ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
የ ፡ ፲ኛ ፊደል በአበገደ በጥንታዊው ተራ ቍጥር ("በፊደልነት ስሙ የማን በአኃዝነት የ፲ ይባላል") ።
የ፡ (ኢ) አሉታ ።
የ፡ (ዘ) በኀላፊ አንቀጽ መነሻ ኹሉ እየገባ ባለቤት ሳይኖር በቂ ይኾናል።
የ፡ (ዘ) ባለቤት ሲኖር ቅጽል ይኾ ናል ።
የ፡ (ዘ) የዘርፍ ደፊ ("ወይም አያያዥ የሰማይ · አምላክ የአቤል መሥዋዕት የሙሴ ጽላት የሰሎሞን መቅደስ የልጅ ጥፉ በስም ይደግፉ ቢል ጥፉ የኾነን ልጅ ያሠኛል ቅጽልን ከነተሳቢው ሲደፋ ያህያ ውሃ ጠጪ ይላል ፭ኛውን ያ እይ") ።
የ፡ (ዚኣ) ባለገንዘብነትን የሚገልጥ ጠቃሽ ("ይኸውም አያያዥ ካለው ይገባል ይህ ቤት የሱ የሷ የኔ የኛ የነኛ የናንተ ያንተ ያንቺ ነው") ።
የሐናን ለወለተ ሐና፡ ያንዱን ለሌ ላው ።
የሐዘንና የማድነቅ ቃል ወይም የመልክት ("አንተንም መሬት ይበላኻላ እንደ ሞኝ ሰው እንደ ተላላ ል የዘንድ አንቀጽ መነሻ ሲኾን ከሩቁ ወንድና ከሩቆቹ በቀር በኹሉ በትእ ዛዝ ግን እኔ በሚል ብቻ ይገባል ልትጥፍ ") ("እሷ") ።
የሃይማኖት ቀንቃኞች)፡ በወዲያ ግብጾች ባገራችን ደብረ ሊባኖሶች ።
የሑዳድ ፈሪ፡ ዕጣ ሑዳዱን ሳይሖድድ የቀረ የሚከፍለው ዕዳ ።
የኋሊት፡ ወደ ኋላ አካኼድ/አረማመድ ("ልጁ ፊቱን ሳይመልስ የኋሊት ይ ኼዳል።") ።
የኋላ እሸት/የኋላ ወርቅ፡ የወንድና የሴት ስም ("ዘግይቶ ዘግይታ የተገኘ የተገኘች ማለት ነው") ።
የኋላ የኋላ፡ ቈይቶ ቈይቶ ("በሐሰት ከፍ ከፍ ያለ የኋላ የኋላ መውደቁ አይቀርም") ።
የለ፡ ባለ ("ሐማሴን") ።
የለ/የለም (ኢሀለወ/ወኢሀለወ)፡ እሱ የለ ።
የለ/የል (ኢሀለወ)፡ ኣለ ያለውን የለ በማለት የሚነገር አፍራሽ አሉታ አንቀጽ ።
የለሽ፡ የሌለው ።
የለሽ/የለሽም (ኢሀለወኪ/ወኢ ሀለወኪ)፡ ምንም የለሽ ።
የለሽ/የለሽም (ኢሀሎኪ/ወኢሀሎኪ)፡ አንቺ የለሽ ።
የለበመ ("የሚለብም ዐዋቂ ጭምት አስተዋይ የሚመላ ሠያሚዐቃቢ ልበማ ዕውቂያ ሥየማ መለበም ማወቅ መጨመት መሠየም መምላት የሚያ መለበሚያ ማወቂያ መምሊያ መሠ አለበመ ") ("አለበወ") ።
የለች/የለችም (ኢሀለወት/ወኢሀለወት)፡ እሷ የለች ።
የለን/የለንም (ኢሀለወነ/ወኢሀለወነ)፡ ዕውቀት የለን ይላል ።
የለን/የለንም (ኢሀሎነ/ወኢሀሎነ)፡ እኛ የለን ይላል ።
የለኝ/የለኝም (ኢሀለወኒ/ወኢሀለወኒ)፡ ገንዘብ የለኝ ።
የለኸ/የለኸም (ኢሀለወከ/ወኢሀለወከ)፡ ገንዘብ የለሽ ።
የለኸ/የለኸም (ኢሀሎከ/ወኢሀሎከ)፡ አንተ የለኸ ።
የለኹ/የለኹም (ኢሀሎኩ/ወኢሀሎኩ)፡ እኔ የለኹ ።
የለው/የለውም (ኢሀለዎ/ወኢሀ ለዎ)፡ ዕውቀት ' የለው ።
የሉ/የሉም (ኢሀለዉ/ወኢሀለዉ)፡ እነዚያ የሉ።
የሊ (ዔሊ)፡ ድንጋይ ልብሱ ።
የላመ፡ የጣመ፡ የመኳንንት፡ ምግብ፡ የለሰለሰ፡ የጣፈጠ፡ መብል፡ ገንፎን፡ ዐልጫ፡ መረቅን፡ የመሰለ ።
የላት/የላትም (ኢሀለዋ/ወኢሀለዋ)፡ አላንድ የላት ("እንቅልፍ የላት ነቀሰ ንና (ቀለፋ) ብለኸ እንቅልፍን ተመልከት") ።
የላቸው/የላቸውም (ኢሀለዎሙ ን/ወኢሀለዎሙ ን)፡ ትጋት የላቸው ።
የላችኹ/የላችኹም (ኢሀለወክሙ ን/ወኢሀለወክሙ ን)፡ ዕውቀት የላችኹ ።
የላችኹ/የላችኹም (ኢሀሎክሙ/ወኢሀሎክሙ)፡ እናንተ የላችኹ ።
የላይ ልብስ እጀ ሰፊ ("ከጥጥ ከጠጕር የተሠራ ዐጪር ጥብቆ ረዥም ቀሚስ በስተፊት ክፍት ባላዝራር የኾነ የፈረንጅ ስፌት ኮትና ሱሪ እንዲሉ ኮት እንግሊዝኛ ነው ኩታ ኪታ ኮት አንድ ዘር መኾናቸውን አስተውል ከተበ ") (ከቲብ/ከተበ/ከሰበ) ።
የሌለ ፣ ያልተገኘ፡ ያልተቀመጠ፡ ያልቈየ፡ ያልኖረ፡ ያልነበረ፡ ("ዘዳ. ፳፱፡ ፲፭") ።
የሌለ፡ ያልነበረ፡ ሌለ ።
የሌለበት፡ ያልነበረበት፡ ያልተገኘበት፡ ("ዮሐ. ፰፡ ፯") ።
የሌለው፡ ያልተቀበለ፡ ያሊያዘ።
የልብ ልብ በቃው)፡ በሰው፡ ታመነ፡ የጭካኔ፡ ጭካኔ፡ ተሰጠው፡ አልፈራም፡ እንዳሻው፡ ተናገረ፡ የያዘውን፡ ይዞ
የልካ (ኦሮ፡ ኢልካን)፡ የዝኆን ጥርስ አንባር ።
የልጅ ቅዘን ይንካልኸ)፡ ሰው ዐዲስ ልብስ በለበሰ ጊዜ የሚቀበለው ምርቃት ።
የልጅ ቅዘን)፡ ዐይን አበባ ብጫ ጥለት ።
የልጅ የፈረስ ቍንጮ የተጐነጐነ ጠጕር ("ከልጅነት እስከ ዕውቀት ከኩተት እስከ ሽበት እንዲሉ። ኮተት ጓዝ እክት ዕቃ ግሴት ኮተት እድፍ ጭቅቅት ኮተታም ጓዛም እክታም አድፋም ኮተቴ ጥቍር አደንጓሬ ባለሐረግ ኮተቴ የኔ ኮተት አከታተት አጨማመር መክተት የካ ቲትን እይ የዚህ ዘር ነው ኸ የፊደል ስም የከ ዲቃላና ወራሽ ግእዝ አሰርከኒ ፈታሕከኒ ወሰድከኒ ያለውንአሰርኸኝ ፈታኸኝ ወሰድኸን ማለቱን ያሳ ያል የኀና የኸ ድምጥ አንድ መኾኑንም ባቡጊዳ እይ ዳግመኛም የሀሐ ተለዋጭ ሲኾን ይህ ይኸ ምንዛህ ምንዣኸ በረሓ በረኸኛ ይላል ከሀሐኀም ተለይቶ በግስ መድረሻ ደለኸ ጮኸ ሲል ይገኛል ከካዕብ እስከ ሳብዕ ያለውም ጮኹ ጯኺ ጩኻ መጮኼ ጩኸ ጩኾ እያለ ይነገራል ኹ የኩ ወራሽ እኔ ለሚል የአንቀጽ ዝርዝር ሲኾን በግእዝ በላዕኩ ሰግ ኸ ፮፻፺፮ ከቸቸ ") (ቀጨጩ) ።
የልፍኝ አሽከር)፡ አንጣፊ ጋራጅ አስታጣቢ አልባሽ መጫሚያ አቀባይ ዠርባ ጠቋሚ ተረኛ የውስጥ አሽከር ። በአረብኛም "አስከር" ይባላል ።
የሎሄ፡ ኤሎሄ ።
የሎሄ የሎሄ አለ፡ የጭንቅ ጩኸት ጮኸ ("ኢዮሂ ኢዮሄ አለ ኤሎሄና ኢ ዮሄ የሎሄ ፫ቱ ኹሉ አንድ ዘር ናቸው") ።
የሎሚ እሸት)፡ ቅጠሉ የምስር ቅጠል የሚመስል ታናሽ ዕንጨት (ሽታው የሚጣፍጥ - በመስከረምና በጥቅምት የሚያውድ) ።
የሎስ (ሶች)፡ ያሞራ ስም ("ንስር ግልገል አንሣ መቀነትማ የሎስ ያንሣኸ እንዲሉ መልኩ በስተዠርባው ጥቍር አረንጓዴ በስተፊቱ ከላድማ ነው ባፉና በክንፉ በእግሮቹ ላይ ንጣት አለው ከክንፍ እስከ ክንፉ ፭ ክንድ ይኾናል") ።
የመስቀል መሬት)፡ የካህን ርስት።
የመንግሥታት ማኅበር)፡ የመንግሥታት መልክተኞች ጉባኤ አደባባይ ዐውድ ።
የመጠጥ ዐረፋ)፡ ኰረፌ ።
የመጣ፡ ቢመጣ፡ አስቀድሞ፡ የተደረገ፡ መከራ፡ ወደ፡ ፊትም፡ ቢደረግ።
የሙጥኝ፡ ተማጣኝ የሚጠጋው ሰው ።
የሙጥኝ አለ፡ ተማጠነ (የሰውን ል ብስ ያዘ ተቈራኘ ") ።
የሚ (ዘይ)፡ በትንቢት መነሻ እየገባ ለሩቅ ወንድ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች ቅጽልና በቂ ይኾናል።
የሚለብስ ቀዳሽ ("በግ እዝ ለባሲ ይባላል ሥጋን ተመልከቱ ለበስ የለበሰ ጉም ለበስ ብረት ለ በስ እንዲሉ። 704 ") ።
የሚያስማ/የሚሳማ፡
የማ (ዘኢይ)፡ የትንቢት አሉታ በቂ ቅጽል መነሻ ።
የማምሻ፡ ከመሸ በኋላ የሚነድ የማታ ማገዶ።
የማሪያም መቀነት)፡ ቀስተ ደመና ።
የማሪያም ምሳ)፡ መዠመሪያው ያራስ ገንፎ።
የማሪያም ምሳ)፡ መዠመሪያው ያራስ ገንፎ።
የማር እሸት)፡ ቀጠላ ዐዲስ ማር ።
የማን፡ የፊደል ስም የ ("ቀኝ ማለት ነው") ።
የማይ፡ ዕቃ፡ እንዲሉ።
የም (ዘ)፡ ለቅርቦቹ ለ፫ቱ ሰራዊትና እኔ እኛ ለሚሉ በትንቢት መነሻ እየገባ ቅጽልና በቂ ' ይኾናል ።
የምሥራች፡ ሙሽራው ሙሽራዪቱን ባወቀ ጊዜና ልጅ ዳዊት በደገመ (በጨረሰ) ሰዓት የሚቀበለው ስጦታ ወይም ሽልማት። መሠተረ፡ አጥርቶ ነቀለ፡ መሰተረ።
የምሥራች፡ የደስታ ወሬ፡ ሥራች ።
የምሩ፡ ውሃ ሥንቁ፡ የደስታ ተክለ ወልድ አያት ያባት አባት።
የምሩ፡ የሰው ስም (አባትና እናት ወልደው ከሞተባቸው በኋላ የወለዱትን ልጅ "የምሩ" ይሉታል፡ "አምላክ ይኸን ልጅ የሰጠን የውነቱ ይኾን" ማለት ነው - ሲዘረዝርም የምሩ/የምርኸ/የምራቸው/የምራችኹ/የምሯ/የምርሽ/የምሬ/የምራችን ነው ይላል) ።
የምሩ፡ የውነቱ መረረ ።
የምር፡ የውነት —መረረ ።
የምር፡ የውነት/የርግጥ። "እከሌ ይህ ነገር የምርኸ ነውን?"
የምሽት ረዴ)፡ በሥራ/በነገር እንዲመሽ የሚያደርግ። "የምሽት አለ" (ፈጽሞ መሸ) ።
የምቡት የምቡት፡ የልጆች ፈሊጥ ።
የምቡት የምቡት፡ ይኸን ያልመታ ይሞት ።
የሞት፡ ሞት፡ ሞትን፡ የሚሽር፡ ሕይወት፡ ክርስቶስ ።
የሞት፡ ሞት፡ የሥጋ፡ ወደ፡ መቃብር፡ መውረድ፡ የነፍስ፡ እገሃነም፡ መግባት ።እስረኛው ከወህኒ፡ ቤት፡ የሞት፡ ሞቱን፡ አመለጠ፡ ቢል፡ ብሞትም፡ ልሙት፡ ብሎ፡ ማለት፡ ነው።
የሞት ጥላ)፡ ውድቅት ድቅድቅ ጨለማ ("በጨለማ ላይ የተጨመረ የዛፍ የገ ደል ጥላ ምሳሌ በኀጢአት ላይ የሃይማኖት ክሕደት") (ኢዮ. ፫፡ ፭፡ ኢሳ. ፱፡ ፪) ።
የሠለስት፡ የሦስትኛ ሰዓት ጸሎት አቍጣሮ ።
የሰላበትን ወጭት ሰባሪ)፡ ጥጋበኛ ሰው፡ ዕገውጡ።
የሠላጢን መሬት)፡ የወታደር ይዘታ። ጠፋንን "ለማን (ሸ)" ብለኸ ኣሸንን እይ።
የሰማይ ስባሪ)፡ ሰፊ ምድር።
የሰማይ ቍጣ)፡ መብረቅ ።
የሠሥቴ ከስቴ፡ የሠሠተ ከሳ (የሠሢታ ከሲታ - "ጕይዲ" ግን ዐጪርና ቀጪን ቅጠል አረንጓዴ መልክ ይለዋል) ።
የሰቀላ መሬት)፡ መትከያ/መንቀያ/መሾሚያ/መሻሪያ ምድር።
የሰዓት መርፌ)፡ ሰዓትን/ደቂቃን/ካልኢትን ቅጽበትን የሚቈጥሩ ፫ መርፎች።
የሰው ሰው)፡ የሌላ ሌላ፡ የባዕድ ባዕድ።
የሰው አገር ሰው)፡ የሩቅ/የውጭ አገር።
የሰው ዥብ)፡ ተፈጥሮው ሰው ሲኾን እንደ ዥብ ሰው የሚ በላ ።
የሰይጣን ቍራጭ)፡ ጭራሽ ክፉሰው ።
የሰይጣን ፈረስ)፡ ኹለት እግር ያላት መንኰራኵር ።
የሰዳጅ፡ የላከ፡ የተመረጠ (የሥጋ ብልት) ። "የሰዳጅ ለወዳጅ" እንዲሉ።
የሳታት ሰላምታ)፡ ስንኙ ሦስት እየኾነ የተደረሰ ግእዛዊ ግጥም ("ሰላም ለከ ኪ ክሙ" እያለ የሚነሣ) ። (የበገና ሰላምታ)፡ በበገና የሚዘመር ያማርኛ ግጥም።
የሴት ምራቋ ደንዳና ነው)፡ ስታበስል ከዚያም ከዚያም ትቀምሳለች። ቈበርን እይ።
የሴት ሴት (መልኳ እናቷን ብቻ የሚመስል ሴት) ።
የሴት ቍንጮ)፡ ልባም ባለያ ሴት ።
የስሚስሚ፡ የመስማት መስማት (የወሬ ወሬ) ።
የረር፡ ካዲስ አበባ በስተደቡብ ያለ ተራራ ("በሐረርጌም የሚገኝ ቀበሌ ኤረርን እይ") ።
የሩቅ ሴት)፡ እሷ ።
የርሱ፡ የሱ ("—የዚያ —ርስ እስ") ።
የርብርብ፡ የርዳ ተራዳ ጠብ ("የጕንዳን አያያዝ ") ።
የርቦራ፡ የዝኆን ጥርስ አንባር ("ጠላ ቱን ለገደለ የሚሰጥ") ።
የሮጠ/የሚሮጥ - የሮጠ/የሚሮጥ።
የሸማ ስም ("ዕ ጥፍ የላይ ልብስ መደረቢያ ፳፬ ክንድ ፬ ፈርጅ ሲበዛ ኩታዎች ይላል (ጐዳ ኩታ) አለጥለት የተሠራ ጥለት የሌለው ኩታ (ጥበብ ኩታ) በጫፍና በጫፉ ከ፰ ላይ ጥበብ የ ተሠራበት (የተጣለበት) ባለጥበብ ኩታ ጐዳን ጠበበን ተመልከት ቍጥኔን እይ ኩትኛ የኩታ ዐይነት እንደ ኩታ የተሰፋ ልብስ ዝቅዝቅ ያይዶለ ጋቢን አስተውል ኩታ ገጠም አንድ ላይ ጐን ለጐን ያለ መሬት ወይም ርስት እንደ ኩታ የገጠመ (ጥት) ኩት ") (ዕሽ) ።
የሸማኔ ' ዕቃ)፡ ሸማ ' መሥሪያ ዐርብ ።
የሸንበቆ ምርኵዝ)፡ መቃ የያዥውን እጅ ተሠንጥሮ እንዲወጋ፥ አምኖ የተጠጋውን የሚጐዳ እንጂ የማይጠቅም (ኢሳ. ፴፮፥፮) ።
የሺ፡ የሴት ስም ("የሺመቤት ከፊል ሺን ተመልከት") ።
የሻላ ሀብተ ማርያም፡ የጠራ ገሊላ ባላባት ።
የሻላ፡ የቀድሞ ማዕርግ ስም ("የሻለቃ ከፊል ባለግምጃ ሱሪ") ።
የሻላ ጥሬ ወርቅ፡ ዝኒ ከማሁ ("፩ኛው ፥ ልጅ ፪ኛው አባት ") ።
የቀረ፡ ያልመጣ ።
የቀትር)፡ በቀትር የሚጸለይ ጸሎት አቍጣሮ ። "የቀትር እባብ የቀትር ጋኔን" እንዲሉ ።
የቀጨማ፡ የጠፋ ከብት ይዞ ለተ ጐን ወይም ላሳደረ የከብት ጌታ የሚሰጠው ገንዘብ ("አንድ ብር") ። ዳግመኛም የዥብ አፍ ይባላል ።
የቍላ፡ ያልተወቀጠ/ያልተቀጠቀጠ በሬ ።
የቁም ፍታት)፡ ሳይሞቱ መፈታት (በሕይወት ሳሉ ተዝካር ማውጣት ") ።
የቍራ ምሳ)፡ ውስጡ ደም የሚመስል የወይናደጋ ዐረግ።
የቍራ ምሳ)፡ ውስጡ ደም የሚመስል የወይናደጋ ዐረግ (ፍሬ ወይም ርሱ ራሱ ዐረጉ) ። ሥርና ሥራ ማሰና ምሳ በአማርኛ ይተባበራሉ። (ግጥም)፡ "ብዙ ሥራ ዐዋቂ ትላንት ተቀበረች መድኀኒቱን ምሳ ትሰጠኝ ነበረች"። "ያኵራፊ ምሳ እራት ይኾናል" እንዲሉ።
የቍራ ወስፌ)፡ ታናሽ ቅጠል።
የቍር፡ በቡልጋ ውስጥ ያለ ቀበሌ ።
የቍንጢጥ፡ ትንንሾች ልጆች የመዳ ፋቸውን ዠርባ እየቈነጠጡ በማያያዝ፡ "የቍን ጢጥ የቍንጢጥ ሻ ብትን" እያሉ እጃቸውን በመለያየት የሚያደርጉት ጨዋታ ።
የቈጣሪ፡ ድርን ቈጥሮ ለቋጠረ የሚሰጥ አነባበሮ ። "ድረሽ የቈጣሪ ይዘሽ" እንዲል ሸማኔ ።
የቅ፡ የጭ ወዲያ ቀና ጨ ተወራራሾች ስለ ኾኑ የጭ በማለት ፈንታ የት ይላል ።
የቅርብ ሴት)፡ አንቺ ። "ጠነዛን" አስተውል ። ቅጽል ሲኾን "ሴት ልጅ" ይላል ።
የበረት፡ በበረት የሚደረግ መሥዋዕት፡ የኦሮ አምልኮ ። ቦረንትቻን እይ ።
የበገና መምቻ፡ ድሕንጻ - ዘፀ. ፲፯፥፳፪) ።
የቢስ የቸር፡ የክፉ የበጎ ። ዛሬ ሌሊት የቢስ የቸር ሲለኝ (ሲያሳየኝ) ዐደረ ።
የባ ሕር ዐረፋ)፡ ይደርቅና የዛገ ብረት መወ ልወያና መድመፅ የሚኾን ሻካራ ደንጊያ ።
የባሕር ቍልቋል)፡ ከበርበር የመጣ እሾኻም ተክል ፍሬው የሚበላ ።
የባጕስ፡ ዦሮ ቈራጭ፡ ባጐሰ ።
የብስ (የብሰ)፡ ደረቅ ምድር ("ባሕር የሌለባት") ።
የብረት፡ ልጥ)፡ ሥሥ፡ ብረት፡ የሳንቃና፡ የንጨት፡ ማእዘን፡ ማ ያያዣ፡ የጣቃ፡ መቀፈጃ።
የቦ (ኦሮ)፡ የጦር ስም ("ታናሽ ጦር ጭሬ") ።
የተለበጠ የተጌጠ የተሠነበጠ ("ልባጭ ሥንባጭ ልጣጭ ልብጣት ") ("ልብጠት") ።
የተላከ፡ ካቶ፡ እከሌ፡ እንዲሉ።
የተላከ፡ የደብዳቤ፡ አርእስት።
የተሻ ወርቅ፡ የሰው ስም ።
የተሻ፡ የተፈለገ ።
የተቃረ፡ የጐመዠ/የሠየ ።
የተትረፈረፈ፡ ተርፎ የፈሰሰ ። መጽሐፍ ግን "የተረፈረፈ" ይላል አያሠኝም (ሉቃ. ፮፡ ፴፰) ።
የተንቃቃ፡ የሞቀ የደረቀ ቅይጥ እን ጀራ፡ የተጕላላ ሰው ።
የተከበረ፡ የከበረ፡ ክቡር።
የተከበሩ፡ የከበሩ፡ ክቡራን ክቡራት። ተከባሪ፤("ከባሪ")፡ የሚከበር፡ ራሱን አኵሪ፡ እኔ እከሌ የእከሌ ልጅ ባይ፡ ተጓዳጅ። ተከባሪነት፡ ተከባሪ መኾን። መከበር ("መክበር")፤መኵራት መጓ ደድ ። መከበሪያ፡ ("መክበሪያ")፡ መጓደጃ። ተከባበረ፡ ክብር ተቀባበለ፡ አንተ ትብስ አንተ ትብስ ተባባለ።
የተከተለ ("የሚከተል ለጣቂ አሽከር ገረድ ልጅ ወራሽ ደቀ መዝሙር ጥጃ ግልገል ተተኪ ") (፩ጴጥ. ፫፡ ፲፫) ።
የተከተረ ("የታገደ የ ቆመ ብዙ ውሃ መከተር መከበብ መታገድ መብዛት መከተሪያ መታገጃ መብዣ አካተረ አደላደለ አካበበ አስተጋገደ አባዛ አካታሪ ያካተረ የሚያካትር ማካተር ማካበብ ማስተጋገድ ኩታራ የዶሮ ስም ዶሮ ") (ጕራጌ) ።
የተከታተለ ("የሚከታተል ተጠባባቂ መከታተል መጠባበቅ መከታተያ መጠባበቂያ ") ።
የተካነ፡ የጣመ/የጣፈጠ ("የመኳንንት ወጥ ") ።
የተካነ፡ ዲያቆን/ካህን (ቄስ) የኾነ ("የሠለጠነ ") ።
የተኳለ የተዳረ ("ተኵሎ የተዳረ ወግ ማረግ የደረሰው ልጅ ") ።
የተዋበ/የተዋበች፡ ያማረ/ያማረች (፩ ሳሙ. ፲፯፡ ፵፪) ።
የተገባ፡ የበጀ የተመቸ የቀና፡ ምቾት ቅን ነገር ።
የተጣራ፡ ሰውን የጠራ ።
የተጣራ፡ የማር/የወይን ጠጅ ።
የተጣራ፡ ጠጅ፡ ጠራ (ጸርየ) ።
የታቦት ዘፈን)፡ "ሰዉን ገረ ፈና በቂጥኝ ዐለንጋ ሚጣቅ እሾላው ሥር ጠበሉን አረጋ ። አወጣ ኣፈለቀ ኣመነጨ ቢል በቀና ነበር" ።
የታደለ (ች/ሉ)፡ ዕድላም ባለዕድል ።
የት (አይቴ)፡ ንኡስ አገባብ ("የጥያቄ ቃል የቦታ በቂ ከአንቀጽ በፊት እየገባ ይነገራል። የት አለኸ የት ባጀኸ የት ዋልኸ የት ከረምኸ የት ኼድኸ የት ዐደርኸ የት ሰነበትኸ መምህራንም በየት ፈንታ ሔት ይላሉ ደቂቅ አገባቦች እንደ ከ ወደ እስከ መነሻ ሲኾኑት እንዴት ከየት ወዴት እስከ የት ይላል በዝርዝርነት የስም ምትክ ሲኾን የቱ የትኛው ነው የትኞች ቹ የትኛዎች ቹ ናቸው የትኛዋ ይቱ ናት ይላል የየት ነኸ ቢል የየት አገር ሰው ያሠኛል ቅጽልነትንም ያሳያል (ተረት) አገርኸ የት ነው ማሪያም ውሃ እንግዲያውማ ዘመዴ ነኻ") ።
የት እየለሌ፡ እጅግ መራራቅን ያስረዳል ።
የት ውዬ የት ዐድር ብዬ፡ የወፍ ጩኸትና ስም ።
የነቢ፡ በበረት ፉካ ውስጥ የሚቀመጥ የቦረንትቻ መሥዋዕት (የበግና የፍየል ሥጋ ብልት ቅንጣቢ የጕሽ አተላ ቈሎ በያይነቱ ርሚጦ - ባላገሮች "ነቢ" የሚሉት በቃልቻ ያደረውን ዛር ነው - ተረፈ ዳን. ፲፫፥፪, ፲፯) ።
የነቢ፡ የነቢይ ፈንታ/ድርሻ (፩ነፃ. ፲፯፥፮) ።
የነካ ነካ፡ የዞግ ዞግ የሳቢያ ሳቢያ (አንዱን የነካ ነገር ሌላውን ነካ በጓዱ ሰበብ ባልንጀራው ተያዘ ማለት ነው - "ዳፈ ብለኸ ዳፋን ፪ኛውን ተረፈ" አስተውል) ።
የነጂ፡ ተጠብሶ እረኛ ከብት ጠባቂ የሚበላው (የፍየል/የበግ ወጠጤ ቍላ) ።
የነጂ፡ የረኛ አበል ("—ነዳ") ።
የኔ (የእኔ)፡ መዠመሪያውን የ ባ፭ኛ ተራ ተመልከት ።
የኔታ፡ የኔ (የእኔ) ጌታ ("ጌታዬ አስተማሪዬ መምሬ") ።
የንጉሥ ቍና)፡ ሌባሻይ ።
የንጨት ሽበት) "ሸብቶ ሳለ ግብሩ መጥፎ የኾነ ሰው ወረረ ብለኸ አወረረን" እይ ።
የዓሣ ስም ("ዓሣ ") (ዐረብ) ።
የዕቡይ ሞረድ)፡ ትቢተኛን ከልክ የሚያገባ ዕቡይ ገሪ።
የዕጣን ሙጫ ከቅርፊት ጋራ ዐብሮ የደረቀ መናኛ ዕጣን ("እንደ ጪስ ዕንጨት ሴቶች የሚሞቁት የሚታጠኑት ሊባኖስ በሶርያና በእስራኤል ምድር መካከል ያለ ደጋ ከፍተኛ ስፍራ ዛፋም ደናም ተራራ አርዝ የሚበቅልበት ሊባኖስ በሊባኖስ የተወለደ የሊባኖስ ሰው ጻድቅ መነኵሴ ከተስዐቱ ቅዱሳን በ በፊት ወዳገራችን በ፫ኛው ፫ ዓ ም መጥቶ ወንጌልን እየሰበከ ብዙ ጊዜ የኖረ ካባ ተክሌ አስቀድሞ ደብረ ሊባኖስን ያቀና ፪ኛ ስሙ መጣዕ ፫ኛ ስሙ ይስሪን ይባላል አባ ሊባኖስ እንዲሉ። ሊባኖስ የዛፍ ስም አስታ የሚመስል ዕንጨት ዐዲሳበቦች የሚተክሉት ለበቀ ጐሰመ ጐን እከሌ ሐሞት በዝቶበት ልቡን ሲለብቀው ዋለ ለበቀ በለበቅ መታ ለባቂ የለበቀ የሚለብቅ መጥፎ ጠጥ ኮሶ እንቆቆ ለበቅ ") ("ቆች") ።
የከሰ (ትግ. ወከሰ)፡ ጠየቀ ("ጥያቄ አቀረበ ነው") ።
የከሰል ምርት)፡ የከሰል ብዛት/ብዙነት። ሸለመን/ሰነፈንን እይ።
የከተመ ("የሚከትም ቈርቋሪ ከተማ ") (ሞች) ።
የከተረ ("የሚከት ደ ልዳይ ከባቢ አጋጅ አብዢ ከተሬ የሰው ስም ከተረ ማለት ነው ከተራ የመክበብ የማገድ የማብዛት ሥራ ከተራ በግእዝ ኣገዳት ኣበዛት ማለት ነው ከተራ የበዓል ስም የጥምቀት ዋዜ ጥር ፲ ቀን ወራጅ ውሃ የሚከተርበት ቦትና ሰው ወደ ዠማ ወርዶ የሚያድርበት ጊዜ ንጊያ መክተር መክበብ ማገድ ማብዛት መክተሪያ ማገጃ ማብዣ ዐፈርና - ") ።
የከተበ ("የሚከትብ ጻፊ ጣፊ በጪ ሠንጣቂ አጋቢ አስተላላፊ ከታቢ የከብት ሐኪም ከተባ የመክተብ ሥራ ክታብ ") (ቦች) ።
የከነፈ፡ ያበደ ።
የከንቱ ከንቱ፡ የብላሽ ብላሽ ("የመ ጥፎ መጥፎ ") ።
የኩል፡ (የእኩል)፡ የጋራ ። የኩል ዐራሽ ፥ የኩል ቤት እንዲሉ። (የአመንዝራ ግጥም)፡ ሚስትም ኣላገባ፡ ላሳብም ኣልቸኵል፡ አንዱ ያገባትን እይዛለኹ የኩል ።
የካ (ኦሮ፡ ኤካ፡ እውነት ነው)፡ ባዲስ አበባ ውስጥ በስተምሥራቅ በኩል ያለ ቀበሌ ።
የካህን ቂም)፡ "ጭጐጐት ፍቅሩ ጥኑ" ።
የካሽ (ሾች)፡ የየከሰ/የሚየክስ ("ጠያቂ") ።
የካቲት (ከተተ)፡ የወር ስም ("፯ኛ ወር ከመስከረም የመከር መክተቻ ማለት ነው ከተተን እይ") ።
የክዳን ዐይነት፡ ሰለታ ("ጠበራ ") ።
የክፉ ብድር ከፈለ ደባ ሠራ ወረረ ዘረፈ ። (ተመልከት፡ ደበደበን እይ) ።
የወለፌንድ፡ የጠማማ ዐመል ሥራ ("ከሰው የማይስማማ") ።
የወል፡ በወሎ ክፍል ያለ ተራራ ።
የወል፡ የሕዝብ/የማኅበር/ያንድነት/የጋራ ርስት/ገንዘብ ("ወይም ሌላ ነገር ዳኛ የወል ምሰሶ የመካከል” እንዲሉ) ።
የወል፡ የተራራ ስም፡ ወለለ ።
የወር፡ ቀለብ/ደመ/ወዝ ።
የወርቅ ቀበቶ)፡ ውስጡ ጠፍር ላዩ ወርቀ ዘቦ ያለበት ቀበቶ ። "ሠቅንን" ተመልከት ።
የወግ ዕቃ)፡ ፈረስ በቅሎ ከነሥራቱ (የጦር ልብስ የጦር መሣሪያ ሻለቃ በሞተ ጊዜ ወደ ቤተ መንግሥት የሚመለስ ") ።
የወፍ ቈሎ)፡ ወፍ የሚመገበው የምድር ፍሬ ።
የዋህ (የውሀ)፡ ገር/ቅን/ሞኝ ("እንስላ ደንሴ ሠረየን ርግብን ረባ ብለሽ ርባ ታን ተመልከት") ።
የዋህ ርባታ)፡ ከዐወቀ እስከ ዐወቅና መዠመሪያ በ፱ መደብ የሚረባ ።
የዋህ ኾነ (ተየውሀ)፡ ለዘበ ገራ ("ወደ ወሰዱት ኼደ") ።
የዋህነት፡ ገርነት/ሞኝነት ።
የዋሆች፡ ገሮች/ሞኞች ("እከይ አልቦች") ።
የዋሻ ቤት ተወቅሮ ተጠ ርቦ የተሠራ ።
የውሃ መንገድ፡ ዘወትር መመላለስ) ።
የውሃ ዕቃ)፡ ገንቦ ዳብሬ እን ስራ ቅል መንቀል ርኰት ቀርበታ ።
የውር መሪ)፡ ዕውርን የሚመራ።
የውሻ ቍስል)፡ ቶሎ የሚሽር ።
የውሽንብር፡ የኀዋት የቍትቻ ዕዳ መብልና መጠጥ ።
የውዝፍ፡ ስለ ውዝፍ የሚከፈል ዕዳና መቀጮ ።
የውጥር፡ እጅና አግሩ በገመድ ታስሮ የሚሳብ/የሚጨነቅ ።
የዘለበት ምላስ)፡ መካከለኛ፡ ብረት። ለመለመ፡ ብለኸ፡ ለምለምን፡ አስተውል።
የዘመቻ ፈሪ፡ ዘመቻ ፈርቶ የቀረ የሚከፍለው ገንዘብ ።
የዘወትር፡ የኹለዬ፡ የሠርክ፡ የዕለት፡ የ ጊዜ፡ የቀን፡ ሥራ፡ ምግብ፡ ልብስ፡ ጸሎት፡ ጀ ንበር፡ በሠረቀ፡ ቍጥር፡ የሚደረግ፡ ማንኛውም፡ ነገር፡ ኹሉ። ሠርክን፡ እይ ።
የዘወትር፡ የኹለዬ/የሠርክ/የዕለት/የ ጊዜ/የቀን ሥራ/ምግብ/ልብስ/ጸሎት/ጀ ንበር ("በሠረቀ ቍጥር የሚደረግ ማንኛውም ነገር ኹሉ") ።
የዘይት ቅመም)፡ ተልባ ኑግ ሰሊጥ ሱፍ፡ የዚህ ኹሉ ማጣፈጫ ጨው ነው ።
የዘገር፡ በዘገር የቀና/የተያዘ ("የንጉሥ የመንግሥት ርስት ጕልት የቤተ ክህነት ያይ ዶለ") ።
የዚያ፡ የነዚያ፡ የርሱ፡ የነርሱ፡ ጠቃ ሽና፡ በቂ ።
የዚያ/የነዚያ፡ የርሱ/የነርሱ ጠቃ ሽና በቂ ።
የዚያየሱ፡ ዚያ ።
የዝኆን ዦሮ ተሰጠው)፡ ሰምቶእንዳልሰማ ኾነ፡ ነገርን ኹሉ ናቀ፡ ቸል አለ።
የዝን (የዕዝን)፡ ላዘነተኛ የሚሰጥ ፱ እንጀራ (ንፍሮ - ሕዝ. ፳፬፥፲፯፡ ሆሴ. ፱፥፩ ") ።
የዝንጀሮ ቂጣ)፡ የቅጠል ስም (በገደል ቀጣና የሚበቅል ሰማያዊ ቅጠል ኹናቴው ከማነሱ በቀር ቂጣ የሚመስል ") ። ዳግመኛም እረኞች በአየር ላይ ስለሚያሽከረክሩት ሽክርክሪት ይባላል ።
የዣርት ወስፌ)፡ ወስፌ መሳይ የዣርት ጠጕር ።
የዥብ ምርኵዝ)፡ የታናሽ ዛፍ ስም (በወይናደጋ ቈላ የሚበቅል ተራ ዕንጨት) ።
የየ (ዘዘ)፡ የደጊመ ቃል በቂ ።
የየካሽ፡ የተየካሽ ("የጠያቂ የተጠያቂ ወይም ራሱን እሱ ጠይቆ እሱው መልስ የሚሰጥ ሌላ መልስ ሰጪ የሌለው መምህራን ግን የተየካሽ ተየካሽ ይሉታል") (ትርጓሜ ትምህርተ ኅቡኣት) ።
የዪ (ኦሮ)፡ የተኩላ ስም ("ተኵላ") ።
የያተኛ፡ የቀን ሠራተኛ ("ደመ ወዝ ቀለብ እኸልና ገንዘብ የጕልበት ዋጋ") ። (ተመልከት፡ ነዳ ብለኸ ምንዳን እይ) ።
የደስ ደስ፡ የጪስ ዕንጨት ።
የደስ ደስ፡ ገባር ለተሾመ የሚሰጠው ገንዘብ መተያያ ።
የደስታ መሬት)፡ የድንኳን ተካይ ምድር።
የደረት ሳንቃ)፡ ጌጠኛ የደረት ልብስ ሴደርያ (ዘፀ. ፳፭፡ ፯፡ ፳፰፡ ፬) ።
የድኻ ፍታት)፡ ዘራዳም ግባተ መ ሬት ። "ጓዘ"ንና "ዐረፈን" "መላን" ተመልከት ።
የዶሮ መከልከያና ሐይ ማያ ማብረሪያ ድምጥ ("ኩቶ በወላምኛ ዶሮ ማለት ነውና ኩት ከዚህ የወጣ ነው ኩት ") (ሑት) ።
የጁ (የእጁ)፡ ያገር ስም ("የቀድሞ ስሙ ገነቴ ነው አለቃ ታየ የጻፉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ ተመልከት") ።
የጁን ይስጠው)፡ ጡር ይድረስበት።
የገቦ (ዘገቦ)፡ የጐን ("በጐን የሚወጣ የሚያፈጠፍጥ የሚያቈጠቍጥ የማሽላ ቅጥይ የበቈሎ ፍሬ መጽሐፍ ግን ገቦ ይላል") (ዘሌ. ፳፭፡ ፭) ።
የገነት ገነታዊት፡ ወይም (ገነትየ) "የኔ ገነት ማለት ነው አገናነን አከባበር አበዛዝ አጀጓጐል መግነን።" (ተመልከት፡ ገነገነን "የዚህ ዘር ነው።")
የገዛ እጁን ሳመ)፡ ለዳኛ/ላገረ ገዢ ከበሬታ ሰጠ በፍርድ ጊዜ ።
የጉም ሽንት)፡ ረቂቅ ካፊያ (ከም የሚጎኝ) ።
የጕድፍ ቅል)፡ ሞኝ ሰው ዐሞተ ቢስ ደካማ ። "ባርን" ተመልከት ።
የጕድፍ፡ ፈንጣጣን የመሰለ ቀላል የልጆች በሽታ (በገላቸው ላይ ዐልፎ ዐልፎ የሚወጣ አካል አጕዳፊ በቶሎ የሚረግፍ ዕከክ)። (ተመልከት፡ ጋኔንን ቅልን) ።
የጋዣ ማር)፡ ንብ ጋዣውን ቀሥማ የጋገረችው ማር።
የግራ ካራ) ዐመለ መጥፎ ሰው ።
የግእዝ ቅኔ፡ መወድስ) ።
የጠረኘ፡ ያፈለ/የጐለመሰ ።
የጠጅ ቀንድ)፡ ጠጅ መያዣ ማኖሪያ ።
የጠገተ ሥር ርሱ ነው፡ ምስጢሩም የጥጃንና ያላቢን ወደ ላም ጡት መጠጋት ያ ስረዳል።
የጠፍ፡ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ("ለሹም ወይም ላምጪው የሚገባ") ።
የጣላ ጣላ፡ ካንዱ ወዳንዱ የተላለፈ ሰው ወሬ ።
የጣመ (ጥዑም)፡ የጣፈጠ ("ጣፋጭ ምግብ የላመ የጣመ እንዲሉ") ።
የጣማ ገንዘብ፡ ዐርሶ/ቈፍሮ/ወጥቶ/ወርዶ/ ነግዶ ያገኙት/ያተረፉት/የለፉበት/ላብ ያፈሰሱበት የድካም ዋጋ ደሙ ወዝ ።
የጣይ ሽንት)፡ በበጋ ሰዓት ቀን የሚወርድ የደጋ ርጥበት...ብል ።
የጥላ)፡ በቍስል አጠገብ የሚታሰር ዛጐል ሴቴ ሬት ።
የጦም ቈሎ)፡ በፍልሰታ ለካህናት የሚሰጥ ቈሎ፡ ገባር በሑዳዴ ለሹም የሚሰጠው ዱቄት ዕንጨት ጭምር (ስም) ።
የጦር ሹም)፡ ያ፲ ያ፶ የ፫ አለቃ (ሻምበል ባላምባራስ ግራዝማች ቀኛዝማች ፊታውራሪ ደጃዝማች ራስ - "ሻለቃን" እይ) ። ፈረንጆች ሹምን "ጉበርነር" ይሉታል ።
የጦጣ ቍላ)፡ ፍሬው የሚንጣጣ ዕንጨት ።
የጦፈ፡ ጧፍ የኾነ/የነደደ ("ያበደ ሙር") ።
የጨረቃ ቀንድ)፡ ለጋ የጨረቃ ቅርጽ ቀንድ መሳይ ።
የጭ (የዕጭ)፡ ኣክሽ የዲያ ወዲያ አስቀያሚ ጸያፍ ነገር ("በማር ውስጥ ያለ ዕጭ እንዲያሠቅቅ ይህም እንደዚያ ነው ") ።
የጭንጫ፵ አሽከር)፡ ለውጭ ሥራ የሚታዘዝ ያደባባይ አሽከር ።
የፀሓይ ቆብ)፡ ለጽ ድቅ ያይዶለ ለፀሓይ የሚደረግ ማታለያ ቆብ ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈረስ ስም)፡ አባ ዲና። (ያሚ ስም)፡ በድብቅ የሚነገር (ፈረንጆች "ሶብሪኬ" ይሉታል) ። (ተረት)፡ "ስም ይወጣል ከቤት ይከተላል ጎረቤት"። "ሰየመን" እይ። የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ስም ሲኾን መጨረሻው ሳድስ ፊደል በኃምስነት ይነገራል ። (ማስረጃ)፡ አግርዴ/ኣዝልቄ/ጐንጤ/ደርቤ/ዳኜ/ድያ/ለጥቄ/ፈንጥቄ/ተምትሜ ። በኀላፊ አንቀጽም "በለጤ ዘለሌ" ይላል።
የፈረንጅ አሽከር)፡ ነጭ ለባሽ ሳሕን አመላላሸ ።
የፈናጅራ፡ የመጥፎ ሰው ጠባይ (ከሌ ላው አንድነት ስምምነት የሌለው ") ።
የፈናፍንት፡ የጕዳጕድ ሥራ ።
የፊጥኝ፡ የኋሊት ("ፈጠነ") ።
የፍንጥር፡ ላሻሻጭ የተገዛ መጠጥ ። "ፍንጥር ያሠኘው ርሱን ለመግዛት ወጪ የኾነው ብር ነው" ።
የፍንጫሪ)፡ በደጀ ሰላም ለፍም ጫሪ የሚሰጥ እንጀራ የዳቦ ጕዝጓዝ የተላኪ ወግ አበል ።
የፍየልና የበግ አንዠት ዐለበ ("ዥማት አወጣ አከረረ") ።
ዩ፡ የዜማ ምልክት ።
ዩ፡ ዬ
ዪ፡ (ኢ) የሣልስ ፊደል መሠረት ።
ዪቱ (ዪት/ዊት)፡ የእንስት የሴት መለዮ ።
ያ (መዋያ)፡ ጥበብ/ዕውቀት/ዘዴ/ ብልኀት ።
ያ፡ (አ) ለሩቅ ሴትለሩቆች ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽና የዝርዝር አያያዥ ("ፍቺው ርሱ ይኸውም ዐወቀ ያት ያቸው ያችኹ በማለት ፈንታ ራሱን ጐርዶ ዐወቃት ዐወቃቸው ዐወቃችኹ እያለ በርባታ ጊዜ የአንቀጹን መድረሻ ራብዕ ማድረጉን ያሳያል።ያ ስምን አ አካልን ይተረጕማል ስም ንም ከዝርዝር ሲያያይዝ እጃችን እግራችን ቀበሌ ቀበሌያችን ዕድሜ ዕድሜያችን ይላል አንድ ዐይነት ቅጽልንና ስምን ሲያናብብ ገራገር ወንዛወንዝ ያሠኛል") ።
ያ፡ (ዊ) ወገን ቅጽል ።
ያ፡ (ውእቱ) የሩቅ ወንድ በቂና ዐጸፋ ።
ያ፡ (ውእቱ) የሩቅ ወንድ ደቂቅ ቅጽል ይኾናል ("ትርጓሜው እሱ ርሱ ያ ሰው ያ ሲበዛ እኒያ እሊያ ይላል በስፍራው ተመልከት ያችን እይ") ።
ያ፡ (የማ) የትንቢት አሉታ በቂና ቅጽል መነሻ ።
ያ ሌላ፡ ይኸ ሌላ ("ያ ቍቅታ ይኸ ሢጥጥታ ምን ገጥሞት") ።
ያ፡ መዋያ/መገኛ ።
ያ፡ ምእላድ እየኾነ በቃል መጨረሻ ይገባል ።
ያ ቢስ፡ ዕውቀተ ቢስ/ሥራ የለሽ ("አውታታ ከርታታ") ።
ያ ተማደሪያ፡ ሌት ተቀን የሚሠራ ሥራ ።
ያ፡ የቀን ሥራ ("ቁም ነገር") (ኢሳ. ፲፱፡ ፲) ።
ያ፡ የግስ ጣልቃ ።
ያለ (አለ/እንበለ)፡ አለ በገባበት እየገባ ሲነገር ("ያላገባብ ያለደንብ ያለውድ በግድ ያለልክ ያለመጠን ያላቅም ያለፈቃድ ማለቱን ያሳያል ከዚህ የቀረውን በአለ ተራ ተመልከት ዚህና ዚያ ዘርፍ ሲኾኑት ያለ ዚህ ያለዚያ ይላል ፍችውም በአለ ተጽሯል") ።
ያለ፡ (የአለ)፡ ዘሀለወ)፡ ቅጽልና፡ በቂ። ያን፡ ጊዜ፡ በቤት፡ ያለ፡ እደጅ፡ አይውጣ ። (ግጥም)፡ ፈረስ፡ በቅሎ፡ ጭኖ፡ ከሚከተለው፡ እቤቱ፡ ያለውን፡ ይወደዋል፡ ሰው፡ በቂ። እንዲህ፡ ያለ፡ ዘመን፡ ዘመነ፣ ግልምቢጥ፡ ውሻ፡ ወደ፡ ሰርዶ፡ አህያ፡ ወደ፡ ሊጥ፡ ቅጽል።
ያለ፡ (የአለ)፡ ዘብህለ)፡ በቂና፡ ቅጽል። እካስ፡ ያለ፡ ታግሦ፡ እጸድቅ፡ ያለ፡ መንኵሶ፡ በቂ ።እገድል፡ ያለ፡ መጋኛ፡ እበላ፡ ያለ፡ ዳኛ፡ ቅጽል ።
ያለ፡ የሌለ፡ (ዘሀለወ፡ ዘኢሀለወ)፡ የታወቀና፡ ያልታወቀ፡ ጥሩና፡ መናኛ። ዛሬ፡ ፻፩ ሌሊት፡ ሌባ፡ እከሌ፡ ቤት፡ ገብቶ ' ያለ፡ የሌለውን፡ ሰረቀው " ሌለን፡ እይ ።ዳግመኛም፡ ያለ፡ ለጊዜው፡ የነበረ፡ የሌለ፡ ፊት፡ ያልኖረ፡ ማለት፡ ነው፡ (ራእ፲፯፡ ፰፡ ፲፩) ።
ያለ የሌለ፡ የነበረ ያልነበረ ("አለ (ሀለወ)") ።
ያለ፡ የተናገረ፡ አለ ("ብህለ") ።
ያለ፡ የነበረ አለ ("ሀለወ") ።
ያለበሰ ("የሚያለብስ ከዳኝ ሸፋኝ ሸላሚ ዐፈርን እይ አልባሽነት ኣልባሽ መኾን አልብሽኝ ደርቢልኝ ሸፍኚኝ አልብሽኝ አንተርሽኝ የጣጣ ብዛት ሰበብ አስባብ የዛሬ ቀን ባልብሽኝ ባንተርሽኝ መሸ ማልበስ መክደን መሸፈን መከለ ማልበሻ መክደኛ መሸፈኛ የድንኳን መደረቢያ ") ("ዘፀ. ፳፮፡ ፲፬") ።
ያለኸ፡ (የአለኸ)፡ ዘሀለወከ)፡ ገንዘብ፡ የያዝኸ፡ የቋጠርኸ ። (ተረት)፡ ያለኸ፡ ምዘዝ፡ የሌለኸ፡ ፍዘዝ ።
ያለኸ፡ የጩኸትና፡ የምጥንታ፡ ቃል። የሰው፡ ያለኸ፡ የንጉሥ፡ ያለኸ፡ እንዲሉ። የሰው፡ ረዳትነት፡ የንጉሥ፡ ዳኝነት፡ ያለኸ፡ ድረስልኝ፡ ማለት፡ ነው፡
ያለኽ፡ የያዝኽ አለ ("ሀለወ") ።
ያለው፡ የሰው፡ ስም፡ ያዘዘው፡ የተናገረው፡ የፈቀደው፡ የወደደው ።ያለው፡ ሊኾን፡ ያለው፡ ሊኾን፡ ዐሳብ፡ አደቀቀው፡ ጐኔን፡ (ታ ቦት፡ ዘፋኝ)።
ያላለ፡ (የአልአለ)፡ ያልተናገረ። ቅጽልና፡ በቂ፡ ነው።
ያላለያልተናገረ፡ አ ።
ያላበ ("የሚያልብ የሚያወዛ ማላብ ማሞቅ ማውዛት ተላላበ ተቀ መላላብ መቅ አላላበ አጝቀ ማላላብ ማቅ አላላብ አወዛዝ መላብ ላባ የወፍ ያሞራ ጠጕር ልብሳቸው ሲበዛ ላባዎች ያሠኛል በጋልኛ ባሊ' ይባላል ላባም ላባ ያለው ባለላባ ሳባ ላባ በካብ በግንብ ዐጥር ዐሰላ ላይየተተከለ ብረት ሹለትና ስለት ያለው ጠላ ") ።
ያላበቀ ("የሚያላብቅ የሚያጣላ አሳባቂ ማላበቅ ማሳበቅ ማጣላት ማማታት ማጋጨት ማላበቂያ ሐሰተኛ ነገር ሰብቅ ለብቃ በመርሐ ቤቴ ክፍል የሚገኝ አገር ፍል ውሃ ያለበት ወባም ሙቀታም። ለብቃ ኢየሱስ በለብቃ ያለ የኢየሱስ ታቦት አለባበቅ አጐሳሰም መለበቅ ለበሰ ") ("ለብሰ") ።
ያል፡ (የአል)፡ በቂና፡ ቅጽል። ያልተነካ፥ ግልግል፡ ያውቃል፡ በቂ፡ ያልጎደለ፡ ዘማች፡ ያልወለደ፡ ዐማች፡ ቅጽል ።ሰማን፡ ተመልከት ።
ያል፡ በቂና ቅጽል፡ አል ።
ያልተገለጸ)፡ የካባ ቆብ አንካቦ መሳይ - የካባ ቆብ መሰል።
ያልጋ ቍራኛ)፡ የማይለቅ በሽታ ።
ያመራማሪ፡ ላመራመረ የሚሰጥ ገንዘብ።
ያመንኳሽ፡ ካህናት የሚበሉት የቆብ ኣርባ ተዝካር ድግስ።
ያማርኛ ቅኔ፡ መወድስ) ።
ያማታል፡ ምግብ አይስማማትም (ያስ ታውካታል ቅሪት ስለ ኾነች ") ።
ያማች ዳሩ፡ መጨረሻ ("ክፉ ዐማች ") ።
ያም (ውእቱኒ)፡ ም ዋዌ ነው ።
ያም ያም፡ አንዱም አንዱም ።
ያሰነካከለ/የሚያሰነካክል፡
ያሳድግኸ፡ ሽማግሌ ለልጅ የሚሰጠው ምርቃት ።
ያስለፍልፍ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ዕፀ፡ ፋርስ።
ያስታራቂ፡ ግብዣ መብል መጠጥ ።
ያስከተለ ("የሚያስከትል አስለጣቂ ጌታ እመቤት አባት እ ናት መምር ማስከተል ማስለጠቅ ማስከተያ ማስለጠቂያ ተከተለ ") (ከተለ) ።
ያስከተበ ("የሚያስ ከትብ የልጅ አባት ዘመድ ማስከተብ ማጻፍ ማስበጣት ማን ተር ማሠንጠቅ ፮፻፺ ኮቲባ ኰተኰተ ማስከተቢያ ማስበጫ ማሠንጠቂያ ተከተበ ") (ተከትበ/ተከስበ) ።
ያሬድ፡ ከዕለት እስካመት በግእዝ ቋንቋ ድጓ የደረሰ የኢትዮጵያ ሊቅ ቅዱስ ካህን ።
ያሬድ፡ የሰው ስም ("ትርጓሜው መውረድ ማለት ነው") ።
ያሻል፡ ያስፈልጋል ።
ያቍራቢ - ላቍራቢ (ለቀዳሾች)፡ የሚ ሰጥ ምሳ ወይም ገንዘብ ።
ያቃባሪ፡ የዝን ንፍሮ ።
ያቃይ፡ የቃጭል መቺ የሰሞነኛ ምድር ።
ያበባ መስቀል)፡ ካበባ የተበጀ የተጐነጐነ እንቍጣጣሽ።
ያባትና የናት ሴቶች ልጆች፡ ወይም ካባት ባንድ ወገን ብቻ የተወለዱ ። (፩ጢሞ ፭ ፥ ፪) ። እት አበባ፡ ያጎት ያክሥት የቤተ ዘመድ ሴት ልጅ መጥሪያ ።
ያቤሎ፡ በሲዳሞ ክፍል ያለ አገር ።
ያቦ ፈረስ)፡ ቀጣኒት ።
ያተኛ (ኞች)፡ ለሰው ሲያርስ፥ሲቈ ፍር፥ሲያርም፥ሲያጭድ፥ሲሸከም፥ሲሠራ የሚ ውል (ማር. ፩፡ ፳) ።
ያቻት፡ ያች ናት አለች ።
ያቻትና፡ ያች እሷ ("ት ናት ና (ናሁ) እንሆ በተገናኝ እንሆ እሷ ናት በሩቅ አለች ያሠኛል") ።
ያች (ይእቲ)፡ የሩቅ ሴት ዐጸፋና " ቅጽል ወይም በቂ ("እሷ ማለት ነው ዋን እይ ያች ትምጣ ያች ትቅር ዐጸፋ ያች ሴት ያች ልጅ ቅጽል ው ሲጨመርበት መኖርን ያሳያል") ።
ያን (ያ/ውእተ)፡ ለሩቅ የነገር ስም የሚነገር ("ገቢር ቅጽልና ዐጸፋ ወይም በቂ ያን ጊዜ ያን ለት ያን ነገር ቅጽል ያን ጥለኸ ያን ያኸላል ያን ውደድያን ጥላ በቂ") ።
ያንቀላፋ ድንጋይ)፡ አረኸ ላይ በቋፍ ያለ የተቀመጠ ድንጋይ፡ ሰው አውሬ ከብት አጠገቡ በደረሰ ጊዜ ወይም እንዲያው አለምክንያት ተፈንቅሎ የሚንከባለል ።
ያንበሳ፡ መደብ)፡ አንበሳ፡ ተዘግቶ፡ የሚኖርበት፡ ስፍራ፡ በብረት፡ የታጠረና የተዘጋ።
ያንበሳ፡ መደብ)፡ የንጉሥ፡ ዐዘቅተ፡ ኵስሕ፡ ጓሮ፡ ቤት።
ያንተ ።
ያንካሴ የወላሴ፡ የልጆች ጨዋታ (ልጆች ፥ አንዳንድ እግራቸውን ዐጥፈው ፥ ያን ካሴ የወላሴ እያሉ ባንድ እግራቸው ያኰ በኵባሉ ") ።
ያንካሴ፡ ያንካሳ ወገን (ወይም ዐይ ነት - የወላሴ የእግረ ምልስ ማለትን ያሳ ያል - "ወለሰን" ተመልከት ") ።
ያኛው፡ ኛው ዝርዝር ምእላድ ነው ("፪ኛውን ኛ እይ") ።
ያክፋይ፡ ላክፋይ የሚሰጥ አንጀራና ወጥ/ዳቦና ጠላ/ሙክት ፍሪዳ ።
ያኸል፡ (ዘየአክል)፡ የሚያኸል፡ ቅጽልና ትንቢት ። ከጥያቄ ጋራ ሲነገር ምን ያኸል ፥ ምን ያኽላል ያሠኛል ።
ያኸል፡ ይሎ
ያኽል፡ የሚያኸል፡ አከለ ።
ያዋዋይ፡ ለዳኛ ስለ ማዋዋል የሚከ ፈል ገንዘብ ("የፍንጥር") ።
ያዋይ በላ፡ ላዋይ የተቀመጠውን የሚ በላ ("ችጋራም ራብ የማይችል ስግብግብ ቅ ልብልብ") ።
ያዋይ፡ በሌማት ውስጥ የሚውል ቍ ራሽ እንጀራ ።
ያው (ያ)፡ እሱ ነው አለ ።
ያውልኸ፡ ዕንካ ውሰደው ።
ያውሬ የጐሽ ውጊያ፡ በስተግራ ወግቶ ወደ ሰማይ ማሽቀንርጠ፡ ወይም ግራ ቀኝ መውጋት መለተም ።
ያውና፡ ያ እሱ ("ው ነው ና እንሆ በተገናኝ እንሆ እሱ ነው (በሩቅ) አለ ና ከናሁ መጥቷል (የባለጌ ግጥም) ያውና እዚያ ማዶ ዛፍ ይወዛወዛል ያንቺ ልብ እንዴት ነው የኔስ ይናውዛል ያውና እዚያ ማዶ ፍሪዳ ተጥሏል ቢላዋው ደንዞ ልብ አልቈርጥ ብሏል ፍሪዳ የተባለው ጌታችን ኢየ ሱስ ክርስቶስ ነው") ።
ያዘ (አኀዘ)፡ አፈፍ ለቀም አደረገ ("ከእጅ አገባ ጨበጠ ተሸከመ ቻለ አገመረ ወሰነ (አፍንጫውን ያዘ) ዐፈነ ደፈነ (በወጥመድ ያዘ) ዐነቀ (በልብስ ያዘ) ታቀፈ (ባፍ ያዘ) ጐረሠ (ልጓም ያዘ) ገታ (መግል ያዘ) ዐቈረ ቋጠረ (ሥጋ ያዘ) ወፈረ (ሥራ ያዘ) ረባ ጠቀመ አገለገለ (ሥር ያዘ) እሥር ገባ ተመለሰ (ዐይን ያዘ) ጨለመ ማየት ከለከለ (ቀለም ያዘ) አጠና ዐወቀ ልብ አደረገ (ቂም ያዘ) በልቡ አሳደረ (ስፍራ ያዘ) ቆመ ተደገፈ ያዘ በነገር ኹሉ እየገባ እንዳመጣጡ መፈታቱን አስተውል (ተረት) ከበሮ በሰው እጅ ያምር ሲይዙት ያደናግር አፍን እይ") ።
ያዝ (አኀዝ)፡ አንሣ ' ጨብጥ ' አን ግብ (መዝ. ፴፭፡ ፪) ።
ያዝ (እኂዝ)፡ መያዝ ።
ያዝ ለቀቅ፡ መያዝ መልቀቅ ።
ያዝ፡ ቶሎ በል ("ንከስ ባላገር ፡ ግ ፡ ጃስ ኵቲ ይላል") ።
ያዝ አደረገ፡ በፍጥነት ያዘ ።
ያዢ/ዥ (ዦች)፡ የያዘ/የሚይዝ ("ተሸካሚ ጨባጭ ገቺ ጐበዝ ያዢ ሲይዘው ብረት ያራል ጠመንዣ ያዥ ሰናድር ያዥ እንዲሉ") ።
ያየር፡ በአየር የሚኖር ጋኔን ፥ ሰይጣን ።
ያየኸ ይራድ፡ የሰው ስም፡ ራደን ተመልከት ።
ያይን ምሳ)፡ አበባ ሥዕል (የሚያምር ፍጥረትና ሥራ ኹሉ) ።
ያይን ምሳ)፡ አበባ ሥዕል (የሚያምር ፍጥረትና ሥራ ኹሉ) ።
ያይን ቆብ)፡ ቅንድብ ሸፋሽፍት ።
ያደግድጉ፡ የወንድና የሴት ስም ።
ያግሉ፡ የሰው ስም "ጠላቶች ይወግዱ ራሳቸውን ያርቁ ማለት ነው።"
ያጣኝ፡ ተዝካር በተበላ በ፫ኛ ቀን የ ሚደረግ የካህናት ግብዣ ።
ያፈላላጊ፡ ጥቅም ረብ ።
ያፋቺ/የተማቺ፡ ሚስቱን የፈታ ባል፡ ባሏን የፈታች ሚስት ("ኺጂ ልኺድ ያለ ያለች ") ።
ያፍ ሳቻ)፡ ነቀፋ ስድብ ።
ያፍጣጭ፡ ሰዎች ሲበሉ ላፈጠጠ የሚ ሰጥ ምግብ ።
ዬ፡ (ኢ) የማድነቅ ቃል።
ዬ፡ (ኤ) የኃምስ ፊደል ኹሉ መሠ ረት ።
ዬ፡ (ወዮ) የሐዘንና የጸጸት ቃል።
ዬ፡ (ዊ) ባገር ስም መጨረሻ እየገባ ለተወላጅ በቂ ይኾናል ።
ዬ፡ (የ) በራብዕና በኃምስ በሳብዕ ፊደል በሚጨርስ ስም እኔ ለሚል ዝርዝር ።
ዬ፡ ዕሠይ ወሰው እኮ ።
ዬ፡ ወገን ቅጽል ።
ዬ፡ ጊዜ " አንደዬ ዐሥረዬ ።
ዬዬ፡ ወዮ ወዮ ።
ይ፡ (ዊ) ወገን ቅጽል ።
ይ፡ ለሩቅ ወንድ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የትንቢት የዘንድ የትእዛዝ አንቀጽ መነሻ ።
ይ፡ በለ የሚጨርስ ግስ የሣልስ ቅጽል መድረሻ ።
ይ፡ በትንቢት መነሻ እየገባበቂ ይኾናል።
ይሁዲ (ዐረ)፡ ይሁዳዊ ("የይሁዳ ወግን ወይም ነገድ ነገደ እስራኤል ፈላሻ ግዙር") ።
ይሁዲነት (ይሁድና)፡ ይሁዲ መኾን ("ፈላሻነት") (ግብ. ሐዋ. ፮፡ ፭) ።
ይሁዲዎች፡ አይሁድ ፥ አይሁዶች " አይሁድ ("የይሁዳ ነገዶች እስራኤሎች ፲ሩ ነገድ በያዕቆብ እስራኤል እንደ ተባሉ በይሁዳም አይሁድ ተብለዋል") (አስቴ. ፫፡ ፮፡ ዮሐ. ፩፡ ፲፱) ።
ይሁዳ (የሀደ)፡ የሰው ስም ("ካቱ ነገደ እስራኤል አንዱ ትርጓሜው ኦኒ (አማኝ) ማለት ነው ሌሎችም በዚህ ስም የሚጠሩ ሰዎች አሉ ይሁዳ የጌታችን ወንድም ይሁዳ አስቆሮታዊ እንዲሉ") ።
ይህ (ዝ)፡ የቅርብ ዐጸፋና ጭብጥ ቅጽል ።
ይሕ፡ ይበሉ ሕዝብ (ቅዳሴ) ።
ይህታ (ይህችታ)፡ ታን ተመልከት ።
ይህች (ይህ)፡ ለቅርብ ሴት ዐጸፋና ቅጽል ።
ይህነን፡ ዝኒ ከማሁ ("ይኸንን ተመል ክት") ።
ይህን፡ የገቢር ቅጽል ።
ይለፍ፡ ኬላውን ይውጣ (አይከልከል ") ።
ይሉኝ፡ (ይብሉኒ)፡ ያኹን፡ ትንቢት፡ አንቀጽ። ደግ፡ ብሠራ ' የጠሉኝ፡ ክፉ፡ ባደርግ፡ ምን፡ ይሉኝ።ገቢኸን፡ ስታውቅ፡ ይሉኝ፡ አትበል ።ይሉኝ፡ አይል፡ ሐሜት፡ የማይፈራ፡ ከይሉኝ፡ ኣይል፡ ዐይብ፡ ኣትብላ፡ ኣይመረው፡ አይተኵሰው፡ ውጦ፡ ውጦ፡ ይጨርሰው። እንዲሉኝ፡ ሊሉኝ፡ ይሉኝ፡ ዘንድ፡ እያለ፡ በሣልሳይ፡ ኣንቀጽ፡ ይገባል ።
ይሉኝ፡ በቁሙ፡ አለ ("ብህለ") ።
ይሉኝተኛ፡ ባለይሉኝታ።
ይሉኝታ፡ ረቂቅ፡ የነገር፡ ስም፡ (ምሳ ፫፡ ፬)፡ እንዲህ፡ ይሉኛል፡ ማለት። ትዝብትን፡ ሐሜትን፡ ነቀፌታን፡ መፍራት። ይሉኝታ፡ የራስ፡ ዐሊን፡ ቤት፡ የፈታ። ይሉኝታና፡ መጠቀም፡ ባንድነት፡ አይገኝም። ይሉኝ፡ የነገር፡ ስም፡ መኾኑ፡ ታ፡ በምእላድነት፡ ስለ፡ ተጨመረበት፡ ነው።
ይሉኝታ፡ በቁሙ አለ ("ብ ህለ)") ።
ይሉኝታ፡ ቢስ፡ ግድ፡ የለሽ፡ ይሉኝ፡ ኣይል " አለና፡ ባለ፡ አንድ፡ አንቀጽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ አስደራጊውንና፡ ተደራጊውን፡ ተደራራጊውን፡ አደራራጊውን፡ በባለ፡ ተራ፡ ተመልከት ።ትእዛዙንም፡ ከበለ፡ ይወስዳል።
ይላሉ ። በግእዝ፡ ኰራኪ፡ ይባላል፡ ዳግመኛም፡ ስለ፡ እግሩ፡ ረዥምነት፡ ሽመላ፡ ይሉታል። እሱም፡ ካ፲፭፻፡ ዓ፡ ም፡ በፊት፡ አሜሪካን፡ ያውቃል ።ሽመላን፡ እይ ።
ይላማ (ዐላማ)፡ ምልክት ("ወርውረው የሚወጉት ተኵሰው የሚመቱት ነገር ጊጤን እይ") ።
ይል፡ ይናገር፡ የጊዜ፡ ትንቢት፡ ነው፡ ይላል (ይል፡ አል)፡ (ይብል፡ ሀለወ)፡ ይናገራል፡ ይመታል ።
ይልማ፡ በምንዝ ውስጥ ያለ ቀበሌ ("የጠይቦች ጎዳም የሚገኝበት ህለ)") ።
ይልማ፡ የሰው፡ ስም፡ ይርባ፡ ይብዛ፡ ማለት፡ ነው ።
ይልማና፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር ።
ይልቅ፡ ይበልጥ ላቀ ።
ይልቅ፡ ይበልጥ፡ እጅግ፡ ("ማሕ. ፩፡ ፬")፡ ይልቅስ፡ ስ፡ አፍራሽ፡ ነው፡ የሚበልጥስ፡ የሚሻልስ ።
ይሎ፡ የጣራ ማዋቀሪያ ረዥም አጣና ("ተለብልቦ የተላጠ ተራዳ ") ።
ይመናሹ፡ የሴት ስም፡ ወንዶች ባንቺ ላይ ይዋጉ ማለት ነው።
ይመናሹ፡ ይዋጉ፡ መንሽ ።
ይመኙሻል፡ የሴት ስም።
ይማማ (ዐረ፡ ዒማማ)፡ የይማሞቶ ጥምጥም ።
ይማም (አመመ/ቀደመ/ሀረ ዐመመ/ጠመጠመ)፡ የስላም ስም ("ግንባር ' ቀደም ካህን ማለት ነው ባላባትነት ንም ያሳያል") ።
ይማሞች፡ ግንባር ቀደሞች ዋኖች ("የወሎ ባላባቶች") ።
ይማና፡ ያደራ ገንዘብ፡ አመነ ።
ይሰበር ደጋኔ)፡ ከባሕር የመጣ ቀጪን ድር።
ይሣቅ (ይሥሐቅ)፡ (ዘፍ. ፳፩፥፫, ፮) የሰው ስም (ያብርሃም ልጅ የያዕቆብ አባት እናቱ ሳራ ካረጀች በኋላ ስለ ወለደችው ሰው ኹሉ ይገረም ይሣቅ በማለቷ በዚህ ስም ተሰየመ ይባላል) ።
ይስሙላ፡ ተሰምቶ የማይፈጸም ነገር (ፍችውም ይስሙላት ማለት ነው) ።
ይስማ ሰራዪት፡ በሠራ አካላት ላይ ግልብጥ ብሎ የሚታይ ቂጥኝ።
ይስገዱ፡ የወንድና የሴት ስም።
ይራድ (ይርዐድ)፡ ይፍራ, ይንቀጥቀጥ. "ወንድ ይራድ, ያየኽ ይራድ እንዲሉ" - "ወንድ ይራድ, ያየኽ ይራድ እንዲሉ".
ይርገዱ፡ የወንድና የሴት ስም ("ሰዎች ይራዱ ይፍሩ ማለት ነው ዳግመኛም ይርገዱልኸ ይርገዱልሽ ይባላሉ")
ይርጋ፡ ልስን ማስተካከያ ዕንጨት የተላገ ።
ይርጋ፡ የሰው ስም ።
ይርጋ፡ የንጉሥ ዐዋጅ ። "መሬት በያዘው ሰው እጅ ይኑር አይወሰድ ማለት ነው" ።
ይቅር ባይ፡ ማሪ ሰላማዊ ። ይቅር ተባለ፡ ታረቀ ሰውየው፡ ተተወ ጥሉ ።
ይቅር ተባባለ፡ ተጐናበሰ ተራረቀ ተሳሳመ ተሰማማ ።
ይቅር፡ ትእዛዝ አንቀጽ ። "ይቅር ለግዜር፡ ይቅር ላንተ፡ ቂሙ አይያዝ አይታሰብ ማለት ነው" ።"በአንተ ፍቅር በስመ አብ ይቅር እንዳለ ሰይጣን" ።
ይቅር አለ፡ ጠላቱን ማረ፡ ቍርሾውን ተወ ከልቡ ፋቀ አጠፋ ።
ይቅር አሠኘ፡ አስታረቀ ።
ይቅር፡ ይተው፡ ቀረ ።
ይቅርታ፡ ይቅር ማለት፡ ምሕረት ዕርቅ ("(መዝ. ፻፴፥ ፬)") ።"ከማስቀመጥ ስጦታ፡ ከቂም ይቅርታ" እንዲሉ ።
ይቅርታ ጠየቀ፡ "በድያለኹ ልካስ፡ ቀምቻለኹ ልመልስ አለ" ።
ይቆን፡ የጋኔን ስም ("ደቂቀ ሴትን ያሳተ ሰይጣን") (ሔኖ. ፲፱፡ ፲፯) ።
ይበል፡ ይናገር፡ ባለ ።
ይበጃል፡ ይሻላል፡ ይኾናል። ይበጃል ያሉት አይበጅም ።
ይበጅ፡ ያድርግ፡ ይበጅ ያድርግ፡ ያደርግ ዘንድ ይገባ ።
ይባዝ፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ ።
ይብላኝ (ይብልዐኒ)፡ የሐዘንና የትካዜ የጸጸት ቃል፡ ንኡስ አገባብ ። ይብላኝ ለሞተ እንዲሉ ።
ይብላኝ፡ በቁሙ፡ በላ ።
ይብላኝለት፡ በማቹ ፈንታ እኔን መሬት ይብላኝ ማለት ነው ።
ይብስ፡ ቅጥራን ("የቅጥራን ዐይነት") ።
ይብረኹ፡ የወንድና የሴት ስም፡ ይስገዱ ማለት ነው ። አቶ ይብረኹ እመት ይብረኹ እንዲሉ ።
ይብራ
ይብራ፡ የውሃ ዶሮ ("እውሃ ውስጥ ጠልቃ የምትወጣ እግረ ቀይ መልከ ብዙ") (ዘሌ. ፲፩፡ ፲፰) ።
ይብጀው፡ ይሻለው ። እሳት ለፈጀው ምን ይብጀው ።
ይብጅኽ፡ አይዞኸ አትፍራ ።
ይተጌ (እኅተ ሐፄጌ)፡ እተጌ ("ንጉሥ እቴ የምትላት ሚስቱ ጣምራው የንጉሥ ባልተ ቤት ይተጌ ጣይቱ ይተጌ መነን ይተጌ ሰብለ ወንጌል እንዲሉ ሲበዛ ይተጌዎች ይላል") ።
ይታክቱ፡ የወንድና የሴት ስም ። ታካች (ቾች)፡ የታከተ/የሚታክት ሰነፍ (ምሳ. ፮፡ ፮, ፴) ።
ይታገሡ፡ የወንድና የሴት ስም።
ይቶት (እኅት)፡ ሴት ስትመነኵስ የምትጠራበት ስም ("የፍቅር የሃይማኖት የማ ይቶት ኅበር እት ማለት ነው ዳግመኛም እመ እማሆይ ትባላለች በግእዝ ቋንቋም መነኵ") ።
ይች/ቺ፡ ይህችን ተመልከት ።
ይችው፡ በቅርቡ አለች ።
ይችውና፡ እንሆ እዚሁ አለች ።
ይኑር፡ ይቀመጥ/ይቈይ/ይዘግይ (ዕድሜው ይብዛ - "ይኑር ዘለዓለም እከሌ ኣብርሃም" እንዲሉ ካህናት) ።
ይናዱ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ("ጠላቶች ይሽሹ" ማለት ነው) ።
ይንበርበሩ፡ የሰው ስም፡ በረ ።
ይንበርበሩ፡ የሰው ስም፡ ጠላቶች ይበርበሩ ይወረሩ ይዘረፉ ማለት ነው ። አንበረበረና ተንበረበረ ከዚህ ቀደም አልተለመደም ። ዳግመኛም እንበለበለና ተንበለበለ በማለት ፈንታ የተነገረ ነው ሊባል ይቻላል ።
ይካ፡ ይበል ካህን (ቅዳሴ) ።
ይኸ (ይህ)፡ የይህን አፈታት ተመ ልከት ("ለማናበብና ሌላ ፊደል ለመጨመር ይህ፥ ይኸ ተብሏል") ።
ይኸን (ዘንተ)፡ የገቢር ቅጽል ።
ይኸው፡ ው የነው ከፊል ነው ("ይኸ ፥ ነው አለ ያሠኛል ሲዘረዝርም ይኸውልዎ ይኸው አለልዎ ይኸውለት ይኸው አለለት ይኸውልሽ ይኸው አለልኸ ይኸውልሽ ይኸው አለልሽ ይኸውላቸው ይኸው አለላቸው -") ።
ይኸውላት፡ ይኸው አለላት ይላል ።
ይኸውላችኹ፡ ይኸው አለላችኹ ።
ይኸውና፡ እንሆ ይኸ አለ ("እንሆ የተባለው ና ከግእዛዊ ቃል ከናሁ የተከፈለ ነው") ።
ይዋይብኸ፡ የርግማን ቃል ("ዋይ ይባ ልብኸ ይለቀስብኸ") ።
ይዋጣለት፡ ኀይሉ ይታወቅለት/ይለይ ለት/ይባባል/ይሸናነፍ ።
ይዘታ (ዎች)፡ የተያዘ ("በጅ ዐደር ነገር") ።
ይዘት (ቶች)፡ እኅዘት) መያዝ ("የዜማ ምልክት አንዲት ነጥብ() የንባብ ማጥበቂያም ትኾናለች መዝገበ ፊደል እይ ነገር") ።
ይደነቃል፡ የሰው ስም ።
ይዲ፡ ይበል ዲያቆን (ቅዳሴ) ።
ይድረስ (ይብጻሕ)፡ የደብዳቤ'የመ ልክት አርእስት ("ይቅረብ ማለት ነው") ።
ይድረስታ፡ ይድረስ ፥ ማለት ("አድራሻ") ።
ይድነቃቸው፡ ዝኒ ከማሁ ("ይግረማቸው ማለት ነው") ።
ይድኖ፡ ከዠማ በስተግራ ያለ አገር ስም ።
ይገም፡ የወረዳ ስም (በመንዝ ክፍል ያለ ቀበሌ - "ይሳብ ይምጠጥ" ማለት ነው - ዐገ መና ገመጠ ባማርኛ ይገጥማሉ - "(ተረት)" - እከሊት ስለ ሞተች ሰዎች ይገምጧት ወጡ ") ።
ይገባል (ብዉሕ መፍትው ርቱዕ ይደሉ)፡ ሰውን ከማመን እግዜርን ማመን ይገባል (ይሻላል) ።
ይገባል (ይትገባእ ሀሎ)፡ መግባት ይቻላል ።
ይጋርዱ፡ የሴት ስም ።
ይግለጡ፡ የሰው ስም "ጠላቶች መንገድ ይልቀቁ ማለት ነው።"
ይግባኝ አለ፡ የተፈረደበትን ፍርድ ሳይቀበል ቀረ፡ ለበላይ አስማለኹ አለ፡ አማጠነ ።
ይግባኝ፡ ወደ በላይ ዳኛ ይግባልኝ ይሰማልኝ ።
ይግባኝ፡ ይሰማልኝ፡ ገባየጕድፍ፡ በቁሙ፡ ጐደፈ ።
ይግባኝታ፡ ይግባኝ ማለት፡ ምጥንታ አቤቱታ ።
ይግባኞች፡ አቤቱታዎች ።
ይጠቅመኛል፡ ያጠግበኛል/ይበቃኛል ።
ይጣ፡ ቀበሌ፡ ዐጣ ።
ይጣ፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ ("ይባዝን" ተመልከት ") ።
ይጣ፡ የሩቅ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ፲ አያግኝ ።
ይፋ (ኦሮ፡ ኢፋ፡ ብርሃን)፡ ግልጥ ስውር ያይዶለ ነገር ።
ይፋታዊ፡ የይፋት ማለት ነው ።
ይፋት፡ በሺዋ አውራጃ ያለ እፃር ።
ይፋቶ፡ የገብስ ስም ።
ይፋቶች፡ የይፋት ሰዎች ("የይፋት ተወ") ።
ይፋግ፡ በበጌምድር ከቃሮዳ በታችያለ አገር ።
ይፋግ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ።
ይፍቱኝ፡ "እግዜር ይፍታ" (የተና ዛዥና ያናዛዥ ቃል ") ።
ይፍጀው፡ ያቃጥለው ይጨርሰው ይቻ ለው ። "ሆድ ይፍጀው" እንዲሉ ።
ዮ፡ (ሆይ) ንኡስ አገባብ ("የአንክሮና የአጋኖ የአክብሮ ቃል። ሰውዮ ሴትዮ ") ።
ዮሐንስ (ጽርእ)፡ የሰው ስም ("በዕ ብራይስጥ ዮሐናን ይባላል ትርጓሜውም እግዜር ምሕረቱን ሰጠ ማለት ነው ዳግመኛም ደስታ ተብሎ ይተረጐማል") (ሉቃ. ፩፡ ፲፫, ፲፬) ።
ዮሐንስ ቅድ)፡ ዐጤ ዮሐንስ ይታጠቁት የ ነበረ ሱሪ ።
ዮር፡ ከፊለ ስም፡ ዮርዳኖስ ።
ዮር፡ የዮርዳኖስ ከፊል ።
ዮርዳኖስ፡ የወንዝ ስም ("ከላይ ፫ ከታች ፩ የኾነ ዠማ ጌታችን የተጠመቀበት ትርጓሜው የዳን ወንዝ ማለት ነው ይላሉ") ።
ዮሽ፡ የነገር ትራስ ።
ዮቅጣን
ዮቅጣን፡ የሰው ስም ("የዔቦር ልጅ ዘሩ ቀጠነ ነው") (ዘፍ. ፲፡ ፳፭-፳፱) ።
ዮናኤል፡ የመልአክ ስም ("ርግበ አምላክ ማለት ነው") (ገድ. ኪሮ) ።
የ ፡ ፲ኛ ፊደል በአበገደ በጥንታዊው ተራ ቍጥር ("በፊደልነት ስሙ የማን በአኃዝነት የ፲ ይባላል") ።
የ፡ (ኢ) አሉታ ።
የ፡ (ዘ) በኀላፊ አንቀጽ መነሻ ኹሉ እየገባ ባለቤት ሳይኖር በቂ ይኾናል።
የ፡ (ዘ) ባለቤት ሲኖር ቅጽል ይኾ ናል ።
የ፡ (ዘ) የዘርፍ ደፊ ("ወይም አያያዥ የሰማይ · አምላክ የአቤል መሥዋዕት የሙሴ ጽላት የሰሎሞን መቅደስ የልጅ ጥፉ በስም ይደግፉ ቢል ጥፉ የኾነን ልጅ ያሠኛል ቅጽልን ከነተሳቢው ሲደፋ ያህያ ውሃ ጠጪ ይላል ፭ኛውን ያ እይ") ።
የ፡ (ዚኣ) ባለገንዘብነትን የሚገልጥ ጠቃሽ ("ይኸውም አያያዥ ካለው ይገባል ይህ ቤት የሱ የሷ የኔ የኛ የነኛ የናንተ ያንተ ያንቺ ነው") ።
የሐናን ለወለተ ሐና፡ ያንዱን ለሌ ላው ።
የሐዘንና የማድነቅ ቃል ወይም የመልክት ("አንተንም መሬት ይበላኻላ እንደ ሞኝ ሰው እንደ ተላላ ል የዘንድ አንቀጽ መነሻ ሲኾን ከሩቁ ወንድና ከሩቆቹ በቀር በኹሉ በትእ ዛዝ ግን እኔ በሚል ብቻ ይገባል ልትጥፍ ") ("እሷ") ።
የሃይማኖት ቀንቃኞች)፡ በወዲያ ግብጾች ባገራችን ደብረ ሊባኖሶች ።
የሑዳድ ፈሪ፡ ዕጣ ሑዳዱን ሳይሖድድ የቀረ የሚከፍለው ዕዳ ።
የኋሊት፡ ወደ ኋላ አካኼድ/አረማመድ ("ልጁ ፊቱን ሳይመልስ የኋሊት ይ ኼዳል።") ።
የኋላ እሸት/የኋላ ወርቅ፡ የወንድና የሴት ስም ("ዘግይቶ ዘግይታ የተገኘ የተገኘች ማለት ነው") ።
የኋላ የኋላ፡ ቈይቶ ቈይቶ ("በሐሰት ከፍ ከፍ ያለ የኋላ የኋላ መውደቁ አይቀርም") ።
የለ፡ ባለ ("ሐማሴን") ።
የለ/የለም (ኢሀለወ/ወኢሀለወ)፡ እሱ የለ ።
የለ/የል (ኢሀለወ)፡ ኣለ ያለውን የለ በማለት የሚነገር አፍራሽ አሉታ አንቀጽ ።
የለሽ፡ የሌለው ።
የለሽ/የለሽም (ኢሀለወኪ/ወኢ ሀለወኪ)፡ ምንም የለሽ ።
የለሽ/የለሽም (ኢሀሎኪ/ወኢሀሎኪ)፡ አንቺ የለሽ ።
የለበመ ("የሚለብም ዐዋቂ ጭምት አስተዋይ የሚመላ ሠያሚዐቃቢ ልበማ ዕውቂያ ሥየማ መለበም ማወቅ መጨመት መሠየም መምላት የሚያ መለበሚያ ማወቂያ መምሊያ መሠ አለበመ ") ("አለበወ") ።
የለች/የለችም (ኢሀለወት/ወኢሀለወት)፡ እሷ የለች ።
የለን/የለንም (ኢሀለወነ/ወኢሀለወነ)፡ ዕውቀት የለን ይላል ።
የለን/የለንም (ኢሀሎነ/ወኢሀሎነ)፡ እኛ የለን ይላል ።
የለኝ/የለኝም (ኢሀለወኒ/ወኢሀለወኒ)፡ ገንዘብ የለኝ ።
የለኸ/የለኸም (ኢሀለወከ/ወኢሀለወከ)፡ ገንዘብ የለሽ ።
የለኸ/የለኸም (ኢሀሎከ/ወኢሀሎከ)፡ አንተ የለኸ ።
የለኹ/የለኹም (ኢሀሎኩ/ወኢሀሎኩ)፡ እኔ የለኹ ።
የለው/የለውም (ኢሀለዎ/ወኢሀ ለዎ)፡ ዕውቀት ' የለው ።
የሉ/የሉም (ኢሀለዉ/ወኢሀለዉ)፡ እነዚያ የሉ።
የሊ (ዔሊ)፡ ድንጋይ ልብሱ ።
የላመ፡ የጣመ፡ የመኳንንት፡ ምግብ፡ የለሰለሰ፡ የጣፈጠ፡ መብል፡ ገንፎን፡ ዐልጫ፡ መረቅን፡ የመሰለ ።
የላት/የላትም (ኢሀለዋ/ወኢሀለዋ)፡ አላንድ የላት ("እንቅልፍ የላት ነቀሰ ንና (ቀለፋ) ብለኸ እንቅልፍን ተመልከት") ።
የላቸው/የላቸውም (ኢሀለዎሙ ን/ወኢሀለዎሙ ን)፡ ትጋት የላቸው ።
የላችኹ/የላችኹም (ኢሀለወክሙ ን/ወኢሀለወክሙ ን)፡ ዕውቀት የላችኹ ።
የላችኹ/የላችኹም (ኢሀሎክሙ/ወኢሀሎክሙ)፡ እናንተ የላችኹ ።
የላይ ልብስ እጀ ሰፊ ("ከጥጥ ከጠጕር የተሠራ ዐጪር ጥብቆ ረዥም ቀሚስ በስተፊት ክፍት ባላዝራር የኾነ የፈረንጅ ስፌት ኮትና ሱሪ እንዲሉ ኮት እንግሊዝኛ ነው ኩታ ኪታ ኮት አንድ ዘር መኾናቸውን አስተውል ከተበ ") (ከቲብ/ከተበ/ከሰበ) ።
የሌለ ፣ ያልተገኘ፡ ያልተቀመጠ፡ ያልቈየ፡ ያልኖረ፡ ያልነበረ፡ ("ዘዳ. ፳፱፡ ፲፭") ።
የሌለ፡ ያልነበረ፡ ሌለ ።
የሌለበት፡ ያልነበረበት፡ ያልተገኘበት፡ ("ዮሐ. ፰፡ ፯") ።
የሌለው፡ ያልተቀበለ፡ ያሊያዘ።
የልብ ልብ በቃው)፡ በሰው፡ ታመነ፡ የጭካኔ፡ ጭካኔ፡ ተሰጠው፡ አልፈራም፡ እንዳሻው፡ ተናገረ፡ የያዘውን፡ ይዞ
የልካ (ኦሮ፡ ኢልካን)፡ የዝኆን ጥርስ አንባር ።
የልጅ ቅዘን ይንካልኸ)፡ ሰው ዐዲስ ልብስ በለበሰ ጊዜ የሚቀበለው ምርቃት ።
የልጅ ቅዘን)፡ ዐይን አበባ ብጫ ጥለት ።
የልጅ የፈረስ ቍንጮ የተጐነጐነ ጠጕር ("ከልጅነት እስከ ዕውቀት ከኩተት እስከ ሽበት እንዲሉ። ኮተት ጓዝ እክት ዕቃ ግሴት ኮተት እድፍ ጭቅቅት ኮተታም ጓዛም እክታም አድፋም ኮተቴ ጥቍር አደንጓሬ ባለሐረግ ኮተቴ የኔ ኮተት አከታተት አጨማመር መክተት የካ ቲትን እይ የዚህ ዘር ነው ኸ የፊደል ስም የከ ዲቃላና ወራሽ ግእዝ አሰርከኒ ፈታሕከኒ ወሰድከኒ ያለውንአሰርኸኝ ፈታኸኝ ወሰድኸን ማለቱን ያሳ ያል የኀና የኸ ድምጥ አንድ መኾኑንም ባቡጊዳ እይ ዳግመኛም የሀሐ ተለዋጭ ሲኾን ይህ ይኸ ምንዛህ ምንዣኸ በረሓ በረኸኛ ይላል ከሀሐኀም ተለይቶ በግስ መድረሻ ደለኸ ጮኸ ሲል ይገኛል ከካዕብ እስከ ሳብዕ ያለውም ጮኹ ጯኺ ጩኻ መጮኼ ጩኸ ጩኾ እያለ ይነገራል ኹ የኩ ወራሽ እኔ ለሚል የአንቀጽ ዝርዝር ሲኾን በግእዝ በላዕኩ ሰግ ኸ ፮፻፺፮ ከቸቸ ") (ቀጨጩ) ።
የልፍኝ አሽከር)፡ አንጣፊ ጋራጅ አስታጣቢ አልባሽ መጫሚያ አቀባይ ዠርባ ጠቋሚ ተረኛ የውስጥ አሽከር ። በአረብኛም "አስከር" ይባላል ።
የሎሄ፡ ኤሎሄ ።
የሎሄ የሎሄ አለ፡ የጭንቅ ጩኸት ጮኸ ("ኢዮሂ ኢዮሄ አለ ኤሎሄና ኢ ዮሄ የሎሄ ፫ቱ ኹሉ አንድ ዘር ናቸው") ።
የሎሚ እሸት)፡ ቅጠሉ የምስር ቅጠል የሚመስል ታናሽ ዕንጨት (ሽታው የሚጣፍጥ - በመስከረምና በጥቅምት የሚያውድ) ።
የሎስ (ሶች)፡ ያሞራ ስም ("ንስር ግልገል አንሣ መቀነትማ የሎስ ያንሣኸ እንዲሉ መልኩ በስተዠርባው ጥቍር አረንጓዴ በስተፊቱ ከላድማ ነው ባፉና በክንፉ በእግሮቹ ላይ ንጣት አለው ከክንፍ እስከ ክንፉ ፭ ክንድ ይኾናል") ።
የመስቀል መሬት)፡ የካህን ርስት።
የመንግሥታት ማኅበር)፡ የመንግሥታት መልክተኞች ጉባኤ አደባባይ ዐውድ ።
የመጠጥ ዐረፋ)፡ ኰረፌ ።
የመጣ፡ ቢመጣ፡ አስቀድሞ፡ የተደረገ፡ መከራ፡ ወደ፡ ፊትም፡ ቢደረግ።
የሙጥኝ፡ ተማጣኝ የሚጠጋው ሰው ።
የሙጥኝ አለ፡ ተማጠነ (የሰውን ል ብስ ያዘ ተቈራኘ ") ።
የሚ (ዘይ)፡ በትንቢት መነሻ እየገባ ለሩቅ ወንድ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች ቅጽልና በቂ ይኾናል።
የሚለብስ ቀዳሽ ("በግ እዝ ለባሲ ይባላል ሥጋን ተመልከቱ ለበስ የለበሰ ጉም ለበስ ብረት ለ በስ እንዲሉ። 704 ") ።
የሚያስማ/የሚሳማ፡
የማ (ዘኢይ)፡ የትንቢት አሉታ በቂ ቅጽል መነሻ ።
የማምሻ፡ ከመሸ በኋላ የሚነድ የማታ ማገዶ።
የማሪያም መቀነት)፡ ቀስተ ደመና ።
የማሪያም ምሳ)፡ መዠመሪያው ያራስ ገንፎ።
የማሪያም ምሳ)፡ መዠመሪያው ያራስ ገንፎ።
የማር እሸት)፡ ቀጠላ ዐዲስ ማር ።
የማን፡ የፊደል ስም የ ("ቀኝ ማለት ነው") ።
የማይ፡ ዕቃ፡ እንዲሉ።
የም (ዘ)፡ ለቅርቦቹ ለ፫ቱ ሰራዊትና እኔ እኛ ለሚሉ በትንቢት መነሻ እየገባ ቅጽልና በቂ ' ይኾናል ።
የምሥራች፡ ሙሽራው ሙሽራዪቱን ባወቀ ጊዜና ልጅ ዳዊት በደገመ (በጨረሰ) ሰዓት የሚቀበለው ስጦታ ወይም ሽልማት። መሠተረ፡ አጥርቶ ነቀለ፡ መሰተረ።
የምሥራች፡ የደስታ ወሬ፡ ሥራች ።
የምሩ፡ ውሃ ሥንቁ፡ የደስታ ተክለ ወልድ አያት ያባት አባት።
የምሩ፡ የሰው ስም (አባትና እናት ወልደው ከሞተባቸው በኋላ የወለዱትን ልጅ "የምሩ" ይሉታል፡ "አምላክ ይኸን ልጅ የሰጠን የውነቱ ይኾን" ማለት ነው - ሲዘረዝርም የምሩ/የምርኸ/የምራቸው/የምራችኹ/የምሯ/የምርሽ/የምሬ/የምራችን ነው ይላል) ።
የምሩ፡ የውነቱ መረረ ።
የምር፡ የውነት —መረረ ።
የምር፡ የውነት/የርግጥ። "እከሌ ይህ ነገር የምርኸ ነውን?"
የምቡት የምቡት፡ የልጆች ፈሊጥ ።
የምቡት የምቡት፡ ይኸን ያልመታ ይሞት ።
የሞት፡ ሞት፡ ሞትን፡ የሚሽር፡ ሕይወት፡ ክርስቶስ ።
የሞት፡ ሞት፡ የሥጋ፡ ወደ፡ መቃብር፡ መውረድ፡ የነፍስ፡ እገሃነም፡ መግባት ።እስረኛው ከወህኒ፡ ቤት፡ የሞት፡ ሞቱን፡ አመለጠ፡ ቢል፡ ብሞትም፡ ልሙት፡ ብሎ፡ ማለት፡ ነው።
የሞት ጥላ)፡ ውድቅት ድቅድቅ ጨለማ ("በጨለማ ላይ የተጨመረ የዛፍ የገ ደል ጥላ ምሳሌ በኀጢአት ላይ የሃይማኖት ክሕደት") (ኢዮ. ፫፡ ፭፡ ኢሳ. ፱፡ ፪) ።
የሠለስት፡ የሦስትኛ ሰዓት ጸሎት አቍጣሮ ።
የሰላበትን ወጭት ሰባሪ)፡ ጥጋበኛ ሰው፡ ዕገውጡ።
የሠላጢን መሬት)፡ የወታደር ይዘታ። ጠፋንን "ለማን (ሸ)" ብለኸ ኣሸንን እይ።
የሰማይ ስባሪ)፡ ሰፊ ምድር።
የሰማይ ቍጣ)፡ መብረቅ ።
የሠሥቴ ከስቴ፡ የሠሠተ ከሳ (የሠሢታ ከሲታ - "ጕይዲ" ግን ዐጪርና ቀጪን ቅጠል አረንጓዴ መልክ ይለዋል) ።
የሰቀላ መሬት)፡ መትከያ/መንቀያ/መሾሚያ/መሻሪያ ምድር።
የሰዓት መርፌ)፡ ሰዓትን/ደቂቃን/ካልኢትን ቅጽበትን የሚቈጥሩ ፫ መርፎች።
የሰው ሰው)፡ የሌላ ሌላ፡ የባዕድ ባዕድ።
የሰው አገር ሰው)፡ የሩቅ/የውጭ አገር።
የሰው ዥብ)፡ ተፈጥሮው ሰው ሲኾን እንደ ዥብ ሰው የሚ በላ ።
የሰይጣን ቍራጭ)፡ ጭራሽ ክፉሰው ።
የሰይጣን ፈረስ)፡ ኹለት እግር ያላት መንኰራኵር ።
የሰዳጅ፡ የላከ፡ የተመረጠ (የሥጋ ብልት) ። "የሰዳጅ ለወዳጅ" እንዲሉ።
የሳታት ሰላምታ)፡ ስንኙ ሦስት እየኾነ የተደረሰ ግእዛዊ ግጥም ("ሰላም ለከ ኪ ክሙ" እያለ የሚነሣ) ። (የበገና ሰላምታ)፡ በበገና የሚዘመር ያማርኛ ግጥም።
የሴት ምራቋ ደንዳና ነው)፡ ስታበስል ከዚያም ከዚያም ትቀምሳለች። ቈበርን እይ።
የሴት ሴት (መልኳ እናቷን ብቻ የሚመስል ሴት) ።
የሴት ቍንጮ)፡ ልባም ባለያ ሴት ።
የስሚስሚ፡ የመስማት መስማት (የወሬ ወሬ) ።
የረር፡ ካዲስ አበባ በስተደቡብ ያለ ተራራ ("በሐረርጌም የሚገኝ ቀበሌ ኤረርን እይ") ።
የሩቅ ሴት)፡ እሷ ።
የርሱ፡ የሱ ("—የዚያ —ርስ እስ") ።
የርብርብ፡ የርዳ ተራዳ ጠብ ("የጕንዳን አያያዝ ") ።
የርቦራ፡ የዝኆን ጥርስ አንባር ("ጠላ ቱን ለገደለ የሚሰጥ") ።
የሮጠ/የሚሮጥ - የሮጠ/የሚሮጥ።
የሸማ ስም ("ዕ ጥፍ የላይ ልብስ መደረቢያ ፳፬ ክንድ ፬ ፈርጅ ሲበዛ ኩታዎች ይላል (ጐዳ ኩታ) አለጥለት የተሠራ ጥለት የሌለው ኩታ (ጥበብ ኩታ) በጫፍና በጫፉ ከ፰ ላይ ጥበብ የ ተሠራበት (የተጣለበት) ባለጥበብ ኩታ ጐዳን ጠበበን ተመልከት ቍጥኔን እይ ኩትኛ የኩታ ዐይነት እንደ ኩታ የተሰፋ ልብስ ዝቅዝቅ ያይዶለ ጋቢን አስተውል ኩታ ገጠም አንድ ላይ ጐን ለጐን ያለ መሬት ወይም ርስት እንደ ኩታ የገጠመ (ጥት) ኩት ") (ዕሽ) ።
የሸማኔ ' ዕቃ)፡ ሸማ ' መሥሪያ ዐርብ ።
የሸንበቆ ምርኵዝ)፡ መቃ የያዥውን እጅ ተሠንጥሮ እንዲወጋ፥ አምኖ የተጠጋውን የሚጐዳ እንጂ የማይጠቅም (ኢሳ. ፴፮፥፮) ።
የሺ፡ የሴት ስም ("የሺመቤት ከፊል ሺን ተመልከት") ።
የሻላ ሀብተ ማርያም፡ የጠራ ገሊላ ባላባት ።
የሻላ፡ የቀድሞ ማዕርግ ስም ("የሻለቃ ከፊል ባለግምጃ ሱሪ") ።
የሻላ ጥሬ ወርቅ፡ ዝኒ ከማሁ ("፩ኛው ፥ ልጅ ፪ኛው አባት ") ።
የቀረ፡ ያልመጣ ።
የቀትር)፡ በቀትር የሚጸለይ ጸሎት አቍጣሮ ። "የቀትር እባብ የቀትር ጋኔን" እንዲሉ ።
የቀጨማ፡ የጠፋ ከብት ይዞ ለተ ጐን ወይም ላሳደረ የከብት ጌታ የሚሰጠው ገንዘብ ("አንድ ብር") ። ዳግመኛም የዥብ አፍ ይባላል ።
የቍላ፡ ያልተወቀጠ/ያልተቀጠቀጠ በሬ ።
የቁም ፍታት)፡ ሳይሞቱ መፈታት (በሕይወት ሳሉ ተዝካር ማውጣት ") ።
የቍራ ምሳ)፡ ውስጡ ደም የሚመስል የወይናደጋ ዐረግ።
የቍራ ምሳ)፡ ውስጡ ደም የሚመስል የወይናደጋ ዐረግ (ፍሬ ወይም ርሱ ራሱ ዐረጉ) ። ሥርና ሥራ ማሰና ምሳ በአማርኛ ይተባበራሉ። (ግጥም)፡ "ብዙ ሥራ ዐዋቂ ትላንት ተቀበረች መድኀኒቱን ምሳ ትሰጠኝ ነበረች"። "ያኵራፊ ምሳ እራት ይኾናል" እንዲሉ።
የቍራ ወስፌ)፡ ታናሽ ቅጠል።
የቍር፡ በቡልጋ ውስጥ ያለ ቀበሌ ።
የቍንጢጥ፡ ትንንሾች ልጆች የመዳ ፋቸውን ዠርባ እየቈነጠጡ በማያያዝ፡ "የቍን ጢጥ የቍንጢጥ ሻ ብትን" እያሉ እጃቸውን በመለያየት የሚያደርጉት ጨዋታ ።
የቈጣሪ፡ ድርን ቈጥሮ ለቋጠረ የሚሰጥ አነባበሮ ። "ድረሽ የቈጣሪ ይዘሽ" እንዲል ሸማኔ ።
የቅ፡ የጭ ወዲያ ቀና ጨ ተወራራሾች ስለ ኾኑ የጭ በማለት ፈንታ የት ይላል ።
የቅርብ ሴት)፡ አንቺ ። "ጠነዛን" አስተውል ። ቅጽል ሲኾን "ሴት ልጅ" ይላል ።
የበረት፡ በበረት የሚደረግ መሥዋዕት፡ የኦሮ አምልኮ ። ቦረንትቻን እይ ።
የበገና መምቻ፡ ድሕንጻ - ዘፀ. ፲፯፥፳፪) ።
የቢስ የቸር፡ የክፉ የበጎ ። ዛሬ ሌሊት የቢስ የቸር ሲለኝ (ሲያሳየኝ) ዐደረ ።
የባ ሕር ዐረፋ)፡ ይደርቅና የዛገ ብረት መወ ልወያና መድመፅ የሚኾን ሻካራ ደንጊያ ።
የባሕር ቍልቋል)፡ ከበርበር የመጣ እሾኻም ተክል ፍሬው የሚበላ ።
የባጕስ፡ ዦሮ ቈራጭ፡ ባጐሰ ።
የብስ (የብሰ)፡ ደረቅ ምድር ("ባሕር የሌለባት") ።
የብረት፡ ልጥ)፡ ሥሥ፡ ብረት፡ የሳንቃና፡ የንጨት፡ ማእዘን፡ ማ ያያዣ፡ የጣቃ፡ መቀፈጃ።
የቦ (ኦሮ)፡ የጦር ስም ("ታናሽ ጦር ጭሬ") ።
የተለበጠ የተጌጠ የተሠነበጠ ("ልባጭ ሥንባጭ ልጣጭ ልብጣት ") ("ልብጠት") ።
የተላከ፡ ካቶ፡ እከሌ፡ እንዲሉ።
የተላከ፡ የደብዳቤ፡ አርእስት።
የተሻ ወርቅ፡ የሰው ስም ።
የተሻ፡ የተፈለገ ።
የተቃረ፡ የጐመዠ/የሠየ ።
የተትረፈረፈ፡ ተርፎ የፈሰሰ ። መጽሐፍ ግን "የተረፈረፈ" ይላል አያሠኝም (ሉቃ. ፮፡ ፴፰) ።
የተንቃቃ፡ የሞቀ የደረቀ ቅይጥ እን ጀራ፡ የተጕላላ ሰው ።
የተከበረ፡ የከበረ፡ ክቡር።
የተከበሩ፡ የከበሩ፡ ክቡራን ክቡራት። ተከባሪ፤("ከባሪ")፡ የሚከበር፡ ራሱን አኵሪ፡ እኔ እከሌ የእከሌ ልጅ ባይ፡ ተጓዳጅ። ተከባሪነት፡ ተከባሪ መኾን። መከበር ("መክበር")፤መኵራት መጓ ደድ ። መከበሪያ፡ ("መክበሪያ")፡ መጓደጃ። ተከባበረ፡ ክብር ተቀባበለ፡ አንተ ትብስ አንተ ትብስ ተባባለ።
የተከተለ ("የሚከተል ለጣቂ አሽከር ገረድ ልጅ ወራሽ ደቀ መዝሙር ጥጃ ግልገል ተተኪ ") (፩ጴጥ. ፫፡ ፲፫) ።
የተከተረ ("የታገደ የ ቆመ ብዙ ውሃ መከተር መከበብ መታገድ መብዛት መከተሪያ መታገጃ መብዣ አካተረ አደላደለ አካበበ አስተጋገደ አባዛ አካታሪ ያካተረ የሚያካትር ማካተር ማካበብ ማስተጋገድ ኩታራ የዶሮ ስም ዶሮ ") (ጕራጌ) ።
የተከታተለ ("የሚከታተል ተጠባባቂ መከታተል መጠባበቅ መከታተያ መጠባበቂያ ") ።
የተካነ፡ የጣመ/የጣፈጠ ("የመኳንንት ወጥ ") ።
የተካነ፡ ዲያቆን/ካህን (ቄስ) የኾነ ("የሠለጠነ ") ።
የተኳለ የተዳረ ("ተኵሎ የተዳረ ወግ ማረግ የደረሰው ልጅ ") ።
የተዋበ/የተዋበች፡ ያማረ/ያማረች (፩ ሳሙ. ፲፯፡ ፵፪) ።
የተገባ፡ የበጀ የተመቸ የቀና፡ ምቾት ቅን ነገር ።
የተጣራ፡ ሰውን የጠራ ።
የተጣራ፡ የማር/የወይን ጠጅ ።
የተጣራ፡ ጠጅ፡ ጠራ (ጸርየ) ።
የታቦት ዘፈን)፡ "ሰዉን ገረ ፈና በቂጥኝ ዐለንጋ ሚጣቅ እሾላው ሥር ጠበሉን አረጋ ። አወጣ ኣፈለቀ ኣመነጨ ቢል በቀና ነበር" ።
የታደለ (ች/ሉ)፡ ዕድላም ባለዕድል ።
የት (አይቴ)፡ ንኡስ አገባብ ("የጥያቄ ቃል የቦታ በቂ ከአንቀጽ በፊት እየገባ ይነገራል። የት አለኸ የት ባጀኸ የት ዋልኸ የት ከረምኸ የት ኼድኸ የት ዐደርኸ የት ሰነበትኸ መምህራንም በየት ፈንታ ሔት ይላሉ ደቂቅ አገባቦች እንደ ከ ወደ እስከ መነሻ ሲኾኑት እንዴት ከየት ወዴት እስከ የት ይላል በዝርዝርነት የስም ምትክ ሲኾን የቱ የትኛው ነው የትኞች ቹ የትኛዎች ቹ ናቸው የትኛዋ ይቱ ናት ይላል የየት ነኸ ቢል የየት አገር ሰው ያሠኛል ቅጽልነትንም ያሳያል (ተረት) አገርኸ የት ነው ማሪያም ውሃ እንግዲያውማ ዘመዴ ነኻ") ።
የት እየለሌ፡ እጅግ መራራቅን ያስረዳል ።
የት ውዬ የት ዐድር ብዬ፡ የወፍ ጩኸትና ስም ።
የነቢ፡ በበረት ፉካ ውስጥ የሚቀመጥ የቦረንትቻ መሥዋዕት (የበግና የፍየል ሥጋ ብልት ቅንጣቢ የጕሽ አተላ ቈሎ በያይነቱ ርሚጦ - ባላገሮች "ነቢ" የሚሉት በቃልቻ ያደረውን ዛር ነው - ተረፈ ዳን. ፲፫፥፪, ፲፯) ።
የነቢ፡ የነቢይ ፈንታ/ድርሻ (፩ነፃ. ፲፯፥፮) ።
የነካ ነካ፡ የዞግ ዞግ የሳቢያ ሳቢያ (አንዱን የነካ ነገር ሌላውን ነካ በጓዱ ሰበብ ባልንጀራው ተያዘ ማለት ነው - "ዳፈ ብለኸ ዳፋን ፪ኛውን ተረፈ" አስተውል) ።
የነጂ፡ ተጠብሶ እረኛ ከብት ጠባቂ የሚበላው (የፍየል/የበግ ወጠጤ ቍላ) ።
የነጂ፡ የረኛ አበል ("—ነዳ") ።
የኔ (የእኔ)፡ መዠመሪያውን የ ባ፭ኛ ተራ ተመልከት ።
የኔታ፡ የኔ (የእኔ) ጌታ ("ጌታዬ አስተማሪዬ መምሬ") ።
የንጉሥ ቍና)፡ ሌባሻይ ።
የንጨት ሽበት) "ሸብቶ ሳለ ግብሩ መጥፎ የኾነ ሰው ወረረ ብለኸ አወረረን" እይ ።
የዓሣ ስም ("ዓሣ ") (ዐረብ) ።
የዕቡይ ሞረድ)፡ ትቢተኛን ከልክ የሚያገባ ዕቡይ ገሪ።
የዕጣን ሙጫ ከቅርፊት ጋራ ዐብሮ የደረቀ መናኛ ዕጣን ("እንደ ጪስ ዕንጨት ሴቶች የሚሞቁት የሚታጠኑት ሊባኖስ በሶርያና በእስራኤል ምድር መካከል ያለ ደጋ ከፍተኛ ስፍራ ዛፋም ደናም ተራራ አርዝ የሚበቅልበት ሊባኖስ በሊባኖስ የተወለደ የሊባኖስ ሰው ጻድቅ መነኵሴ ከተስዐቱ ቅዱሳን በ በፊት ወዳገራችን በ፫ኛው ፫ ዓ ም መጥቶ ወንጌልን እየሰበከ ብዙ ጊዜ የኖረ ካባ ተክሌ አስቀድሞ ደብረ ሊባኖስን ያቀና ፪ኛ ስሙ መጣዕ ፫ኛ ስሙ ይስሪን ይባላል አባ ሊባኖስ እንዲሉ። ሊባኖስ የዛፍ ስም አስታ የሚመስል ዕንጨት ዐዲሳበቦች የሚተክሉት ለበቀ ጐሰመ ጐን እከሌ ሐሞት በዝቶበት ልቡን ሲለብቀው ዋለ ለበቀ በለበቅ መታ ለባቂ የለበቀ የሚለብቅ መጥፎ ጠጥ ኮሶ እንቆቆ ለበቅ ") ("ቆች") ።
የከሰ (ትግ. ወከሰ)፡ ጠየቀ ("ጥያቄ አቀረበ ነው") ።
የከሰል ምርት)፡ የከሰል ብዛት/ብዙነት። ሸለመን/ሰነፈንን እይ።
የከተመ ("የሚከትም ቈርቋሪ ከተማ ") (ሞች) ።
የከተረ ("የሚከት ደ ልዳይ ከባቢ አጋጅ አብዢ ከተሬ የሰው ስም ከተረ ማለት ነው ከተራ የመክበብ የማገድ የማብዛት ሥራ ከተራ በግእዝ ኣገዳት ኣበዛት ማለት ነው ከተራ የበዓል ስም የጥምቀት ዋዜ ጥር ፲ ቀን ወራጅ ውሃ የሚከተርበት ቦትና ሰው ወደ ዠማ ወርዶ የሚያድርበት ጊዜ ንጊያ መክተር መክበብ ማገድ ማብዛት መክተሪያ ማገጃ ማብዣ ዐፈርና - ") ።
የከተበ ("የሚከትብ ጻፊ ጣፊ በጪ ሠንጣቂ አጋቢ አስተላላፊ ከታቢ የከብት ሐኪም ከተባ የመክተብ ሥራ ክታብ ") (ቦች) ።
የከነፈ፡ ያበደ ።
የከንቱ ከንቱ፡ የብላሽ ብላሽ ("የመ ጥፎ መጥፎ ") ።
የኩል፡ (የእኩል)፡ የጋራ ። የኩል ዐራሽ ፥ የኩል ቤት እንዲሉ። (የአመንዝራ ግጥም)፡ ሚስትም ኣላገባ፡ ላሳብም ኣልቸኵል፡ አንዱ ያገባትን እይዛለኹ የኩል ።
የካ (ኦሮ፡ ኤካ፡ እውነት ነው)፡ ባዲስ አበባ ውስጥ በስተምሥራቅ በኩል ያለ ቀበሌ ።
የካህን ቂም)፡ "ጭጐጐት ፍቅሩ ጥኑ" ።
የካሽ (ሾች)፡ የየከሰ/የሚየክስ ("ጠያቂ") ።
የካቲት (ከተተ)፡ የወር ስም ("፯ኛ ወር ከመስከረም የመከር መክተቻ ማለት ነው ከተተን እይ") ።
የክዳን ዐይነት፡ ሰለታ ("ጠበራ ") ።
የክፉ ብድር ከፈለ ደባ ሠራ ወረረ ዘረፈ ። (ተመልከት፡ ደበደበን እይ) ።
የወለፌንድ፡ የጠማማ ዐመል ሥራ ("ከሰው የማይስማማ") ።
የወል፡ በወሎ ክፍል ያለ ተራራ ።
የወል፡ የሕዝብ/የማኅበር/ያንድነት/የጋራ ርስት/ገንዘብ ("ወይም ሌላ ነገር ዳኛ የወል ምሰሶ የመካከል” እንዲሉ) ።
የወል፡ የተራራ ስም፡ ወለለ ።
የወር፡ ቀለብ/ደመ/ወዝ ።
የወርቅ ቀበቶ)፡ ውስጡ ጠፍር ላዩ ወርቀ ዘቦ ያለበት ቀበቶ ። "ሠቅንን" ተመልከት ።
የወግ ዕቃ)፡ ፈረስ በቅሎ ከነሥራቱ (የጦር ልብስ የጦር መሣሪያ ሻለቃ በሞተ ጊዜ ወደ ቤተ መንግሥት የሚመለስ ") ።
የወፍ ቈሎ)፡ ወፍ የሚመገበው የምድር ፍሬ ።
የዋህ (የውሀ)፡ ገር/ቅን/ሞኝ ("እንስላ ደንሴ ሠረየን ርግብን ረባ ብለሽ ርባ ታን ተመልከት") ።
የዋህ ርባታ)፡ ከዐወቀ እስከ ዐወቅና መዠመሪያ በ፱ መደብ የሚረባ ።
የዋህ ኾነ (ተየውሀ)፡ ለዘበ ገራ ("ወደ ወሰዱት ኼደ") ።
የዋህነት፡ ገርነት/ሞኝነት ።
የዋሆች፡ ገሮች/ሞኞች ("እከይ አልቦች") ።
የዋሻ ቤት ተወቅሮ ተጠ ርቦ የተሠራ ።
የውሃ መንገድ፡ ዘወትር መመላለስ) ።
የውሃ ዕቃ)፡ ገንቦ ዳብሬ እን ስራ ቅል መንቀል ርኰት ቀርበታ ።
የውር መሪ)፡ ዕውርን የሚመራ።
የውሻ ቍስል)፡ ቶሎ የሚሽር ።
የውሽንብር፡ የኀዋት የቍትቻ ዕዳ መብልና መጠጥ ።
የውዝፍ፡ ስለ ውዝፍ የሚከፈል ዕዳና መቀጮ ።
የውጥር፡ እጅና አግሩ በገመድ ታስሮ የሚሳብ/የሚጨነቅ ።
የዘለበት ምላስ)፡ መካከለኛ፡ ብረት። ለመለመ፡ ብለኸ፡ ለምለምን፡ አስተውል።
የዘመቻ ፈሪ፡ ዘመቻ ፈርቶ የቀረ የሚከፍለው ገንዘብ ።
የዘወትር፡ የኹለዬ፡ የሠርክ፡ የዕለት፡ የ ጊዜ፡ የቀን፡ ሥራ፡ ምግብ፡ ልብስ፡ ጸሎት፡ ጀ ንበር፡ በሠረቀ፡ ቍጥር፡ የሚደረግ፡ ማንኛውም፡ ነገር፡ ኹሉ። ሠርክን፡ እይ ።
የዘወትር፡ የኹለዬ/የሠርክ/የዕለት/የ ጊዜ/የቀን ሥራ/ምግብ/ልብስ/ጸሎት/ጀ ንበር ("በሠረቀ ቍጥር የሚደረግ ማንኛውም ነገር ኹሉ") ።
የዘይት ቅመም)፡ ተልባ ኑግ ሰሊጥ ሱፍ፡ የዚህ ኹሉ ማጣፈጫ ጨው ነው ።
የዘገር፡ በዘገር የቀና/የተያዘ ("የንጉሥ የመንግሥት ርስት ጕልት የቤተ ክህነት ያይ ዶለ") ።
የዚያ፡ የነዚያ፡ የርሱ፡ የነርሱ፡ ጠቃ ሽና፡ በቂ ።
የዚያ/የነዚያ፡ የርሱ/የነርሱ ጠቃ ሽና በቂ ።
የዚያየሱ፡ ዚያ ።
የዝኆን ዦሮ ተሰጠው)፡ ሰምቶእንዳልሰማ ኾነ፡ ነገርን ኹሉ ናቀ፡ ቸል አለ።
የዝን (የዕዝን)፡ ላዘነተኛ የሚሰጥ ፱ እንጀራ (ንፍሮ - ሕዝ. ፳፬፥፲፯፡ ሆሴ. ፱፥፩ ") ።
የዝንጀሮ ቂጣ)፡ የቅጠል ስም (በገደል ቀጣና የሚበቅል ሰማያዊ ቅጠል ኹናቴው ከማነሱ በቀር ቂጣ የሚመስል ") ። ዳግመኛም እረኞች በአየር ላይ ስለሚያሽከረክሩት ሽክርክሪት ይባላል ።
የዣርት ወስፌ)፡ ወስፌ መሳይ የዣርት ጠጕር ።
የዥብ ምርኵዝ)፡ የታናሽ ዛፍ ስም (በወይናደጋ ቈላ የሚበቅል ተራ ዕንጨት) ።
የየ (ዘዘ)፡ የደጊመ ቃል በቂ ።
የየካሽ፡ የተየካሽ ("የጠያቂ የተጠያቂ ወይም ራሱን እሱ ጠይቆ እሱው መልስ የሚሰጥ ሌላ መልስ ሰጪ የሌለው መምህራን ግን የተየካሽ ተየካሽ ይሉታል") (ትርጓሜ ትምህርተ ኅቡኣት) ።
የዪ (ኦሮ)፡ የተኩላ ስም ("ተኵላ") ።
የያተኛ፡ የቀን ሠራተኛ ("ደመ ወዝ ቀለብ እኸልና ገንዘብ የጕልበት ዋጋ") ። (ተመልከት፡ ነዳ ብለኸ ምንዳን እይ) ።
የደስ ደስ፡ የጪስ ዕንጨት ።
የደስ ደስ፡ ገባር ለተሾመ የሚሰጠው ገንዘብ መተያያ ።
የደስታ መሬት)፡ የድንኳን ተካይ ምድር።
የደረት ሳንቃ)፡ ጌጠኛ የደረት ልብስ ሴደርያ (ዘፀ. ፳፭፡ ፯፡ ፳፰፡ ፬) ።
የድኻ ፍታት)፡ ዘራዳም ግባተ መ ሬት ። "ጓዘ"ንና "ዐረፈን" "መላን" ተመልከት ።
የዶሮ መከልከያና ሐይ ማያ ማብረሪያ ድምጥ ("ኩቶ በወላምኛ ዶሮ ማለት ነውና ኩት ከዚህ የወጣ ነው ኩት ") (ሑት) ።
የጁ (የእጁ)፡ ያገር ስም ("የቀድሞ ስሙ ገነቴ ነው አለቃ ታየ የጻፉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ ተመልከት") ።
የጁን ይስጠው)፡ ጡር ይድረስበት።
የገቦ (ዘገቦ)፡ የጐን ("በጐን የሚወጣ የሚያፈጠፍጥ የሚያቈጠቍጥ የማሽላ ቅጥይ የበቈሎ ፍሬ መጽሐፍ ግን ገቦ ይላል") (ዘሌ. ፳፭፡ ፭) ።
የገነት ገነታዊት፡ ወይም (ገነትየ) "የኔ ገነት ማለት ነው አገናነን አከባበር አበዛዝ አጀጓጐል መግነን።" (ተመልከት፡ ገነገነን "የዚህ ዘር ነው።")
የጉም ሽንት)፡ ረቂቅ ካፊያ (ከም የሚጎኝ) ።
የጕድፍ ቅል)፡ ሞኝ ሰው ዐሞተ ቢስ ደካማ ። "ባርን" ተመልከት ።
የጕድፍ፡ ፈንጣጣን የመሰለ ቀላል የልጆች በሽታ (በገላቸው ላይ ዐልፎ ዐልፎ የሚወጣ አካል አጕዳፊ በቶሎ የሚረግፍ ዕከክ)። (ተመልከት፡ ጋኔንን ቅልን) ።
የጋዣ ማር)፡ ንብ ጋዣውን ቀሥማ የጋገረችው ማር።
የግራ ካራ) ዐመለ መጥፎ ሰው ።
የግእዝ ቅኔ፡ መወድስ) ።
የጠረኘ፡ ያፈለ/የጐለመሰ ።
የጠጅ ቀንድ)፡ ጠጅ መያዣ ማኖሪያ ።
የጠገተ ሥር ርሱ ነው፡ ምስጢሩም የጥጃንና ያላቢን ወደ ላም ጡት መጠጋት ያ ስረዳል።
የጠፍ፡ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ("ለሹም ወይም ላምጪው የሚገባ") ።
የጣላ ጣላ፡ ካንዱ ወዳንዱ የተላለፈ ሰው ወሬ ።
የጣመ (ጥዑም)፡ የጣፈጠ ("ጣፋጭ ምግብ የላመ የጣመ እንዲሉ") ።
የጣማ ገንዘብ፡ ዐርሶ/ቈፍሮ/ወጥቶ/ወርዶ/ ነግዶ ያገኙት/ያተረፉት/የለፉበት/ላብ ያፈሰሱበት የድካም ዋጋ ደሙ ወዝ ።
የጣይ ሽንት)፡ በበጋ ሰዓት ቀን የሚወርድ የደጋ ርጥበት...ብል ።
የጥላ)፡ በቍስል አጠገብ የሚታሰር ዛጐል ሴቴ ሬት ።
የጦም ቈሎ)፡ በፍልሰታ ለካህናት የሚሰጥ ቈሎ፡ ገባር በሑዳዴ ለሹም የሚሰጠው ዱቄት ዕንጨት ጭምር (ስም) ።
የጦር ሹም)፡ ያ፲ ያ፶ የ፫ አለቃ (ሻምበል ባላምባራስ ግራዝማች ቀኛዝማች ፊታውራሪ ደጃዝማች ራስ - "ሻለቃን" እይ) ። ፈረንጆች ሹምን "ጉበርነር" ይሉታል ።
የጦጣ ቍላ)፡ ፍሬው የሚንጣጣ ዕንጨት ።
የጦፈ፡ ጧፍ የኾነ/የነደደ ("ያበደ ሙር") ።
የጨረቃ ቀንድ)፡ ለጋ የጨረቃ ቅርጽ ቀንድ መሳይ ።
የጭ (የዕጭ)፡ ኣክሽ የዲያ ወዲያ አስቀያሚ ጸያፍ ነገር ("በማር ውስጥ ያለ ዕጭ እንዲያሠቅቅ ይህም እንደዚያ ነው ") ።
የጭንጫ፵ አሽከር)፡ ለውጭ ሥራ የሚታዘዝ ያደባባይ አሽከር ።
የፀሓይ ቆብ)፡ ለጽ ድቅ ያይዶለ ለፀሓይ የሚደረግ ማታለያ ቆብ ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈስ ቋት)፡ ምትሀት ያለው የአስማት ድጋም (ባለማቋረጥ ፈስ የሚያስፈሳ ") ።
የፈረስ ስም)፡ አባ ዲና። (ያሚ ስም)፡ በድብቅ የሚነገር (ፈረንጆች "ሶብሪኬ" ይሉታል) ። (ተረት)፡ "ስም ይወጣል ከቤት ይከተላል ጎረቤት"። "ሰየመን" እይ። የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ስም ሲኾን መጨረሻው ሳድስ ፊደል በኃምስነት ይነገራል ። (ማስረጃ)፡ አግርዴ/ኣዝልቄ/ጐንጤ/ደርቤ/ዳኜ/ድያ/ለጥቄ/ፈንጥቄ/ተምትሜ ። በኀላፊ አንቀጽም "በለጤ ዘለሌ" ይላል።
የፈረንጅ አሽከር)፡ ነጭ ለባሽ ሳሕን አመላላሸ ።
የፈናጅራ፡ የመጥፎ ሰው ጠባይ (ከሌ ላው አንድነት ስምምነት የሌለው ") ።
የፈናፍንት፡ የጕዳጕድ ሥራ ።
የፊጥኝ፡ የኋሊት ("ፈጠነ") ።
የፍንጥር፡ ላሻሻጭ የተገዛ መጠጥ ። "ፍንጥር ያሠኘው ርሱን ለመግዛት ወጪ የኾነው ብር ነው" ።
የፍንጫሪ)፡ በደጀ ሰላም ለፍም ጫሪ የሚሰጥ እንጀራ የዳቦ ጕዝጓዝ የተላኪ ወግ አበል ።
የፍየልና የበግ አንዠት ዐለበ ("ዥማት አወጣ አከረረ") ።
ዩ፡ የዜማ ምልክት ።
ዩ፡ ዬ
ዪ፡ (ኢ) የሣልስ ፊደል መሠረት ።
ዪቱ (ዪት/ዊት)፡ የእንስት የሴት መለዮ ።
ያ (መዋያ)፡ ጥበብ/ዕውቀት/ዘዴ/ ብልኀት ።
ያ፡ (አ) ለሩቅ ሴትለሩቆች ለቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽና የዝርዝር አያያዥ ("ፍቺው ርሱ ይኸውም ዐወቀ ያት ያቸው ያችኹ በማለት ፈንታ ራሱን ጐርዶ ዐወቃት ዐወቃቸው ዐወቃችኹ እያለ በርባታ ጊዜ የአንቀጹን መድረሻ ራብዕ ማድረጉን ያሳያል።ያ ስምን አ አካልን ይተረጕማል ስም ንም ከዝርዝር ሲያያይዝ እጃችን እግራችን ቀበሌ ቀበሌያችን ዕድሜ ዕድሜያችን ይላል አንድ ዐይነት ቅጽልንና ስምን ሲያናብብ ገራገር ወንዛወንዝ ያሠኛል") ።
ያ፡ (ዊ) ወገን ቅጽል ።
ያ፡ (ውእቱ) የሩቅ ወንድ በቂና ዐጸፋ ።
ያ፡ (ውእቱ) የሩቅ ወንድ ደቂቅ ቅጽል ይኾናል ("ትርጓሜው እሱ ርሱ ያ ሰው ያ ሲበዛ እኒያ እሊያ ይላል በስፍራው ተመልከት ያችን እይ") ።
ያ፡ (የማ) የትንቢት አሉታ በቂና ቅጽል መነሻ ።
ያ ሌላ፡ ይኸ ሌላ ("ያ ቍቅታ ይኸ ሢጥጥታ ምን ገጥሞት") ።
ያ፡ መዋያ/መገኛ ።
ያ፡ ምእላድ እየኾነ በቃል መጨረሻ ይገባል ።
ያ ቢስ፡ ዕውቀተ ቢስ/ሥራ የለሽ ("አውታታ ከርታታ") ።
ያ ተማደሪያ፡ ሌት ተቀን የሚሠራ ሥራ ።
ያ፡ የቀን ሥራ ("ቁም ነገር") (ኢሳ. ፲፱፡ ፲) ።
ያ፡ የግስ ጣልቃ ።
ያለ (አለ/እንበለ)፡ አለ በገባበት እየገባ ሲነገር ("ያላገባብ ያለደንብ ያለውድ በግድ ያለልክ ያለመጠን ያላቅም ያለፈቃድ ማለቱን ያሳያል ከዚህ የቀረውን በአለ ተራ ተመልከት ዚህና ዚያ ዘርፍ ሲኾኑት ያለ ዚህ ያለዚያ ይላል ፍችውም በአለ ተጽሯል") ።
ያለ፡ (የአለ)፡ ዘሀለወ)፡ ቅጽልና፡ በቂ። ያን፡ ጊዜ፡ በቤት፡ ያለ፡ እደጅ፡ አይውጣ ። (ግጥም)፡ ፈረስ፡ በቅሎ፡ ጭኖ፡ ከሚከተለው፡ እቤቱ፡ ያለውን፡ ይወደዋል፡ ሰው፡ በቂ። እንዲህ፡ ያለ፡ ዘመን፡ ዘመነ፣ ግልምቢጥ፡ ውሻ፡ ወደ፡ ሰርዶ፡ አህያ፡ ወደ፡ ሊጥ፡ ቅጽል።
ያለ፡ (የአለ)፡ ዘብህለ)፡ በቂና፡ ቅጽል። እካስ፡ ያለ፡ ታግሦ፡ እጸድቅ፡ ያለ፡ መንኵሶ፡ በቂ ።እገድል፡ ያለ፡ መጋኛ፡ እበላ፡ ያለ፡ ዳኛ፡ ቅጽል ።
ያለ፡ የሌለ፡ (ዘሀለወ፡ ዘኢሀለወ)፡ የታወቀና፡ ያልታወቀ፡ ጥሩና፡ መናኛ። ዛሬ፡ ፻፩ ሌሊት፡ ሌባ፡ እከሌ፡ ቤት፡ ገብቶ ' ያለ፡ የሌለውን፡ ሰረቀው " ሌለን፡ እይ ።ዳግመኛም፡ ያለ፡ ለጊዜው፡ የነበረ፡ የሌለ፡ ፊት፡ ያልኖረ፡ ማለት፡ ነው፡ (ራእ፲፯፡ ፰፡ ፲፩) ።
ያለ የሌለ፡ የነበረ ያልነበረ ("አለ (ሀለወ)") ።
ያለ፡ የተናገረ፡ አለ ("ብህለ") ።
ያለ፡ የነበረ አለ ("ሀለወ") ።
ያለበሰ ("የሚያለብስ ከዳኝ ሸፋኝ ሸላሚ ዐፈርን እይ አልባሽነት ኣልባሽ መኾን አልብሽኝ ደርቢልኝ ሸፍኚኝ አልብሽኝ አንተርሽኝ የጣጣ ብዛት ሰበብ አስባብ የዛሬ ቀን ባልብሽኝ ባንተርሽኝ መሸ ማልበስ መክደን መሸፈን መከለ ማልበሻ መክደኛ መሸፈኛ የድንኳን መደረቢያ ") ("ዘፀ. ፳፮፡ ፲፬") ።
ያለኸ፡ (የአለኸ)፡ ዘሀለወከ)፡ ገንዘብ፡ የያዝኸ፡ የቋጠርኸ ። (ተረት)፡ ያለኸ፡ ምዘዝ፡ የሌለኸ፡ ፍዘዝ ።
ያለኸ፡ የጩኸትና፡ የምጥንታ፡ ቃል። የሰው፡ ያለኸ፡ የንጉሥ፡ ያለኸ፡ እንዲሉ። የሰው፡ ረዳትነት፡ የንጉሥ፡ ዳኝነት፡ ያለኸ፡ ድረስልኝ፡ ማለት፡ ነው፡
ያለኽ፡ የያዝኽ አለ ("ሀለወ") ።
ያለው፡ የሰው፡ ስም፡ ያዘዘው፡ የተናገረው፡ የፈቀደው፡ የወደደው ።ያለው፡ ሊኾን፡ ያለው፡ ሊኾን፡ ዐሳብ፡ አደቀቀው፡ ጐኔን፡ (ታ ቦት፡ ዘፋኝ)።
ያላለ፡ (የአልአለ)፡ ያልተናገረ። ቅጽልና፡ በቂ፡ ነው።
ያላለያልተናገረ፡ አ ።
ያላበ ("የሚያልብ የሚያወዛ ማላብ ማሞቅ ማውዛት ተላላበ ተቀ መላላብ መቅ አላላበ አጝቀ ማላላብ ማቅ አላላብ አወዛዝ መላብ ላባ የወፍ ያሞራ ጠጕር ልብሳቸው ሲበዛ ላባዎች ያሠኛል በጋልኛ ባሊ' ይባላል ላባም ላባ ያለው ባለላባ ሳባ ላባ በካብ በግንብ ዐጥር ዐሰላ ላይየተተከለ ብረት ሹለትና ስለት ያለው ጠላ ") ።
ያላበቀ ("የሚያላብቅ የሚያጣላ አሳባቂ ማላበቅ ማሳበቅ ማጣላት ማማታት ማጋጨት ማላበቂያ ሐሰተኛ ነገር ሰብቅ ለብቃ በመርሐ ቤቴ ክፍል የሚገኝ አገር ፍል ውሃ ያለበት ወባም ሙቀታም። ለብቃ ኢየሱስ በለብቃ ያለ የኢየሱስ ታቦት አለባበቅ አጐሳሰም መለበቅ ለበሰ ") ("ለብሰ") ።
ያል፡ (የአል)፡ በቂና፡ ቅጽል። ያልተነካ፥ ግልግል፡ ያውቃል፡ በቂ፡ ያልጎደለ፡ ዘማች፡ ያልወለደ፡ ዐማች፡ ቅጽል ።ሰማን፡ ተመልከት ።
ያል፡ በቂና ቅጽል፡ አል ።
ያልተገለጸ)፡ የካባ ቆብ አንካቦ መሳይ - የካባ ቆብ መሰል።
ያልጋ ቍራኛ)፡ የማይለቅ በሽታ ።
ያመራማሪ፡ ላመራመረ የሚሰጥ ገንዘብ።
ያመንኳሽ፡ ካህናት የሚበሉት የቆብ ኣርባ ተዝካር ድግስ።
ያማርኛ ቅኔ፡ መወድስ) ።
ያማታል፡ ምግብ አይስማማትም (ያስ ታውካታል ቅሪት ስለ ኾነች ") ።
ያማች ዳሩ፡ መጨረሻ ("ክፉ ዐማች ") ።
ያም (ውእቱኒ)፡ ም ዋዌ ነው ።
ያም ያም፡ አንዱም አንዱም ።
ያሰነካከለ/የሚያሰነካክል፡
ያሳድግኸ፡ ሽማግሌ ለልጅ የሚሰጠው ምርቃት ።
ያስለፍልፍ፡ ዝኒ፡ ከማሁ፡ ዕፀ፡ ፋርስ።
ያስታራቂ፡ ግብዣ መብል መጠጥ ።
ያስከተለ ("የሚያስከትል አስለጣቂ ጌታ እመቤት አባት እ ናት መምር ማስከተል ማስለጠቅ ማስከተያ ማስለጠቂያ ተከተለ ") (ከተለ) ።
ያስከተበ ("የሚያስ ከትብ የልጅ አባት ዘመድ ማስከተብ ማጻፍ ማስበጣት ማን ተር ማሠንጠቅ ፮፻፺ ኮቲባ ኰተኰተ ማስከተቢያ ማስበጫ ማሠንጠቂያ ተከተበ ") (ተከትበ/ተከስበ) ።
ያሬድ፡ ከዕለት እስካመት በግእዝ ቋንቋ ድጓ የደረሰ የኢትዮጵያ ሊቅ ቅዱስ ካህን ።
ያሬድ፡ የሰው ስም ("ትርጓሜው መውረድ ማለት ነው") ።
ያሻል፡ ያስፈልጋል ።
ያቍራቢ - ላቍራቢ (ለቀዳሾች)፡ የሚ ሰጥ ምሳ ወይም ገንዘብ ።
ያቃባሪ፡ የዝን ንፍሮ ።
ያቃይ፡ የቃጭል መቺ የሰሞነኛ ምድር ።
ያበባ መስቀል)፡ ካበባ የተበጀ የተጐነጐነ እንቍጣጣሽ።
ያባትና የናት ሴቶች ልጆች፡ ወይም ካባት ባንድ ወገን ብቻ የተወለዱ ። (፩ጢሞ ፭ ፥ ፪) ። እት አበባ፡ ያጎት ያክሥት የቤተ ዘመድ ሴት ልጅ መጥሪያ ።
ያቤሎ፡ በሲዳሞ ክፍል ያለ አገር ።
ያቦ ፈረስ)፡ ቀጣኒት ።
ያተኛ (ኞች)፡ ለሰው ሲያርስ፥ሲቈ ፍር፥ሲያርም፥ሲያጭድ፥ሲሸከም፥ሲሠራ የሚ ውል (ማር. ፩፡ ፳) ።
ያቻት፡ ያች ናት አለች ።
ያቻትና፡ ያች እሷ ("ት ናት ና (ናሁ) እንሆ በተገናኝ እንሆ እሷ ናት በሩቅ አለች ያሠኛል") ።
ያች (ይእቲ)፡ የሩቅ ሴት ዐጸፋና " ቅጽል ወይም በቂ ("እሷ ማለት ነው ዋን እይ ያች ትምጣ ያች ትቅር ዐጸፋ ያች ሴት ያች ልጅ ቅጽል ው ሲጨመርበት መኖርን ያሳያል") ።
ያን (ያ/ውእተ)፡ ለሩቅ የነገር ስም የሚነገር ("ገቢር ቅጽልና ዐጸፋ ወይም በቂ ያን ጊዜ ያን ለት ያን ነገር ቅጽል ያን ጥለኸ ያን ያኸላል ያን ውደድያን ጥላ በቂ") ።
ያንቀላፋ ድንጋይ)፡ አረኸ ላይ በቋፍ ያለ የተቀመጠ ድንጋይ፡ ሰው አውሬ ከብት አጠገቡ በደረሰ ጊዜ ወይም እንዲያው አለምክንያት ተፈንቅሎ የሚንከባለል ።
ያንበሳ፡ መደብ)፡ አንበሳ፡ ተዘግቶ፡ የሚኖርበት፡ ስፍራ፡ በብረት፡ የታጠረና የተዘጋ።
ያንበሳ፡ መደብ)፡ የንጉሥ፡ ዐዘቅተ፡ ኵስሕ፡ ጓሮ፡ ቤት።
ያንተ ።
ያንካሴ የወላሴ፡ የልጆች ጨዋታ (ልጆች ፥ አንዳንድ እግራቸውን ዐጥፈው ፥ ያን ካሴ የወላሴ እያሉ ባንድ እግራቸው ያኰ በኵባሉ ") ።
ያንካሴ፡ ያንካሳ ወገን (ወይም ዐይ ነት - የወላሴ የእግረ ምልስ ማለትን ያሳ ያል - "ወለሰን" ተመልከት ") ።
ያኛው፡ ኛው ዝርዝር ምእላድ ነው ("፪ኛውን ኛ እይ") ።
ያክፋይ፡ ላክፋይ የሚሰጥ አንጀራና ወጥ/ዳቦና ጠላ/ሙክት ፍሪዳ ።
ያኸል፡ (ዘየአክል)፡ የሚያኸል፡ ቅጽልና ትንቢት ። ከጥያቄ ጋራ ሲነገር ምን ያኸል ፥ ምን ያኽላል ያሠኛል ።
ያኸል፡ ይሎ
ያኽል፡ የሚያኸል፡ አከለ ።
ያዋዋይ፡ ለዳኛ ስለ ማዋዋል የሚከ ፈል ገንዘብ ("የፍንጥር") ።
ያዋይ በላ፡ ላዋይ የተቀመጠውን የሚ በላ ("ችጋራም ራብ የማይችል ስግብግብ ቅ ልብልብ") ።
ያዋይ፡ በሌማት ውስጥ የሚውል ቍ ራሽ እንጀራ ።
ያው (ያ)፡ እሱ ነው አለ ።
ያውልኸ፡ ዕንካ ውሰደው ።
ያውሬ የጐሽ ውጊያ፡ በስተግራ ወግቶ ወደ ሰማይ ማሽቀንርጠ፡ ወይም ግራ ቀኝ መውጋት መለተም ።
ያውና፡ ያ እሱ ("ው ነው ና እንሆ በተገናኝ እንሆ እሱ ነው (በሩቅ) አለ ና ከናሁ መጥቷል (የባለጌ ግጥም) ያውና እዚያ ማዶ ዛፍ ይወዛወዛል ያንቺ ልብ እንዴት ነው የኔስ ይናውዛል ያውና እዚያ ማዶ ፍሪዳ ተጥሏል ቢላዋው ደንዞ ልብ አልቈርጥ ብሏል ፍሪዳ የተባለው ጌታችን ኢየ ሱስ ክርስቶስ ነው") ።
ያዘ (አኀዘ)፡ አፈፍ ለቀም አደረገ ("ከእጅ አገባ ጨበጠ ተሸከመ ቻለ አገመረ ወሰነ (አፍንጫውን ያዘ) ዐፈነ ደፈነ (በወጥመድ ያዘ) ዐነቀ (በልብስ ያዘ) ታቀፈ (ባፍ ያዘ) ጐረሠ (ልጓም ያዘ) ገታ (መግል ያዘ) ዐቈረ ቋጠረ (ሥጋ ያዘ) ወፈረ (ሥራ ያዘ) ረባ ጠቀመ አገለገለ (ሥር ያዘ) እሥር ገባ ተመለሰ (ዐይን ያዘ) ጨለመ ማየት ከለከለ (ቀለም ያዘ) አጠና ዐወቀ ልብ አደረገ (ቂም ያዘ) በልቡ አሳደረ (ስፍራ ያዘ) ቆመ ተደገፈ ያዘ በነገር ኹሉ እየገባ እንዳመጣጡ መፈታቱን አስተውል (ተረት) ከበሮ በሰው እጅ ያምር ሲይዙት ያደናግር አፍን እይ") ።
ያዝ (አኀዝ)፡ አንሣ ' ጨብጥ ' አን ግብ (መዝ. ፴፭፡ ፪) ።
ያዝ (እኂዝ)፡ መያዝ ።
ያዝ ለቀቅ፡ መያዝ መልቀቅ ።
ያዝ፡ ቶሎ በል ("ንከስ ባላገር ፡ ግ ፡ ጃስ ኵቲ ይላል") ።
ያዝ አደረገ፡ በፍጥነት ያዘ ።
ያዢ/ዥ (ዦች)፡ የያዘ/የሚይዝ ("ተሸካሚ ጨባጭ ገቺ ጐበዝ ያዢ ሲይዘው ብረት ያራል ጠመንዣ ያዥ ሰናድር ያዥ እንዲሉ") ።
ያየር፡ በአየር የሚኖር ጋኔን ፥ ሰይጣን ።
ያየኸ ይራድ፡ የሰው ስም፡ ራደን ተመልከት ።
ያይን ምሳ)፡ አበባ ሥዕል (የሚያምር ፍጥረትና ሥራ ኹሉ) ።
ያይን ምሳ)፡ አበባ ሥዕል (የሚያምር ፍጥረትና ሥራ ኹሉ) ።
ያይን ቆብ)፡ ቅንድብ ሸፋሽፍት ።
ያደግድጉ፡ የወንድና የሴት ስም ።
ያግሉ፡ የሰው ስም "ጠላቶች ይወግዱ ራሳቸውን ያርቁ ማለት ነው።"
ያፈላላጊ፡ ጥቅም ረብ ።
ያፋቺ/የተማቺ፡ ሚስቱን የፈታ ባል፡ ባሏን የፈታች ሚስት ("ኺጂ ልኺድ ያለ ያለች ") ።
ያፍ ሳቻ)፡ ነቀፋ ስድብ ።
ያፍጣጭ፡ ሰዎች ሲበሉ ላፈጠጠ የሚ ሰጥ ምግብ ።
ዬ፡ (ኢ) የማድነቅ ቃል።
ዬ፡ (ኤ) የኃምስ ፊደል ኹሉ መሠ ረት ።
ዬ፡ (ወዮ) የሐዘንና የጸጸት ቃል።
ዬ፡ (ዊ) ባገር ስም መጨረሻ እየገባ ለተወላጅ በቂ ይኾናል ።
ዬ፡ (የ) በራብዕና በኃምስ በሳብዕ ፊደል በሚጨርስ ስም እኔ ለሚል ዝርዝር ።
ዬ፡ ዕሠይ ወሰው እኮ ።
ዬ፡ ወገን ቅጽል ።
ዬ፡ ጊዜ " አንደዬ ዐሥረዬ ።
ዬዬ፡ ወዮ ወዮ ።
ይ፡ (ዊ) ወገን ቅጽል ።
ይ፡ ለሩቅ ወንድ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች የትንቢት የዘንድ የትእዛዝ አንቀጽ መነሻ ።
ይ፡ በለ የሚጨርስ ግስ የሣልስ ቅጽል መድረሻ ።
ይ፡ በትንቢት መነሻ እየገባበቂ ይኾናል።
ይሁዲ (ዐረ)፡ ይሁዳዊ ("የይሁዳ ወግን ወይም ነገድ ነገደ እስራኤል ፈላሻ ግዙር") ።
ይሁዲነት (ይሁድና)፡ ይሁዲ መኾን ("ፈላሻነት") (ግብ. ሐዋ. ፮፡ ፭) ።
ይሁዲዎች፡ አይሁድ ፥ አይሁዶች " አይሁድ ("የይሁዳ ነገዶች እስራኤሎች ፲ሩ ነገድ በያዕቆብ እስራኤል እንደ ተባሉ በይሁዳም አይሁድ ተብለዋል") (አስቴ. ፫፡ ፮፡ ዮሐ. ፩፡ ፲፱) ።
ይሁዳ (የሀደ)፡ የሰው ስም ("ካቱ ነገደ እስራኤል አንዱ ትርጓሜው ኦኒ (አማኝ) ማለት ነው ሌሎችም በዚህ ስም የሚጠሩ ሰዎች አሉ ይሁዳ የጌታችን ወንድም ይሁዳ አስቆሮታዊ እንዲሉ") ።
ይህ (ዝ)፡ የቅርብ ዐጸፋና ጭብጥ ቅጽል ።
ይሕ፡ ይበሉ ሕዝብ (ቅዳሴ) ።
ይህታ (ይህችታ)፡ ታን ተመልከት ።
ይህች (ይህ)፡ ለቅርብ ሴት ዐጸፋና ቅጽል ።
ይህነን፡ ዝኒ ከማሁ ("ይኸንን ተመል ክት") ።
ይህን፡ የገቢር ቅጽል ።
ይለፍ፡ ኬላውን ይውጣ (አይከልከል ") ።
ይሉኝ፡ (ይብሉኒ)፡ ያኹን፡ ትንቢት፡ አንቀጽ። ደግ፡ ብሠራ ' የጠሉኝ፡ ክፉ፡ ባደርግ፡ ምን፡ ይሉኝ።ገቢኸን፡ ስታውቅ፡ ይሉኝ፡ አትበል ።ይሉኝ፡ አይል፡ ሐሜት፡ የማይፈራ፡ ከይሉኝ፡ ኣይል፡ ዐይብ፡ ኣትብላ፡ ኣይመረው፡ አይተኵሰው፡ ውጦ፡ ውጦ፡ ይጨርሰው። እንዲሉኝ፡ ሊሉኝ፡ ይሉኝ፡ ዘንድ፡ እያለ፡ በሣልሳይ፡ ኣንቀጽ፡ ይገባል ።
ይሉኝ፡ በቁሙ፡ አለ ("ብህለ") ።
ይሉኝተኛ፡ ባለይሉኝታ።
ይሉኝታ፡ ረቂቅ፡ የነገር፡ ስም፡ (ምሳ ፫፡ ፬)፡ እንዲህ፡ ይሉኛል፡ ማለት። ትዝብትን፡ ሐሜትን፡ ነቀፌታን፡ መፍራት። ይሉኝታ፡ የራስ፡ ዐሊን፡ ቤት፡ የፈታ። ይሉኝታና፡ መጠቀም፡ ባንድነት፡ አይገኝም። ይሉኝ፡ የነገር፡ ስም፡ መኾኑ፡ ታ፡ በምእላድነት፡ ስለ፡ ተጨመረበት፡ ነው።
ይሉኝታ፡ በቁሙ አለ ("ብ ህለ)") ።
ይሉኝታ፡ ቢስ፡ ግድ፡ የለሽ፡ ይሉኝ፡ ኣይል " አለና፡ ባለ፡ አንድ፡ አንቀጽ፡ ስለ፡ ኾኑ፡ አስደራጊውንና፡ ተደራጊውን፡ ተደራራጊውን፡ አደራራጊውን፡ በባለ፡ ተራ፡ ተመልከት ።ትእዛዙንም፡ ከበለ፡ ይወስዳል።
ይላሉ ። በግእዝ፡ ኰራኪ፡ ይባላል፡ ዳግመኛም፡ ስለ፡ እግሩ፡ ረዥምነት፡ ሽመላ፡ ይሉታል። እሱም፡ ካ፲፭፻፡ ዓ፡ ም፡ በፊት፡ አሜሪካን፡ ያውቃል ።ሽመላን፡ እይ ።
ይላማ (ዐላማ)፡ ምልክት ("ወርውረው የሚወጉት ተኵሰው የሚመቱት ነገር ጊጤን እይ") ።
ይል፡ ይናገር፡ የጊዜ፡ ትንቢት፡ ነው፡ ይላል (ይል፡ አል)፡ (ይብል፡ ሀለወ)፡ ይናገራል፡ ይመታል ።
ይልማ፡ በምንዝ ውስጥ ያለ ቀበሌ ("የጠይቦች ጎዳም የሚገኝበት ህለ)") ።
ይልማ፡ የሰው፡ ስም፡ ይርባ፡ ይብዛ፡ ማለት፡ ነው ።
ይልማና፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር ።
ይልቅ፡ ይበልጥ ላቀ ።
ይልቅ፡ ይበልጥ፡ እጅግ፡ ("ማሕ. ፩፡ ፬")፡ ይልቅስ፡ ስ፡ አፍራሽ፡ ነው፡ የሚበልጥስ፡ የሚሻልስ ።
ይሎ፡ የጣራ ማዋቀሪያ ረዥም አጣና ("ተለብልቦ የተላጠ ተራዳ ") ።
ይመናሹ፡ የሴት ስም፡ ወንዶች ባንቺ ላይ ይዋጉ ማለት ነው።
ይመናሹ፡ ይዋጉ፡ መንሽ ።
ይመኙሻል፡ የሴት ስም።
ይማማ (ዐረ፡ ዒማማ)፡ የይማሞቶ ጥምጥም ።
ይማም (አመመ/ቀደመ/ሀረ ዐመመ/ጠመጠመ)፡ የስላም ስም ("ግንባር ' ቀደም ካህን ማለት ነው ባላባትነት ንም ያሳያል") ።
ይማሞች፡ ግንባር ቀደሞች ዋኖች ("የወሎ ባላባቶች") ።
ይማና፡ ያደራ ገንዘብ፡ አመነ ።
ይሰበር ደጋኔ)፡ ከባሕር የመጣ ቀጪን ድር።
ይሣቅ (ይሥሐቅ)፡ (ዘፍ. ፳፩፥፫, ፮) የሰው ስም (ያብርሃም ልጅ የያዕቆብ አባት እናቱ ሳራ ካረጀች በኋላ ስለ ወለደችው ሰው ኹሉ ይገረም ይሣቅ በማለቷ በዚህ ስም ተሰየመ ይባላል) ።
ይስሙላ፡ ተሰምቶ የማይፈጸም ነገር (ፍችውም ይስሙላት ማለት ነው) ።
ይስማ ሰራዪት፡ በሠራ አካላት ላይ ግልብጥ ብሎ የሚታይ ቂጥኝ።
ይስገዱ፡ የወንድና የሴት ስም።
ይራድ (ይርዐድ)፡ ይፍራ, ይንቀጥቀጥ. "ወንድ ይራድ, ያየኽ ይራድ እንዲሉ" - "ወንድ ይራድ, ያየኽ ይራድ እንዲሉ".
ይርጋ፡ የሰው ስም ።
ይርጋ፡ የንጉሥ ዐዋጅ ። "መሬት በያዘው ሰው እጅ ይኑር አይወሰድ ማለት ነው" ።
ይቅር ባይ፡ ማሪ ሰላማዊ ። ይቅር ተባለ፡ ታረቀ ሰውየው፡ ተተወ ጥሉ ።
ይቅር ተባባለ፡ ተጐናበሰ ተራረቀ ተሳሳመ ተሰማማ ።
ይቅር፡ ትእዛዝ አንቀጽ ። "ይቅር ለግዜር፡ ይቅር ላንተ፡ ቂሙ አይያዝ አይታሰብ ማለት ነው" ።"በአንተ ፍቅር በስመ አብ ይቅር እንዳለ ሰይጣን" ።
ይቅር አለ፡ ጠላቱን ማረ፡ ቍርሾውን ተወ ከልቡ ፋቀ አጠፋ ።
ይቅር አሠኘ፡ አስታረቀ ።
ይቅር፡ ይተው፡ ቀረ ።
ይቅርታ፡ ይቅር ማለት፡ ምሕረት ዕርቅ ("(መዝ. ፻፴፥ ፬)") ።"ከማስቀመጥ ስጦታ፡ ከቂም ይቅርታ" እንዲሉ ።
ይቅርታ ጠየቀ፡ "በድያለኹ ልካስ፡ ቀምቻለኹ ልመልስ አለ" ።
ይቆን፡ የጋኔን ስም ("ደቂቀ ሴትን ያሳተ ሰይጣን") (ሔኖ. ፲፱፡ ፲፯) ።
ይበል፡ ይናገር፡ ባለ ።
ይበጃል፡ ይሻላል፡ ይኾናል። ይበጃል ያሉት አይበጅም ።
ይበጅ፡ ያድርግ፡ ይበጅ ያድርግ፡ ያደርግ ዘንድ ይገባ ።
ይባዝ፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ ።
ይብላኝ (ይብልዐኒ)፡ የሐዘንና የትካዜ የጸጸት ቃል፡ ንኡስ አገባብ ። ይብላኝ ለሞተ እንዲሉ ።
ይብላኝ፡ በቁሙ፡ በላ ።
ይብላኝለት፡ በማቹ ፈንታ እኔን መሬት ይብላኝ ማለት ነው ።
ይብስ፡ ቅጥራን ("የቅጥራን ዐይነት") ።
ይብረኹ፡ የወንድና የሴት ስም፡ ይስገዱ ማለት ነው ። አቶ ይብረኹ እመት ይብረኹ እንዲሉ ።
ይብራ
ይብራ፡ የውሃ ዶሮ ("እውሃ ውስጥ ጠልቃ የምትወጣ እግረ ቀይ መልከ ብዙ") (ዘሌ. ፲፩፡ ፲፰) ።
ይብጀው፡ ይሻለው ። እሳት ለፈጀው ምን ይብጀው ።
ይብጅኽ፡ አይዞኸ አትፍራ ።
ይተጌ (እኅተ ሐፄጌ)፡ እተጌ ("ንጉሥ እቴ የምትላት ሚስቱ ጣምራው የንጉሥ ባልተ ቤት ይተጌ ጣይቱ ይተጌ መነን ይተጌ ሰብለ ወንጌል እንዲሉ ሲበዛ ይተጌዎች ይላል") ።
ይታክቱ፡ የወንድና የሴት ስም ። ታካች (ቾች)፡ የታከተ/የሚታክት ሰነፍ (ምሳ. ፮፡ ፮, ፴) ።
ይታገሡ፡ የወንድና የሴት ስም።
ይቶት (እኅት)፡ ሴት ስትመነኵስ የምትጠራበት ስም ("የፍቅር የሃይማኖት የማ ይቶት ኅበር እት ማለት ነው ዳግመኛም እመ እማሆይ ትባላለች በግእዝ ቋንቋም መነኵ") ።
ይች/ቺ፡ ይህችን ተመልከት ።
ይችው፡ በቅርቡ አለች ።
ይችውና፡ እንሆ እዚሁ አለች ።
ይኑር፡ ይቀመጥ/ይቈይ/ይዘግይ (ዕድሜው ይብዛ - "ይኑር ዘለዓለም እከሌ ኣብርሃም" እንዲሉ ካህናት) ።
ይናዱ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም ("ጠላቶች ይሽሹ" ማለት ነው) ።
ይንበርበሩ፡ የሰው ስም፡ በረ ።
ይንበርበሩ፡ የሰው ስም፡ ጠላቶች ይበርበሩ ይወረሩ ይዘረፉ ማለት ነው ። አንበረበረና ተንበረበረ ከዚህ ቀደም አልተለመደም ። ዳግመኛም እንበለበለና ተንበለበለ በማለት ፈንታ የተነገረ ነው ሊባል ይቻላል ።
ይካ፡ ይበል ካህን (ቅዳሴ) ።
ይኸ (ይህ)፡ የይህን አፈታት ተመ ልከት ("ለማናበብና ሌላ ፊደል ለመጨመር ይህ፥ ይኸ ተብሏል") ።
ይኸን (ዘንተ)፡ የገቢር ቅጽል ።
ይኸው፡ ው የነው ከፊል ነው ("ይኸ ፥ ነው አለ ያሠኛል ሲዘረዝርም ይኸውልዎ ይኸው አለልዎ ይኸውለት ይኸው አለለት ይኸውልሽ ይኸው አለልኸ ይኸውልሽ ይኸው አለልሽ ይኸውላቸው ይኸው አለላቸው -") ።
ይኸውላት፡ ይኸው አለላት ይላል ።
ይኸውላችኹ፡ ይኸው አለላችኹ ።
ይኸውና፡ እንሆ ይኸ አለ ("እንሆ የተባለው ና ከግእዛዊ ቃል ከናሁ የተከፈለ ነው") ።
ይዋይብኸ፡ የርግማን ቃል ("ዋይ ይባ ልብኸ ይለቀስብኸ") ።
ይዋጣለት፡ ኀይሉ ይታወቅለት/ይለይ ለት/ይባባል/ይሸናነፍ ።
ይዘታ (ዎች)፡ የተያዘ ("በጅ ዐደር ነገር") ።
ይዘት (ቶች)፡ እኅዘት) መያዝ ("የዜማ ምልክት አንዲት ነጥብ() የንባብ ማጥበቂያም ትኾናለች መዝገበ ፊደል እይ ነገር") ።
ይደነቃል፡ የሰው ስም ።
ይዲ፡ ይበል ዲያቆን (ቅዳሴ) ።
ይድረስ (ይብጻሕ)፡ የደብዳቤ'የመ ልክት አርእስት ("ይቅረብ ማለት ነው") ።
ይድረስታ፡ ይድረስ ፥ ማለት ("አድራሻ") ።
ይድነቃቸው፡ ዝኒ ከማሁ ("ይግረማቸው ማለት ነው") ።
ይድኖ፡ ከዠማ በስተግራ ያለ አገር ስም ።
ይገም፡ የወረዳ ስም (በመንዝ ክፍል ያለ ቀበሌ - "ይሳብ ይምጠጥ" ማለት ነው - ዐገ መና ገመጠ ባማርኛ ይገጥማሉ - "(ተረት)" - እከሊት ስለ ሞተች ሰዎች ይገምጧት ወጡ ") ።
ይገባል (ብዉሕ መፍትው ርቱዕ ይደሉ)፡ ሰውን ከማመን እግዜርን ማመን ይገባል (ይሻላል) ።
ይገባል (ይትገባእ ሀሎ)፡ መግባት ይቻላል ።
ይጋርዱ፡ የሴት ስም ።
ይግለጡ፡ የሰው ስም "ጠላቶች መንገድ ይልቀቁ ማለት ነው።"
ይግባኝ፡ ወደ በላይ ዳኛ ይግባልኝ ይሰማልኝ ።
ይግባኝ፡ ይሰማልኝ፡ ገባየጕድፍ፡ በቁሙ፡ ጐደፈ ።
ይግባኝታ፡ ይግባኝ ማለት፡ ምጥንታ አቤቱታ ።
ይግባኞች፡ አቤቱታዎች ።
ይጠቅመኛል፡ ያጠግበኛል/ይበቃኛል ።
ይጣ፡ ቀበሌ፡ ዐጣ ።
ይጣ፡ በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ ("ይባዝን" ተመልከት ") ።
ይጣ፡ የሩቅ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ ፲ አያግኝ ።
ይፋ (ኦሮ፡ ኢፋ፡ ብርሃን)፡ ግልጥ ስውር ያይዶለ ነገር ።
ይፋታዊ፡ የይፋት ማለት ነው ።
ይፋት፡ በሺዋ አውራጃ ያለ እፃር ።
ይፋቶ፡ የገብስ ስም ።
ይፋቶች፡ የይፋት ሰዎች ("የይፋት ተወ") ።
ይፋግ፡ በበጌምድር ከቃሮዳ በታችያለ አገር ።
ይፋግ፡ በበጌምድር ክፍል ያለ አገር ።
ይፍቱኝ፡ "እግዜር ይፍታ" (የተና ዛዥና ያናዛዥ ቃል ") ።
ይፍጀው፡ ያቃጥለው ይጨርሰው ይቻ ለው ። "ሆድ ይፍጀው" እንዲሉ ።
ዮ፡ (ሆይ) ንኡስ አገባብ ("የአንክሮና የአጋኖ የአክብሮ ቃል። ሰውዮ ሴትዮ ") ።
ዮሐንስ (ጽርእ)፡ የሰው ስም ("በዕ ብራይስጥ ዮሐናን ይባላል ትርጓሜውም እግዜር ምሕረቱን ሰጠ ማለት ነው ዳግመኛም ደስታ ተብሎ ይተረጐማል") (ሉቃ. ፩፡ ፲፫, ፲፬) ።
ዮሐንስ ቅድ)፡ ዐጤ ዮሐንስ ይታጠቁት የ ነበረ ሱሪ ።
ዮር፡ ከፊለ ስም፡ ዮርዳኖስ ።
ዮር፡ የዮርዳኖስ ከፊል ።
ዮርዳኖስ፡ የወንዝ ስም ("ከላይ ፫ ከታች ፩ የኾነ ዠማ ጌታችን የተጠመቀበት ትርጓሜው የዳን ወንዝ ማለት ነው ይላሉ") ።
ዮሽ፡ የነገር ትራስ ።
ዮቅጣን
ዮቅጣን፡ የሰው ስም ("የዔቦር ልጅ ዘሩ ቀጠነ ነው") (ዘፍ. ፲፡ ፳፭-፳፱) ።
ዮናኤል፡ የመልአክ ስም ("ርግበ አምላክ ማለት ነው") (ገድ. ኪሮ) ።
No comments:
Post a Comment