (ሐረፋት)፡ ዐረፋዎች ። "ሐረ ፋት" በግእዝ ብዛትን እንጂ አንድነትን አያ ሳይም ።
ዐረፋት፡ ዝኒ ከማሁ ("(ማር. ፱፥ ፲ - ፳)") ።
ዐረፋት፡ የቀለጠ ብር ("(ምሳ. ፳፮፥ ፳፫)") ።
ዐረፋት፡ የውሃ ዐረፋ ወዲያው ሻ ብትን ብሎ የሚጠፋ ("(ሆሴ. ፲፥ ፯)") ።
ዐሩር (ሐሩር)፡ የፀሓይ ሙቀት (ከሙቀት የተነሣ በገላ ላይ ሽፍ የሚል ዕከክ ") ።
ዐሩር፡ ጥቍር ቀለም የሚኾን የስንዴ (ከሰል - "ሐሩርም" ይባላል ") ።
ዐሩን በላ፡ ተደበደበ መከራውን አየ ።
ዐሪላ፡ ቂጧን የማትጠርግ ሰነፍ ሴት ("ላ ' አላት" ማለት ነው ") ።
ዐሪታ፡ ማታ ኵቲ ። የቀረ የተረሳ ቋ ንቋ ነው ።
ዐሪታ፡ አለጊዜ ያራች የምታራ ሴት ።
ዐሪዛዞ፡ ብርሌ—አሪዛዞ ።
ዐራ (ሐረረ/ሐራ)፡ ጨዋ የጨዋ ልጅ (ባላባት ከመታዘዝ ነጻ የኾነ - "እከሌ ዐራና ገባር ' ይመርጣል" እንዲሉ - ዳግመኛም መዠመሪያ በህንድ አገር የነበረ ሕዝብ አ ርያ ይባል ነበር ይላሉ ") ።
ዐራ (ሐረወ/ዐረ/ኀሪአ)፡ ዕዳሪ ወጣ (ወገቡን ሞከረ ኰሳ ዘበለላ ") ። "አፍኣን" እይ ። "(ተረት)" - አይነጋ መስሏት አቋት ዐራች ። ዐሪ፡ ያራ/የሚያራ ።
ዐራ፡ ዐረበ፡
ዐራሙቻ፡ ተነቅሎ የወደቀው ዐራ ሙቻ ይባላል ።
ዐራሚ (ዎች)፡ ያረመ/የሚያርም (እኸልን መጻፍን - ነቃይ ኰትኳች ") ።
ዐራሚነት፡ ዐራሚ መኾን ።
ዐራም (ሞች)፡ ዐረ ብዙ ኹል ጊዜ የሚያራ የሚዘፈዝፍ ።
ዐራስ (ኀራስ)፡ እመጫት የጨቅላ እናት (ብረት ተንተርሳ የምትተኛ - ለሽንትም ወደ ውጭ ስትወጣ ቢላዋ ጨብጣ የም ትኼድ ") ። "የማሪያም ዐራስ" እንዲሉ ። ሲበዛ "ዐራሶች" ይላል (ለእንስሳትም ይነገራል - መዝ. ፸፰፥ ፸፩) ። "ጥሬን" እይ ።
ዐራስ፡ ርጥብ ጨቅላ ልጅ (የናቱን ጡት የሚጠባ የሚመጠምጥ ቅቤ የሚውጥ - ዞ ለሴትም ይነገራል ") ።
ዐራስ ነብር፡ ቍጡ ኀይለኛ ሰው '
ዐራስ ነብር፡ ግልገሎች የምታጠባ ።
ዐራስ ውሻ፡ ቡችሎች ያሏት (መን ገደኛን የምትነክስ ") ።
ዐራራ፡ ያረረ የከሰለ ። "(ተረት)" - የስንዴ ዐራራ የቄንዦ መራራ እንዲሉ ።
ዐራሽ (ኀራሲ)፡ ያረሰ ("(ጥር)") የሚያ ርስ (መጋቢ ቀላቢ ") ።
ዐራሽ (ሐራሲ)፡ ያረሰ/የሚያርስ (ገበሬ ") ።
ዐራሽ፡ ያራው የኰሳው ("ወፍ ዐራሽ" እንዲሉ) ።
ዐራሾች (ሐራስያን/ሐረስት)፡ ገበሬዎች ("(ኢሳ. ፷፩፥ ፭)") ።
ዐራቂ፡ ያረቀ/የሚያርቅ (አቅኒ ") ።
ዐራቢ፡ ያረበ/የሚያርብ (መላጭ ፋቂ አቅሊ ") ።
ዐራቦ፡ የበሬ መዥገር የሚመልጥ (ራሱ እቈዳ ውስጥ የሚገባ ") ።
ዐራዳ፡ ቍርጥ ነገር ። "ዐራዳውን ንገ ረኝ" እንዲል ባላገር ።
ዐራዳ፡ በላይ ወግዳና በታች ወግዳ መካከል ያለ ስፍራ (ግራ ቀኙ ታርዶ ተቈፍሮ እንደ በር ያለ ጠባብ መንገድ ኹኗል ") ።
ዐራዳ፡ የታረደ የተራራ ዐንገት በር ።
ዐራዳ፡ ያዲስ አበባ ከተማ መካከ ለኛ ቦታ ለገበያነት የተወሰነ የተከለለ (ምሥራቁና ምዕራቡ' በወንዝ የታረደ ") ። ከጣሊ ያን ወዲህ ግን "ዐዲስ አበባ ፒያሳ" ይሉ ታል (የስሕተት ስሕተት ነው ") ። በዘርፍነት ሲነገር "ዐራዳ ጊዮርጊስ" ያራዳ ጊዮርጊስ ይላል ።
ዐራድ፡ ትርጓሜው እንደ መዠመሪ ያው ዐራዳ (ጐራዳ ብሎ ጐራድ እንደ ማለት ያለ ") ።
ዐራድማ፡ በመንዝ ውስጥ ያለ አገር ("ዐራዳማ" ማለት ነው ") ። "(ተረት)" - ምንም በሙቱ ዐራድማ ሸምቱ ።
ዐራጅ (ጆች)፡ ያረደ/የሚያርድ (ዐን ገት ቈራጭ ") ።
ዐራጅ፡ መጎዛ ፥ ፋደት የቀፎ ሌባ ።
ዐራጊ፡ ያረገ/የሚያርግ ።
ዐራጣ (ትግ/ሐረጻ)፡ ወለድ ትርፍ (የወለድ ገንዘብ - ዘሌ. ፳፭፥ ፴፯፡ መዝ. ፲፭፥ ፭) ።
ዐራጭ (ጮች)፡ ያረጠ/የሚያርጥ (ባራጣ አበዳሪ ") ።
ዐራፊ (ዎች)፡ ያረፈ/የሚያርፍ (ተቀ ማቴ ሰሞነኛ ገባር ") ።
ዐራፊ፡ የቈረጠ/የሚቈርጥ ።
ዐራፊነት፡ ዐራፊ መኾን (ተቀማጭነት ") ።
ዐር፡ ኵስ ዐይነ ምድር ዕዳሪ ሠገራ የምግብ ፥ አተላ ዝቃጭ ("የብረት ዐር" -
"የቅቤ ዐር" እንዲሉ) ። "ጪዋን" "ዐይንን" ተመልከት ።
ዐርቆ፡ አቅንቶ ቀጥ አድርጎ ። "(ተረት)" - ዐማች አስታርቆ ቀንበር ዐርቆ ።
ዐርበ ወጥ፡ ካርብ የወጣ ዐዲስ ል ብስ ያልተሰፋ ።
ዐርበኛ (ኝ)ነት፡ ዐርበኛ መኾን (ጦረ
ዐርበኛ (ኝ)ነት፡ ዐርበኛ መኾን (ጦረ
ዐርበኛ (ኞች)፡ ጦረኛ የጦር ገበሬ ጨካኝ (ደፋር ቈራጥ ጐበዝ ኀይለኛ - በግ እዝ "(ያርብሕ/ያርብሓዊ)" ይባላል ") ። "ሐርብን" እይ ።
ዐርበኛ (ኞች)፡ ጦረኛ የጦር ገበሬ ጨካኝ (ደፋር ቈራጥ ጐበዝ ኀይለኛ - በግ እዝ "(ያርብሕ/ያርብሓዊ)" ይባላል ") ። "ሐርብን" እይ ።
ዐርቤ (ሐርቤ)፡ ገብረ ማርያም ' የ ሚባል የላስታ ንጉሥ ስም (ባማርኛ የሚጠ ራበት - "የጦር ሰው" ማለት ' ነው ") ።
ዐርብ (ዐረ/ሐርብ)፡ ጦር ጦርነት ።
ዐርብ (ዐረ/ሐርብ)፡ ጦር ጦርነት ።
ዐርብ ሮብ፡ ካስመራ በታች ያለ ገደል ።
ዐርብ ሮብ፡ የጦም ቀኖች ።
ዐርብ፡ ወርድ ጐን ስፋት (የሸማ - "ይህ ልብስ ዐርቡ ጠባብ ነው ") ።
ዐርብ፡ የሸማኔ ዕቃ ምስጢሩ የድር መግቢያነትን ያሳያል ።
ዐርብ፡ የቀን ስም (፮ኛ ቀን - ትርጓ ሜው የሰንበት መግቢያ ማለት ነው ") ። "ውሃን" እይ ።
ዐርብና ቀስት፡ ዐርብ የተባለ ጊጤ (ቀስት በቁሙ ወጊና ተወጊ ማለት ነው - ዳግመኛም ዐርብ "(ከሐርብ)" ቢወጣ ጦርና ቀስት ይባላል ") ።
ዐርቶ፡ ኰስቶ ። "አባትን" ተመልከት ።
ዐርቶ ገባ (ቦች)፡ ነፍስ ያላወቀ ቂጡን ' ያልጠረገ ልጅ ።
ዐርነት፡ ሐርነት ነጻነት ("(ሮሜ. ፮፥ ፳ - ፳፪)") ።
ዐርነት፡ ነጻነት—ዐራ (ሐራ) ።
ዐርኩ፡ በሐማሴን ጣሊያን የሚጠራ በት ስም ("ወዳጁ" ማለት ነው ") ። " (ግጥም)" - ሴቶች ፥ ተሰብሰቡ ፍል ውሃ ድረስ (ዐርኩ መኼዱ ነው እንድንላቀስ - ፲፱፻፴፩ ዓ ም) ።
ዐርኩ፡ የብረት አጣብቂኝ (ዕንጨትን ፥ ብረትን ጥራዝን አጣብቆ የሚይዝ ባለመ ዘውር የቀጥቃጮችና ያናጢዎች የጻፎች መሣሪያ ") ።
ዐርኬ፡ ዐምስት ስንኝ ያለው የስን ክሳር መርገፍ ግጥም (በእያንዳንዱ መልአክ ነቢይ ' ሐዋርያ ጻድቅና ሰማዕት ታሪክ መ ጨረሻ የሚነበብ - "ዐርከ ሥሉስ" የሚባል ሊቅ ስለ ደረሰው ዐርኬ ተባለ ይላሉ - ዳግመኛም ዐርኬ "(ዐርክየ)" ወዳጄ ማለት ነውና የወዳጅ ምስጋና መኾኑን ያስረዳል ") ።
ዐርኬና፡ የምሥጥ ንጉሥና ንግሥት ' መኖሪያ ቤት (በዙሪያው ብዙ ክፍልና በር ያለው - ሥራው ሠም ይመስላል - ንጥር ዕንጨት ነው ") ።
ዐርኬና፡ የንብ አውራ ዕልፍኝ ።
ዐርኬና፡ የጣዝማ መቀመጫ ።
ዐርክ (ዐረከ)፡ ወዳጅ ባልንጀራ ግጥ
ዐርኳታ (ዐር/ኳች)፡ ጥዳት የሌ ላት ሴት (ዐሣማ ዐይነት ጥርክርክ ") ።
ዐርዝ፡ ዛፍ አርዝ ።
ዐርፎ ዐርፎ፡ ቈርጦ ቈርጦ ። አስተራረፍ፡ አቀማመጥ (ማረፍ ") ።
ዐሮ፡ የመንቀፍና የማዋረድ ቃል ("ሰው የውን ዐር ሆይ" ማለት ነው ") ።
ዐሮ፡ ጠቍሮ ከስሎ ። "(ተረት)" - ዐሮም መሮም ማበሬን ከፈልኩ ።
ዐሸ (ሐሰየ)፡ ዳበሰ ዳሰስ ለወሰ አለፋ አፍተለተለ ዳመጠ አዞረ ጠመዘዘ ደረጠ (ውልቃትን ሊጥን ቈዳን ገላን ብል ትን ሆድን የዘነበለ ጋንን ኑግን ተልባን ነዶን ቈሎን ልስንን እሸትን - ሉቃ. ፮፥ ፩) ። "መከረን" አስተውል ። "ሳያሽ የበላ ዝንጀሮ ሲስል ያድራል" ።
ዐሸለ፡ ለካ—አሸለ ።
ዐሸመ (ሐሠመ)፡ ሲያዩት የማያ ምር ወፍራም ሽሩባ ሠራ (ጐነጐነ ደበለ ") ።
ዐሸቦ፡ ከመሬት የሚታፈሥ ደቃቅ አንኳር ጨው ። ፍችው ("ዐስብ") ዋጋ ዋጋ ነት ያለው ማለት ነው ።
ዐሸት (ሐስይ)፡ ማሸት ።
ዐሸት አደረገ፡ ዘወር ጠምዘዝ አደ ረገ ።
ዐሸን (ሐሴን)፡ ተባት ምሥጥ ባለ፬ ክንፍ ። ክረምት ሲገባ በብዛት ከመ ሬት ወጥቶ ባየር ውር ውር በማለቱ ክረ ምት አግቢ ' ይሉታል ።
ዐሸን፡ ዐተበ፡
ዐሸን ክታብ፡ የክታብ ዐሸን —ከተበ ።
ዐሸን፡ ደቃቅ ረቂቅ በረዶ = "ቧሒ ትን ዳሸንን" ተመልከት ።
ዐሸን፡ ጥቃቅን አንበጣ ኵብኵባ ምድር የሚያለብስ ።
ዐሸንጌ (ጌ/ዐሸን)፡ የምሥጥ ያን በጣ ዐሸን የሚፈላባት ምድር (የራያ ቈላ ") ። "ዐሸንጌው በረሓ ገዳይ መንኖ" እንዳለ ዝኆን ዐዳኝ ።
ዐሸድ ዐሸድ አለ፡ ሸፈፍ ሸፈፍ '
ዐሹራ (ዐረ)፡ ዓሥራት ካሥር ' ዐሻራ
ዐሺ (ዎች/ሐሳዪ)፡ ያሸ/የሚ ያሽ ወጌሻ ።
ዐሺታ (ሐሳዪት)፡ ያሸች/የምታሽ ፥
ዐሻ፡ ዐሰበ፡
ዐሻ፡ ዕሠይ ። "ዐሻ ገዳዎ ረ ፥ ዐሻ ገዳዎ" እንዳለ ዘፋኝ ።
ዐሻል —አራት እግሩ ነጭ ከብት—አሻል ።
ዐሻል፡ ጪው—አሻል ።
ዐሻሚ፡ ያሸመ/የሚያሽም (ጐንጓኝ ") ።
ዐሻሮ (ሐሠር)፡ ከነገለባው የተቈላ ጥምዝ ጠጕር—አሻራ ።
ዐሻሸ፡ ደባበሰ ። "(ግጥም)" - ዐሻሺኝና ጠ ቍሚኝና (ልስጥሽ አንድ ቍና ") ።
ዐሻሻ፡ ዐሾ ሸፋፋ ።
ዐሻዳ፡ እግርና እግሩን የሚያፋትግ (ዐሾ ") ። "ዐሸን" ተመልከት ።
ዐሽቶ ቀዳ፡ ጋንን ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ጥቂት ጥቂት እያዞረ ጠላ ቀዳ ።
ዐሽቶ፡ አዙሮ ጠምዞ ።
ዐሾ (ዎች)፡ እግሩን ከእግሩ ጋራ እያጣመረ እያሸ እያፈጋፈገ የሚኼድ ሰው ። "ዐሾ ገመዳ" እንዲሉ ። "ዐሻዳን" ተመልከት ። ማሸት (ሐስይ)፡ መለወስ ማልፋት (ማዞር መጠምዘዝ ") ።
ዐቀረ/ሐቀረ)፡ አስታቀረ (አ ስተሐቀረ)፡ ናቀ ነቀፈ አቃለለ አዋረደ ።
ዐቀቅ መቀቅ፡ ሙቀጫ ። የቅኔ ቤት አማርኛ ነው ።
ዐቀቅ ዘነዘናው፡ መቀቅ ሙቀ ው ።
ዐቀበ (ዐቂብ/ዐቀበ)፡ ቤተ ፥ ክሲ ያን ጠበቀ (መገበሪያ ፈጬ ልብምን መላ ሠየመ ") ።
ዐቀበ፡ አስጠጋ (ካብን ግንብን ዐፈር አስታቀፈ - ግድግዳን በሣር በቅጠል ሸፈነ ከለለ ") ።
ዐቀበት፡ ሽቅበት ዳገት (የቍልቍለት ተቃራኒ - ፪ዜና. ፳፥ ፲፮፡ ሉቃ. ፫፥ ፬) ። "ሸቀበን" አስተውል ።
ዐቀብ፡ ሽቅብ ወደ ላይ ።
ዐቀብተ ሀገር፡ አገር ጠባቆች ዘበ ኞች ።
ዐቀደ (ዐቂድ/ዐቀደ)፡ ለካ፥ወሰነ (ልክና ውሳኔ አደረገ ") ።
ዐቀደ፡ ቀሰተ አጐበጠ ።
ዐቀደ፡ ዐቀፈ፡
ዐቀድ፡ ቅስት ።
ዐቀድ፡ ብርሃን የሌለው ኮከብ ("(መዝ. ፻፵፰፥ ፫)" - ትርጓሜ ") ።
ዐቀፈ (ሐቀፈ)፡ በክንድ በደረት በ ጭን በክንፍ ያዘ ተሸከመ (ዐቈረ ደገፈ ") ።
ዐቀፈ፡ ተቀበለ ወደደ ልጅን ("ወይ ንቀፈው ወይ ዕቀፈው" እንዲሉ) ።
ዐቀፈ፡ ከበበ በዙሪያ ተቀመጠ ።
ዐቀፋ/ዕቅፊያ፡ ማቀፍ ።
ዐቃ (ትግ)፡ ዕቃ ። የቅዳሴ መምህ ራን ጻሕሉን ጥዋውን ዐቃ ይሉታል ።
ዐቃቂር፡ የመድኀኒት ቅመማቅመም ("እከሌ የነገር ዐቃቂር ያውቃል" እንዲሉ) ።
ዐቃቅማ (ዐቃብ)፡ የኵርንችት ኹለተኛ ስም ።
ዐቃቢ (ዎች)፡ ያቀበ/የሚያቅብ (ጠ ባቂ ፈይ ") ።
ዐቃቢት (ቶች)፡ ያቀበች/የምታቅብ/ ፈጪታ ።
ዐቃባ (ናህብ)፡ በዠማ ግራና ቀኝ የቆመ ዕለት ደገፍ ቃሊም ።
ዐቃቤ ሀገር፡ አገር ጠባቂ ዘበኛ ("ከጣሊያን ወዲህ ግን ፖሊስ ' ይባላል ") ።
ዐቃቤ ሕግ፡ የሕግ ጠበቃ (ስለ ሕግ የሚከራከር ") ።
ዐቃቤ ሰዓት ከብቴ፡ የጐንደር ሊቅ (በግእዝ ቋንቋ ምእላድ የጸፉ - በቅኔ ዕውቀት እጅግ የተራቀቁ - አራቱን ጉባኤ የሚያውቁ ") ። ዐቃቢነት፡ ዐቃቢ መኾን ።
ዐቃቤ ሰዓት፡ የሰዓት መኪና ጠባቂ (መይ አስተካካይ ") ።
ዐቃቤ ሰዓት፡ የሰዓት የጊዜ ልክ' ጠባቂ ሹም ("አንዱን በቃኸ ውጣ ሌላውን ግባ የሚል ") ።
ዐቃቤ ሥራይ፡ ባለመድኀኒት ("ፈረ ንጆች ፋርማሲ ' ይሉታል ") ።
ዐቃቤ ርእስ፡ ራስ ጠባቂ (በገላ ውስጥ የተቀበረ መድኀኒት - የማያስነካ ' የማያስመታ ድጋም ") ።
ዐቃጅ፡ ያቀደ/የሚያቅድ ።
ዐቃፊ (ፎች)፡ ያቀፈ/የሚያቅፍ (ልጅ
ዐቃፊ፡ ከባቢ ("ገበታ ዐቃፊ" እንዲሉ) ። "ሳንባን" እይ ።
ዐቃፋ፡ ጕድጓዳ ሸክላ ስፌት ።
ዐቄትዠር፡ ገንቢና ዐናጢ—አ ቄትዠር፡
ዐቈረ (ዐቊር/ዐቈረ)፡ ቋጠረ ው ሃን ደምን ("ጌሾ የወቀጥኹበት እጄ ውሃ ዐ ቈረ ") ።
ዐቈረ፡ ዐቀፈ ።
ዐቅ (ሐቀቀ)፡ ልክ መጠን ስፍር ("አንድ ዐቅ" - አራት ክንድ ሸማ ") ። "ሐቅን" ተመልከት "
አቅ፡ ልክ ፥ —ዐቅ ።
ዐቅለ በዳ (ሐቅለ በድው)፡ ጠል ልምላሜ የሌለበት በረሓ ምድረ በዳ
ዐቅለ ቢስ፡ ዕውቀተ መጥፎ ሰው ቀልበ ቢስ ።
ዐቅል (ሐቅል)፡ ዱር ።
ዐቅል (ዐረ)፡ አእምሮ ዕውቀት ።
ዐቅመ ሔዋን፡ ዐሥራ ዐምስት ' ዓ መት የመላው የልጃገረድ ሰውነት ገላ ። አ ከለ ብለኸ አካልን እይ ።
ዐቅመ ቢስ፡ አንከሲስ ደካማ ።
ዐቅመ አዳም፡ ሠላሳ ዓመት የኾ ነው ምሉ የጕልማሳ ሰውነት ፥ አካል ።
ዐቅመ አዳም አደረሰ፡ ለዘር በቃ ጐለመሰ ባለቀ ።
ዐቅሙን አያውቅ፡ ክፉ ስድብ (የ ጕልበቱን ልክ የማያውቅ ሰው አለአኩያው የሚጣላ የሚሳደብ ") ።
ዐቅም (ዐቀመ)፡ የሰው የንስሳ ያውሬ የመኪና ኀይል ብርታት ልክ መጠን ። "ቃረመን" "ድምቢጥን" ተመልከት ።
ዐቅም ዐጣ፡ ሰለተ ደከመ አበቃ ።
ዐቅራብ ውሃ፡ ጠንቋይ ላንዳንዱ ሰው "ኮከብኸ ዐቅራብ ውሃ ነው" ይለዋል ("የውሃ ጊንጥ" ማለት ' ነው ") ።
ዐቅራብ፡ የኮከብ ስም (ጊንጥ የሚመ ስል የጥቅምት ኮከብ ") ።
ዐቅራብ፡ ጊንጥ ("(ግእዝ)") ።
ዐቅደ ቢስ፡ ዐቅደ መጥፎ "
ዐቅድ ዐዋቂ፡ ምክርን ከሥራ አጣ ምሮ የሚያውቅ (በዠመረበት የሚጨርስ ") ።
ዐቅድ፡ ዘዴ ብልኀት ስልት ኹናቴ ክፍል ወገን ("እከሌ የነገር የጦር ዐቅድ ያውቃል" እንዲሉ) ።
ዐቋሪ፡ ያቈረ/የሚያቍር (ቋጣሪ ዐቃፊ ") ።
ዐቋራ፡ የታቈረ ቋጣራ ።
ዐበለ (ሐብለ/ዐበለ ቀለጠ)፡ ዋሸ/ ቀጠፈ/ሸፈጠ/ሸመጠጠ ።
ዐበለ (ትግ. ሐበለ)፡ ዐይን ላይ ጣለ ።
ዐበለ (ዐቢል/ዐበለ)፡ ቀለጠ/ወረደ/ ፈሰሰ (ተናዶ ጐረፈ) ።
ዐበለ፡ ከዳ/አሸቀሸቀ/ሸሸ/ተንሸራተተ ("መሬቱ ግንቡ ") ።
ዐበላ (ትግ. ሐበላ)፡ ያይን ሞራ (በ ግእዝ ሥዓዕ ይባላል) ።
ዐበላ፡ ፈሳሽ ("የደም ዐበላ" እንዲሉ) ።
ዐበሌ (ዐብሎ/ዐበለ)፡ አፋ ሰይፍ ("(ግጥም)" - ልጅ እንተሌ የተሳለ ዐበሌ - ቋንዣ አባላ ") ።
ዐበረ (ኀብረ)፡ አንድ ኾነ (በባሳብ በ ሥራ ገጠመ - "ዐደመን" ተመልከት) ።
ዐበረ (ዐቢር/ዐበረ)፡ ደረቀ/ቦና ኾነ ።
ዐበረ፡ ዐለፈ/ተሻገረ።
ዐበር፡ ዐባሪ ("ግብር ዐበር" እንዲሉ - "(ስም ዐበር)" - ሞክሼ ጠም ") ።
ዐበሻ፡ የነገድ ስም (ሐበሻ) ።
ዐበቀ፡ ጨመረ—አበቀ ።
አበቦች፡ በቁሙ አበባ ቅርጾች ጌጦች፡ (ማቴ ፮ ፥ ፳፰ ። ሉቃ ፲፪ ፥ ፳፯ ። ፩ነገ ፲ ፥ ፰) ።
ዐበዘ (ኀበዘ)፡ አሰፋ/ጋገረ።
ዐበዛ (ኀባዚ ት)፡ የጋገረ/የጋገረች የምትጋግር (ጋጋሪ) ።
ዐበዛ፡ ንብ ("የማር ዐበዛ" እንዲሉ) ።
ዐበዛ፡ የሙዝ እንቡጥ (በዛፉ ላይ ተንጨርጎ የሚታይ - "የሙዝ ዐበዛ" እንዲሉ) ።
ዐበዛ፡ የማድ ቤት አዛዥ ሹም ("የንጀራ የጠጅ የጠላ ዐበዛ" እንዲሉ) ።
ዐበዛ፡ የንጀራ ክምር (መቶ እንጀራ) ።
ዐበዛ፡ የጋጋሮች አለቃ (ዘፍ. ፵፥፩-፪) ።
ዐበዞች (ኀባዝያን ት)፡ የሚጋግሩ (ጋጋሮች) ።
ዐበየ (ዐብየ)፡ በለጠ/ከፍ አለ ።
ዐበጠ (ሐብጠ)፡ ተነፋ (ቅል እከለ መሰለ - ተነረተ ተቀበተተ) ።
ዐበጠ (ዐቢጥ/ዐበጠ)፡ ሳበ/ጐተተ (አለፈቃድ ከመንገድ መለሰ አወከ አስቸገረ በጠበጠ - ሰላምን ጸጥታን ዕረፍትን ነሣ - በት ግሪኛ ግን ዱብ አለ ተከመረ በላይ ኾነ አፈፍ አደረገ ይባላል - ይኸውም ያንበሳ የነብር የድመት አያያዝ ነው) ።
ዐበጥ፡ ዐበጠ ("(ተረት)" - ባለጠጋ ሊሰጥ የድኻ ሙርጥ ዐበጥ ") ።
ዐቢይ ርባታ)፡ በ፹ መደብ የሚረባ ኣንቀጽ ።"ይህ በግእዝ ነው ።ባማርኛ ግን ፷፩ ይኾናል" ።
ዐቢይ፡ ትልቅ/ታላቅ ።
ዐባ (ኀብአ)፡ ሸሸገ/ሰወረ/ደበቀ ("(ተረት)" - ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል ") ።
ዐባላ፡
ዐባሎ፡ ዛፍ—አባሎ ።
ዐባሪ (ዎች)፡ ያበረ/የሚያብር ("ዐባሪ ተነባባሪ" እንዲሉ) ።
ዐባሪም፡ ተርታ መናኛ እኸል ከጥሩው ጋራ የሚቀየጥ (ም ብዛትን ያሳያል - "አደፍን" አስተውል - አደፈ ") ።
ዐባሪነት፡ ዐባሪ መኾን።
ዐባር፡ ድርቅ (ዝናም የታጣበት ዘመን - ይህ ቋንቋ የግእዝ ሲኾን በሐረርጌ አውራጃ ይነገራል) ።
ዐባያ፡ እንቢተኛ ወይፈን ("አባያ") ።
ዐባይ (ዮች) (ሐባሊ)፡ ያበለ/የሚ ያብል ፪ ዋሾ/ቀጣፊ ("በሬ ወለደ ብሎ የሚያወራ - ዐባይና ሥንቅ እያደር ይቀላል እን ዲሉ ") ።
ዐባይ ሌባሻይ፡ ያልሰረቀውን የሚይዝ።
ዐባይ ሚዛን፡ አጕዳይ/ቀምጣይ ("የሚዛን ዐባይ ለእሳት የዳኛ ዐባይ ለሰንሰለት" እንዲሉ) ።
ዐባይ ምስክር፡ ያላየውን አየኹ ያልሰማውን ሰማኹ የሚል ።
ዐባይ ቀላጤ፡ ንጉሥ ዳኞች ያላሉትን ያላዘዙትን ብለዋል ባይ ("ቃልን" እይ) ።
ዐባይ፡ ቀጣፊ—ዐበለ ።
ዐባይ፡ ትልቋ/ታላቂቱ።
ዐባይ፡ ዠማ—አባይ ።
ዐባይ ዳኛ፡ ጕቦኛ/ፍርደ ገምድል/ አድላዊ ።
ዐባይ ጠንቋይ፡ የማይኾነውን ይኾናል እያለ የሚናገር ሐሰተኛ ደብተራ ("ዐባይ ጠንቋይ ቤት ያስፈታል" እንዲሉ) ።
ዐባጣ፡ ያበጠ (ታናሽ ጕብታ) ።
ዐባጣ ጐባጣ፡ ወጣ ገባ ስፍራ (በግእዝ መብእስ ወጐዳጕጽ ይባላል) ።
ዐባጭ (ሐባጢ)፡ የሚያብጥ ።
ዐባጭ (ጮች) (ዐባጢ)፡ ያበጠ/የ ሚያብጥ (አዋኪ አስቸጋሪ) ዞ ።
ዐብሎ መስካሪ፡ ዐባይ ምስክር።
ዐብሎ፡ ዋሽቶ/ቀጥፎ ("ዐብሎ አይደክም" - ፍጹም ዐባይ ዋሾ ቀጣፊ መልቲ ቈርጦ ቀጥ ") ።
ዐብረንታንት፡ የገዳም ስም (በዋልድባ ውስጥ የሚገኝ የበረሓ ገዳም - "ዐብረን ታንተ ጋራ እንኺድ" ማለት ነው) ።
ዐብሬ፡ ዐበሩ (የሰው ስም) ።
ዐብሮ መብላት፡ አለመሠሠት/መሳ ተፍ ።
ዐብሮ መኖር፡ አለመለያየት/አለመፋ ታት ("ከዚህም በቀር ዐብሮ መሥራት ዐብሮ መሞት እያለ ይነገራል - ንኡስ አገባብ ነው ") ።
ዐብሮ በቀል፡ ጋማ።
ዐብሮ፡ አንድነት/አንድጋ ኹኖ።
ዐብሮ አደግ፡ የዕድሜ ባልንጀራ እኩያ ባልደረባ ("(ተረት)" - ካብሮ አደግሽ አት ሰደድ ") ተፍ ።
ዐብሮ ኻያጅ፡ የመንገድ ጓድ ።
ዐብዛ፡ እንጀራ ("በና መ" ተወራራሽ ስለ ኾኑ ዐብዛ በማለት ፈንታ ዐምዛ ምጣድ እንዲሉ) ።
ዐብዬ፡ የጋሼ ታላቅ —አብዬ ።
ዐብደላ፡ በቡልጋና በወግዳ ክፍል ያለ ቀበሌ ።
ዐብደላ፡ ያምላክ ባሪያ (በዝርዝር ዐብድ አላህ ይባላል) ።
ዐብደላካኒ፡ ጥሩ የሐር ቀሚስ (መንግሥት ለጦር አለቆችና ለሌሎችም ሹማምት ለካህናት የሚሸልመው ባለቀለም ልብስ ሰንጠ ረዥ ወይም ሰንበር ያለው - ኣንዳንድ ሽማግሎች ዐብደልኻን የሚባል የህንድ ነጋዴ ከባሕር ስላመጣው ዐብደላካኒ ተባለ ይላሉ) ።
ዐብደል፡ የዛር ስም (ያረብ አገር ዛር) ።
አብዱ፡ የድኝ ጭቃ ።
ዐብድ (ዐረ)፡ ባሪያ (የተገዛ የተማረከ አገልጋይ) ።
ዐብድ መለክ (ዕብ. ዔቤድ ሜሌኸ)፡ ገብረ ንጉሥ (የንጉሥ ባሪያ - ኤር. ፴፰፥፯-፰, ፲, ፲፩, ፲፪ - የግእዝ መላሽ ግን አለ ስሙና አለምስጢሩ አቤሜሌክ - አበ ንጉሥ - የንጉሥ አባት ብሎታል - የስሕተት ስሕተት ነው) ።
ዐብድ ናጎ፡ የናጎ ባሪያ (ሚሳኤል ከሠለስቱ ደቂቅ ፫ኛው) ።
ዐብድ እልመሲሕ፡ የመሲሕ ባሪያ (ጎብረ ክርስቶስ) ።
ዐብጤ፡ የሰው ስም ("ጠላትን ዐብጥ አ ስቸግር" ማለት ነው) ።
ዐቦሬ (ዎች)፡ ታላቅ አንኮላ አፈ ሰፊ ("የዐቦሬ ምስጢር ብዙውን የጥልቂት ውሃ አንድ ማድረግ ነው ") ።
ዐቧራ፡ ያፈር/የደንጊያ/የንጨት/የሣር/የቅጠል ዱቄት ብናኝ ።
ዐቧሬ፡ ዐቧራ ያለበት የበዛበት ስፍራ (ባዲስ አበባ ውስጥ ያለ - ያቧራ ዐቧራዊ ማ ለት ነው - "ዐቧሬ ገበያ" እንዲሉ) ።
ዐቧር፡ የዛፍ ስም (የሾላ ዐይነት ዕንጨት ደሙ ሰባራ ዕቃ የሚያጣብቅ) ።
ዐተመ (ኀተመ)፡ ዘጋ ደፈነ (በማ ኅተም ረገጠ ተጫነ - እንዳይከፈት ምል ክት አደረገ - ዳን. ፮፥ ፲፯፡ ማቴ. ፳፯፥ ፷፮)
ዐተመ (በመኪና ጻፈ ") ።
ዐተረ፡ ቈረበጨ ተቋጠረ (ዐተር መሰለ ኣከለ ") ። በትግሪኛ ግን "ዐተረ" ያዘ ጨበጠ ተብሎ ይተረጐማል ።
ዐተሬ (ዐተራዊ)፡ የቂጥኝ ስም (ዐተር የሚያካክል ቂጥኝ ") ።
ዐተሬ (ዐተርየ)፡ የኔ ዐተር ።
ዐተር (ሮች)፡ ክብ እንክብል (ያበባ እኽል አገዳው እንደ ሐረግ ያለ - ኢሳ. ፳፰፥ ፳፯)
ዐተበ (ዐቲብ/ዐተበ)፡ ዕትብት ቈረጠ (ማተብ አሰረ ") ።
ዐተተ (ሐተተ)፡ መረመረ ተቸ ።
ዐተተ፡ ወገደ አተተ ።
ዐታሚ (ዎች)፡ ያተመ/የሚያትም (ማኅተም ያዥ - የማተሚያ ቤት ሠራተኛ ") ።
ዐታሞ፡ አማሪት—ተመመ ።
ዐታቢ (ዎች)፡ ያተበ/የሚያትብ (ዕት ብት ቈራጭ ") ።
ዐታች (ሐታቲ)፡ ያተተ/የሚያትት (መርማሪ ተቺ ") ።
ዐቸር፡ ዐሥረኛ የቀባርዋ ምት ።
ዐነቀ (ኀነቀ)፡ ጕረሮን ያዘ አሰረ
ዐነቀ፡ ሥጋ በጕረሮ ውስጥ ተወትፎ አላናግር ኣላስተነፍስ አለ ።
ዐነቀ፡ አጣበቀ ማደግ ከለከለ ("(ማቴ. ፲፫፥ ፯፡ ማር. ፬፥ ፯)") ።
ዐነቀፈ (ዐቂፍ ዐቀፈ)፡ የእግርን ጣት ገጯ መታ አሰናከለ ። "ወንቃፍን" ተመል
ዐነከሰ (ሐንከሰ)፡ ዐፈረ ተሰቀጠጠ የእግር ። ከዚህ የተነሣ ሰውየው ባንድ እግሩ ረገጠ አነከለ ("(ዕብ. ፲፪፥ ፲፪)") ።
ዐነገተ፡ ባንገት በደረት በዠርባ ተሸ ከመ አንጠለጠለ (ጠመንዣን መጻፍን እንስ ራን ") ።
ዐነጐተ፡ ዕንጐቻ ጋገረ (ለሕፃን ለረኛ ") ።
ዐነጠ (ሐነጸ)፡ ጠረበ ሸለተ ላፃ ፈ ለፈለ በሳ ቀረጻ መገዘ ዕንጨትን ።
ዐነጠ፡ ቤት ሠራ (መዝጊያን መስኮትን ገጠመ ") ።
ዐነጠሰ (ዐጠሰ)፡ ፊቱን ፥ አከፋ (አ ፉን ከፈተ - ባፍና ባፍንጫ ከበርበሬ ከክፉ ሽታ ከካፊያ ከጕንፋን የተነሣ በኀይል ተ ነፈሰ - ትንፋሹ ሲወጣ ተሰማ - ባፍንጫው ንፍጥ ባይኑ እንባ እስኪታይ ድረስ - ፪ነገ. ፬፥ ፴፭) ። ባላገሮች ሕፃን ከናቱ ማሕፀን በወጣ ጊዜ የሚያነጥሰው መልአክ ዐፈር አምጥቶ ሲያሸተው ነው ይላሉ ። ውሻም ሲያነጥስ እ ንግዳ ይመጣል ይባላል ።
ዐነጠጠ (ኀንጸጸ)፡ ፋቀ አለዘበ ሰ ነጠ አሰነበረ (ቀንድን ዋንጫ አበጀ ") ።
ዐናቂ፡ ያነቀ/የሚያንቅ (ጠላት ወጥመድ ") ።
ዐናቋ፡ የምድር ዕጥፋት (ወይም ቅንፋት - ያንድ በኩል ክበብ ፈሳሽን ዐንቆ የሚይዝ ") ።
ዐናት (ትግ/ሐናት)፡ ለግዳ ቅምሖ (የጕረሮ ውስጥ መንታ ዕብጠት የሚቧጠጥ ") ።
ዐናት (ቶች/ድማኅ)፡ መኻል ራስ ቍንጮ ያ
ዐናት፡ እንጥል ("ልጁ ዐናት ወረደው" እንዲሉ) ።
ዐናነጠ፡ ጠራረበ ላላገ ።
ዐናጢ (ዎች/ሐናጺ)፡ ያነጠ/የሚ ያንጥ (ጠራቢ ላጊ ቤተ ሠሪ ገበዝ ዐምባ ") ።
ዐናጢነት፡ ዐናጢ መኾን (ጠራቢነት ") ።
ዐንቃ፡ ዕንጨት—አንቃ ።
ዐንቋሊት፡ ዐይብ—አንቋሊት ።
ዐንበል፡ ሻለቃ ዐምበል ።
ዐንበሪ/ዐንበር (ግእዝ)፡ ታላቅ ዓሣ መርከብ የሚገለብጥ (ታናሹን ዓሣ የሚውጥ የሚሰለቅጥ - ዓሣ ነባሪ ") ።
ዐንበሬ ጭቃ/ዐንበራዊ ጭቃ፡ ወይም የዐንበር ጭቃ (ቅባትነት ያለው የባሕር ሽቱ ") ።
ዐንበር (ግእዝ)፡ የሽቱ ስም (ጥንታዊ ") ።
ዐንከስ (ሐንክሶ)፡ ማንከስ ።
ዐንከስ አለ፡ ዐሸድ አለ ።
ዐንካሲት፡ ያነከሰች/የምታነክስ ሴት እንስት ።
ዐንካሳ
ዐንካሳ (ሶች/ሐንካስ)፡ ያነከሰ/የ ሚያነክስ (ትክክል የማይረግጥ አንካላ - ኢሳ. ፴፫፥ ፳፫) ።
ዐንካሳ ነገር፡ እውነት ብቻ ያይዶለ
ዐንካሳዋ/ዐንካሳዪቱ፡ ያች ዐንካሳ ("(ሚክ. ፬፥ ፮ - ፯)") ።
ዐንካሴ (ሐንካሳዊ)፡ ወፈር ባለና ቅጥነቱ መጠነኛ በኾነ በትር ጫፍ ባንድ በ ኩል የተዋደደ ሹል ብረት ያንካሳ ምርኵዝ ቢወጉበት የሚያስነክስ ምዥራጥ ሽብዳ የመ ሰለው ኹሉ ("(፩ሳሙ. ፲፫፥ ፳፩)")
"
ዐንካስ፡ ዐንካሳ ።
ዐንካስነት፡ ዐንካሳ መኾን ።
ዐንገተ መቃ፡ ዐንገቱ 'ቷ መቃ የሚ መስል ("(የሚያምር)" ወንድ ሴት ") ።
ዐንገተ ሰባራ/ሸቍራራ/ዐይን ዐፋር
ዐንገተ ረዥሜ፡ ዐንገታም ዐንገተ ረዥም (የሜዳ ፍየል ዐይነት የበረሓ እን ስሳ ") ።
ዐንገተ ደንዳና (ኖች)፡ የሚመጣበ ትን የማያውቅ ("(ዘፀ. ፴፪፥ ፱)") ።
ዐንገቱን አዋቃ፡ አንገሸገሸ፡ አነቃነቀ፡ ከትከሻው፡ ጋራ፡ አማታ ።
ዐንገቱን ደፋ፡ አቀረቀረ ("(ኢሳ. ፰፥ ፲፬)") ።
አንገታገተ፡ አመላለሰ/አንገዛገዘ ።
ዐንገት (ቶች)፡ በቁሙ (ከዕልቅት በላይ ካገጭ በታች ያለ ገላ ራስ ተሸ ካሚ - ከወደ ኋላ ማዥራት ይባላል - ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ሐዋርያት ዐንገት ላንገት ተያይዘው አለቀሱ - "(ካንገት በላይ)" - ከሆድ ከልብ ያልኾነ ነገር - "(ተረት)" - ዐንገት ለምን ተፈጠረ - አዙሮ ለማየት ") ።
ዐንገት፡ ሰመግ ።
አንገት በቁሙ፡ ዐንገት።
ዐንገት፡ ዐራዳ በር (በተራራ መካከል ያለ ጠባብ መተላለፊያ ") ።
ዐንገትጌ፡ ያንገት ስፍራ (ዐንገትን የሚ ሸፍን የእጀ ጠባብና የቀሚስ የጥብቆ ክሣድ - በስተላይ ያለ ጫፍ - ዘፀ. ፳፰፥፴፪) ።
ዐንገች፡ አገረ ወገብ (ከቈላ በላይ ያለ ") ።
ዐንጋች (ቾች)፡ ያነገተ/የሚያነግት (ሰ ናድር ያዥ ") ።
ዐንጋችነት፡ ዐንጋች መኾን ።
ዐንጓች፡ ያነጐተ/የሚያነጕት ("ዐዛኝ ቅቤ ዐንጓች" እንዲሉ) ።
ዐንጣሽ፡ ያነጠሰ/የሚያነጥስ ።
ዐንጣጭ (ጮች/ጎንጻጺ)፡ ያነጠጠ የሚያነጥጥ (ፋቂ ዋንጫ እንዝርት ሠራተኛ ") ።
ዐኘከ (ሐነከ)፡ ቈረጠመ በላ ገተገተ አላመጠ አላመ አመነዠኸ አመሰኳ ። "ዐኝከኸ ዐኝከኸ ወደ ወገንኸ ዋጥ" እንዲሉ ። ዐኛኪ፡ ያኘከ/የሚያኝክ (አላማጭ ") ።
አኘከ አላመጠ፡ ዐኘከ።
ዐኛኘከ፡ ቈረጣጠመ በላላ ።
ዐኝ፡ መንከስ መብላት ።
ዐኝ መንከስ፡ ዐኘከ ።
ዐኝ አለ፡ በጥርስ ያዘ ነከሰ በላ ።
ዐኝ አለ፡ ነከሰ,—ዐኘከ ።
ዐኞ፡ ሲያኝኩት የማይደቅ ሥጋ ማንጆ ።
ዐኞ፡ ችኮ ሰው ።
ዐከለ (ዕብ ዐካር)፡ ዐዘነ አለቀሰ (ተቸገረ ") ።
ዐከመ (ሐከመ)፡ ያበጠውን አፈ ረጠ (የጐረበውን ላጠ - ሀገመ ተኰሰ በጣ ቀደደ ጠገነ መድኀኒት ሰጠ አጠጣ አዋጠ በመርፌ' ወጋ - አስታመመ ፈወሰ አዳነ ") ።
ዐከረ፡ ያበባ እኸል ዘራ—አ ከረ ።
ዐከበ፡ ሰበሰበ—አከበ ።
ዐከተ፡ ሰብስቦ አሰረ—አከተ ።
ዐከከ (ሐከከ)፡ በጥፍር በንጨት በመሬት ገላውን ፎከተ (ፈገፈገ - የደግ - "ጠቈ መን ነዘገን" ተመልከት ") ።
ዐከከ፡ በቀላል ላገ ፋቀ ዕንጨትን ።
ዐከከ፡ ወረ ቧጠጠ ሰነዘረ (ሰውን እንስሳን አንበሳ ነብር - የክፉ ") ።
ዐኪም (ሞች/ሐኪም/ሞች)፡ በሽታንና መድኀኒትን ኹሉ የሚያውቅ ፲ ፈዋሽ አዳኝ ወጌሻ ("ያንጐል ያይን የዦሮ የጥርስ የሆድ ዐኪም" - ሐኪም - እንዲሉ - "ዐኪም የሕ ዝብ ሐኪም የካህናት አነጋገር ነው ") ።
ዐካሚ (ዎች)፡ ያከመ የሚያክም (ዐጋሚ ") ።
ዐካከከ፡ መላልሶ ዐከከ ።
ዐካኪ "አካኪ" ተብሎ ቢጻፍ ግን (አዋኪ አሸባሪ በጦር ሜዳ ተከራካሪ የጐበዝ ጐበዝ ማለት ነው - ፩ሳሙ. ፲፯፥፵፮—፶፩) ።
ዐካኪ (ሐካኪ)፡ ያከከ/የሚያክ (ቧጫሪ ቧጣጭ ሰንዛሪ ጥፍራም አውሬ ") ።
ዐካኪ ዘራፍ፡ የፉከራ ቃል ("ዐካ ኪን የሚዘርፍ የሚቀማ ካንበሳ ከድብ በግን የሚያስጥል" - ፩ሳሙ. ፲፯፥፴፬—፴፯) ።
ዐካካ፡ ኹለንተናው ዕከክ "
ዐወሰ/ሖሰ)፡ አስታወሰ ("(አስ ተሐወሰ)" - ዐሰበ - አሳሰበ - አስታወሰ ዐሰበ ተብሎ መፈታቱ (ዐወሰ) በቀን ብዛት ስለ ተዘነጋ ነው ") ።
ዐወረ (አዖረ)፡ ኹለት ዐይን ዐጠፋ (ዕውር አደረገ - ከለለ ጋረደ አጨለመ ሰወረ ") ።
ዐወረ (ዐወሰ)፡ ዐይን ማጣት ("ካይን ማየት የልብ ዕውቀት" እንዲሉ - "(በው ቀት/ባለውቀት)" - እያወቀ ሳያውቅ - ዐውቆ ወዶ ፈቅዶ ") ።
ዐወቀ (ዖቀ)፡ ተማረ/አጠና/ለመደ/ ተረዳ (ለየ ልብ አደረገ አስተዋለ ሠለጠነ - መሳ. ፲፯፥፲፫፡ ፲፰፥፫፡ ዮሐ. ፬፥፶፫ - "(ተረት)" - ለራሱ አያውቅ ነዳይ ቅቤ ለመነ ላዋይ - ሴት ታውቅ በወንድ ያልቅ ") ።
ዐወቀ፡ ብለኽ፡ ዐዋቂን፡ እይ።
ዐወደ (ዖደ)፡ ዞረ (ክብ ኾነ ") ።
ዐወደ፡ ቈራረጠ (መላልሶ ዐጨደ ") ።
ዐወደ፡ ዑድኛ ሸተተ (አልባብ አል ባብ አለ - አጋሙ ርጐፍቱ የሎሚ እሸቱ - ደን ኹሉ በጥቅምት ያውዳል ") ።
ዐወጀ (ዖደ)፡ እየዞረ ዐዋጅ ነገረ ለፈፈ ።
ዐወገ (ዖገ)፡ ጠመመ/ተወላገደ ።
ዐወጠ (ሐወጸ)፡ ጐበኘ ።
ዐዋሪ፡ ያወረ/የሚያውር ።
ዐዋሽ (ሐዋሽ)፡ የወንዝ ስም (የሺ ዋንና የሐረርጌን ግዛት እየለየ ወደ አዳል በረሓ የሚወርድ - ካዲስ አበባ በስተደቡብ ያለ ታላቅ ዠማ ከሜ ተራራ የሚነሣ - በክረምት መልቶ መፍሰሱን መትረፉን መትረ ፍረፉን በዐውሳ በረሓ ብዙ ሜዳ መያዙን መንጣለሉን - በበጋ ግን መሥረጉን ማነሱን መጕደሉን ባሕረ ሸሽ መኾኑን ያሳያል - እሱም ባጤ ዘርዐ ያዕቆብ ታሪክ ሐዋሽ ይባ ላል - ምስጢሩ በሖሰ ዘይቤ መነቃነቅንና መን ቀሳቀስን ያስረዳል ") ።
ዐዋሽ (ሾች)፡ ታላቅ ጋን ገች (፭ ቍና እኸል የሚጠምቅ - ዐዋሽ ወንዝ ወደ ርሱ ከሚገቡት ወንዞች እንዲልቅ - ዐዋሽ ጋ ንም ከጋኖች መብለጡን ጠጁ ወይም ጠላው በብዙ እንስራና ማድጋ መቀዳቱን ያሳያል ") ።
ዐዋቂ (ቆች)፡ ያወቀ/የሚያውቅ ("(መዝ. ፻፯፥፵፫፡ ኤር. ፱፥፲፪)") ።
ዐዋቂ፡ ጠንቋይ/ሐኪም/ወጌሻ/ፈላ ስፋ ("የምድር ዐዋቂ" እንዲሉ - "(የሚዛን ዐዋቂ)" - ሚዛን መመዘኛ ማስተካከያ ብረት ርሳስ ደን ጊያ - ዘሌ. ፲፱፥፴፮፡ ኢሳ. ፵፥፲፭፡ ራእ. ፲፮፥፳፩ - በግእዝ መክሊት ይባላል - "(አላዋቂ)" - ያላወቀ የማያውቅ - ደንቈሮ - አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለ ቀልቃል - "(የልጅ ዐዋቂ)" - ጭምት የረጋ - ቁም ነገርን የሚከተል - "(መጣፍ ዐዋቂ)" - ሊቅ መምር - "(ነገር ዐዋቂ)" - ጠበቃ - "(ሥራ ዐዋቂ)" - ባለማያ ") ።
ዐዋቂ፡ ጨዋ ሽማግሌ (ያምሳ ዓመት ሰው - በግእዝ ልሂቅ ይባላል ") ።
ዐዋቂት፡ ነፍስ ።
ዐዋዜ፡ የዐዋዝ (ፍሬው ከወጣ ቀይ ዛላ በርበሬ የተዘጋጀ ብትን ወይም ብጥብጥ ድልኽ የሥጋ መብሊያ ሲያዩት ደስ የሚያ ሠኝ - ይኸውም ከተቀቀለ ነጭ ሽንኵርት ጋራ ይላማል - ነጭ አዝሙድ ኰረሪማ ዝን ጅብል የበሶብላ ፍሬ ይገባበታል ") ።
ዐዋዝ (ሓወዘ/ሐዋዝ)፡ ያማረ/ የጣፈጠ ።
ዐዋዝ፡ ዐወቀ ።
ዐዋዲ፡ የወንዝ ስም (ከይፋት ፈልቆ ወደ ግራ ይዞርና ዐዋሽ የሚገባ ዠማ - በግእዝ የዞረ የሚዞር ዘዋሪ ማለት ነው ") ።
ዐዋጅ (ዐዋዲ)፡ ያወጀ/የሚያውጅ (የሚለፍ ለፋፊ ") ።
ዐዋጅ (ዐዋድ)፡ ከመንግሥት ለሕዝብ የሚነገር ደንብ/ውሳኔ/ትእዛዝ ("ዐዋጅ ዐዋጅ የደበሎ ቅዳጅ" -
"ያዋጁን በዦሮ" እንዲሉ) ።
ዐዋጅ መንገሪያ፡ ከፍተኛ ስፍራ ዕወጃ (ለፈፋ ") ።
ዐዋጅ ነጋሪ (ነጋሬ ዐዋድ)፡ ዐዋጅን የሚነግር ("ስማ ስማ ባይ" - ዮሐ. ፩፥፳፫) ።
ዐዋጅ፡ ዘዋሪ ("ዐይን ዐዋጅ ኾነበት" እንዲሉ) ።
ዐውላ፡ የማር ርሾ አውላ ።
ዐውሎ ነፋስ (መንፈሰ ዐውሎ)፡ ጥቅል ነፋስ ጠሮ ኵርፊት ኀይለኛ (ቤት የሚያፈርስ መርከብ የሚገለብጥ ዐፈርን ባሕ ርን ወደ ላይ የሚያነሣ የሚያቆም - መዝ. ፲፩፥፮፡ ፪ነገ. ፪፥፩፡ ሕዝ. ፩፥፬) ።
ዐውሳ (ዐረ. ዐውጻህ)፡ የበረሓ ስም (ያዳል አገር ምድረ በዳ ") ።
ዐውሳ፡ ዐዘበ ።
ዐውቂያ (ዐውቅ)፡ የሚያውቁት ሰው ።
ዐውቅልሽ፡ ጥንቈላ ።
ዐውቆ አበድ፡ ሳያብድ ኾነ ብሎ ያበደ ("(ሲያውቅ አበድ)" - ዝኒ ከማሁ ") ።
ዐውቆ ፈረንጅ፡ ሳይማር እንደ ፈረንጅ የሚለብስ ።
ዐውዛ (ሐውዝ)፡ አፍልተው፥ የሚ ጠጡት የት ውሃ የጨብጥ መድኀኒት ።
ዐውዜን፡ የእኸል ጐተራ—ሐ ውዜን ።
ዐውዜን ያገር ስም፡ ሐው ዜን ።
ዐውደ ነገሥት፡ የጥንቈላ መጣፍ (፲፮ ክብ ሰንጠረዥ ያለው - ዐረቦች "ጠላዋት አልሙሉክ" ይሉታል ") ።
ዐውዳመት (ዐውደ ዓመት)፡ ያመት ዐውድማ (መስከረም ሲብት ባመት የሚከብር በዓል - ቅዱስ ዮሐንስ የዘመን መለወጫ - ያመትን መዞርና የሕዝብን ስብ ስባ ያሳያል - ዳግመኛም አጿማትና በዓላት ተሰብስበው በመስከረም ፩ ቀን ይነገራሉና ውዳመት ተባለ ይላሉ - ገናና ጥምቀት ፋሲካ ዕርገት ጰራቅሊጦስ መስቀል ሌላውም ታላላት በዓል ኹሉ ዐውዳመት ይባላል ") ።
ዐውድ፡ አደባባይ/ሸንጎ (የሕዝብ መሰብሰቢያ - ጥጋብ ሲበዛ ዐውድ ይጥላል ") ።
ዐውድ፡ ዙሪያ/ክበብ ።
ዐውድ፡ የቍጥር ስም (ክብነት ያለው ቍጥር ባለሰንጠረዥ - "ዐውደ ጨረቃ ዐውደ ፀሓይ" እንዲሉ) ።
ዐውድ፡ ጻሕል/ሳሕን/ዝርግ/ሰታታ/ወጭት (ክብ የቍርባን መቀመ ") ።
ዐውድማ፡ ዙሪያማ ባለዙሪያ (እኸል የሚወቃበት ምርት የሚታፈሥበት ኵልኵል ያለው ወለል - ይኸውም አስቀድሞ ውሃ እየተ ርከፈከፈ በጭድ በገለባ ይረገጣል - ቀጥሎም በበት ይለቀለቃል - ማቴ. ፫፥፲፪ - ሲበዛ ዐውድ ሞች ይላል - ዮኤ. ፪፥፳፬ - "(የወይን ዐውድማ)" - የወይን ፍሬ መርገጫ ") ።
ዐዘለ (ሐዘለ)፡ በዠርባ ላይ ተሸ ከመ ("እንቡቡ አለ" - ያዘ ለጠፈ ደረበ ") ።
ዐዘል፡ ዝኒ ከማሁ (ያዘለ ያዘለች - "ለቆ ዐዘል አውራ ዐዘል" እንዲሉ) ።
ዐዘሎ፡ የተራራ ስም (ባዳል በረሓ ውስጥ ያለ ረዥም ደብር የመናኞች ኖሪያ ") ።
ዐዘመ፡ በሰው ክፉ መድኀኒት አደ ረገ ፲ ኣፈዘዘ እደነዝዘ (እደነዘዘ ") ።
ዐዘቅት፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም በገደ ልና በወንዝ ውስጥ ያለ ዋሻ (የግሑሣን መ ኖሪያ - በግንብ የተዘጋ ") ።
ዐዘቅት፡ የውሃ የኵስ ጕድጓድ ።
ዐዘበ (ሐዘበ)፡ ጠለፈ/አያያዘ/አወ ራረሰ/አገናዘበ/ቈለፈ (መሚያን ሠራ ") ።
ዐዘበ (ዐዝቦ ዐዘበ)፡ ጣለ/ወረ ወረ/አሽቀነጠረ ።
ዐዘበ፡ ጐነጐነ (ቋድ አበጀ ዕዛብ ") ።
ዐዘቦ፡ አገር—አዘቦ ።
ዐዘቦት፡ ሥራ የማይሠራበት ሰሞን ("በግእዝ በዓለ ተሐውሶ ክብረ ቅዱሳን ይባላል - ዛሬ የሥራ ጊዜ ነውና ይህን ነገር ባዘቦቱ ቀን እንነጋገረዋለን ") ።
ዐዘነ (ሐዘነ)፡ ተከዘ/አለቀሰ/ተጸ ጸተ/ራራ/ተቈረቈረ/ተከፋ/ተቀየመ ("(ዘፍ. ፮፥፮፡ ፪ሳሙ. ፲፱፥፪፡ ዮሐ. ፲፩፥፴፫)") ።
ዐዘነተኛ (ኞች)፡ ዐዘን ያለው (ዐ ዘን ያጠቃው የጐዳው - አልቃሽ አባትና እናት ሚስት ልጅ ወንድም እት ዘመድ ወዳጅ የሞቱበት - ንብረቱ የጠፋበት ታላቅ አደጋ ያገኘው የደረሰበት ሰው ") ።
ዐዘና፡ ርኅራኄ/ጸጸት ።
ዐዘኔታ፡ ቸርነት/ደግነት/ርኅራኄ/ ምሕረት ።
ዐዘን (ሐዘን)፡ ለቅሶ/ትካዜ ("(ዮሐ. ፲፮፥፮፡ ፪ቆሮ. ፪፥፫)" -
"(አልቃሽ)" - የሞተው ወንድምሽ የገደለው ባልሽ - "ዐዘንሽ ቅጥ ዐጣ ከቤትሽም አልወጣ ") ።
ዐዘን ተቀመጠ፡ ፯ ወይም ፵ ቀን አለቀሰ (ለቅሶኛ ተቀበለ ") ።
ዐዘን ተፍሥሓ፡ መወለድና መሞት ማጣትና ማግኘት ሰርግና ለቅሶ ("ይህን የመ ሰለ ኹሉ ባንድ ቀን ቢደረግ ዐዘን ተፍሥሓ ይባላል" - መዝ. ፴፥፭) ።
ዐዘንተኛ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዐዘንተኞች፡ ዐዘነተኞች ("(ዮሐ. ፲፮፥ ፳፪)") ።
ዐዘዘ (ዐዝዞ ዐዘዘ)፡ በለጠ/ተረፈ/ ጠና ።
ዐዘዞ፡ አገር—አዘዞ ።
ዐዚማም፡ ዐዚም ደጋሚ ባለዐዚም ።
ዐዚም፡ አፍዝ/አደንግዝ ።
ዐዛሚ፡ ያዘመ/የሚያዝም (አፍዛዥ ") ።
ዐዛቢ (ዎች)፡ ያዘበ/የሚያዝብ (ጐ ንጓኝ አያያዥ ") ።
ዐዛባ፡ ከመሬት ካፈር ጋራ የላቈጠ እበትና ፋንድያ (በጠጥ ከበረት ከጋጣ ውስጥ አውጥተው የሚጥሉት ") ።
ዐዛት፡ አፈ ሰፊ ቀጪን ቁመተ ሾጣጣ ዓሣ ።
ዐዛኝ (ኞች)፡ ያዘነ/የሚያዝን (ርሩ - "ዐዛኝ ማሪያም" እንዲሉ - "(ተረት)" - ዐዛኝ ቅቤ ዐንጓች ") ።
ዐዛኝቱ፡ ርኅሩኂቱ ርግብ ሆዷ ወላ ላዋ ማሪያም ("(የባለጌ ግጥም)" - የተማሪ ወዳጅ ይቅር ምናባቱ - ጐራዴ ሲመዘዝ ይላል ባዛ ኝቱ - "(የገለሞታ መልስ)" -እንኳን ባዛኝቱ ይበል በሥላሴ - እኔ እወደዋለኹ እስቲወጣ ነፍሴ ") ።
ዐዛውንት (ትግ. ዐዘወ/ደግ ኾነ)፡ ደግ/ደገኛ/ጥኑ/ጠንካራ/ታላቅ/ጪዋ ሽማግሌ (ማለፊያ ሰው መታፈርና መከበር ያለው - በግእዝ ልሂቅ ይባላል - ትግሮችም ዕዝው ይሉታል ") ።
ዐዛውንት፡ የዕዝው ብዥ ሲኾን በአማርኛ ስላንድ ይነገራል ("ይኸውም በግእዝ አነጋገር ኅጻውንት ዐቃርብት ባለው ይታወቃል - ዳግመኛም አውሬ አውሬዎች በማለት ፈንታ አራዊት አራዊቶች እንደ ማለት ያለ ነው - "ዐዞን" ተመልከት ") ።
አዛውንት፡ ጨዋ፡ ዐዛውንት ።
ዐዛውንቶች፡ ደገኞች/ታላላቆች/ጩ ዋዎች/ጐምቱዎች ።
ዐዛዜ፡ ባለትልቅ ፍሬ ስንዴ (ጥናት ጥንካሬ ያለው ዐመድማ ") ።
ዐዛዩን ነካሽ፡ ክፉ ሰው ወረታ ቢስ ወዳጁን ጐጂ ።
ዐዛይ (ዮች/ሐዛሊ)፡ ያዘለ/የሚ ያዝል (አባት - የምታዝል እናት - እንስት ጦጣ ዝንጀሮ - ተሸካሚ - "ሀ ባይ ዳውላን ዐዛይ" እንዳለ ተማሪ ") ።
ዐዞ (ትግ)፡ ሖምጣጣ መጣጣ (ነጭ ሽንኵርትና ሰናፍጭ የገባበት ርጎ ለሰርግ የሚኾን - "(ግጥም)" - እኅቶችኸ የሉ ወይ እና ትኸ የሉ ማን ሠራልኸና ዐዞ በላኸ ኣሉ ") ።
ዐዞ (ዐዘዘ)፡ የባሕር አውሬ (ሆደ መጋዝ ጋድሚያ እንቅልፋም - ዘሌ. ፲፩፥፴ - ያገኘውን ሰውና እንስሳ በዥራቱ እየጠለፈ ወደ ባሕር ይዞ ይገባል - እንስቲቱ ባሸዋ ውስጥ ዕንቍላል ትወልዳለች - ከዚያም ገላግ ልት ይወጣሉ - ሲበዛ ዐዞዎች ያሠኛል - አዘ ዘና ዐዞ በአማርኛ ይተባበራሉ - "(ግጥም)" - ልጄን ኣትጥሉብኝ ቢያዛችኹ ተሹሞ - አዐ)ዞ አያውቅምና ከዚህ አስቀድሞ ግባተ መሬቱን አትድገሙ እናንተ - ታዞ ኺዷል እንጂ ልጄ መቼ ሞተ - ላንድ ቀን ትእዛዝ ሰዉ ይመረ ራል - የኔ ወንድም ታዞ አባይ ላይ ይኖራል - "(ኣባቱና እናቱ እቱ)") ።
ዐዞ ዐረግ፡ ጥኑ ጠንካራ ዐረግ ("አበባው እድልኸ ይገባል ቅጠሉንም በክንድ ላይ ያሰሩት እንደ ኾነ ኣቃጥሎ ያቈስላል - ዐዞ ከያዘች እንደማትለቅ ያዞ ዐረግም ማሰሪ ያነት ጥብቅ መኾኑን ያሳያል - "ዐዛትን" ተመ ልከት ") ።
ዐዞ እንዳለፈው ትግሪኛ፡ ከል ዐረብኛ ነው ።
ዐዞ ከል፡ የስንዴ የወይን የበለስ ቅ ጥራን ።
ዐዠም (ዐጀም)፡ ዐጣ ።
ዐየ (ዐየነ)፡ ተመለከተ/አስተዋለ/ተኰረ (ዐይኑን ጣለ ") ።
ዐየረ (ዐይሮ ዐየረ)፡ ቀላቀለ ደባ ለቀ አዋዋደ ።
ዐየር፡ ሰማይ/ነፋስ—አየር ።
ዐየበ (ሔበ)፡ አረጋ (ዐይብ አበጀ አዘጋጀ - ጠለቀ ቀዳ ") ።
ዐያሪ፡ ያየረ/የሚያይር (ቀላቃይ አዋ
ዐይብ (ሐይብ)፡ አጓትና ቅቤ የወ ጣለት የወተት አተላ (ከንጀራ ጋራ የሚ በላ - "(ተረት)" - ከይሉኝ አይል ዐይብ አትብላ ") ።
ዐይነ ሌባ፡ አመንዝራ (ባይን የሚሰ ርቅ የምትሰርቅ - "የማነሽ ቀዘባ አንች ዐይነ ሌባ" እንዳለ ዘፋኝ ") ።
ዐይነ ልም፡ ዐይነ ደካማ (ቅንድበ
ዐይነ፡ ልም፡ እ ንዲሉ ።
ዐይነ ልብ፡ የልብ ዐይን ።
ዐይነ መዓት፡ የቍጣ ዐይን ።
ዐይነ ማዝ፡ ማዝ የሚባል' ያይን በሽታ (የሚበላ የሚያሳክክ ") ።
ዐይነ ምሕረት፡ የምሕረት የይቅርታ' ዐይን ።
ዐይነ ምድር፡ ኵስ ዐር ("(ኢሳ. ፴፮፥፲፪)") ።
ዐይነ ምድር፡ የምድር ዐይን የተባለ ፊን ጥጣውና ጕድጓዱ ነው ።
ዐይነ ሞራ፡ ያይን ሞራ (ዐበላ - "ዐ ረረ" ብለኸ "ዕርርትን" ተመልከት ") ።
ዐይነ ሥቡን አለው፡ ዐይኑን መ ታው ኣነጐደው ።
ዐይነ ሥብ፡ ያይን ጕድጓድ ("ሥብ የተባለ ነጩ ነው ") ።
ዐይነ ስውር (ሮች)፡ ዐይኑ ባለማ የት የተሰወረ የተከለለ ።
ዐይነ ሥጋ፡ ግዙፍ የሥጋ ዐይን ።
ዐይነ ርግብ፡ ትንሽና ትልቅ ኹለት የድጕስ መሣሪያ ።
ዐይነ ርግብ፡ ከሽቦ የተበጀ የተዘ ጋጀ ጥልፍልፍ ውስብስብ ።
ዐይነ ርግብ፡ የሐር ክር ትት (የወ ይዛዝር ፊት ጌጥ - "ርግብ አይተው መራራታ ቸውን ያይናቸውን ማማር ያሳያል ") ።
ዐይነ ርግብ፡ የደርብ ሰበስብ ጌጥ (በተ በሳሳ ሳንቃ የተሠራ - ፬ነገ. ፯፥፬፡ ፪ነገ. ፩፥፪) ።
ዐይነ ሸውራራ፡ ዐይነ ጠማማ (ወ ይም ' ወልጋዳ ") ።
ዐይነ በጎ፡ ከጨጓራ ጋራ የሚገኝ የብጥብጥ ምግብ (ሥጋዊ ከረጢት ሰፍነግና ባ ለማያ ሴት የጋገረችው ነጭ ጤፍ እንጀራ መ ሳይ ") ።
ዐይነ ባር፡ እንደ መስተዋት ያለ ብራና (የባሕር ዐይነት ጽፈትን በዠርባው የሚ ያሳይ - "ፈረንጆች ትራንስፓራን ይሉታል ") ።
ዐይነ ባና፡ ዐይኑ ባና የመሰለ ፈ ረስ ለምጦ ።
ዐይነ ብሩት (ብርህተ ዐይን)፡ አነባበሮ (ባለብዙ ዐይን ") ።
ዐይነ ብር፡ ድመት ።
ዐይነ ተኵላ፡ ክብ ሞላላ የማር መቍረግ ሸክላ ጪስ መያዣ (ባለብዙ ዐይን - ብስ - ተኵላ የተባለ ቀፎ የሚደፋ ዐራጅ ነው ") ።
ዐይነ ተኵላው ጠፋ፡ የነገሩ መ ላው ኹኔታው ቅጡ ታጣ (ቸገረ - ዐይኑ ባከነ ተቅበዘበዘ ") ።
ዐይነ ነፍስ፡ ረቂቅ የነፍስ ዐይን ።
ዐይነ ወርቅ፡ ሰውን ወደ እንስሳነ ትና ዕቃነት የሚለውጥ ምትሀተኛ ጠንቋይ ።
ዐይነ ወርቅ፡ ዐይንን ብጫ ወርቅ የሚያስመስል የሐሞት በሽታ ።
ዐይነ ወግ፡ ባይን ወግቶ የሚያሳምም ቡዳ ።
ዐይነ ውሃ (ያይን ውሃ)፡ ውሃ የሚመስል ያይን ብረት ።
ዐይነ ውሃ፡ ዘሎ ባይኔ (የውሃ ዐ ይን ክብ እንክብል ") ።
ዐይነ ውሃ፡ የቅኔ ስም ።
ዐይነ ደረቅ፡ ዕፍረተ ቢስ ("የሌባ ዐይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ" እንዲሉ) ።
ዐይነ ደረቅ፡ ያየውን የሚያደርቅ
ዐይነ ደካማ፡ ዐይኑ የደከመ ።
ዐይነ ገመድ (ገመደ ዐይን)፡ ያይን ገመድ ልክ (ማየት ") ።
ዐይነ ገብ፡ የሚያምር መልክ ።
ዐይነ ጥላ፡ ጥላ ከፀሓይ ሙቀት እ ንዲከልል (የሰው ልቡና ትጋትን ዕውቀትን እንዳያገኝ የሚያደርግ የስንፍና መንፈስ ") ።
ዐይነ ጥላ፡ ጸሎት በእንተ ዐይነ ጥላ ብሎ የሚዠምር ያስማት ክታብ ።
ዐይነ ጨምጫማ፡ ዐይኑ ኹል ጊዜ የሚያለቅስ ።
ዐይነተኛ፡ ባለመልክ (ዋና ሰው ግን ባር ቀደም መደበኛ ስሙና ግብሩ የታወቀ - ቀዋሚ ነገር ") ።
ዐይነተኛነት፡ ዋናነት (መደበኛነት - ዐ ይነተኛ መኾን ") ።
ዐይነተኞች፡ ዋኖች ሰዎች በዓሎች ("(፪ዜና. ፰፥፲፡ ሕዝ. ፵፬፥፳፬)") ።
ዐይነታ፡ ጭገሬታ መሰል ዐይነት "
ዐይነት (ሕብር)፡ ልዩ ልዩ መልክ ያለው ፍጥረት (ሥራው ኹኔታው እየራሱ የኾነ ወገን ነገድ ጠባይ - "ምን ዐይነት" -
"ዐይ ነቱ የማይታወቅ" እንዲሉ - የንጨት የደንጊያ የሣር ያውሬ የወፍ የንስሳ የከብት የሰው ዐይነቱ ብዙ ነው - "(ምግብ መጠጥ ልብስ ዕቃ በያይነቱ)" - በየመልኩ በየቀለሙ ማለት ነው ") ።
ዐይነት፡ አምሳያ ምሳሌ ("መልክንና ሕብርን" ተመልከት ") ።
ዐይነት፡ ዐይንነት (ዐይን መኾን
ዐይነት፡ ዕከክ ቍስል (ስፋቱ ዐይን የሚያካክል ") ።
ዐይነቶች፡ መልኮች ቀለሞች ቍስሎች ።
ዐይኑ ላይ ጣለበት፡ ጉም አስመ
ዐይኑ ቀላ)፡ በር በሬ መሰለ ።
ዐይኑ ቍራኛ፡ ያይን ዘበኛ (ወይም እስረኛ ") ።
ዐይኑ ብር አለ፡ ከሳ ጐደጐደ ።
ዐይኑ ተመረገ)፡ አልገለጥ አለ።
ዐይኑ ተሰወረ)፡ ታወረ (ኣላይ አለ) ። ተሰወረ ረቀቀ።
ዐይኑ ተንከራተተ፡ በብዙ ወገን አየ (የሚፈልገውን ለማግኘት ") ።
ዐይኑ ተጐለጐለ፡ ወጣ ፈጠጠ ።
ዐይኑ ዐ፡ ዐይን የሚጻፍ በዐ ስለ ኾነ ' የዐ ' ስም ዐይኑ ተባለ ።
ዐይኑ ደገደገ፡ ወየበ ብጫ መሰለ
ዐይኑ ደፈረሰ፡ ነጩና ጥቍሩ አል ተለየም ።
ዐይኑ ጠገበ፡ ከማእዱ ብዛት የተ ነሣ ሳይበላ በማየት ጠገበ ።
ዐይኑ ጠፋ፡ ታወረ (አላይ አለ ") ።
ዐይኑ ጠፋ፡ ጫፉ ታጣ (የፈትሉ የሐሩ የሽቦው የክሩ ") ።
ዐይኑ ፈሰሰ፡ ጠፋ ወደመ ።
ዐይኑት (ቶች)፡ ከጭንቍላ'የምታንስ
ዐይኑን ሰካ፡ ባለማቋረጥ አስተዋለ ።
ዐይኑን ሰካ)፡ ተኰረ (ትክ ብሎ አየ) ።
ዐይኑን ባይኑ አየ፡ አስመስሎ ወለደ ።
ዐይኑን ተከለ፡ ትክ ብሎ አየ (ተ ኰረ - ግብ. ሐዋ. ፮፥፲፭) ።
ዐይኑን አራመደ፡ ከቅርብ ወደ ሩቅ ተመለከተ ።
ዐይኑን አነሣ፡ አቀና ።
ዐይኑን አያሳየኝ አለ፡ ፈጽሞ ጠላ መረዘ ።
ዐይኑን ገለጠ፡ ዐወቀ ዐዋቂ ኾነ ።
ዐይኑን ገደለ፡ አጨለገ ጨነቈረ ።
ዐይኑን ጣለ፡ አስተያየቱን ባንድ ነገር ላይ አደረገ ።
ዐይና (ሱርስት)፡ ዐይን ("አንድ ዐይና አራት ዐይና" እንዲሉ - በግእዝ ግን "ዐይኗ" ማለት ነው ") ።
ዐይናማ (ሞች)፡ ዐይነ ትልልቅ ("ው/ዋ/ዪቱ" በመጨረሻ ሲጨመሩበት - "ዐይናማው/ዐይናማዋ/ዐይናማዪቱ" እያለ ወንድና ሴትን ይለያል ") ።
ዐይናማ ደንጊያ፡ እንደ ንብ እንጀራ ብስ ጠቃጠቆ ያለው ።
ዐይናማዬ፡ የኔ ዐይናማ ("የዘፈን አዝ ማች" ነው ") ።
ዐይናር፡ ያይን ዐር (ያይን እድፍ ") ።
ዐይኔን ዕጠቡኝ አለ፡ ፈጽሞ እንቢ ኣለ ።
ዐይን (ኖች)፡ የማየት ሕዋስ (በንስ ሳና ባውሬ በወፍ በሰው ፊት ግራና ቀኝ የተተከለ ኹለት ሥጋዊ መብራት ብርሃን - ዙ ሪያው ነጭ መካከሉ ጥቍር - በማየት ከኹሉ ይፈጥናል - "ካይን የፈጠነ ከውሃ የቀጠነ" እን ዲሉ - ርሱ ሲጠፋ አካል ኹሉ በጨለማ ይኖ ራል - ማቴ. ፯፥፳፪፥፳፫) ።
ዐይን ላይን ተሳበረ፡ ዐይን ካ ይን ጋራ በመተያየት ተሸናነፈ ።
ዐይን ላይን፡ ፊት ለፊት ።
ዐይን፡ በቍና ይሰፍራል (የክፉ መጨረሻ ነው - ክፋትን "ይህ ቀረኝ" እያለ ይ ሠራል ") ።
ዐይን፡ በተንቀሳቃሽ መኪና ግንባር ያለ የኤሌትሪክ ብርሃን ።
ዐይን ባይን፡ እየታየ (በግልጥ - "አንዳ ንዱ ሌባ ዐይን ባይን ይሰርቃል ") ።
ዐይን፡ ብስ ቀዳዳ ("የንጀራ ዐይን የ መርፌ' ዐይን" እንዲሉ) ።
ዐይን ዐምባ፡ የቀበሌ ስም (በእን ሳሮ ውስጥ ያለ መንደር ") ።
ዐይን አበባ፡ ብጫ ጥለት ።
ዐይን አብራ፡ የዐይን ሐኪም ።
ዐይን አወጣ፡ አበጀ/አሳመረ ።
ዐይን አወጣ፡ አፈሰሰ/አጠፋ/አፈ ጠጠ (ዕፍረት ዐጣ ") ።
ዐይን ዐዋጅ፡ ዘዋሪ ዐይን ("ዐይን' ዐዋጅ ኾነበት" እንዲሉ) ።
ዐይን አውጣ፡ ባለጌ (ዐይንን የሚያ ወጣ - ዕፍረት የለሽ - ፩ሳሙ. ፲፩፥፪) ።
ዐይን ዐፋር (ሮች)፡ ዐንገተ ሰባራ ሰውን የሚያፍር የሚፈራ (ቀና ብሎ የማያይ - "ዐይን ዐፋር" ለሴትም ይነገራል - "ዐይን ዐፋር ልጃገረድ ከወንድ ታረግዛለች" እንዲሉ) ።
ዐይን፡ የልቃቂት ፈትል ጫፍ ("ዐይን ዘርፍ ይዞ ከአንቀጽ አስቀድሞ እየገባ በዘርፍ ነትና በባለቤትነት በቅጽልነትና በበቂነት በ ተሳቢነት ይነገራል ") ።
ዐይን፡ የንጨት ጕጥ (የቅጥይ መብቀያ ") ።
ዐይን፡ የፊደል ስም (ዐ ") ።
ዐይን ጣለ፡ አስተያየቱን ባንድ ነ ገር ላይ አደረገ ።
ዐይንና ዐፈር፡ ተጣይ የማይሰማማ ባለጋራ ።
ዐይንኸ ላፈር አለ፡ ዐይንሽ ው ስጥ ዐፈር ይግባ (ሞተኸ ተቀበር አለ - ረ ገመ ") ።
ዐደለ (ዐዲል/ዐደለ)፡ ለኹሉ በመ ደዳ በነፍስ ወከፍ ሰጠ/አሳለፈ/አስተናበረ ("(ፍርድ ዐደለ)" - በየነ ፈረደ ") ።
ዐደሌ (ዐደላዊ)፡ ዐደልማ (የዐደል ዓይነት ወንዴ ጥጥ ጧፍና መናኛ ልብስ የሚ ኾን ") ።
ዐደል (ዐድል)፡ ጥኑ/ጠንካራ/ሻካራ (እንደ ማስ ሰበከት ያለ ") ።
ዐደል፡ ዐደመ ።
ዐደመ (ዐድሞ ዐደመ)፡ ጠራ/ቀ ጠረ ("በዚህ ቀን ና" አለ ለሰርግ ") ።
ዐደመ፡ አሤረ (ሰውን ሰበሰበ በድብቅ በስውር ዶለተ መከረ ነገር ቋጠረ - ዐድማ አደረገ ክፉ ለመሥራት ") ።
ዐደመ፡ የሰው ስም ።
ዐደስ፡ ባርሰነት—አደስ ።
ዐደስ፡ ዐወጀ ።
ዐደረ (ኀደረ)፡ ባንድ ቤት ወይም ስፍራ ሌሊቱን አሳለፈ/አነጋ ("(ዘብ ዐደረ)" - ጠበቀ - "(ለግዜር ዐደረ)" - የጽድቅ ሥራ ሠራ - "(ለጌታ ዐደረ)" - ተጠጋ አሽከር ሎሌ ኾነ - "(ጦም ዐደረ)" - እራት አልበላም ምንም አልቀ መሰም - "(ሳይታረስ ዐደረ)" - ቀረ ቈየ - "(ተረት)") ።
ዐደረ፡ ሕዝብን ሰበሰበ (ቁም ነገር ለመሥራት - ዐድሮ ቈይቶ የሚገኝ ሥራት ሠራ ደነባ እጸና የማይፈርስ የማይለወጥ አደ ረገ ዐገገ ") ።
ዐደረ፡ በጥንቃቄ ተጠበቀ ።
ዐደራ በላ፡ የማይታመን (ከዳተኛ ሸፍጠኛ እምነተ ቢስ ") ።
ዐደራ በሰማይ፡ ዐደራ በምድር (ች ስለ ሕፃን ልጁ የሚያደርገው ኑዛዜ - ምድር ሰው ሰማይ እግዜር ") ።
ዐደራ አለ፡ ባደራ አኖረ/አስቀ መጠ/አስጠበቀ ("የሙት ቀናተኛ ሚስቴን ዐደራ ይላል" -
"(ተረት)" - ዐደራ ቢሏቸው ይብ ሳሉ እሳቸው ") ።
ዐደራ ከታች፡ የታመነ ጨዋ ሰው ።
ዐደራ፡ የተጠበቀ ጥብቅ (አኑርልኝ ጠብቅልኝ አሳድግልኝ ብሎ ለሰው የሰጡት ዕቃ ከብት ገንዘብ ማንኛውም ነገር ኹሉ - ግብ. ሐዋ. ፲፬፥፳፮ - "ያደራ ገንዘብ ያደራ ልጅ" እንዲሉ) ።
ዐደራ ጥብቅ ሰማይ ሩቅ፡ ዐደራ የጠበቀ ነው (ሰማይ የራቀ ነው ") ።
ዐደር (ኅዲር)፡ ማደር ("ዋለን" እይ) ። ማደር፡ ሌሊትን ማሳለፍ/መኖር ። ማደር፡ ከሰው መጠጋት (አሽከር መ ኾን ") ።
ዐደር፡ ዐዳሪ ("ዕርስ ዐደር" እንዲሉ) ።
ዐደር፡ ያደረ ያለ የቈየ ("በጅ ዐደር ወርቅ ርካሽ ነው ") ።
ዐደነ (ትግ. ሐደነ)፡ በረሓ ገባ (ሻ ለገ - ፈለገ ፲ ሸመቀ አደባ - ያዘ ሳበ አቀረበ ወጋ ገ ደለ - ዘፍ. ፳፯፥፴፩) ።
ዐደን፡ ታድኖ የመጣ ሥጋ ("(ዘፍ. ፳፯፥ ፳፭)") ።
ዐደን፡ የማድባት የመግደል ሥራ ("(ተረት)" - የንጉሥ ልጅ ዐዘን ቢነግሩት ዐደን) ።
ዐደየ፡ መለሰ/ከፈለ ።
ዐደየ፡ ሰጪ ብ'መሰለ ነጣ ነጭ ኾነ ("ኦሮ ነጭን ዐዲ ፀሓይን ዐዱ የሚለው ከዚህ የወጣ ነው ") ።
ዐደይ አበባ፡ በመስከረም የሚፈነዳ የምድር ጌጧ ሽልማቷ ("ዐደይ ላሰባ ቅጽል ወይም ዘርፍ ነው" -
"ሉልን" አስተውል ") ።
ዐደይ፡ የሰጪጪ ብጫ የኾነ አበባ (የመስቀል ለት ልጃገረዶች አክሊል የሚያደ ርጉት - "(ግጥም)" - ዐደይ ዐደይ የመስከረም ሱስ ንዮስ ንጉሠ ሮም ") ።
ዐደዳ (ዐዲድ/ዐደደ)፡ ንዝንዝ ጭቅ ።
ዐደገ (ኀደገ)፡ ተወ/ለቀቀ ።
ዐደገ (ትግ. ገዛ)፡ መለሰ/አቀና/ቀጥ አደረገ (ጐባጣ ዕንጨትን በመቍረጥ ") ።
ዐደገ፡ ቁመት ጨመረ—አደገ ።
ዐደፈ (ኀደፈ)፡ ጠረገ/ዐሠሠ/ወለ ወለ ("አበሰን" እይ) ።
ዐደፈ፡ እድፋም ኾነ—አደፈ ።
ዐዲስ ልብስ፡ ዐርበ ወጥ ያልተ ለበሰ ።
ዐዲስ ነገር፡ ዘመን አመጣሽ ።
ዐዲስ ዓለም (ሐዲስ ዓለም)፡ መንግሥተ ሰማይ (ጻድቃን ታድሰው ረቀው የሚወርሱት ") ።
ዐዲስ ዓለም፡ ካዲስ አበባ በስተምዕ ራብ ያለ ከተማ ።
ዐዲስነት፡ ዐዲስ መኾን ።
ዐዲት፡ ለሴት/ለእንስት ይነገራል ።
ዐዳ፡ ዐፍንጫ ደፍጣጣ ዝንጀሮ
ዐዳ፡ የሚታጨድ እኸል (መከር - "ዐጨዳዬ ረገፈ አለ" - ቸኰለ ተጣ ") ።
ዐዳል፡ የነገድ ስም—አዳል ።
ዐዳሚ፡ ያደመ/የሚያድም (ጠሪ ቀጣሪ እሢያሪ ") ።
ዐዳሩ ሞቀ፡ ራሱን ቻለ/ከበረ ።
ዐዳሩን መጣ፡ ለማደር መጣ ።
ዐዳሩን ኼደ፡ ሊያድር ኼደ ።
ዐዳሪ (ኀዳሪ)፡ ያደረ/የሚያድር ("(ዱር ዐዳሪ)" - ሽፍታ ወንበዴ ዘላን - "(ጦም ዐዳሪ)" - ምስኪን) ።
ዐዳሪ፡ ሎሌ ታዛዥ ("የጌታ ዐዳሪ" እንዲሉ) ።
ዐዳሪዎች፡ የሚያድሩ (ዘበኞች ጠባቆች) ።
ዐዳር፡ ማደር ("ላንድ ቀን ዐዳር" እን ዲሉ) ።
ዐዳር ቀና፡ ሰላ ማለፊያ ኾነ ።
ዐዳር፡ ትዳር ("(ምሳ. ፴፥፰፡ ሉቃ. ፳፩፥፴፬)" -
"የጠፋ ዐዳር ከለማ አንድ ነው" እን ዲሉ - "(የጌታ ዐዳር)" - አሽከርነት ሎሌነት ") ዲሉ ።
ዐዳኝ (ኞች)፡ ያደነ/የሚያድን (የሚ ፈልግ የሚያደባ የሚሸምቅ - አድቢ ሸማቂ - ዐ ዳኝ ውሻ ጭገር ባፋ በትር ትርፋ እንዲሉ - "(ግጥም)" - ዐዳኝና መናኝ በረሓ ነው ቤቱ እን ዲህ እንዲህ ልበል እኔው ባለቤቱ - "(ዝኆን ገዳዩ)") ።
ዐዳኝነት፡ ዐዳኝ መኾን (ፈላጊነት ሸ ማቂነት ገዳይነት) ።
ዐዳይ (ዮች)፡ ያደለ/የሚያድል (አሳ ላፊ አስተናባሪ ") ።
ዐዳይነት፡ ዐዳይ መኾን (አሳላፊነት) ።
ዐዳጊ፡ ያደገ/የሚያድግ (መላሽ ") ።
ዐዳፊ (ኀዳፊ)፡ ያደፈ/የሚያድፍ (ጠራጊ ዐሣሽ ") ።
ዐዴ፡ የዐድ ዐይነት (ወይም ወገን ") ።
ዐድ፡ ዝኒ ከማሁ (አንኮ ") ።
ዐድመኛ (ኞች)፡ ዐድማ ወዳድ ባለዐ ድማ (ያድማ አለቃ ሤረኛ ") ።
ዐድመኛነት፡ ዐድመኛ መኾን ።
ዐድማ መታ፡ ዐደመ ሤራ ቈረጠ አ ደረገ ።
ዐድማ፡ ተንኰልና ክፋት ያለበት ም ክር/ሤራ/ዱለት ።
ዐድር ብዬ፡ ተለማማጭ ።
ዐድሮ፡ ሌሊቱን አሳልፎ ።
ዐድሮ ኻያጅ፡ እንግዳ መንገደኛ ።
ዐድዋ፡ በትግሬ ክፍል ያለ አገር (በ፲፰፻፹፰ ዓ. ም. የካቲት ፳፫ ቀን እሑድ ዐጤ ምኒልክ ከጣሊያን ጋራ ተዋግተው ድል ያደረጉበት ") ።
ዐዶ (ዐደወ/ዕድው)፡ በበረሓ የሚ ቀመጥ ዐዳኝ (ያውሬ ጠላት ባለጋራ ") ።
ዐዶ (ዐፅ)፡ ባዶ/ባድማ/በረሓ/ደን ("በትግሪኛም አገር ዐድ ይባላል ") ።
ዐዶ (ኦሮ)፡ የቃልቻ አስተርጓሚ ።
ዐዶ ነዳይ (ነዳየ ዐፅ)፡ የምድረ በዳ ድኻ (ጠጕሩ የተንጨረፈፈ ቤት ንብረት የሌለው - "ዐጥን" ተመልከት ") ።
ዐዶ ከቢር (ሮች)፡ ዐፍለኛ ወንድና ሴት እየያዘ የሚያስገዝፍና የሚያስጨፍር ዛር (የብልግና የዝሙት አሠሪ ክፉ መንፈስ - ሲፎክርም የትግሬ ልጅ እባብ ዐለንጋው አሸዋ ልብሱ ዳዊት ደጋሚ ይላል - "ከበረን" እይ ") ።
ዐዶ፡ ከዝኆን ኰቴ የተበጀ እንደ መ ጋዝ ያለ ያዳኝ አንባር ።
ዐዶ ወሸባ፡ ያዳኝ ዘፈን አዝማች ("ዐዶ ወሸባ ዐዶ ወሸባዬ ዐዳኝ ወሸባ ጓሮዬ" እንዲሉ) ።
ዐጀለ (ዐገለ)፡ ሸፈነ/አለበሰ/ጠቀ ለለ/ስለሰለሰ (ደረቅ ቈዳን በቅጠል ገላን ባብሽ ") ላሽ ።
ዐጀሚ/ዐጀማዊ፡ የዐጀም የፋርስ ሰው ("(ኢሳ. ፳፰፥፲፩)") ።
ዐጀም ኰንታ፡ ዐጀም እንዳለፈው (ኰንታ ኵርድ - ወይም በኢትዮጵያ በዳር አገር ኰንታ የሚባል ዘር የዐጀም ዘርፍ የኾነ ይመስላል - ጊዮርጊስ ወልደ ሐሚድም ኰን ታን ኵርድ ይለዋል) ።
ዐጀም፡ የነገድ ስም (በፋርስ ውስጥ የሚገኝ አረመኔ ቀማኛ ሕዝብ - ይህ ባረብኛ ነው - ቈላ. ፫፥፲፩ - በግእዝም ዐዠም ሀገሪት ሐቃል ይባላል) ።
ዐጀረ (ዘኀረ/ትግ. ዐዘረ/ተ መካ)፡ አሰፋ/ዘረጋ/አሳበጠ/ነፋ/አኰራ/አስታበየ/ኣስመካ ።
ዐጀረ፡ ዐደሰ ።
ዐጀበ (ዐረ. ሐጀበ/ሸፈነ)፡ ከበበ/ ተከተለ (ጌታውን እመቤቱን ") ።
ዐጀበ (ዐጺብ/ዐጸበ)፡ ገረመ/ደነቀ።
ዐጀበ፡ ሰበሰበ/አከማቸ/መሰገ/አንድ ላይ አደረገ/ዐጨቀ ።
ዐጀበ፡ ዐደለ ።
አጀበ፡ ከበበ ፥ —ዐጀበ ።
ዐጀባ፡ ከበባ/ክተላ (መጋረጃ - "(ግጥም)" - እንዳላይሽ እንዳላይሽ ዐጀባ ኹኗል ጥላሽ - ባጀባ የሴት ስም) ።
ዐጀብ፡ ብዙ ጭፍራ/ሰራዊት ("የሻለቃው ዐጀብ ይሰበር ይመስላል ") ።
ዐጀብ ና ጃሎ፡ እንዲል ሐ ርበኛ ።
ዐጀብ፡ እ የወለዱ ማጀብ ።
ዐጀብ፡ ዕጹብ ድንቅ ግሩም ።
ዐጀብ፡ የመክበብ/የመከተል ኹኔታ ("ዛሬ ዐጀብ አለብኝ" እንዲል ወታደር) ።
ዐጃ (ዐዘዘ)፡ የእኸል ስም (ከነገለባው ተዘርቶ ከነገለባው የሚመርት አኸል የስንዴ የዐዛዜ ዐይነት - ኢሳ. ፳፰፥፳፭ - "(ተረት)" - ዐጃ ወቅጦ ቢዘሩ ተመልሶ ከዘሩ ") ።
ዐጃቢ (ቦች)፡ ያጀበ/የሚያጅብ (ከባቢ ተከታይ ሰብሳቢ አካባቢ ") ።
ዐጃይ፡ ያጀለ/የሚያጅል (አልባሽ አለስ ") ጫን ።
ዐጅሪት፡ ወንዲት አንበሲት (እንደ ያይልና እንደ ዮዲት ያለች ሴት - መሳ. ፬፥፳፩፡ ዮዲ. ፲፫፥ ፰, ፱፲) ።
ዐጅራች (መዝኅራት)፡ ገለሞቶች ።
ዐጅሬ (መዝኅራዊ)፡ እሱ የዐጅር ወገን (አኵሪ አትንኩኝ ባይ - "(ሽለላ)" - ወንድ ልጅ ተወልዶ ካልተባለ ዐጅሬ እሜዳ ስደ ዱት ሣር ይብላ እንደ በሬ ") ።
ዐጅር (አዝኃሪ)፡ ያጀረ/የሚያጅር (የሚያኰራ የሚያስታብይ - አስመኪ ") ።
ዐጅሮች (መዝኅራን)፡ የሚያኰሩ የሚያስመኩ (አኩሪዎች አስመኪዎች ወንዶች ጐበዞች ") ።
ዐገለ (ዐግሎ/ዐገለ)፡ ጫረ/ ዐፈር አስታቀፈ ተክልን ።
ዐገለ፡ መለሰ/ዐደሰ ቂጥኝን።
ዐገመ (ሐገመ)፡ ሳበ/ጠባ/መጠጠ/ መጠመጠ (መጥፎ ደምን አወጣ) ።
ዐገም (ሐጊም)፡ ማገም ።
ዐገም ጠቀም፡ ደግ ወይም ክፉ የማይባል ሥራ (እነገር ኹሉ መግባት እዚ ያም እዚያም ማለት - ዐገም ጠቀም ቀዶ መስፋትን ያሳያል) ።
ዐገሠ)፡ ዐግሦ/ዐገሠ ። አስታገሠ (አስተዐገሠ)፡ አስቻለ (ትግሥት ሰጠ ዝም አሠኘ አጸና) ።
ዐገሸ፡ አቋተ/ደቀነ ።
ዐገተ (ዐጊት/ዐገተ)፡ የዋስን ገንዘብና ዕቃ ወሰደ (ሰብልን ክልክልን ኣትክልትን የበላ ከብትን ከቦ ያዘ ወደ በረቱ አገባ ") ።
ዐገዘ (ሐገዝ)፡ ረዳ ("ሥራን ድካምን ተካፈለ" - ዕዝ. ፯፥፴፮) ።
ዐገዜታ፡ ዝኒ ከማሁ (ርዳታ) ።
ዐገገ (ሐገገ)፡ ደነባ/ወሰነ/ደነገገ (ሕግ ሥርዐት ሠራ - "ሐገገን" እይ) ።
ዐጕለቲ፡ ያጕል ወገን ።
ዐጕሊጥ (ዐጕለቲ)፡ ቧልተኛ ዋዘኛ ።
ዐጕሊጥ፡ ዐጒል ሊጥ ማለት ይመስላል።
ዐጕል፡ መጥፎ የጠባይ የግብር (እካብ አይገባ ድንጋይ) ።
ዐጕል ሰው (መጥፎ ጌጥ ") ።
ዐጕል፡ ዐጕልነቱ በብዙ ወገን የሚታይ (ኹለት ልብ - ፬ነገ. ፲፰፥፳፩) ።
ዐጕል ጊዜ፡ ለሥራ የማይመች ሰዓት ።
ዐጋሚ (ዎች)፡ ያገመ/የሚያግም ("ዦ ሮን" ተመልከት ") ።
ዐጋም፡ እሾኻም ዕንጪ ት—አ ጋም ።
ዐጋች (ቾች)፡ ያገተ/የሚያግት (ያዥ ዋስ - "ዐጋች" እንዲሉ) ።
ዐጋዥ (ዦች)፡ ያገዘ/የሚያግዝ (ረዳት - ፊልሞ. ፩፡ ፊልጵ. ፬፥፫ - "(ተረት)" - ባሪያ ዐጋዥ ብታገኝ መጇን ደበቀች ") ።
ዐጋዥ ግንድ፡ ከፊት ግንድ ቀጥሎ የተተከለ (ድርን በማፈጋፈግና ወጥሮ በመያዝ የፊት ግንድን ስለሚያግዝ ዐጋዥ ግንድ ተ ባለ ") ።
ዐጋዥ፡ ጥርስ የሌለው ማጭድ ጐዣሜ ።
ዐጋይ (ሐጋይ)፡ በጋ ("ጤፍ ዐጋይ" እንዲሉ) ።
ዐጋይ (ዮች)፡ ያገለ/የሚያግል (ኰትኳች - "አትክልት ዐጋይ" እንዲሉ) ።
ዐጋይነት፡ ኰትኳችነት ።
ዐጋጊ (ሐጋጊ)፡ ያገገ/የሚያግግ (ደንጋጊ - ያዕ. ፬፥፲፪) ።
ዐጐለ አስቀረ፡ አጐለ።
ዐጎት፡ ያባት/የናት ወንድም አ ጎት ።
ዐጐዛ፡ ጌጠኛ ደበሎ (የረኛ የጦረኛ ልብስ በለምድ ዐይነት የተዘጋጀ ሸማ ማገዣ - ዘሌ. ፲፫፥፵፰, ፵፱ - "(የባሕር ዐጐዛ)" - ነጭ ሐር የሚመስል ረዥምና ለስላሳ ጠጕር ያለው የታናሽ እስያ ፍየል ሎፊሳ - "ሱፋላን" እይ ") ።
ዐጓት፡ የወተትውሃ—አጓት ።
ዐጓጕሊት፡ ወንድ አይሏት ሴት የማት ረባ ።
ዐጓጕል (ሎች)፡ ያጕል ዐጕል (ፍጹም ") ።
ዐጠረ (ሐጸረ)፡ ዕንወት ተከለ (ገ ረገረ ማገረ ሸመጠጠ ጀጐለ ቀጠረ - የጠርብ የሳንቃ ዐጥር አበጀ - ገነባ ካበ ከበበ ዙሪያ ውን ዘጋ - "(አርቆ ዐጠረ)" - በዳር በወደብ በወ ሰን በድንበር ምሽግ አደረገ - ጠላትን ተከላ ከለ ") ።
ዐጠረ (ኀጽረ)፡ ዐጪር ኾነ (ቁመቱ ዕድሜው አነሰ - "(እጅ ዐጠረው)" - ገንዘብ ዐለ ቀበት ") ።
ዐጠረ (ዐረ)፡ ሸተተ (አማረ ተዋበ ") ።
ዐጠረ (ዐጽሮ/ዐጸረ)፡ ጠመቀ (ጨ መቀ ዘለለ - መሸተ ") ።
ዐጠረ፡ መሸተኛን ዐጣሪን ፥ አስገበረ (ከልክ አሳልፎ ቀረጠ ") ።
ዐጠረ፡ አመነዘረ (ነውር ሠራ ") ።
ዐጠረ፡ ዕጥርን ጥለትን ማተብን የ ጪስ ዕንወትን ዕጣንን ሼጠ ለወጠ ሸቀጠ በማታለል ("ቸረቸረን" እይ ") ።
ዐጠራ፡ ያጥር ሥራ (ከበባ ") ።
ዐጠቀ/ዐጢቅ ዐጠቀ)፡ ታ ጠቀ (በወገቡ ላይ ሰይፍን ዝናርን ሽጕ ጥን ሱሪን ቀሚስን ቀበቶን አሰረ ሸብ አደ ረገ - መቀነትን ጠመጠመ - ሸማን አደገደገ - ዘፀ. ፲፪፥፲፩፡ ፩ሳሙ. ፲፯፥፴፱፡ ኢሳ. ፴፪፥፲፩ - "(ባጪር ታጠቀ)" - ለሥራ ለጦርነት ተዘጋጀ - "ያረገዘች ታስታውቅ ከደረቷ ትታጠቅ" እንዲሉ - "ቦዶነን ሸነቀረን" አስተውል - ስላልተለመደ ነው እንጂ - "(ዐጠቀ)ን" አሰረ ቀነተ - "ታጠቀን" ታሰረ ተቀነተ ቢል በቀና ነበር - "(ከተለ)" ብለኸ "ተከተለን" -
"ዐቀፈ" ብለኸ "ታቀፈን" ተመ ልከት ") ።
ዐጠበ (ኀፀበ)፡ ረገጠ/አንጨፈጨፈ/ ዐሸ/አጐረፈ/ለቀለቀ/አጠራ/አነጣ/አጸዳ (እድፍን አስለቀቀ - "(እጄን ዐጠበኝ)" - ክፉኛ ቈረጠኝ - "(ተረት)" - እጅ ሲያጥቡት ያድፋል ልጅ ሲመክሩት ይጠፋል - "ዐወቅሽ ዐወቅሽ ቢሏት መጣፍ ዐጠበች ") ።
ዐጠበ፡ ሰረቀ/አሞለጩ ።
ዐጠባ (ኀፀባ)፡ የማጠብ ሥራ (ረ ገጣ ልቅለቃ - "ልብስ ዐጠባ" እንዲሉ) ።
ዐጠብ፡ ሌባ/ሰራቂ ።
ዐጠነ (ሐፀነ)፡ አሳደገ ልጅኝ ("ዐጠ ነን አሳደገ" ማለት ኣልተለመደም ") ።
ዐጠነ (ዐጢን ዐጠነ)፡ ጥናን ከፍምና ከዕጣን ጋራ ወዘወዘ ("የዕጣንን የወገር ትንን የቡክቡካን የርጐፍትን የሎሚ እሸትን የጪስ ዕንጨትን የመድኅኒትን የጥድን የ ንብ ኣስልን ሽታ" - መዐዛ - "አጨሰ ሰጠ አ ቀበለ ለታቦት ለጣዖት ለልብስ ለቡዳ ለ ቀፎ ") ።
ዐጠነ/አሳጠነ፡ ብለኸ "አሳጣኝን" እይ ።
ዐጠደ መልካም፡ ደጎች ቤተ ሰቦች ያሉት ሹም ("ዳግመኛም አሽከሮች ቤተ ሰቦች ካህናት - መኰንን ሹም ታቦት ነው - ዐጠደ ክፉ ታቦተ ደግ" እንዲሉ) ።
ዐጠደ ማሪያም (ዐጸደ ማርያም)፡ ሴት የምትጠራበት የክርስትና ስም ("የማሪያም ቦታ" ማለት ነው ") ።
ዐጠደ ክፉ፡ ምግባር ያነሳቸው አሽ ከሮች ያሉት መኰንን ።
ዐጠድ (ዐጸደ/ዐጸድ/ቦታ)፡ የቤተ ክሲያን ዛፍ ከገረገራ ግቢ ያለ ("ዐ ጠድ የሌለው ደብር ጢም የሌለው መምር" እንዲሉ) ።
ዐጠድ፡ ገረገራ ። "ገረገረን/ዐጸድን" ተመ
ዐጠዶች፡ ዛፎች/ጥዶች/ወይሮች/ግራ ሮችና ሌሎችም ።
ዐጠጠ (ሐጸ)፡ ጐደለ/አነሰ ።
ዐጠጥ፡ ያጠጠ/ጐደሎ/ባለጌ ።
ዐጠፈ (ዐጢፍ ዐጠፈ)፡ ጠቀለለ (ሸበለለ - "(ግእዝ)") ።
ዐጠፈ (ዐጺፍ ዐጸፈ)፡ ጥንድ አ ደረገ (ደረበ ለበሰ መለሰ ቀለበሰ ጫፍና ፍን ገጠመ ኰረመተ ") ።
ዐጠፈ፡ በመጽሐፍ ማለ ተማሪው ።
ዐጠፋ፡ ዕጥፈት (የማጠፍ ሥራ - ዐጠፋ፡ የስም ምትክ፡ ዐጸፈ/ዐጸፋ ") ።
ዐጠፌታ፡ ባንድ ፈንታ ኹለት ኹኖ የሚከፈል ዕዳ (መቀጮ ") ።
ዐጡን ባር (ዕጣነ ባሕር)፡ የእ ንዡባን ዐይነት ቅጠል (ማለፊያ ሽታ ያለው በሶ ብላ መሳይ ") ።
ዐጣ ።
ዐጣ (ኀጥአ)፡
("ኀጢአት ሠራ") ።
ዐጣ ነጣ፡ ፈጽሞ ደኸየ (የንጀራ ገመዱ ተበጠሰ - ንጣት ያዘው ") ።
ዐጣ፡ ገደፈ/ረሳ ።
ዐጣሪ (ኀጻሪ)፡ የሚያጥር ልብስ ።
ዐጣሪ (ሐጻሪ)፡ ያጠረ/የሚያጥር ("ዐጥር ሠሪ" -
"(ተረት)" - እሾኸ ዐጣሪውን ነገር ሠሪውን "(ይወጋል ይጐዳል)") ።
ዐጣሪ (መጸብሓዊ)፡ ሽቱ ሸያጭን መሸተኛን ሌላውንም (አስገባሪ ቀረጥ ተቀባይ - ማቴ. ፲፥፫፡ ፲፰፥፲፯) ።
ዐጣሪ (ዐጻሪ/ወዐጺር)፡ ሠያጤ ዕጥር (ዕጥር መሸታ ሸያጭ - ጥቂቱን ለ ብዙ ገንዘብ ለዋጭ - ጠማቂ መሻች - አታላይ ሸርሙጣ አመንዝራ - ዐጺር በግእዝ የወይን' ጥማቂ "(ጭማቂ)" ነው - ጺ ' ይጠብቃል ") ።
ዐጣሪ ሰፈር፡ ዐዲስ አበባ በቅዱስ ሩፋኤል ኣጥቢያ ያለ ቀበሌ ።
ዐጣሮች (መጸብሓን)፡ መሻቾች (ቀ ራጮች - ማቴ. ፳፩፥፴፩) ።
ዐጣቢ (ዎች)፡ ያጠበ/የሚያጥብ (እ ካጣቢ' አድራቂ - "ከተጋች ታራቂ" እን ዲሉ) ።
ዐጣኝ (ኞች)፡ ያጠነ/የሚያጥን (ቄስ ወይም ሌላ ሰው - "ዘውድ ዐጣኝ ቡዳ ዐጣኝ" እንዲሉ) ።
ዐጣኝነት፡ ዐጣኝ መኾን (ጸሎተ ዕ ጣን መድገም ") ።
ዐጣጠበ፡ አነጣጣ/አጸዳዳ ።
ዐጣጠፈ፡ ኹለት ሦስት ጊዜ ዐጠፈ ።
ዐጣጥ (ጦች)፡ የንጨት ስም (እሾኸ ትንንሽ ዕንጨት - ሉቃ. ፮፥፵፬) ።
ዐጣፊ፡ ያጠፈ/የሚያጥፍ ።
ዐጣፋ፡ ኀሣ (የማእዘን ደንጊያ ቀናፋ ") ።
ዐጤ (ሐፄ/ሐፄጌ)፡ ዐጪ (ምድ ርን ለመግዛት ያጨ የመንግሥት ዕጮኛ የም ድር ጌታ - ዐፄ ንጉሠ ነገሥት - "ዐጤ ካሌብ ዐጤ ፋሲል ዐጤ ቴዎድሮስ ዐጤ ምኒልክ ዐጤ ኀይለ ሥላሴ" እንዲሉ) ።
ዐጤ ምኒልክና ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የተ ዋጉበት አገር (በወለጋ ክፍል በጉድሩ ያለ ") ።
ዐጤ፡ ንጉሠ ነገሥት—ዐጪ ።
ዐጤ፡ ዐል ።
ዐጥ (ዐፅ)፡ በረሓ/ጠፍ ("ትግሮችም አገርን ዐድ' ይሉታል - ይኸውም ፀና ደ ተወ ራራሾች ስለ ኾኑ ነው ") ።
ዐጥ ረገጥ፡ ሰው የረገጠው ስፍራ ("አቶ እከሌ ካቶ እከሌ ዐጥ ረገጥ አይደር ስም - ዐጥረ ገጥ ቢል ግን ያጥር ፊት ማ ለት ነው - "ረገጠን" እይ ") ።
ዐጥመ ርስት (ርስተ ዐፅም)፡
("(ዘፍ. ፶፥፲፫)") ያባት ያያት የቅድም አያት ዐ ጥም የተቀበረበት ርስት ።
ዐጥሚት፡ ያጃ ሙቅ ("ጠምዐ ") ።
ዐጥም (ዐፅም)፡ ዐጥንት/አስከሬን ።
ዐጥራም፡ ዐጥር ያለበት (ባላጥር ቤት ቦታ ተክል ") ።
ዐጥር (ሮች/ሐጹር)፡ በቤትና ባ ትክልት ዙሪያ ያለ የንጨት የካብ የግንብ የግርግር የድድቅ ቅጥር (የቅጠል ጀጐል - ዐጥር የሾኸ ዘለሳ ወዘፍ ") ።
ዐጥር ቅጥር፡ ዐጥር የውስጥ (ቅጥር የውጭ መካበቢያ - ኢሳ. ፭፥፭ - "ዐጥር ጣሽ ቅጥር አፍራሽ" እንዲሉ) ።
ዐጥር አፋፍ፡ ዐልፎ ዐልፎ በደን ጊያ ዐጥር የተከበበ መዋጊያ አፋፍ (በላይ ኛው ወግዳ ያለ ውሎ ማዋያ ") ።
ዐጥር ግቢ፡ ከቅጥር በስተውስጥ ያለ ስፍራ ።
ዐጥቅ የለሽ፡ የሴት ስም ("ወሰን የ ለሽ" ማለት ነው ") ።
ዐጥቅ፡ የመቃ የሽመል የቀርክሓ ያገዳ የሸንኰራገዳ የቅልጥም የጣት አንጓ (ወሰን ትጥቅ መሳይ ") ።
ዐጥቆች፡ ያንጓ ሰንበሮች መሥመር የሚመስሉ ።
ዐጥበኸ ዕዘን፡ አንድ ጊዜ ሲታ ጠብ የሚለቅ ጥለት ።
ዐጥንታም፡ ዐጥንተ ሰፊ ሰው ። ዐጥንተ ጥሩ፡ የጨዋ'የባላባት ዘር ።
ዐጥንቴ እሾኽ ኹኖ ይውጋኸ አለ፡ ፈጽሞ ረገመ ።
ዐጥንት (ቶች/ዐፅም/አዕፅምት)፡ የንስሳ ያውሬ የወፍ የሰው ውሳጣዊ ገላ (በቈዳ የተሸፈነ በሥርና በዥማት የተያያዘ እንደ ዕንጨት ጥንካሬ ያለው - "(የጌሾ ዐጥንት)" - ሳ ይወቀጥ ለጠጅ ተወቅጦ ለጠላ ድፍድፍ የ ሚኾን · የጌሾ ዕንጨት - "ዐጥምን አስከሬንን" ተመልከት ") ።
ዐጥንት ለባለዐጥንት፡ የሚጋጥ ' ዐ ጥንት የሚመጠጥ ቅልጥም ለባለቤት ለጨዋ ልጅ ይገባል ።
ዐጥፍ (ዐጽፍ)፡ ከበሬ ካጋዘን ' ከ ድኵላ ማስ የተበጀ የመነኵሴና የመነኵሲት ተደራቢ ልብስ (ዳባ ወይባ የገባና ያልገባ ") ።
ዐጥፎ አሰረ (ያህያን የበግን የፍየልን ፊተኛ እግር -
"ሰከለን"
ተመልከት) ።
ዐጨቀ (ዐጸቀ)፡ ወጠቀ (ሰብስቦ አ ገባ ጨመረ ከተተ ዐጀበ እንደ ቅጠል ") ።
ዐጨደ (ዐጸደ)፡ ብዙውን ባንድነት ጠረገ/ቈረጠ/ቦጨቀ/አመሸከ (የሣር የስንዴ የገብስ ያጃ የጤፍ ") ።
ዐጨዳ፡ የማጨድ ሥራ (ቈረጣ - ዘሌ. ፲፱፥፱፡ ኢሳ. ፲፯፥፲፩) ።
ዐጪ (ኀጣኢ)፡ ያጣ/የሚያጣ (ያላ ገኘ የማያገኝ ") ።
ዐጪ (ሐፀየ)፡ ሚስት ፈለገ (የወ ንድ አባት የሴትን አባት "ልጅሽን ለልጄ ስጠኝ" አለ - ሽማግሌ ላከ - እጪዋ ቤት ገባ - ከዚህ በኋላ ልጁ ለልጃገረዲቱ ማተብና ቀለ በት ሰጥቶ ቃል አሰረ - "(ተረት)" - ልጃገረድ ዐሥር ያጭሽ አንድ ያገባሽ - ያጨሽ ላያገባሽ ከባልሽ ሆድ አትባባሽ ") ።
ዐጪ (ሐፃዪ)፡ ያጨ/የሚያጭ (ሚ ስት ፈላጊ ") ።
ዐጪ(ጭ)ር (ሮች/ኅጺር)፡ ያጠረ (ድንክ ድንክዬ ኵርምባጥ ዝራጭ ድውይ ድኑር ከርከሮ ታናሽ ቁመተ ዶሮ ") ።
ዐጪሬ፡ ያጪር ወገን (የዶሮ ዳሌ - "ጐሰረ" ብለኸ "ጐሳራን ጕስርን" እይ - ዐጪሬ ዘንጋዳ ") ።
ዐጪር ቀጪን፡ ዐጪርነት ከቀጪን ነት ያለው ሰው ።
ዐጪር ቍርጭኝ፡ ታናሽ መጣፍ 1 ወይም ታሪክ "
ዐጪር ቃል፡ ዝብዝብ የሌለበት ነ
ዐጪርነት፡ ዐጪር መኾን (ድንክነት ") ።
ዐጪታ (ሓፃዪት)፡ ያጨች/የም ታጭ (ልታገባው የፈለገችውን ወንድ በልቧ የምታኖር ልጃገረድ ወይም ሴት ") ።
ዐጫቂ (ዐጻቂ)፡ ያጨቀ/የሚያጭቅ (ከታች ዐጃቢ ") ።
ዐጫጅ (ዐጻዲ)፡ ያጨደ/የሚያጭድ (ቈራጭ - ኢሳ. ፲፯፥፭) ።
ዐጫጆች (ዐጸድ)፡ የሚያጭዱ ("ማ ቴ. ፲፫፥፴፥፴፱፡ ያዕ. ፭፥፬ ") ።
ዐጭዶ፡ ቈርጦ/ጠርጎ ።
ዐጭዶ ገብ፡ የማንንም እኸል ዐ ጭዶ የሚገባ ማን ዘራሽ ።
ዐጯ ("በተክሊል በቍርባን ሚስት አገባ ባለሕግ እንዲሉ")
።
ዐጯደ፡ ዐጠነ ።
ዐጸባ (ዐጸበ/ጨነቀ/ደነቀ)፡ ከራ ችግር ጭንቀት ዕጦት ድኽነት ።
ዐጸደ ምኵሳሕ፡ ጓሮ ቤት ።
ዐጸደ ሥጋ፡ የሥጋ መኖሪያ ምድር ይህ ዓለም ።
ዐጸደ ነፍስ፡ የነፍስ ስፍራ ገነት መንግሥተ ሰማያት "
ዐጸዳም፡ ዐጸድ ያለው ባለዐጸድ ደ ብር መቅደስ ።
ዐጸድ (ዐጸደ)፡ ስፍራ ቦታ ሰፈር ።
ዐጸድ (ዶች)፡ የቤተ ክሲያን ዛፍ (አድባር - ፪ዜና. ፴፩፥ ፩) ። "ዐጠድን" እይ ።
ዐጸጸ (ሐጸ)፡ ጐደለ አነሰ ። "ዐጠጠን" ተመልከት ።
ዐጸፈ (ዐጺፍ/ዐጸፈ)፡ ለበስ ዐ ጠፈ መለሰ ። "ዐጠፈን" እይ ።
ዐጸፋ፡ አስቀድሞ በተነገረ ስም ፈንታ የሚነገር የስም ምትክ ። ይኸውም ርሱ ያ አንተ እነሱ እነዚያ እናንተ ርሷ ያች እኔ እኛ የሚል ቃል ነው ።
ዐፄ መስቀል በዓል፡ ዐጯ ።
ዐጼ፡ ንጉሠ ነገሥት—ዐፄ ።
ዐፄ፡ የንጉሠ ነገሥት ስም ቅጽል ። "ዐጨ" ብለኸ "ዐጤን" አስተውል ።
ዐፄ ፈንታ፡ የዐፄ ፈንታ (ነጭ ማር ማለፊያ ዶቄት ") ።
ዐፅም፡ ዐጥንት ። "ዐጥምን" እይ ።
ዐጽቅ (ቆች/ዐጸቀ)፡ የዛፍ የሐ ረግ ቅጥይ ክንፍ ከነፉ ።
ዐጽፍ፡ በቁሙ ዐጥፍ ።
ዐፈሌ፡ የ፴ ዓመት ጐበዝ (ያ፲፭ ዓመት ቈንዦ - ዐፍል ያለው/ያላት - ባለዐፍል ") ።
ዐፈሌ፡ ያፈለ/ያፈለች
ዐፈሩን ገለባ ያድርግለትና፡ የችን ስም ለማንሣት አስቀድሞ እንዲህ ይባላል ።
ዐፈር (ዕብ/ዓፋር)፡ መሬት ት ቢያ ("(ወንዴ ዐፈር)" - መረሬ ጥቍር መሬት - "(ሴቴ ዐፈር)" - ቀይ መሬት - "ያፈር ወይዘሮ ገንቦሬ ") ።
ዐፈር (ዕፍረት)፡ የሽቱ ስም (ሽቱ ") ። ዕፍረት ግእዝኛ ነው ።
ዐፈር መለሰ፡ ቀበረ ደፈነ ።
ዐፈር መልስ፡ ለሚጠጣው ታላቅ ጐዳት የሚሰጥ እስከ መቃብር የሚያደርስ መጥፎ መጠጥ ካቲካላ ።
ዐፈር ቀመሰ፡ ተቀበረ ።
ዐፈር ቃም፡ በውስጡ ዐፈር ያለ በት ካብ ("ዐፈር የቃመ" ማለት ነው ") ።
ዐፈር ብዛት፡ ብዙ ።
ዐፈር አልባሽ፡ ባል ወይም ሚስት ።
ዐፈር ኰቸር፡ በቈሎ የሚመስል ደ ረቅ የንጨት ቅርጣፊ (ሴቶች እንደ አደስ ደቍሰው ከቅቤ ጋራ የሚቀቡት ") ።
ዐፈር ኾነ፡ ወደ መሬት ተመለሰ ።
ዐፈር ይፈጫል፡ ሕፃን ነው።
ዐፈር ገደል፡ ዐፈርን ገደል የሚሰድ ጭንጫ ግርግራ ሸርታቴ ስፍራ ።
ዐፈር ገፊ፡ ዐራሽ ገበሬ ("(ጐንደር)") ።
ዐፈር ጠራው፡ በባዕድ አገር ሞተ ።
ዐፈር ፋሪ፡ ዐፈር የሚመስል ሰው
ዐፈር ፋሮ፡ የፋሮ ዐፈር ።
ዐፈርማ፡ ዐፈር መሳይ ባለዐፈር ።
ዐፈርሳታ፡ አውጫጭኝ አፈር
ዐፈርቻ፡ ዐፈር አስተኔ ።
ዐፈርነት፡ ዐፈር መኾን ።
ዐፈሮ፡ ብዙ ሰራዊት (ብዛቱ እንዳፈር ' የኾነ ባለነጋሪት ጭፍራ ") ።
ዐፈነ (ሐፈነ)፡ ዘገነ ያዘ እኸልን ።
ዐፈነ፡ ሸፈነ ደፈነ ጠቀጠቀ ኣ ለመ ዋሻን በጪስ ።
ዐፈነ፡ ዘጋ ወተፈ (የባሪያን አፍ በ ኳስ - ጩኸትን ትንፋሽን ከለከለ ") ።
ዐፈነ፡ ፈረስን በቅሎን በቤት አዋለ ቀለበ ።
ዐፈና፡ ሽፈና (ወሊስ የማያቋርጥ ዝና ምና ጉም ") ።
ዐፋኝ (ኞች/ሐፋኒ)፡ ያፈነ/የሚ ያፍን (ዘጋኝ ሸፋኝ ") ።
ዐፍለኛ (ኞች)
ዐፍለኛ፡ ቂጣነትና ሑምጣጤ የሌለው እንጀራ ዳቤ ዳቦ ።
ዐፍለኛነት፡ ዐፍለኛ መኾን ።
ዐፍላ እንቅልፍ፡ ከባድ ብርቱ ("(ኢ ዮ. ፴፫፥ ፲፭)") ።
ዐፍላ ጦር፡ ብርታት ያለው ያልበ ረደ ጋብ ያላለ ።
ዐፍላ/ዐፍል፡ ሙሉ ሰውነት ጕብ ዝና አካለ መጠን ጕልምስና ።
ዐፍሌታ፡ ጥዋ—አፍሌታ ።
ዐፍሮ ቀረ፡ ሰውን ማየት ፈርቶ አልመጣም አለ ።
ዐፍሮ አይገባ
ዐፍሮ አይገባ፡ ያሞራ ስም (እንደ ጥንበ በላ ያለ ታናሽ አሞራ - ሰው ሲያይ በሩቁ የማይሸሽ የማይፈራ - ደረቅ ዐጥንት ውዳቂ ለቃቃሚ ' ሦስት ዐይነት መልክ ") ።
ዐፍሮ፡ ፈርቶ ግንባሩ ታጥፎ ።
ዐፍሻት፡ ጥዋ—ዐፈሠ ።
ዑመር (ዐረ)፡ የሰው ስም ("ዕድሜያም ማለት ነው ይላሉ ") ።
ዑመር፡ ሸኅ ዑመር (የወረ ሸኆች አ ባት በየጁ የነበረ ") ።
ዑመር ዐመሰ ።
ዑመር እብነ እልኸጣብ፡ ጻድቅ ሰው (የእስላም ንጉሥ ለክርስቲያኖች ነጻነት የሰጠ - የጦር አለቆች ድኻን እንዳያጠቁ የከ ለከለ - ሰሌን እየሠራ ፍሬ ጻማውን የተመገበ ") ።
ዑመር ወልደ ዐፅ፡ በ፰፻ ዓ ም ግብጽን የያዘ (በቅብጥ ቋንቋ የተጻፉ ፭ "(ዐ ምሳ ሺሕ)" የጥበብ መጻሕፍት ያቃጠለ ") ።
ዑቃቤ/ውቃቢ፡ ጥበቃ ። "ውቃቢን" ተ መልከት ።
ዑደት ዙረት —ዐወደ ።
ዑደት፡ የታቦት የካህናት የሕዝብ ፫ ጊዜ ዙረት ።
ዑድ (ዐረ)፡ ዋግራ (የሬት ዕንጨት ሽቱ - በግእዝ ዐልው ይባላል ") ።
ዑድ ሰንደል፡ ዑድና ሰንደል ለየ ብቻው ሲኾን (ባንድነት መነገሩ ዐማሮች ሰንደልን በዑድ ስም ስለ ጠሩት ነው - ይኸውም የጪስ ዕንጨታቸው ኹኔታ መመ ሳሰሉን ያሳያል - "ነድንና ሰንደልን" እይ ") ።
ዑድ፡ ዙር ("(ግእዝ)") ።
ዑድ፡ የሽቱ ስም (እንደ ሰንደል የተበጀ ሽቱ - ኹለቱም የጪስ ዕንጨቶች ናቸው ") ።
ዑድ፡ የሽቱ ስም—ዐወደ ።
ዓለመ መላእክት፡ ሰማይ (ኤረር ራማ ኢዮር ") ።
ዓለመ ሰብእ፡ ምድር የሰው መኖሪያ ።
ዓለመ ሥጋ፡ ይህ ዓለም ።
ዓለመ ነፍስ፡ መንግሥተ ሰማይ ።
ዓለመኛ፡ ዝኒ ከማሁ (የዓለም ሰው ዓለም ወዳድ ባለቅልጣን ") ።
ዓለሙ/ዓለሜ፡ የሰው ስም (የርሱ/የኔ ዓለም ማለት ነው ") ።
ዓለሚት ቱ፡ የሴት ስም ።
ዓለማዊ፡ መናኝ (እውነተኛ መነኵሴ ያይዶለ ጥቍር ራስ በዓለም ያለ ዓለም ፈላጊ ") ።
ዓለም (ሞች)፡ በቁሙ ሰማይና ምድር (ያድራጊና የፈጣሪ መኖር ምልክት ") ።
ዓለም፡ ሰው ኹሉ (አዳሜ - "በዚህ ነገር ዓለም ኹሉ ተስማምቶበታል ") ።
ዓለም ሰገድ፡ ያጤ ፋሲል ስመ መንግሥት ("ዓለም የሰገደለት" ማለት ነው ") ።
ዓለም አየ፡ ተደሰተ (ደላው ተመቸው ") ።
ዓለም፡ እዱኛ (ተድላ ደስታ ሹመት ሀብት ንብረት ጌትነት ቅልጣን - "ዓለም ዐላፊ መልክ ረጋፊ ዓለም ዘዋሪ ዓለም ዋሾ ዓለም አታላይ" እንዲሉ) ።
ዓለም ዘላለም፡ መንግሥተ ሰማይ ("ዘላለምን" እይ ") ።
ዓለም ጥበብ፡ የዓለም ተንኰል ("ዓለም ጥበብ ጨለማ ተገን" እንዲሉ) ።
ዓመተ ምሕረት፡ የምሕረት የይቅርታ ዘመን (ክርስቶስ ከተወለደ ዠምሮ የሚቈ ጠር - ሰው ከፈጣሪ የታረቀበት ድኅነት ያገኘበት ጊዜ ማለት ነው ") ።
ዓመተ ሰማዕታት፡ ሰማዕታት ዐንገ ታቸውን ለስለት ዐይናቸውን ለፍላት የሰጡ በት ዘመን ።
ዓመተ ሥጋዌ፡ ጌታችን ሥጋ የለበ ሰበት (ሰው የኾነበት ዘመን ") ።
ዓመተ ዓለም፡ ዓለም ከተፈጠረ እስ ኪያልፍ ድረስ ያለው ዘመን ።
ዓመተ ኵነኔ፡ የቅጣት የመከራ ዘመን (ከአዳም እስከ ክርስቶስ ያለው ") ።
ዓመተ ፍዳ፡ ዓመተ ኵነኔ ።
ዓመት (ቶች)፡ ፲፪ ወር (፫፻፷፭ "(፮)" ቀን - ፶፪ ጊዜ ፯ ካ፩ "(፪)" ቀን - ወይም ፵፭ ሳምንት ካ፭ "(፮)" ቀን ነው - ፶፪ ሳምንት ማለት ግን ስሕተት ነው - እኩሌታው መን ፈቅ ይባላል - "ዓመት ተመንፈቅ" እንዲሉ - "(ሙት ዓመት)" -
"ሞተ" ብለኸ "ሙትን" ተመልከት ") ።
ዓመት ተመንፈቅ፡ ዐሥራ ስምንት
ዓመት ዐውዳመት፡ መስከረም ፩ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ ("ዐውዳመት የዓመት ቅጽል ነው" -
"ዐወደን" እይ ") ።
ዓመት ዓመት ድገመኝ፡ እዛሬ ዓመት አድርሰኝ (የሚመጣውን ዓመት እሸት አብላኝ ማለት ነው - አንደኛው ዓመት ዐዲ ሱን የሚመጣውን - ኹለተኛው ዓመት የዘንድ ሮውን የተዠመረውን ያሳያል ") ።
ዓመት ዕለት ነው፡ ቶሎ ይደርሳል ("ብዙው ጊዜ ሺሑ ዓመት እንዳንድ ቀን ይታ ሰባል" - ዘኍ. ፲፬፥፴፬፡ መዝ. ፺፥፬፡ ሕዝ. ፬፥ ፭ - ፮) ።
ዓመት፡ ዘመን ጊዜ ።
ዓመትባል፡ ባመት የሚከበር በዓል ("ዐውዳመት ") ።
ዓሣ (ሦች)፡ የውሃ ውስጥ ተንቀሳቃሽ (ትልቅና ትንሽ - ምግብ የሚኾን - ወሸኸሬ ወ ") ።
ዓሣ ለቃሚ፡ ዝኒ ከማሁ (የወንዝ አመቴ ወይም ሌላ ") ።
ዓሣ ነባሪ (የምታጠባ)
ዓሣ ነባሪ፡ ታላቅ ዓሣ (የዓሦች ንጉሥ - መርከብ የሚገለብጥ - ነባሪ ነዋሪ ማለት ነው - በግእዝ ዐንበር ይባላል ") ።
ዓሣ ነባሪ፡ አዝራር (ከሰደፍ ዐጥንት ከባሕር ዛጐል የተሠራ የእጀ ጠባብና የጥ ብቆ የቀሚስ ቍልፍ ") ። ዓሣ ነባሪ መባሉ በ ቀድሞ ዘመን ዓሣ ነባሪ ሲሞት ዐጥንቱ አዝራር ይበጅ እንደ ነበረ ያስረዳል ።
ዓሣ ነባሪዎች (ዐናብርት)፡ ታላላ ቆች ዓሦች ።
ዓሣ ነባሪዎች፡ አዝራሮች ።
ዓሣ አሥጋሪ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዓሣ አውጭ፡ ዓሣን ከባሕር የሚያወጣ አሞራ ("(ዘሌ. ፲፩፥ ፲፫)") ።
ዓሣ አጥማጅ (ጆች)፡ ዓሣን በወጥ መድ የሚይዝ ("(ኢሳ. ፲፱ ' ፰)") ።
ዓሣ ወጋሪ፡ ዓሣን ይይዝና እደንጊያ ላይ እየመታ የሚገድል ።
ዓሣ ዋጭ
ዓሣ ዋጭ፡ ዓሣ የሚውጥ ("(ዘዳ. ፲፬፥ ፲፫)") ። በግእዝ አልያጦን ይባላል ።
ዓሥራታይ (ዓሥራት አይ)፡ ዓሥ ራት የሚያይ (ዓሥራት አሰፋሪ ጭቃ ሹም ") ።
ዓሥራት (ዐሥራት)፡ ካሥር አንድ (ለቤተ ክህነትና ለቤተ መንግሥት የሚሰጥ እኸል ገንዘብ ከብት - ቀረጥ ግብር ") ።
ዓሥራት በኵራት፡ ዓሥራት እንዳ ለፈው (በኵራት የከብት የተክል የእሸት የልጅ መዠመሪያዎች መልካካም ነገሮች ምርጦች ናቸው ") ።
ዓሥራት አወጣ፡ ከፈለ ሰጠ (ካሥር አንድን ") ።
ዓሥርት (ዓሥሪት)፡ የወላድ ሴት
ዓደን፡ የጠረፍ ስም (የየመን ወደብ - ከ፲፱፻፴፫ ዓ. ም. ወዲህ ግን ዐዲስ አበባዎች እንደ እንግሊዝኛ ኤደን ይሉታል - ስሕተት ነው ") ።
ዓዲ፡ ዳግመኛ ("(ግእዝ)") ።
ዔሊ (ሔለይ)፡ ያውሬ ስም (ድንጋይ ልብሱ - ፬፻ ዓመት የሚኖር አውሬ - ዘሌ. ፲፩፥፴ - አንድ ነገር ባየ ጊዜ ራሱን የፊት እግሩንና የኋላ እግሩን በልብሱ ውስጥ ይደብ ቃል - "ለዔሊ ድንጋይ ያለበሰ አምላክ" እንዲሉ - ሲበዛ "ዔሊዎች" ይላል - ተባቱንና እንስቱን ለመ ለየት ") ።
ኤሊ፡ የሰው፡ ስም፡ ፡ ዔሊ።
ዔሊ፡ የሰው ስም (ከሳሙኤል በፊት የነበረ ሊቀ ካህናት ") ።
ኤሊ፡ ደንጊያ፡ ልብሱ፡ ዔሊ።
ዔሊዋ፡ ያች ዔሊ (የርሷ ዔሊ ") ይሏል ።
ዔሊው፡ ያ ዔሊ (የርሱ ዔሊ ") ።
ዔላም፡ በደብረ ሊባኖስ ውስጥ ያለ ስፍራ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት ኹለተኛ የተቀ በሩበት - ምንጫም ጠበላም ማለት ነው ") ።
ዔሮባ ጳ (ኤሮፓ)፡ የፈረንጆች አገር (ምዕራብ ማለት ነው - ሌላም አፈታ ትና ትርጓሜ ይኖረዋል - አንዳንድ ፈረን ጆች ግን በተረት ኤሮፓ ከአፍሪቃ ወደ ያፌት ክፍል የተሻገረች ሴት አምላክ ነች ") ይላሉ ።
ዔሮባ ጳ (ኤሮፓ)፡ የፈረንጆች አገር (ምዕራብ ማለት ነው - ሌላም አፈታ ትና ትርጓሜ ይኖረዋል - አንዳንድ ፈረን ጆች ግን በተረት ኤሮፓ ከአፍሪቃ ወደ ያፌት ክፍል የተሻገረች ሴት አምላክ ነች ") ይላሉ ።
ዔሮፓ/ዔሮባ፡ ዐረበ ።
ዔቦር፡ የሰው ስም (የሳላሕ ልጅ የሴም ፭ኛ ትውልድ) ።
ዔድን (ዔዶም)፡ ምቹ ስፍራ ("(ገ ነተ ተድላ)") ። የግእዝ መጽሓፍ ኤዶም ይለ ዋል (አዳምና ሔዋን ከስሕተት በፊት የነበሩ በት ምድረ ገነት ነው - ዘፍ. ፪፥፰, ፲፡ ፫፥፳፬) ።
ዕሕ አለ፡ ተነፈሰ (እፎይ አለ ") ።
ዕሕ አለ፡ አማጠ ፲ ወደ ውጭ ገፋ ።
ዕሕ አለ፡ ጠየቀ—እህ ።
ዕሕ፡ የወላድ ድምፅ ።
ዕሕታ፡ ምጥ/ማማጥ (የተቅማጥ በሽታ ") ።
ዕሕታ፡ ጥያቄ—እህ ።
ዕለተ ምጽአት፡ ጌታችን በክብር ወደዚህ ዓለም መጥቶ ጻድቃንን "ወደኔ ኑ" ኃጥኣንን "ከኔ ዘንድ ኺዱ" የሚልበት ቀን ።
ዕለተ ሞት፡ የሞት ቀን (ነፍስ ከ ሥጋ የምትለይበት ") ።
ዕለተ ቀኑ፡ ዕለት የግአዝ (ቀን ያማ ርኛ - ኑ የጌታ የመልአክ የጻድቅ የሰማዕት ዝርዝር ነው - መጋቢት ፳፯ የመድኀኔ ዓለም ዕለተ ቀኑ ነው - "(በዓሉ ይከብራል)") ።
ዕለተ ቀን፡ ከጧት እስከ ማታ ።
ዕለተ ደይን፡ የፍርድ የምጽአት ቀን ።
ዕለተ ጠብ፡ ድንገተኛ የጊዜ ጠብ (ቍርሾ የሌለው ") ።
ዕለት (ወዐለ)፡ ቀን ("በግእዝ ግን ዕለት የሚባለው ሌሊቱን ጨምሮ ፳፬ ሰዓት ነው - ዓመትን ተመልከት ") ።
ዕላቂ፡ ውራጅ ወርቅ ቍረንጮ ደላጎ ።
ዕላቆ (ዎች)፡ የማረሻ የዶማ ብረታብረት ቅሬታ ።
ዕላፊ፡ ሰው ወደ ሥራውና ወደ ጕ ዳዩ በተወሰነው ሰዓት ሳይገባ ያሳለፈው ጊዜ ("የሰዓት ዕላፊ" እንዲሉ) ።
ዕላፊ፡ ዐለፌታ ("ያፍ ዕላፊ" እንዲሉ) ።
ዕላፊ፡ ግማሽ ብራና ("ኅላፍ አጋማሹ ወደ ሌላ የሚያልፍ ") ።
ዕልል (ዕሉል)፡ የታለለ (በደም የተ ነከረ - ራእ. ፲፱፥፲፫)
ዕልም (ሕልም)፡ ራእይ በንቅልፍ ልብ የሚታይ (ማግኘትና ማጣት ደስታና ሐዘን ማንኛውም እውነተኛ ነገርና ሐሞታዊ' ቅዠት ኹሉ ") ።
ዕልም (ሕልም)፡ ራእይ በንቅልፍ ልብ የሚታይ (ማግኘትና ማጣት ደስታና ሐዘን ማንኛውም እውነተኛ ነገርና ሐሞታዊ' ቅዠት ኹሉ ") ።
ዕልም (ዕሉም)፡ የጠፋ ዕቡ ። ዕልም "
ዕልም አለ፡ ጥፍት ውድም ኣለ (የመ ብራት ያይን የሰው የመንፈስ ") ።
ዕልም ያድርገው፡ አምላክ ይህን ነገር በሥራ አይግለጠው (አይፈጽመው ") ።
ዕልም ድርግም አለ፡ ፈጽሞ ጠፋ ደለመ ።
ዕልቂያ/ዕልቀት/ዕልቂት (ኅልቅት)፡ የብዙ ሰው ሞት ("(የከብት ዕልቂት)" - ባ፲፰፻፹፪ ዓ ም በኢትዮጵያ የኾነ የተደረገ - ይኸውም ጣሊያኖች በሽታ ያለበትን ጐሽ ከህንድ አገር አምጥተው በትግሬ በረሓ ስለ ለቀቁት ነው የሚል ጽሑፍ በጣሊያንኛ ይገ ኛል - "(ያላለቀለት)" - ዐፍላውን ያልጨረስ ጸያ ፉን ያልከተተ ምራቁን ያልዋጠ ሰው - "(ያላ ለቀላት)" - ያላረጠች ባልቴትነት የሌላት ሴት ") ።
ዕልቅ (ኅሉቅ)፡ ያለቀ የተወረሰ ።
ዕልቅ (ኅልቅ)፡ ዕልቂያ ማለቅ "
ዕልቅ አለ፡ ጭርስ ፍጽም አለ ።
ዕልቅት (ሐለቀ/ሕልቅ)፡ የደረት ሣፍ (የጕረሮ ሥር ") ።
ዕልቆ (ኍልቍ)፡ ቍጥር ልክ ።
ዕልቆ መሳፍርት፡ የመስፈሪያዎች ቍጥር ፲ ወይም የቍጥር መስፈሪያዎች ("ያሜ ሪካ ገንዘብ ዕልቆ መሳፍርት የለውም ") ።
ዕልበት (ሕልበት)፡ ጨው ነጭ ሽን ኵርት ቅመም የሱፍ ውሃ ሰናፍጭ የገባበት ነጭ የባቄላ ወጥ (በጦም የሚበላ ") ።
ዕልባት (ቶች)፡ የፈትል ፥ የሐር ክር ' በመጻፍ ውስጥ ያለ ።
ዕልባት አደረገ፡ ዐለበ (አመለከተ ") ።
ዕልብ (ሕሉብ)፡ የታለበ ጡት ወተት ።
ዕልብ (ዕሉም)፡ የታለበ ምልክት ' የተደረገበት ።
ዕልክ፡ በቁሙ አለከ ።
ዕልዋ (ኀለወ)፡ ሌሊት በፈረቃ ከብ ትን መጠበቅ (ወይም ጥበቃ ዘብ - ሉቃ. ፪፥፰) ።
ዕልፈት፡ ሞት (ከዚህ ዓለም ተሰና ብቶ መኼድ - ምሳ. ፲፥፳፭)
ዕልፊት፡ ድፍረት ዐለፌታ ነቀፋ ።
ዕልፍ (ኅሉፍ)፡ ከልክ ከስፍር ከመ ጠን ከቍጥር ያለፈ (ዕላፊ - "ዕልፍ ትርፍ" እን ዲሉ - "እልፍ" ተብሎ ቢጻፍ ትርፉ ዐሥር ሺ መኾኑን ያሳያል ") ።
ዕልፍ አደረገ፡ ፈቀቅ አደረገ ።
ዕልፍ፡ ፈቀቅ ስፍራ መልቀቅ ("(ግ ጥም)" - ዕልፍ ሲሉ ዕልፍ ይገኛል ድኻ ሞኝ ነው ሞቱን ይመኛል ") ።
ዕልፍታ፡ ዕልፍ ማለት (ፈቀቅታ ") ።
ዕልፍኝ (ኞች)፡
("(፪ዜና. ፳፪፥፲፩)") በሐር የተቈነጠጠ በግምጃ የተለበጠ ጌጠኛ ራስጌ ቤት (ባዳራሽ ዐልፎ የሚገባበት ") ።
ዕልፍኝ ታዳራሽ፡ ዕልፍኝነት ካዳ ራሽነት ያለው ቤት (የታላላቆች ሰዎች ግብር መብሊያ ") ።
ዕልፍኝ አዳራሽ፡ ሰውን ወደ ዕል ፍኝ የሚያቃርብ ("(የሚያደርስ)") ቤት
ዕልፍኝ አዳራሽ፡ የንጉሥ ድንኳን ።
ዕመም (ሕማም)፡ በሽታ ምታት መ ጋኛ ቍርጥማት ቍርጠት ፍልጠት ውጋት ወባ ተስቦ ተቅማጥ እውከት፡ የመሰለው ኹሉ ።
ዕመምተኛ (ኞች)፡ ዕመም ያለበት ያ ደረበት (በሽተኛ ዱያታም ") ።
ዕመምተኛነት፡ ዕመምተኛ መኾን (በ ሽተኛነት ") ።
ዕመት፡ የቅዱሳን መሬት (ደማቸው የፈሰሰበት ዐፅማቸው የረገፈበት - ምስጢሩ እምነትን ያሳያል - "ዕመትና ጠበል" እንዲሉ) ። ማመት፡ ዐመድ ማድረግ (መቍረጥ መ ክተፍ ") ።
ዕምስ (ኅሙስ)፡ ዐምስት የኾነ የተ
ዕምስ (ሕሙስ)፡ የታመሰ/የሞቀ ፥ የተ ንቃቃ (ሙቀት የተቀበለ ቅይጥ ዱቄት ው ቅጥ በርበሬ ") ።
ዕምስ (ኅምስ)፡ የሴት ኀፍረት (፭ኛ ሕዋስ ") ።
ዕምስ አንቀጥቅጥ፡ ሽታ ያለው ቅ ጠል (ጕዝጓዝ የሚኾን ከዐመጃይ ጋራ የሚ በቅል ") ።
ዕምስ አንቀጥቅጥ/ዕምስ ፈሪ፡ ዝኒ ከማሁ ("ኅምስ ዘይ
ዕምቅ (ዕሙቅ)፡ የታመቀ የተረጠጠ
ዕምት (ትግ/ሕምቶ/ዱለት)፡ የታ መተ/የተከተፈ ክትፎ (የታመሰ ዕምስ ") ።
ዕምድ መታው፡ ዐመዳይ አጠፋው አበላሸው ።
ዕምድ፡ ዐመዳይ ("(ስም)") ።
ዕምድ፡ የታመደ/የተቈረጠ - ቍርጥ "(ቅጽል)") ።
ዕምግ (ሕሙግ)፡ የታመገ (ስብስብ ክምቹ ") ።
ዕሰባ፡ በልብ የሚሠራ ያሳብ ኹኔታ ።
ዕሠዬ፡ የሰው ስም ("የኔ ዕሠይ" ማለት ነው ") ።
ዕሠዬው፡ ው ያው ከማለት የመጣ
ዕሠይ፡ ንኡስ አገባብ (ደግ ማለፊያ - ሰው ከደስታ የተነሣ የሚናገረው ቃል - "ዕሠይ እንኳዕ ደኅና መጣኸ" እንዲሉ - በግ እዝ እንቋዕ ይባላል - "ወሰውን" ተመልከት ") ።
ዕሠይ ዕሠይ፡ ደግ ደግ (ማለፊያ ማለፊያ - መልካም መልካም - ይበጅ ያድርግ - የእልልታ ምስጢር አለበት - ሕዝ. ፳፮፥ ፪) ።
ዕሰይ፡ የደስታ ቃል—ዕሠይ ።
ዕሠይታ፡ ዕሠይ ማለት (መደሰት ") ።
ዕሣሽ፡ የምጣድ ጥራጊ ።
ዕሣሽ/ዕሥሥ፡ ብናኝ ዐቧራ ።
ዕሴይ፡ የሰው ስም—እሴይ ። ዕስክ/ዕሽክ/ዕችክ "
ዕሥሥ፡ የታሠሠ የተ ጠረገ ውልውል ።
ዕሥሥት (ቶች/ኅሥ ሥት)፡ የተንቀሳቃሽ ስም (ያየ ውን መልክ የሚመስል ተለዋ ዋጭ ኣውሬ - ዘሌ. ፲፩፥ ፴) s
ዕሥሥት፡ ማንቊርት ዐንቆ ለመግ ደል የምትፈለግ ማለት ነው ።
ዕሥሥት፡ ወረተኛ ገል ባጣ ሰው (ዛሬ ካንዱ ነገ ከሌ ላው የሚወዳጅ ") ።
ዕሥር፡ የታሠረ (ዐሥር የኾነ ") ። ዐፈለ (ፈሐለ)፡ አደገ ፥ ጐለመሰ ጐ በዘ በረታ ።
ዕስቅ (ዕሱቅ)፡ የታሰቀ የተጠለፈ ' የተጌጠ (ዝንጕርጕር ልብስ ") ።
ዕስባት፡ ሒሳብ ስሌት ።
ዕስብ (ሕሱብ)፡ የታሰበ “
ዕስብታ፡ ትውስታ ።
ዕሦ (ሐሠየ/ዐሠየ)፡ የዕሠይን ፍች እይ ። ተደጋግሞ ሲነገር ዕሦ ዕሦ ይላል ።
ዕሶ/ዕሠይ፡ ዕሦ ።
ዕረፍ፡ ተቀመጥ (ዝም በል ") ።
ዕሩር (ሮች)፡ ላይ ላዩ በእሳት ያረረ የከሰለ (የንጨት ፥ ጥንግ ") ።
ዕሩቅ ብእሲ፡ የጳውሎስ ሳሚሳጢና የንስጥሮስ ባህል (የክርስቶስን ኣምላክነት ክዶ - "(ዕሩቅ ብእሲ)" - ሰው ብቻ ነው ማለት ") ። "ኀድረትን" እይ ።
ዕሩቅ፡ የተራቈተ- የታረዘ (ብቻ - "(ግእዝ)") ።
ዕሪ ጩኸት፡ አረረ ።
ዕሪም (ሞች)፡ ታናሽ የመሬት ክፍል (ሰፊና ታላቅ ከኾነ ርስት ተከፍሎ ላገለገለ አሽከር ለሎሌ ለወዳጅ ለካህን የተሰጠ ማሳ - ዕን ጐርዶ ሪም ቢል ዕዛብን ዛብ እንደ ማለት ያለው ነው ") ።
ዕሪያ (ሐራውያ)፡ በዱር የሚኖር ያሣማ ዐይነት አውሬ (ጥርሱ ተከንፈሩ ውጭ ወጥቶ የሚታይ እንስሳ - ሲበዛ ዕሪያ ዎች ያሠኛል - ዕሪያ ሲባል እንዳሣማ በሰው መብት የማይኖር ነጻነት ያለው ማለት ነው ") ። "ከርከሮን" እይ ።
ዕሪያ ጥርስ፡ ጥርሰ ገጣጣ ሰው ("የሪያ ጥርስ" ተብሎም ይተረጐማል ") ።
ዕራሪ (ሕራር)፡ የነጠፈ የደረቀ የሸሸ ።
ዕራሪ፡ ንጥፈት ድርቀት ("የጡት ዕራሪ" እንዲሉ) ።
ዕራሪ፡ ከራራ ድውይ ።
ዕራሽ፡ የርሻ ይዘታ ።
ዕራቍት (ዕሩቅ)፡ የተራቈተ ("(ዮሐ. ፳፩፥ ፯)") ። ያለፈው ጥሬ (ይህ ቅጽል መኾ ኑን አስተውል ") ።
ዕራፊ (ዎች)፡ የሸማ ቍራጭ ዐዲስ (ወይም አሮጌ ያለቀ የተቀደደ ልብስ መጣ ፊያ ") ።
ዕር፡ ፍየል መከልከያ—እር ።
ዕርመ በላ፡ እዘመዱ ለቅሶ ያልደ ረሰ ያላለቀሰ ።
ዕርሙን አወጣ፡ ለሞተ ዘመዱ አለቀሰ ።
ዕርማት፡ የማረም የመታረም ሥራ ። አስተራረም፡ አነቃቀል (ማረም ") ።
ዕርም (ሕሩም)፡ የታረመ የተነቀለ ። (ላር) ዕርም (ሕርም)፡ ሊቀምሱት ሊበ ሉት ሊነኩት የማይገባ ክልክል ነገር (ኢያ. ፯፥ ፲፩ - ፲፫) ። "ዕርም የሰው ሥጋ" እንዲሉ ። "(ተረት)" - ዳገት ዕርሙ ሜዳ ወን ድሙ ።
ዕርም፡ ለወገን ለዘመድ አለማልቀስ ። "በላ" ብለኽ "አበላን" እይ ።
ዕርም ተባለ፡ ታረመ ("ዕርም ኾነ ") ።
ዕርም ታኽል፡ በጣም ያነ ሰች—እምር ታኸል፡ አመረ ።
ዕርም ነው፡ አይቀመስም አይበላም (ክልክል ነው ") ።
ዕርም አለ፡ ዐረመ ("እንደ ሰው ሥጋ ቈጠረ ") ።
ዕርምኸን አውጣ፡ አልቅስ (እንባ ኸን አፍስስ ") ።
ዕርስ (ሕሩስ)፡ የታረሰ የተሰበተ ።
ዕርስ ዐደር፡ ታርሶ ሳይዘራ የቀረ መሬት ።
ዕርስ ዐደር ኾነ፡ ጦም ዐደረ ።
ዕርር (ሐሪር)፡ ማረር ።
ዕርር ምርር አለ፡ ፈጽሞ ኦለቀሰ በሐዘን ተጨበጠ ።
ዕርር አለ፡ ክስል ግምን አለ ።
ዕርር ኵምትር አለ፡ እጅግ ዐረረ ተኰማተረ ።
ዕርርታም፡ ዕርርት ያለበት ባለዕር ት ።
ዕርርት (ሕርርት)፡ ያረረች ።
ዕርርት፡ ሞራ (በበሬ በሰው ዐይን ላይ የሚወጣ ትርፍ ሥጋ ዐራራ መሳይ ") ። የባላገር ሐኪምም በሬውን ጥሎ ዕርርቱን በመርፌ ወግቶ በክር ይስብና ከቈረጠ በኋላ ዐይን ውስጥ የወይናግፍት ዶቄት ይጨምር በታል ። የበሬን ጭራ የሚቈርጥ ቍስል ።
ዕርሻ (ሕርስ)፡ ማሳ ቅብቅብ ("(ኤር. ፴፪፥ ፵፫)")
ዕርሻዎች/ዕርሾች፡ ማሳዎች ቅብቅ ቦች ("(ኤር. ፴፪፥ ፵፬)") ።
ዕርቃነ ሥጋ፡ የሥጋ ዕራቍት ። የስ ቅለት ለት የጌታችን ዕርቃነ ሥጋ እንዳ ይታይ ፀሓይ ጨለመ (ጨረቃ ደም ኾነ ") ።
ዕርቃን፡ ዕራቍት አካላዊ ግንድ ' መለመላ ልብስ የሌለው ባዶ ገላ ። "ዕርቃን" የግእዝ ("ዕራቍት" ያማርኛ ነው - ዘፍ. ፪፥ ፳፭፡ ፱፥ ፳፩) ።
ዕርቅ፡ የታረቀ ቀጥ ያለ ("(ርቱዕ)") ። (ላር) ዕርቅ፡ ("(ምሳ. ፲፭፥ ፬)") ስምም ፍቅር
ዕርቅና፡ ዕራቍትነት (ዕራቍት መ ኾን ልብስ አልባነት - ሚክ. ፩፥ ፲፩፡ ዘፍ. ፱፥ ፳፪ - ፳፫) ።
ዕርበት፡ ጥልቀት ("(ግእዝ)" -
"ሞት የጀንበር ዕርበት" እንዲሉ) ።
ዕርቡን፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዕርከን (ኖች)፡ የመሬት ደረጃ ' ከፍና ዝቅ ብሎ የሚታይ (ከደንጊያ ከሳ ንቃ ከስሚንቶ የተበጀ የደርብ የመንበር መውጫና መውረጃ - ፬ነገ. ፲፥ ፲፱ - ፳) ።
ዕርዝ (ዕሩዝ/የለበሰ)፡ የታረዘ የተ ራቈተ ።
ዕርዝተኛ (ኞች)፡ ዝኒ ከማሁ (ልብሱ' ያለቀበት ገላው የሚታይ ') ።
ዕርዝና/ዕርዛት፡ ዕርዝተኛ መኾን (ዕራቍትነት ") ።
ዕርድ (ሕሩድ)፡ የታረደ ማንቍርቱ የተቈረጠ ።
ዕርድ፡ ሥጋ ("የርድ ከብት" እንዲሉ) ።
ዕርድ አደረገ፡ ዐረደ (ቍርጥ አደረገ ") ።
ዕርድ፡ ደም የሚመስል ዕንጨት ቅቤ ማቅሊያ ።
ዕርድ፡ ጕድባ ምሽግ ፈፋ ጕድጓድ ።
ዕርድነት፡ ዕርድ መኾን ።
ዕርጃ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዕርገተ ቃል፡ የቃል የጌታ ወደ ላይ ማረግ ። የክርስትና ስም ።
ዕርገተ ቃል፡ የቃል የጌታ ወደ ላይ ማረግ ። የክርስትና ስም ።
ዕርገት፡ ወደ ሰማይ መውጣት "
ዕርገት፡ የበዓል ስም (ጌታችን እንደ ሰውነቱ ያረገበት - በግንቦት ፰ ቀን ኀሙስ የሚከብር ታላቅ በዓል ") ።
እርጉዝ፡ ያረገዘች/የፀነሰች ("ቅሪት ውሎ ክበድ ") ("(፩ተሰ. ፭፥ ፫)") ።"ሲበዛ እርጉዞች ይላል"
("(ሆሴ. ፲፫፥ ፲፯ ። ዓሞ. ፩፥ ፲፫ ። ማቴ. ፳፬፥ j)) =
") ።
ዕርግ በራሕ፡ ሕፃናት በነቢዩ ኤል ሳዕ ያላገጡት ለግጥ ።
እርግዝና፡ እርጉዝነት ("እርጉዝ መኾን ቅሪትነት ") ።
ዕርጓ ቀጪን ሽመል፡ ረጋ ።
ዕርጥ (የደም ዕርጥ)፡ በብዛት የሚ ወርደውን የሴት ደም የምታቆም ታናሽ ዶቃ (ኣስማት የተደገመባት ቀይ ድባ ሳንባ መሳይ ") ።
ዕርጥ፡ የክርስቶስ ኀይል ("(ማር. ፭፥ ፳፬)") ።
ዕርጭ፡ ዝም—ረ ።
ዕርፈ መስቀል፡ በመጨበጫው ጫፍ መስቀል ያለበት ማንካ (የሥጋ ወደሙ መስጫ ማቀበያ ከንዋየ ቅድሳት አንዱ ") ።
ዕርፈ መስቀል፡ የምሳሌ አነጋገር (ዕርፍ ሠም መስቀል ወርቅ ") ።
ዕርፊተ ቢስ፡ የማያርፍ እፎይ የማ
ዕርፊት (ዕረፍት)፡ ማረፍ ሞት ፪ ዝምታ ጸጥታ ።
ዕርፊት የለሽ፡ ዝኒ ከማሁ (የሚ ዋትት ") ።
ዕርፍ (ፎች)፡ ለርሻ ሥራ የተቈ ረጠ (ከሞፈርና ከማረሻ የተዋደደ የበሬ ዕቃ - ከኹለት ድግር ጋራ ወገል የጐረሠው የርሻ መሣሪያ - ሢራ. ፴፰፥ ፳፭፡ ሉቃ. ፱፥ ፷፪) ።
ዕርፍ መጣያ፡ የነሐሴ ፲፯ኛ ቀን ፍልሰታ (ዕርፍ ከርሻ ተለይቶ የሚቀመጥ በት ማለት ነው ') ።
ዕሸማ፡ ጕንጐና ።
ዕሺ (ዐሠየ)፡ የእንቢ ተቃራኒ (በጄ እሠራለኹ አደርጋለኹ ") ። "ዕሺ ይበልጣል ከሺ" እንዲሉ ።
ዕሺ በጎ አለ፡ ደግ ማለፊያ ይኹን '
ዕሺ ባይ፡ ታዛዥ ፈቃደኛ ትሑት ገር ("(ኦሆ በሃሊ)") ።
ዕሺ አለ፡ ታዘዘ ትዛዝ ተቀበለ ("(ዳን. ፮፥ ፱)") ።
ዕሺ አሠኘ፡ አንድ ነገርን ዕርቅን አስፈቀደ አስቀበለ ።
ዕሺታ፡ ዕሺ ማለት (መታዘዝ ") ።
ዕሻ፡ ዕሽ (አይዶለም ") ። "ዕሻ ዝም በሉ" እንዲል ጐንደሬ ።
ዕሽ (ሐሰ)፡ ክልከላ ። "(ተረት)" - ዕሽ አትበሉኝ (የሹም ዶሮ ነኝ ") ።
ዕሽ አለ፡ በመቅደስ ውስጥ በቅ ዳሌ ጊዜ ጠቀሰ ጠራ ኣዘዘ ("ና በል" እለ ") ። ይህ ዕሽ ማለት ቀዳሾቹ እጆቻቸውን መዘ ርጋታቸውንና የመላእክትን መኖር ያሳያል ። "ዕሺና ዕሽ" በአማርኛ ይተባበራሉ ። "(ግጥም)" - አውራ ዶሮ ጭሮ ስጥሽን ሲያፈሰው (እን ዴት ዕሽ ማለት ይቸግራል ለሰው ") ።
ዕሽ አለ፡ ከለከለ (የዝንብ የዶሮ የወፍ የባለክንፍ ") ።
ዕሽማት፡ የዕሽም ሥራ (ጕንጕናት ") ።
ዕሽም፡ ከ፫ና ካ፬ የማይበልጥ ("(ጥብ)") ድብል ሽሩባ ።
ዕሽሽ (ዐሠሠ/ትግ/ዕሻሽ)፡ የታሠሠ የተጠረገ ።
ዕሽሽ ኵምሽሽ አለ፡ ሰውነቱ ዐለቀ ተጨበጠ ("ዕፍር አለ ") ።
ዕሽሽ፡ ድቄት (ጤና ማጣት ") ። "ውሽሽን" ኣስተውል ።
ዕሽባቦ (ዕሺ/ባቦ)፡ በጄ ማለት (መታዘዝ ") ።
ዕሽባቦ አለ፡ ፈቃድ ' ፈጻሚ ኾነ ! "ኣንተ እንዳልክ" አለ ። "ዕሺንና ባቦን" እይ ።
ዕሽባቦ ዕሽባቦ አለ፡ አሽበለበለ ።
ዕሽታት፡ የማሸት የመታሸት ሥራ ።
ዕሽት (ሕስየት)፡ ማሸት መታሸት (የገላ የልስን ") ።
ዕሽት፡ ሙቅ ውሃ እየተጨመረበት የታሸ ደቃቅ ኑግ (ዳግመኛም በንስራ ውስጥ አድርገው ሲያዞሩት በፀሓይ ሙቀት ቅባት ይወጣዋል ") ።
ዕሽት አደረገ፡ አጥብቆዐሸ "
ዕቁብ፡ የተጠበቀ ጥብቅ (የመዋጮ ገንዘብ - ባንድ ሰው እጅ ተጠብቆ በዕጣ ለዕቁብተኛው የሚታደል - መጨረሻ ከሚወስ ደው በቀር ሌላው ኹሉ ይመልሳል ") ።
ዕቁብተኛ (ኞች)፡ ባለዕቁብ (የዕቁብ ማኅበረተኛ ") ።
ዕቃ መጥረቢያ፡ ዕንጨት ማለዘቢያ' ማሾያ መሸለቻ ስለት ' ያላት ታናሽ መጥ ረቢያ (ሞፈር ቀንበርን ድግርን ቈሬን ገበ ቴን መዝጊያን መቃንና ጕበንን ዋልታን ጠርብን ማእዘንን ሣጥንን ያልጋ ሸንኰ ርን ' ደንብን ዘንግን ኮርቻን በርጩማን ወንበርን መንበርን የመሰለውን ኹሉ ያን ጡባታል ") ።
ዕቃ፡ በር የመለሰው ማጀት የጐረ ሠው (በቈጥ የተሰቀለ በማጎር የተንጠለ ጠለ - የንጨት የብረት የማዕድን የሸክላ የስፌት የቈዳ ማንኛውም መሣሪያ ኹሉ - የበሬ የበቅሎ የፈረስ የቤት የንግድ የማይ ዕቃ እንዲሉ - ሲበዛ ዕቆች ይላል - ዘፀ. ፴፭፥ ፲፮) ። "ቡሖን" "ሆድን" "ለመጠ" "ላመ" ብለሽ "ልሙጥን" "ልምን" እይ ።
ዕቃ ቤት፡ ማንኛውም ዕቃ የሚቀ መጥበት ቤት (ቤተ መዛግብት ") ።
ዕቃ ቤት፡ ዕቃ ጠባቂ (የዕቃ ቤት ሹም ") ።
ዕቃ ቤትነት፡ የዕቃ ቤት ሹመት ሹምነት ። "(ተረት)" - ሰባት ወልዶ ዕቃ ቤት ነት ።
ዕቃ ቤቶች፡ የዕቃ መቀመጫዎች መኖሪያዎች ("(ሕዝ. ፵፪፥ ፲ - ፲፪)")
ዕቃ ቤቶች፡ የዕቃ ዘበኞች "
ዕቃ ግምጃ ቤት፡ ዕቃና ግምጃ ' የሚቀመጥበት ቤት "
ዕቃ ግሴት፡ ሰባራ ሥንጥር ቅራቅ ንቦ ቋንቍሬ ኵተት ።
ዕቃ ጦር፡ የጦር መሣሪያ ("(፪ቆሮ ' ፮ ' ፯)") ።
ዕቅባት፡ ሽፍናት ። "ተንበረክን" እይ ።
ዕቅብ፡ የተመላ የተሠየመ ።
ዕቅብ፡ የታቀበ የተሸፈነ ግድግዳ ድግፍ ።
ዕቅብና፡ ዝኒ ከማሁ (ጥበቃ ") ።
ዕቅታ/ሕቅታ ። "ሕቅን" እይ ።
ዕቅዳት፡ የዐቅድ አኳዃን ።
ዕቅድ፡ የታቀደ (ባሳብ የተለካ የተመ ጠነ 'ምጥን ") ።
ዕቅፍ (ሐቃፊ)፡ ያቀፈ የያዘ ።
ዕቅፍ (ሕቁፍ)፡ የታቀፈ (በዕቅፍ የተያዘ - "አንድ ዕቅፍ ዕንጨት" -
"ዕቅፍ ቂል" እንዲሉ ") ።
ዕቅፍ (ትግ/ሐባ/ሕቅፍ)፡ ሕ ፅን ብብት ።
ዕቅፍ፡ ማቀፊያ (፪ እጅ ወይም ክ ንድና ጡንቻ - "ዕንጨት በቅፍሽ ይዘኸ ና ") ።
ዕቅፍ አደረገ፡ በፍጥነት ዐቀፈ ። ፬ኛ ውን ና እይ ።
ዕቅፍ ዶሮ፡ በ፪ ክንፎቿ ውስጥ ጫጩቶች የታቀፈች እመጫት ዶሮ ።
ዕቅፍቅፍ አለ፡ ተቃቀፈ ።
ዕቅፍቅፍ፡ የተቃቀፈ ድግፍግፍ ።
ዕቅፍታ፡ የማቀፍ ሥራ ።
ዕቋ (ሕቍ)፡ የርቦ አራተኛ መስ ፈሪያ (የሰንደል የዞጲ የብረት የቈርቈሮ የታኒካ ታናሽ ሙዳይ - ባረብኛ ሖቀት ትባ ላለች ") ።
ዕቋ (ሕቋ)፡ የሱረት ማስቀመጫ ታ ናሽ ቅል (ከሕቍ የተበጀ ባለመግጠሚያ ብ ልቃጥ ") ።
ዕቋሪ፡ የረጋ ውሃ ("(ሕዝ. ፵፯፥ ፲፩)") ።
ዕበጥ (ሕበጥ)፡ ብጕር/ብጕንጅ/ዕጢ (የመሰለው ኹሉ - ዘዳ. ፳፰፥፳፯፡ ፩ሳሙ. ፭፥፮፡ ፮፥፬ - ሲበዛ ዕበጦች ይላል - ፩ሳሙ. ፮፥፲፯) ።
ዕቡ (ኅቡእ)፡ የታባ (ሽሽግ ስውር ድብቅ - "(ተረት)" - እግዜር የሔዋንን ልጆች ሊያይ በመጣ ጊዜ እኩሌቶቹን ደብቃ እኩሌ ቶቹን ብታሳየው ልጆችሽ እነዚህ ብቻ ናቸውን አላት እሷም አዎን አለችው - እንግዲያውስ ያባሻቸው ዕቡ ይኹኑብሽ አለ ይላሉ - ዕቡ የተባሉም የብሔረ ብፁዓን ሰዎች ናቸው) ።
ዕቡ ኾነ (ኅቡአ ኮነ)፡ ሽሽግ ረቂቅ የማይታይ ኾነ (ጠፋ ታጣ) ።
ዕቡይ (ዮች)፡ የታበየ (ትቢተኛ ክፉ ጭቦኛ - ዘኍ. ፲፮፥፳፮፡ ፪ጢሞ. ፫፥፪) ።
ዕቡይ ካሳ፡ የታወቁ የቅኔ መምር (ቅኔያቸው የሚያከራ ") ።
ዕባጭ (ጮች)፡ ዝኒ ከማሁ (ያበጠ የተነፋ ያሞለሞለ ዱባ የመሰለ በጕያ ባንገት ከገላ ባንዱ ክፍል ከምች የተነሣ የሚወጣ - በተኵስ በመድኀኒት ፈንድቶ የሚፈርጥ ክፉ በሽታ - ዕበጥ የካህናት ዕባጭ የሕዝብ ነው - ዕባጫም ዕባጭ የወጣበት ያለበት ሰው ባለዕባጭ) ።
ዕብለታም (ሞች)፡ ዐባይ/ዕብለት ወ ዳድ/ባለዕብለት ።
ዕብለት፡ ውሸት/ቅጥፈት (ፈጽሞ ከውነት የራቀ) ።
ዕብስተ መና፡ ኅብስተ መና ("ባላገር ኅብስት በማለት ፈንታ ዕብስት ይላል - ኅብስትን" ተመልከት ") ።
ዕብስት፡ ዕብዝት/ኅብስት ።
ዕብረት፡ ኅብረት ።
ዕብራዊ፡ የዔቦር ዘርና ወገን።
ዕብራውያን፡ የዔቦር ነገዶች (የዔቦር ተወላጆች ሕዝበ እስራኤል ") ።
ዕብራይስጥ፡ የዔቦር ቋንቋ (ሱርስትን ግእዝን ዐረብኛን የመሰለ ኦሪት ነቢያት የተጻ ") ።
ዕብዝ (ኀቡዝ)፡ የታበዘ (ግግር) ።
ዕብዝት (ኅብዝት)፡ የታበዘች (ታናሽ ዳቦ - "ዕብስት/ኅብስትን" ተመልከት) ።
ዕብጠት (ቶች)፡ ዕበጥ/ዕባጭ ።
ዕተማ፡ የማተም ሥራ ረገጣ ።
ዕትማት (ኅትመት)፡ የማኅተም ጽ ፈት ድርጊት ።
ዕትም (ኅቱም)፡ የታተመ (የእጅ ' ጽፈት ያይዶለ ") ።
ዕትራት (ቶች)፡ የዕብጠት ቅንጣት፥ ቍርብጭታ ።
ዕትባት፡ የዕትብት ቈረጣ ኹናቴ ።
ዕትብት፡ ፍጥረት ኹሉ በናቱ ማሕ ፀን ሳለ በንብርቱ ጫፍ እንዳረቄ አሸንዳ ተተክሎ ከናቱ ሆድ ምግብ የሚቀበልበት ሥጋዊ መትረብ ። በግእዝ ግን የተቈረጠች ማለት ነው ።
ዕችክ (ሐሰከ)፡ ዕስክ ዕሽክ (የዝናብ የውሃ ጠብታ ካፊያ በገላ ላይ ባረፈ ጊዜ የሚባል ዘዬ ") ። "ዕችክ ዕችካ የነጐፌ ወርካ" እንዲሉ ልጆች ☞ ትርጓሜውም በረደኝ ቀዘቀ ዘኝ ማለትን ያሳያል ።
ዕችክ፡ ዐተተ፡
ዕንቍ (ቆች)፡ ሉል (በባሕር ውስጥ ሰደፍ የምትወልደው - ዳግመኛም በግእዚ ' ባሕርይ ይባላል - "ብርጋናን" እይ ") ።
ዕንቍ፡ ኣልማዝ ፈርጥ ክቡር ደንጊያ ' የሚባል (ብዙ ስምና መልክ አለው ") ።
ዕንቍላል (ሎች)፡ ዕንቈ ሉል)፡ ከወፍ ከዶሮ ካሞራ ከእባብ ከዐዞ ሳይቀር የሚወለድ ጥጥር ክብ እንክብል ነገር ። በው ስጡ ያለው ውሃ እየረጋ ጫጩት "(ግልገል)" ይኾናል ። "(ተረት)" - ከሰነበተ ዕንቍላል በእግሩ ይኼዳል ። ካፍ የወጣ ቃል ከእጅ የወደቀ ዕንቍላል - በግእዝ አንቆቅሖ ይባላል ። "(ወይ ዘሮ ዕንቍላል)"፡ የዛር እመቤት ቀይ እንስት ዶሮ የሚገበርላት ። ይህ ነገር ምትሀት እንጂ እውነት አይዶለም ።
ዕንቍላል ቤት፡ ደርብ ሰገነት መስ ጊድ ዕንቍላል የሚመስል ዐናት ያለው
ዕንቍላል፡ የጕንዳን የምሥጥ የዘመ ሚት የሸረሪት የቍጭ የንብ የተርብ ዕጭ ዕንቍላል (የጡንቻ የባት ፈርስ አስ ኳል "(ዕጢ)") ።
ዕንቍጣጣሽ እንግጫ፡ ነቈጠ።
ዕንቂያ/ዕንቂት (ኅንቀት)፡ በእጅ በሸምቀቆ ማነቅ/መታነቅ (ድንገተኛ ሞት - "ታንቆ" ሲል ብሎ ") ።
ዕንቈ ብርሃን፡ የብርሃን ዕንቍ ።
ዕንቅ (ሕኑቅ)፡ የታነቀ (ዕፍን ") ።
ዕንቅ አደረገ፡ ዐነቀ።
ዕንቅርታም (ሞች)፡ ዕንቅርት የወጣ በት ያለበት ባለዕንቅርት ሰው ወፍ ።
ዕንቅርት (ቶች/ሕንቅርት)፡ በሰው ዐንገት ላይ ያለ ዕብጠት (በውሃ ምክንያት የሚመጣ - ድምፅን የሚዘጋ ትንፋሽን የሚከለ ክል - ዕንቅርት በቈላ ይይዛል - ደጋ ሲወጣ ይጠፋል ይሽሻል ") ።
ዕንቅፋታም ስፍራ፡ ዕንቅፋት የሚያ ጠቃው ኹል ጊዜ የሚመታው ሰው ።
ዕንቅፋት (ቶች/ዕቅፍት)፡ በመንገድ ላይ ያለ ደንጊያ (ወይም ሌላ ነገር ጕልጥምት የእግር መሰናክል ") ።
እንቅፋት፡ መሰናክል፡ ዐነቀፈ።
ዕንቅፋትነት፡ ዕንቅፋት መኾን (መሰ ናክልነት ") ።
ዕንቆቅልኸ፡ የምሳሌ ጥያቄ—እ ንቆቅልኸ ።
ዕንቆቆ፡ ዛፍ—እንቆቆ ።
ዕንብሩን ሳተ፡ ጠገበ ከልክ ዐለፈ (ይይዘውን ዐጣ ") ።
ዕንብር (ሕንብርት)፡ ልክ መጠን
ዕንብር ቢጣ፡ ብብት ጐን ("ጡንቻ ንም ያስተረጕማል - የጐን ጓዳ" ማለት ነው - "በንብር ቢጣው ያዘ" እንዲሉ) ።
ዕንብርቱን የተተኰሰ፡ የሰማውን የ ማይደብቅ ሰው
ዕንብርት (ቶች)፡ በሆድ መካከል ያለ ገላ የንዝርት ራስ መሳይ ("ልጅ በናቱ ማሕፀን ሳለ ዕንብርቱ በዕትብት ከናቱ ሆድ ስለ ተያያዘ ምግብን ኹሉ በዚያው ያገኛል - "(የጋሻ ዕንብርት)" - ጕብሩ መካከሉ - "(የምድር ዕንብርት)" - ኢየሩሳሌም ") ።
ዕንብርት የለሽ፡ ሆዳም በልቶ በቶሎ የማይጠግብ (የጋማ ከብት ") ።
ዕንቺ (ሕንኪ)፡ አንቺ ተቀበዪ ው
ዕንኩ፡ ተቀበሉ ውሰዱ ርስዎ ።
ዕንካ (ሕንክ)፡ ትእዛዝ አንቀጽ (ያዝ ተቀበል ውሰድ ") ።
ዕንካ ስላንቲያኸ፡ የባለጌ ጥያቄና የስድብ ጨዋታ (እሽኮለሌ - "ዕንካ ስላንቲ ያኸ - በምን እንቲያኸ" እንዲል እረኛ - "ስላ ንቲያን" እይ ") ።
ዕንካ በንካ፡ ሰጥቶ መቀበል (ማድፋ ፋት አለማበርከት ") ።
ዕንካ አለ (ሐነከ)፡ እጅ በጅ ሰጠ አቀበለ ።
ዕንካችኹ (ሕንክሙ)፡ እናንተ ተቀ በሉ ውሰዱ ።
ዕንክ (ሕንክ)፡ ተሰቅጠጥ ተመለስ ወደ ኋላ በል ("በሬን ተው ዕንክ" እንዲል ገበሬ) ።
ዕንክስ ዕንክስ አለ፡ እንክል እንክል አለ (ዥብኛ ኼደ ") ።
ዕንክስ፡ ዝኒ ከማሁ ለዐንከስ ።
ዕንኳ፡ ንኡስ አገባብ ።
ዕንኾ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዕንዝዝ (ሕንዝዝ)፡ በክንፍ ሲኼድ ዕዝ ጥዝ የሚል ሦስት ዐይነት ጥንዝዛ (ማር የሚሠራ ዞ ") ።
ዕንዝዝ፡ አበት አድበልባይ (ትልቅና ትንሽ - ኹለተኛ ስሙ ሥሥት ነው ") ።
ዕንግት መትረየስ፡ ወታደር፣ያነገተው።
ዕንግት፡ የተነገተ (እንስራ ጠመንዣ ") ።
ዕንጐቻ (ቾች)፡ ታናሽ እንጀራ (ስን ዝር የምታኸል ወይም የምታንስ - ኤር. ፯፥፲፰) ።
ዕንጐቻ (ቾች)፡ ዐነጠጠ
ዕንጐችት (ዕንጐት)፡ ያረግ ስም (ቅ ጠሉ ከማነሱ በቀር እንደ ዕንጐቻ ክብነት ያለው ") ።
ዕንጣ (ሕንጻ)፡ ያናጢ ሥራ ቅርጽ ፍልፍል (በሳንቃ የተሠራ ቤት ዕንጣ የሚል ባላገር ነው - በቤተ ክህነትና በከ ተማ ግን ሕንጻ ይባላል ") ።
ዕንጥስ ቢሉ፡ ቅንጥስ (በጥቂት ነገር የሚጠፋ ትዳር ሥር አልባ ") ።
ዕንጥስ አለ፡ ዐነጠሰ ።
ዕንጥስታ (ዕጠስ)፡ ማንጠስ (የጕንፋን የሳል ዋዜማ - ኢዮ. ፵፩፥ ፲) ።
ዕንጦ፡ ቀሠብ ውስጠ ክፍት ነገር (እንደ ቀረሻሽንቦና እንደ ውዥሞ ያለ ") ።
ዕንጦ፡ ኹለተኛ ጕረሮ የምንዣኸ መ ውጫ (ምንዣኹም ዕንጦ ይባላል ") ።
ዕንጨት ። የዱሮ ሰዎች በሠንጣቃ ዕንጨት ደብዳቤ ይልኩ ነበር ።
ዕንጨት (ዕፀት)፡ ርጥብና ደረቅ ዛፍ ተቈርጦ ተፈልጦ ለቤት መሥሪያና ማገዶ የሚኾን (ትንሹም ትልቁም - "(ተረት)" - ከልጅ ' ኣትወት - ያወጣኻል በንጨት - በሰው ፡ ቍስል ዕንጨት ስደድበት - "(የጅራፍ ዕን ጨት)" - እጀታ - "(የጪስ ዕንጨት)" - ወገርት ") ።
ዕንፉጭ (ሐንፈጸ/ሕንፉጽ)፡ ነፋ ስና ብርድ የመታው ቀላል ፍሬ እኸል (መንሽ በተባለ ጊዜ ከገለባ ጋራ የሚኼድ - ሞኝ ሰውም ዕንፉጭ ይባላል ") ።
ዕኚ፡ ወንፈል ዐኘከ ። ዕ
ዕኛኪ፡ ታኝኮ የተጣለ (ብላቶ ምጣጭ ") ።
ዕኝ፡ ተባብሮ መብላትን የመንጋጋን ምስጢር ያሳ ያል ።
ዕኝ አለ፡ ድዱን ገለጠ አሰጣ (ጥርሱን አሳየ ሰውየው ዝንጀሮው ") ።
ዕኝ፡ ወንፈል የጕልበት ብድር "
ዕኝኝ ብላ፡ ከነሐሴ ፳፰ ቀን እስከ ፴ ባለማቋረጥ የሚዘንብ ዝናብ ወሊስ ።
ዕኝኝ አለ፡ ጨቀጨቀ ነዘነዘ (ነገር ") ።
ዕኝኝ፡ ጭቅጭቅ ንዝንዝ "
ዕኝክ (ሕኑክ)፡ የታኘከ የተበላ የተ መሰኳ የተመነዠኸ (ምንዥኸ ") ።
ዕኝክ አደረገ፡ ዐኘከ ።
ዕከማ፡ የማከም የማስታመም ሥራ ።
ዕከካም፡ ዕከክ ያለበት (ባለዕከክ - ዕከክ የያዘው የወረሰው ") ።
ዕከክ፡ ፎከት/ደረመን/ፈረሳቤት (የጥ ፍር ን ኪት - ዘዳ. ፳፰፥፳፯) ።
ዕክል፡ ዐዘን/ለቅሶ/ችግር ("እከሌን ዕክል ገባው አገኘው" እንዲሉ) ።
ዕክም አለ፡ ጸጥ አለ (ጨመተ ረጋ ከመታከም የተነሣ ") ።
ዕክም፡ የታከመ (መድኀኒት የተደረገ
ዕክምና (ሕክምና)፡ ሐኪምነት (ሐ ኪም መኾን ") ።
ዕወቅ (ዑቅ)፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ("ተጠንቀቅ ተጠበቅ ") ።
ዕወቅልኝ፡ ባታውቅብኝ (ከሳሽና ተከሳሽ ለምስክር የሚያቀርቡት ጥያቄ - "(የልብ ዐውቃ)" - ሥልጡን አሽከር - "ቈነጨ ብለሽ ቍን ጨን" እይ ") ።
ዕውረ ልብ፡ አንዳች ዕውቀት የሌ ለው (ለጣዖት የሚሰግድ አረመኔ - ደንቈሮ ኣላ ዋቂ ልበ ዕውር ") ።
ዕውሪት (ዕውርት)፡ የታወረች ።
ዕውር (ሮች/ዕዉር)፡ የታወረ ዐይን የሌለው (በሰው ትከሻ እየተመራ የሚ ኼድ - "(ተረት)" - ዕውር ሲወበራ ከመሪው ይጣላ - ዕውር ያለበት ደብር ዓሣ ያለበት ባሕር ሳይበጠበጥ አያድር ") ።
ዕውር መሪ፡ ዕውርን የሚመራ ።
ዕውር መሪ)፡ ዕውርን በትከሻው የሚመራ።
ዕውር ዕከክ፡ እዥና መግል የሌ ለው ።
ዕውር፡ የጐለደፈ/ጐልዳፋ (ብርሃናዊ ጥፍሩን ያጣ ") ።
ዕውርነት፡ ዕውር መኾን ("(ዘካ. ፲፪፥፬)") ።
ዕውሮች (ዕዉራን/ዕዉራት)፡ ዐይኖቻቸው የታወሩ የተሰወሩ ወንዶችና ሴቶች ።
ዕውቀት (ቶች)፡ ዘዴ/ፈሊጥ/ ብልኀት/ፍልስፍና (ማወቅ ማስተዋል - "ብዙ ሰዎች ይመረምራሉ ዕውቀትም ይበዛል" - ዳን. ፲፪፥፬ - ዕውቀትና ፍጥረት አንድ ቀን ነው ") ።
ዕውቂያ፡ ልምድ/ማወቅ ("(መሳ. ፲፰፥ ፳፰)") ።
ዕውቅ (ዕዉቅ)፡ የታወቀ/የተለመደ ።
ዕውጪ፡ ዕሠይ ወሸን ።
ዕዛብ (ሕዛብ)፡ የጠፍር ቋድ (የል ጓም መያዣ መግቻ አራት ማእዘን - ሲበዛ ዕዛቦች ይላል ") ።
ዕዝ አለ፡ ጥዝ አለ (ጮኸ ንቡ ጥንዝዛው ተርቡ ዝንቡ ") ።
ዕዝል (ሕዙል)፡ የታዘለ (በዠርባ ላይ ያለ ልጅ - ወይም በሽተኛ ") ።
ዕዝል (ሕዝል)፡ የዜማ ስም (የሐ ዘን ዜማ - በመቤታችን ዠርባ የታዘለ የጌ ታችን ምሳሌ - ይኸውም ከአይሁድ የሚያሳ ዝን መከራ መቀበሉንና መሰቀሉን ያሳያል - ወርድ ንባብም የዕዝል ተከታይ ስለ ኾነ ዜማ ሐዘን ይባላል ") ።
ዕዝል፡ በጽፈት ዐናት የተደረበ ፊ ደል ጭረት ("የውጣ ዕዝል ቅጽል የላትም ") ።
ዕዝናት፡ ለሰው ዐዝኖ ተቈርቍሮ የሚ መክሩት ምክር ተግሣጽ ።
ዕዝን፡ የታዘነ ዐዘን ።
ዕየራ፡ ቅልቀላ ድብለቃ ።
ዕይራት፡ ቅልቅልነት ድብልቅነት ።
ዕይር፡ የታየረ ቀለም ጠገራ ባሩድ አ ቦልሴ ውጥንቅጥ ("(ሔኖ. ፲፬፥፫)" - ትርጓሜ) ።
ዕደላ፡ ማደል ።
ዕደና፡ ፍለጋ/ሽመቃ ።
ዕዳ (ዎች)፡ በቅጣትና በብድር በ ካሳ ምክንያት ለመንግሥት ላበዳሪ ለተበደለ የሚከፈል ገንዘብ ("ዕዳና ደም" -
"ዱብ ዕዳ" እን ዲሉ - "(ተረት)" - ያባት ዕዳ ለልጅ የአፍንጫ ዕዳ ለእጅ ") ።
ዕዳ ሰርጉ፡ ተበድሮ የሚደሰት ።
ዕዳ፡ በቁሙ ዐደየ ።
ዕዳ በዕዳ ኾነ፡ በዕዳ ላይ ዕዳ መጣ ተጨመረ ።
ዕዳ በደል፡ የበደል ዕዳ ካሳ ።
ዕዳ ተሜዳ፡ ያልታሰበ ዕዳ ።
ዕዳ ኾነበት፡ መጣበት/ተደረገበት ።
ዕዳሪ አወጣ፡ ጨፈለቀ ።
ዕዳሪ ወጣ፡ ወገቡን ሞከረ/ኰሳ ።
ዕዳሪ፡ ውጭ ሜዳ አፍኣ ።
ዕዳሪ፡ ያልታረሰ መሬት ቀርጣ ጥጋት ።
ዕድለ ቢስ፡ ዕድለ መጥፎ ።
ዕድለኛ፡ ዝኒ ከማሁ (ባለዕድል) ።
ዕድላም፡ የታደለ ።
ዕድላት፡ የማደል/የመታደል ሥራ ።
ዕድል፡ ስጦታ/ዕጣ/ክፍል/መክፈልት ።
ዕድል የለሽ፡ ያልታደለ ።
ዕድል ፈንታ፡ የድርሻ ዕድል ("ዕድል ፈንታ ጥዋ ተርታ" እንዲሉ) ።
ዕድም (ቅጽል)፡ የታደመ/የተቀጠረ ("(የተቃጠረ)") ።
ዕድሞ፡ ያፈር ቤት—እድሞ ።
ዕድር፡ ስብሰባ ጽኑ ደንብ ("(ተረት)" - ያገር ዕድር ለንጉሥ ያስቸግር ") ።
ዕድር ገባ፡ ከዕድር ስለ ቀረ መቀጮ ከፈለ ።
ዕድርተኛ (ኞች)፡ ዕድር ያለው ባለዕድር ።
ዕድን፡ የታደነ/የተያዘ/የተወጋ/የተገ ደለ እንስሳ (ወይም ሥጋ ") ።
ዕድያት (ትግ)፡ የጥለት ስም (ብጫን መደብ አድርጎ ማንኛውንም ጥለት ያሳያል) ።
ዕድጋት (ኅድገት)፡ በጥለትና በቍ ቲት መካከል የተጣለ ማግ ።
ዕድጋት፡ ቈረጣ/ምለሳ ።
ዕድግ፡ የታደገ/የተመለሰ (ምልስ - የተገዛ ግዝ ") ።
ዕጀላ፡ ሽፈና/ጥቅለላ ።
ዕጅላት፡ ሽፍናት/ጥቅልላት ።
ዕጅል፡ የታጀለ/የተሸፈነ (ስልቻ ቅሪላ ቈርበት ደበሎ እጅ እግር ") ።
ዕጅብ፡ የታጀበ/የተከበበ/የታከበ (ክምቹ ዕጭቅ ") ።
ዕጅብኝ፡ ረፋድ (ከብት የሚመሰግበት ") ።
ዕገውጡ (ውፁአ ሕግ)፡ ሕገ ወጥ ።
ዕገዛ/ዕግዣ፡ የማገዝ/የመርዳት ሥራ ።
ዕጉም (ጐዣም)፡ የሙጥኝ።
ዕጉሥ፡ ታጋሽ (ግእዝ) ።
ዕግ፡ ሕግ/ደንብ/ውሳኔ ("መረን ") ።
ዕግል፡ የቂጥኝ ምላሽ።
ዕግል፡ ያትክልት እንቦቀቅላ (የተጫረ የተኰተኰተ ") ።
ዕግም፡ የታለመ (ደም የወጣው ") ።
ዕግሽ፡ ማቋቻ/መደቀኛ ("(አልቃሽ)" - እትስ ምን ልትኾናት ወንድም ምን ሊኾናት ከዕግሿ ላይ ዐፍሣ አንድብር ሲኾናት ") ።
ዕግት (ዕጉት)፡ የታገተ/የተከበበ/የ ተያዘ/የተወሰደ ።
ዕጎቻ፡ የዋስ ዕቃ ገንዘብ ከብት።
ዕጠ መሰውር (ዕፅ መሰውር)፡ አስ ማተኛን ከአጋንንት ጋራ አንድነት ያደረገውን ሰው ከመታየት የሚሰውር ዕጥ ("ባላገሮችም ጋኔን አንዳንድ ጊዜ በምትሀት ገዝፎ ሲታይ ዕጡን የጣለ ሰይጣን ይሉታል - ዕጥ የተባለም ርቀት ነው ") ።
ዕጠ ፋርስ (ዕፀ ፋርስ)፡ ከፋ ርስ አገር የመጣ ዕንጨት ("ተማሮች ቅጠሉን አፍልተው ከጤፍ እንጀራ ጋራ ፈትፍተው በቀመሱት ጊዜ አእምሯቸውን ለውጦ ማደሪያ ቸውን ያናግራል - ማብረሻውም የኑግ ልጥልጥ ወይም በሶ ነው ") ።
ዕጠ ፋርስ፡ የፍሬው ልብስ እሾኸ ያለበት ተክልነት የሌለው የዱር ዕንጨት ("ቅጠሉን በጎች ቢበሉት ራሳቸውን ያዞራል - ሰውም ቢቀምሰው ያሳብዳል - ባላገሮችም ዐጤ ፋሪስ ይሉታል - ይህ ኹለት ዐይነት ዕን ጨት ባገዳ በቅጠል በፍሬ ልዩ ሲኾን ልብን በመንሣት ስለ ተባበረ ባንድ ስም ተጠራ - በካህናት ዘንድ ግን ፪ኛው ካ፩ኛው ተለይቶ አስተናግር ይባላል - "ነገረን" እይ ") ።
ዕጡ ዱብ አለ፡ ደነገጠ (ክው አለ - ውቃቢ ራቀው ") ።
ዕጡብ (ዐጸበ/ዕጹብ)፡ ድንቅ/ግ ሩም/ልዩ ("ቅጽል ሲኾን ዕጡብ ብልኅት ዕ ጡብ ነገር ያሠኛል - ዕጡብ ድንቅ ቢል የ ድንቅ ድንቅ ማለትን ያሳያል ") ።
ዕጢ (ኀጠጠ/ኅጢ)፡ በገላ ውስጥ ያለ ዕትራት (ቋር - የሥጋ ቅንጣት ጓጓላ ") ።
ዕጣ (ዐፀወ/ዕፃ)፡ ዐጪርና ቀጪን ዕንጨት (ከመካከለኛ ጣት የሚበልጥ - በክ ፍያ ጊዜ በእያንዳንዱ ሰው ዕድልና ድርሻ ላይ የሚወድቅ - ሲበዛ ዕጣዎች ይላል - በእስ ራኤልም መንግሥት ክፉ የሠራ ሰው ዕጣ ይወድቅበት ነበር - ኢያ. ፯፥፲፰፡ ፩ሳሙ. ፲፬፥፵፪፡ ዮና. ፩፥፯ - "ዕጣ በድግጣ" እንዲሉ) ።
ዕጣ ሑዳድ፡ ላንድ ገባር በዕጣ የ ተሰጠ የሑዳድ ድርሻ ።
ዕጣ ሰበረ፡ ዕጣ አዘጋጀ (ምልክት' አደረገበት ") ።
ዕጣ ተጣጣለ፡ ዕጣ ዕጣ ለዚህ ጌታ ይውጣ ተባባለ ("(ዐብድ. ፩፥፲፩፡ ማቴ. ፳፯፥፴፭)") ።
ዕጣ፡ ዕጣ ያረፈበት የወደቀበት ፈ ንታ ።
ዕጣ ወጣ፡ ድርሻው ለባለዕድሉ ።
ዕጣ ወጣለት፡ አንድ ነገር አገኘ (ተሾመ ተሸለመ ") ።
ዕጣ ወጣበት፡ ለቅጣት ለሞት ተ ወሰነ ።
ዕጣ ጣለ፡ በማንኛውም ዕቃና በቅ ርግን ሥጋ ላይ አስቀመጠ ።
ዕጣቢ፡ የልብስ የዕቃ እድፍ ("ተስ ዐቱ ቅዱሳን ከደብረ ሲና የመጡ የኹለት መነኮሳት እግር ዕጣቢ ጠጡ - መነኮሳቱም ቅ ዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ናቸው ይ ባላል ") ።
ዕጣነ ሞገር፡ የቅኔ ስም (በቅዳሴ መጨረሻ የሚቀኙት ፱ኛ ቅኔ ኹለት ዐይነት ዜማ ግእዝና ዕዝል ያለው - "ወገረ" ብ ለኸ "ሞገርን" ተመልከት ") ።
ዕጣን (ሕፃን)፡ በቁሙ ዐራስ ፥ ጨ ቅላ ርጥብ ለጋ ትንሽ ልጅ (ማሞ ማሚት ") ።
ዕጣን (ኖች)፡ ሽታው የሚጣፍጥ የዛፍ ሙጫ ("ዕንጨቱ በውጋዴና በመርሐ ቤቴ በረሓ ይገኛል ") ።
ዕጥ (ዕፅ)፡ ዕንጨት/ዛፍ (ትልቁም ትንሹም ርጥቡም ደረቁም ") ።
ዕጥ፡ የክታብ ውስጥ ታናሽ ዕንጨት ።
ዕጥ የኾነ ስምጥ፡ ድንገት የ ጠፋ ነገር የደረሰበት ባይታወቅ ("ዕጥ የኾነ ስምጥ" ይባላል - ዕጥ ቅለትን "(ቅጠልነትን)" ስምጥ ክብደትን "(ደንጊያነትን)" ያሳያል - ነፋስ ይውሰደው ውሃ ይብላው አልታወቀም ማለት ነው ") ።
ዕጥር (ኅጥር)፡ የሽቱ ስም (ማንኛ ውም ሽቱ - ባረብኛ ዐጥር ይባላል - "ኅጥርን" ተመልከት ") ።
ዕጥር (ሕጸር)፡ የታጠረ/የተከበበ ።
ዕጥር፡ ማጠር ።
ዕጥር ምጥን አለ፡ ረዥም ወይም ዐጪር ሳይኾን መካከለኛ ድልድል ኾነ ።
ዕጥር አለ፡ ዐጠረ ።
ዕጥበት፡ ዐጠባ/መታጠብ ።
ዕጥቤ፡ ዐጠብ ።
ዕጥብ (ኅፁብ)፡ የታጠበ/ጥሩ/ጸዐዳ ።
ዕጥብ ያለ፡ ዋና ሌባ = ልብስ ሲታ ጠብ ከእድፍ እንዲለይ (ከጨዋነትና ሠርቶ ከ መብላት የራቀ ማለት ነው ") ።
ዕጥብጣቢ፡ የብዙ ሸማና ዕቃ የዕጣቢ' ።
ዕጥጥ ሙጥጥ አለ፡ ጕድል ጥርግ ።
ዕጥጥ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ዕጥፋት (ቶች)፡ የማጠፍ የመታጠፍ አኳዃን (ቅልብሳት ቅንፋት - የልብስ የቈዳ ስብራት ") ።
ዕጥፍ (ዕጹፍ)፡ የታጠፈ ጥንድ (ነ ጠላ ያይዶለ ልብስ ወይም ሌላ ነገር - ካህ ናት ግን ዕጽፍ ይላሉ ") ።
ዕጥፍ አለ፡ ታጠፈ ።
ዕጥፍ አደረገ፡ ዐጠፈ ።
ዕጥፍ ዘርጋ አለ፡ እየታጠፈ ተ ዘረጋ (ጣቱ የጐመኑ ትል ") ።
ዕጥፍ ድርብ (ምክዕቢት)፡ ኹለት እጥፍ ። ዕጥፍ አራት እጅ ።
ዕጥፍጥፍ አለ፡ ተጣጠፈ ።
ዕጥፍጥፍ፡ የተጣጠፈ ።
ዕጦተኛ፡ ችግረኛ ።
ዕጦት (ኅጥአት)፡ ማጣት/ችግር/ድ ኸነት ።
ዕጨ፡ የዕጨጌ ከፊል ("ዕጨ ዮሐንስ ዕጨ ዕንባቆም" እንዲሉ) ።
ዕጨጌ (ዎች/ሕፁየ ጌ)፡ የም ድር ዕጮኛ (ሊቀ ካህናት - ጳጳሳት - መንፈሳዊ ሹም - ባለሢሶ መንግሥት - የደብረ ሊባኖስ ኣበ ምኔት - "(የገዳም ኣባት)" - በነብሪድ ፈንታ የገባ - ይህ ስም የተዠመረው ባጤ ይኩኖ አምላክ ዘመን ነው - በግእዝ ሐፄጌ ይባላል - አላዋቆች ግን ጮጌ ከማለት ከወላምኛ የመጣ ነው ይላሉ - "ጌን ንቡረ እድን" ተመልከት ") ።
ዕጨጌ፡ አቡን ጳጳስ ("(ግጥም)" - መኳንንቱ ሠለጠኑ የወጌን አገር ለመኑ - እኔ የምፈራው ይህነን ካቡን በላይ መኾን ") ።
ዕጨጌ፡ የምድር ዕጮኛ—ዐጪ ።
ዕጨጌነት (ግነት)፡ ዕጨጌ መኾን (መንፈ ሳዊና ሥጋዊ ሹመት ደርቦ መያዝ ") ።
ዕጨጌነት ከሚስት፡ ዐጤ ይኩኖ አምላክን ያነገሡ ፪ኛው ተክለ ሃይማኖት ባለ ሕግ ነበሩና ሚስታቸው ከሞተች በኋላ በደ ብረ ሊባኖስ መንኵሰው ዕጨጌ ስለ ኾኑ አቦ ብላት ዕጩጌነት ከሚስት ይሏቸዋል ("ኪ ወ ክ ") ።
ዕጩ (ሕፁይ)፡ የታጩ (ለቁም ነገር የታሰበ - ሲበዛ ዕጩዎች ያሠኛል ") ።
ዕጩ (ዕፄሁ)፡ ያ ዕጭ (የርሱ ዕጭ ") ።
ዕጩ፡ ትሉ—ዕጭ ።
ዕጭ (ጮች/ዐፀየ/ተላ/ዕፄ/ትል)፡ የንብና የተርብ የጥንዝዛ ዕንቍላል ቅርጽ አበጅቶ እስኪንቀሳቀስና ክንፍ እስኪ ያወጣ ድረስ ዕጭ ይባላል ("ትል ማለት ነው ") ።
ዕጭ አዋለ፡ ሠራ/አበጀ/አተላ ።
ዕጭ ጐመጭ፡ የጐመጭ ዕጭ (ወ ይም ዕጭ ያለበት ጐመ ") ። "ጐመጭን" ተመ ልከት ።
ዕጭቅ፡ የታጨቀ/የተከተተ (ዕጅብ ቅ ጠል ወይም ሌላ ") ።
ዕጭዳት፡ የማጨድ የመታጨድ ኹ ኔታ (የማጭድ ቅሬታ ") ።
ዕጭድ (ዕጹድ)፡ የታጨደ/የተቈ ረጠ (ቍርጥ - "ጭድን" አስተውል - "ዕጭድ አደረገ" - ቍርጥ ቡጭቅ አ ደረገ ") ።
ዕጮኛ (ኞች)፡ ሴት ያጨ ጕል ማሳ (ለባል የታጨች ልጃገረድ - ማቴ. ፩፥፲፮፥፲፰) ።
ዕፀ ሕይወት፡ በገነት የሚገኝ ("የሕ ይወት ዛፍ የሥጋ ወደሙ ምሳሌ - "ሲሎንዲ ስን" እይ ") ።
ዕፀ ልቡና፡ ዕውቀትን ማስተዋልን የሚገልጥ ።
ዕፀ መስቀል፡ የመስቀል ዕንጨት ።
ዕፀ መድኀኒት፡ ዝኒ ከማሁ ለዕፀ ሕይወት ።
ዕፀ ሞት፡ መርዝነት ያለው ዛፍ (ሰውን የሚገድል ") ።
ዕፀ ሳቤቅ፡ ቧሔ ዐረግ ።
ዕፀ በለስ፡ የበለስ ዕንጨት ።
ዕፀ ተከዚ፡ አሓያ ወይም ሌላ ።
ዕፀ አእምሮ፡ በለሶን ።
ዕፀ ጥበብ፡ የገነት በለስ ።
ዕፀ ፋርስ፡ ቅጠል—ዕጥ ።
ዕጹብ፡ ቃለ አንክሮ ።
ዕጹብ፡ ድንቅ ጭንቅ ጥብ ።
ዕፅ፡ ዕንጨት ዛፍ (ርጥቡም ደረቁም ") ።
ዕፅ ከንቱ፡ ጧት ይበቅልና ማታ የሚደርቅ ("(መዝ. ፮፥ ፮)") ።
ዕጽፍ፡ የታጠፈ ጥንድ ዕጥፍ ።
ዕፍረተ ሥጋ (ኀፍረተ ሥጋ)፡ የወንድና የሴት ብልት ሲያዩት የሚያሳፍር ("(፩ቆሮ. ፲፪፥ ፳፫)") ።
ዕፍረተ ቅል፡ የፍርሀት የማፈር ቅል (የምሳሌ አነጋገር - ቅል ሠም ዕፍረት ወርቅ ነው - እከሌ ዕፍረተ ቅሉን ሰብሯል "(ይሉኝ አይል ኾኗል)" እንዲሉ - ዳግመኛም ቅል ራስ ዕፍረት ይሉኝታ ይኾናል ") ።
ዕፍረተ ቢስ፡ ሰውን የማያፍር (የዶሮ ዐይን የበላ ") ።
ዕፍረቱን ጣለ፡ ገለጠ ተጋለጠ ።
ዕፍረት (ኀፍረት)፡ ማፈር (ውርደት ፍራት ገመና ነውር - መዝ. ፻፴፪፥ ፲፰) ።
ዕፍረት፡ አባለ ዘር ሕልጽ ("(ዘሌ. ፲፰፥ ፮—፲፱)") ።
ዕፍረት የለሽ፡ ግንባረ ደረቅ ።
ዕፍኝ (ኞች/ሕፍን)፡ ኹለት ውስ ጥ እጅ ጐን ለጐን ባንድነት ሲገጥም ዕ ፍኝ ይባላል ። በዱር ያለ ሰው በዕፍኙ ውሃ ይጠጣል ። ለዶሮ እኽል በዕፍኙ ይሰጣል ። "ጥርኝን" ተመልከት ።
ዕፍኝ፡ ፪ ጥርኝ ፩ ድብልዝኝ ።
ዕፍኝ፡ በዕፍኝ የተያዘ የተለካ ("አንድ ዕፍኝ እኸል" እንዲሉ) ።
ዖ፡ ስመ አምላክ (ደኃራዊ ኋለኛ መጨረሻ - "አልፋን" ተመልከት - አለፈ ") ።
No comments:
Post a Comment