Friday, June 6, 2025

(ከተ): የተደቀለ የአማርኛ ፊደል (ቸከለንና ቸኩለን ተመልከት)

(የነና፣ የከ፣ የጸና፣ የቀ፣ የጄ ተወራራሽ): "ኄር" "ቸር" "ክህለ" "ቻለ" "ጸፈቀ" "ቸፈገ" "ቃመ" "ቻመ" "ጀነነ" "ቸነነ" የመሰለው ኹሉ (ማለት ነው)

(የፊ): ወራሽ።

ቸለለ (ጸለለ): ተወ፣ ለገመ (ተለለን ተመልከት)

ቸለሰ: ከነበለ፣ ደፋ፣ ገለበጠ፣ ጨርሶ አፈሰሰ (ብዙ ውኃን፣ ደምን) በቀንድ አስተኛ (ማንቍርትን፣ ወንገትን ወደ ላይ፣ ማዥራትን ወደ ታች አደረገ) ዘለሰ (ለማረድ)

ቸላሳ/ችልስ: የተቸለሰ፣ የፈሰሰ (ክንብል፣ ዝልስ)

ቸላሽ (ቸላሾች): የቸለሰ፣ የሚቸልስ፣ አፍሳሽ።

ቸል/ቸለል: መተው፣ መጥመም፣ መለገም፣ ዝም ማለት (ዘዳ ፴፩፡ -)

ቸል አለ/ቸለል አለ: ጠመመ፣ ለገመ፣ ዝም አለ።

ቸልተኛ (ቸልተኞች): ቸል የሚል። (መዝ ፲፭፡ ፬፡ ምሳ ፩፡ ፴፪፡ ፲፫፡ ፲፭)

ቸልታ: ቸል ማለት፣ ጥመት፣ ልግም፣ ዝምታ (ኤር ፵፰፡ )

ቸልቻ (ንኡስ አግባብ): ና። ምሳሌ: "ብሉና ጠመቱና ዕረፉ።" (ቦዝ አንቀጽ) "ሰው ዐርሶ ወይም ነግዶ ያድራል" (እንዲሉ።)

ቸመቸመ (ከተመተመ): ደመደመ፣ ቸረቸመ፣ አጠረሰ፣ አስተካከለ። አብዝቶ ሠራ፡ ዘራ፡ ቤትን፡ እኽልን አቆመ፡ ጦርን።

ቸምቻሚ: የቸመቸመ፣ የሚቸመችም፣ አብ።

ቸምቻማ/ቸርቻማ: ደምዳማ።

ቸሰረ: ረፈቀ፣ ደነሰረ።

ቸሰቸስ/ቸስቻሳ: የተንቸሰቸሰ፣ የሚንቸሰቸስ (እርጥበት ያለው እንጨት)

ቸሳሪ: የቸሰረ፣ የሚቸስር (ደንሳሪ)

ቸሳራ/ችስር: የተቸሰረ (ደንሳራ፣ ድንስር)

ቸስቸስ አለ: አጐበጐበ።

ቸረ/ቼረ (ከሰኀየረ/ኄረወ): ሰጠ፣ ናኘ፣ ለገሰ።

ቸረቸመ: ሰበረ፣ ሸረፈ፣ በጠፈ፣ አጠረሰ፣ ስለት አሳጣ።

ቸረቸረ (ከሰተረተረ): ፈታ፣ በተነ፣ ተነተነ፣ ዘረዘረ (በጥቂት በጥቂቱ) (ዕቃን ከመደብር ገዝቶ በዳ ተቀምጦ)

ቸረቸፈ: ቸረቸመ።

ቸረፈፍ/ቸርፋፋ: የተንቸረፈፈ፣ የሚንቸረፈፍ (እራፊ፣ እንችርፍ)

ቸሩ: ደጉ፣ ለጋሱ፣ ዶልዷሊ፣ ሳይለምኑት ዝናምን ለዘር፣ ጠልን ለመከር የሚሰጥ መጋቢ ዓለማት። ምሳሌ: "ስለ ቸሩ እግዚኦ" እንዲል ተማሪ።

ቸሪቱ/ቸሪት: ደጊቱ/ደጊት።

ቸሬ (የሰው ስም): "የኔ ቸር" ማለት ነው። ቸሬ የሚባል ሰው ከ፲፱፻፳፰ . በፊት በአዲስ አበባ ይሠራው የነበረ የጥይት ክልስ ነው።

ቸር ቸር አለ: መር አለ (እባቡ፣ ነብሩ)

ቸር አገር ሄደ: ሞተ፣ ነፍሱ ወደ ሰማይ ዐረገች።

ቸር አገር: የቸር አገር፣ ገነት፣ መንግሥተ ሰማይ፣ ደግ አገር።

ቸር/ቼር (ኄር): ደግ፣ ጻድቅ ሰው፣ ለጋስ፣ እባ መስጠት፣ እጀ ሰፊ፣ ለነፃ የማይል፣ ለድኻ ቆርሶ የሚያጐርስ፣ ቀዶ የሚያለብስ። (ዮሐ ፯፡ ፲፪፡ ፲፡ ፲፩) በጎ፣ ደህና። ምሳሌ: "ቸር ያውልኽ" "ቸር ያሳድርኽ" "ቸር ያሰማኽ" እንዲሉ።

ቸርቻሚ: የቸረቸመ፣ የሚቸረችም (ሽሪፊ፣ አጥራሽ)

ቸርቻማ: ሰባራ፣ ሸራፋ።

ቸርቻሪ (ቸርቻሪዎች): የቸረቸረ፣ የሚቸረችር (በታኝ፣ ተንታኝ፣ ዘርዛሪ) ከመደብር ውጭ ሽያጭ።

ቸርቻሪነት: ቸርቻሪ መኾን።

ቸርነት (ኂርውና): ቸር መኾን፣ ለጋስነት። (፩ሳሙ ፳፡ ፲፭፡ ሉቃ ፭፡ ፪ቆሮ ፮፡ ) (የሰው ስም)

ቸሮች (ኄራን): ሰዎች፣ ለጋሶች፣ ደጃች ሰዎች፣ ጻድቃን።

ቸበቸበ (ጨበጨበ): ጣለ፣ መታ፣ ደበደበ። ምሳሌ: ወጣ እኽልን በለበት። እሳትን በአፈር ወይም በቅጠል አጠፋ። በርካሽ ሸጠ። ዐረደ፣ ቈረጠ።

ቸባቸበ: ወቃቃ፣ ደባደበ።

ቸብ ቸብ አደረገ: እጁን ጸፋ፣ መላልሶ አጨበጨበ።

ቸብ አደረገ: ጭብጨባ ዠመረ። ምሳሌ: "ቸብ አድርግ" እንዲል ዘፋኝ። በፍጥነት ሸጠ፣ ለወጠ።

ቸብቸቦ: ራስ፣ ካንገት በላይ ያለ የሰውነት ክፍል (ቁንጮንና ቆንዳላንም ያስተረጕማል) ምሳሌ: "ዳዊት የጎልያድን ቸብቸቦ በቈረጠ ጊዜ የፍልስጥኤም ሰዎች ድል ኾነው ሸሹ።" (የወረብና የቅኔ) ጭብጨባ፣ ከጭብጨባ ጋራ የሚባል ወረብ።

ቸብቻቢ: የቸበቸበ፣ የሚቸበችብ (ወቂ)

ቸቸረ: ገፈረ፣ ቃመ።

ቸቻሪ: የቸቸረ፣ የሚቸችር (ገፋሪ፣ ቃሚ)

ቸነነ: ጀነነ፣ አኰራ፣ ቈነነ፣ አጓደደ። ወነገ፣ ወሰጠ።

ቸነኔ/ቸናና/ችንን: የተቸነነ (ጅንን፣ ቍንን) የተወነገ (ውንግ)

ቸነከረ (ከነከረ፡ ተከለ): ሰመረ፣ በችንካር ከእንጨት ጋራ ወጋ፣ መታ፣ አያያዘ፣ አጣበቀ፣ አናኘ፣ አነከረ።

ቸነፈር (ከሰነፈረ): የበሽታ ስም፣ ዕልቂት፣ መቅሰፍት፣ ከጦርነት በኋላ የሚመጣ፣ ሰውን እያናፈረ ቶሎ የሚገድል ሕመም። (በግእዝ ብድብድ ይባላል) ምሳሌ: "ሀባ ቸነፈር" እንዲሉ። (ዕን ፫፡ ፭፡ ማቴ ፳፱፡ )

ቸናኝ: የቸነነ፣ የሚቸንን (ጀናኝ፣ ቈናኝ)

ቸንማ: ከርሳስ የተበጀ፣ የገበጣ ጠጠር።

ቸንቧ ቸንቧ አለ: በጭርቅ በጭርቅ አለ።

ቸንቻም (ቸንቻሞች): ድዳም፣ ቸንቹ። የዓፈር ከንፈር።

ቸንች: ድድ፣ የድድ መስመር።

ቸንካሪ: የቸነከረ፣ የሚቸነክር።

ቸከ (ከስሕከ): ኣደፈ፣ ለመመ፣ ደገደገ።

ቸከለ (የግእዝ): ቸከለና ቸኰለ የአማርኛ ናቸው። ቀበቀበ፣ ከሰመ፣ እመሬት ኣገባ፣ ሻጠ፣ ወተፈ፣ ሸጐጠ፣ አቆመ (፩ኛ ቆሮንቶስ፡ ፫፡ )

ቸከቸከ: ውኃ ነቀሰ፣ ጠቀጠቀ።

ቸካይ: የቸከለ፣ የሚቸል (ቀብቃቢ)

ቸክ አደረገ: ጠቅ አደረገ።

ቸክ አደረገ: ጠቅ አደረገ።

ቸክ: ውግት።

ቸኰለ: ጠደፈ፣ ፈጠነ (በሥራ፣ በነገር) (ተረት): "የቸኰለች አፍሳ ለቀመች።"

ቸኰል (የሰው ስም): "ቶሎ ተወለደ" ማለት ነው።

ቸኳይ (ቸኳዮች): የሚቸኵል፣ ጠዳፊ።

ቸው (የሩቆች ወንዶችና ሴቶች ዝርዝር): ምሳሌ: "እሱ እነሱን ዐወቃቸው፡ ወደዳቸው።" (ጥሬ ሲገባ) "ቤታቸው፡ ሥራቸው።"

ቸገረ: ጠፋ፣ ታጣ፣ ጨነቀ፣ ተሳነ። (ተረት): "የቸገረው እርጉዝ ያገባል፡ የባሰበት እመጫት።" (ተገረን አስተውል)

ቸጋሪ: የቸገረ፣ የሚቸግር (ልብስ፣ ጕርሥ)

ቸግሮ: ገዶ፣ ጨንቆ፣ ተስኖ።

ቸፈረ (ከሰሰፈረ): ቃመ፣ በአፍ መላስ።

ቸፈቸፈ (ከሰተፈተፈ): ጨቀጨቀ፣ ጨፈጨፈ፣ ሸፈሸፈ። አዠ፣ አካፋ (አደረገ)

ቸፈቸፍ: ጨፈጨፍ።

ቸፈነነ (ከሰቸነነ): ጀነነ፣ አኰራ።

ቸፈገ (ከሰጸፈቀ): ፈተ፣ ጠቀጠቀ፣ አቀራረበ፣ አበዛ፣ ጅብ አደረገ።

ቸፋሪ: የቸፈረ፣ የሚቸፍር (ቃሚ)

ቸፋፈር: እቃቃም፣ መቸፈር።

ቸፍቻፊ (ተፍታፊ): የቸፈቸፈ፣ የሚቸፈችፍ (ጨቅጫቂ፣ ፍረ)

ቸፍቻፋ: ጨቅጫቃ፣ ነገረኛ።

(): (የሩቅ ወንድ ዝርዝር) በብዙዎች ስም መጨረሻ የሚነዝር።

ቺን (የአገር/የነገድ ስም): ሺን። (ዝርዝር) "እኛ" የሚሉ ወንዶችና ሴቶች፡ የአንቀጽና የጥሬ ዝርዝር። ምሳሌ: "እሷ እኛን ዐወቀችን፡ ዐይናችን፡ ዦሯችን።"

ቺኮሮ: የተክል ስም፣ የባሕር አገር ተክል ነው።

(ቅጥያ): በስም መጨረሻ ላይ እየገባ ምእላድ የሚሆን። ትርጓሜውም ዓይነትንና ሁኔታን ያሳያል። ምሳሌ: ዳር፡ - ዳርቻ፣ ዐፈር፡ - ዐፈርቻ፣ ፀረም፡ - ዐራሙቻ፣ ሥር፡ - ሥርቻ፣ ጥል፡ - ጥላቻ።

ቻለ (ክህለ): ተሸከመ፣ ወሰነ፣ ያዘ፣ አጻመረ፣ ጨረሰ፣ ማሰ።

ቻል (ከሃል): (በሴት ልጅ ላይ) "አትተው" "ሚስት አድርግ" (ለለፈና ለደፈረ ልጃገረድ ይነገራል) ዐሥረ ፈጅ ጋን።

ቻመ: ቃመ (ቸፈረን እይ)

ቻቻታ: ጩኸት (ቻቻ) የጉባኤ ጩኸት።

ቻቻቼ: ከላይ ካለው ጋር ተመሳሳይ፣ ጩኸት (ቻቻ)

ቻች (ከሰተሐተ): ታናሽ ጥዋ፣ የመንተል ዓይነት። (መስቴን፣ ቡይትንና በግራትን ተመልከት)

ቻይ (ከሃሊ): የቻለ፣ የሚችል፣ ተሸካሚ፣ ወሳኝ፣ ታጋሽ፣ ልበ ሰፊ፣ ነገር ዐላፊ፣ ቻይ ተክልሻይ።

ቻይ: የሚችል (ቻለን እይ)

(ኧዬ): (ዝርዝር) "እኔ" ለሚሉ ወንድና ሴት ባለቤትነትን የሚያሳይ። ምሳሌ: ላሞች፡ - ላሞቼ (የኔ ላሞች) ፈረሶች፡ - ፈረሶቼ (የኔ ፈረሶች) (ቃለ ምልልስ) ፈረስን ለመከልከል፣ ለመንዳትና ለመጋለብ የሚነገር ቃል። ምሳሌ: " ፈረሴ ቍና ገብሴ" እንዲሉ ልጆች።

በለው (ዜማ): የክራር መቺ ዘፈን አዝማች።

(የፈረስ ምስጋና): ሰንጋ ምት በማሲንቆ። " " (ከፈረሰኞች የምናውቃቸው በሻኽ አቦዬ፣ ኀይሌ አንዳርጋቸው) (ቼቼን እይ)

ቼቼ አለ: አዘለ፣ በዠርባ ተሸከመ (ቼን ተመልከት)

ቼቼ: ማዘል፣ እንቡቡ በታች መኾን።

ቼክ: ልዩ ወረቀት፣ ከባንክ ገንዘብ ማዘዣ።

(ቅጥያ): ስምን ለማብዛት የሚውል፣ "ዎች" ማለት ነው። (ቅጥያ) ለሩቅ ሴት የዘማችና የነባር ግስ ዝርዝር።

ችሃ (የአገር/የነገድ ስም): ከሰባት ቤት ጕራጌ አንዱ ችሃ ይባላል።

ችለሳ: ክንበላ፣ ግልበጣ።

ችለሳ: ክንበላ፣ ግልበጣ።

ችላ ባይ: ችላ የሚል፣ ቸልተኛ፣ ሀኪተኛ።

ችላ አለ: ቸል አለ፣ ተከየ።

ችላ አይቶ: እንዳላዩ፣ ሰምቶ እንዳላሰሙ መኾን። ምሳሌ: "መግዛት ቢያምርኽ ችላ፡ ጥጋብ ቢያምርሽ ጠላ" እንዲሉ።

ችላ: ቸል፣ ተወት፣ ሀኬት።

ችልስ ችልስ አለ: ፍስስ ፍስስ አለ።

ችልስ አለ: ግልብጥ አለ፣ ተቸለሰ።

ችልስ አደረገ: ድፍት አደረገ፣ ቸለስ አለ።

ችሎተኛ (ችሎተኞች): በችሎት የሚቀመጥ፣ ነገረተኛ።

ችሎታ: የሥራ ዕውቀት።

ችሎት (ክሂሎሁ): ታግምት። (ክሂሎት) ዳኝነት፣ ሙግት፣ ክርክር። (የዳኝነት ሥራ ብዙ ትዕግሥትና ዕውቀት ስለሚፈልግ ችሎት መቻል ተባለ) ሥልጣን፣ መብት። (ለዜና ፳፱፡ ፲፩፡ ዮሐ ፲፡ ፲፰) ሸንጎ፣ አደባባይ፣ ዐውድ።

ችሎት ተመለሰ: ዳኛ ተነሣ፣ ጉባኤው ተበተነ።

ችሎቶች: ሥልጣኖች፣ መብቶች።

ችምችም ለፎ: ብዙ ሰራዊት (ለፎን ተመልከት) ዘንጋዳ አበቃቀሉ፣ ብዛት ያለው።

ችምችም አለ: በዝቶ ታየ።

ችምችም ያለ: ጭፍቅ፣ ችፍግ ያለ።

ችምችም: የተቸመቸመ፣ ችርችም፣ ስለት መንደር፣ ብዙ ጦር።

ችምችሞ: ብዙ ዓይነት ምግብ።

ችሰራ: ድንሰራ።

ችስ አለ: ፍም ወይም ትኩስ ቈሎ ውሃ በገባበት ጊዜ የጪስ የላበት ድምፅ አሰማ።

ችስር አለ: ድንስር አለ፣ ተቸሰረ።

ችስችሳ: የቈላ ወይም የበረሓ ጕንዳን ምሥል (ሺሾ)

ችርቸራ: መቸርቸር።

ችርቻሪ/ችርቻሮ: ዝርዘራ፣ ብተና፣ ትንተና፣ የብትን፣ የትንትን ዕቃ አሻሻጥ።

ችርችም አለ: ጥርስ አለ።

ችርችም: የተቸረቸመ፣ ስብር፣ ሽርፍ።

ችርንችር: አራት ማእዘን ያለው እንፊት፣ በትረ ሙሴ።

ችሮታ (ኂሩት): "አገኘዋለሁ፡ ይመለስልኛል" የማይባል ስጦታ፣ ቸርነት።

ችብቸባ: ውቂያ፣ ጭብጨባ።

ችቦ: የጭራሮ መብራት፣ ዳቦት፣ ቲሃ።

ችቸራ: የመቸቸር ኹኔታ።

ችችር: የተቸቸረ፣ የተገፈረ፣ በጕንጭ ውስጥ ያለ ጥፊ።

ችንች: ሽንቶ፣ ስንክ ነጭ። (አባ ጨዓረ) ከመከር በኋላ የእንቡስንና የትለምን ዛፍ ቅጠል ከታች እስከ ላይ በልቶ የሚስ።

ችንከራ: የመቸንከር ሥራ።

ችንካር (ችንካሮች): አራት ማዕዘን ያለው የዱሮ ምስማር። (ልብ) ውጋት። በቁመትም በውፍረትም ከዛሬው ይበልጣል። (በግእዝ ቀኖት ይባላል) (ኢሳ ፳፪፡ ፳፭) (ማዕድን) ከድንጋይ የሚገኝ፡ መጣብቅ (ነው) የተሠራውን ወይም የተሰበረውን የነሓስና የመዳብ፣ የብርና የወርቅ ዕቃ ጥቂት ክብረ ሰማይ ተጨምሮበት ማያያዣ፡ ማገናኛ። ሳንቃን ከሳንቃ የሚያገናኝ ውስጣዊ የእንጨት ቅርቃር (ሰፊና ቀን) (ዘፀ ፳፮፡ ፲፯)

ችንክር: የተቸነከረ፣ የተወጋ፣ የተጣበቀ። ቍንወት ብረት (የጌታችን እጅና እግር)

ችኩል (ችኩሎች): የቸኰለ፣ ጥዱፍ (መክ ፯፡ ፱፡ ፪ጢሞ ፫፡ ) ምሳሌ: "የዥብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል" እንዲሉ።

ችኩልነት: ጥዱፍነት።

ችካል: የእንጨት፣ የብረት ቅብቃብ (መሳ ፭፡ ፳፮)

ችካሎች: ቅብቃቦች (ዘኍ ፬፡ ፴፪)

ችካም: በጥርሱ ላይ ችክ ያለበት፣ የበዛበት።

ችክ (ችኽ): የጥርስ እድፍ፣ ልማም፣ ስሓ፣ ሳካ።

ችክ ምንችክ አለ: ሞዘዘ (መነቸከን እይ)

ችክ አለ: ሙዝዝ አለ።

ችክ: የብስ ስም።

ችክል: የተቸከለ፣ የተቀበቀበ፣ ቅብቅብ።

ችክታ: ያፍላ፣ የውበት ተቃራኒ፣ አለማማር፣ የፊት መብረድ፣ ችክ ማለት።

ችኮ: ሞዛዛ፣ ዝኝ፣ መንቻካ።

ችኰላ: ጥድፊያ፣ ፍጥነት (ዘዳ ፲፮፡ ፫፡ ገላ ፮፡ )

ችኹ: (የቅርቦች ወንዶችና ሴቶች የአንቀጽና የስም ዝርዝር) ምሳሌ: "እሱ እናንተን ዐወቃችኹ፡ እጃችኹ፡ እግራችኹ።"

ችጉር: የተቸገረ፣ ችጋረኛ፣ ራብተኛ፣ ዕርዝተኛ። (ጥቸ) መቸገር: መጨነቅ፡ ማጣት፡ መራብ፡ መጠማት፡ መታረዝ።

ችጋረኛ (ችጋረኞች): ራብተኛ፣ ቀጠና የያዘው ሰው፣ ይልሰው ይቀምሰው የሌለው (መዝ ፱፡ ፲፰፣ ፲፡ ፰፣ ፬፣ ፱፡ ፱፣ ፲፪፣ ፻፪፡ ፲፯፡ ኢሳ ፴፪፡ )

ችጋር: ራብ፣ ጠኔ (ምሳ ፯፡ ፲፩)

ችግ (ቃለ ምልልስ): በግን ለመከልከል የሚነገር ቃል ነው። "ዘሩ ሸገገ ነው።"

ችግ አለ: ከለከለ፣ መለሰ (በግን)

ችግረኛ (ችግረኞች): የተቸገረ፣ ችግር የገባው፣ የጸናበት፣ ድኻ።

ችግሬ: የችግር፣ መናኛ ሥራ፣ ልብስ፣ ጣራ ሥሥ (የፈረንጅ ምላጭ)

ችግር አለው: ጨነቀው፣ ጠበበው፣ የሚያደርገውን ዐጣ።

ችግር: ዕጦት፣ የመፍቀድ ጥፋት (አማረን እይ)

ችግኝ (ከተገነ): የሣር፣ የቅጠል፣ የዛፍ፣ የተክል ፍል (ከላይ በዳስ፣ ከታች በጀጐል የሚተገን) (ቍኝንና ጭጕኝን ተመልከት)

ችፌ (ችፋዊ): የቍስል ስም፣ ኹል ጊዜ የሚያዥ፣ የወፈፍ ዓይነት ቍስል፣ አልፎ አልፎ ሽፍ የሚል። (ዘዳ ፳፰፡ ፳፯፡ ዘሌ ፲፬፡ ፶፬) መድኀኒቱም የተወቀጠ ኮሶ በማር ለውሶ መቀባትና ቅጠል ለጥፎ በራቅ ማሰር ነው።

ችፌ: ቍስል ነው። ቸፈቸፈ (ማለት ነው)

ችፍ ችፍ አለ: ጭፍጭፍ፣ ክፍክፍ አለ (በረቂቅ )

ችፍ አለ: እዥ አለ፣ እሳየ ሸፈ።

ችፍ: ሐሩር፣ ረቂቅ፣ ዕከክ።

ችፍርግ (ከሰቸፈገ): ቁመተ ወርቅ፣ ጸጽቀ፣ ብዙ ዕንጨት፣ ችፍግ፣ ሥሯጽ ነው።

ችፍችፋም: ጭቅጭቃም፣ ንዝንዛም።

ችፍችፍ: ጭቅጭቅ፣ ንዝንዝ።

ችፍግ (ጽፉቅ): የተቸፈገ፣ ጭፍቅ፣ ጥቅጥቅ (ዱር) (መዝ ፲፡ ፱፡ ኤር ፬፡ ፯፡ ሕዝ ፲፱፡ ፸፮)

ችፍግ አለ (ከሰተጸፍቀ): ጥቅጥቅ አለ፣ ደን፣ ምሣ ኾነ።

ችፍግነት: ጥቅጥቅነት (ኢሳ ፲፡ ፴፬፡ ሕዝ ፴፩፡ )

(ችዋ): (የሩቅ ሴት ዝርዝር) ምሳሌ: "ቤቶች፡ - ቤቶቿ (የርሷ ቤቶች) ላሞች፡ - ላሞቿ (የርሷ ላሞች)"


No comments:

Post a Comment

ሽፋን

  ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ