ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ሸ፡ የሠሠ ወራሽ ዲቃላ ባማርኛ ። (ማስረጃ)፡ ነገሠ - ነጋሽ፡ ዐሠሠ - ዐሣሽ፡ ቀደሰ - ቀዳሽ፡ ወረሰ - ወራሽ ። በዕብራይስጥና በሱርስት በዐረብ ቋንቋ ግን "ሸ" መደበኛ ፊደል እንጂ ተወራጅ አይዶለም ። በግእዝም ከሠ ላማ በፊት ከዋናነት በቀር ምክትልነት አልነበረውም ይባላል፡ ይኸውም ሠውት "ሠ" ነው ።
ሸ) አሸ (ዠ)፡ በውስጥና በውጭ እሳት አነደደ/ተኰሰ/አገነፈለ (ባዲስ ሸክላ መዠመሪያ ቀቀለ፡ ምጣድን ብዙ ጊዜ ዐሠሠ/ወለወለ ከዚያ በኋላ ጋገረ) ። (መሬት አሸ)፡ ከሰው ኹሉ በፊት ሞተ/ተቀበረ (አቤል - ዘፍ. ፬፥፰) ።
ሸሐኝ ነቀርሳ ኪንታሮት የመሰለው ኹሉ ("(ስም)")
።
ሸሐኝ/ሻሕኝ (ዕብ ሺሒን)፡ በአፍንጫና በፊት ላይ የሚወጣ ደረቅ ቍስል እሾኻም ። "ጭንቍን" ተመልከት ።
ሸኅ (ኆች)፡ የአስላም ቄስ (የቍርኣን ካህን ሰባኪ) ።
ሸኅ አንበሶ፡ የዛር ስም (ያረብ አገር...ዛር) ።
ሸሖገሌ፡ የነገድ ስም (በወለጋ ክፍል ያለ ሻንቅላ) ። ገና
"ጀ" ተወራራሽ ስለ ኾኑ "ሸሖጀሌ" ተብሎም ይጠራል።
ሸለለ (ሰለለ)፡ አቅራራ ጃሎ መፃን ኣለ (የጦር ግጥም ገጠመ) ።
ሸለለ፡ ሸለመ
ሸለለ፡ ሸለተ ሸለፈ ሸነገለ ።
ሸለለ፡ ሸረረ ።
ሸለለ፡ ሸደሸደ ወሰወሰ ቶረበ አያያዘ አጋጠመ ሰፋ (ዘፍ. ፫፡ ፯) ።
ሸለለ፡ ጠፍ ባድማ ባዶ አደረገ ።
ሸለሊት፡ ሸረሪት ። ወደ ፊት እንሽላሊትን እይ ።
ሸለሊት፡ ያውሬ ሽንት የበሰበሰ ጭቃ ። "የእግሬን ጣት ሸለሊት ቈረጠችኝ"
እንዲል ባላገር ።
ሸለል አለ፡ ሸረር አለ (በፍጥነት ተሳበ ተጐተተ) ።
ሸለል፡ ዕዳሪ ኵስ ጓሮ ቤት ዐይነ ምድር ሠሣራ ። "የብዔልንም ቤት አፈረሱ ሸለልም (ጕድፍ መጣያም) አደረጉት"
(፪ነገ. ፲፡ ፳፯) ።
ሸለመ ("ደረበ ከ ደነ ሸፈነ ሸሸገ ደበቀ ሰወረ ከለለ አልባሽ ") ("ሾች") ።
ሸለመ (ዐረ. ሰለመ/ከፈለ)፡ ሣለ ቀረጸ መሰለ (ሐረግ ጣለ ነቀሰ በቀለም አስጌጠ አዥጐረጐረ - ኢሳ. ፶፬፡ ፲፩) ። ("ምርትን ሸለመ")፡ የአክሊል ምልክት አደረገ (ቁመቱን ዙሪያውን በላይዳ አሠመረ) ።
ሸለመ፡ ሽልማት ሰጠ እለበሰ አንቈጠቈጠ ። ያ ለሠራ ሰው ብድሩን ለመክፈል ሸለመ ። በቀላል ዐመመና ተወ ወጣ ለቀቀ (በሽታ ከብትን ፈንጣጣ ሰውን) ።
ሸለመ፡ ጠቃጠቆ አደረገ (ፊትን) ።
ሸለም፡ የዘንባባ የኮባ የንሰት የሙዝ ሙሽራ ውልብልቢት ።
ሸለሸለ (ሰለሰለ)፡ ገመሰ በቀበቀ (በዝቶ የበቀለ አገዳን ነቀለ) ።
ሸለሸለ፡ ሻም
ሸለሸል (ሎች)፡ የዱር ኵበት ። ከሸ...ለል ጋራ አንድ ነው ።
ሸለቀቀ (ለቀቀ)፡ ቀደደ ላጠ ገፈፈ (ከውስጥ አወጣ ቍርዝን) ።
ሸለቀቀ፡ አጠበበ አቀጠነ ።
ሸለቆ (ዎች)፡ የተራራ የገደል የግንብ መጋጠሚያ (የዠርባ ወንዝ መሳይ ጠባብ የዳገት መንገድ - ነሐ. ፫፡ ፳፬-፳፭) ።
ሸለበ (ሰለበ)፡ ተከደነ ተጨፈነ (ዐይኑ ተዠመረ እንቅልፉ) ።
ሸለተ (ሰለተ)፡ ቀረፀ ቈረጠ (ጠጕርን) ።
ሸለተ፡ ዘበተ አታለለ አሳተ ።
ሸለተ፡ ጠረበ ላገ አሾለ (ዕንጨትን) ።
ሸለገ፡ ዐሰበ ለካ አሰላ ገመተ (ገመገመ ነፋ - በቅሎ ሲጭኑት ቅናት እንዳያጠብቀው ሆዱን ይሸልጋል - ይነፋል) ።
ሸለግ፡ ስሌት ሒሳብ (በገንዘብ ፈንታ ለንጉሥ የተሰጠ ልጅ) ።
ሸለፈ (ሰለፈ)፡ እሣሣ አቀለለ ።
ሸለፈ፡ አታለለ ሸነገለ (ካንገት በላይ ተናገረ አላገጠ - ኢሳ. ፴፯፡ ፬ - "እከሌ እንዲህ ያለኸ ሲሸልፍኸ ነው")
።
ሸለፈታም፡ ልንበጣም ሽፍን ።
ሸለፈት (ቍልፈት ከተማ ነፍስት)፡ ልንቡጥ ወሸላ ።
ሸለፈፈ፡ ገለፈፈ ላጠ ዐማ ።
ሸለፈፍ/ሸልፋፋ፡ የተሸለፈፈ ።
ሸላ (ሰላ)፡ ሾላካ የዱር ኣውሬ (የድ...መት ወገን የቆቅና የዶሮ ጠላት መልከጥ ቍር ዐፈርማ) ። ትግሬ ሐባብም "ቀጠነ" ሲል "ሸልሐ" ይላልና "ሸላ" ከዚህ ሲወጣ ይችላል ።
ሸላ፡ ተንኰለኛ ሰው መኼጃ የማይታወቅ እባብ ።
ሸላለመ፡ መላልሶ አስጌጠ አለባበሰ ።
ሸላለተ፡ ቈራረጠ ጠራረበ ዐናነጠ ።
ሸላሚ (ዎች)፡ የሸለመ/የሚሸልም (አስጊያ አንጥረኛ - "ጃን ሸላሚ"
እንዲሉ) ።
ሸላች (ቾች)፡ የሸለተ/የሚሸልት (ቈራጭ - ፩ሳሙ. ፳፭፡ ፲፩፡ ኢሳ. ፶፫፡ ፯፡ ግብ. ሐዋ. ፰፡ ፴፪) ።
ሸላች፡ አሿይ አታላይ አሳች ።
ሸላይ (ዮች)፡ የሸለለ/የሚሸልል (አቅ...ራሪ ጌትዬ ወይም ሌላ) ።
ሸላይ፡ ሸድሻጅ ወስዋሽ ።
ሸላጊ፡ የሸለገ/የሚሸልግ (ገማች ገም...ጋሚ) ።
ሸላፊ፡ የሸለፈ/የሚሸልፍ (አታላይ ሸን...ጋይ) ።
ሸሌ፡ መጠማጥ ።
ሸሌ መጠማጥ፡ ሸሌ ሰልቶ ሾልኮ የሚኼድ መጠማጥ ጠቢ መጥማጭ ማለት ነው ። ይኸውም ሊታወቅ በባላገር የፍየልን እግር በዥራቱ እየጋዳ ጡቷን ይጠባል ይባላል እሱም ሽንጣም ዥራተ ረዥም እግሮቹ ዐጫጭሮች ናቸው ። ሸላ ትንሹ መጠማጥ ትልቁ ።
ሸሌ/ሸላዊ፡ የሸላ ወገን ።
ሸልቃቂ፡ የሸለቀቀ/የሚሸለቅቅ (ቀዳጅ ገፋፊ አውጪ) ።
ሸልቋቋ/ሸልቋቍቻ፡ ጠባብ ሱሪ ሠላጤ ቀልቀሎ (ባንድ እግር የወጣ ስልቻ) ።
ሸሎ በርደዶ፡ ልብ ራስ የሚመታ የሚቀጠቅጥ ስካሩ የጸና የበረታ መጠጥ ማለት ነው ። "በረደደን"
እያ...በረደዶ ለሸሎ ቅጽል መኾኑን አስተውል ። የሸሎ ምስጢር በደም ሥር መስላትን ያሳያል ።
ሸሎ/ሾላ
ሸመለ፡ ሽመል ነጠቀ መዘዘ (በሽመል መታ ደበደበ) ።
ሸመመ (ዘመመ)፡ ዘነበለ ዐነከሰ ።
ሸመሸመ (ሰመሰመ)፡ ጤፍን እቋተ ኣጐረሠ (ከረተፈ ሸረከተ በቀላል ፈ) ።
ሸመሸመ፡ ብዙ ቃመ ።
ሸመቀ፡ በደን በጐድጓዳ ስፍራ ተቀመጠ ተደበቀ ደፈጠ (አደባ ለመውጋት ለመግደል - ዘፀ. ፳፩፡ ፲፫፡ ፪ሳሙ. ፳፫፡ ፳፫) ።
ሸመቀቀ፡ ሳለ አሳጠረ ወር አደረገ ጨመደደ (እግርን ሸበሸበ አቀራረበ አጢጋጋ አጠበበ - የከረጢትን አፍ ወገብጌን - ፪ኛው ቃል ተቀጥላ ነው) ።
ሸመቀቀ፡ ሸመተ
ሸመቀቅ/ሸምቃቃ (ቆች)፡ ጨመ...ደድ ምዳዳ (ትክክል የማይረግጥ) ።
ሸመቃ/ሽመቃ፡ ደፈጣ ደባ (ኤር ፶፩፡ ፲፪) ።
ሸመተ፡ እኸልን በገንዘብ ገዛ (ለብር ሼጠ ለወጠ አቀና -
"መከራ ሸመተ በሽታ...
ሸመተረ (ሸመተ መተረ)፡ ሸነቈጠ...ገረፈ ።
ሸመታ፡ ልወጣ ግዥ ።
ሸመነ (ሰመነ)፡ መንን በመርገጫ አወጣ አወረደ (መወርወሪያን ከቀኝ ወደ ግራ ከግራ ወደ ቀኝ ወረወረ ሸማ ሠራ) ።
ሸመደ፡ ሸመጠጠ
ሸመደ፡ ወገብን ዝተገተ ሰበረ አነከተ ጐተተ ።
ሸመድማዳ/ሽምድምድ፡ የተሽመደ...መደ (እግረ ወልጋዳ) ።
ሸመገለ፡ ሸበተ አረጀ ሰመግ መሰለ (ዘፍ. ፲፰፡ ፲፪) ።
ሸመጠ) አሸመጠ፡ አኰረፈ ኣዶበረ ። "ሰመጠን"
አስተውል ።
ሸመጠረ (ሸመተረ)፡ አለልክ ሓመ...ጠጠ (ዦሮ ወጋ) ።
ሸመጠረ፡ ሸመቀ
ሸመጠጠ (መጠጠ)፡ ጠጣ ጨለጠ (ዥው አደረገ ለጋ ለገሸ ፊረሰ በፍጥነት) ።
ሸመጠጠ፡ መዠመሪያ ሽሩባ ሠራ ።
ሸመጠጠ፡ ሮጠ ጋለበ
("ዦሮውን ሸመጠጠ" - ወደ ኋላ አለ መለሰ) ።
ሸመጠጠ፡ ቀኙን ወይም ግራ እጁን ተመረኰዘ (ገላውን እሰየፈ ኳስ እንዳይመው) ።
ሸመጠጠ፡ ተራ መናኛ ፈትልፈተለ ።
ሸመጠጠ፡ ዐጥር ዐጠረ አዋሰበ (ክት ክታን አጋምን ከግርግር ጋራ) ።
ሸመጠጠ፡ ዠመገገ እሸትን ፍሬን ።
ሸመጠጠ፡ ድርቄን በባሕር ዐረብ አስጌጠ ሸለመ ደጐሰ ።
ሸመጠጠ፡ ፀበል ዋሸ ቀጠፈ ።
ሸመጥ፡ ጥቍርና ቀን ስንዴ ።
ሸማ፡ ልብስ ሸመነ ።
ሸማ መሥሪያ፡ የሸማኔ ጕድጓድ ።
ሸማ፡ በየፈርጁ ይለበሳል (ሰው በየጠባዩ ይወደዳል) ።
ሸማ ዐጣቢ፡ ሸማ የሚያጥብ/የሚያጐርፍ/የሚለቀልቅ ።
ሸማ ኩታ ነጠላ ጋቢ ልግም በገላ ዝቅዝቅ ጃኖ ድርብ ቀሚስ ኪታ ግምጃ መጐናጸፊያ እጅ ጠባብ ጥብቆ ካባ ለምድ ለምደኛ ቡልኮ በርኖስ ዝተት ደበሎ ዳባ ዐጽፍ ሌጦ ሱሪ ("የውስጥ ልብስ የላይ ልብስ የክት ልብስ የሠርክ ልብስ የሥራ ልብስ የበዓል ልብስ ") ።
ሸማ፡ የተሰፋና ያልተሰፋ ልብስ ዐርበ...
ሸማ ፈጅ፡ በልብስ ስፌት ውስጥ ያለ የፈትል ድቃቂ ዐቧራ ።
ሸማመተ፡ ገዛዛ ለዋወጠ ።
ሸማማ፡ የሸመመ (ዐንካሳ) ።
ሸማሜ፡ ሪሰ ትልቅ ስንዴ ። "ሸማሜ ያሠኘው በራሱ ክብደት ወዳንድ ወገን መዝመው ነው"።
ሸማሜ፡ የሸማማ ዐይነት ።
ሸማቂ (ቆች)፡ የሚሸምቅ (ደፋጭ አድቢ - ኢዮ. ፩፡ ፭) ።
ሸማች (ቾች)፡ የሸመተ/የሚሸምት (እኸል ገዢ ሸያጭ) ።
ሸማኔ (ሸማኒ)፡ የሸመነ/የሚሸምን (ሸማ የሚሠራ) ።
ሸማጥር፡ በንግሥት በይተጊ ዙሪያ የሚያዝ የሸማ ዐጥር (በመካከሉ ዐልፎ ዐልፎ ዘንግ አለበት) ።
ሸማጥር፡ የቤተ መቅደስ መጋረጃ (ዘኍ. ፫፡ ፳፮) ።
ሸምሸም (ትግ/ሐባ)፡ አሸዋ (ሽም ሽም - ጤፍ የሚመስል) ።
ሸምሸር፡ ሸጢን የማይነቅዝ ዕዕ (የበረሓ ግራር ሀሎ - ዘፀ. ፳፳፭፡ ፲, ፲፫) ። አርዝ ልምጭ ዝግባ በለጥ ወይም ጥቍር ዕንጨት ዞጲ (ሕቍ) ዋንዛ ኮሶ ሰንደል ጐቢል ታቦት የሚኾን ።
ሸምሻሚ፡ የሸመሸመ/የሸመሽም (አጕራሽ ከርታፊ ሸርካች) ።
ሸምቀቆ (ዎች)፡ የበሬ ያውሬ የወፍ መያዣ ማነቂያ ወጥመድ (ከቀላድ ከፍር ከጭራ የተበጀ - በግእዝ "ፀንፈርት" ይባላል - "ሸምቀቆ ማጡኔ")
።
ሸምቃቂ፡ የሸመቀቀ/የሚሸመቅቅ ።
ሸምታሪ፡ የሸመተረ/የሚሸመትር (ሸን...ቋጭ ገራፊ) ።
ሸምን፡ ከደብረ ሊባኖስ በስተቀኝ ቀበሌ ያለ ታናሽ ወንዝ (ትርጓሜው
"ሸማ ሥራ" ማለት ነው - ገድለ ተክለ ሃይማኖት ፈለገ ሸምን ይለዋል) ።
ሸምጣራ፡ ሖምጣጣ ።
ሸምጣጭ፡ የሸመጠጠ/የሚሸመጥጥ (ሯጭ ሽምጥ ኦሮቢ ዝምጋገ) ።
ሸሞረ (ሰመረ/ፀመረ)፡ ጠቀሰ (ጓጐጠ ወ...አነ አተ) ።
ሸሞረ፡ አጣምሮ ሰደበ ። ፱ኛውን
"ሰመረ" እ!
ሸሞነ) ኣሽሞነሞነ፡ በሸማ ሸፈነ ኣከናነበ (አነሰነሰ እንዳሻንጕሊት አደረ - "የባለጌ ግጥም - ሰሞነኛ አሽሞነሞነኛ")
።
ሸረሞጠ፡ ኣመነዘረ ሴሰነ ቀነዘረ ጐ...ደለ ።
ሸረሞጠች፡ ሴሰነች
("አንተ ውጣ እንተ ግባ ኣለች") ።
ሸረረ (ሰረረ)፡ ወጣ ታዘለ ።
ሸረረ፡ ሸረሸረ
ሸረረ፡ ተነኰለ (ተንኰል ሠራ አደረገ) ።
ሸረሪት (ቶች)፡ የተንቀሳቃሽ ስም (በፈትላ መሰላልነት ከላይ ወደ ታች የምትወርድ ከታች ወደ ላይ የምትወጣ ተሐ...ሸረሪት) ።
ሸረሪት፡ ምስር ዐኝኮ ሲተፉበት የሚድን ቍስል ስም
("ሸለለ" ብለኸ "ሸለሊትን" እይ) ።
ሸረሪት፡ ዋሲት ። ዳግመኛም በዱር ዕንጨት ላይ ከቀኝ ወደ ግራ ከግራ ወደ ቀኝ ሌሊት ስታደራ ታድራለች ። የግእዝ ስማ
"ሣሬት" ነው ።
ሸረሪቶች፡ የዘር የነገድ ስም
("ከሸሪሪት ትውልድ አለን" የሚሉ ሰዎች - እነዚህም ሸረሪት አይገድሉም ሸረሪት በሚባለው ቍስል ላይ ምስር ይተፋሉ - ዋና ስማቸው "እነሴ" ነው) ።
ሸረር (ጐዣም)፡ ፈር ።
ሸረር አለ፡ እባብኛ/ሸረሪትኛ ኼደ
("ሀወር" አለ) ።
ሸረር፡ የቀበሌ ስም (በቡልጋና በደብረ ሊባኖስ ቈላ በስተደቡብ ያለ የሥላሴ ኣጥቢያ ባለሸንተረር) ።
ሸረሸረ (ትግ. ሸርሸረ፡ መገዘ)፡ በረበረ ፈረፈረ ነደለ አፈረሰ ። "ሰረሰረን" ተመልከት (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሸረሸር/ፈረፈር፡ ፈፋ ጕድባ ።
ሸረቈጠ፡ ተሰበሰበ ቀለጠፈ (ባለባበስ ባቀማመጥ -
"ሸነቀጠን" እይ) ።
ሸረበ (ዐረ)፡ ሰቸ ("ረበን" እይ) ።
ሸረበ፡ ፫ቱን/፬ቱን ገመድ ባንድነት ወደ አንድ አደረገ (ደበለ ጠሞረ ደረበ - ሹርባና ሽራብ ሠራ ታታ) ።
ሸረተተ) አንሸራተተ፡ አዳለጠ እንሻተተ (እግርን ነቀለ ጣለ በቅምጥ ወይም በዠርባ ቍልቍል ወሰደ ኣወረደ - እኻልን ከቍና ላይ በቶሎ ገለበጠ) ።
ሸረተት/ሸርታታ፡ ተዳፋት (ዐፈር...ገደል) ።
ሸረኛ (ኞች)፡ ክፋተኛ ተንኰለኛ መሠሪ ሰበበኛ ።
ሸረከ (ሠረከ)፡ ወደደ ዐበረ ገጠመ (አንድ ኾነ በሥራ በንግድ) ።
ሸረከተ፡ ሳያደቅ ፈ... ።
ሸረከተ፡ ቀደደ ዘረከተ ።
ሸረከት/ሸርካታ/ሽርክትረከተ፡ ቅድ...የተሸ ።
ሸረክራካ/ሽርክርክ፡ የተሽረከረከ (ፍ...ርክርክ) ።
ሸረደመ፡ የጋማ ከብቱ ብዙ ጥሬ...
ሸረደደ፡ ዋሸ ቀጠፈ ሰደበ ዐማ ነቀፈ አፌዘ አላገጠ አሾፈ (ምፀት ተናገረ) ።
ሸረገደ፡ ጠፋ ጐደለ ተበደለ ።
ሸረጠ (ዐረ)፡ ገደበ ገደብ እደረገ ።
ሸረጠ) (ሠረጠ) አሸረጠ፡ አገለደመ (በወገብ ላይ ኣሰረ) ።
ሸረፈ (ሰረፈ/በሳ)፡ ስበረ ቈረሰ...ዕቃን ዳቦን ከፍ ።
ሸረፈ (ዐረ. ጸረፈ)፡ መነዘረ ዘረዘረ...አበዛ (ብርን ላላድ ለትሙን ለሩብ ለመሐለቅ ለቤሳ ለመቶ ሳንቲም ለወጠ) ።
ሸረፈ፡ ነቀለ (ከብት ጥርስን ከሥር) ።
ሸረፋ፡ ሰበራ ቈረሳ ምንዘራ ምንዛሪ ።
ሸረፍ፡ የሰበረ/የነቀለ ። "አንድ ሸረፍ ኹለት ሸረፍ"
እንዲሉ ።
ሸሪት፡ (ሻሻ)
ሸሪክ (ኮች)፡ ወዳጅ ባልንጀራ ጓ...ደኛ ።
ሸራ (ሥራዕ)፡ ውሃ የሚቋጥር ወፍራም ልብስ (ርኰት ድንኳን የሚኾን የመርከብ ሸማ) ።
ሸራረበ፡ ገማመደ ።
ሸራረፈ፡ መነዛዘረ ።
ሸራረፈ፡ ሰባበረ ቈራረሰ ።
ሸራረፈ፡ ነቃቀለ ።
ሸራቢ፡ የሸረበ/የሚሸርብ (ጠሪ) ።
ሸራፊ (ፎች)፡ የሸረፈ/የሚሸርፍ...ሰባሪ ቈራሽ መንዛሪ ። "ካህናት ግን አንቀጹን ሰረፈ ቅጽሉንም ሰራፊ ይላሉ"።
ሸራፋ፡ ሰባራ ። "ጥርሰ ሸራፋ አፈ ሸ...ራፋ"
እንዲሉ ።
ሸሬታ፡ ለውጥ ፈንታ ምትክ ። "ባለቅኔዎች 'ሴረተ ሸመተ' የሚሉት ከዚህ የወጣ ነው"።
ሸር (ዐረ)፡ ተንኰል ክፋት ።
ሸር፡ ተንኰል፡ ሸረረ ።
ሸርሙጣ (ጦች)፡ የሸረሞጠ/የሚሸረሙጥ (አመንዝራ ጋለሞታ ቅሬ ሴሰኛ ቅንዝርኛ) ።
ሸርሙጣ ቍልፍ)፡ በወስፌ በምስማር የሚከፈት መናኛ ። "ሠረገላን" ተመልከት ።
ሸርሙጣነት፡ ሸርሙጣ መኾን (አመ...ንዝራነት) ።
ሸርማ፡ መንታ ጥንድ ።
ሸርሜ፡ የቍልም አጠራር (ዘማዊ) ።
ሸርሞ ለሸርሞ፡ ጐን ለጐን (፪ነገ. ፬፡ ፳፭) ።
ሸርሞ፡ ጐን አጠገብ ።
ሸርሻሪ (ሰርሳሪ)፡ የሸረሸረ/የሚሸረ...ሽር (በርባሪ ፈርፋሪ አፍራሽ ነዳሊ) ። ውሃ መሸርሸር፡ መበርበር/መፈርፈር/ማፍ...መ...ረስ መንደል ።
ሸርቋጣ/ሽርቍጥ፡ ስብስብ ቀልጣፋ ።
ሸርተት፡ መንሸራተት ።
ሸርተት አለ፡ ተንሸራተተ ።
ሸርታቴ፡ የሸርታታ ዐይነት (የልጆች ልብስ መጨረሻ ስፍራ) ።
ሸርካች (ቾች)፡ የሸረከተ/የሚሸረክት (ቀዳጅ ፈይ) ።
ሸርዳሚ፡ የሸረደመ/የሚሸረድም (ቈርጣሚ ዐኛኪ) ።
ሸርዳጅ (ጆች)፡ የሸረደደ/የሚሸረድድ (ዋሾ ቀጣፊ ነቃፊ እሿፊ) ።
ሸርጣን (ኖች)፡ ጐርምጥ (ብዙ እጅና እግር ያለው የባሕር ተንቀሳቃሽ አቡ - መቀስ) ።
ሸርጣን፡ መልኩ ጐርምጥ የሚመስል የሠኔ ኮከብ ። "ሸርጣን ነገረ ሰይጣን"
እንዲል ጠንቋይ ።
ሸርጣን፡ ሸረሞጠ
ሸሸ (ሠሥዐ)፡ አፈገፈገ ወደ ኋላ ኣለ (ዠርባውን አሳየ ሮጠ ጋለበ ፈረጠጠ ኰበለለ) ።
ሸሸ፡ ተጠጋ ተማጠነ (ከጠብ ከጦርነት - ፬ነገ. ፲፪፡ ፲፰፡ ኢሳ. ፴፡ ፲፯) ። ("ተረት - ከዥብ ጐሬ ሲሸሹ እዥብ ጐሬ") ።
ሸሸ፡ ፈሳ/ጐደለ/ተበላሸ/ደረቀ/ጠፋ (የተነፋው ስልቻ ሆዱ ቅሉ ላስቲኩ - ቧሸሸን ተመልከት) ።
ሸሸገ፡ ደፈነ ዐባ ሰወረ ደበቀ ቀበረ (ዘፀ. ፪፡ ፲፪፡ ፪ዜና. ፳፪፡ ፲፩, ፲፪፡ ምሳ. ፩፡ ፲፩፡ ኢሳ. ፵፱፡ ፪) ። ("ተረት - ሆድና ግንባር አይሸሸግም") ።
ሸሺ፡ የሸሸ/የሚሸሽ (ሯጭ ፈርጣጭ...ኰብላይ ፈሪ ቡኩን) ።
ሸሻጊ፡ የሸሸገ/የሚሸሽግ (ሰዋሪ ደባቂ) ።
ሸሽ፡ ዝኒ ከማሁ ። "ባሕረ ሸሽ ብረ...ሸሽ ሬሳ ሸሽ"
እንዲሉ ።
ሸሽቦ፡ ያፍንጫ ቀለበት ። "ጒይዲ ግን 'ሸሽቦና ሻሽል አንድ ናቸው' ይላል"።
ሸሽታ፡ የሸሸች/የምትሸሽ ።
ሸቀሸቀ፡ ሠቀሠቀ ጓጐጠ (መላልሶ ወጋ -
"ሸከሸከን" አስተውል) ።
ሸቀሸቀ ሻረ
ሸቀቀ (ሠቀቀ)፡ ገደለ ጨረሰ ጠነገደ ።
ሸቀበ (ዐረ)፡ ለከፈ አታለለ ሰለበ ።
ሸቀበ፡ ልውጣ ልውጣ አለ (ምግቡ እንባው) ።
ሸቀነ፡ ዐከከ አደፈ ።
ሸቀናም፡ ሸቀን ያለበት (ባለሸቀን) ።
ሸቀን፡ የራስ እድፍ ደረቅ ወዝ
("ፈረፈረ" ብለኸ "ፎረፎርን" እይ) ።
ሸቀጠ (ዐረ)፡ ሸጠ ለወጠ (ከነጋዴ እየገዛ አተረፈ) ።
ሸቀጣም፡ ባለብዙ ሸቀጥ ።
ሸቀጣሸቀጥ፡ የሸቀጥ ሸቀጥ (ብዙ ዐይነት ሸቀጥ) ።
ሸቀጥ (ጦች)፡ የንግድ ዕቃ (በየረድፉ በመደብር የተደረደረ) ።
ሸቀጥ፡ መብልና መጠጥ ምግብ በያይነቱ ።
ሸቃቢ፡ የሸቀበ/የሚሸቅብ (የሚያታልል) ።
ሸቃባ፡ አታላይ ግደ ቢስ ሰላቢ ።
ሸቃጭ፡ የሸቀጠ/የሚሸቅጥ (ሸያጭ ለዋጭ ዐጣሪ) ።
ሸቃጭነት፡ ሸቃጭ መኾን (ሸያጭነት) ።
ሸቃጮች፡ ለዋጮች አትራፊዎች (ኢዮ. ፵፡ ፴፡ ፪ዜና. ፱፡ ፲፬) ።
ሸቈረረ (ሰቈራር)፡ ዐፈረ ፈራ ሠጋ ።
ሸቈረር/ሸቍራራ (ስቍሩር)፡ ጥይፍተኛ ዐፋር ዐንገተ ሰባራ ።
ሸቅማጥ፡ ሽንት ማጥ (የሽንት ምጥ) ።
ሸቅሻቂ፡ የሸቀሸቀ/የሚሸቀሽቅ (ጓጓጭ) ።
ሸበለቀ፡ ሽብልቅ አበጀ/እሾለ/አገባ/ቀረቀረ (በሽብልቅ ወጋ) ።
ሸበላ (ሰብል)፡ ወጣት ልጅ (ሽንጥ...መልካም ሽንቅጥ ፎጠና ጠምጣማ) ።
ሸበላ፡ የሰሌን የኮባ የንሰት ሙሽራ ።
ሸበላዊ/ሸበልማ/ሸበላም ። "ዋቢ ሸበሌ" እንዲሉ። "ዋቢ ንብ ሸበሌ ነብር" (በተገናኝ ንብና ነብር ያለበት ወንዝ ማለት ነው) ።
ሸበሌ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሸበል፡ በጐዣም ክፍል ያለ አገር ።
ሸበል፡ ነብር (ሱማሌ) ።
ሸበሎች፡ ሽንቅጦች ፎጠኖች ።
ሸበረ) (ሰበረ)፡ አሸበረ/አስደነገጠ/ኣወከ/ኣስፈራ (በጠበጠ ጸጥታን ሰላምን ኣጠፋ አስጠፋ) ።
ሸበረቀ (ጸብረቀ/ሣርኅ)፡ ጠራ/በራ/ጸደለ/አማረ/ተዋበ (የፊት) ። ሥሩ "በረቀ" ነው፡ "ሸ" በባዕድነት ወይም በ"ጸ" ለውጥነት ተጨምሮበታል ።
ሸበረከ (በረከ)፡ ተንበረከከ ።
ሸበረከ፡ ሸበተ፤
ሸበሸበ (ሠብሠበ)፡ ሸነሸነ/እጠጋጋ/ኣቀራረበ (ልብስን በስፌት) ። "ሰበሰበን" ተመልከት ።
ሸበሽብ፡ ደብተራ ።
ሸበበ፡ የጋማ ከብትን አገጭ ጠለፈ፡ ወይም ላይኛውን ስርንና ታችኛውን መንገጭሊ ፥ ባንድነት አሰረ፡ መሳቢያን ኣበተ ። ሥሩ በግእዝ ሠበብ/ሠበ ነው ።
ሸበተ (ሤብ)፡ ነጣ ጥጥ መሰለ፡ አረጀ፡ ሸመገለ ። "አፍ ቂጡ ሸበተ" እንዲሉ። እንስሳትና አራዊትም ይሸብታሉ።
ሸበተ፡ ሻገተ ጉም መሰለ (ሸነበት...እየሩ) ።
ሸበቶ፡ የሸበተ ጠጕሩ የነጣ ሽማግሌ ።
ሸበየ (ሠቢብ/ሠበ)፡ ደረቀ/ሰለለ/ቀጠነ/ዐጪር ኾነ (ተንጠለጠለ) ።
ሸበየ፡ ሽቦ (ዎች)፡ የብረት የብር የወርቅ የንሓስ የመዳብ ክር (ቀጪንና ወፍራም - ሕዝ. ፵፡ ፲፮, ፳፮) ።
ሸበደደ፡ ጐነበሰ/ጐበደደ (በሸበድ ታጠፈ) ።
ሸበደድ/ሸብዳዳ፡ ጐበደድ/ጐብዳዳ (ጐንባሳ) ።
ሸበዲያም፡ ከበዠዱ ሸበዱ በልጦ የሚታይ ሰው ።
ሸበድ (ሸበረ)፡
ሸበድ፡ ከበዠድ ግራና ቀኝ ያለ የጭንና የሆድ መጋጠሚያ ቈዳ ተላ ።
ሸባ (ሰሐበ)፡ መሸቢያ አበጀ ለጠፈ በመሸቢያ አሰረ ። "ሸበበን" እይ ።
ሸባቢ፡ የሸበበ/የሚሸብብ (አፍ ኣሳሪ) ።
ሸባታ፡ ሻጋታ (እንጀራ ዳቦ ሥጋ) ።
ሸባች፡ የሚሸብት/የሚሻግት ።
ሸብ፡ መሸበብ ።
ሸብ፡ መሸበብ፡ ሸበበ ።
ሸብ ሸብ አደረገ፡ መላልሶ ጠለፈ ።
ሸብ ተደረገ፡ በቀላል ታሰረ ።
ሸብ አደረገ፡ ሳያጠብቅ አሰረ ።
ሸብ፡ ከደንጊያ የሚገኝ ማዕድን (ለተቀደደ ቈርቈሮና ታኒካ ከርሳስ ራ ተመማሪ መጣብቅ) ። ለታመመ ዐይንም በኵልነት መድኀኒት ይኾናል ።
ሸብላቂ፡ የሸበለቀ/የሚሸበልቅ (ወጊ) ።
ሸብላይ (ዮች)፡ የሸበለለ/የሚሸበልል (ጠቅላይ) ።
ሸብረክ አለ፡ አሸድ አለ (እልኩ ረገበ ቍጣው በረያ) ።
ሸብራካ፡ አሻዳ ።
ሸብሻቢ (ዎች)፡ የሸበሸበ/የሚሸበ...
ሸተረ (ሰተረ)፡ ሸለመ አስጌጠ ።
ሸተረ (ሻተተ)፡
ሸተተ፡ ግማ ከረፋ ጠነባ ቈነሰ (ተነፈገ ቀረና ቍስሉ ሽንቱ ውዳቂው ጥንቡ - ጠረኑ የክፉ - ዘፀ. ፯፡ ፳፩) ።
ሸተተ፡ ጥሩ ሽታ ሰጠ (ላፍንጫ ጣፈጠ - አበባው ሽቶው ጠጁ ወጡ -
"የበጎ ሸተን" እይ) ።
ሸተቴ (ትግ. ሸተት)፡ ሸርታቴ ተዳፋት
("የሸተት ሸተትማ" ማለት ነው) ።
ሸተት፡ መሽተት ።
ሸተት አለ፡ ሸተተ ።
ሸታች፡ የሸተተ/የሚሸት ።
ሸነ/ሸና (ሤነ)፡ አጨረቀ ረጨ ፈነጠቀ አንፎከፎከ ለቀቀ አፈሰሰ አንዣረረ (ፊር አደረገ - "ሸነና ሺ ነዋ"
በአማርኛ ይገጥማሉ - "፭፻ና ፭፻ ስንት ነው ሺነዋ")
።
ሸነሸነ (ሰነሰነ)፡ ሸበሸበ ሠነጠቀ (በ...ቀጫኑ) ።
ሸነቀለ፡ ሸነተረ
ሸነቀለ፡ ጠቈረ ከሰል መሰለ ።
ሸነቀረ (ሰነቀረ)፡ ሰበሰበ ዐጠፈ ቀ...ነፈ ሸጐጠ (የሱሪን የቀሚስን ጝፍ ውሃና ጭቃ እድፍ እንዳይነካው) ።
ሸነቀጠ፡ ተኰሰተረ ተሰበሰበ ቀለጠፈ ።
ሸነቈረ (ሰቈረ)፡ በሳ ነደለ ቀደደ ።
ሸነቈጠ፡ ሾጥ አደረገ ገረፈ
("ሸመተሪ" መ) ።
ሸነቋቈረ፡ በሳሳ ነዳደለ ።
ሸነተረ (ሠነተረ)፡ በጣ ቀደደ ። "ሠነተረ የካህናት ሸነተረ የሕዝብ አነጋገር ነው"።
ሸነከፈ (ሸከፈ)፡ ዐጠፈ ኰረተመ...
ሸነገለ (ሰነገለ)፡ ጥቂት ምግብ መ...ገበ (አባበለ አረሳሳ ደለለ አታለለ አሞኘ - "የማ ይሰጠውን እሰጣለኹ"
አለ - ሮሜ. ፫፡ ፲፫ - "ሸግላን"
እይ - የዚህ ዘር ነው) ።
ሸነገለኝ፡ የሰው ስም
("ደለለኝ" ማለት ነው) ።
ሸነጓ (ሰንጐጐ)፡ ሰውን ሰበሰበ...ኣከበ (አበጀ አዘጋጀ ሸንጎን) ።
ሸነጠ (ሰነጠ/ነሸጠ)፡ በለተ ነ...ለየ (ሽንጥ አወጣ) ።
ሸነጠ፡ ሸንኰር
ሸነፈ) (ሰነፈ) አሸነፈ (ዘፍ. ፯፡ ፲፱, ፳፬፡ ራእ. ፭፡ ፭)፡ አሰነፈ (አቃተ አባተ ሠለጠነ ዐየለ በረታ ድል ነሣ ድል አደረገ ረታ መታ ሻረ አዋረደ አታከተ አደከመ - "ትዳሩን አሸነፈ"
- ራሱን ቻለ - "ዓለምን አሸነፈ"
- እውነትን ወደደ ዐመፅን ጠላ) ።
ሸነፈጠ) አሸነፈጠ፡ ዐጥፎ ዘቅዝቆ ታጠቀ (ልብስን ለሐዘን -
"ኣሸነፈጠች" ተብሎ በሴት አንቀጽ ይነገራል፡ ለወንድ ግን በርኖሱን ገልብጦ ለበሰ ይባላል - ዘሩ ሸፈጠ ነው "ነ" በስሯጽነት ገብቶበታል) ።
ሸናሽ (ሾች)፡ የነገድ ስም (በዳሞት ባባይ ዳርና ዳር በሌላም ስፍራ የሚገኝ ሕዝብ) ።
ሸናጣ፡ ዥላላ ሾጣጣ መሬት ሠላጤ ኦራፊ መጣፊያ ።
ሸናጭ፡ የሸነጠ/የሚሻንጥ (ነጣይ) ።
ሸንሻኝ (ኞች)፡ የሸነሸነ/የሚሸነሽን (ሸብሻቢ ሠንጣቂ) ።
ሸንቍጤ/ሸንቍጥ፡ የሰው ስም
("ጠላታችንን ግረፍ" ማለት ነው) ።
ሸንቃሪ፡ የሸነቀረ/የሚሸነቅር (ሰብሳቢ ዐጣፊ ቀናፊ) ።
ሸንቃጣ/ሽንቅጥ (ጦች)፡ ኰስታራ ኵስትር ቀልጣፋ (አለባበሱ ሰውነቱ ዘርፋፋ ዘርፋጣ ያይዶለ ጠምጣማ ሸበላ ሾጤ) ።
ሸንቋሪ፡ የሸነቈረ/የሚሸነቍር (በሺ...ቀዳጅ) ።
ሸንቋራ/ሽንቍር፡ የተሸነቈረ (ብስ...ቀዳዳ ነዳላ) ።
ሸንቋጭ (ጮች)፡ የሸነቈጠ/የሚሸነ...ቍጥ (ገራፊ) ።
ሸንበቆ (ሥን፡ በቍዖ)፡ መቃ ። "ሸንበቆ ትግሪኛ መቃ ዐማርኛ ነው"።
ሸንተረር (ሮች)፡ ሰው የሚወጣበትና የሚወርድበት ጠባብ መንገድ (ግራ ቀኙ ገደል ወይም ተዳፋት ዘቅዛቃ - የተራራና የኰረብታ ሲኾን "ተረተር" ይባላል - የሸንተረር ምሳሌው በስተውጭ ያለ ያራት ማእዘን ግንብ መመለሻና ማጠፊያ ነው) ።
ሸንተረር፡ ሸፈነ
ሸንካፊ፡ የሸነክፈ/የሚሸነክፍ (ዐጣፊ...አሳሪ) ።
ሸንካፋ/ሽንክፍ፡ የተሸነከፈ (ታጥፎ የታሰረ ኵርትም) ።
ሸንኰራ፡ በቡልጋና በምንጃር አጠገብ ያለ አገር (ሸንኰር የሚበቅልበት) ።
ሸንኰራገዳ (ሸንኰር አገዳ)፡ ሸንኰ...ርነት (ሱካርነት ያለው የሱካር አገዳ - ጥንቅሽም ሸንኰራገዳ ሊባል ይገባል - "ግጥም")
።
ሸንኰሬ፡ የኔ ሸንኰር (የታላቅ እት የታላቅ የእትዬ ተከታይ ያበባ ተቀዳሚ) ።
ሸንኰር፡ ያልጋ እግር (በሸንኰር አም...ሳል የታነጸ የተቀረጸ) ።
ሸንኰር፡ ጌጠኛ መስቴ (ዐልፎ ዐልፎ መሸቢያ ያላት -
"ሻንኵራን" እይ) ።
ሸንኰር/ሸንኰራ (ሶከር)፡ የተክል ስም (ዐጥቁ ሽመልን ቀርክሓን መቃን ጐሽ መቃን የሚመስል ጣፋጭ ተክል - ፈረንጆች በመኪና እየፈጩ ሱካር ያደርጉታል) ።
ሸንኰፍ (ሰንኰፍ)፡ ልንበጥ ቈለ...ፈት ወሸላ ሽፍን ።
ሸንጋይ (ዮች)፡ የሸነገለ/የሚሸነግል (ደላይ አታላይ - መዝ. ፭፡ ፮፡ ምሳ. ፲፬፡ ፳፭፡ ሚል. ፩፡ ፲፬) ።
ሸንጎ (ች)፡ አደባባይ ዐውድ የሕዝብ መሰብሰቢያ ዳኛ የሚያስችልበት ወግ ሥርዐት የሚሠራበት ዐዋጅ የሚነገርበት ። በግእዝ "ዐውድ/ጽጕ" ይባላል (ዮሐ. ፲፰፡ ፳፰, ፴፫) ። (ገበሬ ሸንጎ)፡ ገበሬ ተሰብስቦ ዕድር የሚያድርበት ስፍራ...ውል ።
ሸንጎ፡ ሕዝብ ጉባይ (ማር. ፲፭፡ ፩) ።
ሸንጎበት፡ በታችኛ ከንፈር መካከልና ባዦጭ ላይ የበቀለ ሪዝ (ዘሌ. ፲፫፡ ፳፱-፴) ። "የውበት ሸንጎ ማለት ነው፡ ጕራጌም ጢምን ሸንጎበት ይለዋል"።
ሸንጎኛ፡ ሸንጎ ወዳድ (በሸንጎ የሚ...ውል) ።
ሸንጥሮ፡ ሸለቆ (፪ሳሙ. ፲፭፡ ፳፫፡ ፲፯፡ ፳፡ ፩ነገ. ፪፡ ፴፯) ። "ሸነተረ" ብለኸ "ሽንትርን" እይ ።
ሸንጥሮች፡ ሸለቆዎች (መዝ. ፻፬፡ ፲) ። ሸነከ፡ ተነኰለ እጠፋ ።
ሸኘ (ሰነየ/ትግ. አሰነየ)፡ እንግዳን ጋበዘ (ከቤት ወደ ውጭ ወሰደ እመንገድ አደረሰ ጐዳናን መራ አሳየ - አሰናበተ ሰውን ዛርን - "የሸኘ ትርጓሜ ፪ኛነትን ያሳያል"
- "በጥርስ ሸኘ" - በሣቅ በፈገግታ ሳያበላ ሳያጠጣ) ።
ሸኘ፡ ሸነገለ
ሸኚ (ዎች) (ትግ. መሰነይታ)፡ የሸኘ/የሚሸኝ (ከመንገደኛ ተለይቶ የሚመለስ - "ሸኚ እቤት አያገባም"
እንዲሉ - ድረስ) ።
ሸኚታ፡ የሸኘች/የምትሸኝ ።
ሸከመ/ሰከመ) አሸከመ፡ ከምድር አንሥቶ በሰው ራስና ትከሻ ላይ አደረገ (ነ...አሳዘለ አሲያዘ አስነገተ - ፩ነገ. ፲፡ ፪፡ ሉቃ. ፳፩፡ ፵፯) ።
ሸከማ፡ የሸክም ሥራ ።
ሸከረ (ሠክረ)፡ አነሰ ተቀጠረ ተከ...ተለ ። "ወሸከሬን" እይ (የዚህ ዘር ነው) ።
ሸከሸከ (ሠቀሠቀ)፡ በቀላል ወቀጠ (የቈሎ ያሻሮ) ።
ሸከሸከ፡ ሸደሸደ ወጋጋ (በሳሳ አላላ...ዘረዘረ ዘከዘከ አራራቀ - የልብስ የስፌት) ።
ሸከኛ፡ ክፋተኛ ተንኰለኛ ።
ሸከከ/ሠጠጠ) ሸከክ አደረገ፡ ሠጠጥ አደረገ ።
ሸከክ አለ፡ ሠጠጥ አለ ሐሩ ።
ሸከፈ፡ አካፋ ተፈተፈ አጠቀነ ።
ሸካሸከ፡ ወቃቀጠ ።
ሸክ አደረገ፡ ተንኰል ሠራ ።
ሸክ፡ ክፋት ። ሸከሸከ ።
ሸክ፡ ክፋት ተንኰል ።
ሸክለኛ (ኞች)፡ ሸክላ ሠሪ ባለሸክላ ("ይብ ረጋ" - ኢሳ. ፵፩፡ ፳፭) ።
ሸክላ (ሎች)፡ የሸክላ ዕቃ (ከሸክላ የተሠራ) ።
ሸክላ፡ ቀይ ዐፈር (መዝ. ፪፡ ፬) ።
ሸክላ በቅሎ፡ ቀይ በቅሎ ።
ሸክላ ቧጣጭ፡ የጠይብ ሚስት ።
ሸክም (ሞች)፡ ዕንጨት ውሃ ዐፈር ደንጊያ ዕቃ መሣሪያ እኸል ሣር (በሰው ላይ ኹኖ ታስሮ ወይም ሳይታሰር በኹለት እጅ የተያዘ) ።
ሸክም ኾነ፡ አስቸገረ ።
ሸክሻኪ፡ የሸከሸከ/የሚሸከሽክ (ወቃጭ...ሸድሻጅ ዘርዛሪ ዘክዛኪ) ።
ሸክሻካ/ሽክሽክ፡ የተሸከሸከ (ውቅጥ ዘርዛራ ዝርዝር በለሴ) ።
ሸኰተ፡ መታ ጸፋ ውስጥ እጅን በው...ስጥ እጅ ።
ሸኰተ፡ መናኛ ጠላ ጠመቀ ።
ሸኰቴ፡ ከብቅልና ከእንኵሮ ካንድ ዕፍኝ የጌሾ ቅጠል ዱቄት በቀር ጌሾ በብዛት የማይገባበት ጠላ (ትሕርምተኛ መነኵሴ የሚጠጣው) ።
ሸኽ፡ የቍርኣን ካህን፡ ሸኅ ።
ሸወረረ (ሾረ)፡ ዞረ ጠመመ ወል...ጋዳ ኾነ ።
ሸወረር/ሸውራራ (ሮች)፡ ዘዋራ ጠማማ ዐይን ።
ሸወርኒ፡ ያይን ቍራኛ (ዐይን እያየ ያላየ መምሰል) ። አንቀጹ
"ሾረ" ነው ።
ሸወተ፡ ሽኩቻ አደረገ ።
ሸወታ፡ ቍትቻ ሽኵቻ ።
ሸወከ፡ ሰበቀ አዋሸከ ። "ወሸከን"
እይ ።
ሸወደ፡ አሳተ ።
ሸዋዳ፡ አሳች ።
ሸውረር አለ፡ ሸወረረ ።
ሸውሸዌ፡ የዛፍ ስም (ነፋስ ሲነካው ሽው ሽው የሚል ዕንወት) ።
ሸውሻዋ፡ ቀላል ወሬኛ ሰው (አባ ንፋው) ።
ሸውከኛ (ኞች)፡ ሰብቀኛ አዋሻኪ ።
ሸውከኛነት፡ ሸውከኛ መኾን (አሳባ...ቂነት) ።
ሸውክ (ሦክ)፡ ሰብቅ ሰውን እንደ እሾኸ የሚጐዳ ።
ሸውዳራ፡ ከሰው የማይገጥም ።
ሸየተ (ሸወተ)፡ ዕጣ ጣለ ። ሽየታ፡ መሸየት ።
ሸየጠ/ሼጠ (ሤጠ)፡ አቀና/ለወጠ (ለገዢ ሰጠ) ።
ሸያጭ (ሠያጢ)፡ የሼጠ/የሚሼጥ (ለዋጭ ዐጣሪ ባለመደብር) ።
ሸያጭነት፡ ሸያጭ መኾን ። "ሽጦሽ ልወጣ"።
ሸያጮች፡ ለዋጮች ዐጣሮች ። መጽሐፍ ግን
"ሻጮች" ይላል ስሕተት ነው (ዘካ. ፲፩፡ ፭) ። "ሻጠን" ተመልከት ።
ሸዬ/ሾዬ (ኮሞል)፡ የዛፍ ስም (ዐጥንታም ፍሬው ከታች ሰፋ ከላይ ሾጠጥ የሚል ምግብነት ያለው) ። "እሼን" እይ (ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሸደሆ፡ የቀበሌ ስም (በላስታ ክፍል ያለ ገጠር) ።
ሸደሸድ/ሸድሻዳ/ሽድሽድ፡ የተሸደሸደ (ውስውስ ሽክሽክ ሽል) ።
ሸድሻጅ፡ የሸደሸደ/የሚሽደሽድ (ወስዋሽ ሸክሻኪ) ።
ሸገሸገ) (ሸሸገ)፡ አሸገሸገ (አፈገ ፈገ - ለመራቅ ለመቅረብ) ። "ሰገሰገንና ሸቀሸቀን" ተመልከት ።
ሸገነ (ሰገነ)፡ አማረ/ተዋበ/ቈነዠ ።
ሸገነ፡ ሽግ/ሽጕችቦ፡ ሸገገ ።
ሸገና/ሸገን፡ የሰው ስም (መልከመልካም) ።
ሸገገ (ጸጐጐ)፡ ሞቀ ለብ አለ ።
ሸገገን ተመልከት ("ለቤ/ለሴ ጢብኛ መላብ መሞቅ መውዛት መፍሰስ አላሰ ") ("አልሀበ") ።
ሸጕራ፡ ሻግያ (የሚሼጥ ባሪያ ዐመለ ሻካራ) ።
ሸጊቱ፡ ውቢቱ ቈንዦዪቱ ። "ሸጋ ሸጌ ሸጊቱ"
በጋልኛም ይነገራል።
ሸጋ (ጎች)፡ የሸገነ ያማረ የተዋበ (ውብ ቈንዦ) ።
ሸጋ፡ ሸገነ፤
ሸጋ፡ ውብ ።
ሸጋኝ፡ የሚሸግን (የሚያምር) ።
ሸጋዝ፡ የዛፍ ስም ።
ሸጌ/ሸጋዊ፡ የሸጋ ወገን ዐይነት
("የኔ ሸጋ") ።
ሸግ አለ፡ ሞቅ አለ ተንገረገበ ።
ሸግ አለ፡ ተንገረገበ (ሸገገ) ።
ሸግ አደረገ፡ አሞቀ አንገረገበ ።
ሸግላ፡ ድለላ
("ላይሰጥ እሰጣለኹ ላያደርግ አደርጋለኹ" የማለት ቃል) ። "ወላወለ ብለኸ ወላን" ተመልከት ።
ሸግታ፡ ሸግ ማለት ።
ሸጐረ (ሠጊር/ሠገረ)፡ ወረወረ/ቀረቀረ (ዘጋ ደነቀረ) ።
ሸጐረ (ሸገሸገ)፡
ሸጐበ (ሰገበ)፡ ፈራ ዥራቱን ዐጠፈ ቀለሰ እጕያው አገባ ("ሸጐ ውሻው") ።
ሸጐጠ (ሰገጠ)፡ አገባ ወተፈ (በቅርብ ደበቀ ሸሸገ) ።
ሸጓሪ፡ የሸጐረ/የሚሸጕር (ቀርቃሪ) ።
ሸጓቢ፡ የሸጐበ/የሚሸጕብ (ፈሪ) ።
ሸጓባ/ሽጕብ፡ የተሸጐበ የታጠፈ ቅልስ ።
ሸጓጐጠ፡ ወታተፈ ደባበቀ ።
ሸጓጭ፡ የሸጐጠ/የሚሸጕጥ (ወታፊ) ።
ሸጠ፡ -ለወጠ (ሸየጠ) ።
ሸጠጠ፡ መጠጠ ።
ሸጠጥ፡ መጠጥ ።
ሸጠጥ አደረገ፡ ሠጠጥ አደረገ (በፍጥነት ቀደደ ሸረከተ -
"ሸከከኝ" አስተውል) ።
ሸጢን፡ የማይነቅዝ ዕንጨት (የሸምሸር ዐይነት ሣጥን የሚኾን) ።
ሸጥ አለ፡ ተለወጠ (ሸየጠ) ።
ሸጥ፡ ፈረፈር ፈፋ (ጐዣም) ።
ሸፈሬ፡ የቈላ ዛፍ (ሞፈር ቀንበር የሚኾን ዕንጨት -
"ቡክቡካን" አስተውል) ።
ሸፈሸፈ (ሸፈፈ)፡ በመደዳው ዐጨደ (ቈረጠ አሳጠረ ሸራረፈ) ።
ሸፈተ (ሸፈጠ)፡ ከሕዝብ ተለየ ከዳ ዐመጠ ወነበደ (እዱር እበረሓ ገባ - ለሕግ ለመንግሥት አልታዘዝ አለ - ፬ነገ. ፲፪፡ ፲፱) ። ሸፋች (ሸፋጭ)፡ የሚሸፍት/የሚከዳ...ዐማቦ ።
ሸፈተ፡ ሸቈረረ
ሸፈነ (ጸፈነ/ሰፈነ)፡ አለበሰ ጋረደ (እንዳይታይ አደረገ ከለለ ጨፈነ ከደነ) ።
ሸፈጠ (ሰፈጠ)፡ ካደ ከዳ ዐበለ አሞኘ አቄለ ኣታለለ ሸነገለ ።
ሸፈጣ/ሽፈጣ/ሸፍጥ (ስፍጠት)፡ አሉታ ክዳት (የኾነውን የተደረገውን አልኾነም የለም አይዶለም ማለት) ።
ሸፈጥ (ሰፊጥ)፡ ነሸጥ ።
ሸፈጥ አደረገ፡ ነሸጠ ።
ሸፈፈ (ሰፈፈ)፡ ሰፋ ሽፋፍ አበጀ (ሸለመ አስጌጠ) ።
ሸፈፈ፡ ሰበሰበ አከበ አገባ ከተተ ።
ሸፈፈ፡ እወጣ እበቀለ ።
ሸፈፈ፡ ወደ ጐን ረገጠ
("ሸነደለን" እይ) ።
ሸፈፍ ሸፈፍ አለ፡ ዐሸድ ዐሸድ...ተንሻፈፈ (ሸፋፋ ኾነ ወነከሰ ነፋስ እንደ ነካው አንበጣ ባንድ ወገን ረገጠ ኼደ) ።
ሸፈፍ፡ ባንድ እግር መርገጥ ።
ሸፈፍ አለ፡ ዐሸድ ዐንከስ አለ ።
ሸፋሽፍት (ቶች)፡ የቅንድብ ጠጕር ምርቅ የሚመስል ያይን ጨፈቃ የማያድግ ። ዳግመኛም ሸፋሽፍት በመብቀያው ስም ቅንድብ ይባላል ። "ቅንድብን" ተመልከት (ምሳ. ፴፡ ፲፫፡ ኤር. ፱፡ ፲፰) ።
ሸፋኝ (ኞች)፡ የሸፈነ/የሚሸፍን (አል...ባሽ ከላይ ፊፋኝ ከዳኝ) ።
ሸፋጭ (ጮች) (ሰፋጢ)፡ የሸፈጠ/የሚሸፍጥ (ሀባይ ታላይ ሸንጋይ መልቲ - ጐንደሮች ጠበቃን ሸፋጭ ይሉታል - ግብ. ሐዋ. ፳፬፡ ፩, ፲፱) ።
ሸፋጭነት፡ ሸፋጭ መኾን (ዐባይነት አታላይነት) ።
ሸፋፈነ፡ አለባበሰ ከዳደነ ።
ሸፋፋ፡ ዐሻዳ እግረ ወልጋዳ (ባካኼድ ባረማመድ) ።
ሸፍሻፊ፡ የሸፈሸፈ/የሚሸፈሽፍ (ሀጅ ቈራጭ) ።
ሸፍሻፋ፡ የተሸፈሸፈ ።
ሸፍት (ሸፈሸፈ)፡ የበሬ ሽንት መ...ሸኛ (የቀዳዳው ዙሪያ) ።
ሸፍጠኛ (ኞች)፡ ባለሸፍጥ እሉተኛ...ከዳተኛ (ፀባይ ቀጣፊ) ።
ሸፍጠኛነት፡ ሸፍጠኛ መኾን ።
ሸፎ፡ ዐሻዳ፡ ሸፈፈ ።
ሸፎ፡ ዝኒ ከማሁ (ዐሾ) ።
ሸፎ ገመዳ፡ እግሩን እያጋመደ የሚኼድ ሰው ።
ሹለት፡ የጫፍ ቅጥነት (እንደ ጦር እ...ንደ ወስፌ መኾን) ።
ሹላፍ (ሹል አፍ)፡ አፈ ሹል ነገረኛ ሰው (አሳባቂ) ።
ሹል (ስሑል)፡ የሾለ የቀጠነ ሾጣጣ ።
ሹል፡ የሾለ፡ ሾለ ።
ሹልኪት፡ የሾለከች ።
ሹልክ አለ፡ ሾለከ ። (ተረት)፡ "ዋስ ጠርቼ ሹልክ ብዬ መጣኹ"።
ሹልክልኪት፡ ዐጨር ባሕረ ሐሳብ ከ፳ው ፩ እያለ የሚቈጥር ።
ሹልክልኪት፡ የተሹለከለከች ።
ሹልክልክ፡ የተሹለከለከ/የሚሹለከለክ (እባብ ሸላ ዋልጋ ማንኛውም አውሬ ነፍሰ ገዳይ ሰው) ።
ሹልክታ፡ ሹልክ ማለት ።
ሹልዳ (ዶች)፡ ታናሽ በሚባለው የሥጋ ብልት ውስጥ የሚገኝ ቀይ ሥጋ ። በግእዝ "ጸክ" ይባላል እሱንም የእስራኤልና የአማራ ዘር አይበላውም ። ዳግመኛም ስለ መንቀጥቀጡ "ሥጋ ፈሪ" ይሉታል ።
ሹመት (ሢመት)፡ ክብር ማዕርግ መብት የበላይነት ። መንፈሳውያን ግን ሹመትን ሺሕ ሞት ይሉታል ።
ሹመት፡ የሴት ደም አለመውረድ ።
ሹመት ያዳብር ይጨምር ያሳድግ (ለተሾመ ይነገራል) ።
ሹመን፡ ስምንተኛ የቀባርዋ ምት ።
ሹማምት፡ ሹሞች (፪ዜና. ፱፡ ፲፬፡ ዕዝ. ፯፡ ፳፭፡ ኢሳ. ፷፡ ፲፯) ። "ሹማምቶች" ቢል የብዙ ብዙ ነው ።
ሹም (ሥዩም)፡ የተሾመ ማዕርግ ያገኘ አገረ ገዥ አዛዥ ባለሥልጣን ባለመብት ።
ሹም ሽር (ሥዩም ስዑር)፡ የተ...ሻረ ሹም ። ዳግመኛም
ሹም ሽር፡ ሹም የተሾመው ሽር የተሻረው ማለት ነው (ሹመትን ሽረትን ያሳያል) ።
ሹም ተንቤን (ሥዩመ ተንቤን)፡ የተንቤን ሹም (የተንቤን ገዥ ባላባት) ።
ሹምነት፡ ሹም መኾን ።
ሹሞች (ሥዩማን)፡ የተሾሙ የተሸለሙ አለቆች አዛዦች መኳንንት ።
ሹራብ (ቦች)፡ ከጥጥ ከጠጕር ገመድ የተታታ ጥብቆ (ቀሚስ መደረቢያ) ።
ሹራብ፡ እጅን እግርን ማግቢያ መክተቻ
("የእጅ ሹራብ የእግር ሹራብ" እንዲሉ) ።
ሹር፡ ዝኒ ከማሁ (በክርስቲያን ዘንድ ያለፈ የቀረ የአይሁድ ሰንበት -
"ቅዳሜ ሹር" እንዲሉ) ።
ሹር፡ የተሻረ፡ ሻረ ።
ሹርባ፡ ሠራ ጣሰ ከፈለ ወሸመ ቈነነ ጐነጐነ ቈነጣጠረ ቈነደለ ።
ሹርባ/ሽሩባ፡ የሴት ራስ ጠጕር የተ...ጐነጐነ ።
ሹርቤ፡ ባለመሥመር (ብርሌ የሹርባ ዐይነት) ።
ሹሽ (ዐረ. ሱስ፡ ትል. ወላሞ. ሾሻ. እባብ)፡ ከሕፃናት ሆድ የሚወጣ ነጭ ትል (ፈጽሞ ያነሰ የቀጠነ - ዐረብ
"ሱስ" የሚለው ባማርኛ "መስክ" ይባላል) ።
ሹካ (ሦክ)፡ ባለጣት ማንካ (ጣቶቹ እሾኸ የሚመስሉ ጥብስ ወይም ቅቅል ሥጋ መውጊያ ወደ አፍ ማስጠጊያ የምግብ መሣሪያ - ፩ሳሙ. ፪፡ ፲፫-፲፬) ። ሲበዛ "ሹካዎች/ሹኮች" ያሠኛል (፪ዜና. ፬፡ ፲፮) ።
ሹካና ማንካ፡ ኹለቱ ባንድነት ።
ሹክ ሹክ አለ (አልኈሰሰ)፡ አሾከ...ሾከ ።
ሹክ አለ (ሸከመ)፡
ሹክ አለ (ሾከ) ።
ሹክ አለ፡ ዦሮን ተጠግቶ ተናገረ ።
ሹክሹክታ፡ ብዙ ሸክታ ማሾክሾክ (፪ሳሙ. ፲፪፡ ፲፱) ።
ሹክታ (ለኈሳስ)፡ ከተናጋሪውና ከሰ...ሚው በቀር ሌላ ሰው የማያውቀው ጕዳይ ።
ሹክክ፡ መሾከክ ።
ሹክክ አለ፡ ሾከከ (ቅልል አለ ተንሿከከ ሾካካ ኾነ ጥላ ቀለለው) ።
ሹገረ —ፈደለ፡
ሹገረ፡ ፋገረ ።
ሹጣም (ሞች)፡ ሹጥ ያለበት የበዛበት (ባለሹጥ) ። "ኮሶን" እይ ።
ሹጥ (ሰሐጠ/ሶጠ)፡ የሆድ ውስጥ ትል (ትርጓሜው "የተሻጠ የተጨመረ ጭምር" ማለት ነው) ። ሲበዛ "ሸጦች" ይላል ።
ሺ (ሺሕ)፡ የቍጥር ስም (፲፪፥ ዐሥር ጊዜ መቶ፡ ወይም መቶ ጊዜ ዐሥር) ። ሺ በንባብ ውስጥ እንጂ ከአኃዝ ጋራ እየተዛነቀ በገጽና በምዕራፍ አይጻፍም ።
ሺ መልስ፡ ታናሽ ዋንጫ መጠጥ ማዳረሻ ።
ሺ መልስ፡ የሰው ስም (የጐበዝ ጐ...በዝ) ።
ሺ በሺ፡ የሰው ስም (የሺ መሣ የሺ ለውጥ ማለት ነው) ።
ሺ እግር፡ ክረምት አፈራሽ ትል ባለብዙ እግር ። ከፊት ሲነኩት ሳይዞር ወደ ኋላ ይኼዳል ።
ሺ ገዳይ፡ ሺ የገደለ ሐርበኛ እንደ ሳኦል ያለ ።
ሺ ጊዜ ሺ፡ መቶ እልፍ (አንድ ሚሊዮን) ።
ሺ ፈራ፡ የሰው ስም ።
ሺ ፈራው፡ ዝኒ ከማሁ ። ሺ የስም ዘርፍ እየኾነ ሲነገር
"የሺ የሺእመቤት የሻረግ" ይላል ። "ሻውልን ሻለቃን ሻምበልን ሻቃን" በየስፍራው አስተውል ።
ሺ ፈጅ፡ የመስቀል ስም (በታች ወግዳ ማጢ በሚባል አገር በጊዮርጊስ ቤተ ክሲያን የሚገኝ መማማያ መስቀል) ። እሱንም ቄሶቹ ከሰማይ ወርዶ የነካውን ሺ ማይምን ስለ ገደለ
"ሺ ፈጅ" ተባለ ይላሉ ።
ሺሓምጥ፡ የሰው ስም
("አንተ አንድ ስትኾን - ሺሕ ዐምጥ" - ሸሑን ሰው ክዳ በድል ማለት ነው) ።
ሺሕ (ሖች)፡ ዐሥር መቶ ። "ሺን" ተመልከት ።
ሺራራ፡ የቈዳ ግልድም (ትግ) ። (ሸረሸ) ተሸራሸ፡ ተደላደለ ተመቻቸ ተንዘራፈጠ ።
ሺሾ፡ የቈላ ጕንዳን ሲኼድ የሚንሻሻ (ሽንጣም ችስችሳ) ።
ሺሾጕንዳን (ሻሻ) ።
ሺን (ኖች)፡ የነገድና ያገር ስም (ሴማዊ ነገድ የምሥራቅ መዠመሪያ - ዘፍ. ፲፡ ፪ - የህንድና የመስኮብ ጎረቤት - በግእዝ "ሲን" ይባላል - "ተረት - ሺን ዐሸን"
- "ስኒን ሻይን" እይ) ።
ሺዋ (ሺሕ ሽኋ)፡ የሴት ስም (የግሼ ባላባት ያገባት የወሎ ባላባት ሴት ልጅ) ። ብዙ ልጆች ስለ ወለደች አባቷ "ልጄ ሺኋ አላት" በዚህ ምክንያት የልጆቿ አገር "ሺዋ" ተባለ ይላሉ (ኪ.ወ.ክ) ።
ሺዋ ረገድ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሺዋ ረጋ፡ የወንድና የሴት ስም ።
ሺዋ ርካብሽ፡ የሴት ስም ።
ሺዋ ርካብኸ፡ የወንድ ስም ።
ሺዋ ታጠቅ፡ የሰው ስም ።
ሺዋ፡ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች አንዱ ። ሺዋ የሚባለው ከግሼ ከመንዝ ዠምሮ ዋየት በመለስ እስከ ዐዋሽ ነው ይባላል ።
ሺዋ ጊሚራ፡ በከፋ አጠገብ ቀድሞ የሺዋ ሰው የሰፈረበት አገር ።
ሺዋ ጽዮን (የሺዋ ጽዮን)
ሺዋን ላንቺ፡ የሴት ስም ።
ሺዋን ከተርሽ፡ የሴት ስም ።
ሺዋን ዳኝ፡ የወንድ ስም ።
ሺዋን ግዛው፡ የወንድ ስም ።
ሺዋን ግዢው፡ የሴት ስም ።
ሺዌ (ሺዬ)፡ የሺዋ ሰው (የሺዋ ተወላጅ) ። ሲበዛ "ሺዎች" ያሠኛል ።
ሺዬ፡ የሺዋ ሰው፡ ሺዋ ።
ሻ (ስሒው/ተሥዕዮ)፡ መበተን/መጕደል ።
ሻ (ዐረ ሻአ)፡ ኀላፊ አንቀጽ (ፈለገ ፈቀደ - ፩ነገ. ፲፱፡ ፲) ።
ሻ ብትን፡ መለያየት/መጥፋት ።
ሻ ብትን፡ የሕፃናት ጨዋታ (እጆቻቸውን በማቈናጠጥ አነባብረው የቍንጢጥ የቀንጢጥ ይሉና እጃቸውን ሲለዩ
"ሻ ብትን" ይላሉ) ።
ሻ አለ (ተሥዕየ - ዐረ ሸዐ)፡ ተበተነ/ጐደለ (ምግብ ከሆድ ውስጥ) ።
ሻ አለው (ስሕወ ልቡ)፡ ልቡ ከዳው ።
ሻ አደረገ (ሠዐየ)፡ በተነ ። "ፀረቄ ምግብን ሻ ያደርጋል"።
ሻ፡ የቅርብ ወንድ ትእዛዝ አንቀጽ
("ፈልግ" - ተረት)፡ "ምናልባት ቢሰበር ዐናት ቅቤ ሻ ለመተኰሻ"። ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች "ሻ ሹ ሺ" በማለት ፈንታ "እሻ እሹ እሺ" እያሉ ይጽፋሉ፡ ስሕተት ነው ።
ሻሖ፡ በጥልጣል አጠገብ አሳሑርታ ውስጥ የሚገኝ ነገድ ።
ሻለ (ሣህለ/ሥዕረ)፡ ሻረ ዳነ በጥ...ቂቱ ።
ሻለ (ተሥህለ)፡ በሽታው ቀለለ ቍ...ስል ጠገገ ዳነ ።
ሻለቃ (ቆች)፡ የሺ አለቃ ጦር ጠቅላይ አገረ ገዢ (ከባላምባራስ እስከ ራስ ያለ የሺ ጭፍራ አዛዥ ምክትሉ ሻምበል ነው) ። ከሺ በላይም ሰራዊት በኖረው ሻለቃ ይባላል (ዘፍ. ፬፡ ዘፀ. ፲፰፡ ፳፩) ። "የሻላን" ተመልከት ።
ሻል (ሥሂል)፡ ጥቂት ጤና ድኅነት መሻል ።
ሻል፡ ራስ መሸፈኛ ቀጸላ ሻሽ ።
ሻል ብሎታል፡ ድኗል (ከሞት አፋር...ሷል) ።
ሻል አለው፡ ጤና አገኘ ።
ሻሚት፡ ፈራ ።
ሻማ (ሠምዕ)፡ የማር ሰፈፍ (ማር ጠጅ ሲጣል ሲነጠር ይንሳፈፋል) ። በግእዝ "ምዕ" በአረብኛ "ሸመዕ" በአማርኛ "ሠም ሻማ" ይባላል ። ይኸውም ግግሩ ልጥልጡ እየቀለጠ ጧፍ ፋና የሚኾን ነው ። ሻማ ግን በፍንታ ይነገራል።
ሻማ (ትግ - ነጠቀ ቀማ ጥል አልባ) ።
ሻማ፡ ዝኒ ከማሁ ነጠቃ ። "ግዳይ ሻማ ነው"
("ሻማ" እንዲል ዝኆን ገዳይ) ።
ሻሜ፡ ታናሽ ገንዘብ (ቤሳ ክንሓስ የተሠራ) ። በግእዝ
"ጸሪቅ" ይባላል ።
ሻሜ፡ ነጭ ሞላላ የዛጐል ዶቃ (የጮሌ ማፈኛ የሻም ሻማዊ ማለት ይመስላል -
"ሻምን" አስተውል) ።
ሻሜት፡ ሸነ
ሻሜት፡ አጥሚት ።
ሻሜት፡ የበሶና የማር ጭ...ብጦ፡ (ጥማ) ሻማ ።
ሻሜት፡ የበሾና የማር ጭብጦ (እየተሻሙ የሚበሉት) ።
ሻም፡ ያገር ስም (ሶርያ - ግብ. ሐዋ. ፲፭፡ ፳፫) ።
ሻምበል (የሺ ዐምበል)፡ የሺ አጋፋሪ በላይ (የሻለቃ ምክትል የሺ ነፍጠኛ አዛዥ - "ሻለቃን"
እይ) ።
ሻምበልነት፡ የሻምበል ሹመት (ሻም...በል መኾን) ።
ሻምበሎች፡ የሸ ጭፍራ አለቆች ።
ሻሞች፡ የሻም ሰዎች (የሻም ተወላጆች ዐረቦች የደማስቆ ሕዝቦች) ።
ሻረ (ሰዐረ)፡ አዋረደ ወሰደ (ሹመትን ገፈፈ ክብርን - ፪ዜና. ፴፯፡ ፫) ።
ሻረ (ሥዕረ)፡ ሻለ ዳነ ተፈወሰ (እሸ...ለተ ሰውነቱ ተመለሰ) ።
ሻረ፡ አሳለፈ አስቀረ ማንኛውንም ነገር (ኢሳ. ፳፭፡ ፰፡ ማቴ. ፭፡ ፲፱) ።
ሻረ፡ አጠፋ ደመሰሰ (አደረቀ ባሕርን) ።
ሻረ፡ አፈረሰ ካብን ።
ሻረ፡ ፈታ አሸነፈ (ድል ነሣ ጦርን) ።
ሻሪ (ሠዓሪ)፡ የሚሽር/የሚድን ።
ሻሪ (ዎች) (ሰዓሪ)፡ የሻረ/የሚሽር (በዓል ሻሪ)፡ በዓልን የሚደፍር (በበዓል ቀን የሚሠራ) ።
ሻሸረ፡ ዕርቁ ፈረሰ ።
ሻሸረ፡ ፍራ ኣልባ ኾነ እኸሉ ።
ሻሸጎ፡ የቀድሞ ዘመን ነፍጥ ።
ሻሻቴ (ወሎ)፡ ታናሽ መስፈሪያ ።
ሻሻቴ (ዎች)፡ ብዙ ፊት ።
ሻሻቴ፡ ጩት (ሻሻ) ሿሿቴ ፈሳሽ (ሿሿ) ሸተ (ሠወየ)፡ በሰለ ጐመራ ደረሰ ። ("ተረት - ብቻ የበሉት ይሸታል ከሰው የበሉት ይሸታል"
- ይገማል እሸት ይኾናል) ።
ሻሽ (ሠሥዐ)፡ ነጭ በፍታ ሥሥ ራስ ማሰሪያ መሸፈኛ (ዘፀ. ፳፭፡ ፬) ። ("ተረት - የፊት ወዳጅኸኝ በምን ቀበርከው - በሻሽ የኋለኛው እንዳይሸሽ") ።
ሻሽል፡ የዦሮ ቀለበት ።
ሻሽዬ፡ ሻሽ አበባ (የንቍጣጣሽለት ልጃገረዶች የሚዘፍኑት ዘፈን አዝማች) ።
ሻሾ፡ የበሬ ስም (ነጭ በራ ወይም ዐምባላይ ፈረስ) ።
ሻቃ (ሺ)፡ ሻለቃ (የሥጋ ቤት ሹም) ።
ሻበ (ሰሐበ/ሠቢብ/ሠበ)፡ ሽቦ ሠራ/መዘመዘ/አቀጠነ/ጠመዘዘ/ጠመጠመ ።
ሻተረ) አሻተረ፡ አጫረ አሾተለ...ኣቈተመ
("ተረን" ተመልከት) ።
ሻተተ) አንሻተተ፡ አንሸራተተ እግ...ርን ሚዛንን ። አንሻታች፡ ያንሻተተ/የሚያንሻትት...ሸራታች ።
ሻታ (ስሕተት)፡ ተቅማጥ አጣዳፊ ቅዘን ። "የሽታ ምስጢር አለበት"።
ሻታ፡ ዋግንቦ (ባፉ ውስጥ ብዙ ሹል ዕንጨት ያለበት ዓሣ መያዣ) ።
ሻታ፡ ያሣ ቀፎ
ሻታ፡ ያሣ ቀፎ ውስጤ ብስ ግንድ ።
ሻንቅላ (ሎች)፡ የነገድ ስም (ባፍ...ሪታ ውስጥ የሚኖር የካም የኵሽ ዘር ጥቍር ሕዝብ ገላው በፀሓይ ሙቀት ብዛት የጠቈረ - ባሜሪካም ላገር ማቅኒያ ካፍሪቃ...የኼዱ ሻንቅሎች አሉ) ።
ሻንቆ፡ የንጉሥ ሚካኤል ፈረስ ስም...አባን እይ ።
ሻንቆ፡ ጌጥ አልባ ልሙጥ ጋሻ ።
ሻንቆ፡ ጥቍረትና ውፍረት ያለው ንብ ።
ሻንቆ፡ ጥቍር ንብ ።
ሻንበል፡ የሻለቃ ምክትል...ምበል ።
ሻንኵራ፡ ሸነቈጠ
ሻንኵራ፡ ባላንድ ዦሮ ዳብሬ ማድጋ ።
ሻንጣ (ዐረ. ሻምጣ)፡ ከቈዳ የተበጀ ኰረጀ ማፉዳ (ከሐረግ ከካርቶን ከቈርቈሮ የተሠራ ቀላል የመንገድ ጥን) ።
ሻኛ (ስናም)፡ በበሬ በጐሽ በግመል ዠርባ ላይ ያለ የሥጋ ዲብ ክብ እንክብል (ጥብ - ጕብል - ዘዳ. ፲፰፡ ፫) ።
ሻኛማ፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሻኛም (ዘስናም)፡ ሻኛው ትልቅ የኾነ ኣውራ ኰርማ በሬ ።
ሻኝ፡ የሸነ/የሚሽን ።
ሻከረ፡ ተቅረፈረፈ (ከመለዘብ ራቀ ልስላሴ ዐጣ ሞዠቀ -
"ሆዱ ሻከረ" - ነገር ገባው) ።
ሻኵራ፡ የልጅ ቍንጮና የበግ ላት ጠጕር (በቅቤና በጥጥ ፍሬ ባዛባ የተድበለበለ) ።
ሻኵራ/ሻኹራ፡ የጥና የጕልላት የመሶብ የመረሻት አጫዋች (ከንሓስ ከመዳብ የተበጀ የተዘጋጀ) ። እጅና ነፋስ ሲነካው ይንሿሿል ድምፅ ይሰጣል።
ሻካራ/ሸካራ፡ የሻከረ/የሚሻክር (እርጃኖ ዝኆን ገላ የበሬ ምላስ ሞረድ እንቧይ ሰበከት ክፉ ነገር) ። "ሻካራ የሕዝብ ሸካራ የካህናት"
ነው ።
ሻክላ በላው፡ ቀረፈው አበላሸው ።
ሻክላ፡ የንስራና የጋን በሽታ (ከቡሖ ከጠላ የሚመጣ የውስጥ ቅርፍርፍነት - ፍርክ ርክነት) ።
ሻኰረ፡ ክብ እንክብል ኾነ ።
ሻኽ/ሻሽ፡ ፈለግ'ኸ/ፈለግሽ ።
ሻው/ሻኽ/ሻሽ፡ ፈለገው/ፈለገኸ/ፈለገሽ ። ዐቢይ አገባብ ቀድሞት በስምነት ሲነገር
"እንደሻው እንደሻኸ እንደሻሽ" ይላል ። "እንደን" እይ ።
ሻውል (ሺ አውል)፡ የሰው ስም (የሺ ሰው አዛዥ የሺ ጌታ የሺእመቤት አንጻር ሺውን ሰው በፈቃድኸ ኣውል ማለት ነው) ። "ሻውል ሲሞት ሺ ይሙት" እንዲሉ።
ሻይ (ቻይ)፡ የቅጠል ስም (ዓለም ኹሉ ከሱካር ጋራ እያፈላ የሚጠጣው የሺን አገር ተክል - ሺናዊ ቻይናዊ ማለት ነው) ።
ሻይ፡ የሚሻ (ሻ ሻየ) ።
ሻይ፡ የሻ/የሚሻ/የሻየ/የሚሻይ (ፈላጊ -
"ሌባላይ" እንዲሉ) ።
ሻድሬ፡ የሻድር ዐይነት ዋጋው ርካሽ የኾነ መናኛ ።
ሻድር፡ የእስላም ልብስ ።
ሻገረ) ተሻገረ፡ በወንዝ በዥረት በዠማ በባሕር በጐድጓዳ ስፍራ ላይ ዐለፈ (ወዲያ ማዶ ኼደ - ዘፍ. ፴፪፡ ፳፪፡ ዮሐ. ፭፡ ፳፬) ። ሥሩ
"ሠገረ" ነው ። (ተረት)፡ "ይኽን ውሃ ማ ይሻገረዋል ቢሉ፡ ተዝካር ያየ ተማሪ"።
ሻገተ፡ ሸወከ፤
ሻገተ፡ ታመመ/በሰበሰ/ተለወጠ/ተበላሸ (ጥጥ ለበሰ - ኢያ. ፱፡ ፲፪) ።
ሻጕራ፡ ቅርቃር ።
ሻጋታ፡ የሻገተ የተበላሸ እንጀራ ዳቦ መጠጥ ።
ሻጋች፡ የሚሻግት ።
ሻግሌ፡ የግምጃ ስም ጥንታዊ ግምጃ ።
ሻግያ፡ በትግሬ በረሓ ያለ ባለመከራ የሻንቅላ ዘር (ጥቍር ጠቋራ) ።
ሻጠ (ሰሐጠ)፡ ተከለ/ሰካ/ሳገ/አቆመ ።
ሻጣ፡ ትንሽ ሥንጥር ጕድፍ (የገብስ ገለባ በሊጥ በንጀራ ውስጥ የሚገኝ - ያልተነፋ ዶቄት) ።
ሻጣም፡ ሻጣ ያለበት (ባለሻ...ሳካ) ።
ሻጥ (ስሒጥ)፡ መሻጥ ።
ሻጥ አደረገ፡ ስክት አደረገ ።
ሻጥር (ዐረ)፡ ብልጥ ሰው በማንኛውም ሥራና ነገር የሚገባ ።
ሻጭ (ጮች) (ሰሓጢ)፡ የሻጠ/የሚሽጥ (ተካይ ሰኪ) ። የግስን ጠባይ ያልመረመሩ ሰዎች ግን "በሸያጭ" ፈንታ "ሻጭ" እያሉ ይጽፋሉ፡ ስሕተት ነው ።
ሻፈረ) አሻፈረ፡ እንቢ አለ (ጭራሽ ፈጽሞ) ።
ሻፈሪ)፡ ከሰፈረ ይወጣል ("ሻገረን" እይ) ።
ሻፈደ (ትግ. ሠይዐ)፡ ሠየ ጐመዠ (ሴትን እንስትንሻ - ፈለገ) ።
ሻፈደች፡ ሠየች ጐመዦች (ወንድ ተ...ባት ፈለገች - ደራች እንደ ሰፌድ ኾነች) ።
ሻፋጅ/ሻፋዳ/ሽፍድ፡ የሻፈደ/የሚሻፍድ (ፈታዊ) ።
ሻፎ፡ ስለታም ዱላ ።
ሻፎ፡ ስለትና ሹለት ያለው የባሕር ቋጥኝ (በየብስም ይገኛል) ።
ሻፎ፡ ሹል ቋጥኝ፡ ሸፈሸፈ ።
ሼጠ፡ ለገዢ ሰጠ (ሸየጠ) ።
ሼጥ፡ ለወጥ ።
ሼጥ አለ፡ ጊዜው ተለወጠ (ሸመታ ተወደደ ትንሽ ረኃብ ኾነ) ።
ሼጦ፡ ለውጦ ።
ሼጦ ለጕዳይ፡ ባሪያ ።
ሽ (ኪ)፡ የአንቀጽና የስም ዝርዝር ወይም ምእላድ ለቅርብ ሴት ። "በላሽ ጠጣሽ ኼድሽ መጣሽ ነሽ እጅሽ እግርሽ ። እሱ አንቺን ዐወቀሽ"።
ሽ፡ የቅጽል ባዕድ መነሻ ከደጊመ ቃል ተደራጊ አንቀጽ የሚወጣ ። ከረከረ - ተሽከረከረ - ሽክርክር ። ቈጠቈጠ - ተሽቈጠቈጠ - ሽቍጥቍጥ ። ቀረቀረ - ተሽቀረቀረ - ሽቅርቅር ።
ሽ፡ የነገር ትራስ
("ግንዶሽ ውጦሽ ስርቆሽ ርሚጦሽ") ።
ሽህር —
ሽሕር (ሮች)፡ መሲና (የላም ድልብ) ።
ሽሕኛ፡ ከሺ አንድ የሺ ቤት አኃዝ ፲፻ (1000)
።
ሽለ በላ፡ ስል የሚበላ አረመኔ ።
ሽለላ፡ ሽድሽዳ ውስወሳ ።
ሽለላ፡ ቅርርት ። "አለ ነገር አለ ነገር ቍልቍለቱን ወርደን ወንዙን ስንሻገር"
ማለት ።
ሽለላ)፡ ነፋኝ ቀበተተኝ እታራጄ ድረስ (አምላኬ አትግደ ለኝ የልቤን ሳላደርስ ") ።
ሽለላ)፡ ከወታደርም፡ አለ፡ ተልካሻ፡ ጠመንዣ፡ ይዞ፡ ድንጋይ፡ የሚሻ፡
ሽለማ፡ የማስጌጥ ሥራ ።
ሽለታ (ቅርፀት)፡ ጠጕር ቈረጣ ።
ሽለጋ፡ ግመታ ግምገማ ።
ሽላች፡ ሹል ሾጣጣ ሥራ ።
ሽላን (ትግ)፡ እንስላል ። በግእዝ "ሲላን" ይባላል ።
ሽላን፡ ሸለቀቀ ።
ሽል (ሰይል)፡ በማሕፀን የተሣለ የተረገዘ (መላወስመንቀሳቀስ የዠመረ ፅንስ) ። ሲበዛ "ስሎች" ይላል ።
ሽል አለ፡ ስለለ ቀጠነ (ሽል መሰለ) ።
ሽል ያለ ራሱ፡ ትንሽ ገላው አካሉ ወፍራም የኾነ ሰው ።
ሽልል፡ የተሸለለ (ሽድሽድ ውስውስ) ።
ሽልማት (ትርሲት)፡ ጌጥ ካባ ቀሚስ ድርብ ኒሻን ጌጠኛ የጦር መመሪያ የውቀት የትልቅ ሥራ ዋጋ ።
ሽልሜ፡ የሽልም ወገን (ወታደር የጦር ስው ጥሩርና ቍር ለባሽ) ። ልጅንም ለማቈላመጥ ይነገራል
("የኔ ቈንዦ" እንደ ማለት) ።
ሽልም፡ ሓረግና ጠልሰም (በያይነቱ ሥዕል የሰው ምሳሌ ያለበት አንኮላ) ።
ሽልም፡ የተሸለመ/የተመሰለ (ሽልማት ያገኘ የተቀበለ የለበስ የተጌጠ የተንቈጠቈጠ ለተሸላሚ የተሰጠ - ኢሳ. ፲፫፡ ፲፱) ።
ሽልምልሜ (ሽመልመሌ)፡ የሽልምልም ዐይነት ወገን ።
ሽልምልሜ፡ የድፎ ግርፍ ።
ሽልምልም፡ የተዥጐረጐረ ዥጕርጕር (ዙሪያ ገባው የተሸለመ) ።
ሽልሸላ/ሽልሻሎ፡ ጐመሳ ብቅበቃ ነቀላ ።
ሽልቃቂ/ሽልቅቅ፡ የተሸለቀቀ (እንደ ዥራት እንደ ኮባ ሙሽራ እንደ ወይል ዕንጨት ተሸልቅቆ የወጣ) ።
ሽልቅቅ አለ፡ ተሸለቀቀ ።
ሽልባት/ሽልብታ፡ ጭፈና እንጕልቻ ።
ሽልብ አደረገ፡ ጭፍን ክድን አደ...ረገ ።
ሽልብ፡ የሸለበ የተከደነ (ጭፍን) ።
ሽልት (ቅሩዕ)፡ የተሸለተ/የተጠረበ (የተላፃ ቍርጥ ጥርብ ጠጕር ዕንጨት) ።
ሽልጋት፡ ግምጋሚ (የዋጋ ለውጥ) ።
ሽልግ፡ የተሸለገ የተገመተ (ግምት ልክ) ።
ሽልጦ (ዎች)፡ አለቅጠል ባምዛ ምጣድ የተጋገረ ጢብኛ ። ዘሩ በግእዝ "ሰለጠ" ይመስላል ።
ሽልፋ፡ ሥሥ ቀላል ቈዳ ።
ሽልፋፊ፡ ግልፋፊ ።
ሽልፍ፡ የተሸለፈ (ሽንግል) ።
ሽመለኛ፡ ተማች ደብዳቢ ።
ሽመላ (ዎች)፡ ሽመላዊ እግረ ረዥም የባሕር ዳር አሞራ ትለ በላ ። በግእዝ "ሄሮድያኖስ" ይባላል ።
ሽመላ፡ እግሩ እንደ ሽመል የኾኑ ቍርዬ (በዓለም እየዞረ በመከር ጊዜ የማንንም አዝመራ የሚበላ - ኤር. ፰፡ ፯) ። (ተረት)፡ "ካህንና ሽመላ ያልዘራውን ይበላ"።
ሽመል (ሎች)፡ እንደ መቃ ዐጥቅ አንጓ ያለው ዕንጨት (ውስጥ ድፍን ዘንግ ሶማያ በትር የሚኾን - ኢሳ. ፳፰፡ ፳፯፡ ኤር. ፰፡ ፲፯) ።
ሽመልመሌ (ዎች)፡ የበትር ስምንጣ ትና ጥቍረት ያለው በትር (እረኞች የደመራ ለት የሚይዙት ርስ በርሱ የሚያሳብሩት ርጥብ ዱላ) ። "የሽመልመሌ ትርጓሜ ሽልምልሚ" ማለት ነው ።
ሽሙር/አሽሙር (ሮች)፡ ጠቃሽ (ቀጻቢ) ችንካር (የብረት እሾኸ አርቃሾ መውግያ መንጐ ማትጊያ ማነቃቂያ - በግእዝ "ቅትር/ቅትራት" ይባላል) ።
ሽሙንሙኒ፡ የሽሙንሙን ዐይነት
("የኔ ሽሙንሙን") ።
ሽሙንሙን፡ የተሽሞነሞነ (ኵንስንስ) ።
ሽሙጥ፡ ምፀት፡ ማጠጠ ።
ሽሙጥ፡ የንቀት፡ ስድብ፡ ምፀት፡ ቀልድ፡ ለግጥ፡ ("ሕዝ. ፭፡ ፲፩")
ሽሚያ፡ ሰላማዊ ንጥቂያ ቅሚያ ።
ሽማት፡ ስመ አያት...፭ኛ፡ የቅማት ኣባት/እናት ።
ሽማች፡ ልዋጭ ዋጋ
("የእኸል ሽማች" እንዲሉ) ።
ሽማግሌ (ሎች)፡ የሸመገለ ያረጀ አሮጌ ወግ ታሪክ ዐዋቂ (ጨዋ ገላጋይ አስታራቂ - ራእ. ፬፡ ፩, ፲፡ ፭፡ ፭, ፰, ፲፩, ፲፬) ።
ሽማግሌነት፡ ሽማግሌ መኾን ገላጋይነት ።
ሽማግሌው፡ ያ ሽማግሌ (የርሱ ሽማግሌ - ፪ዮሐ. ፩፡ ፫ዮሐ. - ፩) ።
ሽሜ፡ ዘመን አመጣሽ የንቀት አጠራር (ከጣሊያን ወዲህ) ።
ሽምልምል አለ፡ ሽብልል አለ።
ሽምሸማ፡ ክተፋ ።
ሽምሽማት፡ ክርትፋት ።
ሽምሽም፡ የተሸመሸመ (የጤፍ ገርም ክርትፍ) ።
ሽምቀቃ፡ ጭምደዳ ሽብሸባ ።
ሽምቅ፡ የሸመቀ (የደፈጠ) ።
ሽምቅቃት፡ ጥበት ሽብሽባት ።
ሽምቅቅ አለ፡ ጭምድድ አለ ።
ሽምቅቅ፡ የተሸመቀቃ (የከረጢት አፍ ቋንዣ ጭን...ደያ) ።
ሽምት፡ የተሸመተ/የተገዛ እኸል ።
ሽምትር አደረገ፡ ሸመተረ ።
ሽምትር፡ የተሸመተረ (ሽንቍጥ ግርፍ) ።
ሽምገላ/ሽምግልና፡ እርጅና (ዘፍ. ፲፩፡ ፲፭፡ ፩ነገ. ፲፬፡ ፬፡ ፪ዜና. ፳፱፡ ፳፰) ።
ሽምግል አለ፡ እርጅት አለ ።
ሽምግል፡ እርጅት ።
ሽምጠጣ፡ ዥም ። "የለመደች ጦጣ ኹል ጊዜ ሽምጠጣ"
።
ሽምጠጣ፡ ጋለባ ግልቢያ ።
ሽምጣጦ፡ ፅሽም የማያምር ሽሩባ (የፋፊ ፈትል) ።
ሽምጣጭ፡ በስያፍ ያጐበሰሰው ።
ሽምጥ/ሽምጥጥ፡ የተሸመጠጠ (ጥር ግልቢያ ሰገባ) ።
ሽምጥር አለ፡ ሑምጥጥ አለ ።
ሽምጥር፡ የሸመጠረ/የሖመጠ ።
ሽምጥጥ አደረገ፡ ጭልጥ አደረገ (እውነትን ትቶ ሐሰት ብቻ ተናገረ) ።
ሽምጥጥ፡ ጭልጥ ጭርስ ። "ኮሶ ሲጠጣ ስቅጥጥ ወተት ሲጠጣ ሽምጥጥ"
እንዲሉ ።
ሽረባ፡ የመሸረብ ሥራ ።
ሽረት (ሥዕረት)፡ የሕመም ተቃራኒ (ድኅነት ጤና ጤንነት - በሽተኛው ቍርባን ይቀበልና ሽረቱንና ሞቱን ይለይለት) ።
ሽረት (ስዕረት)፡ የሹመት ተቃራኒ
ሽራፊ፡ ስባሪ ቍራሽ (ያሞሌ የዳቦ...ቲም) ።
ሽሬ፡ በትግሬ ክፍል ያለ አር ።
ሽር (ስዑር)፡ የተሻረ (ከሹመት የተ...ወገደ - "ሹም ሽር"
እንዲሉ) ።
ሽር አለ፡ ሠለጠነ ።
ሽር አደረገ፡ ሸነ ለቀቀ ።
ሽርሙጥ አለ፡ ጕድል አለ ።
ሽርሙጥ፡ የጐደለ ።
ሽርሙጥሙጥ አለ፡ ተሸረሞጠ (ቅሉ ዱባው) ።
ሽርሙጥሙጥ፡ የተሸሪሞጠ (ሥር...ድጕድ ጐደሎና ሙሉ።) ።
ሽርሙጥና፡ ዝኒ ከማሁ ።
ሽርሽር አለ፡ ተንሸረሸረ ።
ሽርሽር፡ ዙረት መንሸርሸር (ኣየር መለወጥ) ።
ሽርሽር፡ የተሸረሸረ (ንድል) ።
ሽርቍጥ አለ፡ ቅልጥፍ አለ ።
ሽርብ፡ የተሸረበ (ድብል ጥር ድርብ) ።
ሽርቦሽ/ሽርባት፡ የሽርብ ሥራ ።
ሽርንክት፡ ሸረቈጠ
ሽርንክት፡ ያልደቀቀ ዶቄት ።
ሽርንክት፡ ያልደቀቀ ዶቄት ሸ...ረከተ ።
ሽርከታ፡ ቀደዳ ።
ሽርክርክ አለ፡ ተሽረከረከ ።
ሽርክት አለ፡ ቅድድ አለ ።
ሽርክትክት አለ፡ ተሸረካከተ ።
ሽርክትክት፡ የተሸረካከተ (ዝርክትክት) ።
ሽርክና፡ ሸሪክ መኾን (ወዳጅነት ግጥሚያ አንድነት) ።
ሽርደዳ፡ ቅጥፈት ሐሜት ነቀፋ ለበጣ (ከውነት የራቀ ነገር ለግጥ ፌዝ) ።
ሽርጣም፡ ባለሽርጥ (የባላገር ሴት ግልድማም ዐረብ እስላም) ።
ሽርጥ (ጦች)፡ የተሸረጠ (ከደረት በታች የታሰረ ግልድም) ።
ሽርፍ አለ፡ ተሸረፈ ።
ሽርፍ፡ የተሸረፈ/የተሰበረ ።
ሽርፍራፊ፡ ስብርባሪ ምንዛሪ (ቤሳ ሳን...ዛሪ) ።
ሽርፍርፍ፡ ስብርብር ቍርስርስ ።
ሽርፍርፍ አለ፡ ተሸራረፈ ።
ሽሮ (ሥዒሮ)፡ ደፍሮ ። "በዓል ሽሮ የከበረ ጦም ገድፎ የወፈረ የለም"።
ሽሮ/ሹሮ (ሥዒሮ)፡ ከተቈላ ባቄላና ዐተር ጓያ የተዘጋጀ ዶቄት (የጦም ወጥ የሚኾን - "ግጥም - ዐል መረቁን ወጡን ሸለቸን ምኒልክ ተነሥቶ ሽሮ ባበላን - ዐተር አልዘራኹም አልሰጥዎ ክክ ይህን ኹሉ ሽሮ በሰጠዎ አምላክ"
- ስለ ገጤ ቴዎ) ።
ሽሮሽ (ሥዒሮኪ)፡ በታችኛው ወግዳ ውስጥ ያለ ቀበሌ ("ሸመትሽን ወስዶብሽ" ወይም "ያንቺ ሽሮ" ማለት ነው) ።
ሽሸጋ፡ ደፈና ስወራ ድበቃ ።
ሽሹ (ሸሸ)፡ በዠድ ("ጕያን" ተመልከት) ።
ሽሽተኛ፡ ሸሸ ኦሮቢ ።
ሽሽት፡ መሸሽ/ሩጫ/ግልቢያ/ፍር...ጠጣ/ኵብለላ ።
ሽሽጉ፡ ጌ የሰው ስም (ዲቃላ ወይም በጓዳ ያደገ) ።
ሽሽጋት፡ ስውርነት ድብቅነት ።
ሽሽግ (ጎች)፡ የተሸሸገ/የተደበቀ (ስውር ድብቅ - ኢሳ. ፵፰፡ ፲፯) ።
ሽሽግነት፡ ሽሽግ መኾን ።
ሽሽጓ፡ የሴት ስም ።
ሽሾ (ሽሸ)፡ ማረጃ ካራ ።
ሽቍጥቍጥ፡ የተለማመጠ ቈ...ጠቈጠ ።
ሽቍጥቍጥ፡ የተሽቈጠቈጠ/የተለማ
ሽቅ አለ፡ ሞተ ዐለቀ ተጨረሰ ተ...ጠነገደ ።
ሽቅ አለ፡ ዐለቀ፡ ሸቀቀ ።
ሽቅርቅር (ሮች)፡ የተሽቀረቀረ (ጌጠኛ ") ።
ሽቅሽቅ አለ፡ ተንሸቀሸቀ ።
ሽቅብ፡ ዐቀብ ዐቀበት (ወደ ላይ -
"ዐቀብ" ግእዝ "ዐቀበትና ሽቅብ" ዐማርኛ ነው) ።
ሽቅታ፡ ሽቅ ማለት (ዕልቂት) ።
ሽቅታ፡ ዕልቂት፡ ሸቀቀ ።
ሽበባ/ሽቢያ፡ ጠለፋ አሰራ ።
ሽበታም (ሞች)፡ ሽበት ያለው ባለ ሽበት (ሸበቶ) ።
ሽበት (ቶች) (ሢበት)፡ ነጭ የሰው ጠጕር (በዘርና በዕድሜ የሚወጣ) ። በንጨትና በደንጊያ ላይም ይታያል ።
ሽባ (ዎች)፡ እጁ የማይጨብጥ እግሩ የማይረግጥ ሰው (ጥምልምል) ።
ሽባ፡ እጅ እግሩ ሰላላ ።
ሽባ ኾነ፡ ተጥመለመለ ።
ሽባይ (ሳብዓይ)፡ ሰባተኛ የቀባርዋ...
ሽባጥ (ሠበጠ/ሥባጥ/ዳረጎት)፡ ስሯጽ ሽብልቅ ጣልቃ ሠላጤ ። አለሥራውም የገባ ሰው ሽባጥ ይባላል ። "ወሽመጥን" እይ ።
ሽብ፡ ሸንሻኝ ።
ሽብለላ፡ ጥቅለላ ።
ሽብልላት፡ ጥቅልላት ።
ሽብልል አለ፡ ጥቅልል አለ ።
ሽብልል፡ የተሸበለለ (ጥቅል ብራና ወረቀት ቍርበት ሸማ የሙዝ የኮባ ቅጠል ኣምልማሎ) ።
ሽብልቅ (ቆች)፡ ሹል ዕንጨት ወይም ብረት (ስም) ።
ሽብልቅ፡ የተሸበለቀ (ቅርቅር ውግ - ቅጽል) ።
ሽብልብል ልምን ሸበለለ፡ በቁመት ጠቀለለ ።
ሽብረቃ (ሡራኄ)፡ ወዝ ውበት ጸዳል (የመልክ ጥራት ጥሩነት ወለልታ ላሕይ) ።
ሽብረኛ (ኞች)፡ ሽብር ፈጣሪ (አሸባሪ ተሸባሪ - ዘኍ. ፳፬፡ ፲፯) ።
ሽብሩ/ሽብሬ፡ በሽብር ጊዜ የተወለደ ሰው ስም ።
ሽብር፡ ሁከት ግርግር ታፍጅት ብጥብጥ ።
ሽብርቅ አለ፡ ሸበረቀ ።
ሽብርቅ፡ የሸበረቀ (ወዛም) ።
ሽብሸባ፡ ሽንሸና ።
ሽብሽብ፡ የተሸበሸበ/የተጨማደደ ።
ሽብሽቦ/ሽ...ሽንሽን ። ሽብሽባት፡ የወገብጌ የቀሚስ የእጅጌ ሽንሽናት ።
ሽብባት፡ ያፍ ያገጭ እስራት ሽቢያ ።
ሽብብ፡ የተሸበበ አፉ የታሰረ ።
ሽብት፡ መሸበት ።
ሽብት አለ፡ ሸበተ ።
ሽብዳ፡ ጫፉ አራት ማእዘን የኾነ ዐር ዐንካሴ፡ ረዥሙ ምዥራጥ ይባላል ።
ሽቱ፡ ሽቶ ዕጣንን ሎሚን ርጐፍትን ባርሰነትን ሽነትን ከመሰሉ ዕፀዋት ተቀምሞ የነጠረ ጣፋጭ ፈሳሽ (ያፍንጫ ምግብ - ፪ቆሮ. ፪፡ ፲፭) ። እንዝባን ሪሓን ጠጅ ሣር ።
ሽቱ/ሽቶ፡ በቁሙ ሸተተ ።
ሽታ፡ ሕፃን ሲወለድ በፊቱ ላይ ዐልፎ ዐልፎ የሚታይ ጥቍር - ነጠብጣብ (ማሪ ያም የሳመችው) ።
ሽታ፡ ጣዕም መዐዛ ማለፊያና መጥፎ (፪ቆሮ. ፪፡ ፲፯) ።
ሽትር፡ የተሸተረ (ጌጠኛ) ።
ሽነት (ቶች)፡ የዛፍ ስም (ሽታው...መዐዛው የሚጣፍጥ ዕንጨት - ጕይዲ ግን መዠመሪያ ሽነትን "ሽሾ" ብሎ ተርጕሞታል) ።
ሽንሸና፡ ሽብሸባ ሥንጠቃ ።
ሽንሽና፡ አልቃሽ ልጅ ላንቍሶ ።
ሽንሽናት፡ የሽንሸና ሥራ (ሽብሽቦ) ።
ሽንሽን (ኖች)፡ የተሸነሸነ/የተሸበሸበ (ሽብሽብ ፍልጥ) ።
ሽንቀራ፡ ስብሰባ ዐጠፋ ቅነፋ ።
ሽንቍራት፡ ነዳላነት ቀዳዳነት ።
ሽንቍር አለ፡ ብስት አለ (ተሸነቈረ) ።
ሽንቍርቍር፡ የተሸነቋቈረ (ብስትስት) ።
ሽንቍጥ፡ የተሸነቈጠ (ግርፍ) ።
ሽንቈራ፡ ቀደዳ ነደላ ።
ሽንቈጣ፡ ገረፋ ግርፊያ ።
ሽንቅራት፡ ዕጥፋት ቅንፋት ።
ሽንቅር፡ የተሸነቀረ (ስብስብ ቅንፍ) ።
ሽንብሩት (ሽንብራዊት)፡ ቅጠሏ...ሽንብራ የሚመስል ዐረግ ።
ሽንብሩት፡ መልከ ሽንብራ ንብ ።
ሽንብራ (ሽን፡ ብራ)፡ የእኸል ስም (ክረምት ውጭ በመስከረም የሚዘራ ያበባ እኸል - "ዱባን ዓሣን"
አስተውል - ዎች) ።
ሽንብራው ፈሰሰ)፡ ሕፃን በወደቀ ጊዜ የሚባል ቃል ።
ሽንብሮች፡ ፪ና ከ፪ በላይ ያሉ ፍሬ ።
ሽንታም (ሞች)፡ ሽንተ ብዙ (አኹንም አኹንም የሚሸን) ።
ሽንታም፡ ፈሪ ጡርቂ ።
ሽንት፡ በቁሙ፡ ሸነ ።
ሽንት ቤት፡ በውስጡ የሽንትና ያይነ ምድር ጕድጓድ ያለበት ቤት ።
ሽንት፡ አፍን መንገድ አድርጎ ወደ ሆድ የገባ የመጠጥ ቅሬታ (ሽታው ጕንፋንና ሳል የሚያመጣ ግማታም የሆድ ውስጥ ፈሳሽ -
"የበሬ ሽንት" - ውልግድግድ የሸማ...
ሽንት፡ ዘር ልጅ ። "ሣይንትን"
ተመልከት ።
ሽንትር፡ የተሸነተረ (የተበጣ ብጥ -
"ሸንጥሮን" እይ - በምስጢር ከዚህ ጋራ አንድ ነው) ።
ሽንትርትር፡ የተሸነታተረ ።
ሽንቶ፡ ችንች፡ ሸነ ።
ሽንቶ/ሽንክ፡ ችንች ።
ሽንከፋ፡ ዐጠፋ ኣሰራ ።
ሽንኵርት (ሶመት በጸል)፡ የተክል ስም (ነጭና ቀይ ተክል ለወጥ ቅመም የሚኾን - "ነጭ ሽንኵርት ቀይ ሽንኵርት"
እንዲሉ - ሲበዛ "ሽንኩርቶች" ይላል - "የዥብ ሽንኵርት"
- የዱር ቅጠል) ።
ሽንኵርት፡ የቀበሌ ስም (ከደብረ ሊባኖስ በስተግራ አፋፍ ላይ ያለ የራስ ዳርጌ ከተማ ከቈላ እየመጣ ብዙ ሽንኩርት የሚ ሼጥበት ገበያ ያለው) ።
ሽንክ፡ ችንች ነጭ አባ ጨጓሬ (ሽንቶ ክመክር በኋላ የቅሞን የኰሽምን የጦሚትን የትለምን የእንቡስን ቅጠል በልቶ የሚጨርስ አጥፊ) ።
ሽንክፋት፡ ዕጥፋት እስራት ።
ሽንጣም፡ ሽንጠ ረዥም ሰው ወይም ከብት ሞላላ ድንጋይ ።
ሽንጣሞች፡ ረዣዥሞች ሰዎች ከብቶች ደንጎች ።
ሽንጥ ራስ፡ የሽንጥ ጫፍ ።
ሽንጥ፡ የታወቀ የሥጋ ብልት (ከፍሪዳ ዠርባ ላይ ተከፍሎ የሚወጣ ጥንትና ክዳ ያለበት ክፍል።) ።
ሽንጥ፡ የዠርባ ወንዝ (ከማዥራት እስከ መቀመጫ ግራና ቀኝ ያለ ዝላ - በግእዝ
"ስመጥ" ይባላል) ።
ሽንጦች፡ ኹለትና ከኹለት በላይ ያሉ ሥጋዎች ።
ሽንፍ፡ የተሸነፈ (ድል የኾነ የተረታ የተመታ) ።
ሽንፍላ (ሎች)፡ የሆድ ዕቃ ስም (ምግብ የሚከማችበት ብዙ ክፍል ያለው ውስጠ ንብብር ሥጋዊ ከረጢት - የጨጓራ ዘርፍ ቢያጥቡ አይጠራ) ።
ሽንፍጥ፡ የተሸነፈጠ (የታጠፈ ዝቅዝቅ) ።
ሽኵምኵም፡ ሸከሸከ
ሽኵምኵም፡ ተጫዋች፡
ሽኩቻ፡ የእጅ የጣት ውድድር ። ይኸውም መቀስ ወስፌን ሰይፍ መቀስን መዶሻ ሰይፍን ታቦት ኹሉን ይረታል ። "አገናንን"
አስተውል ።
ሽክ፡ ማጌጥ (ሸከከ) ።
ሽክ፡ ማጌጥ/መሸተር ።
ሽክ አለ፡ አጌጠ/ተሸተረ ።
ሽክረት፡ ሻካራነት ።
ሽክርክር፡ የተሽከረከረ (ከረከረ) ።
ሽክሸካ፡ ወቀጣ ሽድሽዳ ዝርዘራ ዝክዘካ ።
ሽክሽካት፡ ሽድሽዳት (መናኛ ስፌት) ።
ሽክት፡ የዛፍ ስም (በዠማ ዳር የሚበቅል ዕንጨት ቅጠሉ የሽንብራ ቅጠል ይመስላል ዐዲሳበቦችም የፈረንጅ ግራር ይሉታል) ።
ሽክና (ሰከነ)፡ ጥልቂት እንኮላ ። ሲበዛ "ሽክኖች" ይላል ።
ሽክፍ፡ የተሸከፈ (ትፍትፍ ጥቃቅን ጥርስ ካፊያ) ።
ሽኮኮ (ዎች) (መስቈቅው)፡ ያውሬ ስም (በጐሬ በየቋጥኙ ሥር የሚኖር የጥንቸል ዐይነት አውሬ ማታ በጨለማ ሲጸልይ የሚያለቅስ ይመስላል) ። ከጩኸቱም በኋላ ይነፋነፋል ስለዚህ "የሽኮኮ ጸሎት" ይባላል ።
ሽኾሮ፡ ድብልብል ጌጥ (ከወርቅና ከብር የተሠራ) ።
ሽው፡ መንፈስ መብረር ። "ሸውሻዋን"
እይ (ከዚህ ጋራ አንድ ዘር ነው) ።
ሽው ሽው፡ ንፍስ ንፍስ ብር ብር
("አካል ሽው ሽው ትዳሬ ብለሽው" እንዳለ ዘፋኝ) ።
ሽው ሽው አለ፡ መላልሶ ነፈሰ (ሣሩ ድምጥ ሰጠ ከነፋስ የተነሣ) ።
ሽው አለ፡ ነፈሰ/በረረ/ዐለፈ (ነፋሱ አሞራው በጥቂቱ ተሰማ ወሬው...)
ሽውታ፡ ምች ምታት ግርፋት (ከነፋስ ከፀሓይ የሚመጣ) ።
ሽውታ፡ ምች ሽው ።
ሽውታ፡ ሽው ማለት ።
ሽድሸዳ፡ ውስወሳ ሽክሸካ ሽለላ ።
ሽድሽዳት፡ ሽክሽካት (መናኛ ስፌት) ።
ሽድይ፡ ስድስተኛ የቀባርዋ ምት ።
ሽጕር፡ የተሸጐረ (ቅርቅር) ።
ሽጕብ አደረገ፡ ሸጐበ ።
ሽጕዱ ምንድር ነው፡ ጕዳዩ ምንድር ነው ።
ሽጕድ (ሰገደደ)፡ አንቂድ ጕዳይ ስውር ነገር ።
ሽጕጥ
ሽጕጥ (ጦች)፡ የመሣሪያ ስም (፮ ጥይት የሚጐርሥ ዝናርና ቤት ያለው በወገብ የሚያዝ የሚንጠለጠል ዕቃ ጦር) ።
ሽጕጥ ሽጕጥ አለ፡ ድብቅ ድብቅ አለ ።
ሽጕጥ አለ፡ ውትፍ አለ ።
ሽጕጥ፡ የተሸጐጠ የገባ የተደበቀ ።
ሽጕጥ ጠጣ፡ የሽጕጥን ጥይት በአፉ አገባ በገዛ እጁ ለመሞት ።
ሽግ/ሽጕ (ጽገ)፡ ችቦ ዳቦት ።
ሽግል፡ ጨብጥ ።
ሽግት፡ መሻገት ።
ሽግት አለ፡ ሻገተ ።
ሽጐራ፡ ውርወራ ቅርቀራ ።
ሽጐጣ፡ ውተፋ ድበቃ ።
ሽፈና፡ ክለላ ጭፈና ከደና ።
ሽፋ፡ ሽፋፍ፡ ሸፈፈ ።
ሽፋ፡ የሰው ስም (የሽፋፋ ከፊል ነው) ።
ሽፋ/ሽፍ፡ የተሸፈሸፈ (የታጨደ) ።
ሽፋል (ሎች)፡ ግንባርን ሰርጓን አማክሎ ግራና ቀኝ የሚገኝ ገላ (ወይም ዐጪርና ቀጪን ጠጕር - በጐንደር ቅንድብ ይባላል) ።
ሽፋን፡ ልባስ ከለላ (ቀጸላ ሻሽ ዕራፊ...ክዳን) ።
ሽፋው፡ ዝኒ ከማሁ (የው ዝርዝርነት ኣባትን ያያል) ።
ሽፋፍ (ፎች)፡ የጦር የቢላዋ የፍላጻ ቤት (ማግቢያ መክተቻ ማኅደር - "ጐረንጐሬን"
ተመልከት) ።
ሽፍ፡ መውጣት መብቀል ።
ሽፍ አለ፡ ወጣ፡ ሸፈፈ ።
ሽፍ አለ፡ ፈላ ገነፈለ ወጣ (በተለተገለበጠ በላይ ኾነ) ።
ሽፍሻፊ፡ መናኛ ሳንቃ ወይም ጠርብ (ገማጣ ሽርፍራፊ) ።
ሽፍሽፋ፡ ዐጨዳ ቈረጣ ።
ሽፍታ (ቶች)፡ የሸፈተ (ዐመጠኛ ዳንዴ ወንበዴ ቀማኛ ጋዱ) ።
ሽፍታ ሐሩር፡ ሸፈፈ...በረሓ ።
ሽፍታ፡ ሥራው የሚያምር ቀጪን...ሽሩባ ።
ሽፍታ፡ ሽፍ ማለት (ሐሩር የቡቃያ የዕከክ ፍል ረቂቅ በረዶ) ።
ሽፍታ፡ በሚናጥ ወተት ላይ ሽፍ ብሎ ሰፎ የሚታይ የቅቤ ውጥን ።
ሽፍታ(ት)ነት፡ ሽፍታ መኾን (ዐመጠኛነት ከዳተኛነት - ዕዝ. ፬፡ ፲፱) ።
ሽፍናት፡ ሽፋን መሸፈኛ ።
ሽፍን አደረገ፡ ሸፈነ ።
ሽፍን ኣለ፡ ተሸፈነ ።
ሽፍን፡ የተሸፈነ (ጭፍን ባር ማሽላ ወሸላ ቈላፍ - ሮሜ. ፪፡ ፳፭, ፳፮) ።
ሽፍን፡ የተሸፈነች እመቤት ወይዘሮ ።
ሽፍንነት፡ ወሸላነት (ሮሜ. ፪፡ ፳፮) ።
ሽፍንፍን አለ፡ ተሸፋፈነ ።
ሽፍንፍን፡ የተሸፋፈነ (ክንብንብ) ።
ሽፍድ አለ፡ ሻፈደ...9 ።
ሽፍጃ/ሽፍደት፡ ድራት ፍትወት ።
ሽፍጥ (ስፉጥ)፡ የተሸፈጠ (ድልል ሽ...ንግል) ።
ሽፍጥ አደረገ፡ ሸፈጠ ።
ሾ፡ የይፋት በርበሬ ።
ሾለ (ተስሕለ)፡ ክፉ ቀጠነ (ሾጠጠ - ኢሳ. ፵፱፡ ፪) ።
ሾለቀ፡ ሾለ ሾጠጠ (ከስምንት ተከፈለ የዳቤ) ። "ሾለከን"
እይ ።
ሾለቅ (ቆች)፡ አፈ ሹል አሞራ (እሱ ሲጮኸ ዝናም ይመጣል ይባላል) ። ሶለግና ሾለቅ በምስጢር አንድ ናቸው ።
ሾለቅ፡ ሕፅን ሠላጤ ሾጣጣ ዳቤ (ከስምንት አንድ የኵርማን እኩሌታ) ።
ሾለከ (ሰለከ)፡ በቀዳዳ ኼደ ወጣ ወ...ለቀ አመለጠ ።
ሾላ (ዎች)፡ የዛፍ ስም (ፍሬው የሚበላ ዕንጨት የበለስና የወርካ ወፃን) ። በግእዝ "ሰግላ" ይባላል ።
ሾላ ሜዳ፡ ሾላ የበቀለበት ሜዳ (በይፋት ክፍል ያለ ቀበሌ) ። "አላንኮበር ሾላ ሜዳ አይገኝም"
እንዳሉ መምር ዕዝራ ።
ሾላ፡ በድፍን ያልተገለጠ ነገር ።
ሾላካ፡ የሾለከ/የሚሾልክ ።
ሾላጌ፡ ሾላ ያለባት የበዛባት ምድር ።
ሾሌ (ሾላዊ)፡ ኣፉ ከንፈሩ የበሰለ ሾላ የሚመስል ፈረስ ። "አፈ ሾሌ" እንዲሉ።
ሾመ (መ)፡ አክበረ እሠለጠነ (ማዕ...ርግ ሰ...አገር አስገዛ ሰውን መ...ሾመ መባለ ወና የ...ተወራራሽ ስለ ኾኑ ነው) ።
ሾመ፡ መላ ጢም አደረገ (ጠላን...ሆድን ባሕርን) ።
ሾመ ሸመገለ
ሾመ፡ አበጀ አዘጋጀ (እንዝርትን ጠ...ግን) ።
ሾመ፡ እከ...ሰበሰበ አንድነት አደረግ (ሸለመ ኣክሊል እስመሰለ ምርትን) ።
ሾመ፡ ዝም አሠኘ ።
ሾመየ፡ ሹም ኾነ ።
ሾረ፡ ዞረ ሠሠረ ተሽከረከረ ።
ሾርባ (ዐረ)፡ የስንዴ ሙቅ እንትክ...ትክ ።
ሾርቤት፡ የማያሰክር የሴቶች መጠጥ (ብጥብጥ ሱካር) ።
ሾቀ፡ ተቀቀለ ራስ ረሰረሰ (የባቄላ ያተር የሽንብራ ቈሎ በፈላ ውሃ) ።
ሾቅ፡ ራስ...
ሾቅ አለ፡ ራስ አለ ።
ሾተላ፡ ያገር ስም ።
ሾተላይ፡ የሾተል (ባለሾተል - ሾተላም/ሾተልማ - በሴቶች ማሕፀን እያደረ ወንዶችን የሚገድል ሕፃናትን ሲወለዱ የሚያጨናጕል - በግእዝ አስማንድዮስ ይባላል - ጦቢ. ፫፡ ፰) ።
ሾተሌ፡ ሲላ ነጣቂ አሞራ (ጥፍረ ሾተል - አሞሮች ኹሉ የያዙትን የሚቀማ) ።
ሾተሌ፡ ዥብሪ (ልጆችን በጥላው የሚያከሳ የሚያቀጥን የሚያመነምን የሰማይ...) ።
ሾተሌ፡ ጠሮ የባሕር ጋኔን (መርከብን እየገለበጠ ሰውን የሚያሰጥም) ።
ሾተል (ሰውተል)፡ በኹለት ወገን...ስለት ያለው ቀን ሰይፍ ።
ሾተል (ትግ. ሐባ)፡ አፋ ፊቢ ።
ሾቴ፡ ጥቃቅን በረዶ በምድር ላይ ሽፍ ብሎ የሚታይ ።
ሾከሾከ)፡ ሸላ
ሾከከ (ሦክ)፡ ሾለ ቀጠነ (እንደ እሾኸ እንደ ሹካ ኾነ ቀለለ) ።
ሾካካ፡ የሾከከ (ጥላ ቢስ) ።
ሾኬ፡ የሾካካ ዐይነት ወገን (ሰብቀኛ ዦሮ ዐጋሚ) ።
ሾክሾከ/ሾከከ) አሾከሾከ፡ በዦሮ ነገረ ።
ሾክሿካ፡ አሾክሿኪ ።
ሾኸ/እሾኸ (ኾች)፡ የዕፀዋት ቀንድ (እግዜር በተፈጥሮ የሰጣቸው የጦር መሣሪያ) ። ግራርን አጋምን ቀጋን ቀንጠፋን ቈንጥርን ዐጣጥን ጥንዡትን ና፵ን ሳማን አለብላቢትን የመሰሉ ዕንጨቶችና ቅጠሎች ዐረጎች ኹሉ በዐጽቃቸው ጭፍና በቅርፊታቸው ላይ የበዳ ጸብታቸውን ይዘው ይታያሉ (ኢሳ. ፳፯፡ ፬) ። (ተረት)፡ "እሾኸ በሾኸ ይነቀሳል ገንዘብ በገንዘብ ይመለሳል"።
ሾዬ/እሼ፡ ሸዬ ።
ሾጠጠ (ሶጠ)፡ ከፍ ቀጠነ (ሾለቀ) ።
ሾጠጥ፡ ቀጠን ።
ሾጣጣ (ጦች)፡ የሾጠጠ (እንደ ዐለን በስተላይ የቀጠነ) ።
ሾጤ፡ የሾጥ ዐይነት (ወገበ ቀን ሴት አንዠቷ በመርፌ የማይገኝ - ተረት)፡ "ቢቸግረነ ሾጤ ኾነ"።
ሾጤነት፡ ሾ መኾን (ቅጥነት) ።
ሾጥ (ሰዊጥ)፡ መሸንቈጥ/መግረፍ ። ሾጥ አደረገ (ሶጠ)፡ ሸነቈጠ (በጨንገር መታ ገረፈ) ።
ሾጥ (ሰውጥ)፡ ዐለንጋ ልምጭ ።
ሾፈ) (ዐረ. ሻፍ አየ)፡ አሾፈ ቀለደ ዘበተ (ባስተያየት አላገጠ ናቀ እቃለለ ሸነገለ አታለለ) ።
ሿ አለ/ዧ አለ፡ ተንሿሿ ።
ሿ አለፈሰሰ፡
ሿሚ (ሞች)፡ የሾመ/የሚሾም (እክ...ባሪ - "ሿሚ ሸላሚ"
እንዲሉ) ።
ሿሚነት፡ ሿሚ መኾን (አክባሪነት - መሾም ማክበር ማሠልጠን ማበጀት...ማከብ መምላት) ።
ሿሚያ፡ ለሿሚ የሚሰጥ ገንዘብ ።
ሿሿ) (ሳዕስዐ) አንሿሿ (አንሳዕስዐ)፡ አፈላ አገነፈለ አፈሰሰ አወረደ (ድምዕ ኣሰማ) ።
ሿሿ) ሾተል
ሿሿመ፡ ብዙ ሰው ሾመ ።
ሿሿቴ (ሰርብ)፡ የገደል ላይ ውሃ ፋፋቴ (የጽና የጸናጽል ሻኩራ የመረሻት የጕልላት አጫዋች መርገፍ) ።
ሿሿቴዎች (አስራብ)፡ ፋፋቴዎች ።
No comments:
Post a Comment