Friday, June 6, 2025

 

: ፯ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ። በአኃዝነት ዘ፯፣ በፊደልነት ዛይ ይባላል።

: በቂ። ከታቦት ስም እየተናበበ፡ ገብረ፣ ወልደ፣ ተክለ፡ በማለት ፋንታ፡ ዘገብሬል፣ ዘወልዴ፣ ዘሚካኤል፣ ዘማሪያም፣ ዛማኔል፣ ዘመንፈስ፣ ዘሴ እያለ የክርስትና ስም ይኾናል። ይኸውም ከግእዝ የመጣ ነው።

: የደ ወራሽ። ደፈቀ ዘፈቀ።

ዘኅነን/ዝኅንን (ፐፒራ) ምንጭርር የሚባል ሐረግ ሲሆን የሥሩ ዱቄት ነው።

ዘኅነን/ዝኅንን (ፐፒራ) ምንጭርር የሚባል ሐረግ ሲሆን የሥሩ ዱቄት ነው።

ዘህነን የቀለም ዱቄት፡ ዘኅነን።

ዘለለ (ዘሊል፣ ዘለ፣ ቀነጸ፣ አንፈርዐጸ) ናረ፡ ነጠረ፡ ጓነ፡ መር አለ፡ ፈረ (2ሳሙ 6:17)

ዘለለ (ዘልሐ ዐጸረ): ውሃ ጨመረ፡ መላ፡ ጠመቀ፡ በጠበጠ፡ አቦካ።

ዘለለ: ተወ፡ ዐለፈ፡ ተራመደ።

ዘለለ: አሳረፈ፡ ዘረጋ፡ ዘረረ። (ለናና ተወራራሽ ስለሆኑ፣ በዘለለ ፈንታ ዘለነ ይላል)

ዘለለ: አደገ፡ ከፍ አለ፡ ላቀ፡ በለጠ፡ ዘለግ አለ።

ዘለላ (ዎች): ፍሬዎች ያሉባት አንዲት ዐረግ። (ዘፍ 40:10 ዘኍ 13:23-24)

ዘለላ: አንድ ጊዜ የወረደ እንባ።

ዘለሌ: ዘለለው (የሰው ስም)"በለጤ በለጠው" ማለት ነው። ዘለሌ ለወንድና ለሴት ሲሆን፣ በለጢ ግን ለሴት ብቻ ይነገራል። (በለጠን የሚለውን ተመልከት።)

ዘለል (ሎች): የዘለለች። "አጕራ ዘለል ጥዶ ዘለል" እንዲሉ።

ዘለል አለ: ከፍ አለ፡ ላቀ።

ዘለል: መር፡ ላቅ፡ በለጥ። "አለል ዘለል" እንዲሉ።

ዘለልታ: ዝኒ ከማሁ። (አለለን የሚለውን ተመልከት።)

ዘለመ (ዐረ፣ ከዳ፣ ካደ፣ ሸፈጠ): ወለመ፡ ጠመመ፡ ጠማማ ሆነ።

ዘለም አለ: ወለም ጠመም አለ።

ዘለሰ (ዘለፈ): ቈረጠ፡ ቈጠቈጠ፡ መለመለ፡ አወደቀ፡ ቀለሰ፡ አስተኛ፡ አጋደመ፡ ለሸለሸ (የደን)

ዘለሠ: አስተኛ።

ዘለሰ: አቀረቀረ (ዐንገቱን)፡ አዘነበለ።

ዘለሰኛ: የመሰንቆ ምት ባለኹለት ግጥም፡ ረገብ አድርጎ የሚዜም። "ትሰሙ እንደኾን የወንጌል ቃል፣ አለመስጠት ያጸድቃል። "

ዘለሳ: ቈረጣ፡ ቍጥቈጣ፡ ምልመላ።

ዘለሳ: የወዘፍ ዐጥር።

ዘለሳ: ዳስ፡ የዳስ ዐይነት፡ ማስቀመጫ የመሰለ ሰቀላ።

ዘለስ: ተደራርቦ የወደቀ ቅርንጫፍ፡ ዐጽቅ ቅጠል።

ዘለስላሳ: የሚዝለሰለስ፡ ዘለፍላፋ፡ ቀለስላሳ።

ዘለቀ (ዘለገ): መጣ፡ ገባ፡ ጠለቀ፡ ጥልቅ ሆነ።

ዘለቀ: ቈየ፡ ሰነበተ። "አይዘልቅ ጸሎት ለቅሥፈት። "

ዘለቀ: በሳ፡ ነደለ፡ ዐለፈ፡ ኼደ፡ ራቀ።

ዘለቀ: ብቅ አለ፡ ታየ (2ነገ 6:26)

ዘለቀ: አነበበ፡ ወጣ፡ ፈጸመ፡ ጨረሰ።

ዘለቀ: የሰው ስም።

ዘለቃ ወጋ: በስተዠርባ ወጣ (የጦሩ ውልብልሲት)

ዘለቃ፣ ዘለቄታ: ፍጻሜ፡ መጨረሻ።

ዘለቃ ጦር: ጨርሶ ወግቶ ከነሶማው ሾልኮ የሚኼድ።

ዘለቃ: የወንድና የሴት ስም። "አቶ ዘለቃ" "እመት ዘለቃ"

ዘለቅ አለ: ገባ አለ፡ አራሰ።

ዘለቅ: መዝለቅ።

ዘለበት (ቶች): የፈረስ ወይም የበቅሎ ዕቃ፡ የቀበቶ፣ የሠቅ፣ የዝናር ማጋጠሚያ ብረት። (ምላስን የሚለውን ተመልከቱ።)

ዘለባበደ: ነገር ለዋወጠ፡ ንግግሩ ወይም ቃሉ ዕሥሥትኛ ሆነ (የተዘበራረቀ)

ዘለባብዳ: ዕሥሥት (መዘባረቅ)

ዘለብ (ዘነብ): ጅራት። ለምሳሌ: "አቡነ ዘለብ" እንዲሉ።

ዘለነ: አጐዳኘ፡ አዛወረ (የማደሪያ፣ የመንጋ) (2ኛውን ዘለለ የሚለውን ተመልከት።)

ዘለንጋ (ጎች): በያይነቱ ዕቃ ማስቀመጫ ቆጥ፡ እንደ መንበር ሆኖ የተሠራ፡ በጭቃ ተመርጎ በበት የተለቀለቀ፡ 2 እና 3 ረድፍ ያለው። (ዘሩ ዘለገ ነው፡ ምጭጭትን ተመልከት።)

ዘለዘለ (ዘረዘረ): ሠነጠቀ፡ ሸነሸነ፡ አቀጠነ፡ አረዘመ (የሥጋ) (ዘለለን የሚለውን ተመልከት፡ ሥሩ እሱ ነው።)

ዘለዘለ: በጣም ነከሰ፡ ዘነተረ።

ዘለዘል፣ ዘልዛላ፣ ዘልዘልቱ: የተንዘለዘለ፡ ሐግ ያልተባለ፡ መረን፡ ስድ፡ አግድሞ አደግ፡ ዘዋሪ፡ ወሮበላ፡ እንዛዝላ።

ዘለገ (ዘለቀ): ረዘመ፣ አደገ፣ ከፍ አለ።

ዘለግ አለ: መለል አለ።

ዘለግ ያለ: የረዘመ። (1 ሳሙ 9:2)

ዘለግተኛ: ከፍተኛ፣ ቁመታም።

ዘለግታ: ዘለግ ማለት፣ መርዘም፡ መለልታ፣ ከፍታ። (1 ሳሙ 16:7)

ዘለጐሰ (ዘልገሰ፣ ቈሰለ): ጥፋትን ዘለለ፡ ገደፈ፡ አበላሸ፡ አላገባብ ጻፈ።

ዘለፈ (ዘሊፍ ዘለፈ): ገሠጸ፡ ወቀሠ፡ መከረ፡ ነቀፈ፡ ሰደበ (ዘፍ 21:25 2ሳሙ 3:8 ሚል 3:11)

ዘለፈ: ዘለሰ፡ አዘነበለ።

ዘለፋ: ግሠጻ፣ ነቀፋ፣ ስድብ፡ ምክር።

ዘለፍ አለ: ዘንበል አለ፡ ተጐነበሰ።

ዘለፍ አደረገ: ዐንገቱን ደፋ፡ አዘነበለ። "ጌታችን ነፍሱ በወጣች ጊዜ ራሱን ዘለፍ አደረገ። "

ዘለፍላፋ: የሚዝለፈለፍ፡ ደካማ፡ ልል።

ዘለፍላፌ: የዘለፍላፋ ወገን፡ ዐይነት።

ዘሊል: ሰነፍ፡ የሰንበት እበት። "ሊል ዘሊል" እንዲሉ። (ሊልን የሚለውን ተመልከት።)

ዘሊሞ: የዛፍ ስም፡ ጠማማ ዕንጨት።

ዘሊቅ: ዝኒ ከማሁ።

ዘሊቅ: የሰው ስም።

ዘሊቦ (ዝሉፍ): ወራዳ፣ ልፍስፍስ።

ዘላለለ: ጨፋፈረ፡ መር መር አለ።

ዘላለማዊ: የዘላለም፡ እግዚአብሔር።

ዘላለም (ዘለዓለም): ፍጻሜ፣ መጨረሻ የሌለው ጊዜ፣ ዓመት፣ ዘመን። (ፍጻሜ ላለውም ይነገራል) "እከሌ በደንጊያ ብቻ የዘላለም ቤት ሠራ። " በግእዝ ግን (ዘለዓለም) የዘላለም ማለት ነው።

ዘላለምነት: ዘላለም መሆን፡ መኖር።

ዘላለፈ: ገሣጸጸ፡ ነቃቀፈ፡ ተቈጣጣ።

ዘላላ: ዝኒ ከማሁ።

ዘላሌ: የዘላላ ወገን።

ዘላሳ: ወደ ታች የተመለሰ፡ ቀላሳ፡ ቀንድ።

ዘላሽ (ሾች): የዘለሰ፣ የሚዘልስ፡ ቈራጭ፡ ቈጥቋጭ።

ዘላቂ: የዘለቀ፣ የሚዘልቅ፡ ጠላቂ፡ ገቢ ጦር፡ ቅባት።

ዘላበደ (ለበደ): ወላበደ፣ ወላወለ፣ ቃል ለወጠ፣ ቀላመደ (አላዋቂነት ማውራት)

ዘላባጅ (ጆች): ወላባጅ፣ ወላዋይ።

ዘላን (ኖች): በዱር በበረሓ ከብት እያረባና እየጐዳኘ የሚኖር ሕዝብ።

ዘላንነት: ዘላን መሆን።

ዘላይ (ዮች): የዘለለ፣ የሚዘል፡ የሚጨፍር፡ የሚያልፍ፡ ዐላፊ፡ ጨፋሪ።

ዘላይ: ዘለላን የሚዘልል፡ የሚጠምቅ፡ ጠማቂ፡ በጥባጭ (ጠላን፣ ጠጅን)

ዘላጋ: ረጅም፣ መለሎ።

ዘላፊ (ፎች): የዘለፈ፣ የሚዘልፍ፡ የሚገሥጽ፡ ነቃፊ (ኢዮ 40:2)

ዘላፊ: ዘላሽ።

ዘል መንዘል አለ: ወዳንድ ፊት ደፋ።

ዘልስ: የፈረስ ስም። "አባ ዘልስ" እንዲሉ።

ዘልባዳ: ሁለት ምላስ ያለው፣ ቀልማዳ (አፉ ያልተስተካከለ)

ዘልዘል አለ: ተንዘለዘለ።

ዘልዛላነት: ዘልዛላ መሆን፡ መረንነት።

ዘልዛይ (ዮች): የዘለዘለ፣ የሚዘለዝል፡ አጥብቆ ነካሽ።

ዘልዳ: የልዳ ከተማ ሰው።

ዘልጓሳ፣ ዝልጕስ: የተዘለጐሰ፡ ብላሽ መጽሐፍ፡ አላዋቂ የጻፈው።

ዘልጓሽ: የዘለጐሰ፣ የሚዘለጕስ፡ ገዳፍ።

ዘሎ ባይኔ: ዐይነ ውሃ፡ የውሃ ዐይን፡ ወይም እንክብል።

ዘሎ ባይኔ: ውሃና መስተዋት መሳይ ትልቅ ዶቃ፡ መካከሉ ተረተርማ የሆነ፡ አምሮ ስለሚታይ "ዘሎ ባይኔ" ተባለ።

ዘሎ ገባ: ጌታውን ትቶ ሌላ ሰው ቤት የገባ፡ ዘው ያለ ውሻ።

ዘሎ: ትቶ፡ ዐልፎ፡ ንሮ፡ ነጥሮ።

ዘመላክ: ዘመልአክ፡ የክርስትና ስም።

ዘመመ (ዘሚም፣ ዘመ): ዘነበለ፡ ጋደለ፡ በዘንግ ወይም በመቋሚያ ምድርን በመድቃትና በመውጋት አዜመ።

ዘመመ: ከለከለ፡ ዝም አሰኘ።

ዘመመ: ዝማም ሠራ፡ አገባ።

ዘመመ: ደረደረ፡ ከመረ፡ ጐቸ ሞላላ አድርጎ።

ዘመመን: ሞላላና ዥልጥ ጕቾ ድርድር።

ዘመሚት (ቶች): ቀይ የደጋ ምሥጥ፡ ደም የሚመስል። እሱ የበላው እንጨት ስለሚዘም ዘመሚት ተባለ።

ዘመም (ዘሚም): መዝመም።

ዘመም አለ: ዘንበል አለ።

ዘመስ: ዝኒ ከማሁ (ራእ 14:9)፡ ትርጓሜ።

ዘመረ (ዘምሮ፣ ዘመረ): ዝማሬ ቃኘ፡ በገና መታ፡ ደረደረ፡ ዳዊት አዜመ፡ ምስጋና አቀረበ። (ዠመረን እይ፡ የዚህ ዘር ነው።)

ዘመር: የሐሳዊ መሲሕ ስም፡ አጭር ምልክት።

ዘመተ (ትግ፣ ዘመተ፣ ዘረፈ፣ ቀማ): ወደ ጦርነት፣ ወደ ውጊያ ኼደ፡ ለመግደል፣ ለመውረር፣ ለመዝረፍ፣ ለመቀማት።

ዘመቻ ፈሪ: ዘመቻን የፈራ፡ የሚፈራ።

ዘመቻ: የውጊያ ጕዞ፡ ወይም ግስገሳ።

ዘመቻ: ጠብ፡ ጥል፡ ግድያ፡ ውጊት፡ ዘረፋ፡ ቅሚያ።

ዘመነ ሐዲስ: የወንጌል ዘመን።

ዘመነ ሰማዕታት: የዲዮቅልጥያኖስ ጊዜ፡ ሰማዕታት መከራ እየተቀበሉ የሞቱበት። (ዓመትን ተመልከት።)

ዘመነ ሥጋዌ: ጌታችን ሥጋ የለበሰበት፡ ሰው የሆነበት ጊዜ፡ ከዚያም ወዲህ ያለው ዓመት። (ዘበንን እይ፡ ዘመን የግእዝ፡ ዘበን የአማርኛ ነው።)

ዘመነ ብሉይ: የኦሪት ዘመን።

ዘመነ እንኰዬ: እንደ ልብ የሚበሉበት፡ የሚጠጡበት የጥጋብ ጊዜ።

ዘመነ ግልምቢጥ: የግልብጮ ዘመን፡ እውነት የጠፋበት፡ ሐሰት የሠለጠነበት ጊዜ።

ዘመናይ (ዮች)/ዘመናዊ: ዘበናይ፡ ባለጊዜ።

ዘመናይ ማርዬ: የዘፈን አዝማች።

ዘመን (ኖች): ረዥም ጊዜ፡ ብዙ ዓመት።

ዘመን አመጣሽ: ዘመን ያመጣው፡ የወለደው ዘፈን፣ ልብስ፡ ወይም ሌላ ነገር።

ዘመንፈስ: የክርስትና ስም።

ዘመወ: አመነዘረ፡ ሴሰነ፡ ቀነዘረ።

ዘመዘመ (ዐረ፣ ዘምዘመ): አገደ፡ ከተረ።

ዘመዘመ (ዘመመ): ሰፋ፡ ጠቀመ፡ ቀመቀመ፡ ጠለፈ፡ አስጌጠ (የበርኖስ፣ የቀሚስ ዐንገትጌን፣ ያዝራር መግቢያን)

ዘመደ (ዘሚድ፣ ዘመደ): ወለደ፡ ዘመድ አደረገ፡ ወገነ፡ ቀላቀለ ደምን ከደም።

ዘመዳም (ሞች): ባለዘመድ፡ ዘመደ ብዙ።

ዘመዴ: የኔ ዘመድ። (ወዳደ፣ ወለደ ብለህ ወዳጅን፣ ልጅን አስተውል)

ዘመድ (ዶች): ተወላጅ፣ ዘር፣ የአባትና የእናት ወገን (ቅርብና ሩቅ)፡ አንድ ቤት፣ ሁለት ቤት፣ ሶስት ቤት፣ አራት ቤት፣ አምስት ቤት፡ ከዚህም በላይ ያለ ቤተዘመድ።

ዘመድ ኹን: የሰው ስም።

ዘመድ ዘር: ቃሉ ከአባት ዘር ያልተለየ፡ በሥሩ ባዕድ፣ በጫፉ ምእላድ ያልጨመረ ስም ወይም ጥሬ። ይህም "ዘለቀ" ብሎ "ዘለቃ""ዘመተ" ብሎ "ዘመቻ" ማለቱን ያሳያል።

ዘመድ ገዛ: ወዳጅ አበጀ፡ ወገን አበዛ።

ዘመድነት: ዘመድ መሆን።

ዘሚካኤል: የክርስትና ስም፡ ገብረሚካኤል ወልዶ ሚካኤል ማለት ነው። ባላገር ግን "ዘሚኻዬል" ይላል።

ዘሚካኤል: የክርስትና ስም። ገብረሚካኤል ወልዶ ሚካኤል ማለት ነው። ባላገር ግን "ዘሚኻዬል" ይላል።

ዘማ: አመንዝራ ሴት (ዘመወ)

ዘማ: ጋለሞታ፡ አመንዝራ ሴት፡ ሽርሙጣ፡ ኻያጅ።

ዘማሚ (ላማ): የሚዘም፡ የሚያዜም ካህን፡ ደብተራ፡ ዘንባይ።

ዘማሚ (ጥማ): የሚዘምም፡ ደርዳሪ፡ ከማሪ።

ዘማሪ (ዎች): የዘመረ፣ የሚዘምር፡ በገና መቺ፡ ደርዳሪ።

ዘማሪያም (ዘማርያም): የክርስትና ስም (የማርያም ዘር)

ዘማት: ቅጠሉ ሽነት የሚመስል፡ ሥሩ ብዙ ዛፍ፡ በገደል ላይ የሚዘምት፡ ዐጽቃም፡ ደም የሚወጣው።

ዘማች (ቾች): የዘመተ፣ የሚዘምት የጦር ሰራዊት፡ ወታደር፡ ጭፍራ።

ዘማች አሞራ: ተወግቶ የወደቀውን ሰው ዐይን ለመጥቃትና ሥጋውን ለመብላት ከዘማች ጋራ የሚኼድ አሞራ። በግእዝ አውስት ይባላል።

ዘማች አንቀጽ: በኀላፊ፣ በትንቢት፣ በዘንድ፣ በትእዛዝ፡ በአምስት አዕማድ፣ በአድራጊ፣ በአስደራጊ፣ በተደራጊ፣ በተደራራጊ፣ በአደራራጊ የሚረባ ግስ፡ "ዐወቀን" "ገደለን" "ቀደሰን" የመሰለ።

ዘማኑም: የጥንብ በላ ዓይነት አሞራ።

ዘማዊ: የሚሴስን፡ ሴሰኛ፡ ቅንዝረኛ፡ አመንዝራ ወንድ፡ የዘማ ወገን።

ዘምቶ ተወረስ: ዘምቶ የተወረሰ፡ ባጕል የቀረ ጥፋተኛ።

ዘምቶ: እጦር ኺዶ።

ዘምዘም: የእስላሞች ጠበል፡ እግዚአብሔር ለአጋርና ለልጇ ለይስማኤል ያፈለቀው (ዘፍ 21:19)

ዘምዛሚ (ሞች): የዘመዘመ፣ የሚዘመዝም፡ ጠቃሚ፡ ቀምቃሚ፡ ጠላፊ።

ዘሞተ (ዘመወ): ከሰው ሴት ኼደ፡ ያችንም ያችንም ለከፈ።

ዘሞተ: አመነዘረ (ዘመወ)

ዘሴ: የክርስትና የፊደል ስም፡ ዘሥላሴ ማለት ነው።

ዘረ መልካም: ዘረ ደግ፣ ዘረ ማለፊያ።

ዘረ መትር: የአሣ ወጥመድ፣ ባለወንፊት መረብ የአሣን ዘር የሚመትር።

ዘረ መጥፎ: ዘረ ቢስ።

ዘረ ቈርጥም: የዘሩበትን የማያበቅል መሬት።

ዘረ ቢስ: ዘሩ ወገኑ ንፉግ የሆነ፣ ዘረ መጥፎ።

ዘረ ክፉ: ዘሩ ክፉ የሆነ።

ዘረ ደግ: ዘሩ ቸር የሆነ፣ ዘረ መልካም።

ዘረ ጥሩ: የጨዋ ልጅ፣ ነውር እንከን የሌለበት።

ዘረመትርያሣ: ወጥመድ።

ዘረመጠ: በኀይል ሰረረ (የእንስሳ)

ዘረምቦ (ዘረንቦ): ከሻሻቴ የሚበልጥ፣ ከሲውሲዋ የሚያንስ (ዶሮ)

ዘረረ: አደረሰ።

ዘረረ: ዘለለ፣ ዘረጋ፣ አሰጣ፣ ሰተረ፣ ለፀሓይ ሰጠ፡ አስተኛ፣ አጋደመ። (ኹለተኛውን ዘለለ እይ)

ዘረር: የጐመን ስም። ሰናፍጭ የሚመስል ነጭ የዱር ጐመን በማሳ ውስጥ የሚበቅል። (የወፍ ዘረር እንዲሉ። ዘረር ማለት ፍሬው ረግፎ በመሬት መሰጣቱንና የወፍ መኖ መኾኑን ያሳያል።)

ዘረበ (ዘሪብ ዘረበ): መታ፣ ቀጠቀጠ (ግእዝ)

ዘረበበ (ረበበ): ውሃን ከተቀቀለ ነገር ውስጥ አፈሰሰ፣ አጠነፈፈ፣ አንጠፈጠፈ።

ዘረበብ/ዘረበቦ/ዘርባባ: የተንዘረበበ፣ እንዝርብ። (በግእዝም ዘረበበ፣ ዘረበቦ የዘረጋ፣ የዘረጋው ማለት ነው)

ዘረብረብ አለ: ጠብ ጠብ፣ ዘረክርክ አለ።

ዘረብረብ: የቧልት ንግግር። (ለምሳሌ: አቡነ ዘረብረብ በቅባ ኑግ ረብ እንዲል እረኛ)

ዘረብራብ/ዝርብርብ: የተዝረበረበ፣ እንጥብጥብ፣ ልጋግ።

ዘረት: የቀበሌ ስም፡ ካዳባይ በስተቀኝ ያለ ገጠር።

ዘረነቀ (ዘረቀ): አለስፍራው፣ አለጕዳዩ አገባ፣ ጨመረ፣ ዶለ፣ ነከረ። (ዘነቀን ተመልክት)

ዘረነቀ: ነገር አበላሸ፣ ዘባረቀ።

ዘረከ (ዘሪክ ዘረከ): አዝረከረከ፣ በያለበት ዐልፎ ዐልፎ ጣለ፣ ገደፈ፣ አዝረፈረፈ።

ዘረከቦ (ዘከረቦ): ቅርጫት ሆድ፡ ዘርጣጣ። በግእዝ ግን ያገኘው ተብሎ በቅጽልነት ይፈታል።

ዘረከተ: ቀደደ፣ ቦጨቀ፣ ሸረከተ፣ ዘረገፈ።

ዘረከተ: ነፋ (ሆድን)

ዘረኰተ (ረኰተ): ዘለጎሰ፣ አበላሸ (ቃል)፡ ዘለለ፣ ጣለ።

ዘረወ/ዘረየ (አዘራ): በሁለት እጅ እየነቀነቀ አፈሰሰ፣ ለነፋስ ሰጠ፣ ፍሬን ከገለባ ለየ (ኢዮብ ፴፡ ፳፪)

ዘረዘረ : ሞረደ፣ ፈገፈገ፣ ሳለ (ለማጭድ፣ ለመጋዝ ጥርስ አወጣ)

ዘረዘረ : ሸከሸከ፣ ዘከዘከ፣ አሳሳ፣ አራራቀ (የሸማ፣ የወንፊት፣ የጥርስ)

ዘረዘረ : ብርን መነዘረ፣ ሸረፈ።

ዘረዘረ : ነገርን አንድ ባንድ አስረዳ።

ዘረዘረ : የፊደልን ቅርጽ አሳጥን ውስጥ አገባ፣ መለሰ።

ዘረዘረ (ዘርዘረ ሰብለ): ምርቅ አበጀ፣ በተነ፣ ለየ (ድብድቡን)፡ ፍሬ ጀመረ ለመውለድ፣ ለመሸት።

ዘረዘረ: ነጠለ

ዘረዘረች: አደገች፣ ባል ሳታገባ ቆየች፣ ተላለፋት ልጃገረዷ።

ዘረገገ (ትግርኛ: ዘረገ): በጠበጠ፣ አደፈረሰ።

ዘረገገ: ዘረዘረ።

ዘረገግ/ዘርጋጋ: የተንዘረገገ፣ የሚንዘረገግ፣ ጉትት፣ እንዝርግ።

ዘረገፈ : ክፉኛ ነከሰ፣ ቦጨቀ፣ ዘበተረ፣ ቦተረፈ፣ ዘረከተ (ውሻ ባትን፣ አስኳልን)

ዘረገፈ (ትግርኛ: ዘርፈ፣ ጠጉርን አበጠረ): ጎመንን፣ ስጋን፣ ንፍሮን ከማሰሮ፡ አንጀትን፣ ፈርስን ከሆድ ከጨጓራ፡ እህልን ከስልቻ ጨርሶ አወጣ፣ አፈሰሰ (፪ኛ ሳሙኤል ፳፡ ፲) (ረገፈን እይ፡ የዚህ ከፊል ነው።)

ዘረጋ (ትግርኛ: ዘርግሐ): ሰተረ፣ አሰጣ፣ ዘረረ፣ አጠፈጠፈ፣ አሣሣ (መዝሙር ፻፴፮፡ ፮)

ዘረጋ: እሰጣ ለፀሓይ ሰጠ።

ዘረጋጋ: አነጣጠፈ።

ዘረጠ : ተሳደበ።

ዘረጠ : ተፈሳ።

ዘረጠ: ተሳደበ።

ዘረጠ: ተፈሳ።

ዘረጠ: ዐጠረ፣ ዐጪር ኾነ።

ዘረጠ: አጠረ፣ አጭር ሆነ።

ዘረጠጠ: ሳበ፣ ጎተተ (እግርን)

ዘረጠጠ: ናደ፣ አፈረሰ (ክምርን)

ዘረጠጠ: አዋረደ (ሰውን)

ዘረጠጥ: ዘርጣጣ፡ የተንዘረጠጠ፡ እንዝርጥ፣ ዘረከቦ።

ዘረጠፈ: ፀረፈ፣ ፈጽሞ ሰደበ።

ዘረጥ አደረገ አለ: አህይኛ ፈላ፣ ተፈሳ።

ዘረጥራጣ: የተዝረጠረጠ፣ ፈሪ።

ዘረጥራጤ: የዘረጥራጣ ወገን፣ ዐይነት። (ባከነ ብለኸ በከንን እይ)

ዘረጦ: ፈሳም።

ዘረፈ (ትግርኛ: ሐባ ዘርፈ፡ ማረከ): ወረረ፡ በዘበዘ፣ ቀማ፡ ነጠቀ፣ ገፈፈ፣ ወሰደ (በጦርነት)

ዘረፈ: ቅኔ ሳይቈጥር አመጣ፣ ተቀኘ፣ ተናገረ።

ዘረፈጠ: ተረፈቀ። (ደረፎጩን እይ፡ የዚህ ተቃራኒ ነው።)

ዘረፈጥ/ዘርፋጣ: ርፍቅ ከተቀመጠበት የማይነሣ ሆደ ትልቅ።

ዘረፈፈ/አንዘረፈፈ: ዘርፍ አወጣ፣ አረዘመ፡ ጎተተ፣ አንቀረፈፈ። (በተገብሮነትም ይፈታል።)

ዘረፈፍ/ዘርፋፋ: የተንዘረፈፈ፡ የታቦት ልብስ ረዥም ጉትት፡ ቀርፋፋ ሰው።

ዘረፉ: የሰው ስም። ( አባትንና እናትን ያያል)

ዘረፋ (ትግርኛ: ሐባ ምርኮ): ወረራ፣ ቅሚያ።

ዘረፋ: የወንድና የሴት መጠሪያ ስም።

ዘረፋ: ድንገተኛ ቅኔ።

ዘረፍራፋ/ዝርፍራፊ/ዝርፍርፍ: የተዝረፈረፈ፡ ዝርክርክ።

ዘሩ ፪ኛው ረመሰ ነው

ዘሩ ሶራ ነው፡ ወሰራን እይ

ዘሩ በረቀ ነው፡ በባዕድነት ወይም በጸ ለውጥነት ተጨምሮበታል።

ዘሩ ኰመሸሸ ነው: (ይህ ሐረግ ትርጉም አልተሰጠውም፣ ምናልባት ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል)

ዘሪ (ብዙ ቁጥር: ዘሪዎች): የዘራ፣ የሚዘራ፣ በታኝ፣ ገበሬ (ኢሳይያስ ፶፭፡ ፲፣ ማቴዎስ ፲፫፡ ፫) (ነገር ብለኸ ነገርን እይ)

ዘራ : ሸነ (የሩካቤ)

ዘራ : አገባ፣ አሳደረ። (ለምሳሌ: እከሌ ከሞተ በኋላ ፈጣሪ ነፍስ ዘራበት)

ዘራ (ዘርዐ): በተነ፣ ነሰነሰ፣ እንጠባጠበ (ማቴዎስ ፲፫፡ ፳፬) (ተረት): ዐጃ ወቅጦ ቢዘሩ ተመልሶ ከዘሩ። (ግጥም): በሠኔ ካልዘሩ፣ በጥቅምት ካለቀሙ፣ እኽል የት ይገኛል በድንበር ቢቆሙ።

ዘራረፈ: መላልሶ ዘረፈ።

ዘራንዘር: የዘር ዘር። (ብዛትን ያሳያል)

ዘራፊ (ብዙ ቁጥር: ዘራፎች): የዘረፈ፣ የሚዘርፍ፡ ወራሪ፣ ቀማኛ (ናሖ፪ )

ዘራፊነት: ዘራፊ መኾን፡ ቀማኛነት።

ዘራፍ ለወሬ መካች: ከፉከራ የሚበልጥ ፉከራ።

ዘራፍ ዘራፍ: ተደጋግሞ ሲነገርና ሲፎከር።

ዘራፍ: ዘርፎ በብዙ የሚሰጥ፡ ቸር፣ ለጋስ።

ዘራፍ: ዝኒ ከማሁ ለዘራፊ፡ ጐበዝ። (ሐመር ዘራፍ ዐካኪ ዘራፍ እንዲል ሐርበኛ)

ዘራፍ: የፉከራ ቃል። (ዘራፍ አትበሉ ይቈጣችኋል ተሰማ ሣህሉ። ከፍ ቢል ከዚያ ሰውዬ፡ ዝቅ ቢል ከነገብርዬ። ተሰማ ሣህሉ ሐውዜን ቢመታ በፈንዜ፡ ሽዋ ተሰማ በጊዜ።)

ዘር : ልጅ፣ ትውልድ፣ ወገን፣ ነገድ።

ዘር : የእንስሳና ያውሬ፣ የወፍ ዐይነት ሁሉ በየዘመዱ ዘር ይባላል።

ዘር (ብዙ ቁጥር: ዘሮች): (ዘርዕ) የእኽል፣ የተክል ፍሬ፣ ቅንጣት፣ ተዘርቶ የሚበቅል፣ በቅሎ የሚረግፍ።

ዘር ቈጠራ: እከሌ ቢወልድ እከሌን ማለት። (ከታች ወደ ላይ) አባት፣ አያት፣ ቅድማያት (እሚታ) ቅማት፣ ቅማያት፣ ሽማት፣ ምዝላት፣ እንጅላት።

ዘር በዘር (ዕንብርተ ቀዳዳ): እንደ ልጅ ያየውንና የሰማውን የሚናገር።

ዘር አሰዳቢ: እንደ አስቆሮታዊ ያለ ዘሩን የሚያሰድብ፣ ነውረኛ።

ዘር አዳም (ዘርዐ አዳም): ክርስቲያን ለሆነ ለአዳም ዘር (ልጅ) ሁሉ የሚደረግ ዐጪር የባይተዋርና የድኻ ፍታት። ገንዘብ የማይከፈልበት።

ዘር ይመስክር: የልዑል ራስ መኰንን አባት ክቡር ደጃዝማች ወልደ ሚካኤል የተናገሩት ነው።

ዘር ይውጣልኸ: እንዲል መራቂ። (ተረት): የዘሬን ብተው ያንዘርዝረኝ።

ዘር ይውጣልኸ: የበቃ፣ የነቃ ልጅ ውለድ፣ ተባረክ።

ዘር: አይነቱ፣ ቅንጣቱ።

ዘርቶ: በትኖ፣ አንጠባጥቦ። (ተረት): ወልዶ አይስም፣ ዘርቶ አይቅም።

ዘርና ነባር: አባት ዘርና ጥሬ ዘር ከነባር ጋራ።

ዘርናቂ: የዘረነቀ፣ የሚዘርንቅ፡ ነካሪ፣ ዘባራቂ።

ዘርካታ: ዘርጋፋ፣ ሆደ ትልቅ፣ ቦርጫም።

ዘርካች: የዘረከተ፣ የሚዘርክት፡ ዘርጋፊ።

ዘርኳታ: ዘልጓሳ (መጽሐፍ)

ዘርኳች: የዘረኰተ፣ የሚዘረኵት፡ ዘልጓሽ፣ ገዳፍ።

ዘርዘር አለ: ራቅ ራቅ አለ።

ዘርዘር አለ: ራቅ ራቅ አለ። (ግጥም): "አገሩ ደብረ ብርሃን ታቦቱ ስላሴ፡ ዘርዘር ያለ ነው ጥርሱ እንደ በለሴ፡ ዳዊቱን ጨርሶ ገብቷል አቅዳሴ። "

ዘርዛሪ: የዘረዘረ፣ የሚዘረዝር፣ በታኝ፣ ሸክሻኪ፣ ሞራጅ፣ ሸማኔ፣ ባለጅ።

ዘርዛሪዎች: የዘረዘሩ፣ የሚዘረዝሩ፣ ባለጆች፣ ጠይቦች፣ ሰራተኞች።

ዘርዛራ: የተዘረዘረ፣ ሸክሻካ (ወንፊት፣ በለሴ፣ ማጭድ፣ ጥርስ)

ዘርያ: ዐይነት፣ ነገድ፣ ዘመድ፣ ተወላጅ፣ ወገን።

ዘርያ: ዐይነት፣ ዘራ።

ዘርጊ ዘርጊባቸው: የሴት ስም።

ዘርጊ: የዘረጋ፣ የሚዘረጋ፣ አስጪ፣ ዘራሪ።

ዘርጋ አለ: ተዘረጋ። (ለምሳሌ: ዕጥፍ ዘርጋ አለ እንዲሉ)

ዘርጋ አደረገ: ዘረጋ።

ዘርጋ: መዘርጋት።

ዘርጋው/ዘርጋባቸው: የወንድ ስም።

ዘርጋፊ (ብዙ ቁጥር: ዘርጋፎች): የዘረገፈ፣ የሚዘረግፍ፣ አውጪ።

ዘርጋፋ: ቦርጫም፣ ሆደ ትልቅ፣ ዘርካታ።

ዘርጠጥ አለ: ተንዘረጠጠ።

ዘርጣ: ተሳዳቢ፣ አፈኛ፣ ሰው አዋራጅ።

ዘርጣጭ (ብዙ ቁጥር: ዘርጣጮች): የዘረጠጠ፣ የሚዘረጥጥ፡ ናጂ፣ አፍራሽ፣ ሳቢ፣ ጎታች።

ዘርጭ እንቧይ: ከበር እንቧይ በጣም ያነሰ።

ዘርጭ: ታናሽ፣ አነስተኛ።

ዘርፈሽዋል: የሴት ስም። (ሀብቱን፣ ውበቱን ማለት ነው)

ዘርፉ/ዘርፋ: የወንድና የሴት መጠሪያ ስም። ( አባትን፣ እናትን ያያል፡ የርሱ፣ የርሷ ዘርፍ ማለት ነው)

ዘርፍ (ዘፈር): ቍቲት፣ መርገፍ፣ አጫዋች፣ እንጥልጥል (ዘኍ፲፭፡ ፴፰፡ ፴፱። መዝ ፻፴፫፡ ፪። ኢሳ፮፡ ፩)

ዘርፍ ቀድሞት ሲነገር፡ "ኅዳር ሚካኤል" "ሠኔ ሚካኤል" ይላል: (የቅዱሳን በዓላት መጠሪያ)

ዘርፍ ቀድሞት ሲነገር: "ኅዳር ሚካኤል" "ሠኔ ሚካኤል" ይላል።

ዘርፍ አያያዥ: ዘርፍን ከባለቤት የሚያያይዝ ፊደል፡ ይኸውም ነው። (የሰማይ አምላክ የአዳም ልጅ እንዲሉ። በግእዝ ልማድ ግን ዘሰማይ አምላክ ዘአዳም ወልድ ቢል ደፊ ይባላል።)

ዘርፍ አያያዥ: የሳድስ ወራሽ ግእዝ ፊደል። እም ባል፡ እመቤት ባለቤት።

ዘርፍ: እንደ ግእዝ አካሄድ ተከትሎ፡ እንዳማርኛ ልማድ ቀድሞ ተከትሎ የሚነገር ቃል። (ግእዝ አምላከ ሰማይ ሲል ሰማይ ዘርፍ ይባላል። ባማርኛም እጀ ሰብ ቢል ሰብ ዘርፍ ነው፡ ቤተ ሰብ ሲል ቤት ዘርፍ፡ ሰብ ባለቤት ይኾናል።)

ዘርፍና ባለቤት: ተቀዳሚና ተከታይ፡ ወይም ተናባቢ ቃል።

ዘርፎች (አዝፋር): ቍቲቶች፣ መርገፎች፣ አጫዋቾች፣ እንጥልጥሎች፣ ያንቀልባ፣ የቈርበት፣ የደበሎ ጫፎች። (ዘረፈፈን እይ፡ የዚህ ዘር ነው።)

ዘቀቀ (ዕብ፡ ዛቃቅ): አጠራ፣ ጥሩ አደረገ። (ዘቀዘቀን አስተውል፣ የዚህ ዲቃላ ነው።)

ዘቀዘቀ (ዘቀ): (ኢዮብ ፳፪፡ ፳፱) አቈለቈለ፣ አፈሰሰ፣ ደፋ፣ አርእስትን ወደ ታች ኅዳግን ወደ ላይ አደረገ፣ ቍልቍል ሰቀለ። (ለምሳሌ: ተማሪው መጽሐፉን ዘቀዘቀው)

ዘቀጠ (ዘገጠ): ሰጠመ፣ ሠረገ፣ አተለ (በታች በሥር ሆነ)

ዘቀጠ: ዘራ።

ዘቃ: በሶብላ። (ዜጋ ማለት ነው)

ዘቃቅቤ (ዜጋ ቅቤ): የበሶብላ ቅጠል። (በወጥ ቢጨምሩት ቅቤ ቅቤ ይላልና በዚህ ምክንያት ዘቃቅቤ ተባለ)

ዘቅዛቂ: የዘቀዘቀ፣ የሚዘቀዝቅ፣ አቈልቋይ።

ዘቅዛቃ: ቍልቍለት፣ ተዳፋት።

ዘበለለ (ዘቢል፣ ዘበለ): አብዝቶ ዐራ፣ ዘፈዘፈ፣ ኰሳ።

ዘበሬታ: ቀልድ፣ ቧልት፣ ፍሬ ቢስ ነገር።

ዘበተ (ሰለተ): ቀለደ፣ አላገጠ፣ ተሣለቀ።

ዘበተ: ቈለለ፣ ከመረ፣ አነባበረ።

ዘበተ: ዛተ፣ ፎከረ፣ አስፈራራ። መሰለ ብለኸ አመሰለን እይ።

ዘበተረ: ዘነተረ።

ዘበተን እይ፡ ከአፌጠናና ከአፌዘ ጋራ አንድ ነው።

ዘበታ: መዘበት።

ዘበት (ስላት): ዋዛ፣ ቀልድ፣ ለግጥ፣ ሥላቅ።

ዘበነ (ዘመነ): ዘበናይ ኾነ፡ ዘበን ሰጠው፡ አገኘ፣ ከበረ።

ዘበነ በልግ: የበልግ ዘመን። በግእዝ ተወን ጸደይ ይባላል።

ዘበነ ግልምቢጥ: የተገላቢጦ ዘመን።

ዘበነነ): ተዘባነነ፡ ዘበናይኛ ተናገረ፡ ተጓደደ፣ ኰራ። ወበነነ እይ።

ዘበናይ (ዮች): የዘመን፡ ባለጊዜ፡ ዘመን የወለደው፡ ንጉሥ የወደደው። በግእዝ ዘመናዊ ይባላል።

ዘበናይነት: ባለጊዜነት፣ ጌትነት።

ዘበን (ኖች): ዘመን፣ ጊዜ፣ ዓመት። (ተረት): ዘበን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል።

ዘበኛ (ኞች): ዘባናዊ፡ ባለዘብ፣ ዘብ ዐዳሪ፣ ዘብ ጠባቂ፡ ወር ተረኛ፡ ቤትን፣ ዕቃን፣ ከተማን፣ አገርን የሚጠብቅ (ነሐ፬፡ ፱) ከጣሊያን ወዲህ ግን ፖሊስ ይሉታል። ፈረስን እይ።

ዘበኛ: ጠባቂ፡ ዘብ።

ዘበኛነት: ዘበኛ መኾን፡ ጠባቂነት።

ዘበኝነት: ዝኒ ከማሁ።

ዘበዘበ (ዘብዘበ): ነዘነዘ፣ ነተረከ፣ ጨቀጨቀ፡ ነገር አበዛ፣ ጐተተ።

ዘበደ: ጠረገ፣ አጠራቀመ።

ዘበጠ (ዘቢጥ፣ ዘበጠ): መታ፡ ደራ፣ ተለመጠ፡ ለጥ አለ፡ ወዳቃ ኾነ፡ የጣራ፣ የዠርባ፣ የስፍራ (መክ ፲፡ ፲፰)

ዘበጠረ: ሠበጠረ። ዘና ሠሰ ይወራረሱ።

ዘበጠጠ (ዘፈጠጠ): ወደ ኋላ አለ፡ ቀረ፣ ዘቀጠ።

ዘበጠጥ: ዘብጣጣ፡ የዘበጠጠ፣ የቀረ።

ዘቢ: የሚዘባ፣ የሚለመጥ፡ ተለማጭ።

ዘቢብ: የወይን ፍሬ፡ ዘይብ።

ዘቢጥ: በበጌምድር ክፍል ያለ አገር። በግእዝም መምታት ማለት ነው።

ዘባ (ዘብሐ፣ ትግ. ዘብዐ): ደራ፣ ተለመጠ፡ በቀጥታና በጕብጠት መካከል ኾነ፡ የበትር፣ የጣራ፣ የሌላውም ዕንጨት።

ዘባረቀ (ባረቀ): ክፉና በጎ ተናገረ።

ዘባረቀ: አማሰለ፣ ቀላቀለ፣ ደባለቀ።

ዘባራቂ (ዎች): የዘባረቀ፣ የሚዘባርቅ፡ ደባላቂ።

ዘባተሎ (ዘበጠለ): ዛተሎ፡ የተቀዳደድ፣ የተበታተነ፣ የባታይ ጨርቅ። ባተለን እይ።

ዘባች: የዘበተ፣ የሚዘብት፡ ቀላጅ፣ አላጋጭ፡ ፎካሪ፣ አስፈራሪ።

ዘባጣ: ዘብጥ፡ የዘበጠ፡ በዳገትና በዳገት ሥር ያለ ቀጥታ ሰታታ ቦታ፣ ረባዳ፡ የምድር ዋዲያት።

ዘባጭ: የሚዘብጥ፣ የሚደራ፡ ተለማጭ።

ዘብ (ዘቢን፣ ዘበነ): ጥበቃ፣ የመጠበቅ ሥራ በተራ በፈረቃ የሚደረግ (ግብ ሐዋ ፲፪፡ ፲)

ዘብ ዐደረ: ሌሊት ጠበቀ።

ዘብ ይደሩ: የወንድና የሴት ስም።

ዘብ: ዘበኛ

ዘብላይ: የዘበለለ፣ የሚዘበልል፡ የሚያራ።

ዘብራ: ኀይለኛ የበረሓ አህያ፡ ሯጭ፣ ፈርጣጭ፡ በዐውሳና በውጋዴ ይገኛል። በሱማልኛ ወይልድአስ ይባላል።

ዘብር: በመንዝ ክፍል ያለ አገር።

ዘብታሪ: የዘበተረ፣ የሚዘበትር፡ ዘንታሪ።

ዘብዛቢ: የዘበዘበ፣ የሚዘበዝብ፡ ነዝናዥ፣ ነትራኪ፣ ጨቅጫቂ።

ዘብዛባ: ነዝናዛ፣ ነትራካ፣ ጨቅጫቃ።

ዘብጥያ (ዘብጣዊ): የሌባ፣ የቀጣፊ፣ የወስላታ ማሰሪያ ቤት፡ በዝቅተኛና በጐድጓዳ ስፍራ የተሠራ፡ የሲኦል ምሳሌ። እከሌ ስለ ሰረቀ ዘብጥያ ገባ። ወህኒን እይ።

ዘቦ (ዘቦ፣ ዘቦቱ): ያለው። ወርቀ ዘቦ ግምጃ እንዲሉ። ወርቅን ተመልከት።

ዘቦጠ): አዝቦጠቦጠ (ቦጠቦጠ፣ አስቦጠቦጠ)፡ ደባለቀ፣ ቀላቀለ፣ በጠበጠ፡ አወፈረ።

ዘተረስዐ፡ ሳይጻፍ የቀረ

ዘተር: ዱባ፡ ዘጠር።

ዘተበ: አፉን መላ፡ ብዙ በላ።

ዘተዘተ: ነከሰ፣ ነካከሰ፣ በጣጠሰ፣ ገተገተ፡ ዐኝ ዐኝ አለ፡ እንደ ዝተት አደረገ። (ዘከዘከንን እይ)

ዘትብ: የአፍ ምላት፣ ምሉነት።

ዘች ዘች አለ: ሩጭ ሩጭ አለ (የበሬ) (ዘጠዘጠንን እይ)

ዘች: መሮጥ።

ዘነመ: በቁሙ ዘነበ።

ዘነመ: በቁሙ፡ ዘነበ።

ዘነመ: በትክክለኛ ፍቺው፣ ዝናብ ዘነበ።

ዘነቀ: ቀላቀለ፡ አዋሀደ።

ዘነቀ: ቀየጠ፣ ቀላቀለ፣ ደባለቀ።

ዘነቀ: የካህናት ነው።

ዘነቈለ: ደነቈለ፣ ጠነቈለ፣ ኣነቈረ፣ ወጋ።

ዘነቈለ: ደንቆሮና ሞኝ ሆነ፡ ደነዘዘ፡ ወጋ።

ዘነበ (ዘንመ): ከላይ ከሰማይ፣ ከደመና ተንጠባጠበ፡ በዝቶ ወረደ፡ መጣ፡ ዱብ ዱብ፣ ጠብ ጠብ አለ (የዝናብ፣ የበረዶ፣ የእሳት)

ዘነበ: ዘነብ፡ የወንድ ስም።

ዘነበለ: ዐነከሰ

ዘነበለ: ጋደለ፡ ዘለፍ አለ፡ ጐነበሰ፡ ዘመመ፡ ተቈለቈለ፡ ተዘቀዘቀ (ዕቃው፣ ሰዉ፣ ፀሓዩ) (መዝ 40:1 ሉቃ 24:29)

ዘነበች: የሴት ስም።

ዘነተረ (ሠነተረ): ነከሰ፣ ዘበተረ፣ ቦጨቀ፣ ቦተረፈ፣ በላ።

ዘነተረ (ሠነተረ): ነከስ፡ በጥርስ ቀደደ፡ አኘከ፡ በሚንጨባረቅ ሁኔታ በላ።

ዘነነ (ትግ፣ ዘነነ): ቁስልን አሰረ፣ ጠቀለለ።

ዘነነ (ትግርኛ፡ ዘነነ): ቁስልን ጠቀለለ ወይም አሰረ።

ዘነነ: (ትግርኛ: ዘነነ) ቁስልን አሰረ፣ ጠቀለለ።

ዘነነ: ራሱን መለስ ቀለስ አደረገ።

ዘነነ: ራሳም ሆነ፡ ከራሱ ከበደ። (ደነደነን ተመልከት)

ዘነነ: ራስን ከበደ፡ በራሱ ላይ ከበደ። (ደነደነ ተመልከት)

ዘነነ: ራስን ወደ ኋላና ወደ ፊት ማንቀሳቀስ።

ዘነከተ: በንግግር ወይም በባህሪ ደግ፣ የዋህ ወይም የሰለጠነ ሆነ።

ዘነከተ: ደግ፣ የዋህ ሆነ (በነገር፣ በጠባይ)

ዘነከተ: ደግና የዋህ ሆነ፣ በነገርም ሆነ በጠባይ ገራ።

ዘነኰረ/ዘነከረ (ነኰረ፣ ነከረ) ነገር አበላሸ። (ዘነጐለን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው)

ዘነዘና (ሺዋ): የሙቀጫ ልጅ፡ መውቀጫ። "ሐሚናሚና፡ ዘነዘና፡ የብር ዘነዘና" እንዲሉ ልጆች። ሲበዛ ዘነዘኖች ይላል። (ነቀሰን እይ፡ ዘነነን አስተውል)

ዘነዘና (ጐንደር): ከዘነዘና የተበጀ ውዥሞ።

ዘነዘና (ጐዣም): የእንጨት ስም፡ ታናሽ ዛፍ፡ ውስጠ ክፍት፡ ንጣት ቀጥታነት ያለው፡ ቀፎ የሚሆን።

ዘነደበ: አረዘመ፡ በሩቅ መታ።

ዘነደበ: ወለደ። "እከሊት ወንድ ወንዱን ትዘነድበዋለች። "

ዘነጀረ: አሰረ፡ ቀፈደደ።

ዘነጋ (ዘንግዐ): ረሳ፡ የሚያውቀውን አጠፋ፡ ዐጣ፡ ጥንቃቄና ንቃት አልባ ሆነ (ኢሳ 28:7)

ዘነጐለ (ዛጐለ): ብላሽ ሆነ (የነገር)

ዘነጐረ (ዘጐረ): ነብር መሰለ። ስሯጽ ነው።

ዘነጠ: አውደለደለ፡ ቀበጠ፡ ዘመን አመጣሽ ቋንቋ ነው።

ዘነጠለ (ነጠለ): በሾኽ ነደለ፡ በሳ፡ ቀደደ፡ ፈነቀለ (እግርን)

ዘነጠለ: ነፋ፡ አወፈረ።

ዘነጠለ: ንባብ አበላሸ፡ የማይነሣውን ቃል አነሣ።

ዘነጠለ: ክምርን ናደ፡ አፈረሰ።

ዘነጠፈ (ነጠፈ): ዠመገገ፡ ሸመጠጠ፡ ቈረጠ፡ ገነጠለ፡ አረገፈ፡ አወረደ። (ዠነጠፈን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።)

ዘነጠፈ: አረዘመ፡ ሽንጣም አደረገ።

ዘነጣጠለ: በሳሳ፡ ቀዳደደ።

ዘነፈ (ትግ፣ ሰደበ): በዛ፡ ተረፈ፡ ረዘመ፡ በለጠ።

ዘነፈ (ትግርኛ፡ ሰደበ): በዝቶ ተገኘ፡ ትርፍ ሆነ፡ ረዘመ፡ በልጧል።

ዘነፈ: (ትግርኛ: ሰደበ)

ዘነፈለ : ዘፈዘፈ።

ዘነፈለ/ዘነበለ: ጋደም አለ።

ዘነፈለ: ተጋደመ፡ ተኛ (ከዘነበለ ጋር ተመሳሳይ ነው)

ዘና (ዘነየ): ቀበጠ፡ ደራ፡ በፍትወት ሳተ።

ዘና (ዝኅነ): ዐረፈ፡ ረጋ፡ ጸጥ አለ፡ ዐሳብ ተወ።

ዘናቂ: የሚቀላቅል ወይም የሚያዋህድ ሰው።

ዘናቂ: የዘነቀ፣ የሚዘንቅ፣ ቀያጭ፣ ቀላቃይ።

ዘናነበ: ወራረደ፡ መላልሶ ዘነበ።

ዘናና: ክብ፣ እንክብል፡ መካከለ ብስ ድንጋይ፡ በእንጨት ላይ የሚሰካ።

ዘናና: ክብ፣ ኳስ የሚመስል ድንጋይ መሃሉ ላይ ቀዳዳ ያለው፣ በእንጨት ምሰሶ ላይ የሚገባ።

ዘናና: ክብ ወይም እንክብል የሆነ፣ በመሃከሉ ብስብሱ ድንጋይ በእንጨት ላይ የሚሰካ (የአውድማ ዘንግ አይነት)

ዘናና: የመርከብ መልህቅ (አትሮንስ) ዘነዘና (ሙቀጫ) ከዚህ ግስ ጋር የተያያዘ ነው።

ዘናና: የአትሮንስ መልህቅ። ዘነዘና ማለት የዚህ ዘር ነው።

ዘናፊ: ብዙ ያለው ወይም የሚበልጥ ሰው።

ዘናፊ: የሚዘንፍ።

ዘንቅ: ቅየጣ፣ ቅልቀላ፣ ድብለቃ።

ዘንቅ: የመቀላቀል፣ የማዋሃድ ወይም የማጣመር ተግባር።

ዘንበል አለ: ጋደል አለ።

ዘንበል: ጋደል፡ ዘለፍ።

ዘንቢል (ሎች) (ዐረ): ከቃጫ፣ ከሰሌን የተበጀ አኩፋዳ፡ ዕቃ መያዣ።

ዘንባላ: የዘነበለ፡ የዘመመ።

ዘንባባ (ዎች): የተምር ዓይነት ዛፍ፡ ወንዴ ተምር፡ ፍሬው የማይበላ። (ሰሌንን ተመልከት)

ዘንባባ: በወግዳ ውስጥ ያለ ቀበሌ።

ዘንባይ: የሚዘነብል፡ ጋዳይ።

ዘንተራ: በደምቢያ ውስጥ ያለ አንድ አካባቢ።

ዘንተራ: በደንቢያ ውስጥ ያለ ቀበሌ።

ዘንታሪ (ሮች): የሚነክስ ወይም የሚቀድድ፡ ነካሽ፡ ውሻ፡ ጅብ።

ዘንታሪ (ብዙ ቁጥር: ዘንታሪዎች): የዘነተረ፣ የሚዘነትር፣ ነካሽ፣ ዘብታሪ፣ ውሻ፣ ዥብ።

ዘንቶ (ወሎ): ከቅል የተበጀ መስፈሪያ። አራት ዘንቶ አንድ ቆና ነው።

ዘንቶ መስፈሪያ: ዘና።

ዘንቶ: መመዘኛ ዕቃ (ዘና ተመልከት)

ዘንቶ: ተደላድሎ፡ ተሸራሽቶ፡ ተመቻችቶ። "ዘንቶ ተቀመጠ" እንዲሉ።

ዘንች (ብዙ ቁጥር: ዘንቾች): የታላቅ ጐታ፣ የሪቅ፣ የጐተራ ጋድም መረጋገጫ እንጨት በስተውስጥ በመካከል ያለ።

ዘንች (ቾች): በትላልቅ የጥራጥሬ መጋዘኖች ወይም ማከማቻ ክፍሎች ውስጥ የሚገኝ የእንጨት ድጋፍ ምሰሶ።

ዘንካታ (ቅጽል): ገር፣ የዋህ፣ አነጋገሩ የሚገርም ወይም የሚያስቅ (ለምሳሌ: እንደ ንጉሥ ኃይለ መለኮት እናት እመት በዛብሽ ያለ)

ዘንካታ (ቲት): ደግ፣ የዋህ እና ብዙ ጊዜ ቀልደኛ ሰው፡ እንደ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ እናት እመቤት በዛብሽ ንግግሯ ማራኪና አዝናኝ የሆነ ሰው።

ዘንካታ (ቲት): ገር፣ የዋህ፡ አነጋገሩ የሚገርም፣ የሚያስቅ፡ እንደ ንጉሥ ኃይለ መለኮት እናት፣ እንደ እመት በዛብሽ ያለ።

ዘንካቶች: ደጎች፣ የዋሆች እና ይቅር ባዮች (ብዙ ቁጥር)

ዘንካቶች: ገሮች፣ የዋሆች፣ ቂም አልባዎች።

ዘንኳራ/ዝንኵር: ብላሽ ነገር። ሰውየውም ዘንኳራ ይባላል።

ዘንኳራ/ዝንኵር: ብላሽ ነገር። ዘንኳራ ሰው ይባላል።

ዘንኳራ/ዝንኵር: የጠፋ ወይም ያለቀ ነገር። እንዲሁም የተበላሸ ወይም መጥፎ ባህሪ ያለው ሰው ለመግለጽ ይጠቅማል።

ዘንዘሪጡ: የዲያቆን ተወራጅ፡ ገፈፎ።

ዘንዳባ/ዝንድብ: የተዘነደበ፡ ቁመተ ረዥም።

ዘንድ/ዘንዳ: ጋ፡ ጌ፡ ጐን፡ አጠገብ፡ ቀበሌ፡ ስፍራ፡ ቦታ። "እሱ ዘንድ" "አንተ ዘንድ" "" ሲጨመርበት ዓመት ወይም ዘመን ይሆናል።

ዘንድ አንቀጽ: በትንቢትና በትእዛዝ መካከል ያለ፡ "ይበላ ዘንድ" "ይጠጣ ዘንድ" "እንዲበላ" "ሊበላ" እያለ የሚነገር (ማቴ 5:45 6:1 8:4) ይህም ነገርን እያረጋገጠ የውል አገባብ መሆኑን ያሳያል። ከኀላፊ አንቀጽ ጋራ "" ሲቀድመው፡ "ከመጣ ዘንድ" "ከኼደ ዘንድ" እያለ አንቀጽ ያስቀራል። በግእዝ መሠረቶቹ ኀበ እምከመ ናቸው።

ዘንድሮ: ንኡስ አገባብ፡ የዱሮ ተቃራኒ። የዛሬ፣ የኣሁን ዓመት፡ ዘመን ያልተፈጸመ፡ ገና የተጀመረ፡ የተያዘ ጊዜ። (ዘንድን ተመልከት)

ዘንድብ: የዘነደበ፣ የሚዘነድብ፡ አርዛሚ፡ ለቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽም ይሆናል።

ዘንዶ (ዎች): የምድር አውሬ፡ እግር የሌለው፡ መርዘኛ፡ የእባብ ወገን፡ አስቀድሞ በዛፍ ላይ (ዘንድ) ይጠመጠምና አራዊትንና እንስሳትን በዥራቱ እየጠለፈ ልሶ የሚውጥ ወይም የሚሰለቅጥ። (ጐረጐረ፣ ዘወረ፣ ዞረ ብለህ ጐርጓሪን፣ ዙሪያን ተመልከት)

ዘንዶ ጕር: በተጕለት ዐናት ከዛንጅራ በታች ያለ ቀበሌ። "ዘንዶ ያለበት" "የዘንዶ ጕር" ማለት ነው።

ዘንዶ: በገመድ የተጠቀለለ ጭራሮ፡ የጣራ ክባስ፡ የክዳን ትራስ፡ የጋን፣ የገበር፣ ምጣድ፣ ማቶት ዓይነት፡ በቤት ውስጥ ዙሪያውን ወጋግራ የሚሸከመውና በስተሰበሰብ፣ ክፍክፋት ተሸካሚ።

ዘንገሊል (ዘንገ፣ ልል): ሞኝ፡ ተዘንጎች፡ በትሮች፡ ምርኵዞች (ዘፀ 27:11)፡ በያዘው በትር የሚመታ።

ዘንገሊል: ሞኝ (ዘንግ የሚለውን ተመልከት)

ዘንገኛ (ኞች): ባለዘንግ፡ ዘንጋም፡ ጠበቃ፡ ተማጋች፡ ዘንግ ይዞ የሚገት። "የሴት ዘንገኛ የናት ምቀኛ" እንዲሉ።

ዘንጊ: የሚዘነጋ፡ ረሺ።

ዘንጋ (ዘንግዖ): መዘንጋት።

ዘንጋ አለ: ዘነጋ።

ዘንጋዳ (ዶች) (ዘንገ፣ አገዳ): አንጓ ላንፋ ያለው የአገዳ እህል፡ በቆላ የሚበቅል የጥቁሬታ ዓይነት። እንጭብሌ፣ ጐምዠ፣ ጐረንጆ፣ ድኵዬ፣ ዘገብሬል፣ ዠተሬ፣ ኰልኝ፣ ዐጪሬ የመሰለው ሁሉ ይጠቃለላል።

ዘንግ (ጎች): ቀጠን ያለ በትር፡ ምርኵዝ፡ ረዥምና አጭር (ዘፀ 6:38)

ዘንግ: እስኪት፡ የወንድ ኀፍረት።

ዘንግ: የሸማኔ ልክ። (አንድ ዘንግ ስድስት ክንድ ሸማ ነው።)

ዘንግ: የእግር ብረት ቅርቃር።

ዘንጎባ: የቅጥራን ስም፡ ቅጥራን።

ዘንጠፍ አለ: ዱብ፣ ጠብ አለ፡ ወረደ።

ዘንጣላ/ዝንጥል: የተዘነጠለ፡ ቦርጭም፡ ንድል፡ ፍንቅል፡ ቅድ።

ዘንጣይ (ዮች): የዘነጠለ፣ የሚዘነጥል፡ ፈንቃይ።

ዘንጣፊ: የዘነጠፈ፣ የሚዘነጥፍ፡ ዠምጋጊ።

ዘንጣፋ (ፎች): ረዥም፡ ዠርጋዳ፡ አቋቋሙ መልካም።

ዘንፋላ (ሎች): የተዘረጋጋ፡ የተጨነቀ አለቃ።

ዘንፋላ (ብዙ ቁጥር: ዘንፋሎች): የተዘናፈለ፣ መከዳ፣ የጨነቀው ጌታ።

ዘንፋላዬ: የተዘረጋጋው የኔ።

ዘንፋላዬ: የኔ ዘንፋላ።

ዘአምላኪየ: የቅኔ ስም፡ ፪ኛ ቅኔ።

ዘኢያገድፍ፡ የተማሩትን የማያስረሳ አስማት ወይም መድኃኒት (አፍልሖ)

ዘከረ: (ዘኪር፣ ዘከረ፣ ዘክሮ፣ ዘከረ) የእግዚአብሔርን፣ የማርያምን፣ የመላእክትን ስም ጠራ፡ በስማቸው ጸለየ። የዕለቱን ውዳሴ ማርያምና ከመዝሙር አራት፣ ከነቢያት አንድ ደገመ፡ አቡነ ዘበሰማያት በሰላመ ገብርኤል አለ። ጸዲቅን ባረከ፣ ገመሰ (ቆረሰ) ፈተተ (አብራራ) ተነተነ (በዝርዝር ተናገረ)

ዘከረ: አሰበ፣ አስታወሰ፣ አወሳ።

ዘከዘከ: (ዘሕዝሐ) ዘቀዘቀ፣ ዘረገፈ ማለትም አወጣ፣ አፈሰሰ።

ዘከዘከ: ነቀነቀ፣ ሰነገጨ (አንቀጠቀጠ)

ዘከዘከ: ውሻ ሰውን አጥብቆ ነከሰ። (ዘተዘተ የሚለውንም ይመልከቱ።)

ዘከዘከ: ዘረዘረ፣ ሸከሸከ፣ ቀደደ።

ዘከዘከ: የሰማውን ሁሉ አወራ (አፈረጠው)

ዘከዘክ፣ ዘክዛካ: ዘርዛራ፣ ሸክሻካ፡ ለሴ ወንፊት ሲሄድ ዘክዘክ የሚል በቅሎ (ስለሚበታትን)

ዘካ: (ከዐረብኛ የመጣ) አስራት፡ የአስራት እህል ወይም ምርት።

ዘካሪ (ዎች): የዘከረ፣ የሚዘክር፡ ባራኪ፣ ቆራሽ፣ ካህን፣ ቄስ፣ ደብተራ። (መጽሐፍ ግን 'ሰካሪ' በሚለው ፈንታ 'ዘካሪ' ይላል ይህም ስህተት ነው - ምሳ 23:21 ቲቶ 1:7)

ዘካሪ: አሳቢ፣ ተቆርቋሪ። (እንዲሉ "መካሪ ዘካሪ አያሳጣን። ")

ዘኬ ለቃሚ: ዘኬ የሚለቅም ወይም የሚሰበስብ ተማሪ።

ዘኬ: "ዘካዊ" ማለትም ከተዝካር እንጀራ ላይ አስራ አንድ በመቀነስ የሚዘጋጅ ሆምጣጣ እንጀራ። (ኰቸሮ የሚለውንም ይመልከቱ።)

ዘክዘክ አለ: (ገቸገቸ)

ዘክዘክ አለ: እንደ አህያ ወይም አጋሰስ አመነታ፣ ተንገዳገደ።

ዘክዛኪ: የዘከዘከ፣ የሚዘከዝክ፡ ዘርጋፊ፣ አፍሳሽ፣ ነቅናቂ፣ ዘርዛሪ፣ ሸክሻኪ።

ዘኸተት (ቶች): ቂል፣ ግተት፣ ሞኝ፣ ዘርፋፋ፣ ጉትት።

ዘኸነነ (ዘኅነነ) ከዘኅነን አገባ ነከረ፣ አቀለመ፣ ዐለለ፣ አቀላ (ነጭ ጭራን፣ ልብስን)

ዘኸነነ (ዘኅነነ) ከዘኅነን አገባ ነከረ አቀለመ ዐለለ አቀላ (ነጭ ጭራን፣ ልብስን)

ዘወልዴ (ዘወልድ): ገብረ ወልድ፣ ተክለ ወልድ ማለት ነው።

ዘወረ (ዘውሮ፣ ዘወረ): መዘውር ሠራ! አዞረ፣ ጠመዘዘ፡ አሽከረከረ፡ በዙሪያ ኣስኬደ።

ዘወረ ማለት... ማዞሪያ ማንቀዋለያ፣ መጠምዘዣ፣ መመለሻ ስፍራ (ኤርሚያስ 27:3)

ዘወረደ፡ የሑዳዴ መዠመሪያ ሳምንት፡ ጾመ ሕርቃል።

ዘወር (ዘውሮ): መለስ፣ ጠምዘዝ።

ዘወር በል: ወኺድ።

ዘወር አለ: ስፍራ ለቀቀ፣ ተገለለ፣ ተወገደ፡ ዞረ፣ ተመለሰ። (ተረት): አልሸሹም፡ ዘወር አሉ።

ዘወር አለበት: በሽታ ጐበኘው ሰውየውን።

ዘወር አለበት: ጠላው፣ ማለገ።

ዘወር አደረገ: መለሰ፣ አገለለ፣ ወገደ።

ዘወርታ: ዘወር ማለት፡ ምለሳ።

ዘወርዋራ: ዝውርውር፡ የተዘዋወረ፣ የተጣመመ፣ ጠማማ፡ ዙሪያ፣ ክብ መንገድ፣ ቀጥታ ያይዶለ (ምሳ፰፡ ፰)

ዘወቀ: ዘነቀ፣ ዘባረቀ ነገርን።

ዘወትር - ዝውተራ

ዘወትር (ወተረ) ንኡስ አገባብ ሲሆን በቁሙ ወትሮ ማለት ነው። በግእዝ ግን ወትር፣ ወትሮ፣ ዘወትር የወትሮ የዘወትር ማለት ነው። ወትረን ተመልከት።

ዘወትር (ወተረ) ንኡስ አገባብ ሲሆን በቁሙ ወትሮ ማለት ነው። በግእዝ ግን ወትር፣ ወትሮ፣ ዘወትር የወትሮ የዘወትር ማለት ነው። ወትረን ተመልከት። የዘወትር የኹለዬ፣ የሠርክ፣ የዕለት፣ የጊዜ፣ የቀን ሥራ፣ ምግብ፣ ልብስ፣ ጸሎት፣ ጀንበር በሠረቀ ቍጥር የሚደረግ ማንኛውም ነገር ነው። ሠርክን እይ። ዝውተራ የማዘውተር ሥራ ነው። አዘወተረ (አውተረ) ዘወትር፣ ዕለት ዕለት፣ በየጊዜው፣ በየቀኑ መላልሶ ሠራ፣ ደጋገመ፣ ዐሳቡን በአንድ ነገር ላይ አደረገ ማለት ነው።

ዘወደ (ዐረ፣ ሥንቅ ሰጠ): ከበበ፣ ክብ አደረገ፡ ዘውድ ሠራ፣ አበጀ።

ዘወገ (ዘውጎ): ወገነ፡ ጥንድ አደረገ።

ዘወፅእና ዘገብአ (ዘወፅአ ወዘገብአ): ዘወፅአ የወጣ፡ ዘገብአ የገባ፣ የተመለሰ ገንዘብ፡ ወጪና ገቢ። ገባን እይ።

ዘዋሪ (ዎች): የሚዞር፡ ዟሪ፣ ተሽከርካሪ፣ በዙረት ኻያጅ፡ ዕረፍት የለሽ፣ እተነሣበት ተመልሶ የሚመጣ፣ ጨረቃ፣ ኮከብ፣ ቍርዬ፣ አንበጣ፡ መንኰራኵር፣ ሠረገላ፣ አዝማሪ (ምሳ፳፡ ፲፱)

ዘዋሪ (ዎች): የዘወረ፣ የሚዘውር፣ የሚያዞር፡ መዘውር ሠሪ፣ መኪና ነጂ፡ ወይም መሪ፣ አሽከርካሪ።

ዘዋራ: ዝኒ ከማሁ፣ የዞረ፡ ጠምዛዛ ዕንጨት መንገድ።

ዘዌ: የዛፍ ስም፡ የመርዝ መድኀኒት የሚኾን ዕንጨት፣ እባብ ጧት በምሥራቅ ምሽት ሲኾን በምዕራብ ኹኖ ፍሬውን የሚበላው። እንዲህም ማድረጉ ጥላው እንዳያርፍበት ነው። ርግብም እባቡ እንዳይነድፋት ጧት በስተምዕራብ በሠርክ በስተምሥራቅ ኹና ፍሬውን ትመገባለች።

ዘው (ዘዊዕ፣ ዘዊሕ): ድንገት መግባት።

ዘው አለ (ትግ. ዘውሐ): አፈሰሰ፡ ግብት፣ ጥልቅ አለ።

ዘው ዘው አለ: ገባ ገባ አለ፡ መላልሶ ገባ።

ዘውዲቱ: የዳግማዊ ምኒልክ ልጅ። እሳቸውም በ፲፱፻፱ ነገሡ፡ በ፲፱፻፳፪ . ዐረፉ።

ዘውዴ: ዘውዲቱ፡ ዘውድ ነኸ ነሽ፡ የወንድና የሴት መጠሪያ ስም።

ዘውድ (ዶች): የክብር ጕልላት፡ ክብርነት ያለው አክሊል ከወርቅ የተሠራ ውስጠ ክፍት ጌጥ፣ ዕንቍና (አልማዝ) ፈርጥ ያለበት፡ ንጉሥ በነገሡ ጊዜ በራሱ ላይ የሚደፋው፣ የሚቀዳጀው መጨረሻ ማዕርግ፣ የማሸነፍ ምልክት፡ ቤት ተከድኖ ሲያልቅ ጕልላት እንደሚጫንበት ይህም እንደዚያ ነው። (ተረት): ድኻ ባመዱ ንጉሥ በዘውዱ።

ዘውድ ዐጣኝ: ዘውድን የሚያጥን፡ ቄስ፣ ዐጤ።

ዘውድ ደፋ: በራሱ ላይ አደረገ፣ ተቀዳጀ።

ዘውድ ጫነ: ነገሠ።

ዘውግ: ወገን፣ ነገድ፣ ጥንድ፣ ጣምራ። ይህ የግእዝ ነው፡ ዞግን እይ።

ዘየመ) (ዘዪም ዜመ) አዜመ ዜማ ደረሰ፣ ተማረ፣ ጮኸ፣ ሃሌ አለ፣ ማሕሌት ቆመ፣ ዘመረ፣ ቀደሰ፣ ቃኘ፣ ተቀኘ። ወዘመን እይ፡ ከዚህ ጋር አንድ ነው።

ዘየረ (ዐረ) ጐበኘ፣ ደረሰ፡ ሰላም አለ፡ አንጐራጐረ፣ ዘፈነ፣ ምስጋና አቀረበ (በተቀደሰ ቦታ)

ዘየረ (ዐረ): ጐበኘ ደረሰ ሰላም አለ አንጐራጐረ ዘፈነ ወይም ምስጋና አቀረበ (በተቀደሰ ቦታ)

ዘየነ (ዘይኖ ዘየነ) ሸለመ፣ አስጌጠ።

ዘየነ (ዘይኖ ዘየነ): ሸለመ ወይም አስጌጠ

ዘየን ዘየን አለ አጊጦ ተሽኰንትሮ ዞረ፣ ተመላለሰ።

ዘየን ዘየን አለ: አጊጦ ተሽኰንትሮ ዞረ ወይም ተመላለሰ

ዘየደ (ተደራጊ) ዘዴኛ ሆነ፣ ዐወቀ፣ ተጠበበ።

ዘየደ (አድራጊ) ጨመረ፣ አበዛ፣ አተረፈ።

ዘያሪ የዘየረ፣ የሚዘይር፡ ጐብኚ፣ ደራሽ፣ ዘፋኝ፣ አመስጋኝ።

ዘያኝ (ኞች) የዘየነ፣ የሚዘይን፡ ሸላሚ፣ አስጊያጭ።

ዘያኝ (ኞች): የዘየነ ወይም የሚዘይን፤ ሸላሚ አስጊያጭ

ዘዬ (ዘይቤ) የነገር ልማድ፣ ፈሊጥ፣ ባህል ሲሆን አንዳንድ ሰዎች በጨዋታ መኻል ጣልቃ እያገቡ መላልሰው የሚናገሩት ነው።

ዘይ ዘይ አለ ማለትም ዝኒ ከማሁ።

ዘይ ዘይ አለ: ማለትም ልክ እንደዚሁ

ዘይ ዘይ፣ ዘየን ዘየን፣ ዘየነ ዚያ (ዚኣ) "" ቅጽልነትን፣ "" አካልነትን ያሳያል። ትርጓሜው "ርሱ" "እሱ" ነው። 8 ደቂቅ አገባቦች ሲጫኑት ለሚታይና ለማይታይ የሩቅ ነገር፣ ለቦታ፣ ለጊዜ፣ ለአካል አጸፋና በቂ ቅጽል ይሆናል።

ዘይ ዘይ፣ ዘየን ዘየን፣ ዘየነ: ከዚሁ ቃል ጋር የተያያዙ ናቸው።

ዘይቤ ነጠላ ትርጓሜ፡ የሰዋስው ትምህርት ሲሆን ትርፍ ነገር ሳይጨመርበት ቃል በቃል የሚነገር ነው። "ዘይቤ የሚል" ማለት ነው።

ዘይቤ: ነጠላ ትርጓሜ ማለት ነው። የሰዋስው ትምህርት ሲሆን ተጨማሪ ነገር ሳይጨመርበት ቃል በቃል የሚነገር ነው። "ዘይቤ የሚል" ማለት ነው።

ዘይቤው: "የኔ ናስ ግንቤ" ማለት ነው፡ የፈረሰውን ኹለቱን ቤተ መቅደስ ያሳስባል።

ዘይብ (ዘቢብ) ደረቅ የወይን ፍሬ።

ዘይብ (ዘቢብ): ደረቅ የወይን ፍሬ ማለት ነው።

ዘይቱም: ፍሬው የሚበላ የዕፅዋት ዝርያ ሲሆን በሐረርጌ አውራጃ የሚበቅል ነው።

ዘይታ: በመራቤቴ አካባቢ የሚገኝ አንድ ስፍራ። "ዘይቷ" ማለት "የእርሷ ዘይት" ማለት ነው።

ዘይት (ቶች) የወይራ ዓይነት ዛፍ ነው። እንስት ወይራ ፍሬው የሚበላ ነው።

ዘይት (ቶች): የወይራ ዓይነት ዛፍ ነው። ሴቷ የወይራ ዛፍ የሚበላ ፍሬ ትሰጣለች። ዘይት የግእዝ ሲሆን ወይራ ደግሞ የአማርኛ ነው። "ደብረ ዘይት" የሚል አባባል አለ። "ደብረን" የሚለውን ቃል መመልከት ይቻላል።

ዘይት የግእዝ፣ ወይራ የአማርኛ ነው። "ደብረ ዘይት" እንዲሉ። ደብረን እይ።

ዘይት: ከምድር የሚወጣ እንደ ነዳጅ፣ ጋዝ እና ቤንዚን የመሳሰሉ ፈሳሾች። በግእዝ "ነፍጥ" ይባላል።

ዘይት: ከሱፍ፣ ከኑግ፣ ከሰሊጥ፣ ከተልባ እና ከጉሎ የሚገኝ ማንኛውም ዓይነት ቅባት።

ዘይት: ከወይራ ፍሬ ተጨምቆ የሚወጣ፣ ሰዎች የሚመገቡት ወይም የሚቀቡት ፈሳሽ። (ሜሮን የሚለው ቃልም ተመሳሳይ ትርጉም አለው።)

ዘይቶን: የዘይት ተክል (የግእዝ ቃል)

ዘይኑን የጽርእ ንጉሥ ስም ሲሆን የቅድስት ኢላርያ አባትና ጉባኤ ኬልቄዶንን የሻረ ነው።

ዘይእዜ የቅኔ ስም፡ 6 ቅኔ።

ዘይእዜ: የቅኔ ስም ሲሆን 6 ቅኔ ነው።

ዘዴ ዕውቀት፣ ፈሊጥ፣ ብልኀት፣ ጥበብ ሲሆን እያደር እየቀደም እየተጨመረ እየሰፋ የሚኼድ ነው። "ኑሮ በዘዴ" እንዲሉ። ዘዴኛ (ኞች) ባለዘዴ፣ ዕውቀተኛ፣ ጥበበኛ።

ዘዴ: ዕውቀት፡ ዘየደ።

ዘዴኛነት ዘዴኛ መሆን፣ ብልኅነት።

ዘገሌ: ከቃፍር የሚበልጥ በግ።

ዘገመ: ዝግ አለ፡ በቀስታ፣ በዝግታ ኼደ፣ ተጓዘ፡ የበሽተኛ፣ የደካማ።

ዘገም አለ: ዘገመ።

ዘገም አደረገ: አዘገመ።

ዘገምተኛ: ዝግተኛ፣ አዝግሞ ኻያጅ።

ዘገምታ: የቀስታ፣ የዝግታ መኼድ አካኼድ።

ዘገረ (ረጊዝ፣ ረገዘ): ወጋ፣ ዘረከተ።

ዘገር (ሮች): ጥንታዊ የንጉሥ ጦር። ዣግርን እይ።

ዘገር ነጠቀ: ጦር አነሣ።

ዘገበ (ዘጊብ፣ ዘገበ): ሰበሰበ፣ እከማቸ፣ አጠራቀመ፡ ብዙውን ባንድነት አደረገ፣ አደለበ።

ዘገበ: ረጨ፣ አርከፈከፈ፡ ተቀባ። እከሌ ሽቱ ዘገበ እንዲሉ።

ዘገባ: ስብሰባ፡ ትልቅ መስፈሪያ።

ዘገብሬል፡ የክርስትና ስም፣ የገብሬል ማለት ነው።

ዘገብሬል፡ የዘንጋዳ ስም፡ ቀይ ዘንጋዳ።

ዘገብሬል: ዘንጋዳ፡ ገበረ።

ዘገነ (ትግ.): ዠገነ፣ በረታ፣ ገነነ። ዠግናን ተመልከት።

ዘገነ (ዘጊን፣ ዘገነ): ጠረን፡ በጥርኝ ያዘ፣ ጨበጠ።

ዘገነ: ዘጋኝ

ዘገነነ: ሰቀጠጠ፡ ጨፈገገ፣ ጭፍግግ አደረገ፡ ጨመደደ፣ አስፈራ ሰውነትን።

ዘገና: መዝገን።

ዘገዘገ (ዘገገ): ረዘመ፣ ረዥም ኾነ፡ የዜማ፣ የስብከት።

ዘገየ: ቈየ፡ ባንድ ስፍራ፣ ባንድ ሥራ ዋለ፣ ዐደረ፡ ሰነበተ (ዘፍ፲፱፡ ፲፮) (ተረት): ሞት ቢዘገይ የቀረ ይመስላል።

ዘገጀ (ዘግደየ): ዝግጁ ኾነ።

ዘገገ: ኣወደቀ፣ ዘረጋ፣ ዘረረ፡ ከፍጥነት አራቀ።

ዘገጠ: ዘቀጠ።

ዘጊ (ዎች): የዘጋ፣ የሚዘጋ። የጭፍራ ስም፡ ደንቡ የቤተ መንግሥት በር መዝጋት የኾነ ሰራዊት።

ዘጋ (ዘጊሕ): መዝጋት።

ዘጋ (ዘግሐ): (፪ነገ ፬፡ ፴፫) ገጠመ፣ ከደነ (ማለ)፡ ደፈነ፣ ዐፈነ፣ አወለነ።

ዘጋ አደረገ: ከደን፣ ገጠም፣ መለስ አደረገ።

ዘጋ: ራሱን ከሰው ለየ፡ በዋሻ (በኣት) ከተተ።

ዘጋበት: አንዱ ሌላው ጥቅም እንዳያገኝ መከረበት።

ዘጋቢ: የዘገበ፣ የሚዘግብ፡ ሰብሳቢ፣ አጠራቃሚ።

ዘጋኝ (ኞች): የዘገነ፣ የሚዘግን፡ ቃሚ።

ዘጋጋ: መላልሶ ዘጋ፡ ገጣጠመ፣ ከዳደነ።

ዘጌ (ዘገየ): በጣና ባሕር አጠገብ ያለ አገር፡ የጐዣም ግዛት። ዘጌ ዘገየ ማለት ይመስላል።

ዘጌዎች: የዘጌ ሰዎች፣ የዘጌ ተወላጆች።

ዘግ አለ: ፱፣ ዘፍ፣ ዘለፍ አለ።

ዘግ: ዘፍ፡ ዘገገ።

ዘግ: ዘፍ፣ ዝርግት።

ዘግዘግ አለ: ዘክዘክ አለ።

ዘግዛጊ: የዘገዘገ፣ የሚዘገዝግ፡ ረዛሚ።

ዘግዛጋ: የረዘመ፡ ረዥም።

ዘግዪ: የሚዘገይ፣ የሚቈይ።

ዘጐረ: ነብርማ ኾነ። ነብርን ዘጓራ እንዲል፣ ጕራጌ። ዠጐረን ተመልከት፡ ከዚህ ጋራ አንድ ነው። ዘነጐረን አስተውል።

ዘጐነ: ዛጐለ፣ ደም ሠረበ፣ ዐዘለ፡ በለዘ፣ ጠቈረ።

ዘጠረ (ዘተረ) ውሃና ጨው ሞጀረ፣ አበዛ፣ መላ፡ ነፋ፣ ወጠረ (ሆድን)

ዘጠር (ዘተር) ዱባ፣ የባሕር ቅል ነው።

ዘጠነ (ተስዐ) ዘጠኝ አደረገ፣ ከዘጠኝ ከፈለ።

ዘጠነኚት ዘጠነኛዪቱ ክፍል ነው።

ዘጠነኛ (፱ኛ) የዘጠኝ ወገን፣ ቍጥር፣ ማዕርግ።

ዘጠና () 80 እና 100 መካከል ያለ 10 ቤት ቍጥር ሲሆን ዘጠኝ አሥር ወይም አሥር ጊዜ ዘጠኝ ማለት ነው።

ዘጠና ዘጠኝ 100 ሊመላ 1 የጐደለው (ማቴዎስ 18:12-13)

ዘጠናኛ (፺ኛ) የዘጠና ወገን፣ ቍጥር፣ ማዕርግ።

ዘጠንያ ከዘጠኝ አንድ።

ዘጠኝ () የቍጥር ስም ሲሆን 8 እና 10 መካከል ያለ ተራ ቍጥር ነው። የአንድ ቤት።

ዘጠኝ ሰዓት: (ተሱዓት ሰዓት)

ዘጠኝ ጐራሽ አመንዝራ፣ ሸርሙጣ ሴት።

ዘጠኝ ጐራሽ ዘጠኝ ጥይት የሚጐርስ ጠመንጃ።

ዘጠኝ ጐራሽ: ለበን የሚባል ጠመንዣ።

ዘጠኝነት ዘጠኝ መሆን።

ዘጠኞ/ዘጠኒዮ ዘጠኝነት ያለው፣ ውስጥ ብዙ።

ዘጠዘጠ) አዘጠዘጠ ሮጠ፣ አነጠነጠ። "ዘጠዘጠ ሮጠ፣ አዘጠዘጠ ሮጠ ቢባል በቀና ነበር"

ዘጠዘጥ፣ ዘጥዛጣ፣ አዘጥዛጭ የበልግ አህያ (ውዲላ)

ዘጣኝ የዘጠነ ወይም የሚዘጥን።

ዘጣኝ የዘጠነ፣ የሚዘጥን።

ዘጥ፣ እንዘጥ በቂጥ መውደቅ።

ዘጥ/ዘጭ መውደቅ ነው።

ዘጥ/ዘጭ ማለት መውደቅ ነው። (ዞጠ) (ሶጠ) አዞጠ ገረፈ፣ መታ፣ ደበደበ፣ መደወተ።

ዘጥር ምላት፣ ብዛት።

ዘጥር: ምላት ወይም ብዛት

ዘጥዘጥ አለ አዘጠዘጠ።

ዘጭ፣ እንዘጭ አለ ማለትም ልክ እንደዚሁ

ዘጭ፣ እንዘጭ አለ ማለትም ዝኒ ከማሁ።

ዘፈቀ: ደፈቀ፣ እውሃ ውስጥ አገባ፣ ነከረ፣ አጠለቀ፣ አሰጠመ።

ዘፈነ : ተንቀጠቀጠ፣ ተንዘፈዘፈ። (ለምሳሌ: ይህ በሽተኛ እጁ ይዘፍናል)

ዘፈነ (ዘፊን ዘፈነ): ቀነቀነ፣ አወረደ፣ ግጥም ገጠመ፣ አዜመ፣ አንጐራጐረ፣ ዘለለ፣ ተረገረገ። (ተረት): ባልዘፈንሽ፣ ከዘፈንሽም ባላሳፈርሽ።

ዘፈነ (ዘፊን፣ ዘፈነ): ዘፈነ፡ ግጥም ደረሰ፡ ቃኘ፡ አዜመ፡ ዘለለ፡ ጨፈረ። ምሳሌ፡ "አልዘፈንክም ቢሉኝ ዘፈንኩኝ፣ ዘፈንኩኝ ቢሉኝ አልለቅህም አሉ። "

ዘፈነ: ተንቀጠቀጠ ወይም ተንቀጠቀጠ። "የዚህ በሽተኛ እጅ ይንቀጠቀጣል"

ዘፈን (ብዙ ቁጥር: ዘፈኖች): (በቀጥታ ትርጉም) ቅንቀና፣ ግጥም፣ እንጕርጕሮ።

ዘፈን (ኖች): በአጠቃላይ፣ መዝሙር፡ ግጥም፡ ዜማ።

ዘፈን አወረደ: የዘፈን ዜማ መራ።

ዘፈዘፈ : ዐራ፣ ወዘፈ።

ዘፈዘፈ : ወፈረ፣ ሆደ ትልቅ ሆነ፣ ከበደ።

ዘፈዘፈ (ዘፍዘፈ): ነከረ፡ አጠበ፡ ውሃ ውስጥ አስገባ፡ ለቀቀ፡ አፈሰሰ። ዘፈዘፈ፡ ዘረጋ፡ አፈሰሰ። ዘፈዘፈ፡ ወፈረ፡ ትልቅ ሆድ አወጣ፡ ከበደ።

ዘፈዘፈ: (ዘፍዘፈ) ነከረ፣ አራሰ፣ በውሃ ውስጥ አስቀመጠ፣ ተወ፣ ደፈደፈ።

ዘፈጠጠ (አንዘፈጠጠ): እንዘረጠጠ፣ አንገፈጠጠ፣ አስረገዘ፣ አንቀበደደ።

ዘፈጠጠ: አዛባ፡ ከቅርጽ አወጣ፡ አረገዘ፡ አጎበጠ ወይም አጣመመ።

ዘፈጠጥ/ዘፍጣጣ: የተዛባ፡ ከቅርጽ የወጣ፡ ነፍሰ ጡር፡ ያበጠ፡ ትልቅ ሆድ ያለው።

ዘፈፈ (ሰፈፈ): ጣለ፣ አወደቀ፣ አጋደመ።

ዘፈፈ: ዛፍ (በቀጥታ ትርጉም): ዘፈፈ።

ዘፈፍ አለ: ተንዛፈፈ።

ዘፋቂ: የዘፈቀ፣ የሚዘፍቅ፣ ደፋቂ፣ አጥላቂ።

ዘፋኝ (ብዙ ቁጥር: ዘፋኞች): የዘፈነ፣ የሚዘፍን፣ አውራጅ፣ አንጐራጓሪ፣ ዘፈን ወዳድ (መዝሙር ፹፯፡ ፯)

ዘፋኝ (ኞች): የሚዘፍን፡ የሙዚቃ አቀናባሪ፡ የዘፈን ወዳጅ (መዝሙረ ዳዊት ፹፯:)

ዘፋኝ ዳዊት: በ፲፯፲ .. ገደማ የነገሠ የኢትዮጵያ ንጉሥ።

ዘፋዘፎ (ብዙ ቁጥር: ዘፋዘፎዎች): ረዥምዥም ጣራ አሞራ፣ ዛፍ።

ዘፋዘፎ (ዎች): ረዥም፣ ሰፊ ጣሪያ፡ አንድ ዓይነት ትልቅ ዛፍ።

ዘፋፈነ: ደጋገመ ዘፈነ።

ዘፋፋ: የተንዛፈፈ፣ ረዥም የዛፍ ዐጽቅ፣ ክንፍ።

ዘፍ አለ: ወደቀ፣ ተጋደመ፣ ተኛ።

ዘፍ: መውደቅ።

ዘፍ: መውደቅ፣ መተኛት፣ መጋደም። (ተረት): አንጣሪያ ላንጣሪያ ቢደጋገፍ ተያይዞ ዘፍ። (ደፋ ብለኸ ደፍንን እይ)

ዘፍዛፊ: የሚነክር ወይም የሚያፈስስ፡ የሚያፈስስ።

ዘፍዛፊ: የዘፈዘፈ፣ የሚዘፈዝፍ፣ ወዛፊ፣ ደፍዳፊ።

ዘፍዛፋ: (ይህን ቃል እንደ ስም ሲጠቀም ዝኒ ከማሁ) ከባድ፣ ሰፊ፣ ወፍራም።

ዙሓ (ሖች) ጠገራ፣ የጠገራ ብረት ነው።

ዙሓ ሰፊ፣ ትልቅ ነው። የላ ጡት ዙሓ ነው።

ዙሓ: ሰፊ ትልቅ ነው።

ዙሃ: ጠገራ ዙሓ።

ዙሐል ከፀሐይ ብርሃን ከሚነሱ 7 ኮከቦች 5ኛው ኮከብ ነው።

ዙሐል: ከፀሐይ ብርሃን ከሚነሱ ከሰባቱ ኮከቦች አምስተኛው ኮከብ ነው።

ዙረት ምለሳ፣ መዞር፣ ዑደት (መዝሙር 19:6 2 ተሰሎንቄ 3:11)

ዙሪያ (ዘውር) ክበብ፣ ዳር (ኢዮብ 41:6)

ዙሪያ ንግግር አግቦ ነው።

ዙሪያ ገባ ገብ በአጥር ግቢ ውስጥ ያለ ስፍራ።

ዙሪያ ገባው መላው፣ ኹለንተናው ነው። "ይህ ግንብ ዙሪያ ገባው ነቅቷል" ይባላል።

ዙሪያ ጥምጥም አጭርና ቅርብ ያይደለ ረዥም መንገድ ነው። በግእዝ "ፍኖት መጐንድይ" ይባላል (ፊልጵስዩስ 14)

ዙሪያ: ክበብ፣ ዞረ።

ዙሪያው ዘንዶ የረኃብ ስም ሲሆን በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ጊዜ የነበረ ክፉ ቀን ነው። ዙሪያው ዘንዶ ብሄሞትንና ሌዋታንን ያሳስባል። (ኢዮብ 41:8-9)

 

ዙራምባ (ዙር ዐምባ) በጋይንት አውራጃ የሚገኝ ክብ ተራራ ሲሆን የመዋስእትና የዝማሬ መምህራን የሚገኙበት የሀገር ስም ነው።

ዙራምቤ እንግዳ የዙራምባ ተወላጅ ወይም መምህር የሆኑ በደብረ ሊባኖስ የነበሩ ኦርቶዶክሳዊ ሊቅ፣ መናኝ፣ መነኩሴ ናቸው።

ዙር (ዒል) ትእዛዝ፣ አንቀጽ ሲሆን "በዙሪያ ኺድ፣ ተመለስ፣ መለስ በል" ማለት ነው።

ዙር የተዞረ ስፌት፣ ሽሩባ፣ ጤፍ፣ እንጀራ ማለት ሲሆን የስፌት ደረጃና እርከንንም ይገልጻል። "ቍናው ቍናችን ነው፡ ምነው ዙሩ በዛ፡ እንዲህ ኖረናል ወይ እኛም ስንገዛ" የሚለው አገላለጽ ግዛው ሰራዊቱ አዚናራ ታስረው የገጠሙት ነው።

ዙር ጋሜ መካከሉ ተላጭቶ በራስ ዙሪያ ያለ ጠጕር ነው።

ዙሮሽ መዞር፣ ጥምጥም ጠጕር ማለት ነው።

ዙፋሪ ልግም በገላ፣ በአንድነት የተሰፋ አራት ኩታ።

ዙፋን (ብዙ ቁጥር: ዙፋኖች) (ሰፈነ) ቁመቱ ረዥም፣ ጐኑ ሰፊ፣ ታላቅ የንጉሥ ዐልጋ ወይም መንበረ ዳዊት ነው።

ዙፋን ቤት ዙፋን ያለበት ወይም የዙፋን ክፍል ነው።

ዙፋን ቤቶች የዙፋን ቤት ሠራተኞች ሲሆኑ አንጣፎች፣ ጋራጆች፣ እና የውስጥ አሽከሮች ይገኙበታል።

ዚህ (ዝ፣ ዝየ፣ ዕብ. ዜህ) "ይህ፣ ይኸ" ማለት ነው። ስምንት የአገባብ ሁኔታዎች ሲጫኑት አመልካች ወይም ጭብጥ ቅጽል፣ ዐጸፋና በቂ እየኾነ ቦታንና አካልን፣ ጊዜን ያስተረጕማል። (ለምሳሌ: እዚህ፣ ለዚህ፣ እስከዚህ፣ በዚህ፣ በዚህም፣ በዚህም ላይ፣ በዚህኛው፣ ወደዚህ፣ የዚህ፣ የነዚህ፣ ከዚህ፣ ከዚህ በኋላ፣ ከዚህ ወዲያ፣ ከዚህ ኼደ፣ ለዚህ፣ ለዚህኛው፣ ለዚች፣ ስለዚህ)

ዚህ ሲበዛ "እነዚህ" ይላል። ዚያን ተመልከት።

ዚቀኛ (ብዙ ቁጥር: ዚቀኞች) ባለዚቅ፣ ዚቅ አውራጅ፣ ነገር ትች ዐዋቂ። (ለምሳሌ: እከሌ ዚቀኛ ነው)

ዚቅ የነገር ውሻል፣ ሽብልቅ፣ ማስረጃ።

ዚቅ (ዪቅ ዜቀ) በማሕሌት ጊዜ ከነግሥ፣ ከመልክ፣ ከማሕሌተ ጽጌ፣ ከሰቆቃወ ድንግል እየተነጻጸረ የሚመዘገብ የዜማ ጥቅስ ነው።

ዚቅ አወረደ ደብተራው አዜመ።

ዚያ (ዚኣ) "" ቅጽልነትን፣ "" አካልነትን ያሳያል። ትርጓሜውም "እርሱ" ወይም "እሱ" ነው። ስምንት የአገባብ ሁኔታዎች ሲጫኑት ለሚታይና ለማይታይ የሩቅ ነገር፣ ለቦታ፣ ለጊዜ፣ ለአካል አጸፋና በቂ ቅጽል ይሆናል። በብዛት ሲነገር "እነዚያ፣ እለዚያ" ይባላል። በስፍራው "ተመልከት" ማለት ነው።

ዛኅርታም (ዝኅራዊ) ሆዳም፣ በላተኛ፣ ልክ የለሽ፣ በልቶ የማይጠግብ፣ ሆደ ሳጥን፣ የአሳማና የዥብ ወገን ነው። "አሲድን" የሚለውን ቃል ይመልከቱ።

ዛኅርት (ዘኀረ፣ ዝኅር) ሰፊ ሆድ፣ የምግብ ጕድጓድ፣ የመብልና የመጠጥ መቃብር።

ዛለ (ዝሕለ) ላላ፣ ደከመ፣ ዝልፍልፍ አለ፣ እንደታረደ ወይም እንደሞተ ሆነ፣ ራሱን ደፋ፣ አቀረቀረ ማለት ነው። መያዝ፣ መጨበጥ፣ መቆም ተሳነው ወይም አቃተው።

ዛላ (ዎች) አንድ የብር እኽል ራስ (የስንዴ፣ የገብስ) ሲሆን "የስንዴው ዛላ ዕፍኝ ይመላ" (ኢሳ 17:5 ማር 4:8) ተብሎ ይገለጻል። ደረቅ ቃሪያ ከፍሬው ጋርንም ያመለክታል። በተጨማሪም የሰውነት አቋምን ሲገልጽ "ዛላው ደህና" ማለት ቁመናው የሚያምር ጎልማሳ ማለት ነው።

ዛላ ደረቅ ቃሪያ ከፍሬው ጋር። ዛላው ደኅና ቁመናው የሚያምር ጕልማሳ።

ዛል (ዘሓል) የጭን ወይም የኋላ እግር ስጋ ነው። (እግርን የሚለውን ይመልከቱ።)

ዛመ (ዐረ፣ ዘሐመ፣ ገፋ) ሞቀ፣ ተኰሰ፣ ተንቀጠቀጠ፣ ዞረ።

ዛራም (ብዙ ቁጥር: ዛራሞች) ዛር ያለበት፣ የፈለቀበት፣ ባለዛር፣ ቆሊያም።

ዛሬ (ዘረየ) በትላንትናና በነገ መካከል ያለ ሌሊትና ቀን። በዘርፍነት ሲነገር ዛሬ ሌሊት ወይም የዛሬ ሌሊት፣ ዛሬ ቀን ወይም የዛሬ ቀን ማለት ነው። ዛሬ ምን ስትፈጥር ዋልክ ስትሠራ ስታደርግ ማለት ነው። ዛሬ (ዛርየ) የኔ ዛር ማለት ነው። ዛሬና ዛር በአማርኛ ይገጥማሉ።

ዛር (ዕብ፡ ባዕድ፣ ልዩ) ክፉ መንፈስ ከግዜር ከመላእክት የተለየ፣ ውቃቢ፣ ትግሬት ነው። በሰው ላይ እያደረ ሰውን የሚያስጓራ፣ የሚያስገዝፍ። (ተረት): ዛር ልመና ሳይያዙ ገና። በብዛት ሲገልጽ "ዛሮች" ይላል (ኢሳይያስ ፴፬፡ ፲፬) (ወለደ ብለው ውላጅን እይ) ዛር ልመና ሳያዙ፣ ገና። ዛር አንጋሽ ዛርን በሰው ላይ የሚያነግሥ፣ የሚያረጋግጥ ቃልቻ። ዛር ወጣበት ፈለቀበት፣ ተቀመጠበት። ዛር ፈረስ (የዛር ፈረስ) ዛር የሰፈረበት ወይም የተቀመጠበት ሰው ወይም ሴት። ዛር እብድ ወንድ ወይም ሴት። (ወጣ ብለው ወጥንን፣ ማጠ ብለው አማማጠን ይመልከቱ) ዛር ዘረጋ።

ዛሮ በተጕለት መጨረሻ አዳባይ በላይ ያለ አገር። (ዛር ሆይ ማለት ነው)

ዛቀ ጫረ ፍምን፣ ሰበሰበ ጋይን። ዛቀ (ዘሐቀ) ጠረገ፣ ጋፈ፣ አወጣ፣ አብዝቶ ወሰደ (ቅቤን፣ ማርን፣ ጭቃን፣ ዐዛባን፣ ዱቄትን፣ እኸልን)

ዛቍኔ ዝቅተኛ ዳኛ፣ ተወራጅ።

ዛቂ የዛቀ፣ የሚዝቅ፣ ጠራጊ። (ለምሳሌ: ዐዛባ ዛቂ፣ ቦይ ዛቂ እንደሚባለው)

ዛቂታ የዛቀች፣ የምትዝቅ ሴት።

ዛቈነ ለፋ፣ ደከመ (እንደ ጦመኛ ዲያቆን) ዛቈነ ዳቈነ፣ ድቍና ተቀበለ። (ዘና ተወራራሽ መሆናቸውን አትዘንጋ)

ዛቅ (ዝሒቅ) መዛቅ። ዛቅ አደረገ አብዝቶ ዛቀ።

ዛቋኝ (ብዙ ቁጥር: ዛቋኞች) የዛቈነ፣ የሚዛቍን፣ ዳቋኝ።

ዛበረ (ዘቢር፣ ዘበረ) ዋለለ፣ ቃዠ፣ አቃሰተ፣ ኢዮሄ፣ ወለሌ o አለ፣ ተጨነቀ፣ ይይዘውን፣ ይናገረውን፣ ይኾነውን ዐጣ፣ ከበሽታ የተነሣ።

ዛቢያ (ትግ.) ሶማያ (፩ነገ ፲፯፡ ) (ተረት): ጦር ሲመጣ ዛቢያ ቈረጣ። ዛቢያ (ዎች) ዘበየ፣ የዶማና የመጥረቢያ እጀታ፣ ቀላሳ ወይም ቈላፋ ዕንጨት፣ ወዶ ገባ። ዛቢያ ገንጥል ጕልበታም ሰው ሲቈፍር ዛቢያ የሚገነጥል።

ዛባሪ የዛበረ፣ የሚዛብር፣ አቃሳች።

ዛብ (ቦች) ዝኒ ከማሁ [ያው ማለት ነው] ዛብ የልጓም ቋድ፣ ዐዘበ፣ ዕዛብ። ዛብሽ ወርቅ የምራት ስም።

ዛተ (ዝህተ) አስፈራራ፣ ዘበተ፣ ፎከረ፣ ዳነተ።

ዛተሎ ዕላቂ ጨርቅ፣ ዘባተሎ።

ዛቲ ታናሽ ዕንጕቻ፣ ባልቴቶች የሚሰጡት የቤተ ክርስቲያን መባ። (በግእዝ ግን ዛቲ ይህች ማለት ነው፣ ስንክሳር (ወበዛቲ ዕለት) ካለው መጥቷል)

ዛቻ (ዛህት) ዘበት፣ ፉከራ፣ ጕራ፣ ማስፈራሪያ።

ዛች የዛተ፣ የሚዝት፣ ፎካሪ።

ዛነፈ አባለጠ፣ አተረፈ፣ አራዘመ።

ዛኒጋባ (ዘንትጋባእ ባቲ) ሰቀላ፣ ጓሮ ቤት፣ አንድ ጣራ (2ነገ 4:10, 11 ሕዝ 40:46) ሲበዛ "ዛኒጋቦች" ይላል (ሕዝ 40:44)

ዛንቂል ሞኝ ወይም ደንቆሮ፣ ቂል።

ዛንታ ተረት፣ ታሪክ ወይም ወግ። (ዝናን ይመልከቱ)

ዛንጅራ የቀበሌ ስም ሲሆን በደብረ ብርሃን አጠገብ ያለ ገጠር ነው። የእስረኛ ስፍራ ማለት ይመስላል።

ዛንጅር (ዐረ፣ ዘንጊር) የአንገትና የእጅ ማሰሪያ ሰንሰለት ሲሆን ሠዓሊዎች በዲያብሎስ ዐንገት ላይ ያደርጉታል። መንቋር፣ የሽፍታ ቀንበር (2ዜና 33:11) በግእዝ "ጋጋ" ይባላል።

ዛንጅሮ (ጃን ጅሮ) ጃን ንጉሥ ሲሆን ጅሮ ደግሞ ጅር ሰራዊት ማለት ይመስላል። የእናሪያ ከተማ ስም ሲሆን በጅማ አውራጃ ያለ ጥንታዊ ከተማ ነው። ዛንጅሮ የዘንዶ ምስጢር አለበት።

ዛዘለ ረዘመ፣ ተጐተተ፣ ተግዠለዠለ። ዛዘለና ዛዘነ አንድ ዘር ናቸው።

ዛዘነ (ሰሰነ) ጮኸ፣ ሚያው ሚያው አለ፣ ዞረ።

ዛዛ (ዛሕዝሐ፣ ሳሕስሐ) አንዛዛ ማለት አበዛ፣ አሰፋ፣ አረዘመ (የቤት)

ዛዛቴ የተንዛዛ ሰው፣ ረዥምና ሰፊ ቤት።

ዛዛኝ (ኞች) የዛዘነ፣ የሚዛዝን ድምጽ ነው።

ዛይ የፊደል ስም ሲሆን ዘን ይወክላል። "ዘየነን እይ" ተብሎ ይገኛል።

ዛይን የፊደል ስም ሲሆን ወይም ዛይ ነው። ጌጥ፣ ሽልማት ማለትም ነው።

ዛይዳ ጭማሪ፣ ትርፍ፣ ፍድፋጅ።

ዛገ (ትግ. ዘዐገ) ወረዛ፣ አዠጠበ፣ ራሰ፣ አደፈ፣ መረተ፣ ዐፈር፣ መሬት መሰለ፣ ተበላሸ፣ ጠቈረ (ያዕ፭፡ )

ዛጉፍ ከቀርክሓ፣ ከሸንበቆ፣ ከውስጠ ክፍት ዕንወት የተበጀ ዋሽንት (፩ሳሙ ፲፰፡ ፮፡ ዳን፫፡ ) ሳንቲን ከዚህ ጋር አንድ ነው።

ዛጊ የዛግ፣ የሚዝግ፣ የሚያድፍ፣ ጥቍር ብረት።

ዛጔ ሰሎሞን ከንግሥተ አዜብ ገረድ የወለደው የላስታ ነገሥታት መዠመሪያ አባት። ይህ ቃል እውነት መኾኑን እንጂ ዛጔ የመራ ተክለ ሃይማኖት ስመ መንግሥት ነው። ዘአጕየየ ማለት ነው ይላሉ።

ዛጐለ ዛጐል መሰለ፣ ዘጐነ።

ዛጐል (ሎች) ደረቅ፣ ጠንካራ የባሕር ተሳቦ ልብስ፣ ትልቅና ትንሽ፣ ሕብሩ ነጭና አረንጓዴ የኾነ። ዛጐል ለባሽ የበጋ ች፣ የክረምት ተንቀሳቃሽ። (ጥላን እይ) ዛጐል ልብሱ የየብስ ተሳቦ ቀንድ አውጣ። ዛጐል በርበሬ መናኛ የበርበሬ ዛላ። ዛጐል ዐይን ዐይኑ ዛጐል የሚመስል ሰው። ዛጐል ጣለ ዛጐልን እመሬት ላይ በተነ፣ ጠነቈለ።

 

ዛጐል ጣይ (ዮች) ማርተኛ፣ ጠንቋይ፣ ወይም መለኛ (፪ነገ ፲፯፡ ፲፯) ሲሆኑ ዛጐል እየጣሉ "እንዲህ ይሆናል፣ እንዲህ ይደረጋል" የሚሉ ናቸው። (ጠጠርንና ጨሌን ይመልከቱ)

ዛጐልማ የዛጐል ዓይነት ወይም የዛጐል መልክ ያለው ዶሮ።

ዛጐምቢል ቀንበርና ደጋን የሚሆን ቀላል እንጨት ያለው የዛፍ ስም።

ዛጠጠ ፈሳ፣ ፈሱን ለቀቀ።

ዛጤ ፈሳም፣ ላጤ።

ዛፉ ወንድ ዛፍ፣ ዛፍ፣ የእሱ ዛፍ። ዛፉም ፍሬውም ትርንጎ ይባላል (የፍራፍሬ አይነት) ዛፋ/ዛፊቱ ሴት ዛፍ (ዘፍጥረት ፫፡ ) ያች ዛፍ፣ የርሷ ዛፍ። ዛፋም ብዙ ዛፍ ያለበት ቦታ፣ ጫካ ወይም ባለዛፍ ዱር። ዛፍ በአጠቃላይ፣ ዛፍ፡ ግንደ፣ ቅርንጫፎችና ቅጠሎች ያለው ሕይወት ያለው ተክል ነው። በዱር የሚበቅል ረጥብ እንጨት፣ ዐጽቃም፣ ቅጠላም፣ ክንፋም። ትናንሽም ሆኑ ትልልቅ፣ አጭርም ሆኑ ረጅም ዛፎች በጠቅላላ ዛፍ ይባላሉ። (ተረት): "ለዛፍ ያለው ቍጥቋጦ አይኾንም። ሁለት እግር አለኝ ብሎ እሁለት ዛፍ አይወጡም" ዛፎች ከሁለትና ከሁለት በላይ ያሉ ብዙዎች (ኢሳይያስ ፷፩፡ )

ዜመኛ (ኞች) ዜማ አዋቂ ወይም ባለዜማ።

ዜማ (ሞች) መንፈሳዊ ዘፈን ሲሆን የራሱ ምልክት አለው። "ጠጅ በብርሌ፣ ዜማ በሃሌ" የሚል አባባል አለ። ዜማ ሐዘን ወርድ ንባብ ነው። ዜማ ሰበረ የቅኔን ንባብ ከውሳኔው አሳለፈ ወይም አላገባብ ተቀኘ። ዜማ በቁሙ (ዘየመ)

ዜር (ዘየረ) በላይኛው ወግዳ በጋሾጥ በላይ ያለ አፋፍ የሆነ የቀበሌ ስም።

ዜሮ (ብዙ ቁጥር: ዜሮዎች) የህንድ ቍጥር ማብዣ አኃዝ ነው። ከአንድ እስከ ዘጠኝ ያሉትን ቍጥሮች ዐሥር፣ ሃያ፣ መቶ፣ ሺህ የሚያደርግ ሲሆን ከዚህም በላይ ያበዛል። ሌላ አኃዝ ካልቀደመው ግን የዜሮ (0) ትርጓሜ ባዶ ማለት ነው።

ዜና ያለፈ ነገር በቃልም ሆነ በመጽሐፍ ሲያያዝ የመጣ።

ዜገ (ዘዪግ ዜገ) ደኸየ፣ ማዕርጉን ዐጣ፣ ተዋረደ፣ ተገዛ፣ ዜጋ ሆነ፣ ገበረ። ዜገ የቅባት ባህል ወይም የሃይማኖት ቃል ሲሆን፣ ሰው ሲሆን የባሕርይ ክብሩን አጣ፣ ሲቀባ ግን ተገብሮ ተፈጥሮ ጠፋለት ማለት ነው።

ዜጋ ገባር፣ ተገዥ፣ የሌላ ሰው ቅኝ። "እግር ዜጋ ነው" እንዲሉ።

ዜጋመል ማሪያም በዜጋመል ያለ የማሪያም ታቦት።

ዜጋመል ከዜጋወደም በላይ በስተግራ ያለ ቀበሌና የማሪያም አጥቢያ ነው። ባላገሮች ግን ደብረ ሊባኖስን ዜጋመል ይሉታል። (ዜጋ ዐመል) የሥራ ዜጋ ማለት ነው፣ ረድንና አናኮን ያስተረጕማል። የቀበሌ ስም ነው።

ዜጋመሎች የዜጋመል ሰዎች፣ ተወላጆች፣ ቤተ ተክለ ሃይማኖቶች፣ ተዋሕዶዎች (ጸጋ ልጆች)

ዜጋወደም ዠማ ነው። የወንዝ ስም ሲሆን በደብረ ሊባኖስ በታች ያለ ዠማ ነው። ትርጕሙ ዜጋና ደም (ዘመድ) ማለት ነው።

ዜግነት ተገዥነት፣ ጎባርነት፣ ዜጋ መሆን።

ዜጎች ገባሮች፣ ታዛዦች (፩ነገ ፭፡ ፲፫)

የዜማ ምልክት ሲሆን የፍዝ ከፊል ነው። (ፈዘዘ ብለው ፍዝን ይመልከቱ)

ዝሓ (ዛሕዝሐ) ጠንካራ ፈትል፣ ድር፣ ቀጪን ወይም ወፍራም። መጽሐፍ ቅዱስ (ዘሌዋውያን 13:48-59) ላይ ግን "ዝሃብ" ተብሎ ቢገኝም ስህተት ነው። በግእዝ "ስፍሕ" ይባላል። ዝሓ በዝሓ መጥረቢያ የእንጨት ዛቢያ የሌለው፣ ከብረት ብቻ የተበጀ መጥረቢያ። ዝሓ በዝሓ ድር በድር ማለትም እርስ በእርስ የተሰራ ሸማ። ዝሓ አዝጊ ድር አድሪ ነው። ለሩቅ ወንድ በቂ፣ ለቅርብ ሴት ትእዛዝ ነው። ዝሓ የሸረሪት ፈትል ወይም ወተር (ኢሳይያስ 59:5)

ዝሃ ድር፣ ዝሓ።

ዝሁራ ከፀሐይ ብርሃን ከሚነሱት ከሰባቱ ኮከቦች ሁለተኛው ኮከብ።

ዝኆኔ የዝኆን፣ ዝኆናዊ ቅርፍርፍ ቂጥኝ ነው።

ዝኆን (ኖች) (ዝኅነ፣ ዝኁን) ታላቅ አውሬ ሲሆን በየብስ ካሉት አራዊት ሁሉ የሚበልጥ ነው። ረዣዥሞች ቀንድ የሚመስሉ ጥርሶቹ በውድ ተሸጠው ለተለያዩ ጌጥ መሣሪያዎች ይሆናሉ። ዝኆን እግር ኮብሽ የያዘው ሙቀጫ እግር።

ዝለላ ብጥብጥ፣ ጠመቃ።

ዝለቅ ወደ ቤት ግባ።

ዝለት ድካም፣ ዝልፍልፍነት።

ዝሊያ፣ ዝላይ ጭፈራ፣ ጮቤ፣ ለምዶ፣ መርታ፣ እንደርዶ፣ ጨዋታ።

ዝል የተዘለለ፣ የታለፈ፣ የተተወ።

 

ዝልል: ዝርር፣ ዝርግ። እንዲሁም የተዘለለ፣ የተጠመቀ፣ የተበጠበጠ፣ ብጥብጥ፣ ወይም በገበር ምጣድ ውስጥ የተመረገ የዳቦ ሊጥ ነው። "ዝልል" መባሉ ኩፍ ስላላለ ነው። ባለትንሽ ቅሬታ ሊጥ ሲሆን እሷን አይተው እሳት ያነዱበታል።

ዝልስ አለ: ትኝት አለ፣ ተዘለሰ። ዝልስ: የተዘለሰ፣ የተኛ፣ የተጋደመ፣ ቅልስ። ዝልስልስ አለ: ዝልፍልፍ፣ ቅልስልስ አለ። ዝልስልስ: የተዝለሰለሰ።

ዝልቀት: ጥልቀት። ዝልቅ (ቆች): የተዘለቀ፣ የተጨረሰ፣ ፍጹም። ዝልቅ ነገር: እውነተኛ፣ ርግጥ፣ ሐቅ። ዝልቅ ዋሻ: ጥልቅ፣ ሩቅ። ዝልቅልቅ: የተበሳሳ የብረት ወንፊት የሚመስል መስኮት፣ ሠቅሠቅ። ዝልቅነት: ዝልቅ መሆን።

ዝልቦ: ሳይቀረደድ የተቀቀለ ጎመን።

ዝልንግድ: ረዥም፣ ቀውላላ፣ ሰነፍ፣ የማይረባ ሰው።

ዝልዘላ: ሥንጠቃ፣ ሽንሸና፣ ነከሳ። ዝልዝላት: ሥንጥቃት፣ ሽንሽናት፣ ንክሳት፣ የዝልዝል ኹኔታ። ዝልዝል (ሎች): የተዘለዘለ፣ ሥንጥቅ፣ ሽንሽን፣ ንክስ።

ዝልይት: ጋድሚያ፣ ርጥጥ ሴት፣ ወይም የባሏ ቢስ የጋገረችው የማይበላ።

ዝልጊት (ቶች): ወንጠፍት፣ የጠላ ወይም የጠጅ ማጥለያ ወይም ማጥሪያ።

ዝልፊያ: ዝኒ ከማሁ (ያው ማለት ነው)

ዝልፍልፍ አለ: ተዝለፈለፈ። ዝልፍልፍ: የተዝለፈለፈ፣ ጥምልምል፣ ራሱን የማይችል፣ ዞላ። ዝልፍልፍታ: ስልምልምታ። ዝልፍልፍነት: ጥምልምልነት።

ዝመራ: መዘመር።

ዝሙተኛ (ኞች): ዘማዊ፣ ዝሙት ወዳድ ወንድ ወይም ሴት።

ዝሙት: ሴሰን፣ ቅንዝር፣ ሽርሙጥና፣ ምንዝር (ዮሐ 8:41)

ዝማ (መርዘም): ራስ ምታት፣ የራስ በሽታ። ዝማ: ምንሾ፣ ተቅማጥ። "ሆድ ዝማ" እንዲሉ።

ዝማሜ: መቋሚያን በመወዝወዝ የሚባል ዜማ።

ዝማም (ሞች): የከብት ወይም የጥጃ አፍ መዝጊያ፣ ታናሽ የገመድ ቅርጫት፣ የማያስበላ፣ የማያስጠባ። ዝማም ወርቅ: የተቀጠቀጠ ጥሩ ወርቅ (ዘፀ 37:17) እንዲሁም የወርቅ ዝማም፣ በሴቶች አፍንጫና ጆሮ መካከል የተንጠለጠለ ቀለበት። ዝማም: በተጫነ አጋሰስ ወይም አህያ አፍ የተወተፈ ጐባጣ እንጨት፣ ዋይክማ ልጓጥ። የበሬ፣ የላም ወይም የግመል ስናግ።

ዝማሞ: በመንዝ ውስጥ ያለ አገር። "ዝማም ሆይ" ማለት ነው።

ዝማሬ መዋሥእት: የዝማሬና የመዋሥእት መጽሐፍ ወይም ትምህርት፣ ቅዱስ ያሬድ የደረሰው። ዝማሬ: የቁርባን ምስጋና ከድርገት በኋላ በግእዝ፣ በዕዝል፣ በአራራይ የሚዘመር ወይም የሚዘመም ነው። ባለ አምስት ክፍል ሲሆን ክፍሎቹም ኀብስት፣ ጽዋዕ፣ መንፈስ (የደብተራ) አኰቴት (የዲያቆን) ምስጢር (የቄስ) ናቸው።

ዝም (ጸመ፣ ጽም): ጭጭ፣ ቃል አለመስጠት፣ አለመናገር፣ ምንም አለማለት። ዝም በል: አትናገር፣ አፍህን ያዝ። ዝም ባይ: ዝም ያለ ወይም የሚል፣ የማይናገር። ዝም ብሎ (ጽመ ክመ): ሳይናገር፣ እንዲሁ፣ እንዲያው፣ አለምክንያት (1ቆሮ 7:19 15:14) ዝም አለ: አረመመ፣ ከመናገር ተከለከለ። ዝም አሠኘ: አስረመመ። ዝም ዕክም አለ: ጸጥተኛ ሆነ። ዝም ዝም አለ: አንዱም አንዱም፣ ኹሉም ድምቡጭ፣ ጭጭ አለ፣ አፉን ገጠሙ። ዝም: መጨረሻ ቁጥር። ዝም: አለመናገር። ዝም: የሸማ ጥበብ፣ በኩታና በቀሚስ ላይ የሚጣል፣ የሚጠበብ።

ዝምም: የተዘመመ፣ የተጐት፣ አፉ ከዝማም የገባ ከብት።

ዝምተኛ (ኞች): ዝምታ ወዳድ፣ ባለዝምታ፣ አርማሚ፣ ባሕታዊ። ዝምተኛነት: አርማሚነት፣ ዝምተኛ መሆን።

ዝምታ: ዝም ማለት፣ ማታ (ኢዮ 4:16 መዝ 122:2 መክ 3:7 ራእ 8:1) ዝምታ: ጫታ፣ ዘመመ።

ዝምዘማ: ጠቀማ፣ ቅምቀማ፣ ጠለፋ። ዝምዝማት (ቶች): ጥቅማት፣ ቅምቅማት። ዝምዝም: የተዘመዘመ፣ የተቀመቀመ፣ ቅምቅም በርኖስ፣ ቀሚስ፣ ዝናር።

ዝምድ: የቅኔ አገባብ ስም። "ተበልዐ ሃይማኖት ኅብስተ ጴጥሮስ ባዕል" ይህም የወርቁ ዘርፍ ለሠሙ መሆኑን ያሳያል።

ዝምድና: ዘመድነት።

ዝሞት (ቶች): ያለቃና የምንዝር ተወላጅ፣ ርስት ተካፋይ፣ የወንድማማችና የትማማች ልጅ። (ባላንጣንና ምንዝርን ይመልከቱ)

ዝሪት (ዝርዕት): የተዘራች፣ ዘር፣ ብቋያ ሰብል።

ዝራር/አዝራር (ብዙ ቁጥር: ዝራሮች): ዝርግ፣ ሰታታ የልብስ ቍልፍ። ሞላላውና ክቡም በዚሁ ስም ይጠራል።

ዝራንጭ (ዝራጭ): ቍንጮ፣ የቍንጮ ዐይነት።

ዝራጭ (ብዙ ቁጥር: ዝራጮች): አጭር ሰው፣ ድንክ።

ዝር (ዝሩዕ): የተዘራ፣ ብትን፣ ንስንስ እኽል። ዝር መድረስ: ዘረረ። ዝር አለ: ደረሰ፣ ትርው አለ። ዝር: መድረስ።

 

ዝርር: የተዘረረ፣ ዝልል፣ ዝርግ፣ ስትር፣ ስጥ፣ ጋድሚያ።

ዝርኵት: የተዘረኰተ፣ ዝልጎስ፣ ግዱፍ።

ዝርክራኪ/ዝርክርክ: የተዝረከረከ፣ ግዱፍ። ዝርክርካም: ባለዝርክርክ ግድፈታም፣ ስሕተት ያለበት፣ የመላበት መጣፍ። ዝርክርክ አለ: ዝርፍርፍ አለ። ዝርክርክ: ልብሱን የማይሰበስብ ሞኝ፣ ከረፈፍ፣ ሽማግሌ።

ዝርክት አለ: ቅድድ፣ ቡጭቅ አለ። ዝርክት: የተዘረከተ፣ ቀዳዳ፣ ቡጭቅ። ዝርክትክት: የተዘረካከተ፣ ቡጭቅጭቅ፣ ሽርክትክት።

ዝርዘራ: ብተና፣ ሽክሸካ፣ የመዘርዘር፣ የመሞረድ ስራ። ዝርዝረ ቀጭ: ዝርዝርን የሚቀጭ ሕፃን፣ ታናሽ ልጅ።

ዝርዝር : በብዙ ገጽ ተጽፎ ያልተደመረ ብር ወይም ሌላ እቃ። ተራ ያለው ነገር። ዝርዝር : ኮኮኔ (በአውራ ዶሮ ግንባር ላይ ያለ ነጠላና ሳሳ የሆነ ረዥም) ወይም የቄዳ ቁንጮ ጫፉ ክፍል ክፍል ያለው። (አጭሩ ዱልዱም ይባላል) ዝርዝር : የተመነዘረ፣ ብትን ገንዘብ፣ መሃለቅ፣ ተሙን፣ ቤሳ። ዝርዝር (ብዙ ቁጥር: ዝርዝሮች)/ዝርዙር: ምርቁ የተበተነ፣ ጨርቁ፣ ሰብል፣ ዛላ። ዝርዝር (ብዙ ቁጥር: ዝርዝሮች): በየአንቀጹና በየጥሬው ጫፍ እየተጨመረ ሩቅና ቅርብን፣ አንድና ብዙን፣ ወንድና ሴትን የሚለይ ፊደል። ሁለተኛ ስሙ ምእላድ ይባላል። እነዚሁም ግእዝ፡ ኸ፣ ካዕብ፡ ችኹ፣ ች፣ ሽ፣ ኹ፣ ናቸው። ተናባቢ ቅጽልነትና ባለቤትን ይገልጣሉ። በጥሬ የሩቁ ወንድ ካዕብና ው፣ የሩቋ ሴት ራብዕ፡ ዋ፣ እኔ የሚለው ሃምስ፡ ናቸው። ካዕብና ሃምስም ዘመድ ዝርዝር፣ የቀሩት ሁሉም ባዕድ ዝርዝር ይባላሉ። ሁለተኛው ዝይጠበቃል። ዝርዝር ምስክር: አውራምስክር ያይደለ። (ያለፈው ቅጽል የሚመጣው ጥሬ ስም መሆኑን አስተውል) ዝርዝር ርባታ: እነዚህ ከዚህ በላይ ያሉትና ሌሎችም () ዎ፣ ቸው፣ ት፣ እየተጨመሩበት በስሳ መደብ የሚረባ ቃል ነው።

ዝርጊት/ምርጊት: ሰፊ የእግር ፵ማ።

ዝርግ : ሥራ ፈት ሴት። ዝርግ: የተዘረጋ፣ ስትር፣ ስጥ፣ ዝርር፣ ጠፍጣፋ፣ ሥሥ፣ ውጥር፣ ንጥፍ።

ዝርግት : መዘርጋት። ዝርግት አለ: ስትር አለ (ኢዮብ ፴፮፡ ፳፱)

ዝርግፍ አለ: ውጥት፣ ፍስስ አለ። ዝርግፍ ወርቅ: ከወርቅ የተበጀ ዶቃ ወይም እንጥልጥል ጌጥ። (ዝርግፍ መባሉ አለክር፣ አለማተብ ሲሆን ነው (፩ኛ ጴጥሮስ ፫፡ ) በግእዝ ቃማ ይባላል) ዝርግፍ: የተዘረገፈ፣ የወጣ።

ዝርጥርጥ አለ: ተዝረጠረጠ። ዝርጥርጥ: ዝርክርክ፣ የቀረ።

ዝርጥጣ: የመናድ፣ የመጎተት ሥራ። ዝርጥጥ አደረገ: ዘረጠጠ። ዝርጥጥ: የተዘረጠጠ፣ የተናደ (ክምር)

ዝርፊያ: ዝኒ ከማሁ ለዘረፋ፣ ብዝበዛ።

ዝቀት (ዝሕቀት): ዝኒ ከማሁ (ያው ማለት ነው)

ዝቃጭ: የዘቀጠ፣ አተላ፣ አንቡላ።

ዝቄ: ዝኒ ከማሁ፣ የከፊለ ስም።

ዝቅ/ወረድ: መውረድ። ዝቅ አለ: ከላይ ለቀቀ፣ ወረድ አለ፣ ወደ ታች ሆነ፣ አነሰ። ዝቅ አሠኘ: ወደ ግርጌ አስወረደ። ዝቅ አርጋቸው: የሰው ስም። ዝቅ አደረገ: ራስጌን አስለቀቀ፣ አወረደ (ዳንኤል ፬፡ ፴፯) ዝቅ ዝቅ አደረገ: ሌላውን ወይም ራሱን አዋረደ (ሉቃስ ፲፰፡ ፲፬) ዝቅ: የማስ ጋን ርኰት። (ዘሩ ዛቀ (ዘሐቀ) ነው (ግእዝ))

ዝቅተኛ (ብዙ ቁጥር: ዝቅተኞች): ታናሽ ነገር፣ አንስተኛ፣ ምክትል፣ ተወራጅ።

ዝቅታ : ተዋረድ ገበታ። ዝቅ ማለት። ዝቅታ: ተዋረድ፣ ዘቀዘቀ። ዝቅታ: ታች፣ የከፍታ ግርጌ (መሳፍንት ፲፰፡ ፳፰፣ ሕዝቅኤል ፮፡ ፫፣ ሮሜ ፰፡ ፴፱)

ዝቅወረድ: ዘቀዘቀ።

ዝቅዝቃ/ዝቅዝቆሽ/ዝቅዝጊት: የመዘቅዘቅ፣ የማቈልቈል ሥራ፣ ድርጊት።

ዝቅዝቅ : ሰባት ፈርጅ ጋቢ ተዘቅዝቆ የተሰፋ። ዝቅዝቅ (ብዙ ቁጥር: ዝቅዝቆች): የተዘቀዘቀ፣ ቍልቍል። ዝቅዝቅ አለ: ተዘቀዘቀ፣ ፍስስ አለ።

ዝቅጥቃጭ: የዝቃጭ ዝቃጭ።

ዝቆሽ: ጠረጋ፣ ስብሰባ፣ የቦይ ሥራ።

ዝቋላ ( ቈላ): በሺዋ ግዛት ያለ የአቦ ገዳም የተራራ ስም። እሳቸው ያቀኑትና የጸለዩበት። ዝቋላ ማለት በስተምሥራቁ ያለውን ቈላ ያመለክታል። ዝቋሎች: የዝቋላ መነኵሴዎች፣ ሕዝቦች፣ እንግዳ ተቀባዮች።

 

ዝቡቅቡቅ (ሰበቀ): ወፍራም፣ ለስላሳ፣ ለምለም፣ ማለፊያ እንጀራ። ዝቡቅቡቅ አለ: ወፈረ፣ ለሰለሰ፣ ወዛም ሆነ።

ዝቡጥቡጥ አለ: ተዝቦጠቦጠ። ዝቡጥቡጥ: የተዝቦጠቦጠ ብጥብጥ፣ ቡሖ፣ ጠሳ፣ ጠጅ፣ ቅቤ፣ ማር፣ ኑግ፣ ተልባ፣ ሰሊጥ።

ዝባዝንኪያም (ሞች): ኰተታም፣ ባለጣጣ። ዝባዝንኬ: የማይረባ ኰተት፣ ምናምን፣ ምናምንቴ፣ እንቶ ፈንቶ፣ ጣጣ።

ዝባድ: ጥርኝ ከምትባል አውሬ የሚገኝ የሽቱ ቅባት። (ጥርኝን ይመልከቱ)

ዝብ: የዘባ ድር፣ ለማጣ፣ ልምጥ፣ ቀጥታ የሌለው።

ዝብለላ: ዝፍዘፋ፣ መዘብለል። ዝብልል አደረገ: ዘበለለ። ዝብልል: የተዘበለለ፣ የታራ፣ ዐር፣ ኵስ።

ዝብርቅ (ድብርቅ): የተዘባረቀ፣ የተሳሳተ፣ ቅልቅል፣ ድብልቅ። ዝብርቅርቅ አለ: ድብልቅልቅ አለ፣ ተዘበራረቀ። ዝብርቅርቅ: የተዘበራረቀ ድብልቅልቅ።

ዝብብት: ዛቻ፣ ፉከራ፣ ፉክክር።

ዝብት: የፍግ ክምር።

ዝብትር: የተዘበተረ፣ ዝንትር።

ዝብዘባ: ንዝነዛ፣ ንትረካ፣ ጭቅጨቃ። ዝብዝብ: ንዝንዝ፣ ንትርክ፣ ጭቅጭቅ፣ ውዝግብ፣ እስከ የሌለው ነገር። ሁለተኛውን "" አጥብቀው ይናገሩ። ዝብዝብ: የተዘበዘበ፣ የተነተረከ።

ዝብድይ (ፍያል): እግራም ጣባ፣ ወይም ወጭት፣ የዝባድ፣ የለስታ ቅቤ መቀበያ ማስቀመጫ (ኢሳ ፷፭፡ )

ዝብጥር: ሥብጥር። ዝብጥርጥር አለ: ሥብጥርጥር አለ።

ዝተታም: ዝተት ለባሽ፣ አሸራጭ፣ ባለዝተት። ዝተት (ብዙ ቁጥር: ዝተቶች): ያልተሰፋ ነጠላ ማቅ። (በርኖስን ይመልከቱ)

ዝትዝት: የተዘተዘተ፣ ብጥስጥስ፣ ግትግት።

ዝኒ ከማሁ: ይህም እንደዚያው ነው። ዝኒ: ዝ፣ ይህ፣ ኒ፣ ም፣ ይህም።

ዝና (ዜነወ፣ ዜና): ወሬ፣ ነገር፣ ዝብዱ። "እከሌና እከሌ በዝና ይተዋወቃሉ" "ለዝና ሲሉ ቁም ነገር ሠሩ" ዝና ወዳድ (): ታሪክ ወይም ዝብዱ ወዳድ። "እንዲህ ሠራ፣ እንዲህ አደረገ" ልባል፣ ስሜ ይጠራ ባይ፣ ሐርበኛ፣ ጐበዝ፣ ጦረኛ። "ሆያ ሆዬ ጕዴ ዝና ወዳዴ" እንዲሉ ልጆች።

ዝናመ መዓት: የመዓት ዝናብ፣ የቁጣ ዝናም ኖኅ። ዝናመ ምሕረት: የምሕረት ዝናብ።

ዝናማ (ዜናዊ): ባለዝና፣ ስመ ጥር።

ዝናም: ዝናብ።

ዝናር (ሮች): የወታደር ቀበቶ፣ የጥይት ቀበቶ፣ የቀስት መያዣ። ምሳሌ፡ "ጠመንጃ ያለ ዝናር፡ ፈረሰኛ ያለ ጅራፍ አይሄድም።" በግዕዝ፣ ማንኛውም አይነት ቀበቶ ዝናር ይባላል። የወታደር መታጠቂያ (የጥይትና የቀለሕ ጐሬ)

ዝናሽ: የሴት ስም፣ "ዝናሽ ብዙ"

ዝናበ ከልክል: ጉዴላ፣ የከንባታ ሰው። እህል ሳይቀምስ ወደ ሰማይ አፍ እያለ በዘንግ ደመናን ግራና ቀኝ ይመራል፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ያደርጋል።

ዝናቡ: ዝናብ፣ የእርሱ ዝናብ።

ዝናባም: ባለዝናብ፣ ብዙ ዝናብ ያለበት አገር፣ ተራራ፣ ደን።

ዝናብ (ቦች)/ዝናም (ማት): ከባሕር የወጣ የሰማይ ውሃ።

ዝናት (ዝኅነት): ዕረፍት፣ ጸጥታ። ዝናት (ዝንየት): ድራት፣ ፍትወት፣ የዝሙት ሥራ።

ዝናኸ: የሰው ስም፣ "ዝናኸ ብዙ" "ያንተ ዝና፡ ዝናኸ ብዙ ነው።"

ዝናው ተሰማ: ታላቅ ሥራው በሰው ሁሉ ጆሮ ፈሰሰ፣ ተደመጠ (ማቴ 4:24) ዝናው: የሰው ስም፣ "የእርሱ ዝና" ማለት ነው።

ዝናድ: አስቴ።

ዝናፊ: ትርፍ፣ ዕላፊ፣ የቃል ዝንፋት (ልክ እንደ ርዝማኔ)

ዝንቅ አለ: ቅልቅል አለ፣ ተቀላቀለ ወይም ተዘበራረቀ። ዝንቅ: የተቀላቀለ፣ የተዘበራረቀ፣ ግራ የተጋባ፣ ቅይጥ፣ ውጥንቅጥ፣ ድብልቅ፣ ዝብርቅ።

ዝንበ ከልክል: ዝንብ የማያስገባ፣ ሌማት መሶብ።

ዝንበላ (ጽናኔ): መዘንበል (2ጴጥ 2:12)

ዝንባሌ: ዝኒ ከማሁ (ያው ማለት ነው)

ዝንባም (ሞች): ባለዝንብ፣ ዝንብ የወረረው፣ ፈዛዛ፣ ፊቱን የማያጥብ፣ የማያጸዳ። ዝንባምነት: ዝንባም መሆን፣ ፈዛዛነት። (ተለለ ብለው ተላላን ይመልከቱ)

ዝንብ (ቦች): የታወቀ ተንቀሳቃሽ፣ በክንፍ የሚበር፣ የሚንዣበብ። በአረብኛ "ዝቡብ" ይባላል። ዝንብ ቢሰበሰብ መግላሊት አይከፍት: ብዙ ደካማ አንዱን ኃይለኛ አያሸንፍም።

ዝንብል (ድኑን፣ ጽኑን): የዘነበለ፣ የተዘነበለ።

ዝንቦ: የበር ላይ ጣራ። (እድሞን ይመልከቱ) ዝንቦ: የገና ስድብ፣ ቃለ አኅስሮ። "ዕሽ እነዝንቦ" እንዲል የገና ተሳዳቢ። "ዝንብ ሆይ" ማለት ነው።

ዝንተ ዓለም: ድንተ ዓለም።

ዝንት ያማርኛ: ድንት ድልት ግእዝ ነው።

ዝንት: የድሮ የአማርኛ ቃል ሲሆን "ይህ" ማለት ነው። ለምሳሌ፣ ዝንት ዓለም ማለት "ይህ ዓለም" ወይም "ዘላለም" ማለት ነው። በአጠቃላይ፣ ዓለም እና ዘላለም ዝንት ዘላለም ዓለም ዘላለም ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው። (ስለ ዓለም ሁለተኛ ትርጉም ለማየት የተሰጠውን መመሪያ ይመልከቱ)

ዝንት: ድንት

ዝንትር: የተነከሰ፣ የተቀደደ፣ የታኘከ፣ ወይም በሚንጨባረቅ ሁኔታ የተበላ።

ዝንትር: የተዘነተረ፣ ንክስ፣ ዝብትር፣ ቡጭቅ፣ ቡትርፍ።

ዝንኵርኵር አለ: ሙሉ በሙሉ ጠፋ ወይም ትርምስ ውስጥ ወደቀ። በተጨማሪም ብልሽትሽት አለ።

ዝንኵርኵር: ሙሉ በሙሉ የጠፋ ወይም ያለቀ ነገር።

ዝንኵርኵር: የተዘነኳኰረ።

ዝንኵት: የዘነከተ፣ ዘንካታ

ዝንኵት: ደግ ወይም የዋህ የሆነ ሰው፣ ዘንካታ

ዝንኪላ መሰለ: ቀላ፣ ደም ለበሰ (የዓይን)

ዝንኪላ: ጕመሮና ቀንጠፋ ዓይነት እንጨት ሲሆን ፍሬው ቀይ ነው።

ዝንድ: የበር ብረት፣ የመዝጊያ መሸጐሪያ። ረዥም ሸንገል ሲሆን ጫፍና ጫፉ እንደ ወገል ሜንጦነትና ቀለበትነት አለው።

ዝንጀር (ሪት): ዝኒ ከማሁ። ዝንጀር ተባቱ ሲሆን ዝንጀሪት እንስቲቱ ወይም ታናሽቱ ናት።

ዝንጀር ጐሹ: በጥይት የሞተ ገመር

ዝንጀሮ (ዎች): ፊቱ ሰው የሚመስል አውሬ። ጥቁርና ነጭ፣ አፍንጫ ዐዳ፣ በገደል ላይ ዐዳሪ። ተባቱም እንስቱም ዝንጀሮ ይባላል (2ዜና 9:21)

ዝንጅብል (ሎች): ሥሩ ለወጥ ቅመም የሚሆን፣ እንደ በርበራ የሚያቃጥል የተክል ስም። "ዝንጅብልና ኰረሪማ" እንዲሉ።

ዝንጉ: የዘነጋ፣ የረሳ (ምሳ 13:17 ኢሳ 3:10, 11)

ዝንጕር: ሽልም

ዝንጕርጕሪት (): ሽልምልሚት (ዘፍ 37:23, 32)

ዝንጕርጕር (ሮች): ዥጕርጕር ሽልምልም

ዝንጕርጕርነት: ነጭነትና ጥቁርነት

ዝንጉነት: ዝንጉ መሆን (ኢሳ 9:18)

ዝንጋታ: ርሳታ ዕጦት

ዝንግ: የተዘነጋ፣ የተረሳ።

ዝንግልግል አለ: ከከ።

ዝንግልግል: ከከ፣ ሙክክ ያለ።

ዝንግሪር: ትልቅ ጠላ ጋን ሳሌ

ዝንግት: ርስት

ዝንጎች: ዝንጉዎች የዘነጉ፣ የረሱ (ኢዮ 34:18 ኢሳ 14:5)

ዝንጠላ: ፍንቀላ ነደላ

ዝንጠፋ: ዥምግጋ ሽምጠጣ ቈረጣ

ዝንጣፊ: የተዘነጠፈ፣ ተምር በለስ ወይን የሌላውም ተክል ዘለላ ቍራጭ ግንጣይ (ዮሐ 12:13)

ዝንጣፎች: ቍራጮች ግንጣዮች (ራእ 7:9)

ዝንጥል አለ: ብስት ቅድድ አለ።

ዝንጥል ጉፍታ: የተበሳ፣ የተቀደደ።

ዝንጥልጥል አለ: ሽርክትክት አለ።

ዝንጥልጥል አደረገ: ብስትስት አደረገ።

ዝንጥልጥል: የተዘነጣጠለ፣ የተበሳሳ፣ ሽርክትክት

ዝንጥፍ: ዝኒ ከማሁ ዝንጣፊ ዥምግግ

ዝንፋት: ትርፍ የመሆን ሁኔታ፣ ትርፍ፣ ርዝመት።

ዝንፋት: ዝኒ ከማሁ (ማለትም ትርፎች፣ ርዝማኔ)

ዝንፍ አለ: ረዘመ፣ ወሰንን ወይም መለኪያን አለፈ፣ ትርፍ ነገር ተናገረ።

ዝንፍ: ልዩ፣ በልጧል።

ዝንፍ: የዘነፈ፣ የበለጠ።

ዝክር (ሮች): የአምላክ፣ የማርያም፣ የመላእክት፣ የጻድቅ እና የሰማዕት በዓል በሚውልበት ቀን የሚደረግ ድግስ ወይም የስም መጠሪያ።

ዝክዘካ: ንቅንቅያ ዝርገፋ

ዝክዝክ (ዝሕዙሕ): የተዘከዘከ፣ ዝርግፍ፣ ዝርዝር፣ ሽክሽክ።

ዝክዝክ አደረገ: ዘከዘከ (እንደገና)

ዝውር: የተዘወረ።

ዝውትር: የተዘወተረ።

ዝየራ: ጕብኝታ ዘፈን ምስጋና

ዝየና: ሽልማት

አይዙር: 772 . ሰባት ሰዓት የነገሠ የኢትዮጵያ ንጉሥ።

ዙረት: ምለሳ መዞር ዑደት (መዝሙር 19:6 2 ተሰሎንቄ 3:11)

ዝየዳ: ጭመራ

ዝዪ (ዮች): የባሕር አሞራ ዋነኛ ሲሆን በጋልኛ ዳክዬ ይባላል። ወደ ውስጥ የምትጠልቀው ይብራ ናት።

ዝይን: የተዘየነ ወይም ያጌጠ ሽልም

ዝዶም: ቈላ ዛፍ

ዝገት: እድፈት ጥቍረት (ምሳ፳፭፡ ፬፡ ሕዝ፳፬፡ -፲፩፡ ፲፪፡ ያዕ፭፡ )

ዝጕን: የዘጐነ፣ ጥቍር ገላ ብልዝ ጥርስ ዐይን

ዝጉዳ: ብርሌ ባለአረንጓዴ ቀለም ወይም ሌላ ዓይነት።

ዝጋግ (ትግ.): በዝግታ ዐንገትን የሚያበላሽ ምሽሮ ወይም ነቀርሳ

ዝግ (ዝጉሕ): የተዘጋ፣ ድፍን ደንቆሮ ውለናም

ዝግ አለ: ቀስ አለ።

ዝግ: ቀስ አለመፍጠን

ዝግ: ቀስ ዘገገ

ዝግ: ከሰው ተለይቶ በኣት ተከቶ የሚኖር ባሕታዊ መናኝ መነኵሴ

ዝግ: የተዘጋ፣ ዘጋ

ዝግራ (ሥግሪያ): ወንከር ወንከር ድንኵል ድንኵል ማለት፤ ዥግርኛ መኼድ መሥገር "ታቱ ዝግራ" እንዲሉ።

ዝግባ (ዘግባ): ብዙ ቅጠልና ዐጽቅ ያለው እንጨት ስም

ዝግብ (ዝጉብ): የተዘገበ፣ ስብስብ ክምቹ ጥርቅም ድልብ

ዝግብ: በተጒለት ያለ ወረዳ የሆነ አገር ስም

ዝግተኛ (ኞች): ባለዝግታ ዝግ ባይ

ዝግታ: ቀስታ

ዝግታ: ቀስታ፣ ዘገገ

ዝግት (ዝግሐት): መዝጋት

ዝግት አለ: ግጥም ክድን አለ።

ዝግትግት አደረገ: ግጥምጥም ክድንድን አደረገ።

ዝግን (ትግ. ዝግኒ): ቅቤና ድልኸ ጋር የታመሰ ሥጋ ወጥ በእጅ፣ ጭልፋ እንጀራ ተዘግኖ የሚበላ ክትፎ

ዝግን አደረገ: ዘገነ፣ ቃም አደረገ።

ዝግን: በጨው የተቀቀለ መተሮ እየተዘገነ የሚታደል።

ዝግንትላም: ዝግንትል ለባሽ ባለዝግንትል ወይም ተሸካሚ እብድ ሰው

ዝግንትል (ዝግን ትል): የተቀዳደደ፣ የተበጫጨቀ ጨርቅ ስልቻ ደላጎ ባለ ብዙ ተባይ

ዝግንን አለው: አስፈራው፣ አኹን አኹን ኣለው።

ዝግንንታ (ሰዖዛዝ): ስቅጥጥታ

ዝግኝ (ኞች): የተዘገነ፣ ጥርኝ (ዘኍ፳፭፡ ፳፮)

ዝግዘጋ: ርዝማኔ ረዥምነት

ዝግዝግታ: ዝክዘካ

ዝግየታ: ዝግይት ቈይታ

ዝግዩ: የዘገየ፣ የቈየ።

ዝግይት አለ: ዘገየ።

ዝግጁ (ዎች): የተዘጋጀ፣ ድርጁ ስንዱ

ዝግጅት: ድርጅት መሰናዶ

ዝግጅቶች: ድርጅቶች

ዝግጣ ዕንጨት: ድግጣ

ዝጠና: መዘጠን

ዝጥር: የተዘጠረ፣ ንፉግ ውጥር

ዝጥን: የተዘጠነ ወይም ዘጠኝ የሆነ።

ዝፍቅ: የተዘፈቀ፣ የተነከረ፣ ነከርት ሞኝ (ለምሳሌ: "ዝፍቅ ቂል" እንዲሉ)

ዝፍት : ሰነፍ ሴት ዝቃጭ አተላ ማለት ነው።

ዝፍት: የእንጨት፣ የሙጫ፣ የቅጥራን መጣበቅ የሚሆን (ኢሳይያስ ፴፡ ፬፡ )

ዝፍዘፋ: መንከር ማፍሰስ

ዝፍዘፋ: ነከራ ድፍድፋ

ዝፍዝፍ: የተዘፈዘፈ፣ ንክር ድፍድፍ ርጥጥ ውዝፍ

ዝፍዝፍ: የታነከረ፣ የታጠበ፣ እርጥብ፣ የፈሰሰ።

ፈንቃላ: የተፈነቀለ።

ዞላ (ዝሑል): ልል ደካማ አቅመ ቢስ ሴታውል (የግእዝ ቃል)

ዞላ ዋለ: ቦዘነ ሥራ ፈታ

ዞላ: ቦዘነ ሥራ መፍታት

ዞላ: ቦዘነ ዘለለ

ዞልዞል አለ: ዝኒ ከማሁ (ያው ማለት ነው)

ዞማ: መራቤቴ ክፍል ያለ ቀበሌ

ዞማ: ዝርግ፣ ማለፊ የሆነ ረዥም ራስ ጠጕር ቶሎ ቶሎ የሚያድግ፣ የሚገሠግሥ።

ዞረ (ዘዊር ዞረ): ተንቀዋለለ፣ ተንከዋረረ፣ ዐወደ፣ በዙሪያው ኼደ፣ ከበበ፣ ታጠፈ፣ ተጠመጠመ፣ ተጠመዘዘ፣ ተመለሰ፣ መንገድ ለቀቀ ማለት ነው።

ዞረ: ሠሣረ፣ ተሽከረከረ።

ዞረ: በዙሪያ ኼደ (መዝ፳፮፡ )

ዞረ: ዐወደ።

ዞረ: ደግሞ ሰከረ፣ አበደ፣ ተናወጠ (ራሱ) ማለት ነው።

ዞረሬ: የቀድሞ ምንጃር ስም።

ዞረሽ ዕቀፊኝ: ከባሕር የመጣ ድር ኰምታሬ የሆነ ፈትል ስም

ዞሪቴ: ዝኒ ከማሁ፣ ሶራዊት

ዞሪት (ሶሪት): ጀርባዋ ጥቍር፣ ደረቷ ነጭ፣ ክንፏ ቀይ የሆነች የምታምር ወፍ። (በአረብኛ ዙራ በጋልኛ ጆሮ ትባላለች)

ዞሮ: ተመልሶ፣ ተጠምዞ ማለት ነው። ግጥሙ "በየት ዞሮ መጣ በየት ዞሮ፡ የገደል ዝንጀሮ" ይላል። "ዞሮ ገባ" እንዲሉ።

ዞብል: የጁ አውራጃ ያለ ተራራ

ዞግ (ዘውግ): ወገን ነገድ (ስለ ዘወገን ለመመልከት የተሰጠውን መመሪያ ይመልከቱ)

ዞግ: ሰበብ ምክንያት ወገን ሳቢያ "የዞግ ዞግ" እንዲሉ።

ዞጠ (ሶጠ): አዞጠ ማለት ገረፈ መታ ደበደበ መደወተ

ዞጲ (ዘኢትዮጵያ): አፍሪቃዊ በኢትዮጵያ የሚበቅል ጥቍር ዕንጨት ሲሆን ዋጋው ክቡርና ውድ የሆነ (ኢሳ፵፩፡ ፲፱) (በግእዝም አብኖስ ይባላል)

ዞፍ: እንግዴ ልጅ (ስለ ወዘፈ ለመመልከት የተሰጠውን መመሪያ ይመልከቱ)

ዞፍ: ከወላድ ማሕፀን እንግዴ ልጅ ጋር የሚወጣ ብዙ ልፋጭ ንቍላል ውሃ ጣዝማ ማር ከረጢት በምድር ላይ የሚወዘፍ።

ዞፍ: ማሕፀን ልፋጭ

አለ (ትግ. ዘውሐ): አሰፋ፣ ሰፊ አደረገ፣ ተሰጣ፣ ተዘረጋ፣ አለ፣ ተኛ። (ስለ ዟይን እና ዘውን ለመመልከት የተሰጠውን መመሪያ ይመልከቱ)

: ዘግ ዘፍ መሰጠት መዘርጋት

ዟሪ (ዎች): የዞረ፣ የሚዞር፣ የሚንቀዋለል፣ ዘዋሪ ከውታታ ቀውላላ አገር ላገር ኻያጅ አግዳማይ ማለት ነው።

ዟይ (ዝዋይ): ሀገርና ባሕር ስም ሲሆን ባሩሲ ወረዳ ውስጥ ያለ ባሕር ነው። በውስጡ ካለው ደሴት ጋር አንድ ላይ ዟይ ተብሎ ይጠራል። "" ብሎ የተሰጣ፣ የተዘረጋ፣ ከአምስት ደሴት የገጠመ ውሃ ማለት ነው። (ስለ ላቂን ለመመልከት የተሰጠውን መመሪያ ይመልከቱ)

No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ